"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ"
1.2K subscribers
26 photos
3 videos
5 files
21 links
ኤልሮኢ
"በእውኑ የሚያየኝን ጌታ አየሁት"
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ
አምላክ አሜን።
ይህ መንፈሳዊ ቻናል
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ:- +ዝማሬ
+ ምክሮች
+ ስነፅሁፎች
+ አጫጭር ትርክቶች እንዲሁም
+ ምስባክና
+ ወንጌል ይለቀቁበታል።

ለበለጠ መረጃ @AleroeBot
ግሩፑን ለማግኘት @alero
Download Telegram
ኤልሮኢ:
አልፋና ዖሜጋ

አልፋና ኦሜጋ ፈጣሪ የሆንክ
በከሀዲዎች እጅ ተይዘህ ቀረብክ/2/
ተገፋህ ተደፋህ በጥፊ ተመታህ
እየደበደቡ ክርስቶስ ሆይ አሉህ
ጽድቅን ስለሠራህ በወንጀል ከሰሱህ
ለአደም ቤዛ ልትሆን ብዙ ተንገላታህ
አዝ ---
ቅዱሳን እጆችህ የፊጥኝ ታስረው
እደበግ ጎተቱህ ልትምራቸው
የትም ቦታ ያለህ ሁሉን የምታውቅ
ፊትህን ሸፈኑህ ለመመጻደቅ
አዝ ---
በዚያ አደባባይ በጲላጦስ ዘንድ
አሳልፈው ሰጡህ አጋልጠው ለፍርድ
ከሐና ቀያፋ ከካህናቱ ደጅ
ከእነሄሮድስ ዘንድ አቀረቡህ በአወጅ
አዝ---
ግርፋት ሕማሙ አልበቃ ብሎህ
በመስቀል ላይ ልትውል ተፈረደብህ
ሳዶርና አላዶር ጸናትና አዴራ
ተፈልገው መጡ ለችንካር መከራ
አዝ---
አምስቱ ችንካሮች ቅንዋተ መስቀል
አይሁዶች አመጡ ገላህን ለማቁሰል
ሊያያዝ በችንካር እጅህ ተዘረጋ
የሰላም ባለቤት ደረትህ ተወጋ
አዝ---
ግፈኞቹ አይሁድ በአንተ ላይ ቀለዱ
ምራቅ ተፉብህ አንተኑ ሊጎዱ
ለእኛ ወገኖች ሀጢያት ላደከመን
የመስቀልህ ጥላ ማረፊያ ይሁነን

@aleroe
ኤልሮኢ:
እናት ሰንበት ትምህርት ቤት

………አንዳንድ ጊዜ ‹ትምህርት ቤት› የሚለው ሐረግ ሰንበት ትምህርት ቤትን
አይገልጻት ይሆን ብዬ አስባለሁ፡፡ ‹ሰንበት ትምህርት ቤት› ከምትባል ይልቅ
‹የሰንበት ቤተሰብ ቤት› ብትባል ይሻል ይኾን?
የቤተሰባዊነት ስሜት ለአገልጋዮች እጅግ አስፈላጊ ነው፡፡ ሐዋርያት እርስ
በእርሳቸው ‹ወንድሞች› ይባባሉ ነበር፡፡ ወንድሞች መባባላቸው ከአንድ እናትና
አባት ተወልደው አይደለም፤ እንዲሁ አገልግሎት የጋራ እናታቸው ሆናቸው ነው
እንጂ፡፡ የሳቱትን እንኳን ‹ቢፅ ሐሳውያን (ሐሰተኛ ወንድሞች)› ይሉ ነበር፡፡
ይህንን ቤተሰባዊነት ለማጉላት እኔ ባደግኩባት ሰንበት ትምህርት ቤት የቤተሰብ
ጉባኤ የሚባል ጉባኤ አለ፡፡ በዚያ ቀን የሚከወነው እንደ ቤተሰብ ቤተሰባዊና
መንፈሳዊ ወጎችን እንዲሁ ሲጨዋወቱ መዋል ነው፡፡ የሰንበት ትምህርት ቤቱ
ሰብሳቢ ‹ሰብሳቢ› ሳይሆን ‹አባት› ይባላል፡፡ ኹሉም ‹አባታችን› እያለ
ይጠራዋል፡፡ የቀድሞ ሰብሳቢ ‹አያታችን› ይባላል፡፡ ከእርሱ የቀደመው ‹ቅድመ
አያታችን› ይባላል፡፡ የአመራር አባላት ወንዶቹ ‹አጎቶች› ሴቶቹ ‹አክስቶች›
ይባላሉ፡፡ ሌላው አባል በሙሉ ‹ልጅ› ነው፡፡
ይህ ስሜት ኹሉም ሰንበት ትምህርት ቤት ውስጥ አለ፡፡
ሰንበት ተማሪ ዘመደ ብዙ ነው፡፡ አያድርስበትና አንድ ችግር በእርሱ ወይም
በቤተሰቡ ላይ ቢደርስበት የእናት ሰንበት ትምህርት ቤቱ ወንድሞቹና እኅቶቹ
ነቅለው ቤቱ ይሔዳሉ፡፡ ታምሞ ከሆነ ቤቱን ሞልተው ፣ ውዳሴ ማርያምን
አድርሰው ዘምረው ያበረቱታል፡፡ ኃዘን ገጥሞት ከኾነ እስኪጽናና ከቤቱ
አይለዩም፡፡ ዕድርተኛው ‹ጉድ› እስኪል ድረስ ድንኳን የሚተክሉት ፣ ወንበር
የሚደረድሩት ፣ ግቢ የሚያጸዱት ፣ ዕቃ የሚያጥቡት የሰንበት ትምህርት ቤት
እኅትና ወንድሞቹ ናቸው፡፡
ባለቤቱ እንዲደረግ የፈለገውንና የሚያስፈልገውን በማድረግ ልቡን በእርካታ
ይሞሉታል፤ እንደ ልቡ ይሆኑለታል፡፡ የዮናታን ጋሻጃግሬ ለዮናታን እንዳለው
‹‹እንዳንተ ልብ ሁሉ የኔም ልብ እንዲሁ ነው›› ብለው የልባቸውን መሻት
ከወዳጃቸው ልብ መሻት ጋር አንድ ያደርጉታል፡፡ (1ሳሙ.14፡7)፡፡ እርሱ ሲያዝን
የእርሱ አፍ ሳይኾን የራሳቸው ልብ ይነግራቸዋል፤ ‹እንደርሱ ልብ ሁሉ የእነርሱም
ልብ እንዲሁ ነውና›፡፡
ሰርግ ካለበትም የሥጋ ቤተሰቡ አብዝቶ መጨነቅ የለበትም፡፡ በጎደለው ኹሉ
የመንፈስ ቤተሰቦቹ አሉለት፡፡ ምናልባትም ልጅየው ብዙ ጊዜውን ለሰንበት
ትምህርት ቤት በመስጠቱ የሚበሳጭ ቤተሰብ ቢኖረው እንኳን ከእንደዚህ
ዓይነት ገጠመኝ በኋላ ኹሉም ነገር ይለወጣል፡፡ የወንድሞቹና የእኅቶቹ
መተሳሰብ፣ የሚቃወም ልቡናን ኹሉ በፍቅር ሊያነድ የተቀጣጠለ ስንዱ እሳት
ነው - ‹‹ፍቅር የኃጢአትን ብዛት ይሸፍናል›› እንዲል፡፡ (1ጴጥ. 4፡8)፡፡
የሰንበት ትምህርት ቤት ወንድሞች እውነተኛ ወንድሞች ናቸው - በፍቅር
የተገመደ ትሥሥር ያላቸው፡፡ ወንድማቸው ሲበርደው እነርሱ የሚንቀጠቀጡ ፣
ሲርበው አንጀታቸው የሚላወስ ፣ ሲከፋው አብረው የሚያለቅሱ ውድ ወንድሞች
ናቸው፡፡ ለእኅታቸው ድጋፍን ከመስጠት የማይሰንፉ ፣ ታናሻቸውን በትምህርት
የሚረዱ ፣ ለጥያቄዎቹ የማይሰለቹ ልበ ወርቆች ናቸው፡፡ አብረው መብላት ፣
መጎራረስ ፣ አብረው ማደግ ፣ አብረው መሳቅ ፣ አብረው መጫወት ፣ አብረው
መሔድ ፣ አብረው ማንበብ ፣ አብረው መኖር የሚያጓጓቸው የኁባሬ ስልቻዎች
ናቸው፡፡ የሰንበት ትምህርት ቤት ወንድሞች በሰንበት ትምህርት ቤት እንጂ
በየትም በሌላ ቦታ አይገኙም፡፡
የሰንበት ትምህርት ቤት ወንድሞች እንደ ዮናታን ናቸው፡፡ ዳዊት ጎልያድን ገድሎ
በዮናታን አባት በንጉሡ በሳኦል እልፍኝ ከተገኘና የራሱን ማንነት ለንጉሡ ካስረዳ
በኋላ ‹‹የዮናታን ነፍስ በዳዊት ነፍስ ታሠረች፥ ዮናታንም እንደ ነፍሱ
ወደደው›› (1ሳሙ.18፡1)፡፡ ዮናታን ዳዊትን እንደ ነፍሱ ስለ ወደደው አባቱ ሳኦል
በጠላትነት ሲነሣበት እንኳን እንደ ነፍሱ የወደደውን ዳዊትን ከአባቱ በምክሩ
ይደብቀው ነበር፡፡ የሰንበት ትምህርት ቤት እውነተኛ ወንድሞችም እንዲሁ
ናቸው፡፡ ዳዊት የተባሉ አዳዲስ አባላት ጎልያድ የተባለ ከአገልግሎት መራቅን
ድል ነሥተው ወደ ሰንበት ትምህርት ቤት ሲመጡ ነፍሳቸው በዳዊቶቹ ነፍሶች
ትታሰራለች፣ እንደ ነፍሳቸውም ይወዷቸዋል፡፡ ምንም ዓይነት ‹ሳኦል› ቢመጣ
ከዳዊቶች ጎን ይቆማሉ፡፡ እንዲህ ዓይነት ወንድሞች በሰንበት ትምህርት ቤት
ወይም የሰንበት ትምህርት ቤት ልብ ባላቸው ዘንድ እንጂ በየትም በሌላ ቦታ
አይገኙም፡፡
የሰንበት ትምህርት ቤት እኅቶች ትሕትና የቀበራቸው ፣ ሃይማኖት ያስጌጣቸው ፣
ቅንነት ያቆነጃቸው ፣ የፍቅር ኩራዞች ናቸው - ፀሐዩአ ለጠፋባት የሴትነት ዓለም
ክራቸው እየተቃጠለ ብርሃንን የሚለግሱ ፣ እየጨሱ መቅረዝ የኾኑ፡፡
ወንድሞቻቸውን የሚያከብሩ ፣ ለሥርዐተ ቤተ ክርስቲያን የሚታመኑ ፣ ካህናትን
ሲያዩ ልባቸው በሚገባ ፍርሐትና አክብሮት የሚርድ የሀገር ኩራቶች ናቸው፡፡
ወንድሞቻቸውን አጥብቀው የሚሹ የቤተሰቡ የወርቅ ምሰሶዎች እነርሱ ናቸው፡፡
በብዙ ትግልና ልፋት ወደ ሰንበት ትምህርት ቤት ይመጣሉ፤ ሰማይ የሚያክል
ጫናን አገር የሚያክል ጾታዊ ተፅዕኖን ተቋቁመው ያገለግላሉ፡፡ የሰንበት
ትምህርት ቤት እኅቶች በሰንበት ትምህርት ቤት እንጂ በየትም በሌላ ቦታ
አይገኙም፡፡
የሰንበት ትምህርት ቤት እኅቶች እንደ አቢጊያ ናቸው፡፡ የናባል ሚስት አቢጊያ
ባሏ ንጉሡን እስከ መዳፈር የደፈረ እጅግ አስቸጋሪ ሰው ነበር፡፡ ንጉሥ ዳዊትም
እርሱን ሊገድለው ሲሔድ ብልኋ አቢግያ በመንገድ ጠብቃ ንጉሡ ይቅርታ
ያደርግለት ዘንድ በብዙ ትሕትናና እጅ መንሻ ለመነችው፡፡ ዳዊትም አቢግያን
አደነቀ፤ ‹‹ወደ ደም እንዳልሄድ፥ በእጄም በቀል እንዳላደርግ ዛሬ የከለከለኝ
አእምሮሽ የተመሰገነ ይሁን፥ አንቺም የተመሰገንሽ ሁኚ›› አላት፡፡ (1ሳሙ.25፡
33)፡፡ የሰንበት ትምህርት ቤት እውነተኛ እኅቶችም እንደ አቢጊያ ናቸው፡፡ ሰውን
ከክፋት በመመለስ ፣ በእርጋት ፣ በትሕትና ፣ በአስተዋይነት አዕምሮአቸው
የተመሰገነ፡፡ ሰውን ጎትተው ወደ ስሕተት የሚከቱ አሰናካይ ሴቶች በበዙበት
በዚህ ዘመን ብልጭልጭን ንቀው የሚስተውን የሚመልሱ የተመሰገኑ ናቸው፡፡
ስለ ወንድሞቻቸውና ስለ እኅቶቻቸው አብዝተው የሚጨነቁና የሚጸልዩ ፣ ጸብን
ለማራቅ ዘወትር በብልኃት የሚመክሩ ፣ ‹ልታይ› ከሚሉት ጀርባ የሚገኙ ባለ
ምስጉን አዕምሮዎች ናቸው፡፡ እንዲህ ዓይነት እኅቶች በሰንበት ትምህርት ቤት
ወይም የሰንበት ትምህርት ቤት ልብ ባላቸው ዘንድ እንጂ በየትም በሌላ ቦታ
አይገኙም፡፡
እኔ በግሌ ልጅ እያለሁ እነዚህ እኅቶችና ወንድሞች ዕቅፍ አድርገው ተቀብለውኝ
ወንድማቸው ባያደርጉኝ ኖሮ አሁን ያለው ማንነቴ አይኖርም ነበር፡፡ ለመጀመሪያ
ጊዜ ሰንበት ትምህርት ቤት ስገባ በፍቅር ሸማ ፣ በመውደድ ብሉኮ ያከናነቡኝን ፣
በጉጉት የተቀበሉኝን ውድ የኆኅተ ብርሃን ቤተሰቦቼን የልጅነት አዕምሮዬ
አይዘነጋቸውም፡፡ እነዚህን ወንድሞችና እኅቶች በሰንበት ትምህርት ቤት እንጂ
በሌላ በየትም ቦታ እስካሁንም አላገኘኋቸውም፡፡
ሰንበት ተማሪ ሌላ ሰንበት ተማሪን በመንገድ ሲያገኝ ወይም በአጋጣሚ
ሲተዋወቅ የጠፋ የእናቱን ልጅ እንዳገኘ ልቡ በፍቅር ስስት ይቃጠላል፡፡ ኹለት
የማይተዋወቁ ሰንበት ተማሪዎች ቢገናኙ ለመግባባት ጊዜ አይወስድባቸውም፤
ልቡናቸው ቀድሞ ይግባባል፡፡ ስማቸውን እንኳን ሳይተዋወቁ ስለ መስቀል ጥናት
፣ ስለ ጥምቀት ፣ስለ ደብረ ታቦር ፣ ስለ ፍልሰታ ፣ ወዘተ… ያወራሉ፡፡ አባባሉስ
ቢሆን ‹‹አንድ ዓይነት ላባ ያላቸው ወፎች……

@aleroe
ኤልሮኢ:
አገልግሎትና_መኪና


በአገልግሎት ጋሪ በልኡክ መኪና
ነዳጁ #ፍቅር ነው ፍሬኑ #ትሕትና
መኪና በመንገድ ፍሬን ከሌለው፣
አገልጋይም እንዲሁ ትሕትና ካነሰው፣
መፃኢ ዕጣቸው መጋጨት ብቻ ነው።
ነዳጅና ፍቅርም ይመሳሰላሉ፣
ፍቅር ይኽኛውን ነዳጅም ያኛውን ያንቀሳቅሳሉ።
#ተስፋ መስታወት ነው #ትውፊት ስፖኪዮ፣
#እምነት ደግሞ መሪው የአቅጣጫ መለዮ፤
በእምነት መሪነት በተስፋ መስታወት ወደፊት እያሉ፣
በአዕምሮ ማኅደር በትውፊት 'ሚታዩ ኋላዎችም አሉ።
'ሚንቀሳቀሱበት 'ሚሽከረከሩበት #ትግኃት ይባላል የመኪናው ጎማ፣
#ትግኃት ቅንዓትም ጡሩምባው 'ጲጵ' የሚያደርጉበት ከሃይማኖት መንገድ ዞር እንዲል ጠማማ።
ከእነዚህ ዕቃዎች አንዱ ከጎደለ ወይ ከተጣመመ ወይም ከተበሳ፣
መኪናው አሮጌ ይባላል ከርካሳ።
ጥገናና ሰርቪስ መለዋወጫ ዕቃ ለሚያስፈልገው ሰው፣
መካኒኩ ካህን ፣ ላቫጆው ንስሐ ፣ ጋራጁ መቅደስ ነው።
ሕግ አስከባሪዎች ፖሊሶችስ ካሉ፣
ሥርዐት ቀኖና ተብለው 'ሚጠሩ ትራፊኮች አሉ።
በሃይማኖት መንገድ ሲወጡ ሲወርዱ፣
መጠመቅ ብቻ ነው የመንጃ ፈቃዱ።
መልካም መንገድ!

@aleroe
ኤልሮኢ:
………“እኛ ግን ጠላቶቻችንንም እንወዳለን”
ቅዱስ ሮማኖስ የተባለ የዘመነ ሰማዕታት ክርስቲያን ሃይማኖትህን ቀይር በማለት ያሰቃየው ለነበረው ዘመን የሰጠው ባለሥልጣን የመለሰለት እንዲህ በማለት ነበር። እናንተስ ክፉ ማድረግን ታውቃላችሁ። እኛ ክርስቲያኖች ግን እግዚአብሔርን በማመን በጎ ማድረግን እናውቃለን። በክርስቶስ ስም አጋንንትን ደዌ ካደረባቸው ሰዎች እናስወጣለን፤ እናስወግዳቸውማለን። እናንተ ለጥቂት ዘመን ሥልጣን አላችሁ ።ያለ መራራትም በሰዎች ላይ ትፈርዳላችሁ። እኛ ግን ጠላቶቻችንንም ሳይቀር እንድንወድ ስለታዘዝን በተግባር እንፈጽመዋለን። ለሚያሳድዱንም እንጸልይላቸዋለን።
እናንተስ ለጥቂት ዘመን ኖረው በሚሞቱ ሰዎች ትተማመናላችሁ። እኛ ግን እግዚአብሔርን በማመን በማይሞቱት በመላእክት ዘንድ እንመሰገናለን። እናንተ ለአጋንንት በመስገድ ሰዎችን ወደ ገሀነም ታቀርቧቸዋላችሁ። እኛ ግን ሰዎችን ከገሀነም እናወጣቸዋለን። እናንተ በምትሀታችሁ ሰዎችን ከዘለዓለም ሕይወት ትለዩዋቸዋላችሁ። እኛ ግን ቅን በሆነች ሥርዓታችን እና በየዋህነታችን ሰዎችን ከሞት እናወጣለቸዋለን።
እናንተ ነገር በማሳመር ሀብት በመሰብሰብ እና በማዳላት በሰው ላይ ሞትን ታመጣላችሁ። እኛ ግን ሰዎች ይድኑ ዘንድ ሥነ ምግባር እናስተማራለቸዋለን። ኃላፊውን ሳይሆን ዘለዓለማዊውን ሕይወት እና ድኅነት እንነግራቸዋለን። እናንተ ኃላፊያን ገዥዎች አሏችሁ። የምትሰግዱላቸውም አምላክ አይደሉም፤ ድንጋይ ናቸው እንጂ።እኛ ግን ዘለዓለማዊውን ንጉሥ እናመልካለን።ለእሱም እንገዛለን፤ እንሰግዳለንም።
እናንተስ የማታገኙትን ትቀበሉ ዘንድ አማልክቶቻችሁን ትለምናላችሁ።ለእኛ ግን አምላካችን በፍጹም እምነት የለመንነውን ይሰጠናል።እኛ ክፉ የሚያደርጉብንን ይቅር እንላቸዋለን። እናንተ ግን ዘለዓለም የምንኖር ስለሚመስላችሁ የሰውን ንብረት ትቀማላችሁ። እግዚአብሔር ለእኛ የሰጠንንም ስለእግዚአብሔር ብለን ለድሆች እንሰጣቸዋለን። በዚህም ሁሉ እናንተን እንበልጣለን በማለት የክርስቲያኖችን እና የአረማውያንን ሕይወት አነጻጽሮ ይነግረዋል። በዘመነ ሰማዕታት የተፈጸመውን ይህን ጉዳይ አሁን ካለው ነባራዊ ሁኔታ ጋር ብናስተያየው ዛሬ የተፈጸመ ያህል ይሰማናል።
ከቅዱሱ በረከት ይክፈለን

@aleroe
ኤልሮኢ:
​​ ተዋህዶ_አትፈርስም

ድርጅት አይደለም በሰዉ የታነፀ፣
ፖለቲካም አይደል ዘርን ያጣቀሰ፣
ሚስጥሩ ፍቅር ነዉ ቃላት የማይበቃዉ፣
እኛን ስለመዉደድ በፍቅር ተስቦ መስቀል ላይ የወጣዉ።
በደም ታንፀናል በማይጠፋ ቀለም፣
ለእኛ ብሎ እርሱ ጌታ ቢሰቀልም፣
መሠረቱ ኢየሱስ ግድግዳዉ ቅዱሳን፣
ግንቦቹ እኛ ነን የእርሱ ምዕመናን።
ልንወድቅ አንችልም በእርሱ ፍቅር ፀንተን፣
እግዚአብሔርን ይዘን ማን ይሆን የሚከሰን?
መሃመዳዊያን ወይም ጅሆቫ ዊትነስ፣
ፕሮቴስታንትም ሁን ወይ ደግሞ ካቶሊክ
አለቱን ላታፈርስ የሰዉ ደም አታፍስስ፣
ምንጩንም ላታደርቅ ከመቅደሱ እራቅ።
ካህኑ ቢታረድ መቅደሱ ቢቃጠል፣
እንበዛለን እንጂ የለም የሚጎድል።
ስንሞት እንበዛለን መከራዉ ሲበዛ በፍቅር እንፀናለን፣
በእሳት ስንቃጠል እንለመልማለን።
ከማይደክም አባት ተፈጥረናልና፣
አርዮስ አትልፋ እንላለን ቀና።
ሰልፉ የእኛ ነዉ ድልም የእኛ ብቻ፣
እንደ አሸዋ የበዛን እስከዓለም ዳርቻ።
ካህኑን ግደሉ መቅደሱን አቃጥሉ፣
ቅጥሩንም አፍርሱ ልጆቹን በትኑ፣
እናንተ ስትጠፉ በገሀነም እሳት፣
ሰማዕታት በአባታቸዉ እቤት
ይሰበሰባሉ መንግስተ ሰማያት።
ይህ ነዉ ክርስትና የማይጠፋ ቀለም፣
በፍፁም ማይጨልም ሁሌ ሚሰጥ ብርሃን።
እናማ አርዮስ ቁርጥህን እወቀ፣
ድል ላታደርግ እንደዉ ራስህን አታስጨንቀዉ፣
ሃሰት እዉነትን መቼ ነዉ አሸንፎ የሚያቀዉ?
ባንድነት ተነሱ የእምነትን ሰይፍ ያዙ፣
በፍቅር ማርኩና የዲያቢሎስን ሴራ በእምነታችሁ ናዱ።
በእምነት እንሞላ በፅናት እንቁም በተስፋ እንዉጣ፣
ጠላት አፍሮ እንዲቀር መድረሻም እንዲያጣ።
የጦር ዕቃችሁን ልበሱ እንደ ካባ፣
ዘመቻዉን አፅኑት ቅድስቲቷ ምድር አርዮስ እንዳይገባ።
የጦር ሠልፍ አንሻም ቀስት አንወረዉርም፣
ደም እያፈሰስን እርሱ የፈጠረዉን እኛ አንገድልም።
ቀስትና ጦር ይዘን አንወጣም ዘመቻ፣
ጠጠርም አንለቅምም አሳዳጁን መምቻ።
መምቻው ክርስቶስ ነው የእሳት መዶሻ፣
ምሽጋችን ቅድስት የኃጥአን መሸሻ።

@aleroe
ኤልሮኢ:
በትዕግሥቱ ብዛት

በትእግሥቱ ብዛት ባይገለጥ ኃይሉ
ስቀለው ስቀለው አይሁድ ተባባሉ/2/
የኃያላን አምላክ አልፋና ኦሜጋ
እንድኛ ታመመ በለበሰው ሥጋ
ኅብስት አበርክቶ የሚመግብ ጌታ
ታሰሮ ተገረፈ እንደክፉ ሽፍታ
እጅና እሮቹ ታሰረው ብታይ
ድንግል አለቀሰች እለች ዋይ ዋይ
የሚንቀጠቀጡለት መላእእክት በፈቱ
እንደምን በችንካር ተወጋ ደረቱ
የንጹሐን አምላክ ወንጀለኛ ተብሎ
ዋለ ቀረንዮ እርቃኑን ተሰቅሎ
በደል ሳይኖርበት ተሰቀለልን
ሞታችንን ሞቶ ሕይወትን ሰጠን

@aleroe
ኤልሮኢ:
‹‹አዝለህ ውሰደኝ››

‹‹አባታችን አባ ኪሮስም በበዓቱ ሳለ ከዕለታት አንድ ቀን ጌታን እጅግ የጎበጠ ፈጽሞ ያረጀ መነኩሴ መስሎ በእጁ ምርኩዝ ይዞ ቀስ ቀስ እያለ ሄዶ ከጥላ ሥር ሲያርፍ ከሩቅ አየው፡፡ አባ ኪሮስም ከሩቅ አይቶ ወደ ‹ይህ መነኩሴ ፈጽሞ ደክሟል› ብሎ አደነቀ፣ ሊጠይቀውም ወደ እርሱ ሄደ፡፡ ያም ሽማግሌ ‹እግዚአብሔርን የምትወድ ከሆንክ ከአንተ ጋር ወደ በዓትህ ውሰደኝ› አለው፡፡ አባ ኪሮስም ‹ከወዴት መጣህ?› አለው፡፡ ሽማግሌውም ‹ኤረር ከሚባል ቦታ ነው የመጣሁት› አለው፡፡ መልሶም ‹ኤረር የሚሉት ቦታ የት ነው ያለው?› አለው፡፡ ያም ሽማግሌ ‹በምሥራቅና በምዕራብ፣ በደቡብና በሰሜን አይደለም› አለው፡፡ አባ ኪሮስም ‹አባ ምን ትላለህ? በምሥራቅና በምዕራብ፣ በደቡብና በሰሜን ካልሆነ በየት ሀገር ነው?› አለው፡፡ ሽማግሌውም ‹ዛሬስ አታውቀውም፣ ኋላ ግን ታውቀዋለህ› አለው፡፡ አባታችን አባ ኪሮስም ‹ሃይማኖትህ ከሃይማኖታችን ጋር አንድ ይሆናልን?› አለው፡፡ ሽማግሌውም ‹አዎ አንድ ነው› አለው፡፡ አባ ኪሮስም ‹ምስጋናህ በሰማይና በምድር የመላ አንድ አምላክ የሚሆን አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ በል› አለው፡፡ ያም ሽማግሌ አባታችን አባ ኪሮስ እንዳለው አለ፡፡ ያንጊዜም አባታችን አባ ከሮስ ‹እውነተኛ ክርስቲያን ነህና ወደ በዓቴም እንሂድ› አለው፡፡ ሽማግሌውም ‹አንተ ብርቱ ነህ፣ እኔ ግን ደካማ ሽማግሌ ነኝ፡፡ እግዚአብሔርን የምትወድ ከሆንክ አዝለህ ውሰደኝ› አለው፡፡ አባታችን አባ ኪሮስም ‹እሺ እሸከምሃለሁ› ብሎ ወገቡን በአፅፉ ታጥቆ አዝሎ ጥቂት ጥቂት እያለ ሔዶ ደከመ፡፡ ያ ሽማግሌም አባ ኪሮስን ‹ደከምክን?› አለው፡፡ አባታችንም ‹ጸሎትህ ይረዳኛል› አለው፡፡ ያንጊዜም የሽማግሌው መልኩ ተለወጠ፣ ነጎድጓድ ብልጭልጭታም ሆነ፡፡ አባ ኪሮስም ክብሩን ማየት ተሳነው፣ ዐይኑም ተጋረደና ወደ መሬት ወደቀ፡፡ ጌታችንም አባ ኪሮስን ‹ፈጽሜ ላከብርህ ነው እንጂ ላጠፋህ አልመጣሁምና ተነሥ› አለው፡፡››


@aleroe
ኤልሮኢ:
አንሱ_አላነሳም
========÷=======
አንዲት ሴት ወይዘሮ በባቡር ጉዞ ላይ ሳሉ አጠገባቸው ባለው ወንበር ላይ የተቀመጠ ሻንጣ ስለነበር አንድ ሠራተኛ መጥቶ ይህ ወንበር ለሰው መቀመጫ እንጂ ለዕቃ ማኖሪያ አልተፈቀደምና እባክዎ ያንሱ ሲላቸው ‹‹አላነሳም›› አሉት፡፡ ‹‹ቢያነሱ ይሻላል እምቢ ካሉ ላለቃዬ እነግራለሁ›› ቢላቸውም
‹‹ሂድ ንገር›› አሉት፡፡ ሂዶ ሲነግረው አለቅየው መጥቶ "ያንሱ እንጂ ለምን አላነሳም ይላሉ?" ብሎ ቢናገራቸው ‹‹አላነሳም›› በሚለው ሐሳባቸው ጸንተው የማይበገሩ ሆኑበት፡፡ በመጨረሻም ዋናው ኃላፊ ተነግሮት ይመጣና ‹‹ይህን ሻንጣ ያንሱ›› ሲላቸው ‹‹አላነሳም›› አሉት፡፡ ዋና ኃላፊውም ‹‹ለምን?›› ሲላቸው ‹‹ገና አሁን አዋቂ ሰው መጣ፡፡ እኔ የቸገረኝ እኮ እስካሁን ድረስ ‹‹ለምን›› ብሎ የጠየቀኝ ባለመኖሩ ነበር፡፡ አንተ ‹‹ #ለምን ?›› ስላልከኝ አመሰግንናለሁ፡፡ በመሠረቱ ግን ሻንጣው የእኔ #አይደለም
ሲሉት በመደነቅ ይቅርታ ጠየቃቸው፡፡
አብዛኞቻችን በሰዎች ላይ በደፈናው እንፈርዳለን፡፡ ምእመኑ ሰንበት ተማሪው ላይ፣ ሰንበት ተማሪው ካህናቱ ላይ ሁሉም በአዙሪት ይፈርዳል ቤተክርስቲያናችን ያጣችው የሚፈርድ ሳይሆን እውነትን እየፈልገ ከጎኗ የሚቆም ሰው ነው። እናም ሁሌም በደፈናው ከመፍረዳችን በፊት "ለምን?" ብሎ መጠየቅም እውቀት ነው፡፡

@aleroe
ኤልሮኢ:
ጥበበኛዋ ትል

አንዲት ትል ከአንድ ረጅም ዛፍ ስር ሆና ወደ ላይ ስትመለከት ዛፉ በማፍራት ላይ ያለውን ፍሬዎች በመመልከቷ ከፍሬው ለመመገብ ወደ ዛፉ ላይ የመውጣትን ጉዞ ጀመረች፡፡
በእሷ ፍጥነት (ዝግመት) ዛፉን ወጥታ ያሰበችበት ለመድረስ ረዘም ያለ ጊዜ እንደሚፈጅ ከተሞክሮ ብታውቀውም በጣም እየጸለየች ወደላይ በወጣች ቁጥር በበለጠ ሁኔታ እየታያት የመጣውን የአካባቢ ገጽታ እያየች በደስታ ዳገቱን ተያያዘችው፡፡
ብዙም ሳትርቅ ከዛፉ ላይ ወደታች የምትወርድ አንዲት ምንነቷ በውል ያልታወቀ እንስሳ ቆም ብላ፣ “ወደየት ነው እንደዚህ በደስታ እየተፍለቀለቅሽ የምትሄጂው አለቻት”፡፡
ትል፣ “ዛፉ ጫፍ ላይ ያለውን ፍሬ ልበላ” አለች፡፡
እንስሳዋም፣ “እኔ ከዚያ ነው የመጣሁት፣ ፍሬዎቹ ገና አልበሰሉምና አትልፊ፡፡ ሲቀጥል ደግሞ አጉል ደስተኛነት አያጥቃሽ ጉዞው ቀላል እንዳይመስልሽ፣ ስለዚህ ብትመለሺ ይሻልሻል” አለቻት፡፡
ትሏም፣ ቆም ብላ እዚያ ለመድረስ የሚፈጅባትን ጊዜ ካሰላች በኋላ፣ “ችግር የለውም፣ እዚያ እስከምደርስ ድረስ ፍሬዎቹ ይበስላሉ” በማለት ጉዞዋን ቀጠለች፡፡
ያሰብከው ከፍታ ለመድረስና የለፋህበትን መንፈሳዊ ፍሬ ለማግኘት . . .
1. ዓላማህን ከጊዜ ጋር አጣጥመህ እቅድ አውጣ
ከሁሉ በፊት ለመድረስ የምትፈልግበትን የዓላማ ከፍታ ወስን፡፡ ከዚያም፣ እዚያ ዓላማህ ጋር ለመድረስ የሚፈጅብህን የጊዜ ሁኔታ አስላና ሁለ-ገብ እቅድ አውጣ፡፡ ሁለ-ገብ እቅድ ማለት፣ እንደ አንተ ሁኔታ ገንዘብን፣ ትምህርትን፣ እድሜን . . . ያካተተ ሊሆን ይችላል፡፡
2. የሰዎችን ሃሳብ አመዛዝን
ሁል ጊዜ ከፍ ያለ እቅድ ስታወጣና መንቀሳቀስ ስትጀምር ተቃራኒውን የሚነግሩህ ሰዎች እንደሚያጋጥሙህ አትርሳ፡፡ አንዳንዶች ለአንተ አስበው በቅንነት፣ ሌሎቹ ደግሞ በአንተ ላይ አስበው በምቀኝነት፡፡ በጭፍንነት ከሰማሃቸው ውጤቱ ያው ስለሆነ ሁለቱንም ቢሆን በጥንቃቄ ማስተናገድ አስፈላጊ ነው፡፡ በዋናነት ደግሞ ዲያቢሎስ በየሄድክበት ሁሉ የእንቅፋት ችግኙን ይተክልብሃል ይህንንም በጸሎት ኃይል ተቃወም ።
3. በጉዞው ተደሰት
ወደ ዓላማህ በአንተ አቅምና ፍጥነት ስትጓዝ ፍጻሜው ላይ የመድረስን ደስታ እስከምታገኝ ተስፋ አትቁረጥ፡፡፡ የመድረስ ደስታ ዓላማህ ላይ እስከምትደርስ ድረስ ያስጠብቅሃል፡፡ የጉዞው ደስታ ደግሞ አሁኑኑ በመደሰት ለጉዞው ጉልበትን ይሰጥሃል፡፡
ያሰብከው ደረጃ መድረስህና ፍሬህን መብላትህ አይቀርምና፣ በፍጹም እንዳትቆም!!!

(ቅዱስ ያሬድንና ያቺን ትል አስብ)

@aleroe
ኤልሮኢ:
ለመላቀቅ መልቀቅ!

የስድስት አመት ልጅ ነው፡፡ የሚኖረው ከአባትና ከእናቱ ጋር እንዲሁም ከሁለት ታላላቅ ወንድሞቹ ጋር ነው፡፡ ይህ ልጅ
ከወንድሞቹ ይልቅ ፈጣንና አንዳንዴም ከመስመር ወጣ ያለ ቅልጥፍና ያለው ልጅ ነው፡፡ አንድን ነገር ካየና ከወደደው ያንን ነገር በእጁ የሚያስገባበትን መንገድ በዚህም ሆነ በዚያ ፈልጎ ነገሩን በእጁ ያስገባል፡፡ አንድን ነገር እጁ ለማስገባት ማልቀስ ካለበት ማልቀስን፣ መጣላት ካለበት መጣላትን፣ መስረቅ ካለበት መስረቅን ከመጠቀም የሚመልሰው የለም፡፡ መኝታ ቤቱ ያለው የመጫወቻ ብዛት ይህ ነው አይባልም፡፡ ከየት ለቃቅሞ እንዳመጣው የማይታወቅ ብዙ ነገር ነው ያለው፡፡ አባቱ ይህንን
ባህሪውን ያውቃል፣ ሆኖም በተለያየ መልኩ ሊያስተምረው ከመሞከር ውጪ ምንም ሊያደርገው አልቻለም፡፡
አንድ ቀን ይህ ልጅ የማይረሳውን ትምህርት አገኘ፡፡ ከትምህርት
ቤት ተመልሶ ትንሽ ምግብ ከቀማመሰ በኋላ በረንዳው ላይ ይጫወታል፡፡ የጎረቤታቸውን በረንዳና የእነርሱን በረንዳ
የሚለየው አንድ ከብረት የተሰራ በሰው ቁመት ልክ የሆነ አጥር
ነው፡፡ ይህ ልጅ ቀና ብሎ ሲያይ የጎረቤታቸው ልጅ ሲጫወትባት
የነበረች ትንሽ ሳንቲም የምታክል መጫወቻ ያያል፡፡ በተለያዩ
ቀለማት ስለምታብረቀርቅ ልቡን ሳበችው፡፡ ዘወር ብሎ ዙሪያውን ሲመለከት ማንም ሰው የለም፡፡ ቀና ብሎ ወደ ጎረቤቱ ግቢ ሲያጤን ያ በጣም የሚፈራው ውሻም በአካባቢው የለም፡፡ በቀስታ እጁን በብረት አጥሩ መካከል አሾልኮ ያችን ያጓጓችውን መጫወቻ በእጁ ከጨበጠ በኋላ በቀስታ አጁን ውጣ ቢለው እንዴት ይውጣ! ሁለት ሶስቴ ከሞከረ በኋላ እምቢ ስላለው መደንገጥ ጀመረ፡፡ ከአሁን ከአሁን ውሻው ይመጣብኛል ብሎ ፈራ፡፡ ብዙ ከታገለ በኋላ አልቦታል፤ ከፍርሃትም የተነሳ እንደ ማልቀስ ቃጥቶታል፡፡
በዚህ ሁኔታ ላይ እያለ ነበር አባት የደረሰው፡፡ ዘወር ብሎ አባቱ
መምጣቱን እንዳየ መለስ ሲል ያ ክፉ የጎረቤትም ውሻ ብቅ
አለ፡፡ ልጁ በፍርሃት ማልቀስ ጀመረ፡፡ አባት፣ “ምን ሆነህ ነው?”
ልጅ፣ “እጄ አልወጣ ብሎኝ”፡፡ አባት፣ “እጅህ በሁለቱ የብረት
አጥሮች መካከል እንዴት ገባና ነው አልወጣ ያለህ?” ልጅ፣
“መዳፌን ዘርግቼ ነው ያስገባሁት፡፡” አባት፣ “ታዲያ ለምን
መዳፍህን ዘርግተህ ልክ እንዳስገባኸው አታስወጣውም?”፡፡
ልጅ፣ “መዳፌን ከዘረጋሁት የያዝኩት ነገር ስለሚያመልጠኝ
መልቀቅ አልፈልግም፡፡”
አባት፣ “ካለህበት ሁኔታ መላቀቅ ከፈለግህ የያዝከውን ነገር
መልቀቅ የግድ ነው፡፡ አለዚያ እንደተያዝክ በዚያው መቅረትህ
ነው” ብሎት ጥሎት ሄደ፡፡ በዚህ ጊዜ ነበር የውሻው ድምጽ
የተሰማው፡፡ ውሻው እየዘለለ ሲመጣ ያየው ይህ ልጅ ምንም
ምርጫ ስለሌለው የጨበጠውን ነገር በመልቀቅ ከተያዘበት ነገር
ተላቀቀ፡፡ የተያዝክበትና የተጨነክበት ነገር እንዲለቅህ ምናልባት መልቀቅ
ያለብህ ነገር ይኖር ይሆን? በሕይወትህ አልሄድና አልተው ያለህ ችግርህ ምናልባት አንተው መልቀቅና መተው ከሚገባህ ነገር ጋር ይገናኝ ይሆን?
ብዙዎቻችን ጨብጠን ያለቀቅናቸው ብዙ ባዕድ ልማዶች አሉን! እነሱን ሳንተው ከፈጣሪ ዘንድ ልንደርስ አይቻለንም። እናም ክርስቲያኖች መልቀቅ ያለብንን ለቀን መያዝ ያለብን ላይ እናተኩር።


@aleroe
ኤልሮኢ:
ታህሳስ 28/04/12ዓ.ም
ዕለተ በዐለ ልደቱ ለእግዚእነ

በዕለቱ ቅዳሴ ሰዓት የሚነበቡ መልዕክታት፣ወንጌልና ምስባክ፡፡

ዲ/ን ገላ 4 ÷1_12
ን/ዲ 1 ዮሐ 4÷9_ፍ.ም
ን/ካ ግብ፡ሐዋ 13÷16_22

#ምስባክ፦መዝ 79÷1
የሐዩ ወይሁብዎ እምወርቀ ዓረብ።
ወዘልፈ ይፄልዩ በእንቲአሁ።
ወኲሎ አሚረ ይድኅርዎ።

#ትርጉም፦ 
እርሱ ይኖራል ከዓረብም ወርቅ ይሰጡታል።ሁልጊዜም ወደ እርሱ ይፀልያሉ።ዘወትር ይባርኩታል።

#ወንጌል፦ ሉቃ 2 ፥1 - 21
#ቅዳሴ፦ ጎርጎርዮስ ካልእ

@aleroe
ኤልሮኢ:
እሰይ እሰይ
===========
እሰይ እሰይ ተወለደ
እሰይ እሰይ ተጠመቀ
ከሰማየ ሰማያት ወረደ
ከድንግል ማርያም ተወለደ/4/
አዝ--------------//
እሱ ባይወለድ እሰይ እሰይ
ቸሩ አምላካችን እሰይ እሰይ
እርሱ ባይጠመቅ እሰይ እሰይ
መደኃኒታችን እሰይ እሰይ
መች ትገኝ ነበር እሰይ እሰይ
ገነት ርስታችን እሰይ እሰይ
አዝ--------------//
ብርሃን ወጣላቸው እሰይ እሰይ
በእውነት ወገኖቹ እሰይ እሰይ
በጨለማው ጉዞ እሰይ እሰይ
እንዳይሰላቹ እሰይ እሰይ
አዝ--------------//
እንደ ጠል ወረደ እሰይ እሰይ
ከሰማይ ወደኛ እሰይ እሰይ
ወገኖቹን ሊያድን እሰይ እሰይ
ከክፉ ቁራኛ እሰይ እሰይ
አዝ--------------//
እግዚአብሔር አብ ላከ እሰይ እሰይ
እንድያ ልጁን እሰይ እሰይ
እርሱ ወዷልና እሰይ እሰይ
እንዲሁ አለሙን እሰይ እሰይ

@aleroe
ኤልሮኢ:
ዝምተኛው መነኩሴ (#ራስአገዝ)

ከዝምተኛው መነኩሴ አባ ዮስጦስ ፀሎት አንዱ "ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ቅዱሳን በተጓዙበት ጎዳና ምራኝ" ነበር፡፡ የዚህ ጸሎት ትርጉም ቅዱስ አድርገኝ ማለት እንደነበር በህይወታቸው ፍፃሜ በሚገባ ተረድተናል፡፡ ቅዱስ እንደሆኑ ማሰብ እንጂ ቅዱስ ለመሆን ማሰብ ወይም በቅድስና መንገድ ለመጓዝ መሻትና መጸለይ መልካም ነው፤ ምክንያቱም ከፈጣሪያችን ትእዛዛትና ፈቃድ አንዱን ለመፈጸም መመኘት ነውና እግዚአብሔርን ደስ ያሰኘዋል፡፡ እግዚአብሔር በቃሉ "እኔ ቅዱስ ነኝና እናንተም ቅዱሳን ሁኑ" እንዳለ ቅዱስ ጳውሎስም "እኔ ክርስቶስን እንደምመስል እኔን ምሰሉ" በማለት የቅድስናን ህይወት እንድንኖር እንደመከረን ስናስተውል ቅዱስ የመሆን ትእዛዝ እንዳለብን እንረዳለን፡፡ ስለቅድስና ሲነሳ እኛ ቅዱሳን ልንሆን ይገባል ማለቱ በራሱ ወደር የማይገኝለት ድፍረት ሆኖ ሳይሰማን አይቀርም፡፡ነገር ግን መሻቱ ሳይሆን የቅድስና ቁምነገር ነኝ አለማለቱ እና በጭራሽም ነኝ ብሎ አለማሰቡ ላይ ነው፡፡ ሰው ቅዱስ የሚሆነውም ከእግዚአብሔር ፈቃድ ባሻገር በምርጫውና በፍላጎቱ ነውና ይህን የሚያስረዳን ነው።

ዲያቢሎስ ስለመረጠ ከቅድስና ጎድሏል፥ ቅዱሳን መላእክት ደሞ በምርጫቸው ቅዱሳን ሆነዋል ፡፡ሰውም እንዲሁ ነው፡፡ ስለዚህ ለቅድስና መጠራታችንን እና መታዘዛችን እንዲፈጸምልን መጸለይ መሻት መጣር ያስፈልገናል፡፡የጌታችን አማናዊ ቃሉ "ለምኑ፥ ይሰጣችሁማል፤ ፈልጉ፥ ታገኙማላችሁ፤ መዝጊያን አንኳኩ፥ ይከፈትላችሁማል።"ይለናልና።(ማቴ 7:7)
ስለዚህ ቅዱስ የመሆን ፍላጎት ቅዱስ ነውና በማሰባችን ወይም በመመኘታችን ድፍረት መስሎን መጨነቅ አይደገፍም፡፡ ነገር ግን በትህትና መለመንና ሁሉም ነገር በእግዚአብሔር ቸርነት እንደሚፈጸም ማመን ነው፡፡ ያለ እግዚአብሔር ቸርነት (ሰጪነት) በጥረታችን የምናገኘው ምንም ነገር የለም፡፡ "እኔ የወይን ግንድ ነኝ እናንተም ቅርንጫፎች ናችሁ። ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉምና በእኔ የሚኖር እኔም በእርሱ፥ እርሱ ብዙ ፍሬ ያፈራል።" (ዮሐ 15:5) እንዳለ ያለእርሱ ቅዱስ መሆን ቀርቶ ቅድስናን ማሰብም እንኳን አይቻልም፤ ከእርሱጋ ግን ሁሉ ይቻላል፡፡ ወደቅድስና ከሚመሩን በርካታ ነገሮች እጅግ ጥቂቶቹ በመቀጠል ቀርበዋል፡፡

✞የእግዚአብሔርን ቸርነት እና ፍቅር ማሰላሰል

✞ህዋሳትን ኃጢአት ከመስራት መጠበቅ

✞ ለሰሩት በደል በቶሎ መፀፀት

✞ከሰው ክብርን አለመፈለግ

✞ምስጋናን አለመሻት

✞ ጥላቻንና ትችትን በፍቅር መቀበል

✞ መጸሐፍቅዱስን አዘውትሮ ማንበብ

✞ ያለማቋረጥ መጸለይ

✞በምስጢራት መካፈል

✞ትእዛዛቱን ለመፈጸም መጣጣር

✞በምክረ ንስሀ መጓዝ

✞ራስን እንደተለየ ነገር አለመቁጠር

✞ራስን መገምገም መመልከት

✞ቃለእግዚአብሔርን ማዳመጥና

✞የምንሰማዉን ቃል መፈጸም

✞ከልብ የሆነ ጾምን መጾምና መጸለይ

✞በጎ አድራጎትን መፈጸም

ማንኛውም የምንሰራው ሥራ እግዚአብሔርን ደስ እንዲያሰኝ ብሎ እንጂ አንዳች ጥቅም አገኝበታለሁ በማለት አይደለም፡፡ መሪ ምክንያቱ ፍቅር እንጂ ጥቅም መሆን የለበትም፡፡ ለቅድስና መጋደል እንጂ ቅዱስ እንደሆኑ ማሰብ መጀመር የውድቀት መጀመሪያው ሳይሆን መጨረሻ መሆኑን ማስመር ይገባል፡፡ እነኚህ በየጥቂቱ ልናድግባቸው የምንችላቸው መንፈሳዊ ተጋድሎ የሚጠይቁ ልምምዶች ናቸው ፡፡

ይቆየን!

@aleroe
ኤልሮኢ:
ምን ይል ይሆን

ዛፍ ቆራጩ የዛፉን ቅርንጫፍ መልምሎ ሲያበቃ ዛፉ እንደቆመ ራሱን ከዛፉ ጋር አስሮ ከግንዱ ጋር ሊታገል ወደ ላይ ተስቦ ከጫፍ ደርሷል። አሳቡ ቅርንጫፉ ተመልምሎ ያለቀለትን ብቻውን የቆመውን ዛፍ ከላይ ጀምሮ እየቆረጠ ወደ ታች ለመውረድ ነው።
መጥረብያውን ወደ ላይ ሲያነሳ ግን ንፋሱ ወደ ኋላ እያስጎነበሰውና በፍጥነት እያቃና ያንገላታዋል። ይሄኔ በሁለት እጁ ግንዱን አፈፍ ያደርግና ዥዋዥዌ ይጫወታል።
ንፋሱ እንኳንስ ስራ ሊያሰራው ቀርቶ ለህይወቱም አስጊ ሆነ። ይሄኔ ሁሉንም ርግፍ አርጎ ዐይኖቹን ወደ ሰማይ በማቅናት "ፈጣሪዬ ሆይ ከዚህ በሰላም ካወረድከኝ በኪሴ ያለውም 50 ብር አምጥቼ አስገባለሁ" ሲል ይሳላል
ወድያው ይህን ተናግሮ ሲጨርስ ነፋሱ ይቆምና በሰላም ይወርዳል። ነገር ግን እግሩ መሬት ሲነካ ፍርሃቱ ሁሉ በኖ ስለጠፋ 50 ብሩን ለማስገባት ሳስቶ ምክንያት ይፈልግ ጀመር
"አዎ በርግጥ ከዚህ ዛፍ ላይ ካወረድከኝ ብዬ ተስያለሁ ነገር ግን የወረድኩት እኔ ራሴ ነኝ። ተሸክሞ ያወረደኝ ሳይኖር ለምንድነው 50ብሬን የማወጣው"  ብሎ እራሱን በማሳመን ወደ ቤቱ ጉዞ ቀጠለ።
ዳሩ ግን ትንሽ እየተራመደ ትከሻው ቀለለውና ቢዳብሰው መጥረብያው የለም። መጥረብያው ከዛፉ ጫፍ እንደተሰካ ነው። አሁንስ ምን ይል ይሆን።
የሰው ልጅ ፍጡር ነው ሁሌ ከፈጣሪ እጅ አይወጣም እንድያው ይመስለናል እንጂ ያለ እግዚአብሔር መኖር አንችልም። ያለእኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉም ይለናል ዮሐ 15፣5

@aleroe
ኤልሮኢ:
+++ ምን ብዬ ልጸልይ? +++

በግሪክ ሀገር ሁለት ሴት ልጆቹን ያሉት አንድ አባት ነበር። በአንድ ዓመት ብቻ የሚበላለጡትን እነዚህን ሕጻናት እንደ አባትም እንደ እናትም ሆኖ ተንከባክቦ ማሳደግ የዚህ ሰው ዋነኛ ሥራው ነበር።
ስለዚህ ወጥቶ በገባ ቁጥር ልጆቹን የሚያስደስት ነገር እየገዛ ፣ የሚጠይቁትን እያሟላ በድሎት ያኖራቸው ነበር። የራሱን ሕይወት ወደ ጎን ትቶ ለልጆቹ መኖሩ ያለ ዋጋ አልቀረም። ሁለቱም ልጆቹ በጤንነት አድገው ዕድሜያቸው ለጋብቻ ደረሰ።
አባት የለፋባቸው ልጆቹን ከመዳሩ በፊት ብዙ መሰብ ነበረበት። አስተዋይ ነበርና ብዙ ሽማግሌ ቢላክበትም ልጆቹን ለመሥጠት የወሰነው ግን በጥንቃቄ ነበር። ስለዚህ ልጆቹ ሁለቱም በአንድ ጊዜ እንዳይቸገሩ በማሰብ የተለያየና የማይነጥፍ መተዳደሪያ ላላቸው ወንዶች ባል እንዲሆኑ ለማድረግ ወሰነ።
እንዲህ ሲልም ያወጣና ያወርድ ጀመር :
"ሰዎች ሁልጊዜም ምግብ ያስፈልጋቸዋል ስለዚህ ገበሬ መቼም ቢሆን እህል ገዢ አያጣም። እንዲሁም ሰዎች ውኃ ለመቅዳት ምግብ ለመሥራት ሸክላ ስለሚፈልጉ ሸክላ ሠሪም ገበያ አያጣም።
ስለዚህ ልጆቼን የምሠጠው ለሸክላ ሠሪና ለገበሬ ነው" አለ። እንዳለውም አንዲቷ ልጁ የገበሬ ሚስት ሌላኛዋ ደግሞ የሸክላ ሠሪ ሚስት እንዲሆኑ ሠጣቸው።
ከብዙ ጊዜ በኋላ በአንድ ሰንበት ይህ ሽማግሌ ዛሬስ ልጆቼን ልጠይቅ ብሎ ተነሣ። በመጀመሪያ ወደ ገበሬው ሚስት ሔዶ ሲጫወት አረፈደ።
ተሰናብቶ ሊወጣ ሲል ልጁ እንዲህ አለችው :
"አባዬ እስካሁን ኑሮአችን ሰላም ነበር። አሁን ግን ችግር ላይ ነን። ላለፉት ሁለት ወራት ዝናም ጨርሶ አልዘነበም። በዚሁ ከቀጠለ የዘራነው አይበቅልም ፣ ተክሎቻችንም ይደርቃሉ።
አባዬ አደራ! በሚመጣው ወር ከባድ ዝናም እንዲጥል ወደ ፈጣሪ ጸልይልን!"
አባት አደራውን ተቀብሎ ተሰናብቶ ወደ ሁለተኛዋ ልጁ ቤት ለመሔድ ጉዞውን ጀመረ።
ከሰዓት በኋላ ወደ ሁለተኛዋ ልጁ ቤት ሲደርስ ከሸክላ ሠሪው ባሏ ጋር በአክብሮት ተቀብለው አስተናገዱት። ከጠዋቱ የበለጠ ደስተኛ ሆኖም አሳለፈ። መሰናበቻው ላይ ግን ልጁ ተነሥታ እንዲህ አለችው:
"አባዬ ለአንተ ለጸሎተኛው አባቴና ለጠንካራው ባለቤቴ ምስጋና ይሁንና ኑሮአችን እስካሁን ጥሩ ነው። እንደምታውቀው ላለፉት ሁለት ወራት ዝናም አልዘነመም። በዚህም ደስተኞች ነን። አሁን የምለምንህ አንድ ነገር ብቻ ነው።
በሜዳ ላይ ተደርድሮ እንደምታየው እጅግ ብዙ ሸክላዎች እየሠራን ነው። በሚመጣው ወር ዝናም ካልዘነመና ደረቅ ከሆነ የሠራናቸው ዕቃዎች ሁሉ ደርቀው ለገበያ ይደርሱልናል። ስለዚህ በሚመጣው ወር ዝናም እንዳይጥል ወደ ፈጣሪህ ጸልይልን"
አባት ተሰናብቶ ሲወጣ ወደ ሰማይ ቀና ብሎ
"ፈጣሪዬ ሆይ አንዲቱ እንዳይዘንም ጸልይ አለችኝ ፣ ሌላዋ እንዲዘንም ጸልይ አለችኝ ፣ ምን ብዬ ልጸልይ?" አለ።
ይህ አረጋዊ የእኛን ቤተ ክርስቲያን ቅዳሴ ቢያስቀድስ ኖሮ ግን እንዲህ አይጨነቅም ነበር። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ቅዳሴ ላይ ዲያቆኑ የሚያነበው ምእመናን በግንባራቸው ተደፍተው የሚሰሙት "በእንተ ቅድሳት" የሚባል ጸሎት ላይ የዚህን ሽማግሌ ልብ የሚያረጋጋ ስለ ዝናም የሚጸለይ አንቀጽ አለ። እንዲህ ይላል:
"በሚሻበት ቦታ እግዚአብሔር ዝናሙን ያዘንም ዘንድ ስለ ዝናም እንማልዳለን"
"በሚሻበት" የሚለው ቃል ላይ "ሻ" ጠብቃ ትነበባለች። "በሚፈለግበት ቦታ እግዚአብሔር ዝናሙን ያዘንም ዘንድ" (ኀበ ዘይትፈቀድ መካን) ማለት ነው። ቀሳውስቱም ስለ ዝናማት በሚጸልዩት መስተብቁዕ ላይ "ወደ ሚሻበት ቦታ ዝናሙን ይልክ ዘንድ" (ከመ ዝናሞ ይፈኑ ውስተ ኀበ ይትፈቀድ መካን) "ወደሚሻበት ቦታ ዝናሞችህን ላክ"(ዝናማቲከ ፈኑ ውስተ ኀበ ይትፈቀድ መካን) ይላሉ።
ዝናም እንደ ገበሬው ቤት የሚፈለግበት ቦታ እንዳለ ሁሉ እንደ ሸክላ ሠሪው ቤት ደግሞ የማይፈለግበት ቦታ አለና ቤተ ክርስቲያን ከፈጣሪዋ ዝናም ከመለመን አልፋ የሚያዘንምበትን ቦታም እየጠቆመች ትጸልያለች።

"ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ "

@aleroe
ኤልሮኢ:
ይህን ያውቁ ሮሯል!!!

በተለምዶ ‹‹ አርባ አራቱ ታቦት›› እያልን የምንጠራቸው አብያተ ክርስቲያናት ያሉት በጐንደር ከተማ ሲሆን ስማቸውም የሚከተለው ነው፡፡

1. ፊት ሚካኤል
2. ፊት አቦ
3. አደባባይ ኢየሱስ
4. ግምጃ ቤት ማርያም
5. እልፍኝ ጊዮርጊስ
6. መድኃኔዓለም
7. ቅዱስ ገብርኤል
8. ጠዳ እግዚአብሔር አብ
9. አባ እንጦንዮስ
10. ደብረ ብርሃን ሥላሴ
11. አደባባይ ተክለሃይማኖት
12. ሠለስቱ ምእት
13. ልደታ ለማርያም
14. አጣጣሚ ሚካኤል
15. አቡነ ኤውስጣቴዎስ
16. ቅዱስ ሩፋኤል
17. ደፈጫ ኪዳነ ምሕረት
18. ቁስቋም ደብረ ፀሐይ
19. መጥምቁ ዮሐንስ
20. በኣታ ለማርያም
21. ቅዱስ ቂርቆስ
22. ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ
23. አባ ጃሌ ተ/ሃይማኖት
24. ፈንጠር ልደታ
25. ደብረ ምጥማቅ ማርያም
26. አባ ዐቢየ እግዚእ
27. ቅዱስ ፋሲለደስ
28. ሐዋርያት
29. ቀሃ ኢየሱስ
30. አርባዕቱ እንስሳት
31. ጎንደሮች ጊዮርጊስ
32. ጎንደሮች ማርያም
33. አበራ ጊዮርጊስ
34. ብላጅግ ቅዱስ ሚካሌል
35. አባ ሳሙኤል
36. አይራ ሚካኤል
37. ጓራ ዮሐንስ
38. ወረንግቦ ጊዮርጊስ
39. አሮጌ ልደታ
40. አዘዞ ተ/ሃይማኖት
41. ምንዝሮ ተ/ሀይማኖት
42. ሰራራ ማርያም
43. ዳሞት ጊዮርጊስ
44. ጫጭቁና ማርያም

በቃል ያለ ይረሳል በ………………………

@aleroe
ኤልሮኢ:
ቤተ ክርስቲያን መሄድ ጥቅም የለውምን ?

የግብጻዊው መነኩሴ ምክር

…………ብዙ ጊዜ በእግረ ስጋው ወደ ቤ/ክ ይመላለስ የነበረ አንድ አማኝ ወደ አንድ አባት ሄዶ ብዙ ጊዜ ቤተ ክርስቲያን መመላለሱ ስሜት አልባ እና ትርጉም የሌለው ነገር እንደሆነበት እየተማረረ እንዲህ አላቸው “ለ 30 አመታት ያህል ቤተ ክርስቲያን ተመላልሻለሁ፣ በእነዚህ አመታት ብዙ ጉባኤያትን ተካፍያለሁ፣ ቅዳሴ አስቀድሻለሁ፣ ንስሀ ገብቻለሁ. . . . . . ግን ትርጉም ያለው ነገር የለኝም፣ ካሳለፍኳቸው አገልግሎቶች ውስጥ ትዝ የሚሉኝ ብዙም የሉም፣ እንደ ትዝታ የሚታወሰኝም የለኝም፣ እንደ ብክነት አየዋለሁ . . . .ካህናቱና ሰባክያኑም ያለ ምንም ትርፍ ጊዜያቸውን እያባከኑ ያለ ይመስለኛል. . . . .”
ካህኑ በጥንቃቄ አዳመጡት፡፡ የብዙ አማኝ ችግርም እንደሆነ አስረዱት፣ ሰይጣን ሆነ ብሎ የቀየሰው ወጥመድ እንደሆነ አስታወሱትና ያለፈውን የህይወት ተሞክሯቸውን እያነሱለት እሱ እንደ ብክነት መስሎት የተመለከተው ነገር ጥቅሙ እንደነበር ነግረውት የእሱ ችግር ሰይጣን ቤተ ክርስቲያን ባሳለፋቸው 30 አመታት የተጠቀመውን እንዳይመለከት አይኑን ዘግቶት ጉድለቱን ብቻ እያሳየው ተስፋ እያስቆረጠው እንደሆነ ነግረውት የራሳቸውን ተሞክሮ በዘይቤ እንዲህ አሉት ፡-
“ትዳር የያዝኩት የዛሬ 30 አመት ነው፣ ካገባሁ 30 አመት ሞልቶኛል፡፡ በእነዚህ 30 አመታት ውስጥ ባለቤቴ ከ 32,000 በላይ የምግብ አይነት ሰርታ መግባኛለች፡፡ ሆኖም ግን አንድም ቀን እነዚህን የምግብ ዝርዝሮች ለአንድ ጊዜም ቢሆን አስታውሻቸው አላውቅም፣ የማውቀው ነገር ቢኖር ግን ይህንን ነው፡- እነዚህ ምግቦች ተንከባክበውኛል፣ በሽታ እንዳያጠቃኝ ተከላክለውልኛል፣ ስራዬን በአግባቡ እንድሰራ ጥንካሬ ሰጥተውኛል፣ የነቃ አእምሮ እንዲኖረኝ አንቅተውኛል፡፡ ባለቤቴ ዛሬ በዚህ ጤንነት እንድቆም ያደረገኝን ምግብ ባትመግበኝ ኖሮ በህይወት ባልኖርኩና በሞትኩ ነበር ፣ አይነታቸው ትዝ ስላላለኝ ጥቅም የላቸውም ልል ይገባኛልን? ለዛሬ መኖሬ ምክንያት ባለፈው 30 አመታት የተመገብኳቸው ግን አሁን ትዝ የማይሉኝ ምግቦች ናቸው፣ ምግብ ሁሌም አዲስ ነው፣ የምንመገበውም እንደ አዲስ ነውና፡፡ ባልሞት እንኳን ንቁ ሆኜ ሰው የሚጠቀምበትን አገልግሎት ባላገለገልኩ እንደ አንተ አይነት ያሉትን ባልመከርኩ ነበር” ልክ እንዲሁ ላለፉት ብዙ ጊዜያት ወደ ቤተ ክርስቲያን ሄጄ ባይሆን ኖሮ በመንፈሴ ሞቼ በኖርኩ ነበር፡፡ ዛሬ ቤተ ክርስቲያንን ተጠግቼ ህይወቴን እንድመለከት ባልሆንኩ ነበር፤ ሌላው ቢቀር እንኳን “ያሳለፍኩት አመታት ብክነት ይሆኑ እንዴ” ያስባለኝ ቤተ ክርስቲያን መመላለሴ ነው፡፡ የሰማኋቸው፣ ያነበብኳቸው የቃል ምግቦቹ በዝተው ዛሬ እንድቆም አድርገውኛል፡፡ ጥቅሜን ማየት ተስኖኝ እንጂ ለካ ዛሬ በመንፈሴ ጤናማ ሆኜ የቆምኩት ባለፉት 30 አመታት የተመገብኳቸው አገልግሎቶች ናቸው? የዛሬ 20 እና 25 ዓመታት የተማርናቸውን ትምህርቶች ላናስታውሳቸው እንችል ይሆናል፡፡ ዛሬ መልካም አእምሮ እንዲኖረን ያደረጉት፣ ኃጥያት ስንሰራ የሚገስፅ አእምሮ እንዲኖረን ያደረጉት እዚህ በመመላለሳችን ያገኘናቸው ሀብቶች ናቸው። ለምንም ወደታች ስትወርድ እግዚአብሔር ለአንድ ነገር ወደ ላይ ያወጣሃል፡፡ የወረድክ ቢመስልህም አትመን ጌታ ወደ ላይ ለጥቅም ያወጣሃልና፡፡ በቤቱ ያለ ትርፍ እየተመላለስክ ያለህ አይምሰልህ ሽልማት ላይ ደርሰሃልና፡፡ እምነት የማይታየውን ያያል፣ የማይታመነውን ያምናል፣ የማይቻለውን ይቀበላል፡፡ ሴጣን ከቤ/ክ እንድንቀር፣ ፀሎት እርግፍ አድርገን እንድንተው ሲፈልግ ነው ያንን ማድረጋችን ምንም ጥቅም እንደሌለው ደጋግሞ ያሳስበናል። በቤቱ መመላለሳችን ግን ጥቅም አለው በረከት አለው። ማንም የአንድ ባለፀጋ ቤት ተጋብዞ ሄዶ ሳይበላ ሳይጠጣ ሚመጣ የለም፣ እኛም ከሁሉ የሚበልጠው ባለፀጋው የመድህን ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ቤት(ቤተክርስቲያን) ኑ ብሎ ጠርቶን ሄደን ባዶአችንን ፍፅም አንመለስም። ለእኛ አሁን ጥቅሙ ባይታየንም የመንፈስ ቅዱስ በረከት ግን እያደረብን ይሄዳል።

በቤቱ ፀንተን ለዘለዓለም እንድንኖር ይርዳን።
አሜን!

@aleroe
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ኤልሮኢ :
ኃዲጎ ተሰአ
ኀዲጎ ተሰአ ወተሰአተ ነገደ /2/
ማእከለ ባሕር /4/ ቆመ ማእከለ ባሕር/2/
ኤልሮኢ:
ልሳነ_ግዕዝ ሞክሼ_ፊደላት

ሞክሼ ፊደላት የሚባሉት አንድ አይነት ድምጽ ያላቸው ነገር ግን በቅርጽ እና በስራቸው የተለያዩ ፊደላት የሆኑ ናቸው።
በድሮ ጊዜ ግን አባቶቻችን ሀን ከ ሐ ፣ ጸን ከ ፀ... ፊደሎችን በድምጽ አወጣጥ ይለዮአቸው ነበር።

እኝህ ፊደላት በቁጥር ፱(9) ሰሆኑ
ሀ ፣ ሐ ፣ ኀ ፣ ሠ ፣ ሰ ፣ አ ፣ ዐ ፣ ጸ ፣ ፀ ናቸው።

ሀ ➺ ሃሌታው "ሀ" ይባላል።
◦ሃሌ ሉያ ብለን ስንጽፍ የምንጠቀመው ይህን ፊደል ስለሆነ ሃሌታው "ሀ" ተብሏል።

ሐ ➺ ሐመሩ "ሐ" ይባላል።
◦ሐመር ብለን ስንጽፍ የምንጠቀመው በዚህ ፊደል ስለሆነ ነው።

ኀ ➺ ብዙኀኑ "ኀ" ይባላል
◦ብዙህ ብለን ስንጽፍ የምንጠቀመው ይህን ስለሆነ ነው።

አ ➺ አልፋው "አ" ይባላል።
◦አልፋ ኦሜጋ ብለን ስንጽፍ የምንጠቀምበት ስለሆነ ነው።

ዐ ➺ ዓይኑ "ዐ" ይባላል።
◦ዓይኑ ብለን ስንጽፍ የምንጠቀምበት ስለሆነ ነው።

ሠ ➺ ንጉሡ "ሠ" ይባላል።
◦ንጉሥ ብለን ስንጽፍ የምንጠቀመው ይሄን ፊደል ስለ ሆነ ነው።

ሰ ➺ እሳቱ "ሰ" ይባላል።
◦እሳት ብለን ስንጽፍ የምንጠቀመው ይህን ስለሆነ ነው።

ጸ ➺ ጸሎቱ "ጸ" ይባላል።
◦ጸሎት ብለን ስንጽፍ የምንጠቀመው ይሄን ፊደል ስለሆነ ነው።

ፀ ➺ ፀሐዩ "ፀ" ይባላል።
◦ፀሐይ ብለን ስንጽፍ የምንጠቀመው ይህን ፊደል ነው።
እነዚህ ሞክሼ ፊደላት አንዱ በአንዱ ቦታ መግባት የለበትም ምክንያቱም የትርጉም ለውጥ ያመጣሉ።
ለምሳሌ ፦
➺ ሠረቀ = ወጣ
ሰረቀ = ሰረቀ
➺ አመት = አገልጋይ
ዓመት = ዘመን
➺ ሰዐለ = ስዕል ሳለ
ሰአለ = ለመነ
➺ መሀረ = አስተማረ
መሐረ = ይቅር አለ
➺ ኀለየ = አመሰገነ
ሐለየ = አሰበ
➺ ፈጸመ = ጨረሰ
ፈፀመ = ነጨ
➺ ማኅሌት = ማመስገን
ማሕሌት = ማሰብ

@aleroe
ኤልሮኢ:
#ፍቅር_ማለት

ያን_ሁሉ መስዋእት ያን ሁሉ ግርፋት
ልጅን_ከአባት ጋር አባትን ከልጅ ጋር
           አስታርቆ ለማየት ፤
እኔ ያ ሰው ነኝ የከበረ ዋጋ የተከፈለበት
እኔ ያ. ሰው ነኝ በደሙ_ታጥቤ
 ነፃ የሆንኩበት ፤
ታድያ ለዚህ ከንቱ አለም ላልወደደው
         በትንሽነቱ ሰው ሁሉ ለናቀው ፤
እንዴትስ ተገብቶት ጌታ ሊሞትለት
እንዴትስ ተደርጎ ክብሩን ሊተውለት ፤

ይህ_ፍጡር ማን ቢሆን ነው ከቶ
የሰማዩን_ንጉስ ግዛቱን አስትቶ
በሀጥያቷ ክርፋት ወደ ገማች ምድር
ጠርቶና ጎትቶ ፤
ሞትን_ያቀመሰው የትኛው ፍቅር ነው
የቱ ቅድስና የቱ ማንነቴ የቱ ንፅህና ፤
ንፁህ_የሆነውን ፅድቅ የለበሰውን
ስጋ ያለበሰው ሀጥያት ያደረገው
የቱ እኔነቴ እሱነቱን ትቶ እንዲያ
ሚያዋርደው ? ፤

ያንን_ፍቅርማ ቃላት ተቆፍረው
ያንን_መውደድማ ፊደላት ተጣምረው ፤
ከቶ አይገልፁትም ፍፁም አይደርሱትም
ብርሀን አያደምቀው ጨለማ አይጋርደው
የቀናት መገስገስ የአመታት መንጎድ
        ዘመን የማይሽረው ፤
ፍ ቅ ር ማለት ያ ያ ነው
ፍቅር_ውልደቱ ነው ፍቅር መከራው ነው
ፍቅር_መሞቱ_ነው ፍቅር ትንሳኤው ነው ፤
በዘመን ጅማሬ በዘመን ፍፃሜም
የፍቅር  ስንኙ   የፍቅር ሀረጉ
         ኢ  የ  ሱ  ስ ብቻ ነው !
__________________
@aleroe