"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
⛰⛰⛰
እንደ ግብሬ ሳይሆን እንደ እግሬ ስጠኝ!
ተወዳጆች ሆይ አንዳንዶች ወደ ቤተ ክርስትያን ያለ ልባችን በእግራችን መመላለሳችን ወጋ እንደ ሌለው ይነግሩናል፡፡ እኛም ልባችን እየባከነ፣ሰውነታችን በኃጢአት እያደፈ ቤተ እግዚብሔር መመላለሳችን ዋጋ ቢስ ይመስለናል፡፡
ወዳጆቼ አንድ ሰው ልቡ ወደ እግዚአብሔር እንዲመለስ በመጀመርያ እግሩ ሊመላለስ ይገባል፡፡ የእግር መመላለስ ልብን በማስቀደስ እውነተኛውን መንፈሳዊ ሕይወት እንድንኖር ያደርገናል፡፡ የእግር መመላለስ ከንቱነትን የሚሰብኩ አሉ፡፡ ይህ ከእግዚአብሔር ቸርነት አንጻር ተገቢ አይደለም፡፡ እስኪ እኛ ወደ ደጁ ከነ ኃጢአታችን እንመላለስ፤እግዚአብሔር ደግሞ በሂደት በቃሉ መስታወት እራሳችንን ያሳየናል፣በወንጌሉ ብርሃን ልባችንን ያበራል፡፡
ወዳጆቼ በእግዚአብሔር ቤት ከነ ኃጢአታችን እየተመላለስን ስለ ሕይወታችን ቢያንስ እንደ ግብሬ ሳይሆን እንደ እግሬ ስጠኝ ብለን መለመን እንችላለን፡፡ ግብራችን ለልመናችን እቅፋት ቢሆንም እግራችን ግን ወደ እግዚአብሔር በመገስገሱ፣በመመላለሱ እግዚአብሔር እንደ ቸርነቱ ያደርግልናል፡፡
በነገራችን ላይ አብዛኞቻችን ከእግዚአብሔር የሚሰጠን ማናቸውም ነገሮች እንደ ሥራችን ሳይሆን እንደ ቸርነቱ ነው፡፡ በውጭ ለሰው የሚታየው ቅድስናችን፣መልካም ሥራችን ለሰው የተገለጠ ነው ግን የውስጥ ገመናችን፣ኃጢአታችን በእግዚአብሔር ቸርነት ለሰዎች የተሰወረ ነው፡፡ ስለዚህ አብዛኞቻችን እንደ ግብራችን ሳይሆን እንደ እግራችን ነው የሚሠጠን፡፡ በደላችን በሰው ፊት ተሰውሮ፣በእግዚአብሔር ፊት ተነውሮ ግን እግራችን በደጁ በመመላለሱ ነው የሚደረግልንና እየተደረገልን ያለው፡፡
እግዚአብሔርም በባሕርይው እንደ ሥራችን ሳይሆን እንደ ቸርነቱ ስንለምነው ነው የበለጠውን የሚሰጠን፡፡ ሰው በመንፈሳዊው ተጋድሎው፣በቅድስና ሥራው፣በበጎ ምግባሩ ልክ ከለመነው የትኛውም ሥራችን ከእሱ ቸርነት በላይ ስለማይሆን በግብራችን ከሚሰጠን ይልቅ በቸርነቱ የሚሰጠን ይበልጣል፡፡ ልመናችንም በግብራችን ልክ ሳይሆን በቸርነቱ ልክ ሲሆን ነው ተሰሚነት የሚኖረው፡፡
ትዝ ይላችኃል ጌታችን በምሳሌ በሚያሰተምርበት ጊዜ ሁለት ሰዎች ፈሪሳዊና ቀራጭ ወደ መቅደስ መጥተው ፈሪሳዊው እንደ ሌሎች ሰዎች ቀማኛ ዓመጸኛ አመንዝራ እንዳልሆነና በሳምንት ሁለት ጊዜ እንደሚጾም ካገኘው ሁሉ አሥራት እንደሚያወጣና የጽድቅ ሥራውን እየዘረዘረ በምስጋና ያቀርብ ነበር። በዚህም ፈሪሳዊው ፈጣሪ እንደ ግበሩ እንዲሰጠው፣ልመናውን እንዲሰማው ጸለየ፡፡ ቀራጩ ደግሞ በቅን ልቦና፣በትሁት ሰብእና ሆኖ ከርቀት ቆሞ፣ ከአንደበቱ ጸሎት ማፍለቅ ብቻ ሳይሆን ሰማይን ማየት እስኪሳቀቅ ድረስ ኃጢአቱን በማስታወስ "አምልኬ ሆይ እኔን ኃጢአተኛውን ማረኝ" በማለት ደረቱን በመድቃት ይጸልይ ነበር። ሉቃ 18÷13
ከፈሪሳዊው ይልቅ ትህትናን የተላበሰው ቀራጩ በጌታው ዘንድ ጻድቅ ሆኖ ተገኘ። ምክንያቱም ቀራጩ እንደ ግብሩ ሳይሆን እንደ እግሩ ነበር የለመነው፡፡ በኃጢአት መርከሱን ሳይሆን በእግሩ መመላለሱን ፈጣሪ እንዲቆጥርለት ለመነ፡፡ ይህንንም ጌታ እራሱ ‹‹እላችኃለሁ፣ከዚያ ይልቅ ጻድቅ ሆኖ ወደ ቤቱ ተመሰለ›› ብሎ መስክሮለታል፡፡ /ሉቃ 18÷14/
ወዳጆቼ ግብርን/ሥራችንን በልመናችን መሃል እንደ ሒሳብ እያወራረድን ከለመንን ልመናችን የፈሪሳዊው ነው። ግብሬን ሳይሆን እግሬን ቁጠርልኝ ካልን ልመናችን የቀራጬ ነውና ቸርነቱ ያደርገናል ቀና። በተለይ አሁን በያዝነው መንፈሳዊ ሕይወት እንደ ልባችን ሳይሆን እንደ እግራችን ነው እየተደረገልን ያለው፡፡ ይህ ማለት የልባችን ክፋት፣የሰውነታችን ኃጢአት ሳይሰፈር፣በእግር መመላለሳችን እየተቆጠረ፣ከቤቱ ባለመጥፋትችን እየታሰበ ነው የሚደረግልን፡፡ ስለዚህ የእግዚአብሔር የቃሉ መዶሻ፣የልባችንን ድንጋይ እስኪሰብረው በእግር መመላለሱ ዋጋ ቢስ ስለማያደርገን በእግራችንን ቢሆን መመላለሱን አንተው፡፡
እግዚአብሔር ልባችንን እስኪመልስ፣ኃጢአትን ከሰውነታችን እስኪያፈርስ፣ቢያንስ በቤቱ በእግር እንመላለስ፡፡
↔️↔️↔️↔️↔️↔️↔️↔️↔️↔️
@aleroe
⛰⛰⛰
እንደ ግብሬ ሳይሆን እንደ እግሬ ስጠኝ!
ተወዳጆች ሆይ አንዳንዶች ወደ ቤተ ክርስትያን ያለ ልባችን በእግራችን መመላለሳችን ወጋ እንደ ሌለው ይነግሩናል፡፡ እኛም ልባችን እየባከነ፣ሰውነታችን በኃጢአት እያደፈ ቤተ እግዚብሔር መመላለሳችን ዋጋ ቢስ ይመስለናል፡፡
ወዳጆቼ አንድ ሰው ልቡ ወደ እግዚአብሔር እንዲመለስ በመጀመርያ እግሩ ሊመላለስ ይገባል፡፡ የእግር መመላለስ ልብን በማስቀደስ እውነተኛውን መንፈሳዊ ሕይወት እንድንኖር ያደርገናል፡፡ የእግር መመላለስ ከንቱነትን የሚሰብኩ አሉ፡፡ ይህ ከእግዚአብሔር ቸርነት አንጻር ተገቢ አይደለም፡፡ እስኪ እኛ ወደ ደጁ ከነ ኃጢአታችን እንመላለስ፤እግዚአብሔር ደግሞ በሂደት በቃሉ መስታወት እራሳችንን ያሳየናል፣በወንጌሉ ብርሃን ልባችንን ያበራል፡፡
ወዳጆቼ በእግዚአብሔር ቤት ከነ ኃጢአታችን እየተመላለስን ስለ ሕይወታችን ቢያንስ እንደ ግብሬ ሳይሆን እንደ እግሬ ስጠኝ ብለን መለመን እንችላለን፡፡ ግብራችን ለልመናችን እቅፋት ቢሆንም እግራችን ግን ወደ እግዚአብሔር በመገስገሱ፣በመመላለሱ እግዚአብሔር እንደ ቸርነቱ ያደርግልናል፡፡
በነገራችን ላይ አብዛኞቻችን ከእግዚአብሔር የሚሰጠን ማናቸውም ነገሮች እንደ ሥራችን ሳይሆን እንደ ቸርነቱ ነው፡፡ በውጭ ለሰው የሚታየው ቅድስናችን፣መልካም ሥራችን ለሰው የተገለጠ ነው ግን የውስጥ ገመናችን፣ኃጢአታችን በእግዚአብሔር ቸርነት ለሰዎች የተሰወረ ነው፡፡ ስለዚህ አብዛኞቻችን እንደ ግብራችን ሳይሆን እንደ እግራችን ነው የሚሠጠን፡፡ በደላችን በሰው ፊት ተሰውሮ፣በእግዚአብሔር ፊት ተነውሮ ግን እግራችን በደጁ በመመላለሱ ነው የሚደረግልንና እየተደረገልን ያለው፡፡
እግዚአብሔርም በባሕርይው እንደ ሥራችን ሳይሆን እንደ ቸርነቱ ስንለምነው ነው የበለጠውን የሚሰጠን፡፡ ሰው በመንፈሳዊው ተጋድሎው፣በቅድስና ሥራው፣በበጎ ምግባሩ ልክ ከለመነው የትኛውም ሥራችን ከእሱ ቸርነት በላይ ስለማይሆን በግብራችን ከሚሰጠን ይልቅ በቸርነቱ የሚሰጠን ይበልጣል፡፡ ልመናችንም በግብራችን ልክ ሳይሆን በቸርነቱ ልክ ሲሆን ነው ተሰሚነት የሚኖረው፡፡
ትዝ ይላችኃል ጌታችን በምሳሌ በሚያሰተምርበት ጊዜ ሁለት ሰዎች ፈሪሳዊና ቀራጭ ወደ መቅደስ መጥተው ፈሪሳዊው እንደ ሌሎች ሰዎች ቀማኛ ዓመጸኛ አመንዝራ እንዳልሆነና በሳምንት ሁለት ጊዜ እንደሚጾም ካገኘው ሁሉ አሥራት እንደሚያወጣና የጽድቅ ሥራውን እየዘረዘረ በምስጋና ያቀርብ ነበር። በዚህም ፈሪሳዊው ፈጣሪ እንደ ግበሩ እንዲሰጠው፣ልመናውን እንዲሰማው ጸለየ፡፡ ቀራጩ ደግሞ በቅን ልቦና፣በትሁት ሰብእና ሆኖ ከርቀት ቆሞ፣ ከአንደበቱ ጸሎት ማፍለቅ ብቻ ሳይሆን ሰማይን ማየት እስኪሳቀቅ ድረስ ኃጢአቱን በማስታወስ "አምልኬ ሆይ እኔን ኃጢአተኛውን ማረኝ" በማለት ደረቱን በመድቃት ይጸልይ ነበር። ሉቃ 18÷13
ከፈሪሳዊው ይልቅ ትህትናን የተላበሰው ቀራጩ በጌታው ዘንድ ጻድቅ ሆኖ ተገኘ። ምክንያቱም ቀራጩ እንደ ግብሩ ሳይሆን እንደ እግሩ ነበር የለመነው፡፡ በኃጢአት መርከሱን ሳይሆን በእግሩ መመላለሱን ፈጣሪ እንዲቆጥርለት ለመነ፡፡ ይህንንም ጌታ እራሱ ‹‹እላችኃለሁ፣ከዚያ ይልቅ ጻድቅ ሆኖ ወደ ቤቱ ተመሰለ›› ብሎ መስክሮለታል፡፡ /ሉቃ 18÷14/
ወዳጆቼ ግብርን/ሥራችንን በልመናችን መሃል እንደ ሒሳብ እያወራረድን ከለመንን ልመናችን የፈሪሳዊው ነው። ግብሬን ሳይሆን እግሬን ቁጠርልኝ ካልን ልመናችን የቀራጬ ነውና ቸርነቱ ያደርገናል ቀና። በተለይ አሁን በያዝነው መንፈሳዊ ሕይወት እንደ ልባችን ሳይሆን እንደ እግራችን ነው እየተደረገልን ያለው፡፡ ይህ ማለት የልባችን ክፋት፣የሰውነታችን ኃጢአት ሳይሰፈር፣በእግር መመላለሳችን እየተቆጠረ፣ከቤቱ ባለመጥፋትችን እየታሰበ ነው የሚደረግልን፡፡ ስለዚህ የእግዚአብሔር የቃሉ መዶሻ፣የልባችንን ድንጋይ እስኪሰብረው በእግር መመላለሱ ዋጋ ቢስ ስለማያደርገን በእግራችንን ቢሆን መመላለሱን አንተው፡፡
እግዚአብሔር ልባችንን እስኪመልስ፣ኃጢአትን ከሰውነታችን እስኪያፈርስ፣ቢያንስ በቤቱ በእግር እንመላለስ፡፡
↔️↔️↔️↔️↔️↔️↔️↔️↔️↔️
@aleroe
"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
"ምዕመናን በቤተመቅደስ ሊኖራቸው የሚገባ ሥርዓት
፦በቤተክርስቲያን ቅፅር ግቢ ገበያ ክልክል ነው። /ማቴ 21፡12 ዮሐ 2፡13-18 ፍትሀነገስት አንቀጽ 1/
፦በቤተክርስቲያን ቅፅር ግቢ ግብዣ ማድረግ፣መብላት፣መጠጣት ክልክል ነው። /የሎዶቅያ ሲኖዶስ (ዶቅ) 44 ፍ.ነገ 1/
፦ማንኛውም መብልም ሆነ መጠጥ ከቤተ መቅደስ 40 ክንድ(20 ሜትር) መራቅ አለበት! በመቅደሱ ሕብስቱና ወይኑ ብቻ ይፈተታልና። /ፍ.ነገ 1/
፦በታቦቱ ፊት ለመስገድ ወይም ለመፀለይ ወይም ለማስቀደስ ካልሆነ በቀር ማንም ወደ ቤተመቅደስ ገብቶ እንዲቀመጥ አይፈቀድም
፦ከካህን በስተቀር(ዲያቆናት፣ካህናት፣ቀሳውስት፣ጳጳሳት..) ከምዕመናን ወገን ወደ መቅደስ(ታቦቱ ያለበት) ገብቶ ሥጋ ወደሙን ሊቀበል(ሥጋ ወደሙን የሚያቀብሉ ካህናት ራሳቸው ሁሌም ከማቀበላቸው በፊት በመቅደስ ውስጥ ይቀበላሉ) ታቦቱን ሊጠጋ አይገባም /ፍ.ነገ 1፣ ቀኖና አብሉዲስ ፣ኢያሱ 3፡4/
፦ሴቶች ወደመቅደስ (ታቦቱ ያለበት) እንዲገቡና እንዲፀልዩ አልተፈቀደም። /የሎዶቅያ ሲኖዶስ(ዶቅ) 44፣ ፍ.ነገ 1/
፦ከቤተ ክርስቲያን አንዴ ለአገልግሎት ተመርጦ የገባውንና የተቀደሰውን ንዋየ ቅድሳት እንደገና ወደውጭ አውጥቶ መጠቀም አይገባም። /ፍ.ነገ 1፣ 1ቀለሚንጦስ (ረስጣ) 28/
፦ያላመኑ፣ ያልተጠመቁ፣ ተወግዘው የተለዩ ወደ ቤተክርስቲያን እንዳይገቡ ተከልክሏል። /ፍ.ነገ 1፣ ድድስቅሊያ (ድስቅ) 12/
፦ለፀሎትና ቅዱስ ቁርባን ለመቀበል ወደ ቤተክርስቲያን በሚኬድባቸው ዕለታት፣ በጾምና በሰንበት፣ በበዓላት ወቅት ወንድና ሴት ግንኙነት ክልክል ነው። /ዘፀ 19፡15፣ 1ቆሮ 7፡5-7/ (ለባለትዳር ብቻ ነው! ያላገባማ በየትኛውም ጊዜ ከጋብቻ በፊት አይፈቀድም)
፦ነውር ያለበት ወደ ቤተክርስቲያን አይገባም። /ፍ.ነገ 13/
፦ሴት ልጅ ወር አበባዋ ሲመጣ ለ7 ቀን፣ ስትወልድ ወንድ ከወለደች እስከ 40 ቀን፣ ሴት ከወለደች እስከ 80 ቀን ወደ ቤተመቅደስ መግባት አይፈቀድም። (ዘሌ 12፡1__፣ ዘሌ 15፡19-28፣ ፍ.ነገ 6፣ ዘኒቂያ 29)
፦ወንድም ቢሆን ከአፉ ወይም ከአፍንጫው የሚወጣ ፈሳሽ ፣ነስር ሲኖርበት ወደ ቤተ መቅደስ አይገባም! ይህም ቤተመቅደሱን ስለሚያረክስ ወይም ለሌላ #ሳይሆን በቤተ መቅደስ ውስጥ የክርስቶስ ደም ብቻ መፈተት ስላለበት ነው።
፦ወንድ ልጅ ሕልመ ሌሊት ከመታው(ህልመ ዝኔት ካየ(ስጋዊ ህልም ካየ) በዕለቱ ወደ ቤተ መቅደስ አይገባም። (ዘሌ 15፡2)
፦ጠዋትና ማታ ቤተክርስቲያን ለመሳለም መትጋት ያስፈልጋል። (ምሳ 8፡34)
፦ወደ ቤተክርስቲያን ሲገባ በቅፅረ ቤተክርስቲያን በር ላይ ሲደርሱ መሳለም ይገባል (መዝ 28፡2፣ መዝ 95፡9፣ ኤር 26፡2፣ ሕዝ 46፡3)
፦ወደ ቤተክርስቲያን (ቤተመቅደስ) ሲገቡ ጫማን አውልቆ ወገብን ታጥቆ አደግድጎ መግባት ይገባል። (ዘፀ 3፡5-6 ፣ ሐዋ 7፡33፣ ኢያሱ 5፡15፣ ፍ.ነገ 12)
፦በቤተክርስቲያን ውስጥ ተስለው የሚገኙ ቅዱሳን ሥዕላትን እጅ መንሳትና መስገድ ይገባል።
፦በቤተክርስቲያን ውስጥ መሳቅ፣ ስለ ዓለማዊ ነገር መነጋገር ክልክል ነው። /ዮሐንስ አፈወርቅ 19፡32 ፤ 48፤6 አቡሊዲስ 7/
፦አጭር፣ ያደፈ፣ የሰውነት ቅርጽን የሚያሳይ ልብስ ለብሶ ወደ ቤተክርስቲያን መሔድ ፈጽሞ የተከለከለ ነው /ዘፀ 19፡10 ፣ ዮሐ.አፈ 4፡49-72/
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
@aleroe
"ምዕመናን በቤተመቅደስ ሊኖራቸው የሚገባ ሥርዓት
፦በቤተክርስቲያን ቅፅር ግቢ ገበያ ክልክል ነው። /ማቴ 21፡12 ዮሐ 2፡13-18 ፍትሀነገስት አንቀጽ 1/
፦በቤተክርስቲያን ቅፅር ግቢ ግብዣ ማድረግ፣መብላት፣መጠጣት ክልክል ነው። /የሎዶቅያ ሲኖዶስ (ዶቅ) 44 ፍ.ነገ 1/
፦ማንኛውም መብልም ሆነ መጠጥ ከቤተ መቅደስ 40 ክንድ(20 ሜትር) መራቅ አለበት! በመቅደሱ ሕብስቱና ወይኑ ብቻ ይፈተታልና። /ፍ.ነገ 1/
፦በታቦቱ ፊት ለመስገድ ወይም ለመፀለይ ወይም ለማስቀደስ ካልሆነ በቀር ማንም ወደ ቤተመቅደስ ገብቶ እንዲቀመጥ አይፈቀድም
፦ከካህን በስተቀር(ዲያቆናት፣ካህናት፣ቀሳውስት፣ጳጳሳት..) ከምዕመናን ወገን ወደ መቅደስ(ታቦቱ ያለበት) ገብቶ ሥጋ ወደሙን ሊቀበል(ሥጋ ወደሙን የሚያቀብሉ ካህናት ራሳቸው ሁሌም ከማቀበላቸው በፊት በመቅደስ ውስጥ ይቀበላሉ) ታቦቱን ሊጠጋ አይገባም /ፍ.ነገ 1፣ ቀኖና አብሉዲስ ፣ኢያሱ 3፡4/
፦ሴቶች ወደመቅደስ (ታቦቱ ያለበት) እንዲገቡና እንዲፀልዩ አልተፈቀደም። /የሎዶቅያ ሲኖዶስ(ዶቅ) 44፣ ፍ.ነገ 1/
፦ከቤተ ክርስቲያን አንዴ ለአገልግሎት ተመርጦ የገባውንና የተቀደሰውን ንዋየ ቅድሳት እንደገና ወደውጭ አውጥቶ መጠቀም አይገባም። /ፍ.ነገ 1፣ 1ቀለሚንጦስ (ረስጣ) 28/
፦ያላመኑ፣ ያልተጠመቁ፣ ተወግዘው የተለዩ ወደ ቤተክርስቲያን እንዳይገቡ ተከልክሏል። /ፍ.ነገ 1፣ ድድስቅሊያ (ድስቅ) 12/
፦ለፀሎትና ቅዱስ ቁርባን ለመቀበል ወደ ቤተክርስቲያን በሚኬድባቸው ዕለታት፣ በጾምና በሰንበት፣ በበዓላት ወቅት ወንድና ሴት ግንኙነት ክልክል ነው። /ዘፀ 19፡15፣ 1ቆሮ 7፡5-7/ (ለባለትዳር ብቻ ነው! ያላገባማ በየትኛውም ጊዜ ከጋብቻ በፊት አይፈቀድም)
፦ነውር ያለበት ወደ ቤተክርስቲያን አይገባም። /ፍ.ነገ 13/
፦ሴት ልጅ ወር አበባዋ ሲመጣ ለ7 ቀን፣ ስትወልድ ወንድ ከወለደች እስከ 40 ቀን፣ ሴት ከወለደች እስከ 80 ቀን ወደ ቤተመቅደስ መግባት አይፈቀድም። (ዘሌ 12፡1__፣ ዘሌ 15፡19-28፣ ፍ.ነገ 6፣ ዘኒቂያ 29)
፦ወንድም ቢሆን ከአፉ ወይም ከአፍንጫው የሚወጣ ፈሳሽ ፣ነስር ሲኖርበት ወደ ቤተ መቅደስ አይገባም! ይህም ቤተመቅደሱን ስለሚያረክስ ወይም ለሌላ #ሳይሆን በቤተ መቅደስ ውስጥ የክርስቶስ ደም ብቻ መፈተት ስላለበት ነው።
፦ወንድ ልጅ ሕልመ ሌሊት ከመታው(ህልመ ዝኔት ካየ(ስጋዊ ህልም ካየ) በዕለቱ ወደ ቤተ መቅደስ አይገባም። (ዘሌ 15፡2)
፦ጠዋትና ማታ ቤተክርስቲያን ለመሳለም መትጋት ያስፈልጋል። (ምሳ 8፡34)
፦ወደ ቤተክርስቲያን ሲገባ በቅፅረ ቤተክርስቲያን በር ላይ ሲደርሱ መሳለም ይገባል (መዝ 28፡2፣ መዝ 95፡9፣ ኤር 26፡2፣ ሕዝ 46፡3)
፦ወደ ቤተክርስቲያን (ቤተመቅደስ) ሲገቡ ጫማን አውልቆ ወገብን ታጥቆ አደግድጎ መግባት ይገባል። (ዘፀ 3፡5-6 ፣ ሐዋ 7፡33፣ ኢያሱ 5፡15፣ ፍ.ነገ 12)
፦በቤተክርስቲያን ውስጥ ተስለው የሚገኙ ቅዱሳን ሥዕላትን እጅ መንሳትና መስገድ ይገባል።
፦በቤተክርስቲያን ውስጥ መሳቅ፣ ስለ ዓለማዊ ነገር መነጋገር ክልክል ነው። /ዮሐንስ አፈወርቅ 19፡32 ፤ 48፤6 አቡሊዲስ 7/
፦አጭር፣ ያደፈ፣ የሰውነት ቅርጽን የሚያሳይ ልብስ ለብሶ ወደ ቤተክርስቲያን መሔድ ፈጽሞ የተከለከለ ነው /ዘፀ 19፡10 ፣ ዮሐ.አፈ 4፡49-72/
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
@aleroe
ኤልሮኢ:
እንዴት ብትወደኝ ነው
እንዴት ብትወደኝ ነው የማትተወኝ (2)
ትዕግስትህን ሳስብ እጅግ ደነቀኝ(2)
እኔን ያዘልክበት ትክሻህ ሰፊ ነው
አእምሮዬም ልቤም አይችልም ሊለካው
ሞት የሚገባውን የስራዬን ብዛት
አይተህ እንዳላየ ተውከው በቸርነት(2)
ድንቅ ስጦታ ነው መልሰህ የሰጠኸኝ
ለኔ የወሰድኩት የማይገባኝ
ፍቅርህ ከሰንሰለት እጅግ ይበረታል
ዓመፀኛው ታዞ ያገለግልሀል(2)
ለበደለ በደል ላጠፋ ጥፋት
ይህን ነበር የማውቀው በዓለም ስርዓት
ያንተ ግን ይደንቃል ገዛኸኝ በምህረት
ፊቴ ትቆማለህ ሁሌ በቸርነት
ያፈቀረን አምላክ ጨክኖ ቢበድል
በፀፀት ይቀጣል በሂሊና ቁስል
ዓላማህ በኔ ላይ ፍቅር ስለሆነ
ህግህ ሊፈርድብኝ አንዴም አልጨከነ
#ሊቀ ዲያቆን ወንደሰን በቀለ
@aleroe
እንዴት ብትወደኝ ነው
እንዴት ብትወደኝ ነው የማትተወኝ (2)
ትዕግስትህን ሳስብ እጅግ ደነቀኝ(2)
እኔን ያዘልክበት ትክሻህ ሰፊ ነው
አእምሮዬም ልቤም አይችልም ሊለካው
ሞት የሚገባውን የስራዬን ብዛት
አይተህ እንዳላየ ተውከው በቸርነት(2)
ድንቅ ስጦታ ነው መልሰህ የሰጠኸኝ
ለኔ የወሰድኩት የማይገባኝ
ፍቅርህ ከሰንሰለት እጅግ ይበረታል
ዓመፀኛው ታዞ ያገለግልሀል(2)
ለበደለ በደል ላጠፋ ጥፋት
ይህን ነበር የማውቀው በዓለም ስርዓት
ያንተ ግን ይደንቃል ገዛኸኝ በምህረት
ፊቴ ትቆማለህ ሁሌ በቸርነት
ያፈቀረን አምላክ ጨክኖ ቢበድል
በፀፀት ይቀጣል በሂሊና ቁስል
ዓላማህ በኔ ላይ ፍቅር ስለሆነ
ህግህ ሊፈርድብኝ አንዴም አልጨከነ
#ሊቀ ዲያቆን ወንደሰን በቀለ
@aleroe
ኤልሮኢ:
11/09/11
#በዕለቱ_ቅዳሴ_ሰዓት_የሚነበ_መልዕክታት_ወንጌልና_ምስባክ፡፡
ዲ/ን 1ቆሮ 5÷6-ፍ.ም
ን/ዲ 1ጴጥ 3፥15- ፍ.ም
ን/ካ ግብ፡ሐዋ 3፥12 ፍ.ም
፡#የዕለቱ_ምስባክ
መዝ 3÷5-ፍፃ
አንሰ ሰከብኩ ወኖምኩ
ወተንሣይኩ እስመ ዘእግዚአብሔር አንሥአኒ
ኢይፈርህ እምአእላፍ አሕዛብ
#የዕለቱ ወንጌል፦
ማቴ 26፥12- ፍፃ
ቅዳሴ፦ ዘዮሐንስ አፈወርቅ
@aleroe
11/09/11
#በዕለቱ_ቅዳሴ_ሰዓት_የሚነበ_መልዕክታት_ወንጌልና_ምስባክ፡፡
ዲ/ን 1ቆሮ 5÷6-ፍ.ም
ን/ዲ 1ጴጥ 3፥15- ፍ.ም
ን/ካ ግብ፡ሐዋ 3፥12 ፍ.ም
፡#የዕለቱ_ምስባክ
መዝ 3÷5-ፍፃ
አንሰ ሰከብኩ ወኖምኩ
ወተንሣይኩ እስመ ዘእግዚአብሔር አንሥአኒ
ኢይፈርህ እምአእላፍ አሕዛብ
#የዕለቱ ወንጌል፦
ማቴ 26፥12- ፍፃ
ቅዳሴ፦ ዘዮሐንስ አፈወርቅ
@aleroe
"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
#ከሳሽ_ዕድፉን_ሳያይ
ስታመነዝር አገኘናት፣
ብለው አካልበዋት፣
ከጌታ ፊት እያቻኮሉ፣
ከእግሩ ሥር አምጥተዋት ጣሉ፡፡
ምን ትላለህ ? ስለዚች ሴት፣
ይዘናታል በማመንዘር ኃጢአት፣
ሙሴ እንደው በሕጉ፣
ብሎናል ወግራችሁ ግደሉ፣
አንተስ ምን ትላለህ ?
ይሰማ እስኪ ፍርድህ … ?
ይላሉ ከሳሾች ….
ወንዱን አስመልጠው ፣ ሴቷን አሳዳጆች፤
እውነት አንሻፋፊ ፣ ግማሽ ምስክሮች፤
ኢየሱስ መለሰ ….
ጐንበስ ብሎ ከምድር ፣ አንዳች እየጻፈ፤
ከʻናንተ መካከል ፣ ነውሯ ያላገኘው፤
ድንጋይን ከሯሷ ፣ አሁኑ ይጫነው፤
ብሎ ሳያበቃ ፣ ቀና ሲል ካለበት፤
ከʻርሷ በቀር የለም ፣ ከተከሳሿ ሴት ፤
ለካስ ሁሉም ጥሎ ፣ ከዚያ ሥፍራ የጠፋው፤
ከʻርሷ ጋር ተጋድሞ ፣ ዕድፉን ባያየው ነው፡፡
ያመነች ግን እርሷ ፣ ተከናወነላት ፤
መንገዷን ቀየረች ፣ ከሞት ወደ ሕይወት፡፡
__________________
@aleroe
#ከሳሽ_ዕድፉን_ሳያይ
ስታመነዝር አገኘናት፣
ብለው አካልበዋት፣
ከጌታ ፊት እያቻኮሉ፣
ከእግሩ ሥር አምጥተዋት ጣሉ፡፡
ምን ትላለህ ? ስለዚች ሴት፣
ይዘናታል በማመንዘር ኃጢአት፣
ሙሴ እንደው በሕጉ፣
ብሎናል ወግራችሁ ግደሉ፣
አንተስ ምን ትላለህ ?
ይሰማ እስኪ ፍርድህ … ?
ይላሉ ከሳሾች ….
ወንዱን አስመልጠው ፣ ሴቷን አሳዳጆች፤
እውነት አንሻፋፊ ፣ ግማሽ ምስክሮች፤
ኢየሱስ መለሰ ….
ጐንበስ ብሎ ከምድር ፣ አንዳች እየጻፈ፤
ከʻናንተ መካከል ፣ ነውሯ ያላገኘው፤
ድንጋይን ከሯሷ ፣ አሁኑ ይጫነው፤
ብሎ ሳያበቃ ፣ ቀና ሲል ካለበት፤
ከʻርሷ በቀር የለም ፣ ከተከሳሿ ሴት ፤
ለካስ ሁሉም ጥሎ ፣ ከዚያ ሥፍራ የጠፋው፤
ከʻርሷ ጋር ተጋድሞ ፣ ዕድፉን ባያየው ነው፡፡
ያመነች ግን እርሷ ፣ ተከናወነላት ፤
መንገዷን ቀየረች ፣ ከሞት ወደ ሕይወት፡፡
__________________
@aleroe
"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
………✍የእርሻ መሬት ወርሰው በጋራ
የሚሰሩ ሁለት ወንድማማቾች ነበሩ፡፡ አንድኛው ትዳር መስርቶ
ትልቅ ቤተሰብ ሲኖረው ሁለተኛው ግን ብቻውን ነበር የሚኖረው፡፡
ከዕለታት አንድ ቀን ወንድማማቾቹ ከቤተሰባቸው የወረሱትን ሀብትና ንብረት በመከፋፈል በየግላቸው ለመስራት ይስማማሉ፡፡ ያለውንም ሀብት እኩል ተከፋፍለው የየግላቸው ኑሮ ይጀምራሉ፡፡ ወድያውኑ ግን ብቻውን የሚኖረው ወንድሙ ከራሱ ጋር መነጋገር ይጀምራል “ያለውን ሀብትና ትርፍ እኩል መከፋፈላችን አግባብ አልነበረም፡፡ እኔ ብቻየን ነው የምኖረው የሚያስፈልገኝ ነገር በጣም ትንሽ ነው፡፡ እርሱ ግን
ብዙ የቤተሰብ ሀላፊነት አለበት” በማለት ያስባል፡፡ እናም በጎተራው ካለው እህል አንድ ጆንያ የሚሆነውን ሁል ግዜ ማታ
ማታ እየተደበቀ ወንድሙ ጎተራ ውስጥ ማስገባት ይጀምራል፡፡
በተመሳሳይ ግዜ ሚስትና ልጆች ያሉት ወንድምም በተመሳሳይ ሁኔታ ያስባል “ይህንን ሀብት እኩል መካፈል አልነበረብንም፡፡ እኔኮ ትዳር አለኝ፡፡ ሚስቴና ልጆቼ ሁል ግዜ ከጎኔ በመሆናቸው ወደፊት በደንብ ይንከባከቡኛል፡፡ወንድሜ ግን ብቸኛ ነው፡፡ ወደፊት አጠገቡ ሆኖ የሚንከባከበው እንኳ የለውም” ሲል ያስባል፡፡ እርሱም እንደዚያኘው ወንድም በጎተራ ካለው እህል አንድ ጆንያ የሚሆነውን ሁል ግዜ ማታ ማታ እየተደበቀ ወንድሙ ጎተራ ውስጥ ማስገባት ይጀምራል፡፡ ወንድማማቾቹ በዚህ ሁኔታ ለብዙ ግዜ ኖሩ፡፡ ከብዙ ግዜ ብኋላ ግን ሁለቱንም አንድ ነገር ያስገርማቸው ጀመር፡፡ በጎተራቸው ውስጥ ያለው እህል መጠን እየቀነሰ አለመሄዱ ግራ ያጋባቸዋል፡፡ ሁለቱም የገጠማቸውን ያልተለመደ ነገር ለመመርመር በየግላቸው እየጣሩ ሳለ ከእለታት አንድ ቀን ሌሊት ላይ የተለመደውን ተግባራቸውን ለመፈጸም እህል የተሞላበት ከረጢት እንደተሸከሙ በድንገት ተገናኙ ። ምንም አይነት ቃላት ሳይለዋወጡ ሸክማቸውን መሬት ላይ በመጣል በፍቅር ተቃቅፈው አለቀሱ
*
የመተሳሰብ ፍቅር… በአይምሮህ አስበህ በአንደበትህ የምታወጣው ቃል ሳይሆን፣ በልብህ የሚንፈራገጥ የማይወለድ ፅንስ ነው።
*
የአንድ አገር ልጆች ነን!
የኢትዮጽያ ልጆች!
@aleroe
………✍የእርሻ መሬት ወርሰው በጋራ
የሚሰሩ ሁለት ወንድማማቾች ነበሩ፡፡ አንድኛው ትዳር መስርቶ
ትልቅ ቤተሰብ ሲኖረው ሁለተኛው ግን ብቻውን ነበር የሚኖረው፡፡
ከዕለታት አንድ ቀን ወንድማማቾቹ ከቤተሰባቸው የወረሱትን ሀብትና ንብረት በመከፋፈል በየግላቸው ለመስራት ይስማማሉ፡፡ ያለውንም ሀብት እኩል ተከፋፍለው የየግላቸው ኑሮ ይጀምራሉ፡፡ ወድያውኑ ግን ብቻውን የሚኖረው ወንድሙ ከራሱ ጋር መነጋገር ይጀምራል “ያለውን ሀብትና ትርፍ እኩል መከፋፈላችን አግባብ አልነበረም፡፡ እኔ ብቻየን ነው የምኖረው የሚያስፈልገኝ ነገር በጣም ትንሽ ነው፡፡ እርሱ ግን
ብዙ የቤተሰብ ሀላፊነት አለበት” በማለት ያስባል፡፡ እናም በጎተራው ካለው እህል አንድ ጆንያ የሚሆነውን ሁል ግዜ ማታ
ማታ እየተደበቀ ወንድሙ ጎተራ ውስጥ ማስገባት ይጀምራል፡፡
በተመሳሳይ ግዜ ሚስትና ልጆች ያሉት ወንድምም በተመሳሳይ ሁኔታ ያስባል “ይህንን ሀብት እኩል መካፈል አልነበረብንም፡፡ እኔኮ ትዳር አለኝ፡፡ ሚስቴና ልጆቼ ሁል ግዜ ከጎኔ በመሆናቸው ወደፊት በደንብ ይንከባከቡኛል፡፡ወንድሜ ግን ብቸኛ ነው፡፡ ወደፊት አጠገቡ ሆኖ የሚንከባከበው እንኳ የለውም” ሲል ያስባል፡፡ እርሱም እንደዚያኘው ወንድም በጎተራ ካለው እህል አንድ ጆንያ የሚሆነውን ሁል ግዜ ማታ ማታ እየተደበቀ ወንድሙ ጎተራ ውስጥ ማስገባት ይጀምራል፡፡ ወንድማማቾቹ በዚህ ሁኔታ ለብዙ ግዜ ኖሩ፡፡ ከብዙ ግዜ ብኋላ ግን ሁለቱንም አንድ ነገር ያስገርማቸው ጀመር፡፡ በጎተራቸው ውስጥ ያለው እህል መጠን እየቀነሰ አለመሄዱ ግራ ያጋባቸዋል፡፡ ሁለቱም የገጠማቸውን ያልተለመደ ነገር ለመመርመር በየግላቸው እየጣሩ ሳለ ከእለታት አንድ ቀን ሌሊት ላይ የተለመደውን ተግባራቸውን ለመፈጸም እህል የተሞላበት ከረጢት እንደተሸከሙ በድንገት ተገናኙ ። ምንም አይነት ቃላት ሳይለዋወጡ ሸክማቸውን መሬት ላይ በመጣል በፍቅር ተቃቅፈው አለቀሱ
*
የመተሳሰብ ፍቅር… በአይምሮህ አስበህ በአንደበትህ የምታወጣው ቃል ሳይሆን፣ በልብህ የሚንፈራገጥ የማይወለድ ፅንስ ነው።
*
የአንድ አገር ልጆች ነን!
የኢትዮጽያ ልጆች!
@aleroe
"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
# ትሕትና + ትእግስት + ተስፋ + ፅናት + ፍቅር + እምነት + አምልኮት + ምግባር=>ስኬት!!
~አንዲት ስጋ የምትጠብስ ሴት ስጋውን መጥበሻው ላይ ትጥደውና ስጋውን ታገላብጠዋለች ።ከዛ መብሰል አለመብሰሉን ለማረጋገጥ በሹካ ወጋ ወጋ አድርጋ ታየዋለች። ከበሰለ ታወርድና ለመዓድ ገበታ ላይ ታቀርበዋለች።ልብ በሉ....
~ፈጣሪም እኛን ይለዉጥናል እውቀት ይሰጡናል ያበስሉናል ብሎ ባሰባቸው በተለያዩ ነገሮች ላይ ይጥደንና ጤና ማጣት፣ስራ ማጣት፣ወዳጅ ማጣት፣ የህይወት አጋር ማጣት፣ገንዘብ ማጣት፣ፍትሕ ማጣት፣ተስፋ ማጣት፣ነገሮችን አለመሳካት፣ሰርቶ መና፣መከዳት፣መናቅ፣ወ ... በተባሉ ሹካዎች ወጋ ወጋ አድርጎ መብሰል አለመብሰላችንን ያረጋግጣል።
~ችግር ውስጥ ሆነን ካመሰገንን በስለናል ካማረርን ግን ይቀረናልና፤አንዳንዴ በተለያዩ ችግር ውስጥ ጥዶ ያገላብጠናል።
~አንድ ካሜራ ማን እኛን ፎቶ ከማንሳቱ በፊት ፈገግ በል ቀና በል ትንሽ ወደ ቀኝ ምናምን እያለ አስቀድሞ ያስተካክለናል ከዛ ያነሳናል። ፈጣሪም እኛን በተለያዩ ችግሮች ውስጥ እያስገባ ነው ህይወታችንን ሚያስተካክለው ምክንያትም የደፈረሰ ህይወታችን መጥራት ስላለበትና ጥርት ለማድረግ።
~መከራ ፈጣሪ እኛን ወደሱ የሚጎትትበት ገመድ ነው። ዳይመንድን ውድ ካደረጉት ነገሮች መካከል አንዱ አቆራረጡ ነው።ዳይመንድን የምናውቀውን ቅርፁን ያስያዘውና ከተለያየ አቅጣጫ እንዲያንፀባርቅ ያደረገው አቆራረጡ ነው ይላሉ። እኛንም ዛሬ እየቆረጡንና እያስጨነቁን ያሉ ሳንቋቋማቸው ቀርተን እያማረርንባቸው ያለን ችግሮቻችንን ነገ እኛን ዉድና የሚያበራ ማንነት ባለቤት የሚያደርጉን ናቸው ።
~ማዕበል ሲነሳና ባህሩን ሲያማስለው ሁሉም እንስሶች ይሸሻሉ።ንስር አሞራው ግን በመሀሉ ገብቶ ዓሳ ይዞ ይወጣል።
~ ወዳጄ ሆይ እንደ ንስር አሞራው በችግር ውስጥ ብትሆንም እራስህን አንፅ። ሸክላ የምትሰራ ሴት እንኳን ሸክላዋን ሰርታ ስትጨርስ እንዲጠነክርላት በእሳት ነው ምትጠብሰው።ዛሬ የሚጠብሱህ ችግሮችና የህይወት መሰናክሎች ከፀናህ ማንነትህን ነው የሚያጠነክሩልህ።
~ ስለዚህ ስለሆነው ስለሚሆነው እየሆነ ስላለው ፣ ስለተደረግልህ ስላልተደረገልህ ፣ ስለ ሰጠህ ስለ ነፈገህ ነገር ሁሉ እሱን አመስግነው።
~ # እንዲ_በለው ፦
"ደስታንም ሆነ መከራን ብትሰጠኝ አመሰግንሀለሁ፤ ከኔ ይልቅ አንተ ነህና ለእኔ ምትቀርበው።ስለዚህም ጌታ ሆይ በመንገዴና በህይወቴ ሁሉ ፈቃድህ እንጂ ፈቃዴ አይሁን።"
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር አሜን።
@aleroe
# ትሕትና + ትእግስት + ተስፋ + ፅናት + ፍቅር + እምነት + አምልኮት + ምግባር=>ስኬት!!
~አንዲት ስጋ የምትጠብስ ሴት ስጋውን መጥበሻው ላይ ትጥደውና ስጋውን ታገላብጠዋለች ።ከዛ መብሰል አለመብሰሉን ለማረጋገጥ በሹካ ወጋ ወጋ አድርጋ ታየዋለች። ከበሰለ ታወርድና ለመዓድ ገበታ ላይ ታቀርበዋለች።ልብ በሉ....
~ፈጣሪም እኛን ይለዉጥናል እውቀት ይሰጡናል ያበስሉናል ብሎ ባሰባቸው በተለያዩ ነገሮች ላይ ይጥደንና ጤና ማጣት፣ስራ ማጣት፣ወዳጅ ማጣት፣ የህይወት አጋር ማጣት፣ገንዘብ ማጣት፣ፍትሕ ማጣት፣ተስፋ ማጣት፣ነገሮችን አለመሳካት፣ሰርቶ መና፣መከዳት፣መናቅ፣ወ ... በተባሉ ሹካዎች ወጋ ወጋ አድርጎ መብሰል አለመብሰላችንን ያረጋግጣል።
~ችግር ውስጥ ሆነን ካመሰገንን በስለናል ካማረርን ግን ይቀረናልና፤አንዳንዴ በተለያዩ ችግር ውስጥ ጥዶ ያገላብጠናል።
~አንድ ካሜራ ማን እኛን ፎቶ ከማንሳቱ በፊት ፈገግ በል ቀና በል ትንሽ ወደ ቀኝ ምናምን እያለ አስቀድሞ ያስተካክለናል ከዛ ያነሳናል። ፈጣሪም እኛን በተለያዩ ችግሮች ውስጥ እያስገባ ነው ህይወታችንን ሚያስተካክለው ምክንያትም የደፈረሰ ህይወታችን መጥራት ስላለበትና ጥርት ለማድረግ።
~መከራ ፈጣሪ እኛን ወደሱ የሚጎትትበት ገመድ ነው። ዳይመንድን ውድ ካደረጉት ነገሮች መካከል አንዱ አቆራረጡ ነው።ዳይመንድን የምናውቀውን ቅርፁን ያስያዘውና ከተለያየ አቅጣጫ እንዲያንፀባርቅ ያደረገው አቆራረጡ ነው ይላሉ። እኛንም ዛሬ እየቆረጡንና እያስጨነቁን ያሉ ሳንቋቋማቸው ቀርተን እያማረርንባቸው ያለን ችግሮቻችንን ነገ እኛን ዉድና የሚያበራ ማንነት ባለቤት የሚያደርጉን ናቸው ።
~ማዕበል ሲነሳና ባህሩን ሲያማስለው ሁሉም እንስሶች ይሸሻሉ።ንስር አሞራው ግን በመሀሉ ገብቶ ዓሳ ይዞ ይወጣል።
~ ወዳጄ ሆይ እንደ ንስር አሞራው በችግር ውስጥ ብትሆንም እራስህን አንፅ። ሸክላ የምትሰራ ሴት እንኳን ሸክላዋን ሰርታ ስትጨርስ እንዲጠነክርላት በእሳት ነው ምትጠብሰው።ዛሬ የሚጠብሱህ ችግሮችና የህይወት መሰናክሎች ከፀናህ ማንነትህን ነው የሚያጠነክሩልህ።
~ ስለዚህ ስለሆነው ስለሚሆነው እየሆነ ስላለው ፣ ስለተደረግልህ ስላልተደረገልህ ፣ ስለ ሰጠህ ስለ ነፈገህ ነገር ሁሉ እሱን አመስግነው።
~ # እንዲ_በለው ፦
"ደስታንም ሆነ መከራን ብትሰጠኝ አመሰግንሀለሁ፤ ከኔ ይልቅ አንተ ነህና ለእኔ ምትቀርበው።ስለዚህም ጌታ ሆይ በመንገዴና በህይወቴ ሁሉ ፈቃድህ እንጂ ፈቃዴ አይሁን።"
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር አሜን።
@aleroe
ኤልሮኢ:
በከበረው_ደምህ
በከበረው ደምህ በአማኑኤል ስምህ
ከብሬያለሁና ልሰዋ ምስጋና/2/
በራስ ቅል ላይ ጨርሰኸው የኔን ስራ
ከፍ አደረከኝ ዝቅ ብለህ ሊጦስጥራ
መኖር ጀመርኩ ስትሞትልኝ መድኀኒቴ
ክበርልኝ ለዘለዓለም ቸር አባቴ
ከቀቄዳር ምንጭ እንቁ ከፍለው የማይገዙት
ያንተ መውደድ የተሰጠኝ ከሰማያት
ማን ይጠማል የዘለዓለም ምንጭ እያለ
እያረካኝ የተጠማ አንድ እርሱ ነው
ለብሰህ ቆምክ ቀራንዮ ከለሜዳ
ጨለማዬን ልትገፈው ያንን ፍዳ
ከዚህ በላይ የት ይገኛል የሚያፈቅር
በትህትና የሚሔድ እስከ መቃብር
የቱ ግብሬ ቢማርክህ ብትወደው ነው
የኔን መስቀል ተሸክመህ የደከምከው
ያሸነፈኝ ተሸነፈ በአንተ ችንካር
ተረገጠ የአሳዳጄ የእዳ ጦማር
@aleroe
በከበረው_ደምህ
በከበረው ደምህ በአማኑኤል ስምህ
ከብሬያለሁና ልሰዋ ምስጋና/2/
በራስ ቅል ላይ ጨርሰኸው የኔን ስራ
ከፍ አደረከኝ ዝቅ ብለህ ሊጦስጥራ
መኖር ጀመርኩ ስትሞትልኝ መድኀኒቴ
ክበርልኝ ለዘለዓለም ቸር አባቴ
ከቀቄዳር ምንጭ እንቁ ከፍለው የማይገዙት
ያንተ መውደድ የተሰጠኝ ከሰማያት
ማን ይጠማል የዘለዓለም ምንጭ እያለ
እያረካኝ የተጠማ አንድ እርሱ ነው
ለብሰህ ቆምክ ቀራንዮ ከለሜዳ
ጨለማዬን ልትገፈው ያንን ፍዳ
ከዚህ በላይ የት ይገኛል የሚያፈቅር
በትህትና የሚሔድ እስከ መቃብር
የቱ ግብሬ ቢማርክህ ብትወደው ነው
የኔን መስቀል ተሸክመህ የደከምከው
ያሸነፈኝ ተሸነፈ በአንተ ችንካር
ተረገጠ የአሳዳጄ የእዳ ጦማር
@aleroe
ኤልሮኢ:
ግንቦት_25 /09/2011
፶፩ እምትንሣኤ እስከ ዕርገት በትንሣኤ እሁድ መዝሙር ይትፌሣሕ፡፡
#ምስባክ
ወተንሥአ እግዚአብሔር ከመ ዘንቃህ እምንዋም
ወከመ ኀያል ወኅዳገ ወይን
ወቀተለ ፀሮ በድኅሬሁ፡፡
#ትርጉም
እግዚአብሔርም ከእንቅልፍ እንደ ሚነቃ ተነሣ
የወይን ስካር እንደ ተወው እንደ ኀይለኛም ሰው
ጠላቶቹንም በኋላቸው መታ፡፡
#መዝ_77:65-66
#ወንጌል
#ማቴዎስ_28:1-ፍጻሜ፡ወሠርክ ሰንበት ለጸቢሖ እሁድ"በሰንበትም ማታ ለእሁድ አጥቢያ ማርያም መግደላዊትና ሁለተኛዋ ማርያም መቃብሩን ሊያዩ መጡ፡፡.............
................................................ቀላውዴዎስ ቄሣር በነገሠ በመጀመሪያው ዓመት ጻፈው፡፡"
#ማርቆስ_16:1-ፍጻሜ፡ወሐለፈት ሰንበት"ሰንበትም ባለፈች ጊዜ ማርያም መግደላዊት የያዕቆብ እናት ማርያም ሰሎሜም መጥተው ሥጋዉን ሊቀቡ ሽቱ ገዙ፡፡.......................................................................................ቀላውዴዎስ ቄሣር በነገሠ በአራት ዓመት ነው፡፡"
#ሉቃስ_24:1-13፡ወበእሑድ ሰንበት"ከሳምንቱም በመጀመሪያዪቱ ቀን ያዘጋጁትን ሽቶ ይዘው እጅግ ማልደው ወደ መቃብሩ ሄዱ ሌሎች ሴቶችም አብረዋቸው ነበሩ፡፡....................
................................................ጴጥሮስም ተነሣ ወደ መቃብርም ፈጥኖ ሄደ ዝቅ ብሎም በተመለከተ ጊዜ በፍታውን ለብቻው ተቀምጦ አየ የሆነውን እያደነቀ ተመለሰ፡፡"
👉 @aleroe
ግንቦት_25 /09/2011
፶፩ እምትንሣኤ እስከ ዕርገት በትንሣኤ እሁድ መዝሙር ይትፌሣሕ፡፡
#ምስባክ
ወተንሥአ እግዚአብሔር ከመ ዘንቃህ እምንዋም
ወከመ ኀያል ወኅዳገ ወይን
ወቀተለ ፀሮ በድኅሬሁ፡፡
#ትርጉም
እግዚአብሔርም ከእንቅልፍ እንደ ሚነቃ ተነሣ
የወይን ስካር እንደ ተወው እንደ ኀይለኛም ሰው
ጠላቶቹንም በኋላቸው መታ፡፡
#መዝ_77:65-66
#ወንጌል
#ማቴዎስ_28:1-ፍጻሜ፡ወሠርክ ሰንበት ለጸቢሖ እሁድ"በሰንበትም ማታ ለእሁድ አጥቢያ ማርያም መግደላዊትና ሁለተኛዋ ማርያም መቃብሩን ሊያዩ መጡ፡፡.............
................................................ቀላውዴዎስ ቄሣር በነገሠ በመጀመሪያው ዓመት ጻፈው፡፡"
#ማርቆስ_16:1-ፍጻሜ፡ወሐለፈት ሰንበት"ሰንበትም ባለፈች ጊዜ ማርያም መግደላዊት የያዕቆብ እናት ማርያም ሰሎሜም መጥተው ሥጋዉን ሊቀቡ ሽቱ ገዙ፡፡.......................................................................................ቀላውዴዎስ ቄሣር በነገሠ በአራት ዓመት ነው፡፡"
#ሉቃስ_24:1-13፡ወበእሑድ ሰንበት"ከሳምንቱም በመጀመሪያዪቱ ቀን ያዘጋጁትን ሽቶ ይዘው እጅግ ማልደው ወደ መቃብሩ ሄዱ ሌሎች ሴቶችም አብረዋቸው ነበሩ፡፡....................
................................................ጴጥሮስም ተነሣ ወደ መቃብርም ፈጥኖ ሄደ ዝቅ ብሎም በተመለከተ ጊዜ በፍታውን ለብቻው ተቀምጦ አየ የሆነውን እያደነቀ ተመለሰ፡፡"
👉 @aleroe
"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
………✍ሁለት ሰዎች በአንድ ጉዳይ አብረው ይፀልያሉ አንደኛው ፀሎቱ ተመለሰለት አንደኛው ሳይመለስለት ቀረ። በዚህ ጊዜ ፀሎቱ ያልተመለሰለት ሰው "ጌታ ሆይ ሁለታችንም እኩል ፀልየን ለእርሱ ሰጥተኸው ለእኔ ከለከልኝ ለምንድ ነው?" አለው። እግዚዘብሔርም "ለእርሱ ባልሰጠው ይጠፋል፣ ላንተ ከሰጠሁህ ደግሞ ትጠፋለህ" አለው ይባላል።
እግዚአብሔር ከራሳችን በላይ እኛን ያውቀናል። ለአንዳችን በመስጠት፣ አንዳችንን በመከልከል ዕድሜያችንን ያረዝመዋል። መስጠቱም መንሳቱም ሁለቱም በፍቅር ነውና በልመናችን በፀሎታችን የአንተ ፈቃድ ይሁንልን ማለት ተገቢ ነው። ስለሁሉም የመድኃኔዓለም ስም የተመሰገነ ይሁን። አሜን!!
እንኳን ለመድኃኔዓለም ወርሀዊ በዓል
በሰላም አደረሳችሁ!!
@aleroe
………✍ሁለት ሰዎች በአንድ ጉዳይ አብረው ይፀልያሉ አንደኛው ፀሎቱ ተመለሰለት አንደኛው ሳይመለስለት ቀረ። በዚህ ጊዜ ፀሎቱ ያልተመለሰለት ሰው "ጌታ ሆይ ሁለታችንም እኩል ፀልየን ለእርሱ ሰጥተኸው ለእኔ ከለከልኝ ለምንድ ነው?" አለው። እግዚዘብሔርም "ለእርሱ ባልሰጠው ይጠፋል፣ ላንተ ከሰጠሁህ ደግሞ ትጠፋለህ" አለው ይባላል።
እግዚአብሔር ከራሳችን በላይ እኛን ያውቀናል። ለአንዳችን በመስጠት፣ አንዳችንን በመከልከል ዕድሜያችንን ያረዝመዋል። መስጠቱም መንሳቱም ሁለቱም በፍቅር ነውና በልመናችን በፀሎታችን የአንተ ፈቃድ ይሁንልን ማለት ተገቢ ነው። ስለሁሉም የመድኃኔዓለም ስም የተመሰገነ ይሁን። አሜን!!
እንኳን ለመድኃኔዓለም ወርሀዊ በዓል
በሰላም አደረሳችሁ!!
@aleroe
"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
ይህን ያውቁ ሮሯል!!!
በተለምዶ ‹‹ አርባ አራቱ ታቦት›› እያልን የምንጠራቸው አብያተ ክርስቲያናት ያሉት በጐንደር ከተማ ሲሆን ስማቸውም የሚከተለው ነው፡፡
1. ፊት ሚካኤል
2. ፊት አቦ
3. አደባባይ ኢየሱስ
4. ግምጃ ቤት ማርያም
5. እልፍኝ ጊዮርጊስ
6. መድኃኔዓለም
7. ቅዱስ ገብርኤል
8. ጠዳ እግዚአብሔር አብ
9. አባ እንጦንዮስ
10. ደብረ ብርሃን ሥላሴ
11. አደባባይ ተክለሃይማኖት
12. ሠለስቱ ምእት
13. ልደታ ለማርያም
14. አጣጣሚ ሚካኤል
15. አቡነ ኤውስጣቴዎስ
16. ቅዱስ ሩፋኤል
17. ደፈጫ ኪዳነ ምሕረት
18. ቁስቋም ደብረ ፀሐይ
19. መጥምቁ ዮሐንስ
20. በኣታ ለማርያም
21. ቅዱስ ቂርቆስ
22. ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ
23. አባ ጃሌ ተ/ሃይማኖት
24. ፈንጠር ልደታ
25. ደብረ ምጥማቅ ማርያም
26. አባ ዐቢየ እግዚእ
27. ቅዱስ ፋሲለደስ
28. ሐዋርያት
29. ቀሃ ኢየሱስ
30. አርባዕቱ እንስሳት
31. ጎንደሮች ጊዮርጊስ
32. ጎንደሮች ማርያም
33. አበራ ጊዮርጊስ
34. ብላጅግ ቅዱስ ሚካሌል
35. አባ ሳሙኤል
36. አይራ ሚካኤል
37. ጓራ ዮሐንስ
38. ወረንግቦ ጊዮርጊስ
39. አሮጌ ልደታ
40. አዘዞ ተ/ሃይማኖት
41. ምንዝሮ ተ/ሀይማኖት
42. ሰራራ ማርያም
43. ዳሞት ጊዮርጊስ
44. ጫጭቁና ማርያም
በቃል ያለ ይረሳል በ………………………
@aleroe
ይህን ያውቁ ሮሯል!!!
በተለምዶ ‹‹ አርባ አራቱ ታቦት›› እያልን የምንጠራቸው አብያተ ክርስቲያናት ያሉት በጐንደር ከተማ ሲሆን ስማቸውም የሚከተለው ነው፡፡
1. ፊት ሚካኤል
2. ፊት አቦ
3. አደባባይ ኢየሱስ
4. ግምጃ ቤት ማርያም
5. እልፍኝ ጊዮርጊስ
6. መድኃኔዓለም
7. ቅዱስ ገብርኤል
8. ጠዳ እግዚአብሔር አብ
9. አባ እንጦንዮስ
10. ደብረ ብርሃን ሥላሴ
11. አደባባይ ተክለሃይማኖት
12. ሠለስቱ ምእት
13. ልደታ ለማርያም
14. አጣጣሚ ሚካኤል
15. አቡነ ኤውስጣቴዎስ
16. ቅዱስ ሩፋኤል
17. ደፈጫ ኪዳነ ምሕረት
18. ቁስቋም ደብረ ፀሐይ
19. መጥምቁ ዮሐንስ
20. በኣታ ለማርያም
21. ቅዱስ ቂርቆስ
22. ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ
23. አባ ጃሌ ተ/ሃይማኖት
24. ፈንጠር ልደታ
25. ደብረ ምጥማቅ ማርያም
26. አባ ዐቢየ እግዚእ
27. ቅዱስ ፋሲለደስ
28. ሐዋርያት
29. ቀሃ ኢየሱስ
30. አርባዕቱ እንስሳት
31. ጎንደሮች ጊዮርጊስ
32. ጎንደሮች ማርያም
33. አበራ ጊዮርጊስ
34. ብላጅግ ቅዱስ ሚካሌል
35. አባ ሳሙኤል
36. አይራ ሚካኤል
37. ጓራ ዮሐንስ
38. ወረንግቦ ጊዮርጊስ
39. አሮጌ ልደታ
40. አዘዞ ተ/ሃይማኖት
41. ምንዝሮ ተ/ሀይማኖት
42. ሰራራ ማርያም
43. ዳሞት ጊዮርጊስ
44. ጫጭቁና ማርያም
በቃል ያለ ይረሳል በ………………………
@aleroe
ኤልሮኢ:
02/10/11
#መዝሙር በሰንበት ዐርገ ሐመረ
#በዕለቱ_ቅዳሴ_ሰዓት_የሚነበ_መልዕክታት_ወንጌልና_ምስባክ፡፡
ዲ/ን ሮሜ10÷1-ፍ.ም
ን/ዲ 1ጴጥ 3÷15-ፍ.ም
ን/ካ ግብ፡ሐዋ 1÷1-12
፡#የዕለቱ_ምስባክ
መዝ 45÷5
ዐርገ እግዚአብሔር በይባቤ።
ወእግዚእነ በቃለ ቀርን።
ዘምሩ ለአምላክነ ዘምሩ።
#ትርጉም፦
እግዚአብሔር በዕልልታ ዐረገ
ጌታችን በመለከት ድምፅ ዐረገ
ዘምሩ ለአምላክችን ዘምሩ።
#ወንጌል
#ሉቃ 24÷45-ፍ ም
#ቅዳሴ
:-ዘዲዮስቆሮስ
@aleroe
02/10/11
#መዝሙር በሰንበት ዐርገ ሐመረ
#በዕለቱ_ቅዳሴ_ሰዓት_የሚነበ_መልዕክታት_ወንጌልና_ምስባክ፡፡
ዲ/ን ሮሜ10÷1-ፍ.ም
ን/ዲ 1ጴጥ 3÷15-ፍ.ም
ን/ካ ግብ፡ሐዋ 1÷1-12
፡#የዕለቱ_ምስባክ
መዝ 45÷5
ዐርገ እግዚአብሔር በይባቤ።
ወእግዚእነ በቃለ ቀርን።
ዘምሩ ለአምላክነ ዘምሩ።
#ትርጉም፦
እግዚአብሔር በዕልልታ ዐረገ
ጌታችን በመለከት ድምፅ ዐረገ
ዘምሩ ለአምላክችን ዘምሩ።
#ወንጌል
#ሉቃ 24÷45-ፍ ም
#ቅዳሴ
:-ዘዲዮስቆሮስ
@aleroe
"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:(ስነ ፅሁፍ)
ዳግም_ልደት
እሳት ወይስ ውሀ
ሀዘን ወይ ፍስሀ
አንዱን የግድ ምረጥ
ልብህ ባንዱ ይቁረጥ
ወይ ብረድ ወይ ተኩስ ፡በመሀል አትልፋ
ለብ ብለህ ካፉ ላይ፡ ውጭ እንዳትተፋ
ጨለማ ወይ ብርሀን
አንዱን ምረጥ ዝገን
ሞት ወይስ ህይወት
ሀሰት ወይስ እውነት
መዝሙር ወይስ ኮንሰርት
(አንዱን የግድ ምረጥ...)
ጣዖት ወይስ ታቦት
ሲዖል ወይስ ገነት
ይሄኔ አስተውለህ
አስበህ መርምረህ
ካላወክ ጠየቀህ
በውነት በቅንነት ፡ በበጎ ህሊና
አንዱን ምረጥና ፡ በንፁህ ልቦና
ተወለድ ወንድሜ ዳግም እንደገና ፡፡
@aleroe
ዳግም_ልደት
እሳት ወይስ ውሀ
ሀዘን ወይ ፍስሀ
አንዱን የግድ ምረጥ
ልብህ ባንዱ ይቁረጥ
ወይ ብረድ ወይ ተኩስ ፡በመሀል አትልፋ
ለብ ብለህ ካፉ ላይ፡ ውጭ እንዳትተፋ
ጨለማ ወይ ብርሀን
አንዱን ምረጥ ዝገን
ሞት ወይስ ህይወት
ሀሰት ወይስ እውነት
መዝሙር ወይስ ኮንሰርት
(አንዱን የግድ ምረጥ...)
ጣዖት ወይስ ታቦት
ሲዖል ወይስ ገነት
ይሄኔ አስተውለህ
አስበህ መርምረህ
ካላወክ ጠየቀህ
በውነት በቅንነት ፡ በበጎ ህሊና
አንዱን ምረጥና ፡ በንፁህ ልቦና
ተወለድ ወንድሜ ዳግም እንደገና ፡፡
@aleroe
ኤልሮኢ:
ሐመረ ኖህ ነሽ
============
ሐመረ ኖህ ነሽ
የምህረት ቃል ኪዳን የተገባልሽ
ትውልድ ይህን አምኖ
ያከብርሻል አልቆ እና አግኖ
አዝ----------------//
በእግዚአብሔር ሀሳብ ነበርሽ በህሊና
ዓለምን ሳይፈጥር አዳምን ሳይሠራ
ሁሉን የናፈቀሽ የወጣብሽ ፀሀይ
ንግሥት ነሽ ድንግል እሙ ለአዶናይ
አዝ----------------//
ያንን የጭንቅ ቀን የጥፋቱን ዘመን
አልፈነዋል ባንቺ በአማናዊት ፅዮን
ምንጭ ነሽ የእርካታ የድህነት መፍለቂያ
የዘለዓለም እረፍት አንባ እና ማረፊያ
አዝ----------------//
የነቢያት ተፈጽሞ አየን
አንቺ ምክንያት ሆነሽ ለመዳናችን
ድምፅሽን ጠላት ይሸበራል
እኛ ግን ሰምተነው በሀሴት ዘለናል
አዝ----------------//
አንዴ በገባልሽ ቃል ኪዳን መሠረት
ትውልዱን ይምራል ይኸው በቸርነት
ስሽ ወለላ ነው ጣፋጭ ለአፋችን
ማርያም ማርያም ብለን ታብሷል እንባችን
@aleroe
ሐመረ ኖህ ነሽ
============
ሐመረ ኖህ ነሽ
የምህረት ቃል ኪዳን የተገባልሽ
ትውልድ ይህን አምኖ
ያከብርሻል አልቆ እና አግኖ
አዝ----------------//
በእግዚአብሔር ሀሳብ ነበርሽ በህሊና
ዓለምን ሳይፈጥር አዳምን ሳይሠራ
ሁሉን የናፈቀሽ የወጣብሽ ፀሀይ
ንግሥት ነሽ ድንግል እሙ ለአዶናይ
አዝ----------------//
ያንን የጭንቅ ቀን የጥፋቱን ዘመን
አልፈነዋል ባንቺ በአማናዊት ፅዮን
ምንጭ ነሽ የእርካታ የድህነት መፍለቂያ
የዘለዓለም እረፍት አንባ እና ማረፊያ
አዝ----------------//
የነቢያት ተፈጽሞ አየን
አንቺ ምክንያት ሆነሽ ለመዳናችን
ድምፅሽን ጠላት ይሸበራል
እኛ ግን ሰምተነው በሀሴት ዘለናል
አዝ----------------//
አንዴ በገባልሽ ቃል ኪዳን መሠረት
ትውልዱን ይምራል ይኸው በቸርነት
ስሽ ወለላ ነው ጣፋጭ ለአፋችን
ማርያም ማርያም ብለን ታብሷል እንባችን
@aleroe
"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
………✍ፈጣሪ ያያል
----------------
አንድ ሰው ወደ እናት አባቱ ቤት አንዲት ሴተኛ አዳሪን ይዞ መጥቶ በእነሡ ፊት ዝሙት ይፈፅማል? ወይስ ማነው ወላጆቹ ፊት የዝሙት ፊልም ከፍቶ ነውር የሚፈፅም? ወላጆቻችን ፊት ጠጥቶ መስከር አያስፈራም? ወይም መስረቅ ወይም ክፉ ስድቦችን ቃላቶችን መናገር እና ሌሎችንም ሀጥያቶች መስራት ይከብዳል አይደል። ደፍሮ ለመፈፀም እጅግ ይከብዳል።
ፈጣሪ የሰማይም የምድርን ንጉሥ ነው!! የምናደርገውን ማንኛውም ድርጊት ይመለከታል። ታዲያ በምድራዊ እናት አባቶቻችን ፊት ከላይ የጠቀስናቸውን ነውሮች ደፍረን የማንፈፅም ከሆነ፥ እንደዚህ ያሉ ተግባራትን በፈጣሪ ፊት ለማከናወን የምንደፍረው ለምንድን ነው?
እግዚአብሔር እኮ ያየናል።
ለምሳሌ ሁላችንም አየርን በአይናችን አይተን አናውቅም አየር መኖሩን ግን አንጠራጠርም። እግዚአብሔርንም በዓይናችን ስላላየነው የለም ማለት አይደለም። እሱ ከኛ ጋር መሆኑን በሱ እይታ ውስጥ መሆናችንን እንዘነጋዋለን። ለመድራዊ ሰዎች የሰጠነውን ክብር እንኳ ለእግዚአብሔር አንሰጠም። ሌላው ይቅርና ሰው ዝሙትን ለመስራት ቢያስብ አንድ ትንሽ ህፃን ቢያየው ያን ተግባር ለማድረግ ያፍራል ይተወዋል። የዝሙት ፊልም የሚያይ ሰውም ትንሽ ህፃን ቢኖር ያፍራል ኡሱ ፊት ነውር አያደርግም። እግዚአብሔርን ግን የዛን ህፃን ያህል አልፈራውም አላከበረውም። በድፍረት ማንም አያየንም እያልን ሀጥያት አንስራ።
ስለዚህ ሰው ሆይ! እያንዳንዷን ድርጊትህ የሚመለከት የሰማይም የምድርም ንጉሥ እንዳለ በፍጹም አትርሳ፡፡ ሁሌም በህይወታችን በምንሰራቸው ነገሮች እግዚአብሔርን ላለማሳዘን በህጉ እና በትእዛዙ እንኑር። በውሎአችን በምንናገረው በምናስበው በምንሰራው ስራ ሁሉ እግዚአብሔር ይህ ነገር ያስደስተዋል ይሆን ወይ ብለን አስቀድመን እራሳችንን ጥይቀን እንደፈቃዱ ልንኖር ይገባል።
"ምን እየሰራቹ ነው ስንባል ለመናገር የምናፍርበትን ድርጊት አንፈፅም"
@aleroe
………✍ፈጣሪ ያያል
----------------
አንድ ሰው ወደ እናት አባቱ ቤት አንዲት ሴተኛ አዳሪን ይዞ መጥቶ በእነሡ ፊት ዝሙት ይፈፅማል? ወይስ ማነው ወላጆቹ ፊት የዝሙት ፊልም ከፍቶ ነውር የሚፈፅም? ወላጆቻችን ፊት ጠጥቶ መስከር አያስፈራም? ወይም መስረቅ ወይም ክፉ ስድቦችን ቃላቶችን መናገር እና ሌሎችንም ሀጥያቶች መስራት ይከብዳል አይደል። ደፍሮ ለመፈፀም እጅግ ይከብዳል።
ፈጣሪ የሰማይም የምድርን ንጉሥ ነው!! የምናደርገውን ማንኛውም ድርጊት ይመለከታል። ታዲያ በምድራዊ እናት አባቶቻችን ፊት ከላይ የጠቀስናቸውን ነውሮች ደፍረን የማንፈፅም ከሆነ፥ እንደዚህ ያሉ ተግባራትን በፈጣሪ ፊት ለማከናወን የምንደፍረው ለምንድን ነው?
እግዚአብሔር እኮ ያየናል።
ለምሳሌ ሁላችንም አየርን በአይናችን አይተን አናውቅም አየር መኖሩን ግን አንጠራጠርም። እግዚአብሔርንም በዓይናችን ስላላየነው የለም ማለት አይደለም። እሱ ከኛ ጋር መሆኑን በሱ እይታ ውስጥ መሆናችንን እንዘነጋዋለን። ለመድራዊ ሰዎች የሰጠነውን ክብር እንኳ ለእግዚአብሔር አንሰጠም። ሌላው ይቅርና ሰው ዝሙትን ለመስራት ቢያስብ አንድ ትንሽ ህፃን ቢያየው ያን ተግባር ለማድረግ ያፍራል ይተወዋል። የዝሙት ፊልም የሚያይ ሰውም ትንሽ ህፃን ቢኖር ያፍራል ኡሱ ፊት ነውር አያደርግም። እግዚአብሔርን ግን የዛን ህፃን ያህል አልፈራውም አላከበረውም። በድፍረት ማንም አያየንም እያልን ሀጥያት አንስራ።
ስለዚህ ሰው ሆይ! እያንዳንዷን ድርጊትህ የሚመለከት የሰማይም የምድርም ንጉሥ እንዳለ በፍጹም አትርሳ፡፡ ሁሌም በህይወታችን በምንሰራቸው ነገሮች እግዚአብሔርን ላለማሳዘን በህጉ እና በትእዛዙ እንኑር። በውሎአችን በምንናገረው በምናስበው በምንሰራው ስራ ሁሉ እግዚአብሔር ይህ ነገር ያስደስተዋል ይሆን ወይ ብለን አስቀድመን እራሳችንን ጥይቀን እንደፈቃዱ ልንኖር ይገባል።
"ምን እየሰራቹ ነው ስንባል ለመናገር የምናፍርበትን ድርጊት አንፈፅም"
@aleroe
ኤልሮኢ:
እንኳን_ደህና_መጣችሁ
እንኳን ደኅና መጣችሁ /2/
ወደ እኔ ወደ እናታችሁ
እጄን ዘርግቼ ስጠብቃችሁ
ወላጆቻችሁን እንድታከብሩ
አምላካችን መናገሩ /2/
እንድትጠብቁ ትእዛዙን
እምቢተኞች ባለመሆን /2/
የዕውቀት ገበያተኞች እንደመሆናችሁ
ምንም ጊዜ ሳይኖራችሁ /2/
እንደዚህ እኮ የምላችሁ
ቤተክርስቲያን ነኝ እናታችሁ /2/
ከሰኞ እስከ ዓርብ እየሠራን
እንጠያየቅ በሰንበት ቀን /2/
@aleroe
እንኳን_ደህና_መጣችሁ
እንኳን ደኅና መጣችሁ /2/
ወደ እኔ ወደ እናታችሁ
እጄን ዘርግቼ ስጠብቃችሁ
ወላጆቻችሁን እንድታከብሩ
አምላካችን መናገሩ /2/
እንድትጠብቁ ትእዛዙን
እምቢተኞች ባለመሆን /2/
የዕውቀት ገበያተኞች እንደመሆናችሁ
ምንም ጊዜ ሳይኖራችሁ /2/
እንደዚህ እኮ የምላችሁ
ቤተክርስቲያን ነኝ እናታችሁ /2/
ከሰኞ እስከ ዓርብ እየሠራን
እንጠያየቅ በሰንበት ቀን /2/
@aleroe