"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
ምክረ አበው
እባብ በህይወት እያለ ጉንዳንን ይበላል፡፡ እባብ ሲሞት ጉንዳኖች ይበሉታል፡፡ ጊዜ በማንኛውም ሰዓት ይለወጣል በህይወትህ የማንንም ዋጋ አታሳንስ
ምን አልባት አንተ ሀይለኛ ትሆን ይሆናል ጊዜ ግን ካንተ የበለጠ ጉልበተኛ ነው አስብ አንድ ዛፍ መቶ ሺ ክብሪቶችን ሲሰራ አንድ ክብሪት ግን መቶ ሺ ዛፎችን ታቃጥላለች፡፡
አንድ መጥፎ ስራም ብዙ መልካምነገሮችን ታጠፋለች፡፡ ወናው ነገር በአስተሳሰብ መልካም ሁን ረጋ ብለህ አስብ ለሁሉም ጊዜ አለው አትጨነቅ !
@aleroe
ምክረ አበው
እባብ በህይወት እያለ ጉንዳንን ይበላል፡፡ እባብ ሲሞት ጉንዳኖች ይበሉታል፡፡ ጊዜ በማንኛውም ሰዓት ይለወጣል በህይወትህ የማንንም ዋጋ አታሳንስ
ምን አልባት አንተ ሀይለኛ ትሆን ይሆናል ጊዜ ግን ካንተ የበለጠ ጉልበተኛ ነው አስብ አንድ ዛፍ መቶ ሺ ክብሪቶችን ሲሰራ አንድ ክብሪት ግን መቶ ሺ ዛፎችን ታቃጥላለች፡፡
አንድ መጥፎ ስራም ብዙ መልካምነገሮችን ታጠፋለች፡፡ ወናው ነገር በአስተሳሰብ መልካም ሁን ረጋ ብለህ አስብ ለሁሉም ጊዜ አለው አትጨነቅ !
@aleroe
ኤልሮኢ:
06/08/11
#መዝሙር_ዘኒቆዲሞስ
" ሖረ ኀቤሁ "
#በዕለቱ_ቅዳሴ_ሰዓት_የሚነበ_መልዕክታት_ወንጌልና_ምስባክ፡፡
ዲ/ን ሮሜ 7÷1-12
ን/ዲ 1ዮሐ 4÷18-ፍ ም
ን/ካ ግብ፡ሐዋ5÷34-ፍ ም
#የዕለቱ_ምስባክ
መዝ 16÷3
ሐወፅከኒ ሌሊተ ወፈተንኮ ለልብየ
አመከርከኒ ወኢተረክበ ዓመፃ በላዕሌየ
ከመ ኢይንብብ አፉየ ግብረ እጓለ እመሕያው::
#ትርጒም፦
በሌሊት ጎበኘኸኝ ልቤንም ፈተንኸው
ፈተንኸኝ ዓመፅ አልተገኘብኝም
የሰውን ሥራ አፌ እንዳይናገር
#የዕለቱ_ወንጌል፦
ዮሐ 3÷1-12
ቅዳሴ: ዘእግዝእትነ
👉 @aleroe
06/08/11
#መዝሙር_ዘኒቆዲሞስ
" ሖረ ኀቤሁ "
#በዕለቱ_ቅዳሴ_ሰዓት_የሚነበ_መልዕክታት_ወንጌልና_ምስባክ፡፡
ዲ/ን ሮሜ 7÷1-12
ን/ዲ 1ዮሐ 4÷18-ፍ ም
ን/ካ ግብ፡ሐዋ5÷34-ፍ ም
#የዕለቱ_ምስባክ
መዝ 16÷3
ሐወፅከኒ ሌሊተ ወፈተንኮ ለልብየ
አመከርከኒ ወኢተረክበ ዓመፃ በላዕሌየ
ከመ ኢይንብብ አፉየ ግብረ እጓለ እመሕያው::
#ትርጒም፦
በሌሊት ጎበኘኸኝ ልቤንም ፈተንኸው
ፈተንኸኝ ዓመፅ አልተገኘብኝም
የሰውን ሥራ አፌ እንዳይናገር
#የዕለቱ_ወንጌል፦
ዮሐ 3÷1-12
ቅዳሴ: ዘእግዝእትነ
👉 @aleroe
ኤልሮኢ:
………✍"የዛሬ 2000 ዓመት ኢየሱስ ክርስቶስ ሲወለድ እጅመንሻ ይዛ ለተገኘች፡ ኢየሱስ ክርስቶስን በሕፃንነቱ ሲሰደድ ለተቀበለች፡ ኢየሱስ ባረገ በዓመቱ በጃንደረባዋ በኩል በስሙ ለተጠመቀች፡ ከማንም በፊት ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ያላትን እምነት በንጉሥዋ በኢዛና በኩል በይፋ ለገለጠች፡ በዓለም ጥንታዊዉን በእጅ የተጻፈ የኢየሱስ ወንጌል በአባ ገሪማ ገዳም ለያዘች፡ በዓመት ከ1825 ጊዜ በላይ የኢየሱስ ወንጌል እንዲነበብ ሥርዓት ለሠራች ኢትዮጵያ፡- "ኢየሱስ ጌታ ነው" የሚለው ሰበር ዜናዋ ሊሆን አይችልም፡፡ ደንቆሮ የሰማ ዕለት ያብዳል ሆኖ ነው እንጅ፡፡"
ዲያቆን ዳንኤል ክብረት
@aleroe
………✍"የዛሬ 2000 ዓመት ኢየሱስ ክርስቶስ ሲወለድ እጅመንሻ ይዛ ለተገኘች፡ ኢየሱስ ክርስቶስን በሕፃንነቱ ሲሰደድ ለተቀበለች፡ ኢየሱስ ባረገ በዓመቱ በጃንደረባዋ በኩል በስሙ ለተጠመቀች፡ ከማንም በፊት ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ያላትን እምነት በንጉሥዋ በኢዛና በኩል በይፋ ለገለጠች፡ በዓለም ጥንታዊዉን በእጅ የተጻፈ የኢየሱስ ወንጌል በአባ ገሪማ ገዳም ለያዘች፡ በዓመት ከ1825 ጊዜ በላይ የኢየሱስ ወንጌል እንዲነበብ ሥርዓት ለሠራች ኢትዮጵያ፡- "ኢየሱስ ጌታ ነው" የሚለው ሰበር ዜናዋ ሊሆን አይችልም፡፡ ደንቆሮ የሰማ ዕለት ያብዳል ሆኖ ነው እንጅ፡፡"
ዲያቆን ዳንኤል ክብረት
@aleroe
ኤልሮኢ:
#ቢፈልግባትም_መልካሙ_ገበሬ
ቢፈልግባትም መልካሙ ገበሬ
አልተገኘባትም ከበለስዋ ፍሬ፤
…
ለስልሶላት ነበር ሀይማኖት መሬቱ፤
ተቀጥሮላት ነበር አጥር ስርዓቱ፤
ተነቅሎላት ነበር ድንጋይ ፈተናዋ፤
ፍሬ ግን ታጣባት በመጨረሻዋ፤
…
ፍሬ የሌለባት ቅጠል ስለሆነች፤
ተካይዋን በምግባር ስላላስደሰተች፤
መልካሙን ገበሬ ሊቆርጣት ተነሳ፤
ሌሎች እንዳይጠፉ በእርሷ የተነሳ፤
…
ለንስሐ የሚሆን እድሜ እንዲሰጣት፤
ጠባቂ መልዐኳ ተማጸነላት፤
ምክር እና ተግሳጽ ይጨመርላት፤
ታፈራ እንደሆነ ለዓመት እንያት፤
…
ልመናውን ሰምቶ ጌታውም ፈቀደ፤
ጥቂት እድሜ ሊሰጥ ሊታገስ ወደደ፤
ዳግመኛ ሲመጣ ፍሬ ካላፈራች፤
ተቆርጣ ወደ ቶን እሳት ትጣላለች፤
👇👇👇👇👇
👉 @aleroe 👈
👉 @aleroe👈
👉 @aleroe👈
👆 👆👆👆👆
#ቢፈልግባትም_መልካሙ_ገበሬ
ቢፈልግባትም መልካሙ ገበሬ
አልተገኘባትም ከበለስዋ ፍሬ፤
…
ለስልሶላት ነበር ሀይማኖት መሬቱ፤
ተቀጥሮላት ነበር አጥር ስርዓቱ፤
ተነቅሎላት ነበር ድንጋይ ፈተናዋ፤
ፍሬ ግን ታጣባት በመጨረሻዋ፤
…
ፍሬ የሌለባት ቅጠል ስለሆነች፤
ተካይዋን በምግባር ስላላስደሰተች፤
መልካሙን ገበሬ ሊቆርጣት ተነሳ፤
ሌሎች እንዳይጠፉ በእርሷ የተነሳ፤
…
ለንስሐ የሚሆን እድሜ እንዲሰጣት፤
ጠባቂ መልዐኳ ተማጸነላት፤
ምክር እና ተግሳጽ ይጨመርላት፤
ታፈራ እንደሆነ ለዓመት እንያት፤
…
ልመናውን ሰምቶ ጌታውም ፈቀደ፤
ጥቂት እድሜ ሊሰጥ ሊታገስ ወደደ፤
ዳግመኛ ሲመጣ ፍሬ ካላፈራች፤
ተቆርጣ ወደ ቶን እሳት ትጣላለች፤
👇👇👇👇👇
👉 @aleroe 👈
👉 @aleroe👈
👉 @aleroe👈
👆 👆👆👆👆
"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
++ ንጉሥ በአህያ ላይ ++
(ሽራፊ ሃሳብ ከሆሳዕና ምንባብ)
"አህያ" ስምዋ ስድብ ከሆነ የቆየች እንስሳ ናት። የዚህች በዓለም ሁሉ የምትገኝ እንስሳ የሕይወት ታሪክዋ በአብዛኛው ተመሳሳይ ነው። በሚበዙት ሀገራት አህያ ከባድ ሸክም ስትሸከም ትውላለች ፣ ደክሟት ለማረፍ ብትፈልግና ሸብረክ ብትል እንኳን በዱላ የሚመታት እንጂ "እስቲ አረፍ በይ" የሚላት የለም። ጀርባዋ በሸክም ብዛት የቆሰለ ፣ እግርዋ በጭነት ብዛት የተብረከረከ ፣ ዱላ ያስመረራት ፣ ዕረፍት የናፈቃት እንስሳ ናት።
ይህችን የተዋረደች እንስሳ በኪሩቤል ላይ የሚቀመጠው ሰማያዊው ንጉሥ ክርስቶስ በትሕትናው ዙፋኑ አደረጋት። ዱላ በለመደችው ፣ ዕረፍት በናፈቃት በዚህች ምስኪን ላይ "ቀንበሬ ልዝብ ሸክሜ ቀሊል ነው" ያለው ንጉሥ ተቀመጠባት።
ኃያላን ነገሥታት ባማረ ሠረገላ ላይ ሆነው ፣ በሠራዊት ታጅበው ፣ ነጋሪት እያስመቱ ፣ መለከት እያስነፉ ፣ ሰይፍ በታጠቁ ጦረኞች እየተፎከረላቸው ወደሚገቡባት ወደ ኢየሩሳሌም ከተማ መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ በአህያ ላይ ተጭኖ ፣ በዓሣ አጥማጆች ተከብቦ ፣ በሕፃናት ዝማሬና በዘንባባ ዝንጣፊ ታጅቦ ገባ።
ፈርተውት ሳይሆን ወደውት የሚዘምሩለት ንጉሥ ፣ ልብስ ገፍፎ የሚረግጥ ሳይሆን ልብሳቸውን አውልቀው ረግጠህ እለፍ የሚሉት ንጉሥ ፣ በቅንጦት ሠረገላ የሚሣፈር ሳይሆን "በአህያ ላይ ከተቀመጥኩ ይበቃኛል" የሚል ንጉሥ ወደ ኢየሩሳሌም ገባ።
"የጽዮን ልጅ ሆይ ደስ ይበልሽ ፣ ንጉሥሽ የዋህ ሆኖ በአህያና በውርጫይቱ ላይ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል" የተባለላት ኢየሩሳሌም ምንኛ የታደለች ናት? "የዋህና ትሑት ንጉሥ" ያላት ሀገር ፣ ከተማይቱን እያየ የሚያለቅስላት ንጉሥ ፣ መልካምነቱን ለመሸፈን የሚፈልጉ ሰዎች ስለ እሱ አትናገሩ ቢሉ እንኳን የቢታንያ ድንጋዮች አፍ አውጥተው የሚመሰከሩለት ንጉሥ ያላት ኢየሩሳሌም ምንኛ የታደለች ናት? የታሰሩትን አስታውሶ "ያስፈልጉኛል ፣ ፈትታችሁ አምጡልኝ" የሚል ንጉሥ የነገሠባት ፣ ዘንባባ ተይዞ ስለ ሰላም የተዘመረባት ፣ "ሰላምሽ ዛሬ ነው" የተባለላት ያቺ ከተማ ምንኛ የታደለች ናት?
ወደ አህያይቱ ነገር እንመለስ ያቺን "ሸክም ያቆሰላትን ፣ ዕረፍት የናፈቃትን አህያ ክርስቶስ ፈትታችሁ አምጡልኝ ብሎ ዙፋኑ አደረጋት" የሚለው ታሪክ ለአህያ ብቻ ክብር የተሠጠበት ቀን መሆኑን የሚያሳይ ከመሰለን የዋሆች ነን። አህዮች አንብበው የማይጽናኑበት ወንጌል ላይ ይህ ክስተት የተጻፈው ለእኛ እንጂ ለምንም አይደለም።
እንደ አህያ ዕቃ ባንሸከምም ፣ ጀርባችን ባይቆስልም የልባችን ጀርባ በኃጢአት ሸክም የጎበጠ ፣ በበደል ብዛት የቆሰለብን ብዙዎች ነን። "መቼ ነው ይህንን የኃጢአት ሸክም አራግፌ ዕርፍ የምለው?" እያልን የምንሠቃይ ሞልተናል። መድኃኔ ዓለም ያኔ የላካቸውን ካህናት ዛሬም ወደ እኛ ልኮ "ፈትታችሁ አምጡልኝ" ብሎ እኛንም ቢያስፈታን ምናለ? ለነገሩ የእኛ የኃጢአት ማሠሪያ እጅግ ትብትብ ያለ ስለሆነ ካህናቱም "ከኃጢአት ማሠሪያ እግዚአብሔር ይፍታ" ሲሉ እንሰማቸዋለን።
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
@aleroe
++ ንጉሥ በአህያ ላይ ++
(ሽራፊ ሃሳብ ከሆሳዕና ምንባብ)
"አህያ" ስምዋ ስድብ ከሆነ የቆየች እንስሳ ናት። የዚህች በዓለም ሁሉ የምትገኝ እንስሳ የሕይወት ታሪክዋ በአብዛኛው ተመሳሳይ ነው። በሚበዙት ሀገራት አህያ ከባድ ሸክም ስትሸከም ትውላለች ፣ ደክሟት ለማረፍ ብትፈልግና ሸብረክ ብትል እንኳን በዱላ የሚመታት እንጂ "እስቲ አረፍ በይ" የሚላት የለም። ጀርባዋ በሸክም ብዛት የቆሰለ ፣ እግርዋ በጭነት ብዛት የተብረከረከ ፣ ዱላ ያስመረራት ፣ ዕረፍት የናፈቃት እንስሳ ናት።
ይህችን የተዋረደች እንስሳ በኪሩቤል ላይ የሚቀመጠው ሰማያዊው ንጉሥ ክርስቶስ በትሕትናው ዙፋኑ አደረጋት። ዱላ በለመደችው ፣ ዕረፍት በናፈቃት በዚህች ምስኪን ላይ "ቀንበሬ ልዝብ ሸክሜ ቀሊል ነው" ያለው ንጉሥ ተቀመጠባት።
ኃያላን ነገሥታት ባማረ ሠረገላ ላይ ሆነው ፣ በሠራዊት ታጅበው ፣ ነጋሪት እያስመቱ ፣ መለከት እያስነፉ ፣ ሰይፍ በታጠቁ ጦረኞች እየተፎከረላቸው ወደሚገቡባት ወደ ኢየሩሳሌም ከተማ መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ በአህያ ላይ ተጭኖ ፣ በዓሣ አጥማጆች ተከብቦ ፣ በሕፃናት ዝማሬና በዘንባባ ዝንጣፊ ታጅቦ ገባ።
ፈርተውት ሳይሆን ወደውት የሚዘምሩለት ንጉሥ ፣ ልብስ ገፍፎ የሚረግጥ ሳይሆን ልብሳቸውን አውልቀው ረግጠህ እለፍ የሚሉት ንጉሥ ፣ በቅንጦት ሠረገላ የሚሣፈር ሳይሆን "በአህያ ላይ ከተቀመጥኩ ይበቃኛል" የሚል ንጉሥ ወደ ኢየሩሳሌም ገባ።
"የጽዮን ልጅ ሆይ ደስ ይበልሽ ፣ ንጉሥሽ የዋህ ሆኖ በአህያና በውርጫይቱ ላይ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል" የተባለላት ኢየሩሳሌም ምንኛ የታደለች ናት? "የዋህና ትሑት ንጉሥ" ያላት ሀገር ፣ ከተማይቱን እያየ የሚያለቅስላት ንጉሥ ፣ መልካምነቱን ለመሸፈን የሚፈልጉ ሰዎች ስለ እሱ አትናገሩ ቢሉ እንኳን የቢታንያ ድንጋዮች አፍ አውጥተው የሚመሰከሩለት ንጉሥ ያላት ኢየሩሳሌም ምንኛ የታደለች ናት? የታሰሩትን አስታውሶ "ያስፈልጉኛል ፣ ፈትታችሁ አምጡልኝ" የሚል ንጉሥ የነገሠባት ፣ ዘንባባ ተይዞ ስለ ሰላም የተዘመረባት ፣ "ሰላምሽ ዛሬ ነው" የተባለላት ያቺ ከተማ ምንኛ የታደለች ናት?
ወደ አህያይቱ ነገር እንመለስ ያቺን "ሸክም ያቆሰላትን ፣ ዕረፍት የናፈቃትን አህያ ክርስቶስ ፈትታችሁ አምጡልኝ ብሎ ዙፋኑ አደረጋት" የሚለው ታሪክ ለአህያ ብቻ ክብር የተሠጠበት ቀን መሆኑን የሚያሳይ ከመሰለን የዋሆች ነን። አህዮች አንብበው የማይጽናኑበት ወንጌል ላይ ይህ ክስተት የተጻፈው ለእኛ እንጂ ለምንም አይደለም።
እንደ አህያ ዕቃ ባንሸከምም ፣ ጀርባችን ባይቆስልም የልባችን ጀርባ በኃጢአት ሸክም የጎበጠ ፣ በበደል ብዛት የቆሰለብን ብዙዎች ነን። "መቼ ነው ይህንን የኃጢአት ሸክም አራግፌ ዕርፍ የምለው?" እያልን የምንሠቃይ ሞልተናል። መድኃኔ ዓለም ያኔ የላካቸውን ካህናት ዛሬም ወደ እኛ ልኮ "ፈትታችሁ አምጡልኝ" ብሎ እኛንም ቢያስፈታን ምናለ? ለነገሩ የእኛ የኃጢአት ማሠሪያ እጅግ ትብትብ ያለ ስለሆነ ካህናቱም "ከኃጢአት ማሠሪያ እግዚአብሔር ይፍታ" ሲሉ እንሰማቸዋለን።
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
@aleroe
ኤልሮኢ:
ሆሣዕና በአርያም
ሆሣዕና/2/ በአርያም ሆሣዕና
ሆሣዕና ብለን እናቅርብ ምስጋና
ሆሣዕና በሉ ሆሣዕና…
ቅድስት ሀገር ሆይ ሆሣዕና
ኢየሩሳሌም "
ምስጋናሽ ብዙ ነዉ "
በመላዉ ዓለም "
አዝ
በአህያ ላይ ሆኖ ሆሣዕና
ወደ አንቺ የገባዉ "
ኢየሱሰ ክርስቶስ "
የዓለም መድኃኒት ነው "
አዝ
ኃይልና ስልጣን ሆሣዕና
በአንድ ላይ ስላለዉ "
ጠላቶችሽ ፈሩ "
ሕዝብሽም ደስ አለዉ "
@aleroe
ሆሣዕና በአርያም
ሆሣዕና/2/ በአርያም ሆሣዕና
ሆሣዕና ብለን እናቅርብ ምስጋና
ሆሣዕና በሉ ሆሣዕና…
ቅድስት ሀገር ሆይ ሆሣዕና
ኢየሩሳሌም "
ምስጋናሽ ብዙ ነዉ "
በመላዉ ዓለም "
አዝ
በአህያ ላይ ሆኖ ሆሣዕና
ወደ አንቺ የገባዉ "
ኢየሱሰ ክርስቶስ "
የዓለም መድኃኒት ነው "
አዝ
ኃይልና ስልጣን ሆሣዕና
በአንድ ላይ ስላለዉ "
ጠላቶችሽ ፈሩ "
ሕዝብሽም ደስ አለዉ "
@aleroe
ኤልሮኢ:(ስነፅሁፍ)
#ሆሳዕና
አንቺ ኢየሩሳሌም ጌታ የመረጠሽ
አለምሽ ዛሬ ነው ክርስቶስ መጣልሽ
አንቺ የፂዮን ልጅ እጅግ ደስ ይበልሽ
ቅዱስ ትሁት ሆኖ ንጉስሽ መጣልሽ
ቀድሞም ነግሮሽ ነበር በትንቢታዊ ቃል
በአህያ ግልገል ላይ ተቀምጦ ይመጣል
ብሎ ዘካሪስ እንደተናገረ
በማቴወስ ወንጌል ትንቢቱን ፈፀመ
ጼጥሮስን ዮሃንስን ላከና ኢያሪኮ
በትዕዛዝ አስመጣት እሷን አስፈትቶ
ኪሩቤል ሱራፌል የሚፈሩት ጌታ
ፍቅርን ትህትና ሊያስተምረን ለኛ
ተቀምጦ መጣ በአህያ ሁርንጫ
ልብስ ሰውነትን እምደሚሸፍነው በደላችን ሸፈንክ በማለት ያለው ሰው ያነጥፍ ነበረ እንዳይቆረቁረው
ፀሀፍት ፈሪሳዊን እስኪደንቅ ድረስ
ህፃናት ዘመሩ ሆሳዕና ብለው ጌታን በማወደስ
እነዛም ፀሀፍታን በህፃናት መዝሙር እጅጉን ቀኑና በክርስቶስ ምግባር በጣም ተከፉና በቃል ከሰሷቸው ድንገት ተነሱና
ክርስቶስም አለ እኔማ እሰማለው
በመዝሙረ ዳዊት ከህፃናትና ከሚጠቡት አፍ ላይ ምስጋና ለራስህ አዘጋጅ ይል የልወይ ብሎም ጠየቃቸው?
እነዛም ፈሪሳዊ በግርምት ዝምታን ተውጠው ቀሩና ጌታም ነገራቸው ጥቅሱን አወጣና።
በንፁህ አንደበት ዘንባባውን ይዘው አመስግነውታል ሆሳዕና እያሉ ህፃናት በእልልታው
አህዛብ ሆይ ንቁ መዳን በክርስቶስ መሆኑን አትዘንጉ ተቀበሉ እውነቱን ከባርነት ውጡ!
@aleroe
#ሆሳዕና
አንቺ ኢየሩሳሌም ጌታ የመረጠሽ
አለምሽ ዛሬ ነው ክርስቶስ መጣልሽ
አንቺ የፂዮን ልጅ እጅግ ደስ ይበልሽ
ቅዱስ ትሁት ሆኖ ንጉስሽ መጣልሽ
ቀድሞም ነግሮሽ ነበር በትንቢታዊ ቃል
በአህያ ግልገል ላይ ተቀምጦ ይመጣል
ብሎ ዘካሪስ እንደተናገረ
በማቴወስ ወንጌል ትንቢቱን ፈፀመ
ጼጥሮስን ዮሃንስን ላከና ኢያሪኮ
በትዕዛዝ አስመጣት እሷን አስፈትቶ
ኪሩቤል ሱራፌል የሚፈሩት ጌታ
ፍቅርን ትህትና ሊያስተምረን ለኛ
ተቀምጦ መጣ በአህያ ሁርንጫ
ልብስ ሰውነትን እምደሚሸፍነው በደላችን ሸፈንክ በማለት ያለው ሰው ያነጥፍ ነበረ እንዳይቆረቁረው
ፀሀፍት ፈሪሳዊን እስኪደንቅ ድረስ
ህፃናት ዘመሩ ሆሳዕና ብለው ጌታን በማወደስ
እነዛም ፀሀፍታን በህፃናት መዝሙር እጅጉን ቀኑና በክርስቶስ ምግባር በጣም ተከፉና በቃል ከሰሷቸው ድንገት ተነሱና
ክርስቶስም አለ እኔማ እሰማለው
በመዝሙረ ዳዊት ከህፃናትና ከሚጠቡት አፍ ላይ ምስጋና ለራስህ አዘጋጅ ይል የልወይ ብሎም ጠየቃቸው?
እነዛም ፈሪሳዊ በግርምት ዝምታን ተውጠው ቀሩና ጌታም ነገራቸው ጥቅሱን አወጣና።
በንፁህ አንደበት ዘንባባውን ይዘው አመስግነውታል ሆሳዕና እያሉ ህፃናት በእልልታው
አህዛብ ሆይ ንቁ መዳን በክርስቶስ መሆኑን አትዘንጉ ተቀበሉ እውነቱን ከባርነት ውጡ!
@aleroe
ኤልሮኢ:
13/08/11
#መዝሙር_ዘሆሳዕና
" ወእንዘ ሰሙን "
#በዕለቱ_ቅዳሴ_ሰዓት_የሚነበ_መልዕክታት_ወንጌልና_ምስባክ፡፡
ዲ/ን ዕብ 9÷11- ፍ ም
ን/ዲ 1ጴጥ 4÷1-12
ን/ካ ግብ፡ሐዋ 28÷11-ፍ ም
#የዕለቱ_ምስባክ
#መዝ 8÷2
እምአፈ ደቂቅ ወሕፃናት አስተዳሎከ ስብሐተ
በእንተ ጸላኢ
ከመ ትንሥቶ ለጸላኢ ወለገፋዒ
#ትርጒም፦
ጠላትን ለማሳፈር ቂመኛንና ግፈኛንም ለማጥፋት ከህፃናትና ከሚጠቡ ልጆች አፍ ምስጋናን አዘጋጀህ::
#የዕለቱ_ወንጌል፦
ዮሐ 5÷11-31
ቅዳሴ: ዘጎርጎርዮስ
👉 @aleroe
13/08/11
#መዝሙር_ዘሆሳዕና
" ወእንዘ ሰሙን "
#በዕለቱ_ቅዳሴ_ሰዓት_የሚነበ_መልዕክታት_ወንጌልና_ምስባክ፡፡
ዲ/ን ዕብ 9÷11- ፍ ም
ን/ዲ 1ጴጥ 4÷1-12
ን/ካ ግብ፡ሐዋ 28÷11-ፍ ም
#የዕለቱ_ምስባክ
#መዝ 8÷2
እምአፈ ደቂቅ ወሕፃናት አስተዳሎከ ስብሐተ
በእንተ ጸላኢ
ከመ ትንሥቶ ለጸላኢ ወለገፋዒ
#ትርጒም፦
ጠላትን ለማሳፈር ቂመኛንና ግፈኛንም ለማጥፋት ከህፃናትና ከሚጠቡ ልጆች አፍ ምስጋናን አዘጋጀህ::
#የዕለቱ_ወንጌል፦
ዮሐ 5÷11-31
ቅዳሴ: ዘጎርጎርዮስ
👉 @aleroe
"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
የሰሙነ ሕማማት ዕለተ ዓርብ
ዕለተ ዓርብ በቤተክርስቲያን ልዩ ቀን ነው፡፡ የማይታመመው ታሞ የዋለበት፣ የወደቁ ከተረሱበት ከትቢያ የሚያነሳ እሱ ሲወድቅ ሲነሳ የዋለበት፣ ሕመምተኞችን የሚፈውስ እሱ ሲያቃስት የዋለበት፣ ከሲኦል የዲያብሎስ ግብር ነፃ የሚያወጣ ሲገረፍ የዋለበት፣ ወልደ እግዚአብሔር ለወዳጆቹ ድኅነት በመስዋዕትነት ሙሽራ የሆነበት የደስታ ቀን፤ አሳዳጅ አሳሪያችን ዲያብሎስ ከነወጥመዱ ድል የተነሳበት ቀን ነው። ከዚህም የተነሳ በቤተክርስቲያን የተለያየ ምስጢራዊ ስያሜዎች ተሰጥቶታል፡፡
#የስቅለት_ዓርብ ይባላል
የዓለም ሁሉ መድኀኒት የሆነው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአዳምና ለልጆቹ ሁሉ ቤዛ ሆኖ በመልዕልተ መስቀል ላይ ተሰቅሎ ለዓለ ድኅነት መስዋዕት ሆኖ የዋለበት ዕለት በመሆኑ የስቅለት ዓርብ ተብሏል። (ማቴ 27፡35)
#መልካሙ_ዓርብ ይባላል
ይህም የሚያስገነዝበን ከስቅለተ ክርስቶስ በፊት ማንም ሰው ሲያጠፋ በመስቀል ተሰቅሎ እንዲሞት ይደረግ ነበር፡፡ በተለይ በሮማውያንና በፈሪሳውያን ሕግ መስቀል የወንጀለኞች መቅጫ ነበረ። በዚህ ዕለት ግን ታሪክን የሚቀይር ነገርን የሚገለብጠው አምላክ የወንጀለኞች መቅጫ ምልክት የነበረውን መስቀል በደሙ ቀድሶ የምህረት ምልክት፣ የሕይወት አርአያ፣ የዲያብሎስ ድል መንሻ ፣ የቤተክርስቲያን ጌጥ፣ የገዳማት ዘውድ ስላደረገውና በዕለተ ዓርብ በሞቱ ሕይወትን ስላገኘን መልካሙ ዓርብ ተብሏል፡፡
በዚህ ዕለትም ጌታ ሁሉ ተፈጸመ ብሎ ቅድስት ነፍሱን ከቅድስት ስጋው በራሱ ፈቃድ ከለየ በኋላ አምላክነቱን ለመግለፅ ተአምራት አሳይቷል፦
1. ፀሐይ ጨልማለች
2. ጨረቃ ደም ሆናለች
3. ከዋክብት ረግፈዋል
4. የቤተ መቅደስ መጋረጃ ከላይ እስከ ታች ተቀዷል
5. ምድር ተናወጣለች (ተንቀጥቅጣለች)
6. መቃብሮች ተከፍተዋል
7. ሙታን ተነስተዋል
በዓመት አንድ ጊዜ የምናገኘው ይህ ዕለት ቀራንዮን የምናስብበት ነገረ መስቀሉን የምናስተውልበት እንጂ ስለምድራዊ ኑሮአችን ስንባክን የምንውልበትና በዋዛ ፈዛዛ ልናሳልፈው አይገባም፡፡
@aleroe
የሰሙነ ሕማማት ዕለተ ዓርብ
ዕለተ ዓርብ በቤተክርስቲያን ልዩ ቀን ነው፡፡ የማይታመመው ታሞ የዋለበት፣ የወደቁ ከተረሱበት ከትቢያ የሚያነሳ እሱ ሲወድቅ ሲነሳ የዋለበት፣ ሕመምተኞችን የሚፈውስ እሱ ሲያቃስት የዋለበት፣ ከሲኦል የዲያብሎስ ግብር ነፃ የሚያወጣ ሲገረፍ የዋለበት፣ ወልደ እግዚአብሔር ለወዳጆቹ ድኅነት በመስዋዕትነት ሙሽራ የሆነበት የደስታ ቀን፤ አሳዳጅ አሳሪያችን ዲያብሎስ ከነወጥመዱ ድል የተነሳበት ቀን ነው። ከዚህም የተነሳ በቤተክርስቲያን የተለያየ ምስጢራዊ ስያሜዎች ተሰጥቶታል፡፡
#የስቅለት_ዓርብ ይባላል
የዓለም ሁሉ መድኀኒት የሆነው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአዳምና ለልጆቹ ሁሉ ቤዛ ሆኖ በመልዕልተ መስቀል ላይ ተሰቅሎ ለዓለ ድኅነት መስዋዕት ሆኖ የዋለበት ዕለት በመሆኑ የስቅለት ዓርብ ተብሏል። (ማቴ 27፡35)
#መልካሙ_ዓርብ ይባላል
ይህም የሚያስገነዝበን ከስቅለተ ክርስቶስ በፊት ማንም ሰው ሲያጠፋ በመስቀል ተሰቅሎ እንዲሞት ይደረግ ነበር፡፡ በተለይ በሮማውያንና በፈሪሳውያን ሕግ መስቀል የወንጀለኞች መቅጫ ነበረ። በዚህ ዕለት ግን ታሪክን የሚቀይር ነገርን የሚገለብጠው አምላክ የወንጀለኞች መቅጫ ምልክት የነበረውን መስቀል በደሙ ቀድሶ የምህረት ምልክት፣ የሕይወት አርአያ፣ የዲያብሎስ ድል መንሻ ፣ የቤተክርስቲያን ጌጥ፣ የገዳማት ዘውድ ስላደረገውና በዕለተ ዓርብ በሞቱ ሕይወትን ስላገኘን መልካሙ ዓርብ ተብሏል፡፡
በዚህ ዕለትም ጌታ ሁሉ ተፈጸመ ብሎ ቅድስት ነፍሱን ከቅድስት ስጋው በራሱ ፈቃድ ከለየ በኋላ አምላክነቱን ለመግለፅ ተአምራት አሳይቷል፦
1. ፀሐይ ጨልማለች
2. ጨረቃ ደም ሆናለች
3. ከዋክብት ረግፈዋል
4. የቤተ መቅደስ መጋረጃ ከላይ እስከ ታች ተቀዷል
5. ምድር ተናወጣለች (ተንቀጥቅጣለች)
6. መቃብሮች ተከፍተዋል
7. ሙታን ተነስተዋል
በዓመት አንድ ጊዜ የምናገኘው ይህ ዕለት ቀራንዮን የምናስብበት ነገረ መስቀሉን የምናስተውልበት እንጂ ስለምድራዊ ኑሮአችን ስንባክን የምንውልበትና በዋዛ ፈዛዛ ልናሳልፈው አይገባም፡፡
@aleroe
ኤልሮኢ:
እልል በሉ
እልል /6 አማኑኤል ተነሣልን
ደስ ይበልን ሁላችንን
የሲኦል ደጆች ተከፈቱ እልል
የሰይጣንም ሠራዊቶች አፈሩ እልል
በጨለማው ዓለም ተወጠን ሳለን
ጌታ በትንሣኤው ዛሬ አበራልን
አዝ ---
መቃብራት ሁሉ ተከፈቱ እልል
የታሠሩ ነፍሳት ከግዞት ተፈቱ እልል
መግደላዊት ማርያም ትንሣኤውን አይታ
ነገረች ለሐዋርያት በደስታ ተሞልታ
አዝ ---
ሁለቱ መላእክት ብርሃን የለበሱ እልል
ተነሥቷል አሏቸው ሴቶቹ ሲደርሱ እልል
ሐዋርያት አይተው ዜና ትንሣኤውን
አሏአቸው ለድኅነት ሰላም ለእናንተ ይሁን
@aleroe
እልል በሉ
እልል /6 አማኑኤል ተነሣልን
ደስ ይበልን ሁላችንን
የሲኦል ደጆች ተከፈቱ እልል
የሰይጣንም ሠራዊቶች አፈሩ እልል
በጨለማው ዓለም ተወጠን ሳለን
ጌታ በትንሣኤው ዛሬ አበራልን
አዝ ---
መቃብራት ሁሉ ተከፈቱ እልል
የታሠሩ ነፍሳት ከግዞት ተፈቱ እልል
መግደላዊት ማርያም ትንሣኤውን አይታ
ነገረች ለሐዋርያት በደስታ ተሞልታ
አዝ ---
ሁለቱ መላእክት ብርሃን የለበሱ እልል
ተነሥቷል አሏቸው ሴቶቹ ሲደርሱ እልል
ሐዋርያት አይተው ዜና ትንሣኤውን
አሏአቸው ለድኅነት ሰላም ለእናንተ ይሁን
@aleroe
"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
●▬▬ ሳትሰስቺ ስጪ
ማታ ለመኝታ አልጋ ላይ ሰትወጪ
ሌሊቱ እንዲሰምር ሳትሰስቺ ስጪ
ጠዋት እንደ ነጋ ሳትወርጂ ከአልጋ
ደግመሽ መስጠትሽም እንዳይዘነጋ
ሻወር ቤትም ቢሆን ኩሽና ስትገቢ
ካንጀትሽ ለግሺው ሳትንገበገቢ
ከዋልሽበት ቦታ በሰላም ስትመጪ
በርከክ በይና ጎንበስ ብለሽ ስጪ
ቀናትን ሳትመርጪ ሰኞ አርብ ሳትዪ
ሰባቱንም ቀናት ለሱ አትከልክዪ
ህይወትሽ እንዲያምር ኑሮሽ እንዲቀና
ለአምላክ ምስጋና ይገባዋልና።
ለእሷ ብቻ አይደለም ላንተም ነው በል ንቃ
@aleroe
●▬▬ ሳትሰስቺ ስጪ
ማታ ለመኝታ አልጋ ላይ ሰትወጪ
ሌሊቱ እንዲሰምር ሳትሰስቺ ስጪ
ጠዋት እንደ ነጋ ሳትወርጂ ከአልጋ
ደግመሽ መስጠትሽም እንዳይዘነጋ
ሻወር ቤትም ቢሆን ኩሽና ስትገቢ
ካንጀትሽ ለግሺው ሳትንገበገቢ
ከዋልሽበት ቦታ በሰላም ስትመጪ
በርከክ በይና ጎንበስ ብለሽ ስጪ
ቀናትን ሳትመርጪ ሰኞ አርብ ሳትዪ
ሰባቱንም ቀናት ለሱ አትከልክዪ
ህይወትሽ እንዲያምር ኑሮሽ እንዲቀና
ለአምላክ ምስጋና ይገባዋልና።
ለእሷ ብቻ አይደለም ላንተም ነው በል ንቃ
@aleroe
"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
✍ …… እኛ ከየትኛው እንሆን ይሆን
አምስት ዓይነት ክርስቲያኖች
✝ አንደኛው ክርስቲያን
ዘወትር ከቤተ ክርስቲያንየማይለይ በየቀኑ እግሮቹ ወደ ቤተክርስቲያን የሚገሰግሱ ጠዋት ኪዳን ከሰዓት ቅዳሴ ማታ ሰርክ ጉባኤ የማይቀር ዘወትር የሚጸልይ የሚጾምስርዓተ ቤተ ክርስቲያንን ጠብቆ የሚኖር የሰበካ ጉባኤ አባል የሆነ ቤተ ክርስቲያንን በሚችለው የሚያገለግል ቤቱን ካህናት የባረኩትየሚቆርብ አስራቱን በኩራቱን የሚያወጣ ክርስትናን በተግባር የሚገልጠው ነው።
✝ ሁለተኛው ክርስቲያን
በሳምንት አንድ ቀን እሁድ እሁድ ብቻ ቤተ ክርስቲያን የሚሄድ
በሳምንት አንድ ቀን የሚጸልይ
ስድስት ቀን ሙሉ ቤተ ክርስቲያን ትዝ የማይለው በሳምንት አንድ ቀን የሚያስቀድስ ስድስቱን ቀን በግል ስራው የተጠመደ በሳምንት አንድ ቀን ብቻ ሂዶ እድር እቁብ አለብኝ ወንጌሉ ይጠር ትምህርቱ በዛ መርሃ ግብር ተንዛዛ ቅዳሴው ረዘመ የሚል በሳምንት አንድ ቀን መጥቶ ሥርዓቱ እስኪፈጸም መቆየት ያቃተው ከመንፈሳዊው ይልቅ ለዓለማዊ የሚያዳላው ነው።
✝ ሶስተኛው ክርስቲያን
በወር አንድ ቀን ብቻ ወራዊ በዓላትን ቆጥሮ ወደ ቤተ ክርስቲያን የሚሄደው ነው
(የመድኀኔዓም) (የማርያም) (የሚካኤል)ወዘተ
ዛሬ እኮ መድኀኔዓለም ነው ቤተ ክርስቲያን ልሂድ ብሎ ቀን ቆጥሮ የሚሄደው29 ቀን ሙሉ ቤተ ክረስቲያንን የረሳ ኪዳን አድርሶ የማያውቅ ወንጌል ቁጭ ብሎ የማይማር የማያስቀድስበወር አንድ ቀን ብቻ ቤተ ክርስቲያን ደርሶ የሚመለስ ለጸሎት ጊዜ የሌለውበቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የማይሳተፍ የሰበካ ጉባኤ መታወቂያ የሌለው የነፍስ አባቱን ስም እንኳየማያውቅ የነፍስ አባትህ ማነው? ተብሎ ሲጠየቅ እንትና እንትና ማን ነበር ረሳሁት የሚል የነፍስ አባቱን ሲያገባ ሲወልድ ሰው ሲሞትበት ብቻ የሚፈልግ ቤቱን አስባርኮ ጸበል አስረጭቶ የማያውቅ በልምድ ብቻ የሚኖረው ነው።
✝ አራተኛው ክርስቲያን
በዓመት አንድ ቀን በንግሥ ጊዜ ቤተ ክረርስቲያን የሚሄደው ነው
ዛሬ የዓመቱ ገብርኤል ነው
ዛሬ ጥምቀት ነው ብሎ የሚሄደው
364 ቀን ከቤተ ክርስቲያን ቀርቶ በዓመት አንድ ቀን ትዝ የሚለው
የበዓል ሰው የሆነ የነፍስ አባት የሌለው የሰበካ ጉባኤ መታወቂያ የሌለው ጸሎት አድርጎ ኪዳን አድርሶ ቅዳሴ አስቀድሶ ጾም ጹሞ ንስሐ ገብቶ የማያውቅ ኳስ ሲደግፍ ፊልም ሲያይ ቻት ሲያደርግ ካራንቡላ ፑል ሲጫዎት ጊዜውን በማባክን ራሱንበዓለማዊ ነገሮች ቢዚ ያደረገ ቤተ ክርስቲያን እንሂድ ሲሉት ቢዚ ነኝ የሚልሁለት ሰዓት ሙሉ ቁጭ ብሎ ኳስ የሚደግፍ ፊልም የሚያይ ሰላሳ ደቂቃ ወንጌል መማርየሚሰለቸው ዓለም አንቃየያዘቸው በሚያልፍ ነገር የሚታለለው ከመንፈሳዊ ነገር የራቀው ነው።
✝ አምስተኛው ክርስቲያን
በሕይወቱ ቤተክርስቲያንን የማያውቃት ነውክርስትና ሲነሳ እናቱ አዝላ ካመጣችው በሇላ ደግሞ ያልመጣ ለጠናቋይለጣኦት ሲገብር የኖረ በባእድ አምልኮ ተተብትቦ ተይዞ ቆሌ ጨሌ እያለ ኑሮ ሲሞት ለመቅበር ሰዎች ክርስቲያን ነው ብለው አስከሬኑን ወደ ቤተ ክረርስቲያን ያመጡት ስሙ ብቻ ክርስቲያን የተባለ የክርስትና ስራ ሰርቶ የማያውቅ በእሱ ምክንያት ከሰበካ ጉባኤ ጋራ ጭቅጭቅ የሚያስነሳ ሰበካ ጉባኤ ስለማለውቀው ኣይቀበርም የቤተ ክርስቲያን አባል አይደለም ሲል ዘመዶቹ ጎረቤቶቹ ክርስቲያን ነው ይቀበር ብለው የሚከራከሩለት ሰውን ግራ የሚያጋባ ከንቱ የሆነ ሰው ነው ።ክርስቲያኖች ሆይ እኔና እናንተ ከየትኛው ነን ???
@aleroe
✍ …… እኛ ከየትኛው እንሆን ይሆን
አምስት ዓይነት ክርስቲያኖች
✝ አንደኛው ክርስቲያን
ዘወትር ከቤተ ክርስቲያንየማይለይ በየቀኑ እግሮቹ ወደ ቤተክርስቲያን የሚገሰግሱ ጠዋት ኪዳን ከሰዓት ቅዳሴ ማታ ሰርክ ጉባኤ የማይቀር ዘወትር የሚጸልይ የሚጾምስርዓተ ቤተ ክርስቲያንን ጠብቆ የሚኖር የሰበካ ጉባኤ አባል የሆነ ቤተ ክርስቲያንን በሚችለው የሚያገለግል ቤቱን ካህናት የባረኩትየሚቆርብ አስራቱን በኩራቱን የሚያወጣ ክርስትናን በተግባር የሚገልጠው ነው።
✝ ሁለተኛው ክርስቲያን
በሳምንት አንድ ቀን እሁድ እሁድ ብቻ ቤተ ክርስቲያን የሚሄድ
በሳምንት አንድ ቀን የሚጸልይ
ስድስት ቀን ሙሉ ቤተ ክርስቲያን ትዝ የማይለው በሳምንት አንድ ቀን የሚያስቀድስ ስድስቱን ቀን በግል ስራው የተጠመደ በሳምንት አንድ ቀን ብቻ ሂዶ እድር እቁብ አለብኝ ወንጌሉ ይጠር ትምህርቱ በዛ መርሃ ግብር ተንዛዛ ቅዳሴው ረዘመ የሚል በሳምንት አንድ ቀን መጥቶ ሥርዓቱ እስኪፈጸም መቆየት ያቃተው ከመንፈሳዊው ይልቅ ለዓለማዊ የሚያዳላው ነው።
✝ ሶስተኛው ክርስቲያን
በወር አንድ ቀን ብቻ ወራዊ በዓላትን ቆጥሮ ወደ ቤተ ክርስቲያን የሚሄደው ነው
(የመድኀኔዓም) (የማርያም) (የሚካኤል)ወዘተ
ዛሬ እኮ መድኀኔዓለም ነው ቤተ ክርስቲያን ልሂድ ብሎ ቀን ቆጥሮ የሚሄደው29 ቀን ሙሉ ቤተ ክረስቲያንን የረሳ ኪዳን አድርሶ የማያውቅ ወንጌል ቁጭ ብሎ የማይማር የማያስቀድስበወር አንድ ቀን ብቻ ቤተ ክርስቲያን ደርሶ የሚመለስ ለጸሎት ጊዜ የሌለውበቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የማይሳተፍ የሰበካ ጉባኤ መታወቂያ የሌለው የነፍስ አባቱን ስም እንኳየማያውቅ የነፍስ አባትህ ማነው? ተብሎ ሲጠየቅ እንትና እንትና ማን ነበር ረሳሁት የሚል የነፍስ አባቱን ሲያገባ ሲወልድ ሰው ሲሞትበት ብቻ የሚፈልግ ቤቱን አስባርኮ ጸበል አስረጭቶ የማያውቅ በልምድ ብቻ የሚኖረው ነው።
✝ አራተኛው ክርስቲያን
በዓመት አንድ ቀን በንግሥ ጊዜ ቤተ ክረርስቲያን የሚሄደው ነው
ዛሬ የዓመቱ ገብርኤል ነው
ዛሬ ጥምቀት ነው ብሎ የሚሄደው
364 ቀን ከቤተ ክርስቲያን ቀርቶ በዓመት አንድ ቀን ትዝ የሚለው
የበዓል ሰው የሆነ የነፍስ አባት የሌለው የሰበካ ጉባኤ መታወቂያ የሌለው ጸሎት አድርጎ ኪዳን አድርሶ ቅዳሴ አስቀድሶ ጾም ጹሞ ንስሐ ገብቶ የማያውቅ ኳስ ሲደግፍ ፊልም ሲያይ ቻት ሲያደርግ ካራንቡላ ፑል ሲጫዎት ጊዜውን በማባክን ራሱንበዓለማዊ ነገሮች ቢዚ ያደረገ ቤተ ክርስቲያን እንሂድ ሲሉት ቢዚ ነኝ የሚልሁለት ሰዓት ሙሉ ቁጭ ብሎ ኳስ የሚደግፍ ፊልም የሚያይ ሰላሳ ደቂቃ ወንጌል መማርየሚሰለቸው ዓለም አንቃየያዘቸው በሚያልፍ ነገር የሚታለለው ከመንፈሳዊ ነገር የራቀው ነው።
✝ አምስተኛው ክርስቲያን
በሕይወቱ ቤተክርስቲያንን የማያውቃት ነውክርስትና ሲነሳ እናቱ አዝላ ካመጣችው በሇላ ደግሞ ያልመጣ ለጠናቋይለጣኦት ሲገብር የኖረ በባእድ አምልኮ ተተብትቦ ተይዞ ቆሌ ጨሌ እያለ ኑሮ ሲሞት ለመቅበር ሰዎች ክርስቲያን ነው ብለው አስከሬኑን ወደ ቤተ ክረርስቲያን ያመጡት ስሙ ብቻ ክርስቲያን የተባለ የክርስትና ስራ ሰርቶ የማያውቅ በእሱ ምክንያት ከሰበካ ጉባኤ ጋራ ጭቅጭቅ የሚያስነሳ ሰበካ ጉባኤ ስለማለውቀው ኣይቀበርም የቤተ ክርስቲያን አባል አይደለም ሲል ዘመዶቹ ጎረቤቶቹ ክርስቲያን ነው ይቀበር ብለው የሚከራከሩለት ሰውን ግራ የሚያጋባ ከንቱ የሆነ ሰው ነው ።ክርስቲያኖች ሆይ እኔና እናንተ ከየትኛው ነን ???
@aleroe
ኤልሮኢ:(መዝሙር)
ባለ ዉለታዬ ባለዉለታዬ
ከአመድ ያነሳኸኝ ከትቢያ ተጥዬ
ተመስገን ጌታዬ
በሩን ቢዘጋብኝ ስምዖን ጨክኖ
ዝቅ አድርጎ ቢያየኝ ከአይሁድጋ ሆኖ
እንድቀርብ ወደ እሱ አዘዘ ጌታዬ
እግሩን አጥበዋለሁ ወድቄ በእንባዬ
አዝ
የቀራጭ አለቃ ቢሆንም ስራዬ
እንድወርድ ከዛፉ አዘዘ ጌታዬ
ማረጌን መሸከም እስኪያቅተኝ ድረስ
ቤቴ ተባረከ በኢየሱስ ክርስቶስ
አዝ
ድንጋይ የጨበጡ ፈራጆች ከበውኝ
ነውሬን ዘርዝረው ጌታ ፊት አቆሙኝ
ፈረደችባቸው ሀጢያትም በነሱ
በሰላም ሂድ ብሎ ምርኛል ንጉሱ
አዝ
የማምነውን አምላክ አውቀዋለሁ እኔ
በሰራልኝ ስራ በእድሜ በዘመኔ
ፍቅሩን ተሸክሟል የልቤ ትከሻ
ልለየው አልችልም እስከመጨረሻ።
አዝ
የቀራጭ አለቃ ቢሆንም ስራዬ
እንድወርድ ከዛፉ አዘዘ ጌታዬ
ማረጌን መሸከም እስኪያቅተኝ ድረስ
ቤቴ ተባረከ በኢየሱስ ክርስቶስ
ባለ ዉለታዬ ባለዉለታዬ
ከአመድ ከያነሳኸኝ ከትቢያ ተጥዬ
ተመስገን ጌታዬ።
@aleroe
ባለ ዉለታዬ ባለዉለታዬ
ከአመድ ያነሳኸኝ ከትቢያ ተጥዬ
ተመስገን ጌታዬ
በሩን ቢዘጋብኝ ስምዖን ጨክኖ
ዝቅ አድርጎ ቢያየኝ ከአይሁድጋ ሆኖ
እንድቀርብ ወደ እሱ አዘዘ ጌታዬ
እግሩን አጥበዋለሁ ወድቄ በእንባዬ
አዝ
የቀራጭ አለቃ ቢሆንም ስራዬ
እንድወርድ ከዛፉ አዘዘ ጌታዬ
ማረጌን መሸከም እስኪያቅተኝ ድረስ
ቤቴ ተባረከ በኢየሱስ ክርስቶስ
አዝ
ድንጋይ የጨበጡ ፈራጆች ከበውኝ
ነውሬን ዘርዝረው ጌታ ፊት አቆሙኝ
ፈረደችባቸው ሀጢያትም በነሱ
በሰላም ሂድ ብሎ ምርኛል ንጉሱ
አዝ
የማምነውን አምላክ አውቀዋለሁ እኔ
በሰራልኝ ስራ በእድሜ በዘመኔ
ፍቅሩን ተሸክሟል የልቤ ትከሻ
ልለየው አልችልም እስከመጨረሻ።
አዝ
የቀራጭ አለቃ ቢሆንም ስራዬ
እንድወርድ ከዛፉ አዘዘ ጌታዬ
ማረጌን መሸከም እስኪያቅተኝ ድረስ
ቤቴ ተባረከ በኢየሱስ ክርስቶስ
ባለ ዉለታዬ ባለዉለታዬ
ከአመድ ከያነሳኸኝ ከትቢያ ተጥዬ
ተመስገን ጌታዬ።
@aleroe
"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ:
…………✍አንድ ሰውዬ በባህር ብቻውን በመርከብ እየተጓዘ በመዕበል ተመታና መርከቡ ተሰባብራ በባህሩ ሰመጠች ሰውዬው እንደምንም እራሱን አድኖ አንድ ደሴት ላይ ያርፍና ጎጆ ነገር ሰርቶ ለቀናት ለብቻው እዛች ደሴት ላይ ይኖራል……ምግቡን ዓሳ አያጠመደ እየተመገበ ብዙ ቆየ። አንድ ቀን ዓሳ ሊያጠምድ ወደ ባህሩ እየሄደ በማሃል እዛች ባህር ላይ ጭስ ሸተተው ዞር ብሎ ሲያይ ያቺ ጎጆው እየነደደች ነው……
እየሮጠ ቢመለስም ጎጆዋን ሊያድናት አልቻለም ለካ ዓሳ ለማብሰል ያቀጣጠለው እሳት ተያይዞ ጎጆውን አንድዷታል አለቀሰ ፈጠሪውን ወቀሰ እንዴት እዚህ ባህር ላይ ብቻዬን ጥለሀኝ
ከቤተሰቦቼ ነጥለሀኝ ስታበቃ በስንት ልፋት የሰራኋትን ጎጆ ታቃጥልብኛለህ ብሎ አለቀሰ አማረረ……ከደቂቃዎች በኃላ አንድ ድምፅ ሰማ ወደ ድምፁ ፊቱን ሲያዞር አንድ ትልቅ መርከብ አየ ተደሰተ……የመርከቡ ሰዎች መጥተው ጭነው ወሰዱት ከዚያም ለመርከቡ ሰዎች ጠየቃቸው! እንዴት አገኛቹኝ እዚህ አካባቢ እዚህ ባህር ላይ ማንም አይመጣም እኮ እናንተ እንዴት አገኛቹኝ?
አላቸው……መርከበኞቹም እኛማ በዛኛው በኩል ዞረን እየሄድን ነበር ከዚህ በኩል ጭስ አየንና እዚህ ሰዉ ይኖራል ብለን መጣን አንተ አገኘን አሉት። አቤት ጌታዬ ለካ ከዚህ ከስቃዬ ልታውጣኝ ፈልገህ ነው ትንሿ ጎጆዬን ያፍርስከው ወደ ትልቁ ቤት ልትውሰደኝ ነው አለ። አንዳዴ የሆነ ነገር ስናጣና ሲበላሽብን ሰውንም ፈጣሪንም ስናማርር እንኖራለን ግን ካጣነው እና ከጎደለብን ነገር ጀርባ
ብዙ ጥሩ ነገር ልናገኝ እንደምንችል እንዘነጋለን በችግራችን ጊዜ መጠጋት ያለብንን ፈጣሪያችን እንረሳዋለን ከዚያም አልፈን የሁሉ ነገር ፈጣሪውን እንኮንነዋለን። ያጣነውን እና የሰጠን ፈጣሪ! አእምሮችን ከሚያስበው በላይ
ሊሰጥህን እንደሚችል ማመን አለብን።
〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰
@aleroe
…………✍አንድ ሰውዬ በባህር ብቻውን በመርከብ እየተጓዘ በመዕበል ተመታና መርከቡ ተሰባብራ በባህሩ ሰመጠች ሰውዬው እንደምንም እራሱን አድኖ አንድ ደሴት ላይ ያርፍና ጎጆ ነገር ሰርቶ ለቀናት ለብቻው እዛች ደሴት ላይ ይኖራል……ምግቡን ዓሳ አያጠመደ እየተመገበ ብዙ ቆየ። አንድ ቀን ዓሳ ሊያጠምድ ወደ ባህሩ እየሄደ በማሃል እዛች ባህር ላይ ጭስ ሸተተው ዞር ብሎ ሲያይ ያቺ ጎጆው እየነደደች ነው……
እየሮጠ ቢመለስም ጎጆዋን ሊያድናት አልቻለም ለካ ዓሳ ለማብሰል ያቀጣጠለው እሳት ተያይዞ ጎጆውን አንድዷታል አለቀሰ ፈጠሪውን ወቀሰ እንዴት እዚህ ባህር ላይ ብቻዬን ጥለሀኝ
ከቤተሰቦቼ ነጥለሀኝ ስታበቃ በስንት ልፋት የሰራኋትን ጎጆ ታቃጥልብኛለህ ብሎ አለቀሰ አማረረ……ከደቂቃዎች በኃላ አንድ ድምፅ ሰማ ወደ ድምፁ ፊቱን ሲያዞር አንድ ትልቅ መርከብ አየ ተደሰተ……የመርከቡ ሰዎች መጥተው ጭነው ወሰዱት ከዚያም ለመርከቡ ሰዎች ጠየቃቸው! እንዴት አገኛቹኝ እዚህ አካባቢ እዚህ ባህር ላይ ማንም አይመጣም እኮ እናንተ እንዴት አገኛቹኝ?
አላቸው……መርከበኞቹም እኛማ በዛኛው በኩል ዞረን እየሄድን ነበር ከዚህ በኩል ጭስ አየንና እዚህ ሰዉ ይኖራል ብለን መጣን አንተ አገኘን አሉት። አቤት ጌታዬ ለካ ከዚህ ከስቃዬ ልታውጣኝ ፈልገህ ነው ትንሿ ጎጆዬን ያፍርስከው ወደ ትልቁ ቤት ልትውሰደኝ ነው አለ። አንዳዴ የሆነ ነገር ስናጣና ሲበላሽብን ሰውንም ፈጣሪንም ስናማርር እንኖራለን ግን ካጣነው እና ከጎደለብን ነገር ጀርባ
ብዙ ጥሩ ነገር ልናገኝ እንደምንችል እንዘነጋለን በችግራችን ጊዜ መጠጋት ያለብንን ፈጣሪያችን እንረሳዋለን ከዚያም አልፈን የሁሉ ነገር ፈጣሪውን እንኮንነዋለን። ያጣነውን እና የሰጠን ፈጣሪ! አእምሮችን ከሚያስበው በላይ
ሊሰጥህን እንደሚችል ማመን አለብን።
〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰
@aleroe
ኤልሮኢ:
# አይሸሸግ እውነቱ
አይሸሸግ እውነቱ ማርያም ብጸት ናት/2
ከእግዚአብሔር ያልተላከ አይችልም ሊያወድሳት (2)
ገብርኤል በከፍታ ከራማ ታላቅ ቤቱ
ገሊላ የተገኘው ወደ ማርያም እህቱ
ከእግዚአብሔር መላኩን ተረዳን በሚስጥር
ለስሟ ክብርንሰቶ ሰምተነዋል ሲየበስር
በዘካርያስ ቤት አቀረብሽ ምስጋና
የባርያውን ውርደት ተመልክቷልና
ፍጥረት ብፅይት ካለሽ ሆኖ ባንድ ቃሉ
ላንቺ ያልዘመረ እንዴት ትውልድ ይባል
ቢያከብርሽ ገብርኤል በታላቅ ትህትና
ልልናሽ በልጦበት ከርሱ ቅድስና
ከልቡ አመንጭቶ መች ሆነ ማክበሩ
እግዚአብሔር ልኮት ነው ለንቺ መዘመሩ
አንዳች አይጎልብኝ አንቺን አወድሼ
ዝማሬን ባበዛው ያለኝንጨርሼ
እንኳን ለማርያም ለአዶናይ እናት
ምስጋናን ሰቷታል ላቤጌያ ዳዊት
@aleroe
# አይሸሸግ እውነቱ
አይሸሸግ እውነቱ ማርያም ብጸት ናት/2
ከእግዚአብሔር ያልተላከ አይችልም ሊያወድሳት (2)
ገብርኤል በከፍታ ከራማ ታላቅ ቤቱ
ገሊላ የተገኘው ወደ ማርያም እህቱ
ከእግዚአብሔር መላኩን ተረዳን በሚስጥር
ለስሟ ክብርንሰቶ ሰምተነዋል ሲየበስር
በዘካርያስ ቤት አቀረብሽ ምስጋና
የባርያውን ውርደት ተመልክቷልና
ፍጥረት ብፅይት ካለሽ ሆኖ ባንድ ቃሉ
ላንቺ ያልዘመረ እንዴት ትውልድ ይባል
ቢያከብርሽ ገብርኤል በታላቅ ትህትና
ልልናሽ በልጦበት ከርሱ ቅድስና
ከልቡ አመንጭቶ መች ሆነ ማክበሩ
እግዚአብሔር ልኮት ነው ለንቺ መዘመሩ
አንዳች አይጎልብኝ አንቺን አወድሼ
ዝማሬን ባበዛው ያለኝንጨርሼ
እንኳን ለማርያም ለአዶናይ እናት
ምስጋናን ሰቷታል ላቤጌያ ዳዊት
@aleroe
"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" via @like
ኤልሮኢ: ( ስነ ፅሁፍ)
#ማህሌት
ፈልቀሽ የተገኘሽ ከአፈ መላእክት፣
ያሬድ የተማረሽ ከላይ ከሰማያት፣
እንከን የሌለብሽ አዲሷ ምስጋና።
ምስጢርሽ ሲገለጥ በአስደናቂ ዜማ፣
ከሰማይ መንጭተሽ በምድር ሲሰማ፣
በቃናሽ መስጠሽ ልቡናን በመክፈት፣
ማርከሽ ትወስጃለሽ ነፍስን ወደ ገነት።
የፍቅር መግለጫ የሕይወታችን አርማ፣
ጣእምሽ ልዩ ነው ሲገለጥ በዜማ።
የአድባራቱ ሁሉ ቋንቋና ድምጻቸው፣
የካህናት ቅኔ ሰምና ወርቃቸው፣
ለህዝብ ኢትዮጵያ የነፍስ ምግባቸው፣
ማኅሌት እኮነሽ ጸጋና ሃብታቸው።
____________________
@aleroe
#ማህሌት
ፈልቀሽ የተገኘሽ ከአፈ መላእክት፣
ያሬድ የተማረሽ ከላይ ከሰማያት፣
እንከን የሌለብሽ አዲሷ ምስጋና።
ምስጢርሽ ሲገለጥ በአስደናቂ ዜማ፣
ከሰማይ መንጭተሽ በምድር ሲሰማ፣
በቃናሽ መስጠሽ ልቡናን በመክፈት፣
ማርከሽ ትወስጃለሽ ነፍስን ወደ ገነት።
የፍቅር መግለጫ የሕይወታችን አርማ፣
ጣእምሽ ልዩ ነው ሲገለጥ በዜማ።
የአድባራቱ ሁሉ ቋንቋና ድምጻቸው፣
የካህናት ቅኔ ሰምና ወርቃቸው፣
ለህዝብ ኢትዮጵያ የነፍስ ምግባቸው፣
ማኅሌት እኮነሽ ጸጋና ሃብታቸው።
____________________
@aleroe