"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ"
1.2K subscribers
26 photos
3 videos
5 files
21 links
ኤልሮኢ
"በእውኑ የሚያየኝን ጌታ አየሁት"
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ
አምላክ አሜን።
ይህ መንፈሳዊ ቻናል
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ:- +ዝማሬ
+ ምክሮች
+ ስነፅሁፎች
+ አጫጭር ትርክቶች እንዲሁም
+ ምስባክና
+ ወንጌል ይለቀቁበታል።

ለበለጠ መረጃ @AleroeBot
ግሩፑን ለማግኘት @alero
Download Telegram
ኤልሮኢ፡(ስነ ፅሁፍ)

……🖌ላዩን ውብ ሆኛለሁ

ላዩን ውብ ሆኛለሁ ውስጤ ግን እረክሷል፣
ንፅህና የለም በኃጥያት ቆሽሿል።
አንደበቴ ሀያል ሁሉን አወቅኩ ባይ ነው፣
የተለሳለሰ ደግ መሳይ መርዝ ነው።
ለተመለከተኝ ላስተዋለኝ ሰው፣
ክንፍ እንጂ ምን ቀረው የማይለኝ ማነው።
በጎ ስነምግባር ትህትና የሌለኝ ፣
መስዬ የምኖር የስም ክርስቲያን ነኝ።
ፍሬ አልባ ወይን ነኝ የማላስደስት፣
አንተ ይቅር በለኝ አምላከ ምህረት።
መወደስ በከንቱ ከእንግዲህ ይብቃኝ፣
እውነተኛ እንድሆን ፈጣሪዬ እርዳኝ።

@aleroe
ለሀሳብ አስተያየት @Aleroebot
ኤልሮኢ:(⚜️ስነ ፅሁፍ⚜️)

#በምህረቱ መራኝ

ትላንት ነበርኩኝ እያለው የሌለው
እንዳማረ ተክል ፍሬ እንደሌለው
ደስታዬም ነበረ ለሞቴ መንገዱ
ህይወቴም ሚመስሉ አንዳች ያልተጎዱ
እውነታው ባይገባኝ የመኖሬ ምክንያት
እጆቼን ዘረጋው እምባዬም ፈሰሰ
ጉልበቴም ታዘዙ ለዳንስ እንዳልተነሱ
ልሳኔም በቃሉ ይቅርታን ለመነ
የወደቀልኝን እርሱን አገነነ
መውደቄን ተረድቶ የማይለኝ ችላ
አምላከ ብርሃን ህይወቴን አጎላ
በመሃሪነቱ ምህረቱን ሽሮኝ
ለህይወቴ ፍዳ መፍትሄው ሆነኝ

@aleroe ለሀሳብ አስተያየት @Aleroebot
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
• ቱርክ ኢስታንቡል የሚገኘውን ግዙፉን የሃጊያ ሶፊያን ቤተ መቅደስ ወርሰው ወደ መስጊድነት ቀይረው ስናይ ቱርክ በጣም ሩቅ ይመስለን ነበር።

…ይሄ የምታዩት ለቅሶ ለሸገር ቅርብ እዚሁ እኛ ሃገር አሩሲ ኦሮሚያ ውስጥ የተፈጸመ ነው። የኦሮሚያ የወሐቢይ እስላሞች ወታደር አሰማርተው፣ በጥምቀትና በመስቀል ደመራ የማክበሪያ ሥፍራችን ላይ የነበረን መስቀላችንን ማየት አንፈልግም ነቅላችሁ ውሰዱ ባሉን ጊዜ… ማረድና መውገርም ሲጀምሩ፣ እኛ ከምንነቅለው ነቅላችሁ ውሰዱት ባሉንም ጊዜ አባቶቻችን መክረው "ቀን እስኪያልፍ በትዕግስት እንለፈው" በማለት በምታዩት መልኩ እያለቀሱ መስቀሉን ሲያነሡ ነው የሚታየው ልቅሶና ዋይታ።

…ጊዜ የሰጠው እንዲህ ያደርጋል። ጊዜ የጣለው ደግሞ እንዲህ ይደረጋል። አሁን የመንግሥቱን ሥልጣን፣ ወታደሩም፣ የፍትሕ መሥሪያቤቱም፣ ባንክና ታንኩም የእነሱ ነው። ሁሉን ስትቆጣጠር ደግሞ እንዲህ ያደርግሃል። መንግሥቱን ታዛለህ። እንዳሻህም ትሆናለህ።

… እኛ ደግሞ ለጊዜው መሪም አባቶችም የሉንም። ባለ ሥልጣናትም የሉንም። ስናሳዝን። አሁን ላይ እኛን መግደል፣ ማፈናቀልና ማረድ በሕግ አያስጠይቅም። ነገርግን ሁሌ ደግሞ እንዲህ እንዳለቀስን ባንቀርም እንደሰው ሲታሰብ ግን በጣም ይቆጫል፣ ያሳዝናል፣ ያንገበግባልም።

…ደግሞም ይበሉን። አቤት ኅብረታቸው ግን ሲያስቀና። ከንቲባዋን በፍጥነት ይቅርታ አስጠየቁ። ቤተ ክህነቱን በዳዴ አንበርክከው አስኬዱ። የባሌ ኦሮሞ ነኝ ባዩን አባ ህጻንን በማያገባው አስገብተው በቤተ ክርስቲያኒቱ ስም ይቅርታ አስጠየቁ። "መብት ይወሰዳል እንጂ አይጠየቅም"ብለው እንዲያውም በመንግሥት ወጪ በሁላችንም ብር ያፈጥሩ ዘንድ አስወሰኑ። ችግሩ ከማፍጠሩ አይደለም።አቦ ወንድ ናቸው፣ ሕብረት ይህን ያመጣል! እኛም አስኪ አንድ እንሁን::
#ሁሉም_ይየው

@Gedamat
ኤልሮኢ:(ምክር)

ለራስህ ነው

አንተ ሰው! ቊጥር የሌላቸው ክፋቶች ቢኖሩብህም እንኳ በጎ ምግባር በልጅህ ይኖር ዘንድ በማድረግ አካክሰው፡፡ ለክርስቶስ የሚኾን ተሽቀዳዳሚ (ሯጭ) አሳድግ! ወዳጄ ሆይ! እንደዚህ ብዬ ስነግርህ አትፍራ፤ አትሸበርም፡፡ ልጅህ እንዳያገባ አድርገው አላልኩህም፡፡ ወደ ገዳም ወስደህ እንድታመነኩሰው ወይም የብሕትውና ሕይወትን እንዲመራ አድርገው አላልኩህም፡፡ እያልኩህ ያለሁት ይህን አይደለም፡፡ ልጅህ ቢመነኩስ እወድ ነበር፡፡ ብዙዎች ወደዚህ ሕይወት እንዲገቡ የዘወትር ጸሎቴ ነውና፡፡ ነገር ግን የምንኵስና ሕይወት [ሳይጠሩ ከገቡበት] ከባድ ሸክም ስለ ኾነ ሰዎች መነኰሳት ካልኾኑ ብዬ ግድ አልልም፡፡ ለአንተም እንደዚህ በግድ አመንኩሰው አልልህም፡፡ እያልኩህ ያለሁት ለክርስቶስ የሚኾን ተሸቀዳዳሚ አሳድግ ነው፡፡ በዚህ ዓለም አግብቶ፣ ልጆችንም ወልዶ የሚኖር ቢኾንም እንኳን ገና ከሕፃንነቱ አንሥቶ ሰውን የሚያከብር እንዲኾን አድርገህ አሳድገው ነው፡፡
ገና ጨቅላ እያለ በጎ በጎ ትእዛዛት በሕሊናው ጓዳ በልቡናው ሰሌዳ ላይ ከተቀረጸ፥ በሰም እንደ ታተመ ጸንቶ ይኖራል እንጂ ሲያድግ እነዚህን ትእዛዛት ሊያጠፋበትና ሊፍቅበት የሚችል ማንም አይኖርምና፡፡ ልጅህ አሁን ያለበት ዕድሜ ደግሞ በሚያየውና በሚነገረው በሌላም ነገር ኹሉ የሚንቀጠቀጥበት፣ የሚፈራበትና የሚደነግጥበት ዕድሜ ነው፡፡ ስለዚህ ልክ እንዳልደረቀ ሰም እንደምትፈልገው አድርገህ ቅረጸው፡፡ እንደዚህ አድርገህ ስታበቃ፥ መልካም ልጅ ቢኖርህ የመጀመሪያው ተጠቃሚ የምትኾነው አንተው ራስህ ነህ፡፡ እግዚአብሔር የሚጠቀመው ከአንተ በኋላ ነው፡፡ ስለዚህ የምትደክመው ለሌላ አካል ሳይኾን ለራስህ ነው፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

@aleroe
ለሀሳብ አስተያየት @Aleroebot
ኤልሮኢ:(ስነፅሁፍ)

#ነበርኩ_መች_ያድናል


ሀጢያትን ስትሰራ አምላክን እረስተህ
ቅዱሱን ሰውነት በሀጢያት አርክሰህ
ትእዛዝን ሳትፈጽም መልካምን ሳትሰራ
ዘይት ሳታዘጋጅ መብራትህ ሳይበራ
በተጠራህ ጊዜ መላከሞት ሲመጣ
ለማያልፈው አለም ሲወጣልህ እጣ
ለሚዛን ስትቀርብ አገልጋይ ነበርኩኝ እያልክ መናገሩ
መዝሙር ዘምሬያለው ሄጃለው ከበሩ
ብሎ መከራከር ያኔ መች ይጠቅማል
ይዞ መገኘት ነው ነበርኩ መች ያድናል!!!!
________________

@aleroe
ለሀሳብ አስተያየት @Aleroebot
ኤልሮኢ:ትርክት

መርሳት

በአንድ ወቅት የግብጹ ሊቀ ጳጳስ ብጹኡ ወቅዱስ አቡነ ሽኖዳ እያስተማሩ ባሉበት ወቅት በዙ ጥያቄዎች በጹሑፍ ይደርሳቸው ነበር። ታዲያ ከነዛ ጹሑፎች መካከል አንዱ እንዲ ይላል
... አባቴ እኔ ታላቅ የመርሳት ችግር አለብኝ ያደረኩትን የሰማሁትን ነገሮች በሙሉ እረሳቸዋለው እና አባቴ ምን እንደማደርግ ይምከሩኝ ነበር የሚለው። ብጹእነታቸውም ልጄ መምከሩንስ እመክርሃለሁ ምን ማድርግ እንዳለብህ እነግርሃለሁ ግን እንዳትረሳው እፈራለሁ አሉት ይባላል።
ቃለ እግዚአብሔር ስንሰማ በማስተዋል ልቦናችንንም ሰብስበን ሊሆን ይገባል።
በነገሮችም ሁሉ አስተዋዮች ልንሆን ይገባል።በዚህም ማስተዋል እና ጥበብን ወደሚሰጥ አምላክ አጥብቀን ልንማጸን ይገባናል።

@aleroe
ለሀሳብ አስተያየት @Aleroebot
ኤልሮኢ:(ስነፅሁፍ)

ሩጫ ✞............🏃🏃🏃🏃

ማልያህን ታጠቅ
ቀበቶህን አጥብቅ
ጫማህን አጠባብቅ
መስመርህን ጠብቅ
አትይ ወደ ኋላ
ተብሎ ተነግሮን
ጀምረን ሩጫ
ለመቀበል ዋንጫ
እኛ ዞርን ስናይ
እነሱ ፈጠኑ
ከሽልማት ጌታ ጽዋም ተቀበሉ።

@aleroe
ለሀሳብ አስተያየት @Aleroebot
Forwarded from "ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" (Tesfabel)
ተግበራዊ ክርስትና.pdf
987.1 KB
ትምህርት

ተግባራዊ ክርስትና
ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ ተርጉሞ እንዳዘጋጀው

አውቀው ለማሳወቅ ይትጉ
share ያድርጉ

@aleroe
ለሀሳብ አስተያየት @Aleroebot
Forwarded from "ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" (Tesfabel)
ኤልሮኢ:(ብሂለ አበው)

+ የአባቶች ድንቅ ጥበብ የተሞሉ መልሶች +

ባለ ብዙ ታሪኩ የወሊሶው ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ ያጠምቁና ያስተምሩ በነበረበት ሥፍራ አንድ በትዕቢት መንፈስ የሚሰቃይ ወጣት መጣና መፈክርነት ያዘለ ቃል ተናገረ:: ክብር ይግባትና ንግግሩ የድንግል ማርያምን ዘላለማዊ ድንግልና የሚቃወም ነበር::

ወደ አባ ዲዮስቆሮስ ቀርቦ እንዲህ አላቸው :-
ወጣቱ :- "ድንግል ማርያም እኮ ብዙ ልጆች አሉአት"
አቡኑ :- "ባታውቀው ነው እንጂ ለአንተም እኮ እናትህ ናት!"

💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠

የቦሩ ሜዳው መምህር አካለ ወልድ ከሌሎች ሊቃውንት ጋር ኢየሩሳሌምን ሲሳለሙ ድንገት የሌላ ሀገር መነኮሳት መጥተው በዱላ አጣደፉአቸው:: ነገሩን ሲጠይቁ ለምን በእግዚአብሔር ሦስትነት እንደማያምን ሰባልዮሳዊ
አንድ ጣታችሁን ብቻ ወደላይ ጠቁማችሁ ታማትባላችሁ? ለምን እንደ እኛ ሦስት ጣቶቻችሁን (እንደሚጎርስ ሰው) በአንድ ገጥማችሁአታማትቡም?" አሉና በቁጣ ጮኹ::

መምህር አካለ ወልድ በፈሊጥ እንጂ በፍልጥ የሚሆን ነገር ስለሌለ ቁጭ ብለን እንነጋገር አሉ::

"እኛ በአንድ ጣት ብናማትብም ሦስትነቱን እናምናለን:: አንድዋ ጣትም እኮ ሦስት አንጉዋዎች አሉአት:: አንድ መሆንዋ አንድነቱን ሦስቱ አንጉዋ ሦስትነቱን ያስረዳል::
የታችኛው አንጉዋ መሠረት ነውና የወልድ የመንፈስ ቅዱስ መሠረት ይሆነው የአብ ምሳሌ ነው:: የመካከለኛው በሁለቱ ህልው የሆነ የመንፈስ ቅዱስ ምሳሌ ነው : የላይኛው ጥፍር የለበሰው ደግሞ ባዕድ ሥጋን የተዋሐደ የወልድ ምሳሌ ነው:: ሀገራችሁ ሔዳችሁ አስተምሩበት" አሉአቸው

(ይህ ትርጓሜ በወንጌል አንድምታ ላይ በእግዚአብሔር ጣት አጋንንትን አወጣለሁ የሚለው በተተረጎመበት ሥፍራ ይገኛል)

💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠

ንቡረ ዕድ ክፍለ ዮሐንስን ደግሞ አንድ ወጣት መጥቶ
"ለእግዚአብሔር የአምልኮ ለቅዱሳን የጸጋ ስግደት እንደሚሰገድ አውቃለሁ:: ግን በቅዱሳን ሥዕል ፊትና በፈጣሪ ፊት ስሰግድ እንዴት ለይቼ የጸጋ የአምልኮ እያልኩ መስገድ እችላለሁ?" አላቸው
ንቡረ ዕድ መለሱ
"አንተ ዝም ብለህ ስገድ እነርሱ የድርሻቸውን ይወስዳሉ!"

💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠


አቡነ ሺኖዳ ከሾፌራቸው ጋር ሲሔዱ ሾፌሩ መኪናውን ከመጠን በላይ አበረረው
ፓትርያርኩ እንዲህ አሉ
"ልጄ ስለምንቸኩል ቀስ በል”

💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠

አንድ ታላቅ የጉባኤ መምህር ተጠየቁ
"ካህናት ዶሮና በግ ወዘተ ማረድ የማይችሉት ለምንድን ነው?"
"የክርስቶስን ሥጋና ደም የሚፈትት ካህን እንደ ኦሪት ካህን የእንስሳ ደም አያፈስስም"
"ካህናቱስ መልካም ሴት ልጅስ ማረድ ለምን ትከለከላለች?"
"ሕይወት የምትሠጥ ሴት ሕይወት አታጠፋም"

💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠

አለቃ ለማ ልጃቸውን ለምን በጣም እንደሚገርፉት ተጠየቁ
"ልጄን እኔ ካልቀጣሁት እግዚአብሔር ይቀጣብኛል
የእግዚአብሔር ቅጣት ደግሞ ሞት ነው"

💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠

አንዱ መጥቶ አንድን የመጽሐፍ መምህር
"ጥምቀት ጋድ አለው ወይ?" አላቸው
እርሳቸውም መለሱ
"አምና ነበረው የዘንድሮን እንጃ"

💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠

አቡነ ዮሐንስ አንድን ሥራ ፈቶ የአብነት ተማሪዎችን
ሲማሩ ከሩቅ የሚያይ ወጣት አዩና
"አንተ አትማርም ወይ?" አሉት
"አይ አባቴ ምን እየበላሁ ልማር ብለው ነው?" አለ እየተቅለሰለሰ
አቡኑ መለሱ
"አሁን ምን እየበላህ ነው የምትደነቁረው?"

💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠

አቡነ ጎርጎርዮስ በዝዋይ ሳሉ አንድ ወጣት ሰርቆ ሲያመልጥ አባርረው ይዘው ሰዎች አመጡላቸው
ዕቃው ከተመለሰ በኁዋላ ሌባውን ለሕግ አሳልፈው ሊሠጡ ሲቸኩሉ አይሆንም አሉአቸው:: ሰዎቹ ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኝ ወደ ፖሊስ እንውሰደው አሉአቸው
እርሳቸውም መለሱ
"ኦርቶዶክሶች ተሰራርቀው ተካስሰው መጡ ከሚል ስም ውጪ ምንም አናተርፍም"

💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠

ብፁዕ አቡነ ሰላማን አንዱ ባለ ሥልጣን ጉዳይ ሊያስፈጽሙ በሔዱበት ቢሮው "አንተ" ብሎ በማናገር ሊያቃልላቸው ሞከረ::
እርሳቸው እንዲህ አሉት
"የቤተ ክርስቲያኔን ጉዳይ ፈጽምልኝ እንጂ እንኩዋን አንተ ቀርቶ አንቺም ብለህ ጥራኝ

💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠💠

የደርግ መንግሥት እንዳሻው ሊዘውራቸው ተስፋ ያደረገባቸው ፓትርያርክ አቡነ ተክለ ሃይማኖትን በመሪው አማካኝነት እንዲህ ሲል ጠየቃቸው
"የቅድስት ሥላሴ ካቴድራልን ወደ ሙዝየምነት የመቀየር ሃሳብ በመንግሥት በኩል ተይዞአል:: ይህንን ለማድረግም የእርስዎን ድጋፍ የግድ ነው"
ፓትርያርኩ መለሱ
"ምን ችግር አለ በቅርቡ የዓመቱ ሥላሴ ክብረ በዓል ስላለ ሕዝቡ ባለበት እናንተም ተገኝታችሁ አብረን ለምን አናወያየውም"
በዚህ ምላሽ ምክንያት እቅዱ ተሠረዘ

@aleroe
ለሀሳብ አስተያየት @Aleroebot
Forwarded from "ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" (Tesfabel)
ኤልሮኢ:(ትምህርት)

የሰንበት ት/ቤት

እግዚአብሔር አምላክ የሰውን ልጅ በአርያውና በአምሳሉ ከፈጠረ በኋላ ሰው ከፈጣሪው ጋር በጥብቅ እንዲናገናኝ ልዩ ልዩ የአገልግሎት መንገዶችን አዘጋጀ። እያንዳንዱ በተሰጠው መክሊት ያተርፍና በጸጋው ያገለግል ዘንድ በመጀመርያ ዕድሜው በፈቀደለት ሁሉ መማርና ማገልገል ይኖርበታል። እግዚአብሔር አምላክ መመለክ በአለበት አግባብ ለማምለክ እምነት ያስፈልጋል፤ ከእምነት እንዳንወጣ ደግሞ ስለምናምነው ነገር በቂ ዕውቀት ሊኖረን ይገባል፤ እምነትን፣ ተስፋና ፍቅርን ሰንቆ እስከመጨረሻ ድረስ ለመጽናት መንፈሳዊ ዕውቀት መሠረታዊ ነው።

“ህዝቤ ዕውቀት በማጣት ጠፍቷል” (ሆሴ 4፥6) የተባለው በእኛ ላይ እንዳይፈጸም ዕድሜያችን በሚፈቅድልን ሁሉ ሃይማኖታዊ ዕውቀትን እንድንማር ቤተ ክርስቲያን በቅዱሳን ጸሎት በእግዚአብሔር መልካም ፍቃድ ሰንበት ት/ቤትን አቋቋመች። ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ልጆቿ ጽድቅን ይማሩ ዘንድ በሰንበት ት/ቤት አሰባስባ ቃለ እግዚአብሔርን አውቀው፣ ባሕርየ እግዚአብሔርን ተረድተው እንዲያመልኩ፣ ሕጉን ጠብቀው፣ በሃይማኖት፣ በምግባርና በትሩፋት ፀንተው አምላካቸውን መስለው እንዲኖሩ የእርሱ የሆነችውን መንግስተ እግዚአብሔርን እንዲወርሱ በብሉይ ከአምላኳ የተቀበለችውን ሕግጋተ እግዚአብሔርን አስተምራ በሐዲስ ኪዳንም በ40 እና በ80 ቀን እያጠመቀች ለምዕመናን እንደ እድሜያቸው እና እንደ አዕምዕሮ ብስለታቸው ቃለ እግዚአብሔርን ደከመኝ ሰለቸኝ ሳትል ታስተላልፋለች። በስብከት፣ በዝማሬ፣ በቅዳሴ፣ በስዓታት፣ በማሕሌት የቅኔውን ምሥጢር በትርጓሜ እያስተማረች ምዕመናንን በእምነት አንፃ ለመንግስተ ሰማያት እያዘጋጀች ዛሬ ላይ ደርሳለች።

ከስሙ እንደምንረዳው ሰንበት ትምህርት ቤት ማለት የጾታ ልዩነት ሳይደረግ የቤተ ክርስቲያን ተተኪ ትውልድ ወይም መንፈሳዊ ወጣቶች በዕለተ ሰንበት፣ በዓበይት በዓላትና አመቺ በሆነ ጊዜ ሁሉ በአጥቢያ ቤተ ክርስቲያን እየተገኙ የቤተ ክርስቲያንን ዶግማ፣ቅኖና፣ሥርዓትና ትውፊት የሚማሩበት እና በእምነት፣በምግባርና በሃይማኖት ጸንተው ይኖሩ ዘንድ መንፈሳዊ ሕይወታቸውን የሚያጠነክሩበት ትምህርት ቤት ነው:: መንፈሳዊ ወጣቶች የሚባሉት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ትምህርተ ሃይማኖት፣ ሥርዓትና ትውፊት በዕድሜ ክልላቸው የሚማሩ የቤተ ክርስቲያን አባላት ናቸው (ቃለ ዓዋዲ ፲፱፻፺፩)።

በመጽሐፍ ቅዱስ ሰንበት ት/ቤት ተብሎ የተፃፈ ቀጥተኛ የሆነ ስም ባይገኝም ዛሬ ላይ በሰንበት ት/ቤት የሚተገበረው መንፈሳዊ አገልግሎት ማለትም ልጆችን በቤተ እግዚአብሔር ማስተማር በብሉይ ኪዳን ዘመንም ይፈጸም እንደነበር መጽሐፍ ቅዱስ ያስረዳናል። የሰንበት ት/ቤት ፅንሰ ሀሳብም ከዚያ የመነጨ ነው። “እነዚህን ቃሎች በልባችሁና በነፍሳችሁ አኑሩ እነርሱንም ለምልክት በእጃችሁ ላይ እሠሯቸው በዐይኖቻችሁም መካከል እንደ ክታብ ይሁን ልጆቻችሁንም አስተምሯቸው በቤትህም ስትቀመጥ በመንገድም ስትሄድ ስትተኛም ስትነሣም አጫውቱአቸው” (ዘዳ 11÷18-21 )በማለት እስራኤላውያን ልጆቻቸውን ሕግጋተ እግዚአብሔር እንዲያስተምሯቸው ታዘዋል፡፡ እነርሱም ይህን አምላካዊ ቃል ተግባራዊ ለማድረግ ልጆቻቸውን ወደ ቤተ እግዚአብሔር እየላኩ እና በቤታቸው ውስጥም ተግተው ያስተምሩ ነበር።

በሐዲስ ኪዳንም መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ሥጋዌ ልዩ ትኩረት ከሰጣቸው ቁም ነገሮች መካከል ሕፃናት ወደ ቤተ ክርስቲያን ይመጡ ዘንድ ነበር። ልበ ንጹሐንን በሕጻናት መስሎ ያስተማረበት አንቀጽም በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ ተጽፎ ይገኛል። ይህም በዘመናችን ላለችው ቤተ ክርስቲያን የሕፃናት፣ የወጣቶች እና የጎልማሶች ማስተማሪያ ለሆነችው ሰንበት ትምህርት ቤት መነሻ የሆነ እና መሠረቱም መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሆኑን ያረጋግጥልናል (ማቴ 18፥3፣ 21፥16፣ ማር 9፥37)፡፡

የሰንበት ትምህርት ቤት አመሠራረት በኢትዮጵያ ስንመለከት ዘመናዊ ትምህርት ቤት እየተስፋፋ ሲመጣ ወጣቱ ትውልድ ከአምልኮተ እግዚአብሔር እንዳይለይ፤ በተለይ ለዘመናዊ ትምህርት አስተማሪነት በመጡ እራሳቸውን ”ኢየሱሳውያን” ብለው በሚጠሩ የውጭ መምህራን ከመጡበት ዓለማዊ ትምህርት ባሻገር የኑፋቄ ትምህርት ማሰራጨታቸው፣ በተቃራኒው ደግሞ ወደ አብነት ትምህርት ቤት የሚሄደው ወጣት ቁጥር በመቀነሱ ምክንያት በ20ኛው ክፍለ ዘመን ወጣቱን ለመያዝ መንፈሳዊ መርሐ ግብሮችና የማኅበራት እንቅስቃሴዎች ተጀመሩ። እነዚህ የተጀመሩ መርሐ ግብሮችና ማኅበራት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮዎቿ ሳይበረዙ ለትውልድ እንዲተላለፉ በተለይ በሕጻናት እና በወጣቶች ላይ ትኩረት ሰጥው እንዲሠሩ ትልቁን ድርሻ ወስደዋል።

በዚህም መሠረት ሰንበት ትምህርት ቤት በማቋቋም ትውልድን በኦርቶዶክሳዊ ሃይማኖት የማነጽ፣ ዶግማን፣ ቀኖናን እና ትውፊትን ማስተማር ተጀመረ። በ1960 ዓ.ም ይህን የሰንበት ትምህርት ቤቶች እንቅስቃሴ ለማስተባበር እና ለማጠናከር ይቻል ዘንድ በጠቅላይ ቤተ ክህነት በስብከተ ወንጌልና ማስታወቂያ መምሪያ ሥር ማእከላዊ ጽ/ቤት በዋናነት ተቋቁሞ ስያሜውም የሰንበት ት/ቤት መምህራን ጽሕፈት ቤት ተብሎ ተሰይሟል፡፡ ይህ አካሄድ እያደገ ሲመጣ በ1965 ዓ.ም ራሱን ችሎ ወደ ወጣቶች ጉዳይ መምሪያነት እንዲያድግ ተደርጓል፡፡ ዛሬ ላይ የሰንበት ትምህርት ቤት ማደራጃ መምርያ የሚል ሰንበት ትምህርት ቤቶችን የሚያደራጅና የሚመራ በተቋም ደረጃ ትልቅ መምርያ ተቋቁሞ አገልግሎቱን እየፈጸመ ይገኛል።

የሰንበት ት/ቤት ጥቅሙና አስፈላጊነቱ የጎላ መሆኑ በተግባር በመረጋገጡ በ1970 ዓ.ም “ሰንበት ት/ቤት” በሚል ስያሜ ሕጋዊ ሆኖ እንዲቀጥል እና በሁሉም አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ ሰንበት ት/ቤቶች እንዲቋቋሙ የተቋቋሙትም እንዲጠናከሩ ተሻሽሎ በወጣው ቃለ ዓዋዲ እንዲጸድቅ ተደርጓል፡፡ የሰ/ት/ቤት አገልግሎትን የበለጠ ለማጠናከር ሰንበት ት/ቤቶች የሚመሩበትን መተዳደሪያ ደንብ አጽድቆ ሥራ ላይ እንዲውል ያደረገ ሲሆን አሁን አስካለንበት ዘመን ድረስ ሰንበት ት/ቤቶች ይህን መመሪያ ከዋናው ቃለ ዐዋዲ ጋር በማስተባበር እየተመሩበትና ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶችን እየፈፀሙ ይገኛሉ፡፡

ይህን ወጣቱን ትውልድ በዘመናዊነት ተፅዕኖ ውስጥ ወድቆ ከመንፈሳዊ ሕይወት እንዳይወጣ ልዩ ክትትል በማድረጉ ረገድ ኢትዮጵያ ብቻ ሳትሆን እኅት አብያተ ክርስቲያናትም ሰንበት ትምህርት ቤትን አቋቁመው አገልግሎት መስጠት ከጀመሩ ብዙ ዓመታትን አስቆጥረዋል። በተለይ ግብፅና ሕንድ በተደራጀ መልኩ እየሠሩበት ይገኛሉ።

የሰንበት ትምህርት ቤት የተቋቋመበት ዋና ዓላማ

የሰንበት ትምህርት ቤት ዓላማ፦

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ዶግማ፣ ቅኖና፣ እምነትና ሥርዓት ተጠብቆ ሳይበረዝ ሳይከለስ ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲተላለፍ ማድረግ

ማንኛውም የቤተ ክርስቲያኒቱ ተከታይ የሆነ ምእመን የሃይማኖቱን ሥርዓት በውል እንዲያውቅና እንዲረዳ ማድረግ

ወጣቶች የቤተ ክርስቲያንን ሕግና ሥርዓት ተምረው ለሀገርና ለወገን ጠቃሚ፣ መልካምና በሥነ ምግባር የታነፁ ዜጎች እንዲሆኑ ማድረግ

በጉብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ (መክ. ፲፪፡፩) የሚለውን የአምላክ ተእዛዝ ወጣቶች እንዲፈጽሙ ማስቻል

እነዚህን ከላይ የተዘረዘሩትን አበይት ዓላማዎች ከግብ ለማድረስ ጠንካራ ሰንበት ትምህርት ቤት ያስፈልጋል። ወጣቶችን በሰንበት ትምህርት ቤት ለማሳደግ ከጠቅላይ ቤተ ክህነት እስከ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉም ባለ ድርሻ አካላት የበ
Forwarded from "ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" (Tesfabel)
ኤልሮኢ:(ስነ ፅሁፍ)

አሻግሪኝ

ውሻን አጠጥተሽ በወርቅ ጫማ ውሃ፡
ጠማሽ ሆይ እናቴ ሲና ዱር በረሃ፡
ምስለ ፍቅሩ ወልዳ የብፁኃን ተስፋ፡
ወደ ግብፅ ወረደች ስደት ልጃን ታቅፋ፡
የመለኮት ድንኳን የእሳት መጋረጃ፡
እንዴት ይለብልባት የሐሩር ምድጃ፡
የሰሎሜ ትእግስት የዮሴፍ ትህትና፡
ነይ ነይ ማርያም ባንቺ መንገዴ ይቅና፡
ከምድር ባይገኝ የውበትሽ ደም፡
እንደ ፀኃይ በራሽ ቤዛይት አለም፡
ብሎ ቢከተልሽ ሙት ስጋው ለአዳም፡
ከሰው ፊት ኮብልለሽ ገባሽ ወይ ቁስቋም፡
በእንባሽ ነይ እጠቢኝ እናቴ ማርያም፡
የፅጌ ውዳሴ ምስማከ ነሽ ፅዮን፡
ስምሽን ስጠራው ብዬ እመብርኅን፡
ከጨለማ ኣውጥተሽ አሻግሪኝ በቀን።

@aleroe
Forwarded from "ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" (Tesfabel)
ኤልሮኢ:(የአበው ታሪክ)

#ቅዱስ_ጐርጐርዮስ_ዘአርማንያ

ይህ ቅዱስ አባት ከሰማዕታት: ከጻድቃን: ከሊቃውንትና ከዻዻሳት ዝርዝር ውስጥ ይገኛል:: በቤተ ክርስቲያንም ዓበይት ከሚባሉ አበው አንዱ ነው:: ቅዱስ ጐርጐርዮስ ሮማዊ ሲሆን ከክርስቲያን ወላጆቹ የተወለደው በዘመነ ሰማዕታት (በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን) ነው::
አበው በትውፊት እንደ ነገሩን ከሆነ ቅዱሱ የታላቁዋ ሰማዕት #ቅድስት_አርሴማ ትልቅ ወንድም ነው:: በዜና ሰማዕታት ተጽፎ እንደሚገኘው በዚያ የመከራ ዘመን ቅዱስ ጐርጐርዮስ ሦስት ኃላፊነቶች ነበሩበት:-
1.ቅድስት አርሴማን ጨምሮ ደናግሉን ማጽናት
2.ትምሕርተ ቤተ ክርስቲያንን በሚገባ ማጥናት
3.የሚመጣውን መከራ ለመቀበል ራሱን ማዘጋጀት:: ቅዱሱ 3ቱንም ኃላፊነቶች በሚገባ በመወጣቱ ከራሱ አልፎ ለሌሎቹ አርአያ መሆን ቻለ:: ያቺን ንጽሕት አርበኛ ቅድስት አርሴማንም አጽንቶ የደናግሉ መሪ አደረጋት:: መከራው በጣም ገፍቶ እስከ መጣበት ጊዜ ድረስ በአንድ የደናግል ገዳም ውስጥ ሆነው ይጸልዩ: ይጾሙ: ገዳማዊ ሥራንም ይሠሩ ነበር::
ለዚህም ነው ቅድስት አርሴማና ቅዱስ ጐርጐርዮስ ጻድቃን የምንላቸው:: በሁዋላ ግን ማሕደረ ሰይጣን ዲዮቅልጢያኖስ በመልኩዋ ተማርኮ ቅድስት አርሴማን ካላገባሁ በማለቱ ቅዱስ ጐርጐርዮስ ድንግሏን አርሴማን ጨምሮ ክርስቲያኖችን ይዞ ወደ አርማንያ ተሰደደ:: በአርማንያም በአንድ ገዳም ውስጥ ተደብቀው በጾምና በጸሎት ለጥቂት ጊዜ ቆዩ: ነገር ግን ረሃብ ፈጃቸው:: የሚላስ የሚቀመስ ነገር በአካባቢው ባለ መኖሩ ቅዱስ ጐርጐርዮስ ወደ ከተማ ለመውጣት ተገደደ:: በዚያም በድርጣድስ ቤተ መንግስት ውስጥ ባርነት ተቀጠረ:: በሚያገኛት ገንዘብም ወገኖቹን ይረዳ ነበር:: መከራው ግን አለቀቃቸውም:: ርጉም ዲዮቅልጢያኖስ ቅዱሳኑ ወደ አርማንያ መሔዳቸውን ስለ ሰማ ይዞ እንዲልክለት ድርጣድስን ላከው:: ድርጣድስ ግን ቅድስት አርሴማን ባያት ጊዜ ከውበቷ የተነሳ መታገስ ባለመቻሉ "ካላገባሁሽ" አላት:: ድንግሊቱ ግን "እኔ የክርስቶስ ሙሽራ ነኝ: አይሆንም" አለችው:: ሊያስፈራራት ሞከረ:: ዐይኗ እያየ ደናግሉን ጨፈጨፋቸው:: አልሳካልህ ቢለው በአደባባይ በግድ ሊያገባት ቢሞክር እጁን ጠምዝዛ በሰው ሁሉ ፊት መሬት ላይ ጣለችው:: እጅግ ስላፈረ አስገረፋት: አሰቃያት: ዐይኗንም አወጣ:: በመጨረሻም አንገቷን አስቆርጦ ከሰማዕታቱ ጋር ተራራ ላይ ጣላት::
ወዲያው ደግሞ የቅዱስ ጐርጐርዮስ ማንነቱ በመታወቁ ይዘው አካሉ እስኪያልቅ ገረፉት:: በእሳትም አቃጠሉት:: በብዙ ስቃይም አሰቃዩት::
በመጨረሻ ግን ከነ ሕይወቱ እንዲቀበር ተወሰነበት:: ወደ መጸዳጃ ቤት ወስደውም ከነ ሕይወቱ ቀበሩት:: ነገር ግን የእግዚአብሔር መልአክ ወርዶ መተንፈሻ ቀዳዳን ሠራለት:: አንዲት ሽማግሌ ክርስቲያንም በዚያች ቀዳዳ ቂጣ እየጣለችለት ለ15 ዓመታት ተቀብሮ ኖረ:: አካሉና አፈሩ ተጣበቀ:: እርሱ ግን ፈጣሪውን እያመሰገነ ቆየ:: ከነገር ሁሉ በሁዋላ ድርጣድስና ባለሟሎቹ ለአደን በሔዱበት ርኩስ መንፈስ ወደ አውሬነት (እሪያነት) ቀየራቸው:: የንጉሡ እንስሳ (አውሬ) መሆን በአርማንያ ታላቅ ድንጋጤን ፈጠረ:: የንጉሡ እህት ስታለቅስ በራዕይ "ለእመ ኢያዕረግምዎ ለጐርጐርዮስ አልብክሙ ድኂን - ጐርጐርዮስን ከተቀበረበት ካላወጣችሁት አትድኑም" አላቸው:: ወዲያውም በዚያች ሽማግሌ መሪነት ቆፍረው አወጡት:: አካሉንም እግዚአብሔር መለሰለት:: ቅዱሱ እንደ ወጣ ዕረፍትን አልፈለገም:: ለ15 ዓመታት ቀባሪ አጥቶ የተበተነውን የቅድስት አርሴማንና የሰማዕታቱን አጽም ሰብስቦ በክብር አኖረው:: ድርጣድስና ባለሟሎቹንም ወደ በርሃ ሒዶ ፈወሳቸው:: ወደ ሰውነትም መልሶ መላ አርማንያን ወደ ክርስትና መለሰ:: የንጉሡን እግር ግን የአውሬ አድርጐት ቀርቷል:: በመጨረሻም ቅዱስ ጐርጐርዮስ የአርማንያ ሊቀ ዻዻሳት ሆኖ ተሹሞ ብዙ መጻሕፍትን ደረሰ:: ከ318ቱ ሊቃውንትም አንዱ ሆኖ ተቆጠረ:: ዕረፍቱ ታሕሳስ 15 ቀን ነው።

@aleroe
Forwarded from "ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" (Tesfabel)
ኤልሮኢ:(ግጥም)

ንግስና እንዴት ነበር?

ንግስና እንዲህ ነበር ተኝቶ በራዕይ
እዛሬ ላይ ሁኖ የነገው ንግስና በህልም የሚታይ
በወንድም ተሽጦ በባርነት ኑሮ
ባላደረገው ላይ ፍርድ ሸንጎ ውሎ
የታየው ራዕይ እውን እንደሚሆን ልቡ ስላመነ
መጣል መገፋቱን አምኖ ይሁን አለ
መመረጥስ እንዲህ መሾምስ እንዲህ ነው
ዮሴፍ የነገሰው ምድረ ግብፅ ላይ ነው

ሙሴ እንዴት ነገሰ?
ሙሴ የተሾመው ከማህጸን ነበር
ፈርኦን ነግሶ ህዝቦችን ሲያሸብር
እስራኤልን ገዝቶ በባርነት ቀንበር

እናም
እናም በዛ ጊዜ
ወልዶ መቅበር እንጅ ማቀፍ እኮ የለም
የራሔል እንባ ግን መሬት ፈሶ አልቀረም
እግዜሩም ጠራና ሙሴን እንዲህ አለ
ህዝቦቸን እንዲለቅ መልዕክት ንገር አለ
ቅንና የዋሁ ሙሴም እንዲህ አለ
እንዴት ነጻ ላውጣ ህዝብህን አድኜ
እኔ አፌ ኮልታፋ በምን አንደበቴ ንጉሥ አሳምኜ
ለእስራኤላውያን የነጻነት ቀን ሲመጣ
ሙሴም በእምነት ህዝቡን ይዞ ወጣ
ከጠራው አምላክ ጋር እየተማከረ
ህዝቡን ለማሻገር ባህርን ከፈለ
በምድረ በዳ ላይ መናን ተቀብሎ ዘመን ተሻገረ

ዳዊት እንዴት መጣ?
ከበረት ተወልዶ እረኛ የሆነው የላይኛው ጌታ
ከእረኝነት ጓዳ ዳዊትን መረጠው ጎልያድ እንዲረታ
ሳኦል የነገሰው ህዝቡ ጠይቆ ነው
የሳኦል ንግሰቱ መንገድ መጥረጊያ ነው
የዳዊት ንግስና ከአምላክ ንግስና ጋር ምሳሌው አንድ ነው
እረኛ ነበረ ዳዊት ሳይጠራ
የነገሰ ጊዜ እንደ ልቤ ተብሎ በአምላኩ ተጠራ

የአሁኑስ እንዴት ነው?
ንጉሱ ባሉበት ግብር ይበላሉ?
መሪና ተመሪ ይተዋወቃሉ?
ንግስናው ከየት ነው?
ምንጩስ ከወዴት ነው?
ንጉስ የሆነውስ ለየቱ ወገን ነው?
ለዛኛው ወገንስ ንጉሥ የትኛው ነው?

መሪማ ሙሴ ነው
ህዝቤ ከሚጠፋ እኔ ልጥፋ ያለው
ልጥፋ ያለው ደግሞ ከሕይወት መዝገብ ነው

የአሁኑ ንጉስስ

ምን ብሎልን ይሆን ምንስ ሲል ተሰማ
ምንም አይበልልን ምንም ሲል አንስማ

ይልቅ ይልቅ

አምላካችን ታርቆን ታሪክ በታደሰ
ሙሴያችን በመጣ ዳዊት በነገሰ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር!

@aleroe
ሰላም የእግዚአብሄር ቤተሰቦች በዚህ መንፈሳዊ ግሩፕ እና ቻናል ላይ አባል የሆናችሁ በሙሉ እንደምትመለከቱት ከጊዜ ወደ ጊዜ የአባላቱ ቁጥር እየቀነሰ ነው ስለዚህም ሁላችሁም link ሼር በማድረግ እና member add በማድረግ ወንድም እህቶቻችሁን ጋብዙ ይህን ስታደርጉ ወንድም እህቶቻችንን አልባሌ ፅሁፎችን ከማንበብ እንደምትታደጓቸው በማሰብ ችላ አትበሉት ።

ሰላመ እግዚአብሄር አይለያቹ !!!
Forwarded from "ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" (Tesfabel)
ኤልሮኢ:(ትምህርት)
ይህን ያውቁ ኖሯል?

ለሰባኪያን መቆሚያ ከፍ ያለ ቦታና አትሮንስ በቤተክርስቲያን መጠቀም የተጀመረው ከ386 ዓ.ም አከባቢ ባለው ዩሐንስ አፈወርቅ ነው። ቅዱስ ዩሐንስ አፍወርቅ ቀሚያስተምርበት ጊዜ ሕዝቡ በብዛት ይሰበሰብ ነበር። ነገር ግን የዩሐንስ ቁመት አጭር ነቀረና ከፍ ብሎ ለሕዝብ እንዲታይና ድምፁም እንዲሰማ መቆሚያ ስፍራና ያጽሐፍት ማንበቢያ አትሮንስ ተሰራች። ቤተክርስቲያንም ከዚያ ዘመን ጀምሮ አትሮንስን ትጠቀምበት ጀመር።

ኑዛዜ በቤተክርስቲያን የተጀመረው ሕጋዊና ድንግል ከሆነው የእስክንድርያ 12እኛ ፓትራያርክ ከአባታችን ከቅዱስ ድሜጥሮስ ወዲህ ነው።አባታችን በከንቱ አምተውት የነበሩ ምእመናን በእግዚአብሔር ፋቃድ ክብሩ ቀተገለጠላቸው ጊዜ አባታችን ይቅርበለን ብለው ንስሐ ሲገቡ ይፍትሕ ይኅድግ ብለው ናዝዘዋል። ኑዛዜም ያን ጊዜ ተጀምሯል።

አንገት ላይ ማተብ ማሰር የተጀመረው ቀን5ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በሶርያ ያስተምር በነበረው በአባታችን በያዕቆብ ዘእልበረዲ ነው። አባታችን እያስተማረ በሚያጠምቅበት ጊዜ ለተጠመቁትና ያልተጠመቁት እየተቀላቀሉ ቢያስቸግሩት ለማየት ይቻል ዘንድ ለተጠመቁት ምዕመናን ማተብ ያስርላቸው ነበር። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ማተብ ለተጠመቁ ክርስቲያኖች መለያ ምልክት ሆነ።

@aleroe
እንኳን አደረሳችሁ
Forwarded from "ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" (Tesfabel)
ኤልሮኢ:(ምክረ አበው)

የአንድ አባት ምክር

በአንድ ወቅት በዳጋ እስጢፋኖስ ገዳም ተገኚቼ ነበር፡፡ በዚያ ገዳም የሚኖሩ አባት የነገሩኝ ነገር ለሕይወት መመርያ የሚሆን ነው፡፡ አሁን ከደረስንበት ወቅት ጋር የሚሄድ ነውና ላካፍላችሁ፡፡

በወቅቱ እንደ ዛሬው በቤተ ክርስቲያን ላይ የፈተና ማዕበል ተነሥቶ ነበር፡፡ ያ ወቅት የፖለቲካው ማዕበልም እጅግ ያየለበት ጊዜ ነው፡፡ አንዳንዶቻችን በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የምንሰጠው አገልግሎት ምን ፋይዳ ይኖረዋል? ምንስ ለውጥ ያመጣል? ችግሩ እንደሆነ እየባሰው እንጂ እየተሻለው አልሄደም፤ ታድያ ጊዜያችንን፣ ገንዘባችንን እና ዕውቀታችንን ዝም ብለን እየከሰከስን ይሆን? አሁን የኛ ልፋት የክፉ ሰዎችን ክፋት ለመሸፈን እና በክፋታቸው እንዲቀጥሉ ለማድረግ ካልሆነ በቀር ችግሩን ይፈታዋል? ወዘተ፣ ወዘተ፣ ጥያቄዎች ይነሡ ነበር::

ያን ጊዜ እኒህ አባት እንዲህ አሉን፡፡

«ብዙ ልጆችን የወለደች የምትወድደው ባሏ የሞተባት አንዲት እናት ነበረች፡፡ ቤተ ዘመዶቿ ምንም ሳይራሩ ያለ ፍላጎቷ ለአንድ ክፉ ባል አጋቧት፡፡ ይህ ባል ግዴለሽ፣ ገንዘብ ወዳድ፣ ጠጥቶ ከመስከር፣ በልቶ ከመጥገብ፣ በስተቀር ሌላ ሞያ የለውም፡፡ ሲወጣ ሲገባ ይደበድባታል፡፡ እንጨት ሽጣ፣ ኩበት ለቅማ፣ እንጀራ ጋግራ፣ ጠላ ጠምቃ ያጠራቀመቻትን ገንዘብ ነጥቆ ይወስድባታል፡፡ ለዘመዶቹም ይበትነዋል፡፡

የት ትሂድ? የሠፈሩ ሕግ፣ ባህሉ እና ልማዱ፣ በሙሉ የእርሷን ሮሮ እና ልመና የሚሰማ አልሆነም፡፡ እርሱን እንደ ሕጋዊ ባልዋ ነው የሚቆጥሩት፡፡ የት ሂዳ መከራዋን ትናገር፡፡ የትስ ሂዳ ከችግሩ ትገላገል?

ይህ ክፉ ባልዋ እርሷን ብቻ ሳይሆን ልጆቿንም ያሰቃያቸው ነበር፡፡ እነርሱም በዚያ ቤት ውስጥ መከራውን እና ስቃዩን፣ ረሃቡን እና ጭቅጭቁን እየሰሙ መኖር መረራቸው፡፡ በዚያ ቤት ሰላም ጠፋ፡፡ ፍቅር ጠፋ፡፡ ምንጊዜም የሚሰማው ክፉ ነገር እና ልብ የሚያደማ ነገር ሆነ፡፡ ሰው ሁሉ ስለዚያ ቤት ያወራል፡፡ መንገድ ላይ ሲያገኛቸው ስለ ቤታቸው ይጠይቃቸዋል፡፡ እነርሱም በሃፍረት ይሸማቀቃሉ፡፡ ስለዚህም እናታቸውን ጥለው ወደ ሌላ ቦታ መሄድና ስለዚያ ቤት ከማያስቡበት እና ከማይሰሙበት ቦታ መድረስ ፈለጉ፡፡ የሚችሉትን ያህል እየሠሩ፣ ለራሳቸው የሚበቃቸውን እየኖሩ፣ መከራውን መገላገል እና እፎይ ብለው መኖር አሰኛቸው፡፡

ታድያ ይህንን ሃሳባቸውን ለአንድ ሽማግሌ ጠቢብ ሰው ነግረው ገንዘብ እና ሃሳብ እንዲሰጣቸው ፈለጉ፡፡ ሄደውም አማከሩት፡፡ ያም ሽማግሌ ሃሳባቸውን ሁሉ ከሰማ በኋላ እንዲህ አላቸው፡፡

«ልጆቼ ልክ ናችሁ ሩቅ ሀገር ሄዳችሁ፣ የምትችሉትን ያህል እየሠራችሁ፣ የራሳችሁን ኑሮ በመኖር ችግሩን ሁሉ መርሳት እና መገላገል ትችላላችሁ፡፡ ምን ያስጨንቃችኋል? ቤት ያለው እዚህ ብቻ ነው እንዴ? ሀገርስ ያለው እዚህ ብቻ ነው እንዴ? ግን አንድ ነገር አስቡ፡፡ እንዲህ ማድረጋችሁ ራሳችሁን ብቻ ከችግሩ ታወጣላችሁ እንጂ ችግሩን አትፈቱትም፤ እናንተ ችግሩን ትረሳላችሁ እንጂ ችግሩን አታስወግዱትም፡፡

«ደግሞም የእንጀራ አባታችሁ እናታችሁን የበደለውን ያህል እናንተም ትበድሏታላችሁ፡፡ እስኪ አስቡት ለዚህች ለእናታችሁ ከእናንተ በቀር የደስታዋ ምንጭ ማን ነው? ሁሉም ነገርዋ የሚያሳዝን እና የሚያስመርር ነው፡፡ እናንተ ግን የደስታዋ ምንጮች ናችሁ፡፡ የእንጀራ አባታችሁ እናታችሁን ያሳዝናታል፤ የእናንተ ጥላችኋት መሄድም ያሳዝናታል፤ እርሱ ብቻዋን እንድትለፋ ትቷታል፤ እናንተ ጥላችኋት ስትሄዱም ያለ አጋዥ ትተዋታላችሁ፤ እርሱ በመስረቅ ዘረፋት፣ እናንተም ባለ መስጠት ዘረፋችኋት፤ ታድያ ከእርሱ በምን ተሻላችሁ?

እናንተኮ ያሰባችሁት ለእናታችሁ ሳይሆን ለራሳችሁ ነው፡፡ እናታችሁ ስለተቸገረች አይደለም ያዘናችሁት፣ ችግሩ እናንተን ስለነካ ነው፤ እናታችሁ ስለተራበች አይደለም ያዘናችሁት ረሃቡ ስለነካችሁ ነው፡፡ በእናታችሁ ላይ የደረሰው ችግሳይሆን ስለችግሩ ከየሰው አፍ መስማት ነው የሰለቻችሁ፤ ችግሩን ለመቅረፍ አይደለም መሄድ የፈለጋችሁት፤ ችግሩን ላለማየት እና ላለመስማት ነው፡፡

ከዚያ ይልቅ ሥራ ሠርታችሁ ገንዘብ አግኙ እና ለእናታችሁ ምግብ ስጧት፤ የሚያስርባትን የእንጀራ አባታችሁን በዚህ ትቃወሙታላችሁ፣ ልብሷን ቀይሩላት፣ የሚያሳርዛትን አባታችሁን በዚህ ትቃወሙታላችሁ፣ ስትታመም አሳክሟት፣ የሚያሳምማትን የእንጀራ አባታችሁን በዚህ ትቃወሙታላችሁ፤ የወግ እቃዎቹን ሰብስቡና አስቀምጡላት፤ዝክረ ታሪኳን ሊያጠፋ የተነሣውን የእንጀራ አባታችሁን በዚህ ትቃወሙታላችሁ፤ እርሱ እያረጀ ሲሄድ እናንተ ግን እያደጋችሁ ነው፡፡ ስለዚህም እየበዛችሁ እና እየመላችሁ ሂዱና ይህንን ቀፍድዶ የያዛትን የመንደሩን ሕግ አስተካክሉት፡፡ ምናልባት የእንጀራ አባታችሁ ቢሞት ሌላ የእንጀራ አባት ደግሞ እንዳይተካ፡፡ እንደዚያ ካደረጋችሁ እናንተ የእናታችሁ ልጆች ናችሁ፡፡ ያለ በለዚያ ግን የእንጀራ አባታችሁ ተባባሪዎች ናችሁ፡፡

ሸረሪት ታውቃላችሁ፡፡ ከሰው ቤት ግድግዳ ላይ ድር አድርታ፤ ወልዳ ከብዳ ትኖራለች፡፡ ቤቱ በእሳት ሲያያዝ ግን ከቤቱ ወጥታ ቀድማ የምትሮጥ እርሷ ናት፡፡ ቤቱ የኖርኩበት ነው፡፡ ወግ መዓርግ ያየሁበት ነው፤ እሳቱን በማጥፋት አስተዋጽዖ ማድረግ አለብኝ አትልም፡፡ መሸሽን ብቻ ነው የምትፈልገው፡፡ ለራስዋ ብቻ ነው የምታስበው፡፡ ይህ ከሸረሪትነቷ የመጣ ነው፡፡

እናንተ ግን ሰዎች እንጂ ሸረሪቶች አይደላችሁም፡፡ ሰዎችን እያያችሁ ከሀገራችሁ እና ከቤተ ክርስቲያናችሁ ልትርቁ አትችሉም፡፡ አያገባንም ልትሉ አትችሉም፡፡ እሳቱን ማጥፋት ትታችሁ ከእሳት ለማምለጥ ብቻ ልትሮጡ አትችሉም፡፡ ይህንን ካደረጋችሁ ሸረሪቶች እንጂ ሰዎች አይደላችሁም፡፡» አሏቸው

ይህንን ሰምተው ልጆቹ ወደ እናታቸው ተመለሱ፡፡

እስኪ እኔም አንድ ጥያቄ ልጠይቃችሁ፡፡ የዚህች ሀገር እና የዚህች ቤተ ክርስቲያን ጠላቶች ፍላጎት ምንድን ነው? ይህች ሀገር እና ይህች ቤተ ክርስቲያን ያለ ረዳት እንዲቀሩ ማድረግ አይደለምን?  እናንተም እንተዋት፣ እናቁም፣ እንሽሽ ስትሉ ያለ ረዳት እያስቀራችኋት ነው፡፡ የእነርሱ ፍላጎት ኢትዮጵያን እና ተዋሕዶን ተስፋ ማስቆረጥ አይደለምን? እናንተም ተስፋ ከቆረጣችሁ ተሳካላቸው ማለት ነው፡፡ ልጆቻቸውን እያስመረሩ ማስኮብለል አይደለምን? ከኮበለላችሁ ተሳካላቸው ማለት ነው፡፡ ታሪክን፣ ቅርስን፣ ክብርን፣ ልዕልናን መመዝበር እና ማራከስ አይደለምን? እናንተም ታሪኩን፣ ቅርሱን፣ ባህሉን፣ ክብሩን ርግፍ አድርጋችሁ ትታችሁ በራሳችሁ ዓለም ብቻ ስትቀሩ የእናንት ፍላጎት ሳይሆን የእነርሱ ፍላጎት ተሳካ ማለት ነው፡፡

ታድያ አሁን እናንተ መመለስ ያለባችሁ አንድ ጥያቄ ነው፡፡ የምትፈልጉት የጠላቶቿ ፍላጎት እንዲሳካ ነው ወይስ በመከራ ውስጥ ያለችውና ቀን የጣላት የእናታችሁ ፍላጎት እንዲሳካ ? ምረጡ፡፡

ሙሐዘ ጥበባት ዲ/ን ዳንኤል ክብረት
ማህሌት መንፈሳዊ የዩቲዩብ ቻናል

"ዛፏ አስተማረችን" መልዕክታዊ መንፈሳዊ ግጥም ይሄንን እና ሌሎች መንፈሳዊ ስነ ፅሁፎችን ለማግኘት ሊንኩን ተጫኑ 👇

https://youtu.be/GxhDSkBEW-M
https://youtu.be/GxhDSkBEW-M
Forwarded from "ኤልሮኢ ዘተዋህዶ" (Tesfabel)
ኤልሮኢ:(ምክር)

ዝምተኛው መነኩሴ (#ራስአገዝ)

ከዝምተኛው መነኩሴ አባ ዮስጦስ ፀሎት አንዱ "ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ቅዱሳን በተጓዙበት ጎዳና ምራኝ" ነበር፡፡ የዚህ ጸሎት ትርጉም ቅዱስ አድርገኝ ማለት እንደነበር በህይወታቸው ፍፃሜ በሚገባ ተረድተናል፡፡ ቅዱስ እንደሆኑ ማሰብ እንጂ ቅዱስ ለመሆን ማሰብ ወይም በቅድስና መንገድ ለመጓዝ መሻትና መጸለይ መልካም ነው፤ ምክንያቱም ከፈጣሪያችን ትእዛዛትና ፈቃድ አንዱን ለመፈጸም መመኘት ነውና እግዚአብሔርን ደስ ያሰኘዋል፡፡ እግዚአብሔር በቃሉ "እኔ ቅዱስ ነኝና እናንተም ቅዱሳን ሁኑ" እንዳለ ቅዱስ ጳውሎስም "እኔ ክርስቶስን እንደምመስል እኔን ምሰሉ" በማለት የቅድስናን ህይወት እንድንኖር እንደመከረን ስናስተውል ቅዱስ የመሆን ትእዛዝ እንዳለብን እንረዳለን፡፡ ስለቅድስና ሲነሳ እኛ ቅዱሳን ልንሆን ይገባል ማለቱ በራሱ ወደር የማይገኝለት ድፍረት ሆኖ ሳይሰማን አይቀርም፡፡ነገር ግን መሻቱ ሳይሆን የቅድስና ቁምነገር ነኝ አለማለቱ እና በጭራሽም ነኝ ብሎ አለማሰቡ ላይ ነው፡፡ ሰው ቅዱስ የሚሆነውም ከእግዚአብሔር ፈቃድ ባሻገር በምርጫውና በፍላጎቱ ነውና ይህን የሚያስረዳን ነው።

ዲያቢሎስ ስለመረጠ ከቅድስና ጎድሏል፥ ቅዱሳን መላእክት ደሞ በምርጫቸው ቅዱሳን ሆነዋል ፡፡ሰውም እንዲሁ ነው፡፡ ስለዚህ ለቅድስና መጠራታችንን እና መታዘዛችን እንዲፈጸምልን መጸለይ መሻት መጣር ያስፈልገናል፡፡የጌታችን አማናዊ ቃሉ "ለምኑ፥ ይሰጣችሁማል፤ ፈልጉ፥ ታገኙማላችሁ፤ መዝጊያን አንኳኩ፥ ይከፈትላችሁማል።"ይለናልና።(ማቴ 7:7)
ስለዚህ ቅዱስ የመሆን ፍላጎት ቅዱስ ነውና በማሰባችን ወይም በመመኘታችን ድፍረት መስሎን መጨነቅ አይደገፍም፡፡ ነገር ግን በትህትና መለመንና ሁሉም ነገር በእግዚአብሔር ቸርነት እንደሚፈጸም ማመን ነው፡፡ ያለ እግዚአብሔር ቸርነት (ሰጪነት) በጥረታችን የምናገኘው ምንም ነገር የለም፡፡ "እኔ የወይን ግንድ ነኝ እናንተም ቅርንጫፎች ናችሁ። ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉምና በእኔ የሚኖር እኔም በእርሱ፥ እርሱ ብዙ ፍሬ ያፈራል።" (ዮሐ 15:5) እንዳለ ያለእርሱ ቅዱስ መሆን ቀርቶ ቅድስናን ማሰብም እንኳን አይቻልም፤ ከእርሱጋ ግን ሁሉ ይቻላል፡፡ ወደቅድስና ከሚመሩን በርካታ ነገሮች እጅግ ጥቂቶቹ በመቀጠል ቀርበዋል፡፡

✞የእግዚአብሔርን ቸርነት እና ፍቅር ማሰላሰል

✞ህዋሳትን ኃጢአት ከመስራት መጠበቅ

✞ ለሰሩት በደል በቶሎ መፀፀት

✞ከሰው ክብርን አለመፈለግ

✞ምስጋናን አለመሻት

✞ ጥላቻንና ትችትን በፍቅር መቀበል

✞ መጸሐፍቅዱስን አዘውትሮ ማንበብ

✞ ያለማቋረጥ መጸለይ

✞በምስጢራት መካፈል

✞ትእዛዛቱን ለመፈጸም መጣጣር

✞በምክረ ንስሀ መጓዝ

✞ራስን እንደተለየ ነገር አለመቁጠር

✞ራስን መገምገም መመልከት

✞ቃለእግዚአብሔርን ማዳመጥና

✞የምንሰማዉን ቃል መፈጸም

✞ከልብ የሆነ ጾምን መጾምና መጸለይ

✞በጎ አድራጎትን መፈጸም

ማንኛውም የምንሰራው ሥራ እግዚአብሔርን ደስ እንዲያሰኝ ብሎ እንጂ አንዳች ጥቅም አገኝበታለሁ በማለት አይደለም፡፡ መሪ ምክንያቱ ፍቅር እንጂ ጥቅም መሆን የለበትም፡፡ ለቅድስና መጋደል እንጂ ቅዱስ እንደሆኑ ማሰብ መጀመር የውድቀት መጀመሪያው ሳይሆን መጨረሻ መሆኑን ማስመር ይገባል፡፡ እነኚህ በየጥቂቱ ልናድግባቸው የምንችላቸው መንፈሳዊ ተጋድሎ የሚጠይቁ ልምምዶች ናቸው ፡፡

ይቆየን!

@aleroe
ለሀሳብ አስተያየት @AleroeBot