"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ"
1.2K subscribers
26 photos
3 videos
5 files
21 links
ኤልሮኢ
"በእውኑ የሚያየኝን ጌታ አየሁት"
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ
አምላክ አሜን።
ይህ መንፈሳዊ ቻናል
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ:- +ዝማሬ
+ ምክሮች
+ ስነፅሁፎች
+ አጫጭር ትርክቶች እንዲሁም
+ ምስባክና
+ ወንጌል ይለቀቁበታል።

ለበለጠ መረጃ @AleroeBot
ግሩፑን ለማግኘት @alero
Download Telegram
ኤልሮኢ :(ዝማሬ)

#እንደ_ቸርነትህ_የንስሐ_ዝማሬ

እንደ ቸርነትህ አቤቱ ማረን/2/
እንደ ምህረትህ ይቅርታን ስጠን/2/

ከሀጥያቴም አንጻኝ ከብዙ በደሌ/2/
ለዛች ክፉ ሀጥያት እንዳልሆናት ሎሌ/2/

እኔስ አበሳዬ በደሌን ሳውቀው/2/
ከቶ የሚያድነኝ ቸርነትህ ነው/2/

አንተን ብቻ በደልኩ ክፉም አደረግሁ/2/
አሁን ይቅር በለን ከፌትህ ወደቅን /2/

ከፊትህ ወድቄ ስለምን አንተን ስማጸን አንተን
መውደቄን ተመልከት አምላከ ብርሀን አምላከ ሰላም

@aleroe
ለሀሳብ አስተያየት @Aleroebot
ኤልሮኢ:(ምክረ አበው)

አንዳንድ ጊዜ የእግዚአብሔር ቃል በመከራ ውስጥ ይመጣል

አንድ ሰው መፍትሔ የሌለው የሚመስል መከራ ሊገጥመው ይችላል። በዚህ ጊዜ የእግዚአብሔር ድምፅ መከራው የገጠመው ጥቂት ኃጢአቶችን ስለ ፈጸመ መሆኑን ከማስጠንቀቂያ ጋር ይነግረዋል። አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ቃሉ ንስሓ ከገባህ መከራው ፍጻሜ ያገኛል እያለ ውስጡን ሲመክረው ይሰማል። ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር ስለ ንስሓው ሲል ለሰውየው ይራራለታል።

የእግዚአብሔር ድምፅ አንድ ሰው ሲታመም ወይም እርሱ የሚወደው ሌላ ሰው ሲታመም ሊመጣ ይችላል። በዚህ ጊዜ እንዲጸልይ ወይም ስዕለት እንዲሳል የሚመክረውን ድምፅ ከውስጡ ይሰማል ይህ ድምፅ የእግዚአብሔር ድምፅ ነው።

የዮሴፍ ወንድሞች እህል ሊገዙ ወደ ግብጽ ከወረዱ በኋላ በዚያ ችግር ሲገጥማቸው እርስ በእርሳቸው እንዲህ በማለት ተነጋግረው ነበር “በእውነት ወንድማችንን በድለናል እኛን በማማጠን ነፍሱ ስትጨነቅ አይተን አልሰማነውና። ስለዚህ ይህ መከራ መጣብን።” ዘፍ. 42፥21። ከዚህ በኋላ ለዮሴፍ እንዲህ ብለውታል “ለጌታዬ ምን እንመልሳለን? ምንስ እንናገራለን? ወይስ በምን እንነጻለን? እግዚአብሔር የባሪያዎችህን ኃጢአት ገለጠ...” ዘፍ. 44፥16። ኃጢአታቸውን እንዲያስታውሱ ኀላም እንዲገሰጹ ያደረጋቸው የእግዚአብሔር ድምፅ ነው።

ነቢዩ ዳዊት የጌራ ልጅ በሆነው በሳሚ ሲሰደብ የእግዚአብሔር ድምፅ ውስጡን ስላለፈ ኃጢአቱ እየወቀሰው መሆኑን አዳምጧል። ስለሆነም በዙሪያው ለነበሩ ሰዎች “እግዚአብሔር ዳዊትን ስደበው ብሎታልና ይርገመኝ።” 2ኛ ሳሙ. 16፥10 በማለት በግልጽ ተናግሯል።

ረሀብና የመሬት መንቀጥቀጥ በዓለም ሲደርስ የእግዚአብሔር ድምፅ በመላው ዓለም ውስጥ ይሰማል። በዚህ ጊዜ የእግዚአብሔር ድምፅ የሚናገረን “ወደ እኔ ተመለሱ እኔም ወደ እናንተ እመለሳለሁ።” ሚል. 3፥7 እያለ ነው። ይህ ድምፅ በረሀቡ ወይም በመሬት መንቀጥቀጡ ጉዳት ለደረሰባቸው ሀገሮች የሚሆን የእርዳታ ጥሪ ለማሰማት ወይም ሌሎቹ ከእነርሱ ትምህርት በመውሰድ ንስሓ እንዲገቡ ለማድረግ ወይም ከእግዚአብሔር ጋር ለመገናኝት ዝግጅት እንዲያደርጉ ነው።

ስለዚህ ማንኛውም ዓይነት መከራ ውስጥ ስትገቡ ከውስጣችሁ ያለውን የእግዚአብሔር ድምፅ አድምጡት እርሱ ለእናንተ ሊነግራችሁ የሚወደው ምን እንደ ሆነ ታውቃላችሁና።

@aleroe
ለሀሳብ አስተያየት @Aleroebot
ኤልሮኢ:
#ስጋ_ነው_ምርኩዜ


ስጋዬ ወፍሮ አፌ ክፉ ደፍሮ
ሓሰትን መስክሮ እውነት ቅሉን ሽሮ
እውነት ተሸሸጋ ማን እውነት ሊያወጋ
ስለ ክፉ ስጋ።
ስለ ክፉ ስጋ ነፍሴ ስትወጋ
የአንደበቴ ችቦ የአንደበቴ ሰንጋ
ነፍሴ ስትቃትት የስጋ ጦር ወግቷት
ቀንም ሌሊትም ቁስሉ ሲያሰቃያት
ጭንቅ ጥብብ አለች ቀኑ ጨልሞባት
የምታውቀው ቤቷ ተዘግቶባት
ስጋ ሲበድላት በሐዘን በትካዜ
በሐሰት ባለሟል በስጋ ምርኩዜ
እኔንም ተረድታ በእምነት መደብዘዜ
በህይወት ልታልፍ ልትጓዝ በግዜ
ነፍሴ የተዘጋጀች ልታቀርብ ኑዛዜ።
____________________

@aleroe
ኤልሮኢ:
. #ጸሎት

#ጸሎት ያቆመች ነብስ እየሞተች ያለች ነች።
#ለሊት ተነሥቶ በጸሎት ጠላቱን ያልመታ ጥዋት ቀኑን ሙሉ ሰይጣን ሲመታው (ሲቀጠቅጠው) ይውላል።
#ክርስትያን ተንበርክኮ ማንበርከክ ይችላል። የማይጸልይ ከሆነ ደግሞ ገና ሳይዋጋ ይንበረከካል።
#ሌሊት በጸሎት ያልወረድክበት ሰይጣን። ቀኑን ሙሉ ሲያገሳብህ ይውላል።
#ከእግዚአብሔር ጋር አንዲት ቀን ሳታሳልፍ ከዋልክ፦ ከመልካሙ
ዘመንህ ውስጥ አንዲቷ ቀንህ በከንቱ እንዳባከንካት ቁጠራት።
#እግዚአብሔርን በጸሎት የማይለምን፦ ዘወትር የሰውን ፊት የሚያይ ተለማማጭ ሆኖ ይኖራል።
#ከእግዚአብሔር ጋር መልካም ጊዜን ማሳለፍ፦ገንዘብህን ከፍተኛ ትርፍ ከሚያስገኝ ንግድ (ኢንቨስት) ከማድረግ በላይ እጅግ ጠቃሚ ነው።


@aleroe
ኤልሮኢ፡(ስነ ፅሁፍ)

…አንድ አካል

ጳውሎስ እግር ሆኖ በአህዛብ ሀገር፣
ሲሮጥ አይተነዋል ለቃል ሲመሰክር።
እጅ ነበር ጴጥሮስ ሁሉን የሚባርክ፣
ሶስት ሺህ ሰራዊት በአንዴ የሚማርክ።
የዮሀንስ ዓይን ከሩቅ የሚያስተውል፣
ፍጢሙ ላይ ቆሞ ሰማይ የሚያካልል።
ሉቃስም ጣቱ ነው ቃል የሚፃፍበት፣
የፈጣሪው እናት መልኳ የሚሳልበት።
አንደበተ ትሁት ያዕቆብ መምህር፣
ባለፀጋዎቹን ሲወቅስ የማያፍር።
ማቴዎስም መጥቷል ከቀራጭነቱ፣
የፈጣሪ አካል ሆኗል ሰውነቱ።
ቅዱስ ፊሊጶስም እውነተኛ አባት ነህ፣
ታሪክህ ይታወቅ በእኛ በልጆችህ፣
ለህዝበ ኢትዮጵያም ይድረስ በረከትህ።


@aleroe
ለሀሳብ አስተያየት @Aleroebot
ኤልሮኢ፡(ምክር)

.....ትህትና በአባቶች ሕይወትና ትምህርት ቀዳሚውን ስፍራ ይዞ ይገኛል። ቅዱስ ያዕቆብ እንዲህ ብሏል ስለ ትህትና ማስተማር እፈልጋለሁ። ደግሞ እፈራለሁ። ስለ እግዚአብሔር ለመናገር እንደሚፈራ ሰው እመስላለሁ። ምክንያቱም ትህትና መለኮት ሰው ሆኖ በምድር ሲገለጥ የተጠቀለለበት መጎናጸፊ ነውና። ሰው ሆኖ በአጭር ደረት በጠባብ ቁመት የመገለጡም ምሥጢር እጅግ አስደናቂ በሆነ በትህትናው ነው። ይሄ ሁኔታው ያስደነቀው ነቢዩ ኢሳይያስ "ያልተጠባበቅነውን የጽድቅ ሥራህን ባደረግህ ጊዜ ወረድህ፤ ተራሮችም በፊትህ ተንቀጠቀጡ" ኢሳ. 64፥4 ብሏል። ሰይጣን ትሁት ሰው ሲያይ የሚፈራው በትሁት ሰው ውስጥ የፈጠረውንና በትህትና ያሸነፈውን እግዚአብሔር ስለሚያየው ነው።

@aleroe
ለሀሳብ አስተያየት @Aleroebot
ኤልሮኢ:(ትርክት)

+++ ልብስህን ማን ወሰደው? +++

በአንድ ወቅት አባ ሰራብዮን ወደ እስክንድርያ ሄደ፡፡ በገበያም ስፍራ አንድ ከልብስ የተራቆተ ነዳይ አገኘ፡፡ ለራሱም ‹ይህ ደሃ ሰው ታርዞ መነኩሴ የተባልኩ እኔ እንዴት ለብሼ እታያለሁ? በእውነት ይህ ‹ታርዤ አልብሳችሁኛልና› ብሎ የተናገረው ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ አይደለምን? በዚህ ብርድ አየር እየተሰቃየ እኮ ነው!› ብሎ ፈጥኖ የገዛ ልብሱን ከራሱ በማውለቅ ይለብስ ዘንድ ለዚያ ደሃ ሰጠው፡፡ ከዚያም በእጁ ያለውን መጽሐፍ ቅዱስ እንደያዘ እርቃኑን በጎዳናው ላይ ተቀመጠ፡፡ የከተማውም ባለጠጋ ሰው አባ ሰራብዮን ባለበት ሥፍራ ሲያልፍ ተመልክቶት ወደ እርሱ ቀረበና ‹አባ ሰራብዮን ሆይ ልብስህን ማን ወሰደው?› ሲል ጠየቀው፡፡ ቅዱስም በእጁ ወደ ያዘው መጽሐፍ ቅዱስ እየጠቆመ ‹ልብሴን የወሰደው ይህ ነው!› አለው፡፡ ያም ባለጠጋ ልብስን ገዝቶ ካለበሰው በኋላ አባ ሰራብዮን ከእርሱ እንደ ተለየ በመንገድ ዕዳውን መክፈል ስላልቻለ እየተንገላታ ወደ ወኅኒ ቤት የሚሄድን አንድ ሰው ተመለከተ፡፡ ቅዱሱም አባት የያዘውን መጽሐፍ ቅዱሱን ሽጦ የዚያን ሰው ዕዳ በመክፈል ነጻ አደረገው፡፡ ይህንም ፈጽሞ ጉዞውን ሲጀምር ሌላ አንድ ነዳይ ሲለምን ተመልክቶ ዳግመኛ የለበሰውን ልብስ አውልቆ ሰጥቶ እርቃኑን ወደ በአቱ ተመለሰ፡፡ ደቀ መዛሙርቱም እርቃኑን ባዩት ጊዜ ‹መምህር! ልብስህ ወዴት አለ?› ብለው ጠየቁት፡፡ እርሱም ‹መጸወትኩት› አላቸው፡፡ ደቀ መዛሙርቱም መልሰው ‹እኛን የሚያጽናናን መጽሐፍ ቅዱስህስ አባታችን? › ሲሉ ደግመው ጠየቁት፡፡ አባ ሰራብዮንም ‹መጽሐፍ ቅዱስ ሁል ጊዜ ‹ሂድ ያለህን ሽጠህ ለድሆች ስጥ› ይለኛል፤ ስለዚህ እርሱንም ሸጥኩት› አላቸው፡፡

ምንጭ :–Paradise of the monks, P 89

ኢትዮጵያዊው ቄርሎስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ እንደሚናገረው ምጽዋት የፊት መብራት ናት፡፡ አንድ ሰው በጨለማ ሲጓዝ ከኋላው መብራት ቢያበሩለትም እንኳ ከፊቱ የሚቀድመው የገዛ የአካሉ ጥላ እንቅፋት እየሆነበት ይጥለዋል፡፡ ወደ ፊት ያለውን መንገድ አጥርቶ እያየ ያለ ስጋት ለመሄድ እንዲችል የግድ የፊት መብራት ያስፈልገዋል፡፡ ጾም ፣ጸሎት እና ሌሎች መንፈሳዊ ትሩፋት እንደ ኋላ መብራት ናቸው፡፡ የፊት መብራት የተሰኘች ምጽዋት ካልታከለችባቸው እነዚህ ብቻቸውን ዋጋን አያሰጡንም፡፡ ከምጽዋት በላይ ታላቅ ነገር እንደሌለ ልንረዳ ይገባል፡፡ ዓለም ሁሉ ከነበረበት የበደል ዕዳ የዳነው ቸር እረኛ በሆነው በመድኃኔ ዓለም በአካሉ ምጽዋትነት (በሥጋው በደሙ መሰጠት) ነውና!!!


@aleroe
ለሀሳብ አስተያየት @Aleroebot
Forwarded from 666( ኢልሙናቲ ) ሀይማኖት ምዝገባ ማእከል
መፅሀፍ ቅዱሳዊ ጥያቄዎች ከነመልሶቻቸው እና ከነ ማስረጃዎቻቸው የምናቀርብበት ፕሮግራማችን በተከታታይ ክፍል ለእናንተ ሲደርስ ቆይቶ አሁን ክፍል 6 ላይ ደርሰናል ሆኖም እስከዛሬ ቪዲዮውን ላላገኛችሁ እንዲሁም ቀጣዩን ክፍል ማግኘት ለምትፈልጉ ከስር ሊንኩን በመንካል ማግኘት ይችላሉ።

https://youtu.be/G4S7uXyscEs
https://youtu.be/G4S7uXyscEs
ኤልሮኢ:(ብሂል)

"ሌቦች ወርቅና ብር ያለውን እንጂ ድርቆሽና ገለባ እንዲሁም ሰንበሌጥ ያለውን ቤት አይበረብሩም፡፡ ዲያብሎስም የሚያጠቃው (የሚፈትነው) መንፈሳዊ ምግባራትን የሚያበዙትን ሰዎች ነው፡፡"

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ


@aleroe
ለሀሳብ አስተያየት @Aleroebot
ኤልሮኢ፡(ትርክት)

…… አትማረኝ
--------------
በጣና ገዳማት ውስጥ የአቡነ አሳይ ዋሻ አለ በዚህ ዋሻ አንድ ያልተማረ የቤተክርስቲያንን ትምህርት የማያውቅ ሰው ጸሎት ሲጸልይ አንድ አባት በጀልባ ተሳፍረው ይመጡና ያገኙታል።

ወደ ደሴቷም አረፍ ልበል ብለው ሲገቡ ያ ወጣት ሲጸልይ ይሰሙታል ቀረብ ብለው ቢያደምጡ ይህ ሰው የሚጸልየው "አትማረኝ" እያለ ነው።

እኝህ አባት በጣም ይደነግጡና እንዲህ ያለ ጸሎት አለ ወይ አትማረኝ የሚል ማን ነው ያስተማረህ ሲሉት አንድ መነኩሴ ነው ያስተማሩኝ አላቸው።

እሳቸውም ይህማ ሰይጣን ነው በመነኩሴ ተመስሎ ያስተማረህ እንጂ አትማረኝ ብሎ ጸሎት የለም ብለው "አቡነ ዘበሰማያትን" አስተማሩት። ይኽ ሰው እንደምንም ታግሎ አባታችን ሆይን ከተማረ በኋላ እኝህን አባት ያሰናብታቸዋል።

እሳቸውም በጀልባ ተሳፍረው መንገድ ሲጀምሩ ይኽ ወጣት ወደ ቀደመ በዓቱ ገብቶ መጸለይ ሲጀምር ያን ጸሎት ረሳው። ምን ነበር ያስተማሩኝ ብሎ ቢያስብ ጠፋበት። ከበዓቱም ሮጦ ወጥቶ በጀልባ ተሳፍረው የሚሄዱትን አባት አስቁሞ "ምን ብለው ነው ያስተምሩኝ?" ብሎ ጠየቃቸው እኝህም አባት ሲያዩት ውሃ ላይ ቆሟል፣ በውሃ ላይ ነው ሮጦ የመጣው አትኩረው ቢመለከቱት ውኃው ላይ እንደቆመ ነው።

"በል የእኔ ልጅ እንደቀድሞው አትማረኝ እያልክ ጸልይ" አሉት ይባላል።

ወጣቱ ባለማወቅ በሚጸልየው ጸሎት ውስጥ በቅቶ ነበር። እግዚአብሔር የሰማው ያለውን ሳይሆን የልቦናውን ነው።

የምንጸልየው ጸሎት የተዘበራረቀ ቢሆንም እንኳን እግዚአብሔር እያቃና ይሰማዋል። ስለዚህም ከመጸለይ ወደ ኋላ አንበል እኛ የምንጸልየው ባይገባንም በዙሪያችን ያሉት አጋንንቶች ገብቷቸው ይሸሻሉ።

@aleroe
ለሀሳብ አስተያየት @Aleroebot
ኤልሮኢ: (ምክረ አበው)
……✍️
አባት ልጁ ከቤት ወጥቶ መኪና እንዳይገጭበት፣ ወድቆ እንዳይሰበርበት፣ ድንገት በአከባቢው የሚያልፉ ከብቶች ገፍተው እንዳይጥሉበት መውጫው በሩን ይዘጋበታል፡፡ ይኼኔ ልጁ በሩ ለምን እንደተዘጋበት አያውቅም፤ ልጅ ነውና፡፡ አባቱ የጠላው መስሎትም ምርር ብሎ ሊያለቅስ
ይችላል፡፡ ማልቀስ ብቻ አይደለም፤ ቂምም ሊይዝበት ይችላል፡፡ አባቱ ግን በሩን የዘጋበት ምክንያት ያውቃል፤ ጠልቶት ሳይሆን ይጐዳበታልና ልጁ ቢያለቅስም አይከፍትለትም፡፡

እውነተኛው አባታችን እግዚአብሔርም አንዳንድ ጊዜ የማይጠቅሙን ይልቁንም ክፉኛ ሊጎዱን የሚችሉ በሮችን ይዘጋብናል፡፡ ከእውቀት ከፍለን የምናውቅ ልጆቹ ነንና አባታችን ለምን እንደዘጋብን ለጊዜው አይታወቀንም፤ ብቻ የከለከለን ይመስለናል፡፡ በመሆኑም ቂም ልንይዝበት ልናማርረውም እንችላለን፡፡ እርሱ ግን ይታገሠናል፤ ለእኛ
የሚያስባት መልካሚቱን በር እርሱ ያውቃታልና ይከፍትልናል፤ በእኛ እይታ መልካም የምትመስለንን ነገር ግን ክፉይቱን በር ይዘጋብናል፡፡

ቅዱስ አባት ሆይ ስለ ከፈትክልን ብቻ ሳይሆን ስለ ዘጋህብንም በር እናመሰግንሃለን ልንለው ይገባል። አሜን!

@aleroe
ኤልሮኢ:(ምክር)

#ወዳጄ ሆይ!

የሚታገል ሰው ቢወድቅ አዲስ ነገር አይደለም፤ ወድቆ መቅረቱ ነው እንጂ፡፡ አንድ ቦክስ የሚጋጠም ሰውም ቢቆስል የሚያሳዝን ነገር አይደለም፤ የሚያሳዝነው ቁስሉን ችላ ያለው እንደ ኾነ ነው እንጂ፡፡ አንተም በመንፈሳዊ ሕይወትህ ብትወድቅ አይደንቅም፤ ለቅጽበትም የማይተኛልህ ጠላት አለህና፡፡ ነገር ግን ወድቀህ አትቅር፡፡

አንድ ወታደር ጦር ሜዳ ሔዶ ቢቆስል ማንም ጤነኛ አእምሮ ያለው ሰው አይወቅሰውም፡፡ አንተም ጠላትህ ዲያብሎስ ቢያቆስልህ ማንም አይወቅስህም፡፡ መንፈሳዊ ተጋድሎ ውስጥ ነውና ያለኸው፡፡ የምትወቀሰው ለቁስልህ መድኃኒት ማድረግህን ችላ ያልህ እንደ ኾነ ብቻ ነው፡፡ ይህ ከላይ የነገርኩህ ወታደር ከታከመ፥ ተመልሶ ወደ ጦር ሜዳ ይሔዳል፡፡ ጠላቱን ድል ሲያደርግም ሹመት ሽልማት ይሰጡታል፡፡ አንተም ከወደቅህበት ተነሥና ንስሐ የተባለ ሕክምናን ውሰድ፡፡ ከዚያም ጠላትህ ዲያብሎስን ድል አድርገህ ከክርስቶስ ዘንድ ሹመት ሽልማትን ተቀበል፡፡ ስለዚህ በርታ፡፡ በርታና ተነሥ ዘግይቻለሁ ብለህ በፍጹም ተስፋ አትቁረጥ፤ አሁንም መጀመር ትችላለህና፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

@aleroe
ለሀሳብ አስተያየት @Aleroebot
ኤልሮኢ:(መዝሙር)

አዝናለሁ አለቅሳለሁ

አዝናለሁ አለቅሳለሁ
ስለ በደሌ ሁል ጊዜ አለቅሳለሁ
አዝናለሁ አለቅሳለሁ
ስለ ጥፋቴ ሁል ጊዜ አለቅሳለሁ
ነገር ግን መሐሪ ነህና
እንደምታድነኝ አምናለሁ

ሥጋዬ ለራሱ እያታለለኝ(፪)
ሁሉን በመፈለግ ወሰደና ለጥፋት ሰጠኝ(፪)
አዝ = = = = =
ከመሬት ተገኝታ እስክትገባ
በከንቱ አስቀረችኝ አምላኬ ሆይ ሥጋ ሰገብጋባ(፪)
አዝ = = = = =
ትቻት መምጣቴ ነው አፈር ሥጋዬን
እንድትቀበላት አምላኬ ሆይ አደራ ነፍሴን(፪)

@aleroe
ለሀሳብ አስተያየት @Aleroebot
ኤልሮኢ:(ትርክት)

"አንዱ ስለ ሁሉ ሞተ"

ከእለታት አንድ ቀን አንድ ወጣት የንስሀ አባቱን ለማግኘት ተንስቶ ወደ ቤተክርስቲያን ይሄዳል። ፀሎቱን አድርሶ ግቢ ውስጥ ቁጭ እንዳለ አባ ይመጡና በመስቀል ባርከው ደባብሰው ወደ በአታቸው ይዘውት ይገባሉ። ታድያ ልክ እንደ ገባ የክርስቶስን ስነ ስቅለት የእሾሁን አክሊል ያይና በሀሳብ ወደ ቀራንዮ ይሄዳል። አባ ምነው ልጄ እኔን እዚህ ትተህ አንተ ወደ ቀራንዮ ሄድክ ሲሉት ከሀሳቡ ባህር ወጥቶ ቁጭ አለ።

አባ አየህ ልጄ ምን ሆነ መሰለህ ብለው ጨዋታ ጀመሩለት። "በአንድ ሀገር ትልቅ የባቡር መንገድ ነበር ታድያ የባቡሩ መንገድ ታቹ ባህር ነው በጣም ትላልቅ አዞዎች አሉበት። አንድ ቀን ታድያ ይህ መንገድ ኃይለኛ ዝናብ በመጣሉ ምክንያት ይፈርሳል። አንድ ህፃን ልጅ ይህን ሁኔታ አይቶ ኖሯል ባቡሩ እዛ ቦታ ሳይደርስ ለማስቆም ወሰነና የአደጋ ምልክቶችን ፅፎ በተለያየ ርቀት 2 ቦታዎች ላይ አስቀመጠ። ከዚያም 3ኛው ላይ ባንዲራ ይዞ እራሱ ቆመ ባቡሩም መጣ ልክ የመጀመሪያውን የአደጋ ምልክት ሲያይ ይህ የዱርዬዋች ስራ ነው ብሎ ተበሳጭቶ አለፈ። ሁለተኛውንም እንዲሁ አለፈ። በሶስተኛው ህፃኑ ጋር ደረሰ ጥሩንባውን እያጮኸ ዘወር በል አለው ልጁ ግን በጭራሽ ዘወር ሳይል ባቡሩ እዛው ፈጨው የባቡሩ አሽከርካሪ በጣም ደነገጠ ተሳፋሪዎችም ወረዱ ልጁን ሲያዩት የለም ደቋል። ነገር ግን በእጁ የነበረው ወረቀትና ባንዲራ ወድቆ አገኙት አንስተው ሲያነቡት በዝናቡ ምክንያት ድልድዩ መፍረሱን ነበር የሚያሳየው። እውነትም ጠጋ ብለው ሲያዩ ድልድዩ ፈርሶ አዞዎቹ ብቅ ብቅ ብለው መልአከ ሞት የሚጥልላቻውን ነፍስ የሚጠብቁ ነበር የሚመስሉት። ከዛ ሁሉም በጣም አዘኑ አለቀሱ ለእነርሱ መትረፍ ያ ህፃን ልጅ የከፈለውን መስዋዕትነት ተገነዘቡ አንዱ ስለ ሁላቸው ሞቶ እነርሱን አተረፈ። ይህ ሁሉ ስለ ሰዎች ፍቅር ነው።"

አየህ ልጄ ክርስቶስም ለኛ እንዲህ ነው አሉት ሳያውቁ ሁለቱም በጣም አልቅሰው ነበር በልጁ ታሪክ። "አባቴ እኔ'ኮ ከንቱ ሰው ነኝ እግዚአብሔር እኔን ይቅር ይለኛል?" አላቸው "ልጄ እግዚአብሔር ይቅር ባይ ነው። ግን መጀመሪያ አንተ ቀዶ ጥገና ያልስፈልግሃል" አሉት። "ምን አይነት ቀዶ ጥገና አባቴ?" "ይሄውልህ ልጄ የእስከ አሁኑን ልብህን ልናክመው ይገባል ዳግመኛ ወደ ቀደሞው መጥፎና ኃጢአት የበዛበት ህይወት እንዳትመለስ። ከዚያ ንስሀ የሚባለውን የህይወት መድኃኒት ትወስድና ትድናለህ" አሉት፡፡ ወጣቱም ሁሉን ተናዞ ንስሀ ገብቶ ተፀፅቶ ትላንትን ዳግም ላያየት ከእውነት ጋር ታርቆ ጤናማ ህይውቱን መኖር ጀመረ።


@aleroe
ለሀሳብ አስተያየት @Aleroebot
ኤልሮኢ:(ምክር)

የምክር ቃል ከቅዱስ ኤፍሬም!!

የበደሉንን ይቅር ማለት መሸነፍ ሳይሆን ፍቅርን ማስተማር ነው። ከሰይጣን በቀር ምንም ጠላት አይኑርህ፡፡ የሰዎችን ስህተት አትመራመር፤ የባልንጀራህን ኃጢአት አትግለጥ፡፡
የባልጀራህን ውድቀት ደጋግመህ አታውራ፡፡ በራስህ ኃጢአት ላይ ፍረድ እንጂ በሌሎች ላይ አትፍረድ ገዢያቸው አይደለህምና፡፡

ኃጢአትን በፈጸመ ሰው ላይ ወቀሳ አታብዛ አንተም ትበድላለህና፡፡ ነገር ግን ከኃጢአቱ ይመለስ ዘንድ ረዳትና መካሪ ሁነው፡፡ ከወደቀበትም የስህተት ሥራ እንዲወጣ አበርታው፡፡ ተስፋውን በእግዚአብሔር ላይ ቢያደርግ ኃጢአቱ ልክ በእሳት ፊት እንደ ወደቀ ገለባ ፈጥኖ እንደሚወገድለት ንገረው፡፡

ቅዱስ፣ ጥንቁቅ፣ ግልጽና ብልህ ሁን፡፡ እርጋታን የተላበሰ ሰብእና ይኑርህ፡፡ ደስተኛ ሁን፤ ሰላምታህ በፈገግታ የታጀበ ንጹሕ ይሁን፡፡ ንግግርህ የታረመ አጭርና በጨው እንደ ተቀመመ ጣፋጭ ይሁን፡፡ቃላቶችህ የተመጠኑና ጤናማዎች ሁሉም የሚረዳቸው ይሁኑ፡፡ የጓደኛህን ምስጢር አትግለጥ፤ ለሚወዱህ ሁሉ የታመንክ ሁን፡፡ ወደ ጭቅጭቅና ንትርክ ከመግባት ራስህን ጠብቅ፡፡ የሚሰሙህ ሁሉ እንዳይጠሉህ ወደ ጠብ አትግባ፡፡


@aleroe
ለሀሳብ አስተያየት @aAleroebot
ኤልሮኢ:(ስነፅሁፍ)

🖌……ቅን ከሆንን

ፍቅር ካለ፣
ኅብረት ካለ፣
መደጋገፍ ከታከለ፣
እርስ በእርስ ከተዋደድን፣
ሁላችንም ከተሳሰብን፣
አምላክችን ከእኛ ጋር ነው፣
ምንፈልገው በእጃችን ነው።
ሀዋርያት እንደሰሩት፣
ተደጋግፈው እንደኖሩት ፣
በኛ መሀል ፍቅር ካለ፣
መተሳሰብ ካልጎደለ፣
ማን ተጋፍቶን ማን ደርሶብን፤
መሀላችን ማን ገብቶብን፤
የአምላክን ቃል ከፈፀምን፤
ለሰው ሁሉ ቅን ከሆንን።


@aleroe
ለሀሳብ አስተያየት @Aleroebot
ኤልሮኢ:(ምክር)


#እውነተኛ ወዳጅ


እውነተኛ ወዳጅ፥ ወዳጅ መኾኑ የሚታወቀው ጓደኛውን መገሠጽ ሲችል ነው፡፡ ኹላችንም በየጊዜው ኃጢአት እንሠራለን፡፡ አብዛኞቻችን ደግሞ ኃጢአታችንን እንዳላየነው ኾነን ለማለፍ እንጥራለን፡፡ ለራሳችን ይቅርታ እንቸራለን፡፡ ወይም ምንም እንዳላጠፋ ሰው ለመምሰል እንሞክራለን፡፡ በእንደዚህ ዓይነት ሰዓት እውነታውን በትክክል እናይ ዘንድ ዓይናችንን የሚከፍት እውነተኛ ወዳጅ ያስፈልገናል፡፡

አንተ ሆይ! እስኪ ራስህን መርምር፡፡ ጓደኛህ እውነታውን እንዲያይ ታደርጋለህ? ጓደኛህ ኃጢአት ሠርቶ ሲያበቃ ለራሱ ይቅርታ ሲያደርግ ይቅርታው ያደረገው ይቅርታ ትክክለኛ እንዳልኾነ እንዲያውቅ ታደርጓለህን? እንዲህ እውነታውን ስትነግረው ምናልባት ጓደኛህ አለአግባብ ሊቈጣህ ይችላል፡፡ ታዲያ ሲቈጣህ ለመታገሥ ዝግጁ ነህን? ወይስ ከዚህ በተቃራኒ የጓደኛህን ኃጢአት አይተህ እንዳላየህ ነው የምትኾነው?

ጓደኛ ስንመርጥ ከእኛ ጋር እውነተኛ ወዳጅ ሊኾን የሚገባውን መኾን አለበት፤ ስንቈጣው እንኳን ቁጣችንን ታግሦ ስናጠፋ የሚያርመን ሊኾን ይገባል፡፡ እንደዚህ ካልኾነ ጓደኝነት ጥልቀት አይኖረውምና፤ ጓደኞች ነን መባባላችን ጥቅም የለውምና፡፡

ልናውቀው የሚገባን ነገር ግን አለ፡፡ ጓደኛችን በሚያጠፋበት ሰዓት ተግሣጽ አስመስለን እንዲሁ ክብሩን በሚነካ መልኩ ልንናገረው አይገባንም፡፡ ተግሣጻችን ኹልጊዜ እውነቱን ብቻ እንጂ የተጋነነና ሌላውን መልካምነቱን የሚክድ መኾን የለበትም፡፡ ጥፋቱን ስንነግረው ኹልጊዜ በቀና ልብ እንደምንነግረው እርግጠኛ እንዲኾን ማድረግ አለብን፡፡ ይህን የምናደርገው ከፍቅራችን የተነሣ እንጂ ከቅናት ወይም ከንቀት እንዳልኾነ እንዲያውቅ ማድረግ አለብን፡፡ እውነተኛ ወዳጅነት ማለት ይህ ነውና፡፡


┈┈ • ┈┈┈••●◉ ✞◉●••┈┈•┈┈┈

@aleroe
ለሀሳብ አስተያየት @Aleroebot
ኤልሮኢ:(ምክር)

...........የሀጢያት ትንሽ ..............

ዲያብሎስ ልጅነታችንን እናቆሽሽ ዘንድ በእኛ ላይ የሚተናኰለው ተንኰል በጣም ተደጋጋሚና ኃይለኛ ነው፡፡ ስለዚህ ይህን መንቻካ የዲያብሎስን ደባ ድል እንነሣ ዘንድ ዘወትር ንቁዎችና ጠንቃቆች ልንኾን ይገባናል፡፡ እኛ ይህን ማድረግ ሳንችል ቀርተን እጅግ ጥቂት መግቢያ ቀዳዳ የምንተውለት ከኾነ ግን እርሱ ጥቂቷን ቀዳዳ ሰፊ በር ያደርጋታል፡፡ እንዲህ አድርጎም ኃይሉን ኹሉ ተጠቅሞ ወደ እኛ ይገባል፡፡

ስለዚህ ስለ ድኅነታችን የሚገደን ከኾነ እንደዚህ ጥቂትና ቀልድ በሚመስሉ ነገሮች እንኳን አንዘናጋ፤ እርሱ የሚንቀውና ጥቂት የሚለው ኃጢአት የለምና፡፡ እኛ ጥቃቅን የምንላቸውን ነገሮች መነሻ አድርጎ ልጅነታችንን የምናቆሽሽበትን ታላላቅ ኃጢአቶችን እንድንሠራ አድርጎ እጅግ ይተጋልና፡፡

🖌……ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

@aleroe
ለሀሳብ አስተያየት @Aleroebot
ኤልሮኢ:(ስነፅሁፍ)

#መጎዳቴን_አይቶ


መጎዳቴን አይቶ
ሊቀይር ታሪኬን
ካለሁበት መጥቶ
ሊሞላው ጓዳዬን
መዳን ትወዳለህ ?
ብሎ ቢጠይቀኝ
የሰለለ አካሌን
በአይኔ እያማተርኩኝ
እወዳለሁ ! አልኩት
መፈወስን ሽቼ
የመጥምቁ አምላክ
መሆኑን ሰምቼ፡፡
የጫማውን ጠፍር
መፍታት የተሳነው
ዛሬ ሽባ እግሮቼን
መፈወስ ተቻለው፡፡
ዳንኩኝ በጸበሉ
በእጁ ተጠምቄ
ለምስክር በቃው
በምልጃው ደምቄ፡፡

ከረዳኢ ሃዱሽ
___________



@aleroe
ለሀሳብ አስተያየት @Aleroebot
ኤልሮኢ: (ትምህርት)

#ዝምታ

#ብፁዕ_አቡነ_ሽኖዳ ......

ዝምታ በመጀመሪያ ደረጃው ውስጥ መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚናገረው የአንደበት ስህተትን መግታት ማለት ነው፦ " በቃል ብዛት ውስጥ ኃጢአት ሳይኖር አይቀርም ከንፈሩን የሚገታ ግን አስተዋይ ነው።" ምሳ. 10 ፥ 19። ቅዱስ አርሳኔዎስም እንድህ ብሏል ፦ " ብዙ ጊዜ እናገርና እፀፀታለሁ ስለ ዝምታየ ግን ፈጽሞ ተፀፅቼ አላውቅም ።"

በሌላ በኩል ዝምታ ማለት እግዚአብሔር ይሠራ ዘንድ የሰውን ጥረት ማቆም ማለት ነው። መጽሐፍ ቅዱስ ይህን አስመልክቶ ሲናገር እንድህ ብሏል፦ .." እግዚአብሔር ለእናንተ የሚያደርጋትን የእግዚአብሔርን ማዳን እዩ ። እግዚአብሔር ስለእናንተ ይዋጋል እናንተም ዝም ትላላችሁ .." ዘጸ. 14፥ 13-14።

አንዳንድ ጊዜ አንድ ሰው ለራሱ የማይበቀልና ክፉን በክፉ የማይቃወም ከሆነ ዝምታ እርጋታ ይሆናል።
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሰድቡት መልሶ አልተሳደበም .1ኛ ጴጥ. 2፥23። በአይሁድ ሸንጎ ፣ በሐና ፣ በቀያፍ ወይም በጲላጦስ ፊት ሲከሱት ዝም ነው ያለው።

ዝምታ ውስጥ ግን ኃይል ስለነበረ አገረ ገዥው ጲላጦስ ".. እኔስ አንዲት በደል ስንኳ አላገኜሁበትም ።" ( ዮሐ . 18 ፥ 38) በማለት ተናግሯል።

ከዚህ በተጨማሪ ዝምታ ለፀሎት ለተመስጦ እድሉን ያደላል።
ብዙ የሚያወራ ሰው ለመፀለይም ሆነ ለውስጣዊ መንፈሳዊ ድርጊት ዕድል አይኖረውም።

አንድ ቅዱስ ሰው".. ብዙ የሚናገር ሰው ውስጡ ባዶ መሆኑን ይገልጣል ።" ብሎ መናገሩ ትክክል ነው። ይህም ማለት ውስጣዊ መንፈሳዊ ሥራ የለውም ማለት ነው።
ቅዱስ አርሳኔዎስ ስለዝምታውና ስለ ምናኔው በተጠየቀ ጊዜ ".. በተመሳሳይ ጊዜ ውስጥ ከእግዚአብሔርና ከሰዎች ጋር መሆን አልችልም ።" ብሎ መልሷል።

አንድ ታላቅ መንፈሳዊ አባት የተናገሩት ቃል ምንኛ ድንቅ ነው ፦ " .. ልብህ ይናገር ዘንድ አንደበትህን ዝም አሰኜው እግዚአብሔር ይናገር ዘንድ ልብህን ዝም አሰኜው ።"

የዝምታ አይነቶች ብዙ ቢሆኑም ከነዚህ መካከል ዋና ዋናዎቹ #የአንደበት_ዝምታና_የስሜት_ዝምታ ናቸው። ሰው ስሜቱን ባተሌ እስካላደረገ ድረስ ፀሎቹንና ተመስጦዎቹን ያግዱበት ዘንድ መጥፎ አሳቦችን ያመጡበታል ። ስለሆነም በመንፈሳዊ መንገድ ዝምታውን መጠበቅ የሚወድ ሰው አይኖቹን ፣ ጆሮዎቹንና ስሜቶቹን ሁሉ መጠበቅ አለበት ።

ዝምታ ለሰው መስከንንና እርጋታን አስተምሯል ከጫጫታ፣ ከሁካታ፣ ለመጸለይ አስቸጋሪ ከሚሆኑበትና ሕሊናውን ከሚረብሽበት ብዛት ካላቸው አሳቦች ያርቀዋል።

ከዚህ በተጨማሪ ዝምታ የሚሻው ብቼኝነትንና ጥቂት ጓደኞችን ነው።

ምንጭ፦ መንፈሳዊ ቃላትና ጥቅሞቻቸው ፤ #አያሌው_ዘኢየሱስ እንደተረጎመው ።

የብፁ አባታችን ብራኬ ይደርብን
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን።

@aleroe
ለሀሳብ አስተያየት @Aleroebot