"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ"
1.2K subscribers
26 photos
3 videos
5 files
21 links
ኤልሮኢ
"በእውኑ የሚያየኝን ጌታ አየሁት"
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ
አምላክ አሜን።
ይህ መንፈሳዊ ቻናል
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ:- +ዝማሬ
+ ምክሮች
+ ስነፅሁፎች
+ አጫጭር ትርክቶች እንዲሁም
+ ምስባክና
+ ወንጌል ይለቀቁበታል።

ለበለጠ መረጃ @AleroeBot
ግሩፑን ለማግኘት @alero
Download Telegram
ኤልሮኢ:(የዕለቱ ምስባክና ወንጌል)
መስከረም 10/01/2013 ዓ.ም
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼

ምስባክ ዘነግህ

መዝ ፩፥፪(1፥2)
ወዘሕጎ ያነብብ መዓልተ ወሌሊተ
ወይከውን ከመ ዕፅ እንተ ትክልት ኀበ ሙኀዘ ማይ
እንተ ትሁብ ፍሬሃ በበጊዜሃ

ምስባክ ዘቅዳሴ

ምድርኒ ወሀበት ፍሬሃ፤
ወይባርከነ እግዚአብሔር አምላክነ፤
ወይባርከነ እግዚአብሔር።

ቅዳሴ

ዘእግዝእትነ (ጎሥዓ)
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼

@aleroe
ኤልሮኢ:(የዕለቱ ምስባክና ወንጌል)
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
​መስከረም 12/01/2013 ዓ.ም


ምስባክ ዘነግህ

መዝ ፸፪፥፰(72፥8)
ሐለዩ ወነበቡ ከንቶ
ወነበቡ ዓመፃ ውስተ አርያም
ወአንበሩ ውስተ ሰማይ አፋሆሙ

ምስባክ ዘቅዳሴ

ይትዐየን መልአከ እግዚአብሔር ዐውዶሙ
ለእለ ይፈርህዎ ወያድኅኖሙ
ጠዐሙ ወታእምሩ ከመ ኄር እግዚአብሔር

ቅዳሴ

👉ዘቄርሎስ
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼

@aleroe
ኤልሮኢ:(የዕለቱ ምስባክና ወንጌል)
መስከረም 13/01/2013 ዓ.ም
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼

ምስባክ ዘነግህ

መዝ ፻፩፥፳፬(101፥24)
ኢትስደኒ በመንፈቀ ዓመትየ
ለትውልደ ትውልድ ዓመቲከ
አንተ እግዚኦ አቅደምከ ሣርሮታ ለምድር

ምስባክ ዘቅዳሴ


ብፁዓን እለ ተኀድገ ሎሙ ኃጢእቶሙ
ወእለ ኢሐሰበ ሎሙ ኩሎ ጌጋዮሙ
ብፁዕ ብእሱ ዘኢኈለቁ ሎቱ እግዚአብሔር ኃጢአቶ

ቅዳሴ

ዘባስልዮስ (እግዚኦ መሐረነ)
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼

@aleroe
ኤልሮኢ:(የዕለቱ ምስባክና ወንጌል)
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
መስከረም 14/01/2013 ዓ.ም


ምስባክ ዘነግህ

መዝ ፺፭፥፲፩(95፥11)
ወትትከወስ ባሕር በምልዓ
ትትኃሠይ ገዳም ወኵሉ ዘውስቴታ
ውእተ አሚረ ይትፌሥሑ ኵሉ ዕፀወ ገዳም

ምስባክ ዘቅዳሴ

ወወሀብኮሙ ትእምርተ ለእለ ይፈርሁከ
ከመ ያምስጡ እምገጸ ቅሥት
ወይድኀኑ ፍቁራኒከ

ቅዳሴ

ዘዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ (ኀቤከ)
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼

@aleroe
ኤልሮኢ :(መንፈሳዊ ስነ ፅሁፍ)

🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
"አትናቅ"

በዘር በወገንህ: ከመመካት ራቅ
የፈለገ ቢወድቅ: የፈለገ ቢደቅ
ሰው ሆነህ ተፈጥረህ፡ ሰዎችን አትናቅ!
ያደርገዋልና የተዋረዱን: ከፍ የከበሩትን ዝቅ::

ቢኖርህ አትመካ ፡ሙሉ አካል ከጤና
ምን ትሆን ወደፊት ፡ከቶ አታውቅምና፡፡

አለኝ ብለህ አትናቅ: ወርቅ ብር ገንዘብ
ሀላፊ ነው እና: ጌታ እንዳይታዘብ::

የሚመካ ቢኖር፡ ኑ ከዚህ አለ ሀይል
(ትምክህትህ በሌላ አይሁን)
በእግዚአብሔር ማዳን ነው፡ በመከራው መስቀል::

አላዛርም ነዌም ፡ደሀውም ሀብታሙም
ክፉው ዘረኛውም፡ ከቶም ያልፋል ሁሉም
በጎ ስራ ግና፡ ይኖራል ዘላለም፡፡

(በእርሱ ፊት)
ዘርህ አንተ ምነው፡ ቅማንት ወይ አማራ?
ይህን አትጠየቅ! ስምክን አትጠራ!

( ምነው ታዲያ )
ዘሬን እየጠራህ፡ ማለትህ አህያ¡
ምርጥ ነን ማለትህ: ሰውስ ከኛ ወዲያ!
አህያን ብታውቃት፡ ጌታ ሰጧታል ክብር
የከበረ አምላኳ ፡ተቀምጦባት ነበር፡፡

በአንድ አምላክ ተበጅተን፡ከአንድ አዳም ተፈጥረን፡
ከሰዎች ልዩ ነን፡ ማለትህ ምን ይሆን?
(እርሱ ይወቅልህ)

በዘር በወገንህ: ከመመካት ራቅ፣
የፈለገ ቢወድቅ: የፈለገ ቢደቅ፣
ሰው ሆነህ ተፈጥረህ፡ ሰዎችን አትናቅ!
ያደርገዋልና የተዋረዱን: ከፍ የከበሩትን ዝቅ::
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼

@aleroe
ኤልሮኢ:(የዕለቱ ምስባክና ወንጌል)
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
​መስከረም 15/01/2013 ዓ.ም


ምስባክ ዘነግህ

መዝ ፻፳፭፥፮(125፥6)
ወጾሩ ዘርዖሙ
ወሶበ የአትዉ መጽኡ እንዘ ይትፌሥሑ
ወፆሩ ከላስስቲሆሙ

ምስባክ ዘቅዳሴ

ብፁዕ ዘኀረይኮ ወዘተወከፍኮ
ወዘኀየርኮ ውስተ አዕፃዲከ
ጸገብነ እግዚአ እምበረከተ ቤትከ

ቅዳሴ

ዘዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ (ኀቤከ)
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼

@aleroe
ኤልሮኢ:(የዕለቱ ምስባክና ወንጌል)
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
​መስከረም 16/01/2013 ዓ.ም


ምስባክ ዘነግህ

መዝ ፹፮፥፪(86፥2)
ያበድሮን እግዚአብሔር ለአናቅጸ ጽዮን
እምኵሉ ተዐይኒሁ ለያዕቆብ
ነኪር ነገሩ በእንቲአኪ ሀገረ እግዚአብሔር

ምስባክ ዘቅዳሴ

እቤ አዐቅብ አፉየ ከመ ኢይስሐት በልሳንየ
ወአንበርኩ ዐቃቤ ለአፉየ
ሶበ ይትቃወሙኒ ኃጥኣን ቅድሜየ


ምስባክ ዘቅዳሴ ተለዋጭ

አሠንያ እግዚኦ በሥምረትከ ለጽዮን
ወይትሐነፃ አረፋቲሃ ለኢየሩሳሌም
አመ ትሠምር መሥዋዕተ ጽድቅ

ቅዳሴ

👉ዘእግዚእነ
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼

@aleroe
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ኤልሮኢ:(የዕለቱ ምስባክና ወንጌል )
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
መስከረም 17/01/2013 ዓ.ም

ምስባክ ዘነግህ

መዝ ፶፱፥፬(59፥4)
ወወሀብኮሙ ትእምርተ ለእለ ይፈርሁከ
ከመ ያምስጡ እምገጸ ቅሥት
ወይድኀኑ ፍቁራኒከ

ምስባክ ዘቅዳሴ

ወወሀብኮሙ ትእምርተ ለእለ ይፈርሁከ
ከመ ያምስጡ እምገጸ ቅሥት
ወይድኀኑ ፍቁራኒከ።

ወንጌል ዘቅዳሴ

የማቴዎስ ወንጌል ም. ፰ ቊ. ፲፮-፲፯ - ፳፰

ምስባክ ዘቅዳሴ ተለዋጭ

ወረከብናሁ ውስተ ዖም ገዳም
ንበውዕ እንከሰ ውስተ አብያቲሁ ለእግዚአብሄር
ወንሰግድ ውስተ መካን ኀበ ቆመ እግረ እግዚእነ


ትርጉም

መዝሙረ ዳዊት ም. ፻፴፪ ቊ. ፮ - ፯

ወንጌል ዘቅዳሴ

የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ፲፱፥፳፭-፳፰

ቅዳሴ

ዘዮሐንስ አፈወርቅ

🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼

@aleroe
ኤልሮኢ:(ትምህርት)

🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
#መጋቢት_10_የጌታችን_መስቀል_የተገኘበት

በደመ ወልደ እግዚአብሔር የከበረ፣ ጌታ ቅዱሳት እጆቹን የዘረጋበት፣ ክቡር ደሙን ያፈሰሰበት፣ መርገመ ሥጋና መርገመ ነፍስ የተሻረበት፣ ዘላለማዊ ደዌ የጠፋበት፣ የጥል ግድግዳን ያፈረሰበት፣ ጥንተ ጠላታችን ዲያብሎስ ድል የተነሣበት የጌታችን መስቀል ከጌታችን ዕርገት በኋላ ሙት እያነሣ፣ ደዉይ እየፈወሰ ለክርስያኖች ታላቅ ክብር በመኾኑ፤ አይሁድ በዚኽ ክፉኛ ይበሳጩ ነበር።

ቅዱስ ጳውሎስ በፊልጵ 3፡18-19 ላይ “ብዙዎች ለክርስቶስ መስቀል ጠላቶቹ ሆነው ይመላለሳሉና፤ ብዙ ጊዜ ስለ እነርሱ አልኋችሁ፥ አሁንም እንኳ እያለቀስሁ እላለሁ፤ መጨረሻቸው ጥፋት ነው፥ ሆዳቸው አምላካቸው ነው ክብራቸው በነውራቸው ነው፥ አሳባቸው ምድራዊ ነው” እንዳለ፤ ጒድጓድ ቈፍረው በይሁዳ እና በኢየሩሳሌም ኹሉ ቤቱን የሚጠርግ ጒድፉን አምጥቶ እንዲያፈስስበት በማዘዛቸው ቦታው የቆሻሻ መጣያ ኾኖ ዕሌኒ ንግሥት እስከ መጣችበት ድረስ ለ፫፻ ዓመታት ያኽል ተቀብሮ ኖረ፡፡

የእሌኒ ልጇ ቆስጠንጢኖስም በመስቀሉ ኀይል የክርስቲያኖች ጠላት የኾነውን መክስምያኖስን ድል ከነሣ በኋላ በሶል ጴጥሮስ ተጠምቆ ክርስቲያን ኾነ፤ ርሷም ልጄ ክርስቲያን ከኾነ ኢየሩሳሌም ኼጄ የፈረሱትን አብያተ ክርስቲያናት አሠራለኊ፤ የጌታዬ መስቀልን ከተቀበረበት አስወጣለኊ ብላ ስዕለት ተስላ ነበርና ያ በመፈጸሙ ደስ ተሰኝታ፤ ለልጇ ነገረችው፤ ርሱም በደስታ ብዙዎች ሰራዊትን ስንቅ አስይዞ ወደ ኢየሩሳሌም ላካት፤ በደረሰችም ጊዜ ሱባኤን አድርጋ የመስቀሉ ጠላቶችን በጽኑ እስራት አሰረቻቸው፤ በኋላም አሚኖስና ኪራኮስ የሚባሉ በዕድሜ የጠገቡ ሽማግሌዎችን ብትጠይቃቸው ሊነግሯት ፈቃደኛ አልኾኑምና በጽኑ እስራት ብታስጨንቃቸው፤ ታሪኩን ነገሯት፤ ቦታውንም ጠቈሟት፡፡

ከዚያም በጸሎቷ ላይ ቅዱስ ሚካኤል ተገልጾላት በዕጣን ጢስ አማካይነት እንደምታገኘው ተረድታ፤ መስከረም ፲፮ ደመራን አስደምራ በእሳት እንዲቃጠል አድርጋ እጅግ ብዙ ዕጣንን ብታስጨምር ጢሱ ወደ ሰማያት ወጥቶ መስቀሉ ካለበት ቦታ ላይ ተተክሎ ሰገደ፤ “ተተክለ ጢስ ኀበ አንጻረ መስቀል፤ ሰገደ ጢስ ወባረከ” እንዲል ቅዱስ ያሬድ።

ርሷም ፈጣሪዋ እግዚአብሔርን በፍጹም ደስታ አመስግና ቊፏሮውን ከመስከረም 17 ዠምሮ እስከ መጋቢት 10 ድረስ እንዲቈፈር አስደርጋለች፤ በቊፋሮው ወቅትም የፈያታዊ ዘየማንና የፈያታዊ ዘጸጋም መስቀል ቢገኙም ዕውር አላበሩም፣ ሕሙማንን አልፈወሱም፡፡

ከዚያም መጋቢት 10 በ327 ዓ.ም. ክብር ይግባውና ጌታችን ክቡር ደሙን ያፈሰሰበት ቅዱስ መስቀሉ ተገኘ፤ በዚኽ ጊዜ ከሕሙማን ላይ ቢያደርጉት ኹሉንም ፈወሳቸው፣ ዕዉራን በሩ፣ ሙታንም ተነሡ፡፡ ከዚኹም ጋር የተወጋበት ጦሩ፣ የተቸነከረባቸው ቅንዋት ኹሉ ተገኝተዋል፤ ርሷም በፈረሷ ልጓም ላይ የመስቀል ምልክትን አስቀርጻበታለች፡፡

ርሷም ጌታችን ተአምራት በሠራባቸው ቦታዎች አብያተ ክርስቲያናትን በማሠራት፤ በተለይም በጎልጎታ የተሠራው ቤተ ክርስቲያን መስከረም ፲፯ ጳጳሳት፣ ካህናት፣ ምእመናን በተገኙበት ቅዳሴ ቤተ ክርስቲያኑ ተከብሯልና፡፡ ርሷም ለድኾችና ለጦም አዳሪዎች ብዙ መልካም ነገርን በማድረግ ግንቦት ፱ በሰላም ዐርፋለች፡፡
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼

@aleroe
ኤልሮኢ :(መንፈሳዊ ስነፅሁፍ)


​​​​"አይጣል ነው አይድረስ"


አይጣል ነው፡ አይድረስ
ሰማይ አይታረስ ፡ንጉስ አይከሰስ

የሞት ነገር መቸም ፡ አይሆንልን ዛሬም
ስሙ ሲነሳብን ፡ይቀፈናል ሁሌም፡፡

በዚህ እስካለ፡ ህይወት
ሞትም ፡ከጎኑ ናት፡፡
(ምንም ማድረግ አይቻልም)

"አሁን ብትሞትስ!"ስልህ፡ ምሳሌ ስሰጥህ
ትሰድበኝ ይሆናል፡ "አንት ሟርተኛ"ብለህ
በርግጥም ያስፈራል ፡ወዳላዩት መሄድ
መቸም ቁርጥ ካልሆነ ፡እኔም እንዲዚያ አልወድ፡፡

ምን እናድርግ ?
በተፈጥሮ ህግ!

አይጣል ነው አይድረስ...

ነፍስህ ፡ባንተ አይደለች
በፈጣሪ እጅ ነው፡የተያዘች ያለች
በቤት ውስጥም ሳለህ ፡በመንገድ ጎዳና
በእግርም እየሄድክ፡በአየር መኪና
ልትሞት ትችላለህ ፡አለም ላይ ናትና፡፡


ድንገተኛ አደጋ ፡ምንኛ ሀያል ነው
እዚሁ ከጎናችን ፡በሰፈር ነው ያለው ፡፡
ሀገር ሰላም ብሎ፡ ሰው ከቤቱ ወጦ፣
ከጓደኞቹ ጋ ፡በስርዓት ተቀምጦ፣
የቆመ ግንድ ወድቆ፣
ተባራሪ ጥይት፡ ሌላን ሁሉ ትቶ፣
ሊገድልህ ይችላል ፡አንተኑ ለይቶ፡፡
ምን ይመጣል ብለህ፡ቤትም ብትቀመጥ
ልትሞት ትችላለህ፡በመሬት መንቀጥቀጥ፡፡


(ምን ይታወቃል እያየን ነው)

አይጣል ነው አይድረስ...


ይሄ ሞት የሚሉት ፡ምንም ምርጫ አያውቅም፣
ህፃን ሽማግሌ ፡ሴት ወንድ አይለይም፣
ቀጭኑ ወፍራሙንም፡ ረዥሙ አጭሩን
አያውቅም መሰለኝ፡ በያይነት መኖሩን፡፡

(አይመርጤ አሉ)

ብዙዎች ነጎዱ፡ ሳያውቁ ሳይነቁ
እምነት ምን እንደሆን፡ ቅኔ ሰሙ ወርቁ

ቢደርስም ባይደርስም፡ ሁሌ ተዘጋጁ
ሊመጣ ይችላል፡ ሊወስድ ነፍሱን በጁ፣
ይሄኔ ነቃ በል፡ ነጋሪት ሳይጎሰም ሳይነገር አዋጁ፡፡

እና በል ወዳጄ ፡እችን ያዝ እንግዲህ፣
አንድ ቀን ብለይህ፣
ምንም እንዳይመስልህ፣
አይመርጤ አይመርጥልህ!
እውነቴን ስነግርህ!

በል በል አንተ ወዳጄ፣ ጊዜ አትውሰድብኝ
አንዳንድ ስራ ልስራ፣ ሳይወሰንብኝ
መቸም አይቆጨኝም፣ ዝግጁ ከሆንኩኝ፡፡

አይጣል ነው አይድረስ
ሰማይ አይታረስ ንጉስ አይከሰስ።

@aleroe
ኤልሮኢ:(የዕለቱ ምስባክና ወንጌል)
መስከረም 20/01/2013 ዓ.ም


ምስባክ ዘነግህ

መዝ ፴፱፥፱(39፥9)
ዜኖኩ ጽድቅሰ በማኅበር ዓቢይ
ወናሁ ኢከላዕኩ ከናፍርየ
እግዚኦ ለሊከ ተአምር ጽድቅየ

ምስባክ ዘቅዳሴ

እስመ መምህረ ሕግ ይሁብ በረከተ
ወየሐውር እምኃይል ውስተ ኃይል
ወያስተርኢ አምላከ አማልክት በጽዮን

ቅዳሴ

ዘዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ (ኀቤከ)


@aleroe
ኤልሮኢ:(የዕለቱ ምስባክና ወንጌል)
​መስከረም 21/01/2013 ዓ.ም


ምስባክ ዘነግህ

መዝ ፳፭፥፲፮(25፥16)
አድኅነኒ እግዚኦ ወተሠሃለኒ
እስመ በርቱዕ ቆማ እገርየ
በማኅበር እባርከከ እግዚኦ

ምስባክ ዘቅዳሴ

ወትቀውም ንግሥት በየማንከ
በአልባሰ ወርቅ ዑጽፍት ወኁብርት
ስምዒ ወለትየ ወርእዪ ወአጽምኢ እዝነኪ

ቅዳሴ

ዘሰለስቱ ምዕት (ግሩም) አው እግዝእትነ


@aleroe
ኤልሮኢ:(መንፈሳዊ ትርክት)

……ከእለታት አንድ ቀን አንድ አባት ወደ አባታችን አባ መቃርዮስ በኣት ሄደና "አባቴ ሆይ ድኅነትን አገኝ ዘንድ ምን ላድርግ?" ሲል ጥያቄ አቀረበላቸው። አባታችንም እንዲህ በማለት አሉት።
"ወደ መቃብር ሂድና ሙታንን ሰድበሃቸው ና" አሉት። ይህ አባትም የተባለውን አድርጎ ተመለሰ። አባታችንም "ምን አሉህ?" ሲሉ ጠየቁት። ሰውየዉም "ምንም አልመለሱልኝም" ሲል መለሰ። አባ መቃርዮስም "አሁን ደግሞ ሂድና ሙታንን አመስግናቸው" አሉት። ሄዶም አመሰገናቸው። "አሁንስ ምን አሉህ" ሲል በድጋሚ ጠየቁት። ሰውዬም "ምንም አልመለሱልኝም" ሲል መለሰ። አባታችን አባ መቃርዮስም: "ስትሰድባቸው ፤ስታመሰግናቸው እና ስታወድሳቸው ምንም አልመለሱም፤ አንተም ለነፍስህ ድህነትን ከፈለግህ እንደሞተ ሰው ሆነህ ኑር። ሰዎች ክፉ ቢያደርጉብህም፣ ቢያመሰግኑህም ምንም አይሰማህ" አሉት።
======================
@aleroe
ኤልሮኢ:(መዝሙር)

#የሚጠብቀኝ አይተኛም

የሚጠብቀኝ አይተኛም(×2) አያንቀላፋም(×2)
ቤት ባይኖረኝም
በደጅ ባድር
ቀንና ሌሊት ከኔ አይርቅም
ድምፀ አራዊት የሌሊት ግርማ
ወደ እኔ አይገቡም ድምፅህ ሲሰማ
መሰናከልን ለእግሮቼ አይሰጥም
ይሰውረኛል በቀኙ ሰላም
ፀሀይም በቀን አይተኩሰኝም
የአጋንንትም ሀይል አያስፈራኝም
ነፍሴን ጠበቃት ከጠላት ወጥመድ
ጌታዬ መራኝ በፅድቅ መንገድ
መውጣት መግባቴን እየጠበቀ
ለዚህ አበቃኝ እርሱ ባወቀ
የሰማዩን ጥል እታገሳለሁ
ሰው ከጨከነ ምን እሆናለሁ
ሌሊት በድብቅ ለሚጎበኙ
ለፃድቃኑ ግን አምላክ ይስጥልኝ
እንቅልፌን ባርኮ የሰጠኝ ጌታ
በዓለም ሀሳብ ሳልንገላታ
የዕለት ምግቤንም ላልነሳኝ ፍፁም
ምስጋና ላቅርብ እስከዘላለም

#ዘማሪ ይልማ

@aleroe
ኤልሮኢ:(መንፈሳዊ ትርክት)

……አንድ በምሽት አቅጣጫ የጠፋበት መርከብ ከሩቅ ያየ ሰው ወደ እቤቱ ገብቶ ሻማ ይለኩሳል

ሻማውም ለምን ለኮስከኝ ቢለው ሰውዬው ‹‹አቅጣጫ የጠፋው መርከብ ከሩቅ ያታየኛል
ለሱ በእሳት ልጠቁመው ነው ይለዋል ሻማውም ‹‹ታዲያ እኔ ሻማ ነኝ እንዴት ከሩቅ እታያለሁ›› ቢል ሰውዬውም መለሰ ‹‹ሻማዬ ሆይ አንተ ብቻ የቻልከውን ብራ›› አለውና ይዞት ይወጣና ብዙ ደረቅ እንጨቶችን እንደ ዳመራ ከቆለለ ቦሃላ በሻማው እሳት እንጨቶቹን ለኮሰ ብርሃኑም ብዙ ሆነ
ያኔ መርከቡም ተመልክቶ መጣ

ሰውዬውም ለሻማው እንዲህ አ ለው ‹‹ሻማዬ ሆይ አየህ አንተ በቻልካት መጠን ስለበራህ ያንተን ብርሀን ተቀብለው የሚያደማምቁ ብዙዎች አሉ›› አለው፡፡


እንግዲህ እንዲህ ነው የኔ ጥረት ትንሽ ናት አትበል፡፡ የቻልከውን ካደረክ ሌሎች ያንተን ብርሃን የሚቀበሉ እልፎች አሉ

‹‹የትም ሁን ማንም ሁን ያቅምህን በጎ ለማድረግ ግን አትስነፍ ደግነት
እንደ ጥሩ ሽቶ ነው ከአንዱ ተነስቶ ወደ አንዱ ይጋባል››

እንግዲህ አንዲህ ነው ለመስጠት የግድ ሃብታም መሆን
አይጠበቅብህም፡፡ ደግሞ ማንም ሰው ልስጥ ካለ የሚሰጠው አያጣም፡፡

@aleroe
ኤልሮኢ:(መንፈሳዊ ስነፅሁፍ)

በዜሮ ይባዛል!

ፆም×0=0 ስግደት×0=0
ጸሎት ×0=0


ተግቼ ብጸልይ እጆቼን ዘርግቼ
ቤቴ ባዶ ቢቀር ያለኝን መጽውቼ
ቀኑን ሙሉ ብጾም እስኪቆረጥ አንጀቴ
ዘወትር ብሰግድ እስኪዝል ጉልበቴ
በቀድስ ባስቀድስ በመቅደሱ ግርማ
ብዘምር ባወድስ የሚጣፍጥ ዜማ
ወንጌልን ብሰብክ ምስጢር አመስጥሬ
ብናገር ባስተምር ትርጉሙን ዘርዝሬ
ጥልና ክርክር ካሉ በህይወቴ
ሐሜት ክርክር ካልጠፉ ከቤቴ
በዜሮ ይባዛል ፍቅር በማጣቴ።

ስብሐት ለእግዚአብሔር!

ፆም×ፍቅር= 30 ያማር ፍሬ
ጸሎት×ፍቅር= 60ያማር ፍሬ
ስግደት× ትህትና= 100ያማረ ፍሬ

@aleroe
ኤልሮኢ:(ዝማሬ)

# እጠበኝ ቆሽሻለው

እጠበኝ ቆሽሻለው አምላኬ በድያለው
ያለናት ያሳደከኝ ያላባት የ ጠበከኝ
ያንሁሉ ዛሬ ረሳው እጠበኝ ቆሽሻለው/2/

ከድንኳንክ ብታስገባኝ ሞገስ ሰተህ
የ አፍኒንን ምግባር ይዤ አስ ቀየምኩህ
ቅባሜሮን ያተምክበት ልጅነቴ
እንዳይጎድፍ ጠብቅልኝ ቸር አባቴ


ሀይል አኑረክ እንደ ሶምሶን በፀጉሬ
ጎልያድን አስጥለኅኝ በጠጠሬ
አቅም ቢያንሰኝ በስጋ ጦር ተሸንፌ
ደጅህ መጣው የንባ መባ ባይኔ አቅፌ

እንዳትረሳኝ በመዳፍህ ቀርፀሀኅኛል
እንዳተወኝ ያለመጠን ወደህኛል
ባሰነዝር ልት ቀጣኝ የሞት በትር
የትግስትክ ሰሌዳነው ለኔክብ

ከከንፈሬ ጥበብ ጽፈህ ቅኔ ቢፈስ
በመታበይ አሳዘንኩት ያንተን መንፈስ
ፍቅር ግተህ በቅፍስር ያሳደከኝ
እባክህን በበደሌ አትቅፀፈኝ


@aleroe
ኤልሮኢ:(የዕለቱ ምስባክና ወንጌል)
መስከረም 27/01/2013 ዓ.ም

ምስባክ ዘቅዳሴ

ወረከብናሁ ውስተ ዖም ገዳም
ንበውዕ እንከሰ ውስተ አብያቲሁ ለእግዚአብሄር
ወንሰግድ ውስተ መካን ኀበ ቆመ እግረ እግዚእነ


ወንጌል ዘቅዳሴ

የማቴዎስ ወንጌል ም. ፲፱ ቊ. ፲፮ - ፳፯


ቅዳሴ

ዘዮሐንስ አፈ ወርቅ (ናሁ ንዜኑ)


@aleroe
ኤልሮኢ:(መንፈሳዊ ስነ ፅሁፍ)

፨ ተዘጋችተን እኑር፨

ርቀን ከቆምን
ከተዋሕዶ አምባ
ምግባረ ጎዶሎ
እንዳንሆን ገለባ
ለማይበጀን ዓለም
ጭራሽ ለማይረባ
በማይሆነን ሁሉ
ስንል ወጣ ገባ
ያቺ ቀን ሳትመጣ
ሳናውቅ እንደሌባ
ተዘጋጅተን እንኑር
ንስሐም እንግባ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር


@aleroe