"ኤልሮኢ ዘተዋህዶ"
1.2K subscribers
26 photos
3 videos
5 files
21 links
ኤልሮኢ
"በእውኑ የሚያየኝን ጌታ አየሁት"
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ
አምላክ አሜን።
ይህ መንፈሳዊ ቻናል
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ:- +ዝማሬ
+ ምክሮች
+ ስነፅሁፎች
+ አጫጭር ትርክቶች እንዲሁም
+ ምስባክና
+ ወንጌል ይለቀቁበታል።

ለበለጠ መረጃ @AleroeBot
ግሩፑን ለማግኘት @alero
Download Telegram
ኤልሮኢ:
​​ስምህ በሁሉ

ስምህ በሁሉ ተመሰገነ
ከክብር በላይ ክብርህ ገነነ
አንተን ማወደስ ያስደስተናል
ስምህን ማክበር ክብራችን ሆኗል(፪)

አምላክ ተመስገን በሰማያት
ስምህ ይወደስ በፍጥረታት
ከህፃናት አፍ ምስጋና ይውጣ
አንተን ማመስገን ይሁን የኛ ዕጣ(፪)
አዝ = = = = = =
በምግብ እጦት ብንሰቃይም
ማህሌትህን አናቋርጥም
የመከራ ዶፍ ቢወርድብንም
እንዘምራለን ለአምላካችን ስም(፪)
አዝ = = = = = =
ሰማዩ ዝናብ ደመና ቢያጣም
ፍቅርህ በእኛ ውስጥ አላቋረጠም
ቸርነትህን እንጠብቃለን
ከአንተ ደጅ ጌታ የት እንሄዳለን(፪)


#ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ



@aleroe
ኤልሮኢ:

አብይ ጾም -የካቲት 25 /06/2011 ሰኞ
ደብረ ዘይት- መጋቢት 22/07/2011 እሁድ
ሆሣዕና- ሚያዚያ 13/08/2011 እሁድ
ስቅለት - ሚያዚያ 18/ 08/2011 አርብ
ትንሳኤ- ሚያዚያ 20/08/2011 አሁድ
እርክበ ካህናት - ግንቦት 14/09/2011 እሮብ
ዕርገት - ግንቦት 29/09/2011 ሀሙስ
ጰራቅሊጦስ - ሰኔ 9/10/2011 እሁድ
ጾመ ሀዋርያት - ሰኔ 10/10/11 ሰኞ
ጾመ ድህነት - ሰኔ 12/10/11እሮብ

@aleroe
ኤልሮኢ:

💚💛❤️ የሕጻን ነገር 💚💛❤️
-------------------

አንድ መምህር በስብከተ ወንጌሉ መርሐ ግብራቸው ስለመንግስተ ሰማያት ጥሩ አድርገው ይተርኩና ሕዝብ ሁሉ መመሰጡን ሲያዩ "አሁን ከእናንተ መኻል መንግስተ ሰማያት መግባት የማይፈልግ አለ??" ብለው በጅምላ ሲጠይቁ ሁሉም በህብረት "የለም!" ብለው መለሱ።

:በዚህ ያልረኩት መምህር "እስኪ መንግስተ ሰማይምት መግባት የምትፈልጉ እጃችሁን ወደላይ አውጡ" ይላሉ። ሁሉም ያወጣል

:አንድ ሕጻን ግን ትንንሽ እጆቹን በጉንጮቹ ላይ አድርጎ ክርኑን በጉልበቶቹ ላይ ተክሎ በሚያሳዝን አኳኋን ተቀምጦ መምህሩን ብቻ ያያል። የሕጻኑ ሁኔታ የገዛችው መምህር ወደ ሕጻኑ ጠጋ ብለው "ማሙሽዬ አንተ ለምን እጅህን አላውጣህም? መንግስተ ሰማይ መግባት አትፈልግም?" አሉት

: ሕጻኑም ነቃ ብሎ "መግባትማ እፈልጋለሁ ነገር ግን እናቴ ጉባኤው እንዳለቀ የትም መሔድ የለም ባስቸኳይ እቤት እንድትመጣ ስላለችኝ ነው" አለ ይባላል።

ሕጻኑ የእናቱን ዐደራ ማስታወሱ የሚደነቅ ነው። የሕጻን ነገር ያልነው ግን መንግስተ ሰማይ ላለመግባት ያቀረባትን ምክንያት ለመጥቀስ ነው።
#ዛሬም በየዓውደ ምህረቱ ማዕደ እግዚአብሔር ተዘርግቶ፤ በቤተ ክርስቲያን ሥርዓተ ጸሎት እየደረሰ ልባችን እቤት ሆኖ የተቋጠረ ሲፈታ፤ የተፈታ ሲቋጥር ጊዜውን የምንጨርስ ስንቶች አለን።

#ላለመጸለይ #ላለማስቀደስ #ንስሀ ላለመግባት #ላለመቁረብ ምክንያት መደርደር ከገሃነም እሳት አያድነንም!!!!!!!!!!!!!!!!

@aleroe
ምን ያህል ወደዱት????
ኤልሮኢ:

".....ልቡ ግን ከእኔ ርቋል..."


አንድ ባሕታዊ ብዙ ሰዎች ሰብስበው እየሰበኩ ሳለ ጭራቅ ከጫካ ወደ ጉባኤው ይመጣል። ወደ ባሕታዊው ቀረብ ይልና "አባቴ እንግዲህ እንደምታውቁት የእኔ ሕልውና በሰው ሥጋና ደም ላይ የተመረኮዘ ስለሆነ እነኝህን ሰዎች ልበላቸው ነው" አላቸው።

ባሕታዊውም የሰው ሥጋ መብላትህን አውቃለሁ ግና እነዚህ ልጆቼን አትበላሸቸውም የክርስቶስ ናቸውና አትችልም ብለው ገዘቱት።

አቶዬም ግድ የሎትም አባቴ እኔ የክርስቶስ የሆኑትን አልበላም ንክችም አላረግም ሲል ቃል ገባላቸውና ተለያዩ።

ከሄዱበትም ሲመለሱ ጭራቁ ባሕታዊው ያስተማሩትን ሰው ሁሉ በልቶ ከንፈሮቻቸውንና ምላሳቸውን አስቀርቶ ጠበቃቸው ። በጉዳዩም በጣም የተቆጡት ባሕታዊ ምነው የክርስቶስ ናቸው እንዳትበላ አላልኩህም አሉት።

ጭራቁም በሰው ደም የለሰለሰውን ከንፈሮቹን በምላሱ እያበሰ "የክርስቶስ የሆኑትን አሁንም አልበላሁም" ብሎ በኩራት መለስላቸው።

ምን ማለትህ ነው ያስቀረኸው የለም እኮ ቢሉት "አባቴአባቴ የክርስቶስ የሆነው ምላሳቸው ነው። ክርስቶስ ያለው ከንፈሮቻቸውና ምላሳቸው ላይ ብቻ ስለሆነ ሌላውን አካላቸውን በላሁት" አላቸው።
ዛሬም በክስርቶስ ስም ተጠርተን አካላቱ ሆነን ልንመላለስ በሚያስፈልግበት ጊዜ እኛ በእርግጥ ሆነናል ወይስ እንደሰዎቹ ከወገብ በላይ ታቦት ከወገብ በታች ጣኦት ነን።

ይህ ሕዝብ በከንፈሩ ያከብረኛል ልቡ ግን ከእኔ ርቋል ማቴ ፲፭፣፯ ቃሉን ሰምቶ የማያድርገው ፊቱን በመስታወት እንደሚያይ ሰው ይመስላል። ፊቱን ካየው በኋላ ዞር ሲል ፊቱን ይረሳዋልና።
👉@aleroe👈
👉@aleroe👈
👉@aleroe👈
ኤልሮኢ፡(ስነ ፅሁፍ)

……🖌ላዩን ውብ ሆኛለሁ

ላዩን ውብ ሆኛለሁ ውስጤ ግን እረክሷል፣
ንፅህና የለም በኃጥያት ቆሽሿል።
አንደበቴ ሀያል ሁሉን አወቅኩ ባይ ነው፣
የተለሳለሰ ደግ መሳይ መርዝ ነው።
ለተመለከተኝ ላስተዋለኝ ሰው፣
ክንፍ እንጂ ምን ቀረው የማይለኝ ማነው።
በጎ ስነምግባር ትህትና የሌለኝ ፣
መስዬ የምኖር የስም ክርስቲያን ነኝ።
ፍሬ አልባ ወይን ነኝ የማላስደስት፣
አንተ ይቅር በለኝ አምላከ ምህረት።
መወደስ በከንቱ ከእንግዲህ ይብቃኝ፣
እውነተኛ እንድሆን ፈጣሪዬ እርዳኝ።

👉👉👉👉@aleroe👈👈👈👈
ኤልሮኢ:
#ጽኑ_ሰማዕት

ጽኑ ሰማዕት የእምነት አርበኛ
አርሴማ ነይ ነይ ወደኛ
------------------------------
ነይ ነይ ቅዱስ አትናትዮስ
›› ›› በስዕለት ያገኙሽ
›› ›› ብሉይን ከሀዲስ
›› ›› ጠንቅቀሽ የተማርሽ
›› ›› በፍፁም ትህትና
›› ›› በጸሎት የተጋሽ
›› ›› አርሴማ ልዩ ነሽ
›› ›› አምላክ የመረጠሸ
-------------------------------
ነይ ነይ ውበትም ሀሰት ነው
›› ›› ደም ግባትም ከንቱ
›› ›› ንብረት ትዳር ሁሉ
›› ›› አላፊ ውዕቱ
›› ›› ንግስት መባልን
›› ›› በፍጹም ሳትሻ
›› ›› አለምን በመናቅ
›› ›› ገባች ወደዋሻ
-------------------------------------
ነይ ነይ አረመኔው ድርጣድስ
›› ›› ቢያሰቃይሽም
›› ›› ውበቴ ክርስቶስ
›› ›› ነው ብለሽ ሰበክሽ
›› ›› አንገትሽን ለሰይፍ
›› ›› አሳልፈሽ ሰጠሸ
›› ›› ክብርሽም ተገልጾ
›› ›› ለአለም አበራሽ
---------------------------------
ነይ ነይ አርአያ ልትሆኝን
›› ›› ለእኛ ለሁላችን
›› ›› ፈፅመሽ አሳየሽ
›› ›› ታላቅ ተጋድሎሽን
›› ›› ይህን አለም ድል መንሳት
›› ›› አቅቶናል እና
›› ›› አርሴማ አትለይን
›› ›› በእምነት እንድንጸና

@aleroe
ኤልሮኢ:

#አስተውል

☞ ከጎንህ ያለችው ሚስትህ ~ የላጤዎች ሁሉ ምኞት ናት፤
☞ የከዳሀው ልጅህ ~ መውለድ የማይችሉ ሁሉ ምኞት ነው፤
☞ ደሳሳ ጎጆህ ~ ቤት የሌላቸው ሁሉ ምኞት ነች፤
☞ አድካሚ ስራህ ~ ስራ የሌላቸው ሁሉ ምኞት ነው፤
☞ ትንሿ ሀብትህ ~ ምንም ሀብት የሌላቸው ሁሉ ምኞት ነች፤
☞ ውድ የሆነው ጤናህ ~ አልጋ ላይ የሚማቅቁት ሁሉ ምኞት ነች፤
☞ ትንሿ ፈገግታህ ~ የተጨነቁ ያዘኑት ሁሉ ምኞት ነች፤
☞ ሚስትህ የደበቀችልህ ገበና ~ የተጋለጡት እና
የተዋረዱት ሁሉ ምኞት ነች፤
☞ በነፃነት እንደፈለክ የምትንቀሳቀሰው ~ በእስር የሚሰቃዩ መንቀሳቀስ የማይችሉት ሁሉ ምኞት ነች፤
***፦እስኪ መዳፍህን ተመልከት በብዙ ስጦታ በረከት ተሞልቷል፤ ነገር ግን የፈጣሪ ስጦታ በጣምምም በዛና የተሰጠንን ሁሉ ማየት ተሳነን፤
የሚያይ አይን ሳይሆን የሚያስተውል ልቦና ይስጠን
እና እግዚአብሔርን አመስግን ።

@aleroe
ኤልሮኢ:(ስነ ፅሁፍ)

#በምህረቱ መራኝ

ትላንት ነበርኩኝ እያለው የሌለው
እንዳማረ ተክል ፍሬ እንደሌለው
ደስታዬም ነበረ ለሞቴ መንገዱ
ህይወቴም ሚመስሉ አንዳች ያልተጎዱ
እውነታው ባይገባኝ የመኖሬ ምክንያት
እጆቼን ዘረጋው እምባዬም ፈሰሰ
ጉልበቴም ታዘዙ ለዳንስ እንዳልተነሱ
ልሳኔም በቃሉ ይቅርታን ለመነ
የወደቀልኝን እርሱን አገነነ
መውደቄን ተረድቶ የማይለኝ ችላ
አምላከ ብርሃን ህይወቴን አጎላ
በመሃሪነቱ ምህረቱን ሽሮኝ
ለህይወቴ ፍዳ መፍትሄው ሆነኝ



___
👉👉👉@aleroe👈👈👈
ኤልሮኢ:(መዝሙር)

ገብርኤል ነው

ገብርኤል ነው አምላክ የሾመው(፪)
አናንያን አዛርያን ሚሳኤልን ከእሳት ያዳነው

ናቡከደነፆር አንተን በግልፅ አይቶ
ለእግዚአብሔር ሰገደ ያንን ምስል ትቶ
ሐሰትም እነደሆን ይመስክሩ ሦስቱ
ከዚያች ከባቢሎን (፪) የወጡት ከሳእቱ
አዝ = = = = =
ከዓለመ መላእክት ከቅዱሱ ቦታ
የሰውን ልጅ መረጥክ ልትረዳ ጠዋት ማታ
አንጌቤናይቷ ቅድስት ኢየሉጣ
ትመስክር ስላንተ(፪) ከነልጇ ትምጣ
አዝ = = = = =
ልመስክር ስላንተ ነህና ሕይወቴ
ገብርኤል (፪)ሰመረ ስለቴ
የአናብስቱን አፍ የዘጋኸው መላክ
ገብርኤል አንተ ነህ (፪)በእኛ ሁሉ የታመንክ


ቀሲስ ዘበነ ለማ


@aleroe
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ኤልሮኢ:

ለራስህ ነው

አንተ ሰው! ቊጥር የሌላቸው ክፋቶች ቢኖሩብህም እንኳ በጎ ምግባር በልጅህ ይኖር ዘንድ በማድረግ አካክሰው፡፡ ለክርስቶስ የሚኾን ተሽቀዳዳሚ (ሯጭ) አሳድግ! ወዳጄ ሆይ! እንደዚህ ብዬ ስነግርህ አትፍራ፤ አትሸበርም፡፡ ልጅህ እንዳያገባ አድርገው አላልኩህም፡፡ ወደ ገዳም ወስደህ እንድታመነኩሰው ወይም የብሕትውና ሕይወትን እንዲመራ አድርገው አላልኩህም፡፡ እያልኩህ ያለሁት ይህን አይደለም፡፡ ልጅህ ቢመነኩስ እወድ ነበር፡፡ ብዙዎች ወደዚህ ሕይወት እንዲገቡ የዘወትር ጸሎቴ ነውና፡፡ ነገር ግን የምንኵስና ሕይወት [ሳይጠሩ ከገቡበት] ከባድ ሸክም ስለ ኾነ ሰዎች መነኰሳት ካልኾኑ ብዬ ግድ አልልም፡፡ ለአንተም እንደዚህ በግድ አመንኩሰው አልልህም፡፡ እያልኩህ ያለሁት ለክርስቶስ የሚኾን ተሸቀዳዳሚ አሳድግ ነው፡፡ በዚህ ዓለም አግብቶ፣ ልጆችንም ወልዶ የሚኖር ቢኾንም እንኳን ገና ከሕፃንነቱ አንሥቶ ሰውን የሚያከብር እንዲኾን አድርገህ አሳድገው ነው፡፡
ገና ጨቅላ እያለ በጎ በጎ ትእዛዛት በሕሊናው ጓዳ በልቡናው ሰሌዳ ላይ ከተቀረጸ፥ በሰም እንደ ታተመ ጸንቶ ይኖራል እንጂ ሲያድግ እነዚህን ትእዛዛት ሊያጠፋበትና ሊፍቅበት የሚችል ማንም አይኖርምና፡፡ ልጅህ አሁን ያለበት ዕድሜ ደግሞ በሚያየውና በሚነገረው በሌላም ነገር ኹሉ የሚንቀጠቀጥበት፣ የሚፈራበትና የሚደነግጥበት ዕድሜ ነው፡፡ ስለዚህ ልክ እንዳልደረቀ ሰም እንደምትፈልገው አድርገህ ቅረጸው፡፡ እንደዚህ አድርገህ ስታበቃ፥ መልካም ልጅ ቢኖርህ የመጀመሪያው ተጠቃሚ የምትኾነው አንተው ራስህ ነህ፡፡ እግዚአብሔር የሚጠቀመው ከአንተ በኋላ ነው፡፡ ስለዚህ የምትደክመው ለሌላ አካል ሳይኾን ለራስህ ነው፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ

@aleroe
ኤልሮኢ:

#ነበርኩ_መች_ያድናል


ሀጢያትን ስትሰራ አምላክን እረስተህ
ቅዱሱን ሰውነት በሀጢያት አርክሰህ
ትእዛዝን ሳትፈጽም መልካምን ሳትሰራ
ዘይት ሳታዘጋጅ መብራትህ ሳይበራ
በተጠራህ ጊዜ መላከሞት ሲመጣ
ለማያልፈው አለም ሲወጣልህ እጣ
ለሚዛን ስትቀርብ አገልጋይ ነበርኩኝ እያልክ መናገሩ
መዝሙር ዘምሬያለው ሄጃለው ከበሩ
ብሎ መከራከር ያኔ መች ይጠቅማል
ይዞ መገኘት ነው ነበርኩ መች ያድናል!!!!
____________________

@aleroe
ኤልሮኢ:

​​አድርገህልኛልና በቸርነትህ

አድርገህልኛልና በቸርነትህ
አመሰግንሃለሁ እልል፪
ለዓለመ ዓለም አማኑኤል
እገዛልሃለሁ መድኃኔዓለም፪

ቀኑ ጨልሞብኝ ዙሪያው ገደል ሆኖ
የችግር አረንቋ ፊቴ ተደቅኖ
ረዳት ያጣሁኝ በመሰለኝ ጊዜ
ፍጽሞ አራቅህልኝ የልቤን ትካዜ
አዝ = = = = = =
አምላኬ ጉልበቴ ኃይሌ መመኪያዬ
ጠላት ማሳፈሪያ የእምነት ጋሻዬ
እንደማትተወኝ አሁን አውቄአለሁ
ካለኝ ነገር ይልቅ በአንተ ታምኛለሁ
አዝ = = = = = =
ጥቂቷን አብዝተህ ለምትመግብ ጌታ
የምመልስልህ ባለገኝ ሥጦታ
በቀንም በሌትም ሁሌ ለሚያበራ
መንክር ለባሕርይህ ዕጽብ ለአንተ ሥራ
አዝ = = = = = =
አምላክ ሆይ ምሥጋና ለአንተ ይገባሃል
ለምስኪኗ ጎጆ በረከት ሰጥተሃል
ደሃ ነኝ አልልም ሀብቴ አንተ ነህና
ማሰሮዬ ሞልቷል ላይጎድል እንደገና



<< አድርገህልኛልና ለዘላለም አመሰግንሃለሁ >>
መዝ፶፪፥፱

@aleroe
ኤልሮኢ፡
አድዋ

………………
ምንሊክ ተወልዶ ባያነሳ ጋሻ
ግብሩ እንቁላል ነበር ይህን ጊዜ አበሻ
በሠራው ወጨፎ ባመጣው እርሳስ
ተፈጠመ ጣሊያን አበሻ እንዳይደርስ
ምኒልክ ተጉዞ የምትጠይቁኝ
ፊትም አላለፈ ሁዋላ አይገኝ
አባተ በመድፉ አምሳውን ሲገድል
ባልቻ በመትረየስ ነጥሎ ሲጥል
የጎጃሙ ንጉሥ ግፋ በለው ሲል
እቴጌ ጣይቱ እቴጌ ብርሀን
ዳዊቷን ዘርግታ ሰምዐኒ ስትል
ተማራኪው ባዙቅ ውሃ ውሃ ሲል
ዳኛው ስጠው አለ ሠላሳ በርሜል
እንደ በላዔ ሰብእ እንደመቤታችን
ሲቻለው ይምራል የኛም ጌታችን።

@aleroe
ኤልሮኢ:(መዝሙር)
#ንጹም_ፆመ

ንጹም ፆመ ወናፍቅር ቢጸነ
ወንትፋቀር(፬) ንትፋቀር በበይናቲነ ኧኸ(፫)
#ትርጉም
ፆምን እንጹም ባልንጀራችንን እንውደድ
እርስ በራሳችንም እንፋቀር


@aleroe
ኤልሮኢ:
፨መርሳት፨

በአንድ ወቅት የግብጹ ሊቀ ጳጳስ ብጹኡ ወቅዱስ አቡነ ሽኖዳ እያስተማሩ ባሉበት ወቅት በዙ ጥያቄዎች በጹሑፍ ይደርሳቸው ነበር። ታዲያ ከነዛ ጹሑፎች መካከል አንዱ እንዲ ይላል
... አባቴ እኔ ታላቅ የመርሳት ችግር አለብኝ ያደረኩትን የሰማሁትን ነገሮች በሙሉ እረሳቸዋለው እና አባቴ ምን እንደማደርግ ይምከሩኝ ነበር የሚለው። ብጹእነታቸውም ልጄ መምከሩንስ እመክርሃለሁ ምን ማድርግ እንዳለብህ እነግርሃለሁ ግን እንዳትረሳው እፈራለሁ አሉት ይባላል።
ቃለ እግዚአብሔር ስንሰማ በማስተዋል ልቦናችንንም ሰብስበን ሊሆን ይገባል።
በነገሮችም ሁሉ አስተዋዮች ልንሆን ይገባል።በዚህም ማስተዋል እና ጥበብን ወደሚሰጥ አምላክ አጥብቀን ልንማጸን ይገባናል።

@aleroe
ኤልሮኢ:

ሩጫ ✞............🏃🏃🏃🏃

ማልያህን ታጠቅ
ቀበቶህን አጥብቅ
ጫማህን አጠባብቅ
መስመርህን ጠብቅ
አትይ ወደ ኋላ
ተብሎ ተነግሮን
ጀምረን ሩጫ
ለመቀበል ዋንጫ
እኛ ዞርን ስናይ
እነሱ ፈጠኑ
ከሽልማት ጌታ ጽዋም ተቀበሉ።

@aleroe
ኤልሮኢ:(መዝሙር)

አዝናለሁ አለቅሳለሁ

አዝናለሁ አለቅሳለሁ
ስለ በደሌ ሁል ጊዜ አለቅሳለሁ
አዝናለሁ አለቅሳለሁ
ስለ ጥፋቴ ሁል ጊዜ አለቅሳለሁ
ነገር ግን መሐሪ ነህና
እንደምታድነኝ አምናለሁ

ሥጋዬ ለራሱ እያታለለኝ(፪)
ሁሉን በመፈለግ ወሰደና ለጥፋት ሰጠኝ(፪)
አዝ = = = = =
ከመሬት ተገኝታ እስክትገባ
በከንቱ አስቀረችኝ አምላኬ ሆይ ሥጋ ሰገብጋባ(፪)
አዝ = = = = =
ትቻት መምጣቴ ነው አፈር ሥጋዬን
እንድትቀበላት አምላኬ ሆይ አደራ ነፍሴን(፪)

@aleroe
ኤልሮኢ:
. #ጸሎት

#ጸሎት ያቆመች ነብስ እየሞተች ያለች ነች።
#ለሊት ተነሥቶ በጸሎት ጠላቱን ያልመታ ጥዋት ቀኑን ሙሉ ሰይጣን ሲመታው (ሲቀጠቅጠው) ይውላል።
#ክርስትያን ተንበርክኮ ማንበርከክ ይችላል። የማይጸልይ ከሆነ ደግሞ ገና ሳይዋጋ ይንበረከካል።
#ሌሊት በጸሎት ያልወረድክበት ሰይጣን። ቀኑን ሙሉ ሲያገሳብህ ይውላል።
#ከእግዚአብሔር ጋር አንዲት ቀን ሳታሳልፍ ከዋልክ፦ ከመልካሙ
ዘመንህ ውስጥ አንዲቷ ቀንህ በከንቱ እንዳባከንካት ቁጠራት።
#እግዚአብሔርን በጸሎት የማይለምን፦ ዘወትር የሰውን ፊት የሚያይ ተለማማጭ ሆኖ ይኖራል።
#ከእግዚአብሔር ጋር መልካም ጊዜን ማሳለፍ፦ገንዘብህን ከፍተኛ ትርፍ ከሚያስገኝ ንግድ (ኢንቨስት) ከማድረግ በላይ እጅግ ጠቃሚ ነው።


@aleroe
ኤልሮኢ:
01/07/09

መዝሙር መሐሩነ
#ቅድስት

#በዕለቱ ቅዳሴ ሰዓት የሚነበቡ መልዕክታት፣ወንጌልና ምስባክ፡፡

#የዕለቱ ምስባክ፦ መዝ ፺፭፥፭

እግዚአብሔርሰ ሰማያተ ገብረ
አሚን ወሠናይት ቅድሜሁ
ቅድሳት ወዕበየ ስብሐት ውስተ መቅደሱ

#ትርጉም
እግዚአብሔር ግን ሰማያትን ፈጠረ
እምነትና በጎነት በፊቱ ናቸው
ቅድስና እና የክብር ገናንነት በመቅደሱ ውስጥ ናቸው።

የዕለቱ ወንጌል፦

ማቴ ፮፥፲፯ - ፳፭
ቅዳሴ፦ ዘኤጲፋንዮስ

👉 @aleroe