ኤልሮኢ:(⚜የዕለቱ ምስባክና ወንጌል⚜)
ነሐሴ 29/12/2012 ዓ.ም
ምስባክ ዘነግህ
መዝ ፻፲፥፫(110፥3)
ምስሌከ ቀዳማዊ በዕለተ ኃይል
በብርሃኖሙ ለቅዱሳን
ወለድኩከ እምቅድመ ኮከበ ጽባሕ
ምስባክ ዘቅዳሴ
እዜምር ወእሌቡ ፍኖተ ንጹሐ
ማዕዜ ትመጽእ ኀቤየ
ወአሐውር በየዋሃተ ልብየ ማዕከለ ቤትየ
ቅዳሴ
ዘእግዚእነ (ነአኩተከ)
@aleroe
ነሐሴ 29/12/2012 ዓ.ም
ምስባክ ዘነግህ
መዝ ፻፲፥፫(110፥3)
ምስሌከ ቀዳማዊ በዕለተ ኃይል
በብርሃኖሙ ለቅዱሳን
ወለድኩከ እምቅድመ ኮከበ ጽባሕ
ምስባክ ዘቅዳሴ
እዜምር ወእሌቡ ፍኖተ ንጹሐ
ማዕዜ ትመጽእ ኀቤየ
ወአሐውር በየዋሃተ ልብየ ማዕከለ ቤትየ
ቅዳሴ
ዘእግዚእነ (ነአኩተከ)
@aleroe
ኤልሮኢ:(⚜ትምህርት⚜)
፨ በመንፈስ ጀምሮ በሥጋ መጨረስ ፨
ጌታችን በውኃ ላይ እየተራመደ ወደ ሐዋርያት ሲመጣ ቅዱስ ጴጥሮስ ጌታን ተመልክቶ በእምነት " ጌታ ሆይ
በውኃ ላይ ወደ አንተ እንድመጣ እዘዘኝ" አለው። ጌታም እምነቱን ተመልክቶ "ና" አለው። ቅዱስ ጴጥሮስ ከታንኳይቱ ወርዶ ወንድሞቹ ሐዋርያት እስኪደነቁ ውኃውን
እንደ የብስ በመቁጠር በባህር ላይ እየተራመደ ወደ ጌታ ሄደ። ልክ ጌታችን ጋር ሊደርስ ሲል የንፋሱ ኃይል ሲያናውጠው ባህሩ የሚያሰጥመው ስለመሰለው እምነቱ ጎደለ። አጠገቡ በባህሩ ላይ የቆመውን ና ያለውን ጌታ ማሰብ ትቶ በሥጋ ፈርቶ "እሰጥም ይሆን" አለ። በባህሩ ላይ ያስኬደው፣ያቆመው እምነቱ ሲከዳው፣ ባህሩ አሰጠመው።
ጴጥሮስም በመንፈስ ጀምሮ በሥጋ ጨረሰ። አንተም በእምነት ጀምረህ እምነትህ ልክ ጌታህ ጋር ሊያደርስ ሲል በሥጋ ፍላጎት መናወጥ ከጀመርክ
በኃጢአት ባህር ትሰጥማህ። ብዙዎች መንፈሳዊነትን በጽኑ እምነት ጀምረው፣ልክ ጌታ ጋር ሊደርሱ ሲሉ፤የሰይጣን የፈተና ንፋስ እያንገዳገዳቸው፣ትዕግስት እያሳጣቸው ከመጽናት፤ በኃጢአት ባህር ሰጥመው መዋኘት ይጀምራሉ።
ቅዱስ ጴጥሮስ በእምነት የጀመረውን በሥጋ ቢጨርስም በባህሩ ሰጥሞ እንዳይቀር ጌታውን "ጌታ ሆይ አድነኝ"
ብሎ ጮኸ። ጌታችንም ቅዱስ ጴጥሮስን "አንተ እምነት የጎደለህ፣ስለምን ተጠራጠርህ?" ብሎ ወቅሶት እጁን፣ዘርግቶለት ከባህሩ አውጥቶታል።
አንተም ምንም በኃጢአት ባህር ብትሰጥምም፣ እምነት ቢጎድልህም ጌታህን "አድነኝ" ብለህ ብትጮህ ለጴጥሮስ የተዘረጋ እጁም ላንተ ይዘረጋል፣ከሰጠምክበትም ያወጣኃል። ብቻ አድነኝ ብለህ ጮህ። ማቴ 14÷25
@aleroe
፨ በመንፈስ ጀምሮ በሥጋ መጨረስ ፨
ጌታችን በውኃ ላይ እየተራመደ ወደ ሐዋርያት ሲመጣ ቅዱስ ጴጥሮስ ጌታን ተመልክቶ በእምነት " ጌታ ሆይ
በውኃ ላይ ወደ አንተ እንድመጣ እዘዘኝ" አለው። ጌታም እምነቱን ተመልክቶ "ና" አለው። ቅዱስ ጴጥሮስ ከታንኳይቱ ወርዶ ወንድሞቹ ሐዋርያት እስኪደነቁ ውኃውን
እንደ የብስ በመቁጠር በባህር ላይ እየተራመደ ወደ ጌታ ሄደ። ልክ ጌታችን ጋር ሊደርስ ሲል የንፋሱ ኃይል ሲያናውጠው ባህሩ የሚያሰጥመው ስለመሰለው እምነቱ ጎደለ። አጠገቡ በባህሩ ላይ የቆመውን ና ያለውን ጌታ ማሰብ ትቶ በሥጋ ፈርቶ "እሰጥም ይሆን" አለ። በባህሩ ላይ ያስኬደው፣ያቆመው እምነቱ ሲከዳው፣ ባህሩ አሰጠመው።
ጴጥሮስም በመንፈስ ጀምሮ በሥጋ ጨረሰ። አንተም በእምነት ጀምረህ እምነትህ ልክ ጌታህ ጋር ሊያደርስ ሲል በሥጋ ፍላጎት መናወጥ ከጀመርክ
በኃጢአት ባህር ትሰጥማህ። ብዙዎች መንፈሳዊነትን በጽኑ እምነት ጀምረው፣ልክ ጌታ ጋር ሊደርሱ ሲሉ፤የሰይጣን የፈተና ንፋስ እያንገዳገዳቸው፣ትዕግስት እያሳጣቸው ከመጽናት፤ በኃጢአት ባህር ሰጥመው መዋኘት ይጀምራሉ።
ቅዱስ ጴጥሮስ በእምነት የጀመረውን በሥጋ ቢጨርስም በባህሩ ሰጥሞ እንዳይቀር ጌታውን "ጌታ ሆይ አድነኝ"
ብሎ ጮኸ። ጌታችንም ቅዱስ ጴጥሮስን "አንተ እምነት የጎደለህ፣ስለምን ተጠራጠርህ?" ብሎ ወቅሶት እጁን፣ዘርግቶለት ከባህሩ አውጥቶታል።
አንተም ምንም በኃጢአት ባህር ብትሰጥምም፣ እምነት ቢጎድልህም ጌታህን "አድነኝ" ብለህ ብትጮህ ለጴጥሮስ የተዘረጋ እጁም ላንተ ይዘረጋል፣ከሰጠምክበትም ያወጣኃል። ብቻ አድነኝ ብለህ ጮህ። ማቴ 14÷25
@aleroe
ኤልሮኢ፡(⚜ስነፅሁፍ⚜)
… ✍ምንም አይምሰልህ
የምትሰራው ስራ ሰውን ካልበደለ፣
ክፋትና ተንኮል በልብህ ከሌለ።
ጠንቅቀህ ከፈፀምክ ማድረግ ያለብህን፣
ማንንም ካልጎዳህ ካመንክ አምላክህን።
ላንተ ጥቅም ብለህ ካልገፋህ ሌላውን፣
ይቅርታ ከለመንክ አምነህ ጥፋትህን።
የምታውቀው ታሪክ የምታውቀው ነገር፣
እንዳልሆነ ሆኖ ሲወራ ሲነገር።
የለብህምና ዝም ብሎ መስማት፣
ቀስ ብለህ ብትሞክር ለመስጠት እርማት።
ከእኛ ሌላ አዋቂ ፍፁም የለም ባዮች ፣
የወሬ አንበሳ የተግባር አንካሶች፣
የነገር ሱሰኛ የወሬ ጥመኞች።
ምንም እንደማታውቅ አድርገው ቢቆጡርህ፣
እውቀቱ ካንተ ጋር ታዲያ ምን ቸገረህ፣
አምላክ ካንተ ጋር ነው ምንም አይምሰልህ።
@aleroe
… ✍ምንም አይምሰልህ
የምትሰራው ስራ ሰውን ካልበደለ፣
ክፋትና ተንኮል በልብህ ከሌለ።
ጠንቅቀህ ከፈፀምክ ማድረግ ያለብህን፣
ማንንም ካልጎዳህ ካመንክ አምላክህን።
ላንተ ጥቅም ብለህ ካልገፋህ ሌላውን፣
ይቅርታ ከለመንክ አምነህ ጥፋትህን።
የምታውቀው ታሪክ የምታውቀው ነገር፣
እንዳልሆነ ሆኖ ሲወራ ሲነገር።
የለብህምና ዝም ብሎ መስማት፣
ቀስ ብለህ ብትሞክር ለመስጠት እርማት።
ከእኛ ሌላ አዋቂ ፍፁም የለም ባዮች ፣
የወሬ አንበሳ የተግባር አንካሶች፣
የነገር ሱሰኛ የወሬ ጥመኞች።
ምንም እንደማታውቅ አድርገው ቢቆጡርህ፣
እውቀቱ ካንተ ጋር ታዲያ ምን ቸገረህ፣
አምላክ ካንተ ጋር ነው ምንም አይምሰልህ።
@aleroe
ኤልሮኢ:(⚜የዕለቱ ምስባክና ወንጌል⚜)
ጳጉሜን 01/13/2012 ዓ.ም
ምስባክ
እግዚአብሔርሰ ገሃደ ይመጽእ
ወአምላክነሂ ኢያረምም
እሳት ይነድድ ቅድሜሁ መዝ ፵፱፥፫
ትርጒም
እግዚአብሔር በግልጥ ይመጣል
አምላካችን ዝም አይልም
እሳት በፊቱ ይነዳል
የዕለቱ ወንጌል፦
ሉቃ ፲፯፥፳፪ - ፍጻሜ
ቅዳሴ
ዘዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ (ኀቤከ)
@aleroe
ጳጉሜን 01/13/2012 ዓ.ም
ምስባክ
እግዚአብሔርሰ ገሃደ ይመጽእ
ወአምላክነሂ ኢያረምም
እሳት ይነድድ ቅድሜሁ መዝ ፵፱፥፫
ትርጒም
እግዚአብሔር በግልጥ ይመጣል
አምላካችን ዝም አይልም
እሳት በፊቱ ይነዳል
የዕለቱ ወንጌል፦
ሉቃ ፲፯፥፳፪ - ፍጻሜ
ቅዳሴ
ዘዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ (ኀቤከ)
@aleroe
ኤልሮኢ:(⚜መንፈሳዊ ትርክት⚜)
+++ ልብስህን ማን ወሰደው? +++
በአንድ ወቅት አባ ሰራብዮን ወደ እስክንድርያ ሄደ፡፡ በገበያም ስፍራ አንድ ከልብስ የተራቆተ ነዳይ አገኘ፡፡ ለራሱም ‹ይህ ደሃ ሰው ታርዞ መነኩሴ የተባልኩ እኔ እንዴት ለብሼ እታያለሁ? በእውነት ይህ ‹ታርዤ አልብሳችሁኛልና› ብሎ የተናገረው ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ አይደለምን? በዚህ ብርድ አየር እየተሰቃየ እኮ ነው!› ብሎ ፈጥኖ የገዛ ልብሱን ከራሱ በማውለቅ ይለብስ ዘንድ ለዚያ ደሃ ሰጠው፡፡ ከዚያም በእጁ ያለውን መጽሐፍ ቅዱስ እንደያዘ እርቃኑን በጎዳናው ላይ ተቀመጠ፡፡ የከተማውም ባለጠጋ ሰው አባ ሰራብዮን ባለበት ሥፍራ ሲያልፍ ተመልክቶት ወደ እርሱ ቀረበና ‹አባ ሰራብዮን ሆይ ልብስህን ማን ወሰደው?› ሲል ጠየቀው፡፡ ቅዱስም በእጁ ወደ ያዘው መጽሐፍ ቅዱስ እየጠቆመ ‹ልብሴን የወሰደው ይህ ነው!› አለው፡፡ ያም ባለጠጋ ልብስን ገዝቶ ካለበሰው በኋላ አባ ሰራብዮን ከእርሱ እንደ ተለየ በመንገድ ዕዳውን መክፈል ስላልቻለ እየተንገላታ ወደ ወኅኒ ቤት የሚሄድን አንድ ሰው ተመለከተ፡፡ ቅዱሱም አባት የያዘውን መጽሐፍ ቅዱሱን ሽጦ የዚያን ሰው ዕዳ በመክፈል ነጻ አደረገው፡፡ ይህንም ፈጽሞ ጉዞውን ሲጀምር ሌላ አንድ ነዳይ ሲለምን ተመልክቶ ዳግመኛ የለበሰውን ልብስ አውልቆ ሰጥቶ እርቃኑን ወደ በአቱ ተመለሰ፡፡ ደቀ መዛሙርቱም እርቃኑን ባዩት ጊዜ ‹መምህር! ልብስህ ወዴት አለ?› ብለው ጠየቁት፡፡ እርሱም ‹መጸወትኩት› አላቸው፡፡ ደቀ መዛሙርቱም መልሰው ‹እኛን የሚያጽናናን መጽሐፍ ቅዱስህስ አባታችን? › ሲሉ ደግመው ጠየቁት፡፡ አባ ሰራብዮንም ‹መጽሐፍ ቅዱስ ሁል ጊዜ ‹ሂድ ያለህን ሽጠህ ለድሆች ስጥ› ይለኛል፤ ስለዚህ እርሱንም ሸጥኩት› አላቸው፡፡
ምንጭ :–Paradise of the monks,
ኢትዮጵያዊው ቄርሎስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ እንደሚናገረው ምጽዋት የፊት መብራት ናት፡፡ አንድ ሰው በጨለማ ሲጓዝ ከኋላው መብራት ቢያበሩለትም እንኳ ከፊቱ የሚቀድመው የገዛ የአካሉ ጥላ እንቅፋት እየሆነበት ይጥለዋል፡፡ ወደ ፊት ያለውን መንገድ አጥርቶ እያየ ያለ ስጋት ለመሄድ እንዲችል የግድ የፊት መብራት ያስፈልገዋል፡፡ ጾም ፣ጸሎት እና ሌሎች መንፈሳዊ ትሩፋት እንደ ኋላ መብራት ናቸው፡፡ የፊት መብራት የተሰኘች ምጽዋት ካልታከለችባቸው እነዚህ ብቻቸውን ዋጋን አያሰጡንም፡፡ ከምጽዋት በላይ ታላቅ ነገር እንደሌለ ልንረዳ ይገባል፡፡ ዓለም ሁሉ ከነበረበት የበደል ዕዳ የዳነው ቸር እረኛ በሆነው በመድኃኔ ዓለም በአካሉ ምጽዋትነት (በሥጋው በደሙ መሰጠት) ነውና!!!
@aleroe
+++ ልብስህን ማን ወሰደው? +++
በአንድ ወቅት አባ ሰራብዮን ወደ እስክንድርያ ሄደ፡፡ በገበያም ስፍራ አንድ ከልብስ የተራቆተ ነዳይ አገኘ፡፡ ለራሱም ‹ይህ ደሃ ሰው ታርዞ መነኩሴ የተባልኩ እኔ እንዴት ለብሼ እታያለሁ? በእውነት ይህ ‹ታርዤ አልብሳችሁኛልና› ብሎ የተናገረው ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ አይደለምን? በዚህ ብርድ አየር እየተሰቃየ እኮ ነው!› ብሎ ፈጥኖ የገዛ ልብሱን ከራሱ በማውለቅ ይለብስ ዘንድ ለዚያ ደሃ ሰጠው፡፡ ከዚያም በእጁ ያለውን መጽሐፍ ቅዱስ እንደያዘ እርቃኑን በጎዳናው ላይ ተቀመጠ፡፡ የከተማውም ባለጠጋ ሰው አባ ሰራብዮን ባለበት ሥፍራ ሲያልፍ ተመልክቶት ወደ እርሱ ቀረበና ‹አባ ሰራብዮን ሆይ ልብስህን ማን ወሰደው?› ሲል ጠየቀው፡፡ ቅዱስም በእጁ ወደ ያዘው መጽሐፍ ቅዱስ እየጠቆመ ‹ልብሴን የወሰደው ይህ ነው!› አለው፡፡ ያም ባለጠጋ ልብስን ገዝቶ ካለበሰው በኋላ አባ ሰራብዮን ከእርሱ እንደ ተለየ በመንገድ ዕዳውን መክፈል ስላልቻለ እየተንገላታ ወደ ወኅኒ ቤት የሚሄድን አንድ ሰው ተመለከተ፡፡ ቅዱሱም አባት የያዘውን መጽሐፍ ቅዱሱን ሽጦ የዚያን ሰው ዕዳ በመክፈል ነጻ አደረገው፡፡ ይህንም ፈጽሞ ጉዞውን ሲጀምር ሌላ አንድ ነዳይ ሲለምን ተመልክቶ ዳግመኛ የለበሰውን ልብስ አውልቆ ሰጥቶ እርቃኑን ወደ በአቱ ተመለሰ፡፡ ደቀ መዛሙርቱም እርቃኑን ባዩት ጊዜ ‹መምህር! ልብስህ ወዴት አለ?› ብለው ጠየቁት፡፡ እርሱም ‹መጸወትኩት› አላቸው፡፡ ደቀ መዛሙርቱም መልሰው ‹እኛን የሚያጽናናን መጽሐፍ ቅዱስህስ አባታችን? › ሲሉ ደግመው ጠየቁት፡፡ አባ ሰራብዮንም ‹መጽሐፍ ቅዱስ ሁል ጊዜ ‹ሂድ ያለህን ሽጠህ ለድሆች ስጥ› ይለኛል፤ ስለዚህ እርሱንም ሸጥኩት› አላቸው፡፡
ምንጭ :–Paradise of the monks,
ኢትዮጵያዊው ቄርሎስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ እንደሚናገረው ምጽዋት የፊት መብራት ናት፡፡ አንድ ሰው በጨለማ ሲጓዝ ከኋላው መብራት ቢያበሩለትም እንኳ ከፊቱ የሚቀድመው የገዛ የአካሉ ጥላ እንቅፋት እየሆነበት ይጥለዋል፡፡ ወደ ፊት ያለውን መንገድ አጥርቶ እያየ ያለ ስጋት ለመሄድ እንዲችል የግድ የፊት መብራት ያስፈልገዋል፡፡ ጾም ፣ጸሎት እና ሌሎች መንፈሳዊ ትሩፋት እንደ ኋላ መብራት ናቸው፡፡ የፊት መብራት የተሰኘች ምጽዋት ካልታከለችባቸው እነዚህ ብቻቸውን ዋጋን አያሰጡንም፡፡ ከምጽዋት በላይ ታላቅ ነገር እንደሌለ ልንረዳ ይገባል፡፡ ዓለም ሁሉ ከነበረበት የበደል ዕዳ የዳነው ቸር እረኛ በሆነው በመድኃኔ ዓለም በአካሉ ምጽዋትነት (በሥጋው በደሙ መሰጠት) ነውና!!!
@aleroe
ኤልሮኢ:(⚜ምክረ አበው⚜)
#ወዳጄ ሆይ!
የሚታገል ሰው ቢወድቅ አዲስ ነገር አይደለም፤ ወድቆ መቅረቱ ነው እንጂ፡፡ አንድ ቦክስ የሚጋጠም ሰውም ቢቆስል የሚያሳዝን ነገር አይደለም፤ የሚያሳዝነው ቁስሉን ችላ ያለው እንደ ኾነ ነው እንጂ፡፡ አንተም በመንፈሳዊ ሕይወትህ ብትወድቅ አይደንቅም፤ ለቅጽበትም የማይተኛልህ ጠላት አለህና፡፡ ነገር ግን ወድቀህ አትቅር፡፡
አንድ ወታደር ጦር ሜዳ ሔዶ ቢቆስል ማንም ጤነኛ አእምሮ ያለው ሰው አይወቅሰውም፡፡ አንተም ጠላትህ ዲያብሎስ ቢያቆስልህ ማንም አይወቅስህም፡፡ መንፈሳዊ ተጋድሎ ውስጥ ነውና ያለኸው፡፡ የምትወቀሰው ለቁስልህ መድኃኒት ማድረግህን ችላ ያልህ እንደ ኾነ ብቻ ነው፡፡ ይህ ከላይ የነገርኩህ ወታደር ከታከመ፥ ተመልሶ ወደ ጦር ሜዳ ይሔዳል፡፡ ጠላቱን ድል ሲያደርግም ሹመት ሽልማት ይሰጡታል፡፡ አንተም ከወደቅህበት ተነሥና ንስሐ የተባለ ሕክምናን ውሰድ፡፡ ከዚያም ጠላትህ ዲያብሎስን ድል አድርገህ ከክርስቶስ ዘንድ ሹመት ሽልማትን ተቀበል፡፡ ስለዚህ በርታ፡፡ በርታና ተነሥ ዘግይቻለሁ ብለህ በፍጹም ተስፋ አትቁረጥ፤ አሁንም መጀመር ትችላለህና፡፡
✍ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
@aleroe
#ወዳጄ ሆይ!
የሚታገል ሰው ቢወድቅ አዲስ ነገር አይደለም፤ ወድቆ መቅረቱ ነው እንጂ፡፡ አንድ ቦክስ የሚጋጠም ሰውም ቢቆስል የሚያሳዝን ነገር አይደለም፤ የሚያሳዝነው ቁስሉን ችላ ያለው እንደ ኾነ ነው እንጂ፡፡ አንተም በመንፈሳዊ ሕይወትህ ብትወድቅ አይደንቅም፤ ለቅጽበትም የማይተኛልህ ጠላት አለህና፡፡ ነገር ግን ወድቀህ አትቅር፡፡
አንድ ወታደር ጦር ሜዳ ሔዶ ቢቆስል ማንም ጤነኛ አእምሮ ያለው ሰው አይወቅሰውም፡፡ አንተም ጠላትህ ዲያብሎስ ቢያቆስልህ ማንም አይወቅስህም፡፡ መንፈሳዊ ተጋድሎ ውስጥ ነውና ያለኸው፡፡ የምትወቀሰው ለቁስልህ መድኃኒት ማድረግህን ችላ ያልህ እንደ ኾነ ብቻ ነው፡፡ ይህ ከላይ የነገርኩህ ወታደር ከታከመ፥ ተመልሶ ወደ ጦር ሜዳ ይሔዳል፡፡ ጠላቱን ድል ሲያደርግም ሹመት ሽልማት ይሰጡታል፡፡ አንተም ከወደቅህበት ተነሥና ንስሐ የተባለ ሕክምናን ውሰድ፡፡ ከዚያም ጠላትህ ዲያብሎስን ድል አድርገህ ከክርስቶስ ዘንድ ሹመት ሽልማትን ተቀበል፡፡ ስለዚህ በርታ፡፡ በርታና ተነሥ ዘግይቻለሁ ብለህ በፍጹም ተስፋ አትቁረጥ፤ አሁንም መጀመር ትችላለህና፡፡
✍ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
@aleroe
ኤልሮኢ:(⚜ዝማሬ⚜)
እንዴት ብትወደኝ ነው
እንዴት ብትወደኝ ነው የማትተወኝ (2)
ትዕግስትህን ሳስብ እጅግ ደነቀኝ(2)
እኔን ያዘልክበት ትክሻህ ሰፊ ነው
አእምሮዬም ልቤም አይችልም ሊለካው
ሞት የሚገባውን የስራዬን ብዛት
አይተህ እንዳላየ ተውከው በቸርነት(2)
ድንቅ ስጦታ ነው መልሰህ የሰጠኸኝ
ለኔ የወሰድኩት የማይገባኝ
ፍቅርህ ከሰንሰለት እጅግ ይበረታል
ዓመፀኛው ታዞ ያገለግልሀል(2)
ለበደለ በደል ላጠፋ ጥፋት
ይህን ነበር የማውቀው በዓለም ስርዓት
ያንተ ግን ይደንቃል ገዛኸኝ በምህረት
ፊቴ ትቆማለህ ሁሌ በቸርነት
ያፈቀረን አምላክ ጨክኖ ቢበድል
በፀፀት ይቀጣል በሂሊና ቁስል
ዓላማህ በኔ ላይ ፍቅር ስለሆነ
ህግህ ሊፈርድብኝ አንዴም አልጨከነ
#ሊቀ ዲያቆን ወንደሰን በቀለ
@aleroe
እንዴት ብትወደኝ ነው
እንዴት ብትወደኝ ነው የማትተወኝ (2)
ትዕግስትህን ሳስብ እጅግ ደነቀኝ(2)
እኔን ያዘልክበት ትክሻህ ሰፊ ነው
አእምሮዬም ልቤም አይችልም ሊለካው
ሞት የሚገባውን የስራዬን ብዛት
አይተህ እንዳላየ ተውከው በቸርነት(2)
ድንቅ ስጦታ ነው መልሰህ የሰጠኸኝ
ለኔ የወሰድኩት የማይገባኝ
ፍቅርህ ከሰንሰለት እጅግ ይበረታል
ዓመፀኛው ታዞ ያገለግልሀል(2)
ለበደለ በደል ላጠፋ ጥፋት
ይህን ነበር የማውቀው በዓለም ስርዓት
ያንተ ግን ይደንቃል ገዛኸኝ በምህረት
ፊቴ ትቆማለህ ሁሌ በቸርነት
ያፈቀረን አምላክ ጨክኖ ቢበድል
በፀፀት ይቀጣል በሂሊና ቁስል
ዓላማህ በኔ ላይ ፍቅር ስለሆነ
ህግህ ሊፈርድብኝ አንዴም አልጨከነ
#ሊቀ ዲያቆን ወንደሰን በቀለ
@aleroe
ኤልሮኢ :(⚜ብሒለ አበው⚜)
አንድ ሰው አንድ አባት ጋር ቀርቦ አንዳንዶች መላእክት ተገለጡልን ይላሉ ብሎ ጠየቃቸው።
እሳቸውም ከዚህ የበለጠ ደስ የሚያሰኘውስ ሁልጊዜ በኃጢአታቸውን ቢያዩ ቢያስቡ ነበር ሲሉ መለሱለት።
አንድ አባት እንዲህ አሉ ስሕተተኛ በሆናቹ ጊዜ ሁሉ ሌላውን አትወንጅሉ። ይህ የሆነው በራሴ ኃጢአትና ድክመት ምክንያት ነው በሉ። ቅዱሳን አባቶቻችን እንዲህ በማለት ተናግረዋል በርግጥ መላእክት ሊታዩክ ቢችሉ እንኳን አትቀበል ራስህን አዋርድ። እኔ ሃጢአተኛ ነኝና መላእክትን ባይ ምን ይጠቅመኛል በል።
@aleroe
አንድ ሰው አንድ አባት ጋር ቀርቦ አንዳንዶች መላእክት ተገለጡልን ይላሉ ብሎ ጠየቃቸው።
እሳቸውም ከዚህ የበለጠ ደስ የሚያሰኘውስ ሁልጊዜ በኃጢአታቸውን ቢያዩ ቢያስቡ ነበር ሲሉ መለሱለት።
አንድ አባት እንዲህ አሉ ስሕተተኛ በሆናቹ ጊዜ ሁሉ ሌላውን አትወንጅሉ። ይህ የሆነው በራሴ ኃጢአትና ድክመት ምክንያት ነው በሉ። ቅዱሳን አባቶቻችን እንዲህ በማለት ተናግረዋል በርግጥ መላእክት ሊታዩክ ቢችሉ እንኳን አትቀበል ራስህን አዋርድ። እኔ ሃጢአተኛ ነኝና መላእክትን ባይ ምን ይጠቅመኛል በል።
@aleroe
ኤልሮኢ:(⚜ምክረ አበው⚜)
++ አባቶቻችን እንዲህ አሉ ++
"መካሪ አያስፈልገኝም የማለትን ያህል ታላቅ ትዕቢት የለም"
ቅዱስ ባስልዮስ
"በኃጢአት በወደቅህ ጊዜ ተስፋ ቆርጠህ ጸሎትህን እንዳታቆም። ንስሓ እስከምገባ ድረስ ብለህ ጸሎት ካቆምክ መቼም ንስሓ አትገባም። ምክንያቱም ጸሎት ራሱ የእውነተኛ ንስሓ መግቢያ በር ነው" ቅዱስ ቄርሎስ ሳድሳዊ
"ሰዎች አንድ ሰው ተነሥቶ ሌላውን ሲገድል ወንጀለኛ ነህ ይሉታል። አንድ ላይ ተሰባስበው ብዙ ሰዎችን ሲገድሉ ግን ውጊያ ይሉትና መግደላቸውን ጀግንነት ይሉታል" ቅዱስ ቆጵሮሳዊ
"የክርስቲያኖች መሣሪያ በእጃቸው ሰይፍን መታጠቅ ሳይሆን እጃቸውን ወደላይ ለጸሎት መዘርጋት ነው"
ቅዱስ አትናቴዎስ ዘእስክንድርያ
"እግዚአብሔር ለአብርሃም "ከሀገርህ ውጣ ከወገኖችህ"ተለይ ብሎት ነበር። በዚህ ጥሪ እግዚአብሔር ሁላችንንም የተወለድንበት ዘር እንድንተው ይጠራናል። ሰማዕቱ ዮስጦስ (100 AD-165 AD)
"ክርስቶስ ጴጥሮስን "ሰይፍህን ወደ ሰገባው አስገባ" ሲለው ትጥቅ ያስፈታው ጴጥሮስን ብቻ ሳይሆን እንደ ጴጥሮስ በእርሱ የሚያምኑትን ሁሉ ነበር" ሊቁ ጠርጡለስ (160 AD - 220 AD)
‹‹ይጸልያል ነገር ግን የሌሎችን ጸሎትም ይሰማል፡፡ ያለቅሳል የሌሎችን ዕንባ ግን ያብሳል፡፡ ሰው ነውና አልዓዛር ወዴት እንደተቀበረ ጠየቀ፡፡ አምላክ ነውና አልዓዛርን ከሞት አስነሣ፡፡ እርሱ በርካሽ ዋጋ ያውም በሠላሳ ብር ብቻ ተሸጠ፡፡ ነገር ግን ዓለምን በውድ ዋጋ በከበረ ደሙ ገዛ፡፡ እንደ በግ ለመታረድ ተነዳ እርሱ ግን የእስራኤል እረኛ የዓለምም ሁሉ ጠባቂ ነበረ፡፡ እንደ በግ ዝም አለ ነገር ግን እርሱ በምድረ በዳ በሚጮኽ ሰው ድምፅ የተሰበከ ቃል ነበር፡፡ እርሱ የተሰቃየና የቆሰለ ነበር ፤ ሁሉንም በሽታና ቁስል ግን ይፈውስ ነበር›› ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ
"ለቤተ መቅደስህ ተክል ያደረግኸኝ፡፡ አቤቱ ሆይ የውጭ ተክል አታድርገኝ፡፡ የጽድቅ ተክል አድርገኝ፡፡ የኃጢአት አይደለም፡፡ የዕውነት ተክል አድርገኝ የሐሰት አይደለም የፍቅር ተክል አድርገኝ የጽል አይደለም፡፡
የመጻሕፍት መጀመሪያ የምትሆን ኦሪት ደመና የምትጋርደኝ፡፡ ከቅዱስ ወንጌል ፈሳሽ የምጠጣ ከጎንህ ከፈሰሰው ደም የምረካ ልሁን፡፡ በናትህ በድንግል ጸሎት የሃይማኖት አበባ ላብብ፡፡ የጽድቅ ፍሬን ላፍራ ከቅዱሳንህ ሐዋርያትም ከቃላቸው ፍሬ የተነሣ እስከ ዘለዓለሙ ድረስ የተባረከ የወይን ቦታ ልባል የጽድቅን ፍሬ የሚያስቀረውንም የኃጢአት እሾህ ጠምዝዘው ከደጁም አሜከላውን አረሙንም ሙጃውንም ንቀለው፡፡ አቤቱ ከኔም አርቀው ሥርዓትህን የሚሠሩትን ያበባቸውን ፍጻሜ እንዳፈራ አድርገኝ" ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ግንቦት 26 2011
ጅማ ፣ ኢትዮጵያ
@aleroe
++ አባቶቻችን እንዲህ አሉ ++
"መካሪ አያስፈልገኝም የማለትን ያህል ታላቅ ትዕቢት የለም"
ቅዱስ ባስልዮስ
"በኃጢአት በወደቅህ ጊዜ ተስፋ ቆርጠህ ጸሎትህን እንዳታቆም። ንስሓ እስከምገባ ድረስ ብለህ ጸሎት ካቆምክ መቼም ንስሓ አትገባም። ምክንያቱም ጸሎት ራሱ የእውነተኛ ንስሓ መግቢያ በር ነው" ቅዱስ ቄርሎስ ሳድሳዊ
"ሰዎች አንድ ሰው ተነሥቶ ሌላውን ሲገድል ወንጀለኛ ነህ ይሉታል። አንድ ላይ ተሰባስበው ብዙ ሰዎችን ሲገድሉ ግን ውጊያ ይሉትና መግደላቸውን ጀግንነት ይሉታል" ቅዱስ ቆጵሮሳዊ
"የክርስቲያኖች መሣሪያ በእጃቸው ሰይፍን መታጠቅ ሳይሆን እጃቸውን ወደላይ ለጸሎት መዘርጋት ነው"
ቅዱስ አትናቴዎስ ዘእስክንድርያ
"እግዚአብሔር ለአብርሃም "ከሀገርህ ውጣ ከወገኖችህ"ተለይ ብሎት ነበር። በዚህ ጥሪ እግዚአብሔር ሁላችንንም የተወለድንበት ዘር እንድንተው ይጠራናል። ሰማዕቱ ዮስጦስ (100 AD-165 AD)
"ክርስቶስ ጴጥሮስን "ሰይፍህን ወደ ሰገባው አስገባ" ሲለው ትጥቅ ያስፈታው ጴጥሮስን ብቻ ሳይሆን እንደ ጴጥሮስ በእርሱ የሚያምኑትን ሁሉ ነበር" ሊቁ ጠርጡለስ (160 AD - 220 AD)
‹‹ይጸልያል ነገር ግን የሌሎችን ጸሎትም ይሰማል፡፡ ያለቅሳል የሌሎችን ዕንባ ግን ያብሳል፡፡ ሰው ነውና አልዓዛር ወዴት እንደተቀበረ ጠየቀ፡፡ አምላክ ነውና አልዓዛርን ከሞት አስነሣ፡፡ እርሱ በርካሽ ዋጋ ያውም በሠላሳ ብር ብቻ ተሸጠ፡፡ ነገር ግን ዓለምን በውድ ዋጋ በከበረ ደሙ ገዛ፡፡ እንደ በግ ለመታረድ ተነዳ እርሱ ግን የእስራኤል እረኛ የዓለምም ሁሉ ጠባቂ ነበረ፡፡ እንደ በግ ዝም አለ ነገር ግን እርሱ በምድረ በዳ በሚጮኽ ሰው ድምፅ የተሰበከ ቃል ነበር፡፡ እርሱ የተሰቃየና የቆሰለ ነበር ፤ ሁሉንም በሽታና ቁስል ግን ይፈውስ ነበር›› ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ
"ለቤተ መቅደስህ ተክል ያደረግኸኝ፡፡ አቤቱ ሆይ የውጭ ተክል አታድርገኝ፡፡ የጽድቅ ተክል አድርገኝ፡፡ የኃጢአት አይደለም፡፡ የዕውነት ተክል አድርገኝ የሐሰት አይደለም የፍቅር ተክል አድርገኝ የጽል አይደለም፡፡
የመጻሕፍት መጀመሪያ የምትሆን ኦሪት ደመና የምትጋርደኝ፡፡ ከቅዱስ ወንጌል ፈሳሽ የምጠጣ ከጎንህ ከፈሰሰው ደም የምረካ ልሁን፡፡ በናትህ በድንግል ጸሎት የሃይማኖት አበባ ላብብ፡፡ የጽድቅ ፍሬን ላፍራ ከቅዱሳንህ ሐዋርያትም ከቃላቸው ፍሬ የተነሣ እስከ ዘለዓለሙ ድረስ የተባረከ የወይን ቦታ ልባል የጽድቅን ፍሬ የሚያስቀረውንም የኃጢአት እሾህ ጠምዝዘው ከደጁም አሜከላውን አረሙንም ሙጃውንም ንቀለው፡፡ አቤቱ ከኔም አርቀው ሥርዓትህን የሚሠሩትን ያበባቸውን ፍጻሜ እንዳፈራ አድርገኝ" ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ግንቦት 26 2011
ጅማ ፣ ኢትዮጵያ
@aleroe
ኤልሮኢ:(⚜የዕለቱ ምስባክና ወንጌል⚜)
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
መስከረም 01/01/2013 ዓ.ም
ምስባክ ዘነግህ
መዝ ፷፬፥፲፩(64፥11)
ወትባርክ አክሊለ ዓመተ ምሕረትከ
ወይጸግቡ ጠላተ ገዳም
ወይረውዩ አድባረ በድው
ምስባክ ዘቅዳሴ
አድኅነኒ እምእለ ሮዱኒ እስመ ይኄይሉኒ
ወአውጽኣ እምቅሕ ለነፍስየ
ከመ እግነይ ለስምከ እግዚኦ
ቅዳሴ
👉ዘሐዋርያት (ዘበደኃሪ)
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
@aleroe
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
መስከረም 01/01/2013 ዓ.ም
ምስባክ ዘነግህ
መዝ ፷፬፥፲፩(64፥11)
ወትባርክ አክሊለ ዓመተ ምሕረትከ
ወይጸግቡ ጠላተ ገዳም
ወይረውዩ አድባረ በድው
ምስባክ ዘቅዳሴ
አድኅነኒ እምእለ ሮዱኒ እስመ ይኄይሉኒ
ወአውጽኣ እምቅሕ ለነፍስየ
ከመ እግነይ ለስምከ እግዚኦ
ቅዳሴ
👉ዘሐዋርያት (ዘበደኃሪ)
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
@aleroe
ኤልሮኢ:(⚜ትምህርት⚜)
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
# ዘመን መለወጫ ምንድነው.?
# እንቁጣጣሽ ምንድነው..?
# አዲሱ ዓመት ለምን ቅዱስ ዮሐንስ ይባላል...?
ኢትዮጵያ የወራት ሁሉ መጀመሪያ መስከረም ነው፡፡ ይህ ወር ዘመን መለወጫ፣ ዕንቁጣጣሽ፣ ቅዱስ ዮሐንስ እየተባለ ይጠራል፡፡ ስለ አዲስ ዓመት በተለያየ ስም የመጠራቱ ታሪካዊ አመጣጥና ስያሜ መነሻ አሳቡ ምን እንደሆነ እንደሚከተለው እንመለከታለን፡፡
# ዘመን__መለወጫ
ዘመን መለወጫ መስከረም ወር የሆነበት ምክንያት “ብርሃናት /ፀሐይ፣ ጨረቃ፣ ከዋክብት/ የዓመት ዑደታቸውን በጳጉሜ ወር ጨርሰው በመስከረም ወር ስለሚጀምሩ ነው፡፡ ሌሊቱ ከቀኑ ጋር ይተካከላል፡፡ ዓመቱን ጠንቅቀው ቢቆጥሩ 366 ቀናት ይሆናል፡፡ “ሌሊቱም ከቀኑ ጋራ ይተካከላል፡፡ ዓመቱም ጠንቅቆ ቢቆጥሩት ሦስት መቶ ስልሳ አራት ቀን ይሆናል፡፡ /ሄኖክ.26፥44/ “ዘመናችንን እንደ ቀድሞ አድሱ” /ሰ.ኤር.5፥21/ከቆየ እንዲል፡፡ በዘመነ ኖኅ ዓለምን ንፍር ውኃ አጥለቅልቆት በኋላ ዳግመኛ ውኃው የጎደለበት በመሆኑ /ኩፋሌ 7፥1/ “በመጀመሪያው ወር መባቻም ምድር ታየች” እንዲል፡፡
# ዕንቁጣጣሽ
ዕንቁጣጣሽ የተባለበት ምክንያት አንደኛ “ዕንቁ - ዕፅ አመጣሽ” ብሎ የአበባውን አህጉራትን መፈንዳት ያመለክታል፡፡ ሁለተኛ ኖኅ ለሦስቱ ልጆቹ በእጣ ሲያካፍላቸው አፍሪካ ለካም ደረሰችው፡፡ በአፍሪካ ምድርም ሲገባ በመጀመሪያ
ያረፈው በኢትዮጵያ ነበር፡፡ ሀገሪቱም በአደይ አበባ አሸብርቃ ነበር፡፡ ወሩ ወርኀ
መስከረም በመሆኑ ደስ ብሎት ዕንቁ ዕጣ ወጣሽልኝ ይህችን ወቅት እንቁጣጣሽ ብሏታል፡፡ ሦስተኛው /1ነገ.10፥1-10/ ኢትዮጵያዊቷ ንግሥት ሣባ /መንሻ አዜብ የንጉሡን ጥበብ ከመስማት ማየትን መርጣ ወደ ንጉሥ ሰሎሞን ከብዙ ሠራዊቶቿ ጋር የእጅ በመያዝ ሄደች፡፡ ንጉሡም በደስታ ተቀብሎ እርሱም “እንቁ ለጣትሽ ወርኀ ጌጥ ይሁንሽ” በማለት አራት አይነት ቀለም የሚታይበት በቀንና በሌሊት የምታበራ ቀለበት ሰጥቷታል፡፡ ወሩም መስከረም ነበር፡፡ ከዚህ በመነሣት እንቁጣጣሽ የሚለው ስያሜ ወጥቷል፡፡
# ቅዱስ_ዮሐንስ
ሦስተኛው የአዲስ ዘመን ስያሜ ቅዱስ ዮሐንስ ነው፡፡ የመጥምቁ ዮሐንስ
ተግባር ለዘመነ ወንጌል በር ወይም መነሻ እንዲሆን ለኢትዮጵያ ዐውደ ዓመት
መስከረም አንድ ቀን እንዲከበር አባቶች ወስነዋል፡፡ /ድርሳነ ዮሐንስ አፈወርቅ
ገጽ 1-3/ መጽሐፈ ስንክሳር “የመስከረም ወር የተባረከ ነው፡፡ እርሱም የግብጽና የኢትዮጵያ ዓመቶች መጀመሪያ ነው፡፡ የዚህ ወር ቀኑና ሌሊቱ እኩል 12 ሰዓት ነው፡፡ ከዚህ በኋላ ቀኑ እየጎደለ ይሄዳል” እንዲል፡፡
በአጠቃላይ ዘመን መለወጫ ከላይ ባየናቸው የተለያየ ስያሜ ይጠራ እንጂ ዘመኑ አዲስ እየተባለ ቢጠራም አዲስ መሆን ያለበት ወርና ወቅቱ ብቻ ሳይሆን የእኛ የክርስቲያኖች ሥርዓት ነው፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
ሰውነታችሁን አታርክሱ የእግዚአብሔር ማደሪያ ነውና እያለ በመዋዕለ ሥጋዌው ያስተምር ነበር፡፡ አዲስ ዓመት ሲመጣ በኀጥያት፣ በተንኮል፣ በክፋት የቆሸሸው ሰውነታችን በንስሓ፣ በቅዱስ ቊርባን፣ በመልካም ተግባር አዲስ ልናደርገው ይገባናል፡፡
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
መልካም አዲስ አመት ይሁንልን
አሜን!!!
@aleroe
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
# ዘመን መለወጫ ምንድነው.?
# እንቁጣጣሽ ምንድነው..?
# አዲሱ ዓመት ለምን ቅዱስ ዮሐንስ ይባላል...?
ኢትዮጵያ የወራት ሁሉ መጀመሪያ መስከረም ነው፡፡ ይህ ወር ዘመን መለወጫ፣ ዕንቁጣጣሽ፣ ቅዱስ ዮሐንስ እየተባለ ይጠራል፡፡ ስለ አዲስ ዓመት በተለያየ ስም የመጠራቱ ታሪካዊ አመጣጥና ስያሜ መነሻ አሳቡ ምን እንደሆነ እንደሚከተለው እንመለከታለን፡፡
# ዘመን__መለወጫ
ዘመን መለወጫ መስከረም ወር የሆነበት ምክንያት “ብርሃናት /ፀሐይ፣ ጨረቃ፣ ከዋክብት/ የዓመት ዑደታቸውን በጳጉሜ ወር ጨርሰው በመስከረም ወር ስለሚጀምሩ ነው፡፡ ሌሊቱ ከቀኑ ጋር ይተካከላል፡፡ ዓመቱን ጠንቅቀው ቢቆጥሩ 366 ቀናት ይሆናል፡፡ “ሌሊቱም ከቀኑ ጋራ ይተካከላል፡፡ ዓመቱም ጠንቅቆ ቢቆጥሩት ሦስት መቶ ስልሳ አራት ቀን ይሆናል፡፡ /ሄኖክ.26፥44/ “ዘመናችንን እንደ ቀድሞ አድሱ” /ሰ.ኤር.5፥21/ከቆየ እንዲል፡፡ በዘመነ ኖኅ ዓለምን ንፍር ውኃ አጥለቅልቆት በኋላ ዳግመኛ ውኃው የጎደለበት በመሆኑ /ኩፋሌ 7፥1/ “በመጀመሪያው ወር መባቻም ምድር ታየች” እንዲል፡፡
# ዕንቁጣጣሽ
ዕንቁጣጣሽ የተባለበት ምክንያት አንደኛ “ዕንቁ - ዕፅ አመጣሽ” ብሎ የአበባውን አህጉራትን መፈንዳት ያመለክታል፡፡ ሁለተኛ ኖኅ ለሦስቱ ልጆቹ በእጣ ሲያካፍላቸው አፍሪካ ለካም ደረሰችው፡፡ በአፍሪካ ምድርም ሲገባ በመጀመሪያ
ያረፈው በኢትዮጵያ ነበር፡፡ ሀገሪቱም በአደይ አበባ አሸብርቃ ነበር፡፡ ወሩ ወርኀ
መስከረም በመሆኑ ደስ ብሎት ዕንቁ ዕጣ ወጣሽልኝ ይህችን ወቅት እንቁጣጣሽ ብሏታል፡፡ ሦስተኛው /1ነገ.10፥1-10/ ኢትዮጵያዊቷ ንግሥት ሣባ /መንሻ አዜብ የንጉሡን ጥበብ ከመስማት ማየትን መርጣ ወደ ንጉሥ ሰሎሞን ከብዙ ሠራዊቶቿ ጋር የእጅ በመያዝ ሄደች፡፡ ንጉሡም በደስታ ተቀብሎ እርሱም “እንቁ ለጣትሽ ወርኀ ጌጥ ይሁንሽ” በማለት አራት አይነት ቀለም የሚታይበት በቀንና በሌሊት የምታበራ ቀለበት ሰጥቷታል፡፡ ወሩም መስከረም ነበር፡፡ ከዚህ በመነሣት እንቁጣጣሽ የሚለው ስያሜ ወጥቷል፡፡
# ቅዱስ_ዮሐንስ
ሦስተኛው የአዲስ ዘመን ስያሜ ቅዱስ ዮሐንስ ነው፡፡ የመጥምቁ ዮሐንስ
ተግባር ለዘመነ ወንጌል በር ወይም መነሻ እንዲሆን ለኢትዮጵያ ዐውደ ዓመት
መስከረም አንድ ቀን እንዲከበር አባቶች ወስነዋል፡፡ /ድርሳነ ዮሐንስ አፈወርቅ
ገጽ 1-3/ መጽሐፈ ስንክሳር “የመስከረም ወር የተባረከ ነው፡፡ እርሱም የግብጽና የኢትዮጵያ ዓመቶች መጀመሪያ ነው፡፡ የዚህ ወር ቀኑና ሌሊቱ እኩል 12 ሰዓት ነው፡፡ ከዚህ በኋላ ቀኑ እየጎደለ ይሄዳል” እንዲል፡፡
በአጠቃላይ ዘመን መለወጫ ከላይ ባየናቸው የተለያየ ስያሜ ይጠራ እንጂ ዘመኑ አዲስ እየተባለ ቢጠራም አዲስ መሆን ያለበት ወርና ወቅቱ ብቻ ሳይሆን የእኛ የክርስቲያኖች ሥርዓት ነው፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
ሰውነታችሁን አታርክሱ የእግዚአብሔር ማደሪያ ነውና እያለ በመዋዕለ ሥጋዌው ያስተምር ነበር፡፡ አዲስ ዓመት ሲመጣ በኀጥያት፣ በተንኮል፣ በክፋት የቆሸሸው ሰውነታችን በንስሓ፣ በቅዱስ ቊርባን፣ በመልካም ተግባር አዲስ ልናደርገው ይገባናል፡፡
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
መልካም አዲስ አመት ይሁንልን
አሜን!!!
@aleroe
ኤልሮኢ:(⚜ዝማሬ⚜)
🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻
የእለት የዓመት
ከዚህ ዕለት ከዚህ ዓመት ላደረሰን ሁላችንን /2/
የሰው ልጆች እድሜ ጥንቱንም ሲጀመር
ምን ቢወጣ ቢወርድ ቢበዛ ቢደመር
አንድ ቀን አይሞላም እንደአንተ አቆጣጠር /2/
አዝ . . .
ስለዚህ አምላክ ሆይ ክቡር ነው ቅዱስ ነው
ወደአንተ እንዲመለስ ቀን የሰጠኸው ሰው
ደካማ ነውና ሰው እድሜ ከራበው /2/
አዝ . . .
እጅግ አደንቃለሁ የአምላክን ጥበብ
ምድርን በአበባ ሰማይን በኮከብ
እንዳሸበረቃት አስተውዬ ሳስብ /2/
አዝ . . .
ከንቱ ካሳለፍኩት ጊዜዬን በዋዛ
ምን ያደርግልኛል ዘመኔ ቢበዛ
ደግሞም በጠቅላላ ዓለምን ብገዛ /2/
አዝ . . .
በከንቱ ጊዜያችን ፈጽሞ እንዳይጠፋ
በርትተን ከሠራን ያለአንዳች ነቀፋ
አምላክ የሚሰጠን አለን ፍጹም ተስፋ /2/
🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻
@aleroe
🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻
የእለት የዓመት
ከዚህ ዕለት ከዚህ ዓመት ላደረሰን ሁላችንን /2/
የሰው ልጆች እድሜ ጥንቱንም ሲጀመር
ምን ቢወጣ ቢወርድ ቢበዛ ቢደመር
አንድ ቀን አይሞላም እንደአንተ አቆጣጠር /2/
አዝ . . .
ስለዚህ አምላክ ሆይ ክቡር ነው ቅዱስ ነው
ወደአንተ እንዲመለስ ቀን የሰጠኸው ሰው
ደካማ ነውና ሰው እድሜ ከራበው /2/
አዝ . . .
እጅግ አደንቃለሁ የአምላክን ጥበብ
ምድርን በአበባ ሰማይን በኮከብ
እንዳሸበረቃት አስተውዬ ሳስብ /2/
አዝ . . .
ከንቱ ካሳለፍኩት ጊዜዬን በዋዛ
ምን ያደርግልኛል ዘመኔ ቢበዛ
ደግሞም በጠቅላላ ዓለምን ብገዛ /2/
አዝ . . .
በከንቱ ጊዜያችን ፈጽሞ እንዳይጠፋ
በርትተን ከሠራን ያለአንዳች ነቀፋ
አምላክ የሚሰጠን አለን ፍጹም ተስፋ /2/
🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻
@aleroe
ኤልሮኢ:(⚜ስነፅሁፍ⚜)
"ዘመኔን ባርኪልኝ!!"
🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻
እልፍ አመት ባወራ..... ቅኔ ብዘርፍልሽ
ምንም ቃል አጣሁኝ!..... በምን ልቀኝልሽ?
የሚስጥሬ ሙዳይ..... የሃሳቤ ብራና!
የደስታዬ ባህር.... የኑሮዬ ቃና!
ማርያም እመቤቴ.... የጌታዬ እናት
የአዲስ ተስፋ ብርሃን.... የሰማይ ጉልላት!
የአምላኬ ስጦታ.... ረቂቋ ማህደር
ፍቅርሽ ከልቤ ላይ....እንደዋለ ይደር!
ቢከፋኝ መፅናኛ..... ብጨነቅ ምሽጌ
በፍስሐው ዘመን..... መዋቢያ ማዕረጌ!
ፈጣሪ አክብሮሻል....መች አፍርብሻለው!
የክብሬ ሰንደቅ ነሽ!......"እኮራብሻለው!!"
እንዳለፈው ታሪክ......መንገዴን አፍኪልኝ!
ዛሬም በእቅፍሽ ነኝ!....."ዘመኔን ባርኪልኝ!"
🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻
@aleroe
"ዘመኔን ባርኪልኝ!!"
🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻
እልፍ አመት ባወራ..... ቅኔ ብዘርፍልሽ
ምንም ቃል አጣሁኝ!..... በምን ልቀኝልሽ?
የሚስጥሬ ሙዳይ..... የሃሳቤ ብራና!
የደስታዬ ባህር.... የኑሮዬ ቃና!
ማርያም እመቤቴ.... የጌታዬ እናት
የአዲስ ተስፋ ብርሃን.... የሰማይ ጉልላት!
የአምላኬ ስጦታ.... ረቂቋ ማህደር
ፍቅርሽ ከልቤ ላይ....እንደዋለ ይደር!
ቢከፋኝ መፅናኛ..... ብጨነቅ ምሽጌ
በፍስሐው ዘመን..... መዋቢያ ማዕረጌ!
ፈጣሪ አክብሮሻል....መች አፍርብሻለው!
የክብሬ ሰንደቅ ነሽ!......"እኮራብሻለው!!"
እንዳለፈው ታሪክ......መንገዴን አፍኪልኝ!
ዛሬም በእቅፍሽ ነኝ!....."ዘመኔን ባርኪልኝ!"
🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻
@aleroe
ኤልሮኢ:(⚜የዕለቱ ምስባክና ወንጌል⚜)
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
መስከረም 02/01/2013 ዓ.ም
ምስባክ ዘነግህ
መዝ ፻፴፰፥፱(138፥9)
ወእመኒ ነሣእኩ ክንፈ ከመ ንስር
ወሠረርኩ እስከ ማኅለቅተ ባሕር
ህየኒ እዴከ ትመርሀኒ ወታነብረኒ የማንከ
ምስባክ ዘቅዳሴ
ወይርአዩ አህዛብ በቅድመ አዕይንቲነ
በቀለ ደሞሙ ለአግበርቲከ ዘተክዕወ
ይባዕ ቅድሜከ ገዐሮሙ ለሙቁሓን
ቅዳሴ
👉ዘዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ (ኀቤከ)
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
@aleroe
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
መስከረም 02/01/2013 ዓ.ም
ምስባክ ዘነግህ
መዝ ፻፴፰፥፱(138፥9)
ወእመኒ ነሣእኩ ክንፈ ከመ ንስር
ወሠረርኩ እስከ ማኅለቅተ ባሕር
ህየኒ እዴከ ትመርሀኒ ወታነብረኒ የማንከ
ምስባክ ዘቅዳሴ
ወይርአዩ አህዛብ በቅድመ አዕይንቲነ
በቀለ ደሞሙ ለአግበርቲከ ዘተክዕወ
ይባዕ ቅድሜከ ገዐሮሙ ለሙቁሓን
ቅዳሴ
👉ዘዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ (ኀቤከ)
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
@aleroe
ኤልሮኢ፡(⚜ምክር⚜)
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
✍.....ትህትና በአባቶች ሕይወትና ትምህርት ቀዳሚውን ስፍራ ይዞ ይገኛል። ቅዱስ ያዕቆብ እንዲህ ብሏል ስለ ትህትና ማስተማር እፈልጋለሁ። ደግሞ እፈራለሁ። ስለ እግዚአብሔር ለመናገር እንደሚፈራ ሰው እመስላለሁ። ምክንያቱም ትህትና መለኮት ሰው ሆኖ በምድር ሲገለጥ የተጠቀለለበት መጎናጸፊ ነውና። ሰው ሆኖ በአጭር ደረት በጠባብ ቁመት የመገለጡም ምሥጢር እጅግ አስደናቂ በሆነ በትህትናው ነው። ይሄ ሁኔታው ያስደነቀው ነቢዩ ኢሳይያስ "ያልተጠባበቅነውን የጽድቅ ሥራህን ባደረግህ ጊዜ ወረድህ፤ ተራሮችም በፊትህ ተንቀጠቀጡ" ኢሳ. 64፥4 ብሏል። ሰይጣን ትሁት ሰው ሲያይ የሚፈራው በትሁት ሰው ውስጥ የፈጠረውንና በትህትና ያሸነፈውን እግዚአብሔር ስለሚያየው ነው።
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
@aleroe
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
✍.....ትህትና በአባቶች ሕይወትና ትምህርት ቀዳሚውን ስፍራ ይዞ ይገኛል። ቅዱስ ያዕቆብ እንዲህ ብሏል ስለ ትህትና ማስተማር እፈልጋለሁ። ደግሞ እፈራለሁ። ስለ እግዚአብሔር ለመናገር እንደሚፈራ ሰው እመስላለሁ። ምክንያቱም ትህትና መለኮት ሰው ሆኖ በምድር ሲገለጥ የተጠቀለለበት መጎናጸፊ ነውና። ሰው ሆኖ በአጭር ደረት በጠባብ ቁመት የመገለጡም ምሥጢር እጅግ አስደናቂ በሆነ በትህትናው ነው። ይሄ ሁኔታው ያስደነቀው ነቢዩ ኢሳይያስ "ያልተጠባበቅነውን የጽድቅ ሥራህን ባደረግህ ጊዜ ወረድህ፤ ተራሮችም በፊትህ ተንቀጠቀጡ" ኢሳ. 64፥4 ብሏል። ሰይጣን ትሁት ሰው ሲያይ የሚፈራው በትሁት ሰው ውስጥ የፈጠረውንና በትህትና ያሸነፈውን እግዚአብሔር ስለሚያየው ነው።
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
@aleroe
ኤልሮኢ:(⚜ትምህርት⚜)
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
33ቱ የእመቤታችን በዓላት ሠላሳ ሦስቱ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዓላት እነዚህ ናቸው፡-
+ ነሐሴ 7- እመቤታችን የተፀነሰችበት ዕለት፡፡
+ ነሐሴ 16- ሥጋዋ የፈለሰበት/በልጇ ኃይል ከሞት ተለይታ የተነሣችበትና ወደ ሰማይ ያረገችበት ዕለት፡፡
+ ከነሐሴ 17 እስከ ነሐሴ 21 ድረስ ለ5 ቀናት ትንሣኤዋ እንደልጇ ትንሣኤ ይከበራል፡፡ የጌታ ትንሣኤ አንድ እሑድ ቀን መኾኗ የታወቀ ቢሆንም የትንሳኤው መታሰቢያ እስከ 50 ቀናት ማክበራችንን እናስታውስ የእመቤታችንም እንደዚሁ ነው፡፡
+ መስከረም 10- ሥጋን የለበሰች የምትመስለውና ብዙ ተአምራት ታደርግ የነበረችው የእመቤታችን ሥዕል ፄዴንያ ወደተባለ አገር ገብታ የተቀመጠችበትን ዕለት፡፡
+ መስከረም 21 ትከብራለች፡፡ አርዮስን ለማውገዝ በ326 ዓ.ም በኒቅያ የተሰበሰቡት ቅዱሳን ከሚያዝያ እስከ መስከረም 21 ቀን ድረስ በመሆኑ የመስከረም ማርያም (ብዙኃን ማርያም)
ተብሎ በዓሏ ይከበራል፡፡ እንዲሁም ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ የክርስቶስን ቅዱስ መስቀል ወደ ግሸን ደብረ ከርቤ ገዳም በመስከረም 21 ቀን ስላስገቡ ምእመናን በዓሉን በግሸን ማርያም ያከብሩታል፡፡
+ ጥቅምት 21- ትከብራለች/የምትታሰብበት የግዝት በዓል ነው፡፡
+ ኅዳር 6- ወደ ግብጽ አገር ተሰዳ ስትመለስ ቁስቋም በምትባል ሀገር ገብታ ያረፈችበት ዕለት፡፡
+ ኅዳር 21- ጽላተ ሙሴ አክሱም ቤተ መቅደስ ተሠርቶላት በክብር ያረፈችበት ዕለት፡፡ ዳግመኛም ካህኑ ዘካርያስ የእመቤታችን ምሳሌ የሆነውን የመቅረዝ ፋና ሲበራ ያየበት ዕለት ነው፡፡
+ ታኅሣሥ 3-በሦስት ዓመቷ ወደ ቤተ መቅደስ የገባችበት ዕለት፡፡
+ ታኅሣሥ 21 ትከብራለች፡፡ የምትታሰብበት የግዝት በዓል ነው፡፡
+ ታኅሣሥ 22- ብሥራተ ገብርኤል (ቅዱስ ደቅስዮስ እመቤታችን ጌታን የፀነሰችበትን የመጋቢት 29 ቀንን በዓል በዚህ ዕለት አከበረ)፡፡
+ ታኅሣሥ 28- ጌታችንን የወለደችበት የመታሰቢያ በዓል (በ4 ዓመት አንድ ጊዜወርሃ ጳጉሜን 6 ቀን ስትሆን ልደት በ28 ይውላል)፡፡
+ ታኅሣሥ 29- ጌታችንን በድንግልና የወለደችበት የመታሰቢያ በዓል፡፡
+ ጥር 21- እመቤታችን በ64 ዓመቷ ያረፈችበት ዕለት፡፡
+ የካቲት 16- ከልጇ ታላቅ ቃልኪዳን የተቀበለችበት ዕለት፡፡
+ የካቲት 21 ትከብራለች/የምትታሰብበት የግዝት በዓል ነው፡፡
+ መጋቢት 21 ትከብራለች/የምትታሰብበት የግዝት በዓል ነው፡፡
+ መጋቢት 29 ትከብራለች/ጌታችንን የፀነሰበት ጥንተ በዓል፡፡
+ ሚያዝያ 21 ትከብራለች/የምትታሰብበት የግዝት በዓል ነው፡፡
+ ግንቦት 1- እመቤታችን የተወለደችበት ዕለት፡፡
+ ግንቦት 21- በደብረ ምጥማቅ በገሃድ ተገልጻ ታላቅ ተአምር ያደረገችበት፡፡
+ ግንቦት 22- በደብረ ምጥማቅ ለተሰበሰቡ ምእመናን በግልጽ በመታየት ትነጋገራቸው ነበር፡፡
+ ግንቦት 23- በደብረ ምጥማቅ ለተሰበሰቡ ምእመናን በግልጽ በመታየት ትነጋገራቸው ነበር፡፡
+ግንቦት 24- እመቤታችን ተወዳጅ ልጇን ይዛ ከአረጋዊ ዮሴፍና ሰሎሜ ጋር በመሰደድ ግብፅ አገር የገባችበት ዕለት፡፡
+ ግንቦት 25- ተወዳጅ ልጇ የደረቁ በትሮችን ተክሎ በተአምራት ያለመለመበት ዕለት፡፡
+ ሰኔ 8- ተወዳጅ ልጇ ከደረቅ ዓለት ላይ ውኃ ያፈለቀበት፡፡
+ ሰኔ 21- ጌታችን ሰኔ 20 ተገልጦ ሐዋርያቱን ተሰብስቦ በስሟ ቤተ ክርስቲያን ከሠራላት በኋላ በቀጣዩ ቀን ቅዳሴ ቤቷን ያከበረበት ዕለት ነው፡፡
+ሐምሌ 21 ትከብራለች/የምትታሰብበት የግዝት በዓል ነው፡፡
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
@aleroe
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
33ቱ የእመቤታችን በዓላት ሠላሳ ሦስቱ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዓላት እነዚህ ናቸው፡-
+ ነሐሴ 7- እመቤታችን የተፀነሰችበት ዕለት፡፡
+ ነሐሴ 16- ሥጋዋ የፈለሰበት/በልጇ ኃይል ከሞት ተለይታ የተነሣችበትና ወደ ሰማይ ያረገችበት ዕለት፡፡
+ ከነሐሴ 17 እስከ ነሐሴ 21 ድረስ ለ5 ቀናት ትንሣኤዋ እንደልጇ ትንሣኤ ይከበራል፡፡ የጌታ ትንሣኤ አንድ እሑድ ቀን መኾኗ የታወቀ ቢሆንም የትንሳኤው መታሰቢያ እስከ 50 ቀናት ማክበራችንን እናስታውስ የእመቤታችንም እንደዚሁ ነው፡፡
+ መስከረም 10- ሥጋን የለበሰች የምትመስለውና ብዙ ተአምራት ታደርግ የነበረችው የእመቤታችን ሥዕል ፄዴንያ ወደተባለ አገር ገብታ የተቀመጠችበትን ዕለት፡፡
+ መስከረም 21 ትከብራለች፡፡ አርዮስን ለማውገዝ በ326 ዓ.ም በኒቅያ የተሰበሰቡት ቅዱሳን ከሚያዝያ እስከ መስከረም 21 ቀን ድረስ በመሆኑ የመስከረም ማርያም (ብዙኃን ማርያም)
ተብሎ በዓሏ ይከበራል፡፡ እንዲሁም ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ የክርስቶስን ቅዱስ መስቀል ወደ ግሸን ደብረ ከርቤ ገዳም በመስከረም 21 ቀን ስላስገቡ ምእመናን በዓሉን በግሸን ማርያም ያከብሩታል፡፡
+ ጥቅምት 21- ትከብራለች/የምትታሰብበት የግዝት በዓል ነው፡፡
+ ኅዳር 6- ወደ ግብጽ አገር ተሰዳ ስትመለስ ቁስቋም በምትባል ሀገር ገብታ ያረፈችበት ዕለት፡፡
+ ኅዳር 21- ጽላተ ሙሴ አክሱም ቤተ መቅደስ ተሠርቶላት በክብር ያረፈችበት ዕለት፡፡ ዳግመኛም ካህኑ ዘካርያስ የእመቤታችን ምሳሌ የሆነውን የመቅረዝ ፋና ሲበራ ያየበት ዕለት ነው፡፡
+ ታኅሣሥ 3-በሦስት ዓመቷ ወደ ቤተ መቅደስ የገባችበት ዕለት፡፡
+ ታኅሣሥ 21 ትከብራለች፡፡ የምትታሰብበት የግዝት በዓል ነው፡፡
+ ታኅሣሥ 22- ብሥራተ ገብርኤል (ቅዱስ ደቅስዮስ እመቤታችን ጌታን የፀነሰችበትን የመጋቢት 29 ቀንን በዓል በዚህ ዕለት አከበረ)፡፡
+ ታኅሣሥ 28- ጌታችንን የወለደችበት የመታሰቢያ በዓል (በ4 ዓመት አንድ ጊዜወርሃ ጳጉሜን 6 ቀን ስትሆን ልደት በ28 ይውላል)፡፡
+ ታኅሣሥ 29- ጌታችንን በድንግልና የወለደችበት የመታሰቢያ በዓል፡፡
+ ጥር 21- እመቤታችን በ64 ዓመቷ ያረፈችበት ዕለት፡፡
+ የካቲት 16- ከልጇ ታላቅ ቃልኪዳን የተቀበለችበት ዕለት፡፡
+ የካቲት 21 ትከብራለች/የምትታሰብበት የግዝት በዓል ነው፡፡
+ መጋቢት 21 ትከብራለች/የምትታሰብበት የግዝት በዓል ነው፡፡
+ መጋቢት 29 ትከብራለች/ጌታችንን የፀነሰበት ጥንተ በዓል፡፡
+ ሚያዝያ 21 ትከብራለች/የምትታሰብበት የግዝት በዓል ነው፡፡
+ ግንቦት 1- እመቤታችን የተወለደችበት ዕለት፡፡
+ ግንቦት 21- በደብረ ምጥማቅ በገሃድ ተገልጻ ታላቅ ተአምር ያደረገችበት፡፡
+ ግንቦት 22- በደብረ ምጥማቅ ለተሰበሰቡ ምእመናን በግልጽ በመታየት ትነጋገራቸው ነበር፡፡
+ ግንቦት 23- በደብረ ምጥማቅ ለተሰበሰቡ ምእመናን በግልጽ በመታየት ትነጋገራቸው ነበር፡፡
+ግንቦት 24- እመቤታችን ተወዳጅ ልጇን ይዛ ከአረጋዊ ዮሴፍና ሰሎሜ ጋር በመሰደድ ግብፅ አገር የገባችበት ዕለት፡፡
+ ግንቦት 25- ተወዳጅ ልጇ የደረቁ በትሮችን ተክሎ በተአምራት ያለመለመበት ዕለት፡፡
+ ሰኔ 8- ተወዳጅ ልጇ ከደረቅ ዓለት ላይ ውኃ ያፈለቀበት፡፡
+ ሰኔ 21- ጌታችን ሰኔ 20 ተገልጦ ሐዋርያቱን ተሰብስቦ በስሟ ቤተ ክርስቲያን ከሠራላት በኋላ በቀጣዩ ቀን ቅዳሴ ቤቷን ያከበረበት ዕለት ነው፡፡
+ሐምሌ 21 ትከብራለች/የምትታሰብበት የግዝት በዓል ነው፡፡
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
@aleroe
ኤልሮኢ:(⚜የዕለቱ ምስባክና ወንጌል⚜)
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
መስከረም 05/01/2013 ዓ.ም
ምስባክ ዘነግህ
መዝ ፴፱፥፭(39፥5)
ብዙኅ ገበርከ እግዚኦ አምላኪየ መንክረከ
ወአልቦ ዘይመስሎ ለሕሊናከ
አይዳዕኩ ወነገርኩ ወበዝኀ እምኁልቍ
ምስባክ ዘቅዳሴ
አዋልደ ንግሥት ለክብርከ
ወትቀወወም ንግሥት በየማንከ
በአልባሰ ወርቅ ዑፅፍት ወኁብርት
ቅዳሴ
ዘሰለስቱ ምዕት (ግሩም)
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
@aleroe
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
መስከረም 05/01/2013 ዓ.ም
ምስባክ ዘነግህ
መዝ ፴፱፥፭(39፥5)
ብዙኅ ገበርከ እግዚኦ አምላኪየ መንክረከ
ወአልቦ ዘይመስሎ ለሕሊናከ
አይዳዕኩ ወነገርኩ ወበዝኀ እምኁልቍ
ምስባክ ዘቅዳሴ
አዋልደ ንግሥት ለክብርከ
ወትቀወወም ንግሥት በየማንከ
በአልባሰ ወርቅ ዑፅፍት ወኁብርት
ቅዳሴ
ዘሰለስቱ ምዕት (ግሩም)
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
@aleroe
ኤልሮኢ:(⚜የዕለቱ ምስባክና ወንጌል⚜)
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
መስከረም 07/01/2013 ዓ.ም
ምስባክ ዘነግህ
መዝ ፭፥፱(5፥9)
ወጸልሐዉ በልሳናቲሆሙ
ኵንኖሙ እግዚኦ ወይደቁ በውዴቶሙ
ወበከመ ብዝኀ ሕብሎሙ ስድዶሙ
ምስባክ ዘቅዳሴ
እስመ መምህረ ሕግ ይሁብ በረከተ
ወየሐውር እምኃይል ውስተ ኃይል
ወያስተርኢ አምላከ አማልክት በጽዮን
ቅዳሴ
ዘእግዝእትነ (ጎሥዓ)
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
@aleroe
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
መስከረም 07/01/2013 ዓ.ም
ምስባክ ዘነግህ
መዝ ፭፥፱(5፥9)
ወጸልሐዉ በልሳናቲሆሙ
ኵንኖሙ እግዚኦ ወይደቁ በውዴቶሙ
ወበከመ ብዝኀ ሕብሎሙ ስድዶሙ
ምስባክ ዘቅዳሴ
እስመ መምህረ ሕግ ይሁብ በረከተ
ወየሐውር እምኃይል ውስተ ኃይል
ወያስተርኢ አምላከ አማልክት በጽዮን
ቅዳሴ
ዘእግዝእትነ (ጎሥዓ)
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
@aleroe
ኤልሮኢ:(⚜የዕለቱ ምስባክና ወንጌል⚜)
መስከረም 08/01/2013 ዓ.ም
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
ምስባክ ዘነግህ
መዝ ፻፲፰፥፷፩(118፥61)
ወእምቃልከ ደንገፀኒ ልብየ
ወበቃልከ ተፈሣሕኩ
ከመ ዘረከበ ምህርካ ብዙኀ
ምስባክ ዘቅዳሴ
ካህናቲከ ይለብሱ ጽድቀ
ወጸድቃኒከ ትፍሥሕተ ይትፌሥሑ
በእንተ ዳዊት ገብርከ
ምስባክ ዘቅዳሴ ተለዋጭ
ይትፌሣሕ ጻድቅ ሶበ ይሬኢ በቀለ
ወይትሐፀብ እዴሁ በደመ ኃጥእ
ወይብል ሰብእ ቦኑ እንጋ ፍሬ ለጻድቅ
ቅዳሴ
ዘኤጲፋንዮስ (ዐቢይ)
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
@aleroe
መስከረም 08/01/2013 ዓ.ም
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
ምስባክ ዘነግህ
መዝ ፻፲፰፥፷፩(118፥61)
ወእምቃልከ ደንገፀኒ ልብየ
ወበቃልከ ተፈሣሕኩ
ከመ ዘረከበ ምህርካ ብዙኀ
ምስባክ ዘቅዳሴ
ካህናቲከ ይለብሱ ጽድቀ
ወጸድቃኒከ ትፍሥሕተ ይትፌሥሑ
በእንተ ዳዊት ገብርከ
ምስባክ ዘቅዳሴ ተለዋጭ
ይትፌሣሕ ጻድቅ ሶበ ይሬኢ በቀለ
ወይትሐፀብ እዴሁ በደመ ኃጥእ
ወይብል ሰብእ ቦኑ እንጋ ፍሬ ለጻድቅ
ቅዳሴ
ዘኤጲፋንዮስ (ዐቢይ)
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
@aleroe
ኤልሮኢ :(⚜መንፈሳዊ ስነፅሁፍ⚜)
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
ትህትና
ልበ ትሁታን፡ ብፁዕ ናቸውና
እግዚአብሔርን አዩት፡ በንፁህ ህሊና
እስኪ ከቅዱሳን ፡ጉረኛ ማን አለ?
እኔ አውቃለሁ፡ አንተን ወዲያ ያለ!
ለሰው ልጅ ትህትና: በውነት ያስፈልጋል
እንደ አንበሳ ማጉራት :ለትዝብት ይሰጣል
ዲያቢሎስ በትዕቢት :እንዲያ ተወጥሮ
ያልሰራውን ሰራሁ ሲል: ትልቅ ውሸት ፈጥሮ
ከጥልቁ ወደቀ፡ ከዚያ ከጨለማ
ክብር እንዳልነበረው፡ ከኢዮር ራማ
ጥሩ ይመስለዋል፡ አየ ሰው ሞኙ
በጉራ ሲናገር፡ ማይታወቅ ከቶ ማይገኙ
ትህትና አሳይቷል፡ ሰባቱን ሰማያት
መንገድን ይጠርጋል፡በጎውን ለማየት
እድል ያስጥሀል፡ በሰማይ በገነት
ጉራን አውልቃችሁ ፡ትህትናን ልበሱ
ክርስቶስ አሳይቶናል እሱን አስታውሱ፡፡
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
@aleroe
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
ትህትና
ልበ ትሁታን፡ ብፁዕ ናቸውና
እግዚአብሔርን አዩት፡ በንፁህ ህሊና
እስኪ ከቅዱሳን ፡ጉረኛ ማን አለ?
እኔ አውቃለሁ፡ አንተን ወዲያ ያለ!
ለሰው ልጅ ትህትና: በውነት ያስፈልጋል
እንደ አንበሳ ማጉራት :ለትዝብት ይሰጣል
ዲያቢሎስ በትዕቢት :እንዲያ ተወጥሮ
ያልሰራውን ሰራሁ ሲል: ትልቅ ውሸት ፈጥሮ
ከጥልቁ ወደቀ፡ ከዚያ ከጨለማ
ክብር እንዳልነበረው፡ ከኢዮር ራማ
ጥሩ ይመስለዋል፡ አየ ሰው ሞኙ
በጉራ ሲናገር፡ ማይታወቅ ከቶ ማይገኙ
ትህትና አሳይቷል፡ ሰባቱን ሰማያት
መንገድን ይጠርጋል፡በጎውን ለማየት
እድል ያስጥሀል፡ በሰማይ በገነት
ጉራን አውልቃችሁ ፡ትህትናን ልበሱ
ክርስቶስ አሳይቶናል እሱን አስታውሱ፡፡
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
@aleroe