ምናልባት የአንድ ቀን ስህተት
ትክክለኛውን መንገድ ያሳይሃል!

@alahu_akber1
'
•••✿❒ ነብዩሏህ ሉጥ ዐለይሂ ሰላም ❒✿•••

#ክፍል 2

ከሓዲያኑ የሰዶም ሕዝቦች ሉጥ ላይ ማፌዛቸውንና ማስቸገራቸውን አጠናክረው ቀጠሉ።

#ውዶቼ በባለፈው ትምህርታችን ላይ ታስታውሱ እንደሆነ መላእክት ነቢዩላህ ኢብራሂም ቤት ሄደው ዘይሯዋቸው ከዚያም መላእክት ራሳቸውን ለኢብራሂም አስተዋወቁ።

“እኛ አዋቂ ልጅ እንደምታገኝ ልናበስርህ ከጌታህ ዘንድ የተላክን መልዕከተኞች ነን።” አሏቸው። «አሁን ከአንተ ቤት ወጥተን ወደ ሉጥ ሕዝቦች በመሄድ ሉጥን እንረዳዋለን።
የሕዝቦቹ መጥፊያ በዚህች ሌሊት ነው። ቀጠሯቸው ጐህ ሲቀድ ነው። በማለት መላእክቱ የመጡበትን ዓለማ ለኢብራሂም (ዐ.ሰ) አስረዱ።
ኢብራሂም በሁኔታው ተደናግጠው ነገሩ እንዲዘገይ ለማድረግ ሞከሩ። መላእክቱ ግን የአላህ ትእዛዝ ስለሆነ ሳይዘገይ የሚፈጸም መሆኑን አስረዷቸው።
መላእክቱ ከነብዩ ኢብራሂም ቤት ወጥተው ወደ ሰዶም መንደር አመሩ። አስር ሶላት ወቅት ሲሆን ሰዶም መንደር ዳርቻ ደረሱ።
እዚያ ቦታ ላይ በደን ውስጥ የሚፈስ ወንዝ ነበር። ከወንዙ ዳርቻ አንዲት ልጅ ውሃ ለመቅዳት ቆማ አገኟት። ይህች ልጅ የሉጥ (ዐ.ሰ) ልጅ ነበረች።

4ቱን ወጣቶች ስታይ ለየት ያለ ውበት ስለነበራቸው ተደናገጠች። ከ4ተኛው አንደኛው የሉጥ ቤት የት እንደሆነና እንግዳም ይቀበሉ እንደሆነ ጠየቃት።
ልጅቷም የሰዶም ሰዎችን አስፀያፊ ተግባር ስለምታውቅ «ለአባቴ ነግሬ መልሱን እስከምነግራችሁ ድረስ እዚሁ ቆዩ። ወደ ሰዶም እንዳትገቡ» ብላ አስጠነቅቃቸው የውሃ እቃዋን ወንዙ ዳር ተወችና ፈጥና ወደ አባቷ ሉጥ (ዐ.ሰ) ዘንድ በመሄድ ሦስት ወጣቶች እሳቸውን ፈልገው እንደመጡ ነገረቻቸው።

ሉጥ ይህን መልዕክት ሲሰሙ ተደሰቱ ወይስ አዘኑ? ስለሁኔታው አላህ (ሱ.ወ) በሁድ ምዕራፍ ውስጥ እንዲህ ይላል፦

وَلَمَّا جَآءَتْ رُسُلُنَا لُوطًۭا سِىٓءَ بِهِمْوَضَاقَبِهِمْ ذَرْعًۭا وَقَالَ هَـٰذَا يَوْمٌ عَصِيبٌۭ ﴿٧٧﴾
“መልዕክተኞቻችን ሉጥን በመጡት ጊዜ በነሱ (ምክንያት) አዘነ። ልቡም በነሱ ተጨነቀ። ይህ ብርቱ ቀን ነውም አለ።“ (ሁድ፥ 77)

ሉጥ (ዐ.ሰ) «ዛሬ አስቸጋሪ ቀን ነው። አሉና ፈጥነው ወደ እንግዶቹ ሄዱ። እንግዶቹን ሲያዩ ለሰዶም ሰዎች መጥፎ ተግባር እንዳይጋለጡ በመፍራት ይበልጥ አዘኑ።

ሉጥ እንግዶቹን ከየት እንደመጡ ጠየቋቸው። መልስ ሰጧቸው። ወደ የት እንደሚሄዱ ሲጠይቋቸው ግን መልስ አልሰጧቸውም ነበር። ይልቁንም በእንግድነት እንዲቀበሏቸው ጠየቋቸው። ሉጥ (ዐ.ሰ) እንግዶቹን ለማስተናገድ ስስት አልነበረባቸውም።

ነገር ግን መላእክት መሆናቸውን ስላላወቁ የመንደሩ ሰዎች አስፀያፊ ተግባራቸውን እንዳይፈጽሙባቸው ፈርተው ነበር ያዘኑት።
ከዚያም ፊት ለፊት እየመሩ እንግዶቻቸውን አስከትለው ወደ ሰዶም መንደር ገቡ።
በመንገድ ላይ እያሉ ሉጥ (ዐ.ሰ) ቆም አሉና «ከዚህ አገር ሰዎች አስጠንቅቃችኋለሁ። በመሬት ላይ እንደነዚህ ሰዎች ቆሻሻ ሰው የለም» አሏቸው። መላእክቱ ሉጥ በሰጧቸው ማስጠንቀቂያ ላይ ምንም አስተያየት ሳይሰጡ ዝም ብለው መንገዳቸውን ቀጠሉ።

ሉጥ (ዐ.ሰ) ለእንግዶቹ ይህን ያሏቸው ከሰዶማዊያን ዓይን እንዲርቁ ፈልገው ነበር። እንግዶቹ ግን ምንም ሳይናገሩ ፀጥ ብለው ቆዩ።
በዚህን ጊዜ ሉጥ (ዐ.ሰ) ወደ ሰዶም መንደር በሌሊት ተደብቀው እንዲገቡ ጠየቋቸው።

እንግዶቹ ይህን ተቀብለው ማንም ሳያያቸው ከሉጥ ጋር በመሆን በሌሊት ወደ ከተማዋ ገቡ።

ሉጥ (ዐ.ሰ) እንግዶቹ ሌሊት ገብተው ጠዋት ጐህ ሲቀድ ማንም ሳያያቸው ይወጣሉ በሚል አስበው ነበር።
ሉጥ (ዐ.ሰ) አሁን ካሁን መጥፎዎቹ ሰዎች እነዚህን እንግዶች እንዳያይዋቸው እየተጨነቁ ከ4ቱ እንግዶቻቸው ጋር

እንደምንም ወደ ቤታቸው ገቡ።ከመንደሩ ሰዎች ማንም አላያቸውም ነበር።
ነገር ግን በቤት ውስጥ የነበረችው ከሓዲዋ ሚስታቸው እንግዶቹን እንዳየች ተደብቃና ድምጽዋን አጥፍታ ከቤት ወጣች።

★ የሉጥ (ዐ.ሰ) ሚስት በፍጥነት ወደ ሰዶማዊያኑ በመሄድ በሉጥ ቤት ከሰዶም ያልሆኑ እንግዶች እንዳሉ ነገረቻቸው።

ብልሹዎቹ ሰዎች ይህን ሲሰሙ ተደስተው እየተጠራሩ ወጡ። ከዚያም በአንድ ላይ ተሰብስበው ወደ ሉጥ ቤት አመሩ።
ሉጥ (ዐ.ሰ) ማን እንደነገራቸው ሲያስቡ፡ ሚስታቸው ቤት ውስጥ አለመኖሯን አወቁ። ሐዘናቸው በጣም ጠና።
ከየአቅጣጫው የተሰበሰቡት ሰዶማዊያን የሉጥን ቤት ከበቡ። ቀጥሎም በሩን መቆርቆር ጀመሩ። ሉጥ (ዐ.ሰ) ምን እንደምፈልጉ ጠየቋቸው።
በፊታቸው ላይ መጥፎ ነገር ይነበብ ነበር። ሉጥ (ዐ.ሰ) ተንኮለኞችን ለመመለስ ቢሞክሩም አልቻሉም። ከዚያም፦

وَجَآءَهُۥ قَوْمُهُۥ يُهْرَعُونَ إِلَيْهِ وَمِن قَبْلُ كَانُوا۟يَعْمَلُونَ ٱلسَّيِّـَٔاتِ ۚ قَالَ يَـٰقَوْمِ هَـٰٓؤُلَآءِ بَنَاتِى هُنَّ أَطْهَرُ لَكُمْ ۖ فَٱتَّقُوا۟ ٱللَّهَ وَلَا تُخْزُونِ فِى ضَيْفِىٓ ۖأَلَيْسَ مِنكُمْ رَجُلٌۭ رَّشِيدٌۭ ﴿٧٨﴾
“ሕዝቦቼ ሆይ! እኝህ ሴቶች ልጆቼ ናቸው። እነሱ ለእናንተ ይልቅ በጣም የጸዱ ናቸው። (አግቧቸው)።

አላህንም ፍሩ። በእንግዶቼም አታሳፍሩኝ። ከናንተ ውስጥ ቅን ሰው የለምን?” (ሁድ፥ 78)በማለት አናገሯቸው።
ሉጥ (ዐ.ሰ) ሰዎቹ ሐራምን ትተው ወደ ሐላል እንዲዞሩ መንገድ ቢያሳዩዋቸውም አሻፈረኝ በማለት መጥፎ የመሥራት ፍላጎታቸውን ለማሳካት መሞከራቸውን ቀጠሉ።
በዚህን ጊዜ ሉጥ (ዐ.ሰ) በራቸውን ዘጉ። ሰዎቹም በሩን በኃይል ነቀነቁት። ሉጥ (ዐ.ሰ) በሁኔታው ተስፋ ቆረጡ።

قَالَ لَوْ أَنَّ لِى بِكُمْ قُوَّةً أَوْ ءَاوِىٓ إِلَىٰ رُكْنٍۢ شَدِيدٍۢ ﴿٨٠﴾
“ በናንተ ላይ ለኔ ኃይል በኖረኝ ወይም ወደ ብርቱ ወገን ቢጠጋ ኖሮ (የሚሠራውን በሠራሁ ነበር)።” (ሁድ፥ 80)

አሏቸው። ሉጥ (ዐ.ሰ) የተንኮለኞቹን ክፋት ለመከላከል በቂ ኃይል በነበረኝ ብለው ተመኙ ።
በዚህን ጊዜ መልአኩ ጅብሪል ቆመና፦ይህን የሉጥን ሁኔታ እና እንግልት የተመለከቱት በወጣቶች የተመሰሉት መላዕክት ሉጥን ጠሩት'ና ሁሉንም ነገር ግልፅ አደረጉለት። መላዕክት መሆናቸውንም አክለው ነገሩት።
1፦ጂብሪል
2፦ሚካኢል
3፦ኢስራፊል
4መለከል ሞት....ነበሩ።
በመጨረሻም ይህችን ከተማ ሊያጠፏት እንደሆነ እና ሉጥ ቤተሰቦቹን እና ተከታዮቹን ሁሉ ሰብስቦ ሱብሂ ሰዐት ከተማይቱን ለቅቆ እንዲወጣ አዘዙት።በዚህ ሁኔታ ሉጥ እንግዶቹን እያወራ ሳለ ህዝቡ በሩን ሊገነጥል ተቃረበ ያን ግዜ ጂብሪልም አላህን አስፈቀደ'ና አንድ ግዜ በሩን ከፍቶ በመውጣት በክንፉ ፊት ፊታቸውን ክፉኛ መታቸው አይኖቻቸውም እዛው መፍሰስ ጀመሩ።

ጠዋት ሲነጋ ሉጥን እንደሚገድሉት እየዛቱ ሁሉም ከበሩ እየተተራመሱ ሄዱ።ከዚያም ሉጥ መላዕክቱን፦መቼ ነው እነዚህን ህዝቦች ምታጠፉት አላቸው።
እነሱም፦"ሱብሂ ላይ ነው" አሉት።

ሉጥም፦"አሁኑኑ ብታጠፏቸውስ" ሲላቸው...

መላዕክቱም፦"እንዴ ሱብሂ ቅርብ አይደል ወይ!!!" አሉት።

በነጋታው ሉጥ ተከታዮቹን፣ቤተሰቦቹን እና አመፀኛዋን ሚስቱን ይዞ ከመቅሰፍቱ ሽሽት ከከተማይቱ መውጣት ጀመረ። ሲወጣም ለተከታዮቹ በከተማይቱ የሚወርደውን መቅሰፍት ማንም ዞሮ ማየት እንደሌለበት አስጠንቅቆ ተናገረ።

አሁም ጉዞ ጀምረዋል...መላዕክቱ እዛው ከተማ ውስጥ ናቸው...ሉጥ እና ተከታዮቹ ከተማይቱን ልክ ለቀው እንደወጡ ከወደ ከተማይቱ በኩል ከፍተኛ ድምፅ ሰሙ።
ማንም ወደ ከተማዋ እንዳይዞር ማስጠንቀቂያ ስለተሰጠ ማንም አልዞረም ነበር።የሉጥ ሚስት ግን ወደኋላ በመዞር፦"ወይኔ ወገኔ,,,,!!!" በማለት ጮኸች።
ትልቅ የድንጋይ ፍንጣሪ መጣና እራሷን ለሁለት ከፈለላትና የመቅሰፍቱ ሰለባ ሆነች።

አላህም ይህን ዘግናኝ ክስተት ሲተርክ እንዲህ ይላል፦
"ትዕዛዛችንም በመጣ ግዜ (የከተማይቱን) ላይዋን ከታች አደረግን(ገለባበጥናት) ተከታታይም የሆነ የሸክላ ድንጋይ በርሷ ላይ አዘነብን" (ሱረቱል ሁድ)

እንዴት አድርጎ እንደገለባበጣቻው ታውቃላችሁ...!!!
መጀመሪያ ጂብሪል ክንፉን በከተማይቱ መሬት ውስጥ ዘቅዝቆ አስገባው።
ከዚያም ከተማይቱን ከነ ህንፃዎቿ ነቅሎ ወደ ሰማይ ከፍ ካደረገ በኋላ ገለበጠው'ና መልሶ ወደ ምድር ተከለው።

ሉጥ ከነ ተከታዮቹ ብዙ ርቀት ከተጓዘ በኋላ ሱዒር የተባለ አከባቢ በመስፈር ይህ ነው ተብሎ በታሪክ መዛግብት እድሜው ባይሰፍርም እዛው ሱዒር ላይ ህይወቱ አልፏል። (ዐለይሂ ሰላቱ ወሰላም)

•••✿ ❒ ተ_ፈ_ፀ_መ ❒✿•••

በቀጣይ #ነብዩሏህ ሷሊህ(ዐ.ሰ) ታሪክ እንጀምራለን 🥰
#share
@alahu_akber1
'
ውበትሽ ቤቴ ሊያስገባሽ ይችላል...
ነገር ግን ፀባይሽ አባትሽ ጋር ሊመልስሽ ይችላል እና ተጠንቀቂ 😁

@alahu_akber1
'
•••✿ ❒ ነብዩሏህ_ሷሊህ_ዐለይሂ_ሰላም_ታሪክ ❒✿•••



የሰሙድ ህዝቦች ከሁድ ህዝቦች በኋላ የመጡ ሲሆኑ በጣም ትዕቢተኛ እና ኩራተኛ ናቸው።
በሳውዲ ዐረቢያ ምድር በሂጃዝ እና በተቡክ መሀከል የሚገኝውን ግዙፍ ተራራ በመፈልፈል ከዘመኑ ጋር የማይመጣጠን ውብ ውብ... ህንፃዎችን ሰርተው ነበር የሚኖሩት።በጣም ትላልቅ ናቸው አሁን ያለው ትውልድ በጉልበትም ሆነ በግዝፈት ከነሱ አይስተካከልም።
ምንም እንኳን ድንጋያማ አካባቢ የሚኖሩ ህዝቦች ቢሆኑም አላህ ምድራቸውን ለቡቃያ ምቹ አድርጓት የምንጮቹንም ብዛት ለጉድ አድርጎታል።
ግዜው ከአባቶቻቸው የወረሱርትን የጣኦት አምልኮ አጧጡፈው የያዙበት ዘመን ነበር።

በዱንያ ሰክረው...አላህን ረስተው...በወንጀል ተጨማልቀው ሳለ አላሁ ሱብሀነሁ ወተዓላ ሳሊህ ኢብን ዑበይድ ኢብን ሂሻም ኢብን.....ዓድ ኢብን ኣርም ኢብን ሳም ኢብን ኑህ (ዐ ሰ) የተባለን መልካም ነቢይ ከመሀከላቸው ላከላቸው።
ሳሊህ ዐ ሰ በነቢይነት ከመመረጣቸው በፊት ህዝቡ ዘንድ በምልካም ስነ ምግባራቸው የሚታወቁ፣ከከበርቴ ቤተሰብ የተወለዱ፣ከዚያም አልፎ ሰዎች ለፍርድ ሚያስቸግር ክርክር ሲገጥማቸው እሳቸው ጋር የሚሄዱ ምርጥ የአላህ ባርያ ናቸው።

ወደፊት ሀገሪቷን በንግስና ያስተዳድሯታል ተብሎም ይገመት ነበር።
በንዲህ አይነት ሁኔታ ላይ ሳለ ሳሊህ ዐ ሰ የጌታቸውን ተልዕኮ እንደተቀበሉ በትኩስነቱ፦" ወገኖቼ ሆይ! አላህን ተገዙ፡፡ ከእርሱ ሌላ ለእናንተ ምንም አምላክ የላችሁም፡፡ ከዓድም በኋላ ምትኮች ባደረጋችሁና በምድሪቱም ላይ ባስቀመጣችሁ ጊዜ አስታውሱ፡፡ ከሜዳዎቿ (ሸክላ) ሕንጻዎችን ትገነባላችሁ፡፡ ከተራራዎችም ቤቶችን ትጠርባላችሁ፡፡ ስለዚህ የአላህን ጸጋዎች አስታውሱ፡፡ በምድርም ውስጥ አጥፊዎች ኾናችሁ አታበላሹ" በማለት ጥሪውን አስተጋባ።
ይህን በሰሙ ግዜ ትዕቢታቸው አናታቸው ላይ ወጣ...ኩራታቸው ገነፈለ...የከተማይቱ መሳፍንትም፦"አንተ ሳሊህ! ቆይ አንተ ከኛ በምን ተሽለህ ነው አላህ መልዕክተኛ አድርጎ ሊመርጥህ የቻለው? ይልቁኑ አማልክቶቻችን በመጥፎ አይን ሳያዩህ አልቀሩም'ና አብደሀል" አሉት።

ከዚያም እንደተለመደው ሳሊህ(ዐ ሰ) የድሆች እና ምስኪኖች ተከታይ ይበራከቱለት ጀመር።ይሁን እንጂ በለፀጋዎች እና ጉልበተኞቹ ዝም ማለትን አልመረጡም'ና ምእመናኑ ዘንድ በመሄድ፦"እናንተ ባመናችሁት ነገር እኛ ክደናል" በማለት ይሳለቁባቸው ነበር።

ከዛላችሁ እነዚህ አመፀኛ ህዝቦች አንደ ቀን የሳሊህን ዐ ሰ ጥሪ ለማስቆም እና ተከታዮቹን ከሱ ለማራቅ ምን ማድረግ እንዳለባቸው ሊመካከሩ አንድ ቦታ ተሰበሰቡ።ብዙ ከመከሩ በኋላ በመጨረሻም ሳሊህን (ዐ ሰ) ያለ ተከታይ ብቻውን ለማስቀረት አንድ መፍትሄ አገኙ።
እሱም፦"ሳሊህን የሚከተል ከአማልክቱ በኩል የማይድንን በሽታ ይይዘዋል።ከሳሊህም የሚርቅ ከነዚህ ነገሮች የተጠበቀ ይሆናል" በማለት ከተማይቷን ቀወጧት።

ነገር ግን ትክክለኛይቱ የዳዕዋ ጥሪ መንገዷን ይዛ ቀጥላለች።በዚህ ሁኔታ ላይ ሳሉ አንድ ቀን ሳሊህ ዐ ሰ ጥሪያቸውን በህዝብ ፊት ሲያደርሱ ህዝቡም፦"አንተ ሳሊህ እውን አንተ ነቢይ ከሆንክ ማረጋገጫ ይሆነን ዘንድ እስቲ ተዐምር አምጣልን" አሉት።

የከተማይቱ ሹማምንት እና የተከበሩ ሰዎች በቦታው ነበሩ።የማይችለውን ነገር በመጠየቅ እንዳደናገሩት በማሰብ የማላገጥን ሳቅ ይስቁበትም ጀመር።(ወላሂ ነቢያቶች አላህ ምንዳቸውን ከፍ ያድርግላቸው።በገዛ ሀገራቸው ይሳቀቃሉ)

ከመሳፍንቱ መሀክል አንዱ ቆመ'ና፦"አንተ ሳሊህ ተዐምር ማሳየት እችላለሁ የምትል ከሆነ የተዐምሩን አይነት እኛ ነን ምንመርጠው ያንተ ስራ እኛ የመረጥነውን ተዐምር መተግበር ብቻ ነው" አሉት

እኛ እያየን ከዚህ ተራራ ውስጥ በግዝፈቷ አቻ የሌላት የአስር ወር እርጉዝ የሆነች፣መልኳም ቀይ የሆነ፣ከግዝፈቷ የተነሳ የከተማይቱ ይዝብ እና እንስሳት የሚጠጡትን ውሀ በአንዴው መጠጣት የምትችል ትልቅ ግመል አውጣልን"አሉት።

ነቢዩላህ ሳሊህም (ዐ ሰ) ህዝቡ ሁሉ ተዐምሩን አይተው በማመን ከጀሀነም ይድኑ ዘንድ የከተማይቱ ሰው ሁሉ እንዲሰበሰብ አዘዙ'ና ሁሉም ተሰበሰቡ።

ከዚያም ሳሊህ (ዐ ሰ) ለጌታቸው ሱጁድ በመውረድ ጌታቸውን ይማፀኑ ጀመር።አላህም የሱን መልዕክተኞች በህዝባቸው ፊት አያሳፍራቸውም'ና ተራራው በጣም መንቀጥቀጥ ጀመረ።

ህዝቡ ሁሉ አይኑን ተራራው ላይ ተክሏል።ካሁን አሁን ምን ሊከሰት ነው በማለት እርስ በርስ ይተያያሉ።

በዚህ ሁኔታ ላይ ሳሉ ተራራው ከፍተኛ ጩኸት ካስተጋባ በኋላ በጣም በመሰንጠቅ ከመሀከሉ ህዝቡ በጠየቀው መልኩ ትልቅ እና እርጉዝ ቀይ ግመል ወጣች።

ይህን ባዩ ግዜ አይኖቻቸው ፈጠጠ፣ አንደበታቸው ደረቀ፣ምላሶቻቸው ተሳሰሩ።ሳሊህም ዐ ሰ፦"ህዝቦቼ ሆይ! ይህች ግመል የአላህ ተዐምር ናት።

ታይዋታላችሁ፤ ትዳስሷታላችሁም እናንተ ዘንድም ትኖራለች።

ባስቀመጣችሁት መስፈርት መሰረት ትልቅ እና እርጉዝ ሴት ግመል እንደመሆኗ መጠን ካሁን በኋላ ውሀችሁንም ለጋራ ነው ምትጠጡት።
አንድ ቀን ግመሊቱ ስትጠጣ ቀጣይ ቀን እናንተ ትጠጣላችሁ። ምክንያቱም መጀመርያ ያስቀመጣችሁት መስፈርት ይህ ነው'ና።

ነገር ግን ይህችን ግመል አንዳችሁ በመጥፎ ከተተናኮላችኋት የአላህ ፈጣኑ ቅጣት ይወርድባችኋል" በማለት አስረዳቸው።
ከዚያም ህዝቡ ለሳሊህ ዐ ሰ ያለው አመለካከት 100% ተቀየረ።ሁሉም ከማንም በላይ ሳሊህን ያከብር ጀመረ።ብዙ ሺህ ሰውም የሳሊህ ተከታይ ሆነ።
ይህ ያሳሰባቸው የከተማይቱ ሹማምንት አንድ ቀን ተሰብስበው ምን ማድረግ እንዳለባቸው ሲወያዩ ውለው በመጨረሻም ግመሊቱን በመግደል ተስማሙ።
ይህ የተወሰነውም በአንድ መጠጥ ቤት ውስጥ ሆነው ነበር።አጋጣሚ እዛው መጠጥ ቤት ሳሉ የመጠጥ ጥማቸው ሳይቋረጥም ከመጠጡ ቤት ጓዳ "መጠጥ አልቋል" የሚል መርዶ ደረሳቸው።
ሹመንቱም፦"ለምንድነው በርከት አድርጋችሁ ማትሰሩት" ብለው ሲጮሁባቸው
የመጠጥ ቤቱ ባለቤት፦
"ዛሬ ውሀ የግመሊቱ ተራ ስለሆነ ውሀ የለም'ና ብዙ መስራት አልቻንም" ብላ መለሰችላቸው።

ከመሀከላቸውም አንድ ቀዳር ኢብን ሳሊፍ ኢብን ጁንደዕ የተባለ አመፀኛ ከመሰል ጓደኛው ጋር ተነሳ'ና ግመሏን ሊገድል ጉዞ ጀመረ።
በጉዞ ላይ ሳሉም ሌላ ሰባት ሰዎችን መንገድ ላይ በመቀላቀል ዘጠኝ ሁነው ግመሏ ውሀ የምትጠጣበት ስፍራ ደረሱ።

ውሀው ዘንድም ደረሱ'ና በያዙት ሰይፍ ገደሏት።ከአጠገቧ ግልገሏ ነበር'ና ግልገሏንም አሳድደው በትልቅ ተራራ ላይ ይዘውት ገደሉት።ከሙጅሪምነታቸው የተነሳ የግመሊቱን ስጋ ቀኑኑ ተከፋፈሉት።

ሳሊህም ዐ ሰ ይህን በተመለከተ ግዜ፦"አሁን የጌታችሁን ቅጣት ተጠባበቁ።
የጌታችሁ ቅጣት ከመውረዱም በፊት ስጋውን ተሎ ተሎ በልታችሁ ጨርሱ" አላቸው።

ህዝቡም፦"አንተ ምን ዝም ብለህ ቅጣት ቅጣት እያልክ ትዝትብናለህ! እስቲ አምጣ ቅጣት ምትለውን" ሲሉት
ሳሊህም፦"በዚህ 3 ቀን ውስጥ የጌታችሁ ቅጣት እናንተ ላይ ተፈፃሚ ይሆናል።ለዚህም ማረጋገጫ ዛሬ ፊታችሁ ብጫ ይሆናል።
ነገ ደሞ ቀይ ይሆናል።ከነገ ወዲያ ደግሞ ጥቁር ይሆንና ትጠፋላችሁ ይህም ሀሰት የሌለው ዛቻ ነው" አላቸው።
እነዚህ የሀፅያትን ፅዋ ጠጥተው የማይጠግቡ ህዝቦችም ሳሊህን ዐ ሰ ለመግደል ወስነው ዝግጅታቸውን አጠናቀው ሳለ፣

በመጀመርያ ግመሏን በገደሉት ዘጠኙ ሰዎች ላይ እቤት ተደረመሰባቸው፣
አሁን የአመፀኞቹ ህዝቦች ፊታቸው መቀያየር ጀምሯል።ሀሉም የፊቱ ብጫ መሆን አስፈርቶት እርስ በርስ ይተያያል።
ሁለተኛው ቀን ደርሶ በነጋታው ሰዉ ሲነቃ ሁሉም ፊቱ ደም መስሏል።በድንጋጤ የሞቱትም ብዙ ነበሩ።ያን ቀን በትካዜ እና በፍራቻ ካሳለፉ በኋላ የማይደርስ የለም'ና ሶስተኛዋ ቀን መጣች።

ፊቶቻቸውን ጥቁረት ወረረው፣ተስፋም ቆረጡ ሁሉም በመሰባሰብ ከፈናቸውን ለብሰው ሽቶ ተቀብተው ሞታቸውን መጠባበቅ ጀመሩ።
ልክ ፀሀይ ጀንበሯን ተሻግራ ብቅ ማለት ስትጀመር ከወደ ሰማይ በኩል እንደመብረቅ ያለ፣ ከፍተኛ ድምፅ ያለው ነገር መጣ።ምድርም በሀል መንቀጥቀጥ ጀመረች...ጂብሪልም በከፍተኛ ድምፁ ጮኸባቸው።ያን ግዜ ልቦቻቸው ከደረታቸው መበጣጠስ ጀመረ።አይኖቻቸውን ወደ ሰማይ ያፈጣሉ...

መቅሰፍቱ ከየት በኩል እንኳን እንደመጣ ማወቅ እየተሳናቸው ነፍሶቻቸው ወደ ሰውነታቸው ዳግም ላትመለስ ተነጠለቻቸው።
የከተማይቱ ህዝብ ሁሉም በያሉበት በድን ሁነው ሲሞቱ አንዲት ሴት ብቻ ቀረች ስሟም ከልባ ቢንት ሰለቅ ይባላል።

ለሳሊህ ዐ ሰ ከፍተኛ ጥላቻ ሲኖታት የክህደትን ዘውድ ከራሷ አኑራለች። ይህን ስትመለከት እግሬ አውጭኝ ብላ ከሀገሩ ሸሸች። ብዙ ከተጓዘችም በኋላ አንድ የዐረብ ነገድ የሚኖሩበትን መንደር ደረሰችና የሆነውን ሁሉ ነገረቻቸው።
በመጨረሻም ውሀ እንዲያጠጧት ጠይቃ ልክ ውሀውን ስትቀምሰው ነፍሷ የሙታንን መንደር ተቀላቀለች።
ሳሊህ ዐለይሂሰላም ወደ ሌላ ቦታ ተሰደደ ሷሊህ እና ከሱጋ ያመኑት ሰወች ወደ ተከበረቺው ወደ ተባረከቺው ፊለስጢን ሀገር ተሰደደ፡፡
ከዚያንም በረምላ ከተማ መኖር ጀመረ፡፡ ቆይቶም ሷሊህ ዐለይሂሰለም በ58 አመታቸው በዛው በረምላ ከተማ የዚህችን አለም ጣጣ አጠናቅቀው ነፍሳቸውን ለጌታቸው አስረከቡ።

በነገራችን ላይ ረሱላችን (ሰዐወ) አንድ ቀን ለተቡክ ዘመቻ ባልደረቦቻቸውን ይዘው በመሄድ ላይ ሳሉ የሳሊህ ህዝቦች የጠፉበትን ከተማ ደረሱ። ማንም አይኖርበትም..የተወሰኑ ሶሃቦች በሷሊህ ከተማ ውስጥ ከሚገኙ ምንጮች ውስጥ ሊቀዱ ሄዱ፣ የተወሰኑት፣ ደግሞ መገልገያ እቃወችን አመጡ፥

የአሏህ መልክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም መገልገያ መሰረያወቹ እንዲሰበሩ እና የተቀዳም ውሃ እንዲደፋ አዘዙ፡፡ከዚያ ውሃ የተሰረው ምግብ ሁሉ እንድደፋ አዘዙ፦ከዚያም ነቢያችን ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ፦

"ይህችን ከተማ ስትገቡ እያለቀሳችሁ ፣መልቀስ እንኳዋ ባትችሉ ለማልቀስ የዳዳቹህ ሁናቹህ እንጂ ዝም ብላችሁ እንዳትገቡ።
እኔ በነሱ የወረደው በላእ እናንተን እንዲያገኝብኝ አልፈልግም" አሏቸው።ፊዳከ አቢ ወ ኡም ወነፍሲ ወደሚ ወዒርዲ ያ ረሱሉላህ

በዚያ አከባቢም ያሉ ነገሮችን ሁሉ ለባልደረቦቻቸው አሳይዋቸው።ግመሏም የወጣችበትን እና የተገደለችበትንም ቦታ ወስደው አሳይዋቸው።

•••✿ ❒ ተ_ፈ_ፀ_መ ❒✿•••

በቀጣይ #ነብዩሏህ_ኢብራሂም(ዐ.ሰ) ታሪክ እንጀምራለን 🥰
#share
@alahu_akber1
'
የሆነ ሰዐት ላይ ሁሉም ሰው ደስተኛ ነበር 🥀
ነገ ሐሙስ ነው የቻለ ይፁም ያልቻለ ለሌሎች ያስታውስ😊


መፆም የምትችሉም share አድርጉ እሺ 😁
ደግሞ በ ዱአ አትርሱን
🥹
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
'
ፍላጎታችን በጣም በዛና የተፃፈውን ቀደር ረሳን
መንገደኞች መሆናችንን ዘነጋንና
የጥቂት ቀናት ፈተና የልብ ሰላም ነሳን::

@alahu_akber1
.
እናትህ ያንተን ሰላም መሆን ለማረጋገጥ ብላ
እንድትረግጣት ትመኝ ነበር!🥹

@alahu_akber1
“በኔ ላይ አንድን ሰለዋት ያወረደ አላህ አስር ሰለዋትን ያወርድለታል። አስር ሀጢያቱን ይሰርዝለታል። ደረጃውን በአስር ከፍ ያደርግለታል።”

ረሱል (ﷺ)

@alahu_akber1
ቆይ ግን የምር ማለት ነው የምር
" ቆይ አባቷ ቢድሯትስ?"
" ቆይ ሀብታም አግኝታ ብትሸመጥጠኝስ ?"
"በትንሽ ነገር ተጣልተን ብንለያይስ ?"
"እእ ግን የኔና የሷ ግንኙነት ሀራም ነው ? አይ አይደለም እኛኮ ጊዜያችን ገና ስለሆነ ነው እንጂ እንጋባለን ደሞኮ ከኒካህ በፊት ላለመነካካት ተማምለናል ። ቆይ ብንማማልስ ምን ለውጥ ያመጣል😫!"

ወዘተ በሚል ርዕሶች ሌትተቀን ከራስህ ጋር እየተከራከርክ እንዴት አስችሎህ ነው የወር ደሞዝህን እሷ ላይ ምትጨርሰው አኺ 😑 እንዴት ልበደንዳና ብትሆኑ ነው ከካፌ ካፌ እየዞራቹ የከተማቹን አስፓልት ምታሰረጉዱት? ደሞ እኮ አብራቹ ስትሄዱ ኩራታቹ የሆነ ከጂሀድ የተመለሰ ሙጃሂድ ነው ምትመስሉት ።

እና ደሞ ሀራም ነገር ፍቅር ላይም ሀራም ነው ከጊዜ በኋላ ሀላል ሊሆን ይችላልና እናግራራው የሚባል ነገር የለም ። 

ብቻ አደብ!😁

Copy
'
ለማንም ሰው ቢሆን ከሚገባው በላይ ዋጋ አትስጡ ።

@alahu_akber1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
'
only a muslim can feel these word ❤️
like father, like son 👌💪

@alahu_akber1
'
ዋስትና በሌለበት አላህ ሆይ በምህረትህ እተማመናለው
ሁሉም የሚረጋገጠው በአንተ ብቻ ነውና።🩷

@alahu_akber1
'
ታገስ ስለው ና እስቲ በኔ ቦታ ሁንና ታገስ አለኝ።

በርግጥ መምከር ቀላል ነው ።
የ ነብያት ታሪክ ይቀጥል እንዴ ??
•••✿ ❒ የነብዩሏህ ኢብራሂም ዐ,ሰ ታሪክ ❒✿•••


#ክፍል 1

#ኢብራሂም #(ኡሉል-ዐዝም)ከተባሉት ከአምስቱ ከበርት ነቢያቶች አንዱ ናቸው።
    
ኢብራሂም ከጣኦት አምላኪያን ቤተሰቦች ነው የተወለዱት።አንዱ ድንጋይ ጠርቦ ያመልካል፣ከፊሉ ፀሀይን እና ኮከብን ያመልካል፣ሌላው ደሞ ንጉሶች ያመልካል።
በዚህ የድንቁርና ዘመን ኢብራሂም ገና በልጅነታቸው ነበር የሰዉ ጅልነት ሚያስገርማቸው።ከምንም በላይ እሚገርመው የኢ ብየ አባት ነበር
ለከተማይቱ ህዝብ የተለያዩ ጣኦታትን እየሰራ የሚሸጥላቸው።
በዚህም የተነሳ የነኢብራሂም ቤተሰብ እጅጉን የተከበሩ ነበሩ።

በዚህች ድንቁርና በተጠናወታት ባቢሎን በምትባል ከተማ ኢብራሂም
ከጣኦታት ሁሉ ታቅበው አደጉ።አሁን አሁን ኢብራሂም በጣም ማሰላሰል ጀምረዋል።
ኢብራሂም ብቻውን ቁጭ ብሎ፦"እንዴት አባቴ ከእንጨት እና ከድንጋይ
እየጠረበ የሚሽጠውን ግኡዝ ነገር ሰዉ ያመልከዋል !!!
ሰዉ ጤና የለውም እንዴ !!!
አይ... ! አይ... ! ነገሩ እንኳን እንዲህ አይሆንም። በእርግጠኝነት ጌታ ማለት
ፍጥረታትን ይፈጥራል እንጂ ፍጥረታት እሱን አይፈጥሩትም። 

እሺ እነዚህ አማልክት ምንም አይጠቅሙም አይጎዱም ካልኩ ታዲያ ፈጣሪ
የታለ !!! እራሱስ ማን ነው?" በማለት ያሰላስላል
ከእለታት አንድ ቀን ኢብራሂም ዐ ሰ እንደተለምዶዋቸው ቢቻቸውን ቁጭ
ብለው ስለ ፈጣሪ ማንነት እና ምንነት እያሰላሰሉ ስለ ድንገት አይናቸው
ጨለማ ውስጥ በሚምዘገዘግ ኮከብ ላይ አረፈ
ኢብራሂምም ድምፃቸውን ከፍ አድርገው፦"ይሄው ጌታዬን አገኘሁ። አዎ ጌታዬ
በሰው እጅ አይፈጠርም እንደ ጣኦታትም ወድቆ አይሰበርም" አሉ።
      
  á‰ áŒŁáˆ ተደሰተ ከደስታው ብዛት ለዚያ ኮኮብ ሌሊቱን ሙሉ
ሲሰግድ አደረ።በዚያ ሌሊት ትክክለኛውን ጌታ እንዳገኘ ለህዝቡ ሁሉ
ተናገረ።ሌሊቱን ሲሰግድ ካነጋ በኋላ ድንግት ጠዋት ላይ ቀና ሲል ያ ጌታ
የመሰለው ኮከብ በብርሀን ተሸፈኖ ጠለቀ።
አሀ...አሁን ማታውን ሙሉ ሲሰግድ ያሳለፈው ለትክክለኛ ጌታ እንዳልሆነ
ተገነዘበ።ከዚያም፦"እኔ ጠላቂዎችን አልወድም" አለ።
ኢብራሂም አሁንም ግን ተስፋ አልቆረጠም።ጌታውን ፍለጋ ዳግም አጠናክሮ
ቀጥሏል።በሁለተኛውም ቀን ኢብራሂም በማታ ብቻውን ቁጭ ብሎ ስለ ጌታው
እያሰላሰለ ሳለ ወደ ላይ ቀና ሲል የሰማዩን ፅልመት በብርሀኑ የገፈፈ ውብ
ጨረቃ ተመለከተ።
አሁን ትንሽ ከመጀመርያው ረጋ አለ'ና፦"ትክክለኛ ጌታዬማ ይህ ነው እንዴት ግን
እስካሁን አላየሁትም!!!" ሲል ከራሱ አወራ።
የዛሬዋን ግን እንደትናንቱ እየሰገደ አላደረም ትንሽ ቆይቶ ተኛ።ጠዋት ላይ
ጌታዬን ልየው ብሎ ሲያንጋጥጥ ጨረቃው ተሰውሯል።
ኢብራሂምም እጅጉን አዘነ እዛው ባለበት ሆኖም፦"ጌታዬ ቀጥተኛውን መንገድ
እራሱ ካልመራኝ ከተሳሳቾች እሆናለሁ" አለ።

     
ተስፋ ቆርጦ በባይተዋርነት ውጭ ላይ ቁጭ ብሎ ሳለ ፀሀይን
ተመለከተ።በጣም ግዙፍ ናት፣ከጨረቃ እና ከኮከብ ስትነፃፀር በጣም ጎልታ
ታየችው።
ኢብራሂምም
፦"ጌታዬን አገኘሁ ይህ ትክክለኛው ጌታዬ ነው በዛ ላይ ከሁሉም
ይገዝፋል" ብሎ ቀኑን በደስታ አሳለፈ።
በመጨረሻም ፀሀይ ወደ ጀምበሯ ስትቃረብ ዘውታሪ አለመሆኗን ተረዳ።ጌታ
ሁሌም ያልለ መሆኑን ተገነዘበ እንዲህም አለ፦"ወገኖቼ ሆይ !! እናንተ
ከምታጋሩት ነገር እኔ ነፃ ነኝ"
አሁን ኢብራሂም ሁሉ ነገር እየተገለፀለት መጥቷል..ጨረቃም፣ፀሀይም
፣ኮከብም አንድ አስተናባሪ ጌታ እንዳላቸው እና እነሱም ጌታ እንዳልሆኑ ተረዳ።
ያ ጌታ ደሞ በአይን ሊታይ እንደማይችልም ተገንዝቦ በዛ የፍጥረተ አለሙ ጌታ
በሆነው አላህ አመነበት።

    
አሁን ኢብራሂም ከድንቁርና ወጥቷል...ቀጣይ እቅዱ ህዝቡን ከድንቁርና
ለማውጣት ቢሆንም ቅድሚያ ለአባቱ መስጠት እንዳለበት ተገንዝቧል።
አባቱ ዘንድም ሄደ'ና፦"አባቴ ሆይ! ለምንድነው እነዚህን የማይጠቅሙ
አማልክትን ጌታ አድርገህ የምትገዛው?
እስቲ አባቴ ተመልከት እነኚህ አማልክት... ምንም አያዩም አይሰሙም እንዴት
በነዚህ ታምናለህ።
አባቴ ሆይ!! ፈጣሪያችን አላህ ነው። ልናየው አይቻለንም እሱን ብቻ ነው
ልንገዛ የሚገባን።ይህም ብቻ ነው ቀጥተኛው መንገድ" በማለት አባቱን ጥሪ
አደረገለት።
ያን ግዜ አባቱ ቁጣው ገነፈለ..."ይህ ብላቴና እንዴት እድሜ ልኬን
ካመለክኩት ጣኦት ተው ይለኛል" ብሎ በጣም ተናደደ።

    
ኢብራሂምም፦"አባቴ ! ላንተም ለወገኖችህም ሸይጣን ነው ይህንን መንገድ
አስውቦ ሚያሳያችሁ። በምትፈፅሙት ሺርክ ከዝወተራችሁ መመለሻችሁ ወደ
እሳት ይሆናል" እያለ በመለማመጥ ወደ አላህ ይጠራቸው ጀመር።
ከዚያም አባትየው በጣም በመቆጣት ካሁን በኋላ ግን
ሊመታው፣ሊገድለው፣በድንጋይም ሊወግረው እንደሚችል አስጠንቅቆ
ኢብራሂምን ከቤት አባረረው።

     
ኢብራሂም አባትየውን መምከር ምንም ጥቅም እንደሌለው በተረዳ
ግዜ፦………
"ሰላም ሆንልኝ።ጌታዬንም ላንተ ምህረት እንዲያደርግልህ እለምነዋለሁ
እርሱ ለኔ በጣም ርኅሩኅ ነው'ና" ብሎት ቤቱን ትቶ ተሰናበተው።
በቃ አሁን የዳዕዋው ጥሪ ከቤት ወጣ ለመላው ህዝብ ይሰራጭም
ጀመር።
ኢብራሂምም ከአላህ ሌላ ምንም አምላክ እንደሌለ እና ሌላ

አማልክትም ምንም እንደማይፈይዱ በየሄደበት ማውራት ጀመረ።

ይህ የኢብራሂም ጉዳይ ቀስ በቀስ የከተማዋ ወሬ ሆነ።በዘመኑ ሀገሪቷን ይመራ ለነበረው እና ከአማልክቱ አንዱ አካል ለሆነውም ኑምሩድ ይህ ወሬ ደረሰው።
ኢብራሂምንም እንዲያቀርቡለት ወታደሮቹን አዘዘ።
ኢብራሂምም ከንጉሱ ፊት ቆመ። በሀገሪቱም ሆነ በመላ አለም የሚመለኩ

አማልክት ሁላ እንደማይጠቅሙ እና እንደማይጎዱ በድፍረት አስረዳው።አላህ

ህያው የሚያደርግ እና የሚገድል ጌታ መሆኑንም አክሎ ነገረው።

ንጉሱም፦"እኔ መግደልም ህያው ማድረግም እችላለሁ" አለው።

ኢብራሂምም፦"እንዴት?" አለው።
ያን ግዜ ንጉሱ ሁለት የሞት ፍርድ የተፈረደባቸውን እስረኞች እንዲቀርቡ
ካደረገ በኋላ አንዱን በመግደል አንዱን በመተው፦"ይኸው እገድላለሁም ህያውም አደርጋለሁ" ብሎ ተመፃደቀበት።

ኢብራሂምም፦"አላህ ፀሀይን ከምስራቅ አስወጥቶ በምዕራብ ያስገባታል።እስቲ አንተ ጌታ ከሆንክ ከ ምዕራብ እስወጣት"ሲለው ንጉሱም
በሀፍረት አንገት ደፋ። ነምሩድ ስለተባለው ንጉስ ወደፊት እናያለን ኢንሻ አላህ የኢብራሂምን ጥሪ ለማሰናከል ሲሞክር አላህ እሱንም ወታደሮቹንም በትንኝ አጠፋቸው።ከእለታት አንድ ቀን የሀገሪቱ ህዝብ ለአመታዊ በአል በጠዋት ወደ መሰብሰቢያ ቦታ መትመም ጀመሩ። ኢብራሂምም በዚህ አጋጣሚ አንድ ምርጥ ሀሳብ መጣላቸው'ና ለመፈፀምም ወሰኑ።

ክፍል 2 ይቀጥላል....

#share
@alahu_akber1
ላበስለው እና የተራበ
ልጄን ለመመገብ ስል
እጄን መቁረጥ ይፈቀዳል?

አንዲት የጋዛ እናት ከተናገረችው
አሳማሚ ንግግር💔

@alahu_akber1