Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
1/ የረመዷን ወር ክብር
1000298991245
የኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
ሳዲቅ መሐመድ አሕመድ
0911103231
ምሥኪኖችን ለማስፈጠሪያ ብቻ
00971566331753 whatsapp
1000298991245
የኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
ሳዲቅ መሐመድ አሕመድ
0911103231
ምሥኪኖችን ለማስፈጠሪያ ብቻ
00971566331753 whatsapp
Forwarded from የሕያ ኢብኑ ኑህ - Yahya Ibnu Nuhe
አንዱ ሀሰተኛ ነቢይ ነኝ ብሎ ሲሞግት: ኸሊፋው ዘንድ አመጡት። ንጉሱም ሹማምንቶቹ በተሰበሰቡበት: ነቢይ ነኝ ባዩን:–
እውን አንተ ነቢይ ነህን?
እሱም:– አዎን!
ንጉሱም:– ማስረጃህ ምንድነው?
አሱም:– እናንተ ሁላችሁም በአሁን ሰአት በልባችሁ የምታስቡትን እነግራችኋለሁ! አለው።
ንጉሱም:– እሺ ንገረን ምን እያሰብን ነው?
እሱም:– አሁን የምታስቡት ይህ ሰው ሀሰተኛ ነቢይ ነው! እያላችሁ ነው አለ 😄
© ኡስታዝ አቡ ሀይደር
@Yahya5
እውን አንተ ነቢይ ነህን?
እሱም:– አዎን!
ንጉሱም:– ማስረጃህ ምንድነው?
አሱም:– እናንተ ሁላችሁም በአሁን ሰአት በልባችሁ የምታስቡትን እነግራችኋለሁ! አለው።
ንጉሱም:– እሺ ንገረን ምን እያሰብን ነው?
እሱም:– አሁን የምታስቡት ይህ ሰው ሀሰተኛ ነቢይ ነው! እያላችሁ ነው አለ 😄
© ኡስታዝ አቡ ሀይደር
@Yahya5
Audio
✨ሸህሩ ረመዷን🌙
የፆም አስፈላጊነቱና ጠቀሜታው!ክፍል➋
🎙 አዘጋጅ⇊
➤ በኡስታዝ አቡ ሐይደር
Mp3 ዳውሎድ ለማድረግ
➤ https://goo.gl/ymmyu2
Join us➤ t.me/abuhyder
https://youtu.be/e_tlHgjJkac
የፆም አስፈላጊነቱና ጠቀሜታው!ክፍል➋
🎙 አዘጋጅ⇊
➤ በኡስታዝ አቡ ሐይደር
Mp3 ዳውሎድ ለማድረግ
➤ https://goo.gl/ymmyu2
Join us➤ t.me/abuhyder
https://youtu.be/e_tlHgjJkac
ረመዷን ምንድነው?
በአቡ ሀይደር
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው
ክብርና ምስጋና ለዓለማቱ ጌታ ለአላህ የተገባ ይሁን፡፡(አል-ፋቲሓ 2) የአላህ ሰላምና ውዳሴ የሰው ዘር ታላቅ መሪ ለሆኑት ለነቢዩ ሙሐመድ (አል-አሕዛብ 56) ለመላው የአላህ መልክተኞች (አል-ሷፍፋት 181) የሐቅንም መንገድ በተከተለ ሁሉ ላይ ይሁን (ጣሀ 47)፡፡
ታላቁና ተወዳጁ ነቢያችን (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ሶሐቦቻቸውን የረመዷንን መቃረብ አስመልክቶ የእንኳን አደረሳችሁ ብስራትን ሲገልጹ እንዲህ ይሏቸው ነበር፡- "የተባረከ ወር የሆነው ረመዷን መጣላችሁ!፡፡ አላህ ጾሙን በናንተ ላይ ግዳጅ አድርጓል፡፡ በዚህ ወር የሰማይ ደጃፎች ይከፈታሉ፡፡ የጀሀነም ደጃፎች ይዘጋሉ፡፡ አመጠኛ ሸይጣናት ይታሰራሉ፡፡ አላህ ከአንድ ሺህ ወር (ስራ) የምትበልጥ የሆነች አንድ ለሊት አለችው፡፡ የዚህን ወር መልካም ነገር የተነፈገ ሰው በርግጥም ከብዙ መልካም ነገራት የተነፈገ ነው፡፡" (አሕመድ 7148፣ ነሳኢይ 2106)፡፡
ይህ የነቢያችን (ዐለይሂ-ሶላቱ ወስ-ሰላም) ብስራት ዋና አላማው ሶሐባዎች (ረዲየላሁ ዐንሁም) ከወዲሁ ይህንን የተከበረ ወር ለመቀበል መንፈሳዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ማነሳሳት ነው፡፡ እኛስ ምን ያህል ተዘጋጅተናል? ለዛሬ መግቢያ እንዲሆነን ስለ ረመዷን ፈዷኢል (በረከቶች) የተወሰነ ነገር እንነጋገር፡፡
1. የረመዷን ወር ክብር፡-
የረመዷን ወር በኢስላማዊው የወር አቆጣጠር መሰረት፡ ዘጠነኛ ወር ላይ የሚገኝ ነው፡፡ ይህ ወር ከተቀሩት 11ዱ ወራቶች ለየት የሚያደርገው የራሱ የሆኑ መለያዎች አሉት፡፡ ከነዚህም መለያዎቹ መካከል፡-
ሀ. የጀነት በሮች የሚከፈቱበት ወር መሆኑ፡- የመልካም ስራ መንገዶችና የጥመት ጎዳናዎች በአስራ ሁለቱም ወራት (ሙሉ ዓመት) ለፈላጊዎችና ለሰሪዎች ክፍት ነው፡፡ የአላህ ባሮች ከረመዷን በፊት፣ በረመዷን ውስጥና ከረመዷን በኋላ ባሉት ወራቶች ላይ ወደ ጌታቸው አላህ የሚያቃርባቸውን መልካም ሥራ ከመሥራት አይቦዝኑም፡፡ የሸይጧን ሠራዊቶች ደግሞ (ተውፊቁን ካላገኙ) ከአላህ የሚያርቃቸውን የጥፋት መስመሮች ከመከተልና ክፋትን ከመፈጸም ወደኋላ አይሉም፡፡ የረመዷን ወር የሚለየው ግን ጀነት ለፈላጊዎቿ ተሸሞንሙና ደጃፎቿ ወለል ብለው ተከፍተው ሲታዩ፡ የጀሀነም በሮች ደግሞ የሚከረቸሙ መሆናቸው ነው፡፡
አቢ ሁረይራ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንደነገረን የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- "የረመዷን የመጀመሪው ለሊት ላይ አመጸኛ ሰይጣናት ይታሰራሉ፣ የእሳት በሮች አንድም ሳይቀር ይከረቸማሉ፣ የጀነት በሮች አንድም ሳይቀር ይከፈታሉ፣ በያንዳንዱ ለሊትም አንድ ተጣሪ እንዲህ በማለት ይጣራል፡- ‹‹መልካም ፈላጊ የሆንክ ሆይ! ፊትህን (ወደ መልካም ተግባር) አዙር፡፡ መጥፎን ፈላጊ የሆንከው ሆይ! (የምትሰራውን ክፋት) ቀንስ(አቁም)፡፡ በያንዳንዱ ለሊትም አላህ ከእሳት ነጻ የሚያደርጋቸው ባሮች አሉት" (አሕመድ 18438)፡፡
ለ. የኃጢአት ማስተሰረያ (ማጥፊያ) መሆኑ፡- በማንኛውም ወቅት የሚሰራ መልካም ስራና ወደ አላህ የሚደረግ የንሰሀ ተውበት ኃጢአትን ያጠፋል (ሁድ 114፣ አዝ-ዙመር 53)፡፡ የረመዷን ወር ደግሞ በአግባቡ ከተጾመ፡ ቀጣዩ አመት ረመዷን እስኪመጣ ድረስ በመሀከሉ የተፈጸሙ ጥቃቅን ኃጢአቶችን በመላ ያጠፋል፡፡ ትላልቅ ኃጢአቶች (ከባኢረ-ዙኑብ) የግድ ባለቤቱ ከነሱ ተውበት ሊያደርግ ያስፈልጋቸዋልና፡፡
አቢ ሁረይራ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንደነገረን የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- "አምስት ወቅት ሶላቶችን መስገድ፣ ጁሙዓ ተሰግዶ ቀጣዩ ሳምንት ጁሙዓህ እስኪመጣ፣ ረመዷን ተጹሞ ቀጣዩ ረመዷን እስኪመጣ ድረስ ሰውየው ትላልቅ ኃጢአትን እስከተጠነቀቀ ድረስ በመሀከላቸው ያለውን ትናንሽ ኃጢአት ያስሰርዛሉ" (ሙስሊም)፡፡
ሐ. የዑምራህ ደረጃህ ከፍ ማለቱ፡- ከሐጅ ስርዓት ውጪ ዑምራን ብቻ መፈጸም አጅር የሚያስገኝ የሱና (ሙስተሐብ) ተግባር ነው፡፡ በረመዷን የሚፈጸም ከሆነ ግን አጅሩ ከፍ ብሎ በማደግ የሐጅን ምንዳ ያህል ይደርሳል፡፡
ዐብደላህ ኢብኑ-ዐባስ (ረዲየላሁ ዐንሁማ) እንደነገረን የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- "በረመዷን የሚደረግ ዑምራ (ምንዳው) ከሐጅ ጋር ይስተካከላል" (ሙስሊም)፡፡
መ. ቁርኣን የወረደበት ወር መሆኑ፡- የህይወታችን መመሪያ በመሆን፣ ማን እንደፈጠረን፡ ለምንስ እንደተፈጠርን፣ እንዴት መኖር እንዳለብንና ወደየትስ እንደምንጓዝ በቂ ምላሽን በመስጠት ማንነታችንን፡ የጠራ መስታወት በመሆን የሚነግረን አምላካዊ ቃል የሆነው ቅዱስ ቁርኣን የወረደው በዚሁ የተከበረ ወር፡ በተከበረች ለሊት፡ በውሳኔዋ ምሽት (ለይለቱል ቀድር) ውስጥ ነው፡፡
"(እንድትጾሙ የተጻፈባችሁ) ያ በርሱ ውስጥ ለሰዎች መሪ ከቅን መንገድና (እውነትን ከውሸት) ከሚለዩም ገላጮች (አንቀጾች) ሲኾን ቁርኣን የተወረደበት የረመዳን ወር ነው…" (ሱረቱል በቀራህ 2፡185)፡፡
"እኛ (ቁርኣኑን) በተባረከች ሌሊት ውስጥ አወረድነው፤ እኛ አስፈሪዎች ነበርንና።" (ሱረቱ-ዱኻን 44፡3)፡፡
"እኛ (ቁርኣኑን) በመወሰኛዪቱ ሌሊት አወረድነው።" (ሱረቱል ቀድር 97፡1)፡፡
ቁርኣን በረመዷን ወር ‹‹ወረደ›› የሚለው ሁለት መልእክትን ያቀፈ ነው፡-
1ኛ፡- ከለውሐል መሕፉዝ (ጥብቅ ሰሌዳ) ወደ ምድራዊ ሰማይ የተከበረው ቤት (በይቱል-ዒዝዛህ) ሲወርድ በጠቅላላ አንድ ጊዜ በዚህ ወር ውስጥ ወርዷል ሲሆን፡-
2ኛ. ከምድራዊው ሰማይ (በይቱል-ዒዝዛህ) ወደ ነቢያችን (ዐለይሂ-ሶላቱ ወስ-ሰላም) ልብ በመልአኩ ጂብሪል (ዐለይሂ-ሰላም) አማካኝነት ሲወርድ በዚሁ ወር ነው መውረድ የጀመረው ማለት ነው፡፡ ወላሁ አዕለም፡፡
ሠ. ለይለቱል-ቀድር (የውሳኔው ለሊት) የምትገኝበት ወር መሆኑ፡- በዚህች አንድ ለሊት የሚሠራ መልካም ሥራ አላህ ዘንድ ተቀባይነት ካገኘ፡ የሥራው ደረጃ ሰውየው አንድ ሺህ ወራት (83 ዓመት ከ4 ወር) ተቀምጦ ከሚሠራቸው መልካም ሥራዎች የበለጠ ይሆናል፡፡ አላህ ይወፍቀን፡፡
"መወሰኛይቱ ሌሊት ምን እንደ ሆነች ምን አሳወቅህ? መወሰኛይቱ ሌሊት ከሺሕ ወር በላጭ ናት።" (ሱረቱል ቀደር 97፡2-3)፡፡
ረ. ቂያሙ ረመዷን (ሶላቱ-ተራዊሕ) የሚገኝበት መሆኑ፡- በረመዷን ወር ሙስሊሞች ተሰባስበው ከዒሻእ ሶላት በኋላ በጀመዓ የሚሰግዱት ሶላት ቂያሙ ረመዷን (ሶላቱ-ተራዊሕ) ይባላል፡፡
አቢ ሁረይራ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንደነገረን የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- "የረመዷንን ወር አምኖና (ምንዳውንም) ለማግኘት ነይቶ (በዒባዳ) የቆመ ሰው፡ ከዚህ በፊት የፈጸማቸው ኃጢአቶቹ በመላ ይማራሉ" (ቡኻሪና ሙስሊም)፡፡
ሰ. ኢዕቲካፍ የሚገኝበት ወር መሆኑ፡- በማንኛውም ቀንና ሰዓት አንድ ሙስሊም የተወሰነ ሰዓታትን በዒባዳ ለማሳለፍ ወስኖ በመስጂድ ውስጥ ኢዕቲካፍ መቀመጥ ይችላል (አል በቀራህ 2፡187)፡፡ በረመዷን ግን ለየት ባለ መልኩ የመጨረሻዎቹን ሙሉ አስር ቀናት በመስጂድ ውስጥ በዒባዳ ለማሳለፍ ራሱን በማገድ (ኢዕቲካፍ) ማድረግ ይቻላል፡፡
እናታችን ዓኢሻህ (ረዲየላሁ ዐንሃ) እንዲህ አለች፡- "የአላህ ነቢይ (ዐለይሂ-ሶላቱ ወስ-ሰላም) የረመዷንን የመጨረሻ አስርት ቀናት እስኪሞቱ ድረስ ሁሌም ኢዕቲካፍ ያደርጉ ነበር፡፡ ከሳቸውም ሞት በኋላ ሚስቶቻቸው ኢዕቲካፍ ያደርጉ ነበር" (ቡኻሪይ)፡፡
ሸ. የቸርነትና የለጋስነት ወር መሆኑ፡- ቸር መሆን በማንኛውም ቀንና በማንኛው
በአቡ ሀይደር
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው
ክብርና ምስጋና ለዓለማቱ ጌታ ለአላህ የተገባ ይሁን፡፡(አል-ፋቲሓ 2) የአላህ ሰላምና ውዳሴ የሰው ዘር ታላቅ መሪ ለሆኑት ለነቢዩ ሙሐመድ (አል-አሕዛብ 56) ለመላው የአላህ መልክተኞች (አል-ሷፍፋት 181) የሐቅንም መንገድ በተከተለ ሁሉ ላይ ይሁን (ጣሀ 47)፡፡
ታላቁና ተወዳጁ ነቢያችን (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ሶሐቦቻቸውን የረመዷንን መቃረብ አስመልክቶ የእንኳን አደረሳችሁ ብስራትን ሲገልጹ እንዲህ ይሏቸው ነበር፡- "የተባረከ ወር የሆነው ረመዷን መጣላችሁ!፡፡ አላህ ጾሙን በናንተ ላይ ግዳጅ አድርጓል፡፡ በዚህ ወር የሰማይ ደጃፎች ይከፈታሉ፡፡ የጀሀነም ደጃፎች ይዘጋሉ፡፡ አመጠኛ ሸይጣናት ይታሰራሉ፡፡ አላህ ከአንድ ሺህ ወር (ስራ) የምትበልጥ የሆነች አንድ ለሊት አለችው፡፡ የዚህን ወር መልካም ነገር የተነፈገ ሰው በርግጥም ከብዙ መልካም ነገራት የተነፈገ ነው፡፡" (አሕመድ 7148፣ ነሳኢይ 2106)፡፡
ይህ የነቢያችን (ዐለይሂ-ሶላቱ ወስ-ሰላም) ብስራት ዋና አላማው ሶሐባዎች (ረዲየላሁ ዐንሁም) ከወዲሁ ይህንን የተከበረ ወር ለመቀበል መንፈሳዊ ዝግጅት እንዲያደርጉ ማነሳሳት ነው፡፡ እኛስ ምን ያህል ተዘጋጅተናል? ለዛሬ መግቢያ እንዲሆነን ስለ ረመዷን ፈዷኢል (በረከቶች) የተወሰነ ነገር እንነጋገር፡፡
1. የረመዷን ወር ክብር፡-
የረመዷን ወር በኢስላማዊው የወር አቆጣጠር መሰረት፡ ዘጠነኛ ወር ላይ የሚገኝ ነው፡፡ ይህ ወር ከተቀሩት 11ዱ ወራቶች ለየት የሚያደርገው የራሱ የሆኑ መለያዎች አሉት፡፡ ከነዚህም መለያዎቹ መካከል፡-
ሀ. የጀነት በሮች የሚከፈቱበት ወር መሆኑ፡- የመልካም ስራ መንገዶችና የጥመት ጎዳናዎች በአስራ ሁለቱም ወራት (ሙሉ ዓመት) ለፈላጊዎችና ለሰሪዎች ክፍት ነው፡፡ የአላህ ባሮች ከረመዷን በፊት፣ በረመዷን ውስጥና ከረመዷን በኋላ ባሉት ወራቶች ላይ ወደ ጌታቸው አላህ የሚያቃርባቸውን መልካም ሥራ ከመሥራት አይቦዝኑም፡፡ የሸይጧን ሠራዊቶች ደግሞ (ተውፊቁን ካላገኙ) ከአላህ የሚያርቃቸውን የጥፋት መስመሮች ከመከተልና ክፋትን ከመፈጸም ወደኋላ አይሉም፡፡ የረመዷን ወር የሚለየው ግን ጀነት ለፈላጊዎቿ ተሸሞንሙና ደጃፎቿ ወለል ብለው ተከፍተው ሲታዩ፡ የጀሀነም በሮች ደግሞ የሚከረቸሙ መሆናቸው ነው፡፡
አቢ ሁረይራ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንደነገረን የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- "የረመዷን የመጀመሪው ለሊት ላይ አመጸኛ ሰይጣናት ይታሰራሉ፣ የእሳት በሮች አንድም ሳይቀር ይከረቸማሉ፣ የጀነት በሮች አንድም ሳይቀር ይከፈታሉ፣ በያንዳንዱ ለሊትም አንድ ተጣሪ እንዲህ በማለት ይጣራል፡- ‹‹መልካም ፈላጊ የሆንክ ሆይ! ፊትህን (ወደ መልካም ተግባር) አዙር፡፡ መጥፎን ፈላጊ የሆንከው ሆይ! (የምትሰራውን ክፋት) ቀንስ(አቁም)፡፡ በያንዳንዱ ለሊትም አላህ ከእሳት ነጻ የሚያደርጋቸው ባሮች አሉት" (አሕመድ 18438)፡፡
ለ. የኃጢአት ማስተሰረያ (ማጥፊያ) መሆኑ፡- በማንኛውም ወቅት የሚሰራ መልካም ስራና ወደ አላህ የሚደረግ የንሰሀ ተውበት ኃጢአትን ያጠፋል (ሁድ 114፣ አዝ-ዙመር 53)፡፡ የረመዷን ወር ደግሞ በአግባቡ ከተጾመ፡ ቀጣዩ አመት ረመዷን እስኪመጣ ድረስ በመሀከሉ የተፈጸሙ ጥቃቅን ኃጢአቶችን በመላ ያጠፋል፡፡ ትላልቅ ኃጢአቶች (ከባኢረ-ዙኑብ) የግድ ባለቤቱ ከነሱ ተውበት ሊያደርግ ያስፈልጋቸዋልና፡፡
አቢ ሁረይራ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንደነገረን የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- "አምስት ወቅት ሶላቶችን መስገድ፣ ጁሙዓ ተሰግዶ ቀጣዩ ሳምንት ጁሙዓህ እስኪመጣ፣ ረመዷን ተጹሞ ቀጣዩ ረመዷን እስኪመጣ ድረስ ሰውየው ትላልቅ ኃጢአትን እስከተጠነቀቀ ድረስ በመሀከላቸው ያለውን ትናንሽ ኃጢአት ያስሰርዛሉ" (ሙስሊም)፡፡
ሐ. የዑምራህ ደረጃህ ከፍ ማለቱ፡- ከሐጅ ስርዓት ውጪ ዑምራን ብቻ መፈጸም አጅር የሚያስገኝ የሱና (ሙስተሐብ) ተግባር ነው፡፡ በረመዷን የሚፈጸም ከሆነ ግን አጅሩ ከፍ ብሎ በማደግ የሐጅን ምንዳ ያህል ይደርሳል፡፡
ዐብደላህ ኢብኑ-ዐባስ (ረዲየላሁ ዐንሁማ) እንደነገረን የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- "በረመዷን የሚደረግ ዑምራ (ምንዳው) ከሐጅ ጋር ይስተካከላል" (ሙስሊም)፡፡
መ. ቁርኣን የወረደበት ወር መሆኑ፡- የህይወታችን መመሪያ በመሆን፣ ማን እንደፈጠረን፡ ለምንስ እንደተፈጠርን፣ እንዴት መኖር እንዳለብንና ወደየትስ እንደምንጓዝ በቂ ምላሽን በመስጠት ማንነታችንን፡ የጠራ መስታወት በመሆን የሚነግረን አምላካዊ ቃል የሆነው ቅዱስ ቁርኣን የወረደው በዚሁ የተከበረ ወር፡ በተከበረች ለሊት፡ በውሳኔዋ ምሽት (ለይለቱል ቀድር) ውስጥ ነው፡፡
"(እንድትጾሙ የተጻፈባችሁ) ያ በርሱ ውስጥ ለሰዎች መሪ ከቅን መንገድና (እውነትን ከውሸት) ከሚለዩም ገላጮች (አንቀጾች) ሲኾን ቁርኣን የተወረደበት የረመዳን ወር ነው…" (ሱረቱል በቀራህ 2፡185)፡፡
"እኛ (ቁርኣኑን) በተባረከች ሌሊት ውስጥ አወረድነው፤ እኛ አስፈሪዎች ነበርንና።" (ሱረቱ-ዱኻን 44፡3)፡፡
"እኛ (ቁርኣኑን) በመወሰኛዪቱ ሌሊት አወረድነው።" (ሱረቱል ቀድር 97፡1)፡፡
ቁርኣን በረመዷን ወር ‹‹ወረደ›› የሚለው ሁለት መልእክትን ያቀፈ ነው፡-
1ኛ፡- ከለውሐል መሕፉዝ (ጥብቅ ሰሌዳ) ወደ ምድራዊ ሰማይ የተከበረው ቤት (በይቱል-ዒዝዛህ) ሲወርድ በጠቅላላ አንድ ጊዜ በዚህ ወር ውስጥ ወርዷል ሲሆን፡-
2ኛ. ከምድራዊው ሰማይ (በይቱል-ዒዝዛህ) ወደ ነቢያችን (ዐለይሂ-ሶላቱ ወስ-ሰላም) ልብ በመልአኩ ጂብሪል (ዐለይሂ-ሰላም) አማካኝነት ሲወርድ በዚሁ ወር ነው መውረድ የጀመረው ማለት ነው፡፡ ወላሁ አዕለም፡፡
ሠ. ለይለቱል-ቀድር (የውሳኔው ለሊት) የምትገኝበት ወር መሆኑ፡- በዚህች አንድ ለሊት የሚሠራ መልካም ሥራ አላህ ዘንድ ተቀባይነት ካገኘ፡ የሥራው ደረጃ ሰውየው አንድ ሺህ ወራት (83 ዓመት ከ4 ወር) ተቀምጦ ከሚሠራቸው መልካም ሥራዎች የበለጠ ይሆናል፡፡ አላህ ይወፍቀን፡፡
"መወሰኛይቱ ሌሊት ምን እንደ ሆነች ምን አሳወቅህ? መወሰኛይቱ ሌሊት ከሺሕ ወር በላጭ ናት።" (ሱረቱል ቀደር 97፡2-3)፡፡
ረ. ቂያሙ ረመዷን (ሶላቱ-ተራዊሕ) የሚገኝበት መሆኑ፡- በረመዷን ወር ሙስሊሞች ተሰባስበው ከዒሻእ ሶላት በኋላ በጀመዓ የሚሰግዱት ሶላት ቂያሙ ረመዷን (ሶላቱ-ተራዊሕ) ይባላል፡፡
አቢ ሁረይራ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንደነገረን የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- "የረመዷንን ወር አምኖና (ምንዳውንም) ለማግኘት ነይቶ (በዒባዳ) የቆመ ሰው፡ ከዚህ በፊት የፈጸማቸው ኃጢአቶቹ በመላ ይማራሉ" (ቡኻሪና ሙስሊም)፡፡
ሰ. ኢዕቲካፍ የሚገኝበት ወር መሆኑ፡- በማንኛውም ቀንና ሰዓት አንድ ሙስሊም የተወሰነ ሰዓታትን በዒባዳ ለማሳለፍ ወስኖ በመስጂድ ውስጥ ኢዕቲካፍ መቀመጥ ይችላል (አል በቀራህ 2፡187)፡፡ በረመዷን ግን ለየት ባለ መልኩ የመጨረሻዎቹን ሙሉ አስር ቀናት በመስጂድ ውስጥ በዒባዳ ለማሳለፍ ራሱን በማገድ (ኢዕቲካፍ) ማድረግ ይቻላል፡፡
እናታችን ዓኢሻህ (ረዲየላሁ ዐንሃ) እንዲህ አለች፡- "የአላህ ነቢይ (ዐለይሂ-ሶላቱ ወስ-ሰላም) የረመዷንን የመጨረሻ አስርት ቀናት እስኪሞቱ ድረስ ሁሌም ኢዕቲካፍ ያደርጉ ነበር፡፡ ከሳቸውም ሞት በኋላ ሚስቶቻቸው ኢዕቲካፍ ያደርጉ ነበር" (ቡኻሪይ)፡፡
ሸ. የቸርነትና የለጋስነት ወር መሆኑ፡- ቸር መሆን በማንኛውም ቀንና በማንኛው
ም ሰዓት የተወደደ መልካም ተግባር ነው፡፡ በተለይ ደግሞ በረመዷን!
ዐብደላህ ኢብኑ-ዐባስ (ረዲየላሁ ዐንሁማ) እንዲህ ይላል፡- "የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ከሰዎች ሁሉ በላይ ቸርና ለጋስ ነበሩ፡፡ በተለይም እጅግ ቸርና ለጋስ ይሆኑ የነበረው በረመዷን ጅብሪል በሚገናኛቸው ወቅት ነበር፡፡ ጅብሪል (ዐለይሂ-ሰላም) በየለሊቱ እየመጣ ቁርኣንን ይጠናኑ ነበር፡፡ የሳቸው መልካም ነገር ላይ የነበራቸው ቸርነትም ከተላከ ነፋስ የፈጠነ ነበር" (ቡኻሪይ)፡፡
ቀ. አመጠኛ ሰይጣናት የሚታሰሩበት መሆኑ፡- ሸይጧን በረመዷን ወር የሚታሰር መሆኑን ለማመን ከሐዲሡም ውጪ በተግባር የሚታይ እውነታ ነው፡፡ ቢያንስ ሁለት ምክንያቶችን ማቅረብ ይቻላል፡-
1ኛ. የአላህ ቤቶች ሁሉ በሰጋጅ ይጨናነቃሉ፡፡ መስጂዶች ይሞላሉ፡፡ ሁሉም ሙስሊም፡- ይህ ሁሉ ሰው ከየት መጣ! በማለት ይገረማል፡፡ ኢስላምን የሚቀበሉ አዲስ ገቢዎች ጥቂት ቢሆኑም፡ አብዝኃኛው ግን በቤቱና በስራ ቦታው ይሰግድ የነበረ፡ እንዲሁም ከሶላት ጋር ትውውቅ ያልነበረው ሰው ነው፡፡ ታዲያ ይህ ሁሉ ሕዝብ ከረመዷን በፊት በአላህ ቤት ለመታየት ያልገራለት፡ አሁን በረመዷን ግን መምጣቱ፡ ይፈታተነው የነበረው ሸይጧን መታሰሩን አያመላክትምን?
2ኛ. ዒባዳን ለመተግበር ይቀላል፡፡ ከረመዷን ውጪ ተዘግቶ በክብር ስፍራ የተቀመጠው ቁርኣን በረመዷን አንባቢው ይበዛል፡፡ በፊት 1ብር ለመለገስ የሰሰቱ ልቦች፡ በረመዷን ለማስፈጠርና ለሶደቃ ግን ይቻኮላሉ፡፡ ይህን ኸይር ስራ አሁን ለመስራት ከገራልዎት፡ ከአላህ ተውፊቅ በኋላ የሸይጧን መታሰርን አይጠቁምምን?
"የተባረከ ወር የሆነው ረመዷን መጣላችሁ!፡፡ አላህ ጾሙን በናንተ ላይ ግዳጅ አድርጓል፡፡ በዚህ ወር የሰማይ ደጃፎች ይከፈታሉ፡፡ የጀሀነም ደጃፎች ይዘጋሉ፡፡ አመጠኛ ሸይጣናት ይታሰራሉ…" (አሕመድ 7148፣ ነሳኢይ 2106)፡፡
Click and Like ➤➤ https://www.facebook.com/Ustaz.Abuhyder
Join us ➤➤ t.me/abuhyder
ዐብደላህ ኢብኑ-ዐባስ (ረዲየላሁ ዐንሁማ) እንዲህ ይላል፡- "የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ከሰዎች ሁሉ በላይ ቸርና ለጋስ ነበሩ፡፡ በተለይም እጅግ ቸርና ለጋስ ይሆኑ የነበረው በረመዷን ጅብሪል በሚገናኛቸው ወቅት ነበር፡፡ ጅብሪል (ዐለይሂ-ሰላም) በየለሊቱ እየመጣ ቁርኣንን ይጠናኑ ነበር፡፡ የሳቸው መልካም ነገር ላይ የነበራቸው ቸርነትም ከተላከ ነፋስ የፈጠነ ነበር" (ቡኻሪይ)፡፡
ቀ. አመጠኛ ሰይጣናት የሚታሰሩበት መሆኑ፡- ሸይጧን በረመዷን ወር የሚታሰር መሆኑን ለማመን ከሐዲሡም ውጪ በተግባር የሚታይ እውነታ ነው፡፡ ቢያንስ ሁለት ምክንያቶችን ማቅረብ ይቻላል፡-
1ኛ. የአላህ ቤቶች ሁሉ በሰጋጅ ይጨናነቃሉ፡፡ መስጂዶች ይሞላሉ፡፡ ሁሉም ሙስሊም፡- ይህ ሁሉ ሰው ከየት መጣ! በማለት ይገረማል፡፡ ኢስላምን የሚቀበሉ አዲስ ገቢዎች ጥቂት ቢሆኑም፡ አብዝኃኛው ግን በቤቱና በስራ ቦታው ይሰግድ የነበረ፡ እንዲሁም ከሶላት ጋር ትውውቅ ያልነበረው ሰው ነው፡፡ ታዲያ ይህ ሁሉ ሕዝብ ከረመዷን በፊት በአላህ ቤት ለመታየት ያልገራለት፡ አሁን በረመዷን ግን መምጣቱ፡ ይፈታተነው የነበረው ሸይጧን መታሰሩን አያመላክትምን?
2ኛ. ዒባዳን ለመተግበር ይቀላል፡፡ ከረመዷን ውጪ ተዘግቶ በክብር ስፍራ የተቀመጠው ቁርኣን በረመዷን አንባቢው ይበዛል፡፡ በፊት 1ብር ለመለገስ የሰሰቱ ልቦች፡ በረመዷን ለማስፈጠርና ለሶደቃ ግን ይቻኮላሉ፡፡ ይህን ኸይር ስራ አሁን ለመስራት ከገራልዎት፡ ከአላህ ተውፊቅ በኋላ የሸይጧን መታሰርን አይጠቁምምን?
"የተባረከ ወር የሆነው ረመዷን መጣላችሁ!፡፡ አላህ ጾሙን በናንተ ላይ ግዳጅ አድርጓል፡፡ በዚህ ወር የሰማይ ደጃፎች ይከፈታሉ፡፡ የጀሀነም ደጃፎች ይዘጋሉ፡፡ አመጠኛ ሸይጣናት ይታሰራሉ…" (አሕመድ 7148፣ ነሳኢይ 2106)፡፡
Click and Like ➤➤ https://www.facebook.com/Ustaz.Abuhyder
Join us ➤➤ t.me/abuhyder
ኡስታዝ ሳዲቅ መሃመድ *(አቡ ሃይደር)* 500 ለሚሆኑ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ አደረጉ፡፡
በሃላባ ዞን በኮሮና ቫይረ ምክኒያት የገቢ አቅማቸው ለተዳከመ እንዲሁም የተለያዩ አቅመ ደካማ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ታላቁ የረመዳን ወር ፆምን በደስታ እንዲያሳልፉ ለማስቻል በሃላባ ቁሊቶ ከተማ ብላቴ ወንዝ አከባቢ በሚገኘው ዋዳ መስጂድ ለ400 የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ማለትም ለአንድ አባወራ 50 ኪሎ ግራም በቆሎ ፥ 20 ኪሎ ግራም ቅንጬ እና 3 ሊትር ዘይት ድጋፍ አድርገዋል፡፡
በተመሳሳይ ዜና ኡስታዝ አቡሃይደር በቄረንሶ ቀበሌ ከሃዲያና እና ከምባታ ዞኖች ለተውጣጡ 100 አቅመ ደካማ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ለእያንዳንዳቸው 50 ኪሎ ግራም በቆሎ ፥ 20 ኪሎ ግራም ቅንጬ እና 3 ሊትር ዘይት ድጋፍ አድርገዋል፡፡
ድጋፉ የተሰበሰበው በሃገር ውስጥና ከሃገር ውጭ ከሚኖሩ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች መሆኑን የተናገሩት ኡስታዝ አቡ ሃይደር ድጋፉ በቅርብ ቀናትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አብራርተዋል፡፡
ምንጭ - የሀላባ ዞን ህዝብ ግንኙነት ቢሮ
በሃላባ ዞን በኮሮና ቫይረ ምክኒያት የገቢ አቅማቸው ለተዳከመ እንዲሁም የተለያዩ አቅመ ደካማ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ታላቁ የረመዳን ወር ፆምን በደስታ እንዲያሳልፉ ለማስቻል በሃላባ ቁሊቶ ከተማ ብላቴ ወንዝ አከባቢ በሚገኘው ዋዳ መስጂድ ለ400 የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ማለትም ለአንድ አባወራ 50 ኪሎ ግራም በቆሎ ፥ 20 ኪሎ ግራም ቅንጬ እና 3 ሊትር ዘይት ድጋፍ አድርገዋል፡፡
በተመሳሳይ ዜና ኡስታዝ አቡሃይደር በቄረንሶ ቀበሌ ከሃዲያና እና ከምባታ ዞኖች ለተውጣጡ 100 አቅመ ደካማ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ለእያንዳንዳቸው 50 ኪሎ ግራም በቆሎ ፥ 20 ኪሎ ግራም ቅንጬ እና 3 ሊትር ዘይት ድጋፍ አድርገዋል፡፡
ድጋፉ የተሰበሰበው በሃገር ውስጥና ከሃገር ውጭ ከሚኖሩ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች መሆኑን የተናገሩት ኡስታዝ አቡ ሃይደር ድጋፉ በቅርብ ቀናትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አብራርተዋል፡፡
ምንጭ - የሀላባ ዞን ህዝብ ግንኙነት ቢሮ
የኡስታዝ አቡ ሀይደር ትምህርቶች ስብስብ
✨ሸህሩ ረመዷን🌙 የፆም አስፈላጊነቱና ጠቀሜታው!ክፍል➋ 🎙 አዘጋጅ⇊ ➤ በኡስታዝ አቡ ሐይደር Mp3 ዳውሎድ ለማድረግ ➤ https://goo.gl/ymmyu2 Join us➤ t.me/abuhyder https://youtu.be/e_tlHgjJkac
Audio
✨ሸህሩ ረመዷን🌙
የረመዷን ፆም ግዳጅነትና መስፈርቶቹ! ክፍል 3
🎙 አዘጋጅ⇊
➤ በኡስታዝ አቡ ሐይደር
Mp3 ዳውሎድ ለማድረግ
➤ https://goo.gl/WhNyck
Join us➤ t.me/abuhyder
https://youtu.be/vaKRZOIPIHs
የረመዷን ፆም ግዳጅነትና መስፈርቶቹ! ክፍል 3
🎙 አዘጋጅ⇊
➤ በኡስታዝ አቡ ሐይደር
Mp3 ዳውሎድ ለማድረግ
➤ https://goo.gl/WhNyck
Join us➤ t.me/abuhyder
https://youtu.be/vaKRZOIPIHs
Audio
✨ሸህሩ ረመዷን🌙
የፆም ማእዘናት እና ተወዳጅ ተግባራቱ ክፍል 4
🎙 አዘጋጅ⇊
➤ በኡስታዝ አቡ ሐይደር
Mp3 ዳውሎድ ለማድረግ
➤ https://goo.gl/pTFC67
Join us➤ t.me/abuhyder
https://youtu.be/A3QlooLHSnE
የፆም ማእዘናት እና ተወዳጅ ተግባራቱ ክፍል 4
🎙 አዘጋጅ⇊
➤ በኡስታዝ አቡ ሐይደር
Mp3 ዳውሎድ ለማድረግ
➤ https://goo.gl/pTFC67
Join us➤ t.me/abuhyder
https://youtu.be/A3QlooLHSnE
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ኡስታዝ ሳዲቅ አቡ ሀይደር ለረመዳን የእንኳን አደረሳቹህ መልዕክት አስተላለፈ እነሆ መልዕክቱን ያድምጡ
ለረመዷን
ሰላቱ-ተራዊሕ "ቂያሙ–ለይል"
በአቡ ሀይደር
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኛ በሆነው፡፡
ምስጋና የዓለማት ጌታ ለሆነው ለአላህ የተገባ ነው፡፡ የአላህ ውዳሴና ሰላም የሰላም አለቃና መምህር ለሆኑት ለነቢዩ ሙሐመድ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ይሁን፡፡ ድልና የበላይነት ሐቅን ለማንገስና ሀሰትን ለማርከስ በደልን አጥፎቶ ፍትህን ለማስፈን ዕውቀታቸውን፣ ንብረታቸውን፣ ጉልበታቸውን፣ ጊዜያቸውንና ህይወታቸውን መስዋእት በማድረግ ለሚታገሉት ይሁን፡፡
ብዙ ጊዜ ወደ መስጂድ በመሄድ ከዒሻ ሱንነቱል-ባዕዲያ ቡኋላ የሚሰገደውን ሶላት (ቂያሙ-ለይል) ከኢማሙ ጋር አንጨርሰውም፤ መሐል ላይ እናቋርጣለን፡፡ ወይም ተራዊሕ ጨርሰን ዊትሩን ለቤት ብለን እንወጣለን፡፡፡ ይህ ተግባር የተከለከለ ባይሆንም አግባብነት የለውም፡፡ ለሊቱን ሙሉ በሶላት እንደቆመ እንዲታሰብለት የሚፈልግ አንድ ሙስሊም ከኢማሙ ጋር ሁሉንም አብሮ መጨረስ አለበት፡፡ በመሐል ያለ-ምንም አስገዳጅ ምክንያት ኳቋረጠ ቃል የተገባለትን አጅር ያጣል፡፡ ሐዲሡ የሚለው እንዲህ ነው፡-
አቢ ዘር (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንደነገረን የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- "ከኢማሙ ጋር እስኪያጠናቅቅ አብሮት የቆመ(የሰገደ) ለሊቱን ሙሉ እንደሰገደ ይጻፍለታል" (ነሳኢይ 1605፣ ቲርሚዚይ 806፣ ኢብኑ ማጀህ 1327)፡፡
በዚህ ምክንያት ሁሉንም ከኢማሙ ጋር ማጠናቀቅ ይገባናል፡፡ አንዳንድ ሰዎች ደግሞ፡- በተጨማሪ ለሊት ላይ ተነስቼ ከሰሑር በፊት መስገድ ስለምፈልግ ነው ዊትሩን የተውኩት ይላሉ፡፡
አላህ ወፍቆት ለይል ላይ በድጋሚ ተነስቶ መስገድ የሚፈልግ ሰውም ተራዊሕን እስከ ዊትሩ ከኢማሙ ጋር አብሮ መስገዱ አይከለክለውም፡፡ ‹‹ከዊትር በኋላ ሶላት የለም!›› ወይም ‹‹የመጨረሻ ሶላታችሁን ዊትር አድሩጉ›› የሚለው ሐዲሥ ክልከላን ሳይሆን አለመስገዱ የተወደደ መሆኑን ለማመላከት የመጣ እንደሆነ የኢስላም ሊቃውንት ያስረዳሉ፡፡ በተጨማሪም የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) አንዳንድ ጊዜ ከዊትር በኋላ ረከዐተይን (ሁለት ረከዓህ) ይሰግዱ እንደነበር መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ ይህም የሚጠቁመው ከዊትር በኋላ ሶላት መስገድ እንደሚቻል ነው፡፡ ስለዚህ ለይልን በድጋሚ ተነስተህ የምትሰግድ ከሆነ ባለ ጥንድ ረከዓህ (ሁለት ሁለት) እያደረግህ ስገድ፡፡ በድጋሚ ግን ዊትር እንዳትሰግድ፡፡ በአንድ ለሊት ሁለት ዊትር የለምና፡፡
ሌላው በተራዊሕ ወቅት በጁዝእ የሚሰገድባቸው መስጂድ ውስጥ ከሆንክ ቁርኣን ወይም ሞባይልህ ውስጥ የጫንከውን ከፍተህ ኢማሙን ከምትከታተል ሞባይልህን አጥፍተህ ቀልብህን ሰብስበህ የኢማምህን ቂርኣት በማዳመጥ መከታተሉ ላንተ በላጭ ነው፡፡ ምክንያቱም፡-
1ኛ) ቀኝ እጅን በግራ ላይ ደርቦ በደረት ላይ አሳርፎ የማስቀመጡ ሱንና አያመልጥህምና፡፡ ቁርኣኑን ወይም ሞባይሉን ከፍተህ የምትከታተል ከሆነ ግን የግድ ቀኝ እጅህ ካረፈበት ቦታ ይነሳል፡፡
2ኛ) አላስፈላጊ እንቅስቃሴዎችን ትቆጥባለህ፡፡ ኢማሙ ጨርሶ ወደ ሩኩዕ ሲወርድ አንተ ግን፡ ሞባይልህን ወደ ኪስ ለመክተት፡ ቁርኣን ከሆነ ደግሞ መሬት ለማስቀመጥ ቦታ ፍለጋ ውስጥ ትገባለህ፡፡ ቁርአንን ደግሞ ከስሩ ምንም ነገር ሳይኖር መሬት ማስቀመጥ አይቻልም፡፡
3ኛ) በሞባይል ቁርኣን እየተከታተልክ ምንም ስልክህ ሳይለንት ቢሆንም ሰው ከደወለልህ ቁርኣኑን ሸፍኖ የደዋዩን ቁጥር ማሳየቱ አይቀርም፡፡ ስልኩን በመዝጋት ስራ ተጠምደህ አንተም አዛ ልትሆን ነው፡፡ ልብህም ከሶላቱ ወጥቶ (ኤጭ ምን አይነቱ ነው!) የሚል ስራ ውስጥ ሊገባ ነው፡፡ ታዲያ የቱ ይሻልሀል?
ሶስቱ ታላላቅ የኢስላም ሊቃውንቶች (ኢብኑ ዑሠይሚን፣ ኢብኑ ባዝ፣ አልባኒ ራሕመቱላሂ ዐለይሂም) በዚህ ጉዳይ ላይ ክልክል ነው ብለው ባያወግዙም በላጩ ግን መተዉ ነው በማለት መክረዋል፡፡
4ኛ) እኔ ከሞባይል ወይንም ዋና ቁርኣን ከፍቼ ካልተከታተልኩ እንቅልፍ ይመጣብኛል፡፡ ነሻጣዬም ይጠፋል፡፡ ድካም ድካም ይሰማኛል፡፡ ቀልቤ ከሶላት ይወጣል፡፡ ስከታተል ግን የበለጠ እጠነክራለሁ ምትሉ ካላችሁ ደግሞ፡- ታላቁ ዓሊም ሸይኽ ኢብኑ ጅብሪን (ረሒመሁላህ) ችግር የለውም መጠቀም ይችላሉ በማለት ፈትዋ ሰጥተዋል፡፡ ራሳችንን የምናውቀው እኛው ነን፡፡ በዚህ ጊዜ ግን ሰው እየደወለ አዛ እንዳያደርገን የሞባይሉን ኔትወርክ ኦፍላይን እናድርገው፡፡ ወይም call setting ውስጥ በመግባት ወደሌላ ቁጥር divert እናድርገው፡፡ ወይም ሲስተሙን ቢዚ አድርጉት፡፡
ደግሞም ‹‹ኢንና አዕጠይና ፣ ለወገብ ጤና›› እያልን በጁዝእ ከሚሰገድባቸው መስጂዶች አንራቅ፡፡ ዛሬ በዚህ ዱንያ ላይ እግሮችህ ለአላህ መቆምን ካበዙ በምትኩ ነጌ በአኼራ በቃጠሎው ቀን መቆሙ ይቀንስላቸዋልና፡፡ አላህ ይወፍቀን፡፡
ለእህቶች፡-
‹‹የአላህን ሴት ባሪያዎች ከአላህ ቤት (መስጂድ) መሄድን አትከልክሏቸው›› የሚለውን ስለ-መብታችሁ የተነገረውን ሐዲሥ ምርኩዝ አድርጋችሁ ከእህቶቻችሁ ጋር በኅብረት ለመስገድ ወደ አላህ ቤት ካቀናችሁ ቀጥሎ ያሉትን ነገራት አደራ ተጠንቀቁ፡-
1) ሒጃባችሁን ጠብቁ፡- ከቤት ስትወጡ ብቻ ሳይሆን መስጂድ ገብታችሁ እስክትሰግዱ ሰግዳችሁም ወደ ቤት እስክትመለሱ ድረስ ሒጃባችሁ ጥብቅ ይሁን፡፡ ወንዶችን የሚፈትን አይነት አለባበስ ለብሳችሁ አትውጡ፡፡ አላህን ፍሩ፡፡ ደግሞም ሽቶ ተቀብታችሁ አትውጡ፡፡ ለማነው የምትዋቡት? ውበታችሁና መዓዛችሁ ለባለቤታችሁ እና ለግላችሁ እንጂ ውጪ ላለ ሰው መሆን ስለሌለበት ከቤት ስትወጡ ተጠንቀቁ፡፡
2) ሰልፍ ማስተካከል፡- አንደኛው ችግራችሁ ነው ይባላል፡፡ (ባለቤቴ እንደነገረቺኝ)፡፡ ሶላት ላይ ተራርቃችሁ ሳይሆን ተጠጋግታችሁ እግር ለእግር ተነካክታችሁ ስገዱ፡፡ በመሐል ሸይጣን እንዳይገባባችሁ ክፍተት አትፍጠሩ፡፡ ምነው በረመዷን ታስሮ አይደል? ካላችሁም አዎ! አመጸኞቹ ታስረዋል፡፡ ሽሜዎቹ እና ደካሞቹ ግን ዕድላቸውን ይሞክራሉና ክፍተት አትፍጠሩላቸው፡፡ መስጂዱ ስላልሞላ በሚል ተበታትናችሁም አትስገዱ፡፡
3) ህጻናትን በተቻለ መጠን መስጂድ አታምጧቸው፡፡ እናንተም እህቶቻችሁም በነሱ ሰበብ አዛ እንዳትሆኑ፡፡ ማምጣቱ ግድ ከሆነና ሰውን አዛ የሚያደርጉ ከሆነም ተገንጥላችሁ ስገዱ፡፡
4) የመጣችሁበት ዓላማ ዒባዳ እስከሆነ ድረስ ሙሉ ተራዊሕን ከኢማሙ ጋር ስገዱ፡፡ አንዳንዴ ከሁለቱ ኢማሞች በድምጹ ማማር የምንወደው ኢማም ከግማሽ በኋላ ከሆነ እሱ እስኪመጣ ድረስ በማለት ገለል ብለን ቁርኣን መቅራት ወይም እንተኛና እሱ ሲጀምር ቀስቅሱኝ እንላለን፡፡ ይህ ስህተት ነው፡፡ የለሊቱን ቂያም ሙሉ አጅር ከፈለግን ሁሉንም እንስገድ፡፡ ወላሁ አዕለም፡፡
አላህ ሆይ! በረመዳን ውስጥ ካለው ኸይር ነገር የምንጠቀም አድርገን! አሚን!
Click and Like ➤➤ https://www.facebook.com/Ustaz.Abuhyder
Join us➤ t.me/abuhyder
ሰላቱ-ተራዊሕ "ቂያሙ–ለይል"
በአቡ ሀይደር
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኛ በሆነው፡፡
ምስጋና የዓለማት ጌታ ለሆነው ለአላህ የተገባ ነው፡፡ የአላህ ውዳሴና ሰላም የሰላም አለቃና መምህር ለሆኑት ለነቢዩ ሙሐመድ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ይሁን፡፡ ድልና የበላይነት ሐቅን ለማንገስና ሀሰትን ለማርከስ በደልን አጥፎቶ ፍትህን ለማስፈን ዕውቀታቸውን፣ ንብረታቸውን፣ ጉልበታቸውን፣ ጊዜያቸውንና ህይወታቸውን መስዋእት በማድረግ ለሚታገሉት ይሁን፡፡
ብዙ ጊዜ ወደ መስጂድ በመሄድ ከዒሻ ሱንነቱል-ባዕዲያ ቡኋላ የሚሰገደውን ሶላት (ቂያሙ-ለይል) ከኢማሙ ጋር አንጨርሰውም፤ መሐል ላይ እናቋርጣለን፡፡ ወይም ተራዊሕ ጨርሰን ዊትሩን ለቤት ብለን እንወጣለን፡፡፡ ይህ ተግባር የተከለከለ ባይሆንም አግባብነት የለውም፡፡ ለሊቱን ሙሉ በሶላት እንደቆመ እንዲታሰብለት የሚፈልግ አንድ ሙስሊም ከኢማሙ ጋር ሁሉንም አብሮ መጨረስ አለበት፡፡ በመሐል ያለ-ምንም አስገዳጅ ምክንያት ኳቋረጠ ቃል የተገባለትን አጅር ያጣል፡፡ ሐዲሡ የሚለው እንዲህ ነው፡-
አቢ ዘር (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንደነገረን የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- "ከኢማሙ ጋር እስኪያጠናቅቅ አብሮት የቆመ(የሰገደ) ለሊቱን ሙሉ እንደሰገደ ይጻፍለታል" (ነሳኢይ 1605፣ ቲርሚዚይ 806፣ ኢብኑ ማጀህ 1327)፡፡
በዚህ ምክንያት ሁሉንም ከኢማሙ ጋር ማጠናቀቅ ይገባናል፡፡ አንዳንድ ሰዎች ደግሞ፡- በተጨማሪ ለሊት ላይ ተነስቼ ከሰሑር በፊት መስገድ ስለምፈልግ ነው ዊትሩን የተውኩት ይላሉ፡፡
አላህ ወፍቆት ለይል ላይ በድጋሚ ተነስቶ መስገድ የሚፈልግ ሰውም ተራዊሕን እስከ ዊትሩ ከኢማሙ ጋር አብሮ መስገዱ አይከለክለውም፡፡ ‹‹ከዊትር በኋላ ሶላት የለም!›› ወይም ‹‹የመጨረሻ ሶላታችሁን ዊትር አድሩጉ›› የሚለው ሐዲሥ ክልከላን ሳይሆን አለመስገዱ የተወደደ መሆኑን ለማመላከት የመጣ እንደሆነ የኢስላም ሊቃውንት ያስረዳሉ፡፡ በተጨማሪም የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) አንዳንድ ጊዜ ከዊትር በኋላ ረከዐተይን (ሁለት ረከዓህ) ይሰግዱ እንደነበር መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ ይህም የሚጠቁመው ከዊትር በኋላ ሶላት መስገድ እንደሚቻል ነው፡፡ ስለዚህ ለይልን በድጋሚ ተነስተህ የምትሰግድ ከሆነ ባለ ጥንድ ረከዓህ (ሁለት ሁለት) እያደረግህ ስገድ፡፡ በድጋሚ ግን ዊትር እንዳትሰግድ፡፡ በአንድ ለሊት ሁለት ዊትር የለምና፡፡
ሌላው በተራዊሕ ወቅት በጁዝእ የሚሰገድባቸው መስጂድ ውስጥ ከሆንክ ቁርኣን ወይም ሞባይልህ ውስጥ የጫንከውን ከፍተህ ኢማሙን ከምትከታተል ሞባይልህን አጥፍተህ ቀልብህን ሰብስበህ የኢማምህን ቂርኣት በማዳመጥ መከታተሉ ላንተ በላጭ ነው፡፡ ምክንያቱም፡-
1ኛ) ቀኝ እጅን በግራ ላይ ደርቦ በደረት ላይ አሳርፎ የማስቀመጡ ሱንና አያመልጥህምና፡፡ ቁርኣኑን ወይም ሞባይሉን ከፍተህ የምትከታተል ከሆነ ግን የግድ ቀኝ እጅህ ካረፈበት ቦታ ይነሳል፡፡
2ኛ) አላስፈላጊ እንቅስቃሴዎችን ትቆጥባለህ፡፡ ኢማሙ ጨርሶ ወደ ሩኩዕ ሲወርድ አንተ ግን፡ ሞባይልህን ወደ ኪስ ለመክተት፡ ቁርኣን ከሆነ ደግሞ መሬት ለማስቀመጥ ቦታ ፍለጋ ውስጥ ትገባለህ፡፡ ቁርአንን ደግሞ ከስሩ ምንም ነገር ሳይኖር መሬት ማስቀመጥ አይቻልም፡፡
3ኛ) በሞባይል ቁርኣን እየተከታተልክ ምንም ስልክህ ሳይለንት ቢሆንም ሰው ከደወለልህ ቁርኣኑን ሸፍኖ የደዋዩን ቁጥር ማሳየቱ አይቀርም፡፡ ስልኩን በመዝጋት ስራ ተጠምደህ አንተም አዛ ልትሆን ነው፡፡ ልብህም ከሶላቱ ወጥቶ (ኤጭ ምን አይነቱ ነው!) የሚል ስራ ውስጥ ሊገባ ነው፡፡ ታዲያ የቱ ይሻልሀል?
ሶስቱ ታላላቅ የኢስላም ሊቃውንቶች (ኢብኑ ዑሠይሚን፣ ኢብኑ ባዝ፣ አልባኒ ራሕመቱላሂ ዐለይሂም) በዚህ ጉዳይ ላይ ክልክል ነው ብለው ባያወግዙም በላጩ ግን መተዉ ነው በማለት መክረዋል፡፡
4ኛ) እኔ ከሞባይል ወይንም ዋና ቁርኣን ከፍቼ ካልተከታተልኩ እንቅልፍ ይመጣብኛል፡፡ ነሻጣዬም ይጠፋል፡፡ ድካም ድካም ይሰማኛል፡፡ ቀልቤ ከሶላት ይወጣል፡፡ ስከታተል ግን የበለጠ እጠነክራለሁ ምትሉ ካላችሁ ደግሞ፡- ታላቁ ዓሊም ሸይኽ ኢብኑ ጅብሪን (ረሒመሁላህ) ችግር የለውም መጠቀም ይችላሉ በማለት ፈትዋ ሰጥተዋል፡፡ ራሳችንን የምናውቀው እኛው ነን፡፡ በዚህ ጊዜ ግን ሰው እየደወለ አዛ እንዳያደርገን የሞባይሉን ኔትወርክ ኦፍላይን እናድርገው፡፡ ወይም call setting ውስጥ በመግባት ወደሌላ ቁጥር divert እናድርገው፡፡ ወይም ሲስተሙን ቢዚ አድርጉት፡፡
ደግሞም ‹‹ኢንና አዕጠይና ፣ ለወገብ ጤና›› እያልን በጁዝእ ከሚሰገድባቸው መስጂዶች አንራቅ፡፡ ዛሬ በዚህ ዱንያ ላይ እግሮችህ ለአላህ መቆምን ካበዙ በምትኩ ነጌ በአኼራ በቃጠሎው ቀን መቆሙ ይቀንስላቸዋልና፡፡ አላህ ይወፍቀን፡፡
ለእህቶች፡-
‹‹የአላህን ሴት ባሪያዎች ከአላህ ቤት (መስጂድ) መሄድን አትከልክሏቸው›› የሚለውን ስለ-መብታችሁ የተነገረውን ሐዲሥ ምርኩዝ አድርጋችሁ ከእህቶቻችሁ ጋር በኅብረት ለመስገድ ወደ አላህ ቤት ካቀናችሁ ቀጥሎ ያሉትን ነገራት አደራ ተጠንቀቁ፡-
1) ሒጃባችሁን ጠብቁ፡- ከቤት ስትወጡ ብቻ ሳይሆን መስጂድ ገብታችሁ እስክትሰግዱ ሰግዳችሁም ወደ ቤት እስክትመለሱ ድረስ ሒጃባችሁ ጥብቅ ይሁን፡፡ ወንዶችን የሚፈትን አይነት አለባበስ ለብሳችሁ አትውጡ፡፡ አላህን ፍሩ፡፡ ደግሞም ሽቶ ተቀብታችሁ አትውጡ፡፡ ለማነው የምትዋቡት? ውበታችሁና መዓዛችሁ ለባለቤታችሁ እና ለግላችሁ እንጂ ውጪ ላለ ሰው መሆን ስለሌለበት ከቤት ስትወጡ ተጠንቀቁ፡፡
2) ሰልፍ ማስተካከል፡- አንደኛው ችግራችሁ ነው ይባላል፡፡ (ባለቤቴ እንደነገረቺኝ)፡፡ ሶላት ላይ ተራርቃችሁ ሳይሆን ተጠጋግታችሁ እግር ለእግር ተነካክታችሁ ስገዱ፡፡ በመሐል ሸይጣን እንዳይገባባችሁ ክፍተት አትፍጠሩ፡፡ ምነው በረመዷን ታስሮ አይደል? ካላችሁም አዎ! አመጸኞቹ ታስረዋል፡፡ ሽሜዎቹ እና ደካሞቹ ግን ዕድላቸውን ይሞክራሉና ክፍተት አትፍጠሩላቸው፡፡ መስጂዱ ስላልሞላ በሚል ተበታትናችሁም አትስገዱ፡፡
3) ህጻናትን በተቻለ መጠን መስጂድ አታምጧቸው፡፡ እናንተም እህቶቻችሁም በነሱ ሰበብ አዛ እንዳትሆኑ፡፡ ማምጣቱ ግድ ከሆነና ሰውን አዛ የሚያደርጉ ከሆነም ተገንጥላችሁ ስገዱ፡፡
4) የመጣችሁበት ዓላማ ዒባዳ እስከሆነ ድረስ ሙሉ ተራዊሕን ከኢማሙ ጋር ስገዱ፡፡ አንዳንዴ ከሁለቱ ኢማሞች በድምጹ ማማር የምንወደው ኢማም ከግማሽ በኋላ ከሆነ እሱ እስኪመጣ ድረስ በማለት ገለል ብለን ቁርኣን መቅራት ወይም እንተኛና እሱ ሲጀምር ቀስቅሱኝ እንላለን፡፡ ይህ ስህተት ነው፡፡ የለሊቱን ቂያም ሙሉ አጅር ከፈለግን ሁሉንም እንስገድ፡፡ ወላሁ አዕለም፡፡
አላህ ሆይ! በረመዳን ውስጥ ካለው ኸይር ነገር የምንጠቀም አድርገን! አሚን!
Click and Like ➤➤ https://www.facebook.com/Ustaz.Abuhyder
Join us➤ t.me/abuhyder
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
شَهْرُ رَمَضَانَ الَّذِي أُنزِلَ فِيهِ الْقُرْآنُ هُدًى لِّلنَّاسِ 🕌 🖤🌙
القارئ شريف مصطفى 🌹
القارئ شريف مصطفى 🌹
ለረመን ሰይጣናት ከታሰሩ ሰዎች ለምን አልሰለሙም?
በአቡ ሀይደር
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው
ክብርና ምስጋና ለዓለማቱ ጌታ ለአላህ የተገባ ይሁን (አል-ፋቲሓ 2)፡፡ የአላህ ሰላምና ውዳሴ የሰው ዘር ታላቅ መሪ ለሆኑት ለነቢዩ ሙሐመድ (አል-አሕዛብ 56) ለመላው የአላህ መልክተኞች (አል-ሷፍፋት 181) የሐቅንም መንገድ በተከተለ ሁሉ ላይ ይሁን (ጣሀ 47)፡፡
አንዱ ክርስቲያን ነው ይህን ጥያቄ ያቀረበው፡፡ እናንተ ሙስሊሞች እንደምትሉት በረመዷን ወር ሰይጣናት የሚታሰሩ ከሆነ፡ አሁን የሚያሳስተን የለምና፡ ለምን እኛ ክርስቲያኖች ሙስሊም አልሆንም ታዲያ? የሚል፡፡ ለዚህ ጥያቄም መጠነኛ ምላሹ እንዲህ ይቀርባል፡-
ጥቅላዊ ምላሽ፡-
ወገናችን! ሰዎችን ኹሉ ያከፈረው (ከሀዲ ያደረገው) ሸይጧን ነው ማን አለህ ቀድሞውኑ? እንደዛ ተብሎ ቢሆን ኖሮ፡ በታሰረ ጊዜ የከፈሩት በጠቅላላ ለምን ተመልሰው አልሰለሙም? የሚል ጤናማ ጥያቄ ማቅረቡ ተገቢ ይኾን ነበር፡፡ ግን ባልተባለ ነገር ላይ ቆሞ ጥያቄ ማቅረብ ትልቅ የአስተሳሰብ መዛባት ነው፡፡ ሸይጧን ለሰዎች ክህደትና አመጽ ጎትጓች በመሆኑ፡ የጥፋት ሰበብ ተደርጎ ይወሰዳል እንጂ፡ በሰዎች ልብ ላይ ተሹሞ፡ በልባቸውና በእምነት መካከል ጣልቃ በመግባት እንዳያምኑ ይጋርዳል አልተባለም፡፡ ይህን የማድረግ ስልጣንም አልተሰጠውም፡፡ እሱ ወደ ኃጢአት ይጣራል እንጂ፡ ኃጢአቱን የሚፈጽመው ሰውየው እራሱ ነው፡፡ ስለሆነም ስለ ሥራው ይጠየቃል፡፡ አንተም በሸይጧን መታሰር ሰበብ እኔ ለምን አልሰለምኩም ታዲያ? ላልከው፡ እውን ለመስለምና አላህን ብቻ ለማምለክ እራስህን አዘጋጅተህ ነበርን? ከሸይጧን የከፋውን ጠላትህንስ (ነፍሲያህን) መከተል አቁመህ ነበርን? በማለት ልንጠይቅህ እንወዳለን፡፡ እስኪ አንተም ውስጥህን መርምረውና የዚያኔ መልሱን ታገኘዋለህ፡፡
ዝርዝር ምላሽ፡-
1ኛ/ ከሁሉ በፊት ሊታወቅ የሚገባው ጉዳይ ቢኖር፡- ለማመንም ሆነ ለመካድ ሰበቡ ሰውየው እራሱ መሆኑን ነው፡፡ በእምነትና በክህደት ጉዳይ ላይ አንዱን በመምረጥ ቁርጥ ውሳኔ ለማድረግ የኛ ፈቃድ ሚናውን ይጫወታል፡፡ ሸይጣን ይህንን ውሳኔአችንን ለማስቀየር ወይንም ለመቀልበስ ምንም ስልጣን አልተሰጠውም፡፡ የሱ ድርሻው መጎትጎትና በኃጢአት ባሕር ላይ ዋኝተን እንድንቀር፡ በተውበት (ንሰሀ) ወደ አላህ መንገድ እንዳንመለስ፡ መጥፎውን ጥሩ በማስመሰል የማታለያ መንገዶችን መጠቀም ነው እንጂ፡ በፍጹም ሰው ከልቡ ወስኖ ለመስራት ያቀደውን ነገር (ጥሩም ሆነ መጥፎ) ለማገድና ለመቀየር የሚያስችል ስልጣን አልተሰጠውም! የለውምም፡፡
ያ ቢሆን ኖሮ፡ ስለኛ ኃጢአት የሚጠየቀው እሱ በኾነ ነበር፡፡ ስለዚህ አንተም ሙስሊም ያልኾንከው በተሰጠህ ነጻ-ፈቃድ የአላህን መንገድ ለመከተል ባለመምረጥህ ሰበብ እንጂ፡ ባንተ ፍላጎትና ፈቃድ ላይ ሸይጧን ተሸሞብህ ከልክሎህ አይደለም፡፡ ያ በመኾኑም የሸይጧን መታሰርም ሆነ መፈታት ባንተ ውሳኔ ላይ ምንም የሚያመጣው ለውጥ የለም፡፡ እሱ ከእውነት መንገድ ሰዎችን ለማገድ ከመጎትጎትና ወደ ጥፋት መንገድ ከመጥራት ውጭ ሌላ አቅም አልተሰጠውምና፡፡ የአላህ ቃል በትንሳኤው ዕለት (የውሙል ቂያም) በሸይጧንና በተከታዮቹ መካከል ስለሚደረገው የቃላት ምልልስ እንዲህ ይነግረናል፡-
" وَقَالَ الشَّيْطَانُ لَمَّا قُضِيَ الْأَمْرُ إِنَّ اللَّهَ وَعَدَكُمْ وَعْدَ الْحَقِّ وَوَعَدْتُكُمْ فَأَخْلَفْتُكُمْ وَمَا كَانَ لِيَ عَلَيْكُمْ مِنْ سُلْطَانٍ إِلَّا أَنْ دَعَوْتُكُمْ فَاسْتَجَبْتُمْ لِي فَلَا تَلُومُونِي وَلُومُوا أَنْفُسَكُمْ مَا أَنَا بِمُصْرِخِكُمْ وَمَا أَنْتُمْ بِمُصْرِخِيَّ إِنِّي كَفَرْتُ بِمَا أَشْرَكْتُمُونِ مِنْ قَبْلُ إِنَّ الظَّالِمِينَ لَهُمْ عَذَابٌ أَلِيمٌ " سورة إبراهيم 22
"ነገሩም በተፈጸመ ጊዜ፣ ሰይጣን ይላቸዋል፦ አላህ እውነተኛውን ቃል ኪዳን ገባላችሁ፤ ቃል ኪዳንም ገባሁላችሁ፤ አፈረስኩባችሁም፣ ለኔም በናንተ ላይ ምንም ሥልጣን አልነበረኝም ግን ጠራኋችሁ፤ ለኔም ታዘዛችሁ ስለዚህ አትውቀሱኝ፤ ነፍሶቻችሁንም ውቀሱ እኔ የምረዳችሁ አይደለሁም፤ እናንተም የምትረዱኝ አይደላችሁም፤ እኔ ከአሁን በፊት ለአላህ ተጋሪ በአደረጋችሁት ነገር ካድኩ፤ በዳዮቹ ለነርሱ በእርግጥ አሳማሚ ቅጣት አልላቸው።" (ሱረቱ ኢብራሂም 14፡22)፡፡
ይህ አንቀጽ የሚያስረዳው፡- አላህ በባሮቹ መካከል ፍትሐዊ ዳኝነትን በመዳኘት፡ የጀነቱም ወደ ጀነት፣ የጀሀነሙም ወደ ጀሀነም እንዲገባ ፍርድንና ውሳኔን ባስተላለፈ ወቅት፡ ሸይጧንም ለከሀዲያን፡- አላህ መቀስቀስና ከሞት መነሳት፡ ከዛም በእኔ ዘንድ ቆማችሁ መዳኘትና፡ ለሥራችሁ ተገቢ የኾነን ክፍያ እከፍላችኋለሁ በማለት፡ በነቢያቱ አንደበትና በመለኮታዊ መጽሐፍቱ አማካኝነት እውነተኛ ቃል ኪዳንን ገብቶላችሁ ነበር፡፡ እኔ ደግሞ፡ ሞቶ መቀስቀስ የሚባል ነገር የለም፡፡ ጀነት እና ጀሀነም የሚባለውን ዓለምም ማንም ሄዶ ያየው የለም፡ ስለዚህ በዚህቹ ምድራዊ ህይወታችሁ እንዳሻችሁ ሁኑ፡ ምንም አትሆኑም አይዟችሁ! በማለት የሀሰት ቃልን ገብቼላችሁ አፈረስኩ፡፡ ቢሆንም እናንተ እኔን መውቀስ አትችሉም!፡፡ ምክንያቱም እኔ ስጠራችሁ እሺ ብላችሁ የታዘዛችሁኝ እናንተው ናችሁ እንጂ፡ እኔ እናንተን ለማስገደድ ስልጣን አልነበረኝምና፡፡ ያ በመሆኑም የገዛ ነፍሳችሁን ውቀሱ እንጂ፡ እኔን አትውቀሱ! አሁን እኔ እናንተን የምረዳችሁ፡ ወይም እናንተ እኔን የምትረዱ አይደላችሁምና፡ በምድራዊ ህይወታችሁ ከአላህ ሌላ በማምለክ ባጋራችሁበት ነገር ሁሉ ክጃለሁ አላውቃችሁም! እንደሚላቸው ነው፡፡
እኛም የአላህን ቃል ተከትለን የምንለው፡- ሰዎች ኢስላምን እንዳይቀበሉ ሸይጧን ጉትጎታ ከማቅረብ ውጭ ሌላ ሚና የለውም፡፡ ኃይሉን ተጠቅሞ ማስቆምም አይችልም ነው፡፡ ደግሞም የሸይጧን ተንኮሉ ደካማ ነውና፡ በአላህ ኃይልና እገዛ ኃይሉንና ተንኮሉን መና ማስቀረት ይቻላል፡፡ የአላህ ቃል እንዲህ ይላል፡-
" الَّذِينَ آمَنُوا يُقَاتِلُونَ فِي سَبِيلِ اللَّهِ وَالَّذِينَ كَفَرُوا يُقَاتِلُونَ فِي سَبِيلِ الطَّاغُوتِ فَقَاتِلُوا أَوْلِيَاءَ الشَّيْطَانِ إِنَّ كَيْدَ الشَّيْطَانِ كَانَ ضَعِيفًا " سورة النساء 76
"እነዚያ ያመኑት ሰዎች፣ በአላህ መንገድ ይጋደላሉ፤ እነዛ የካዱትም በጣዖት መንገድ ይጋደላሉ፤ የሰይጣንንም ጭፍሮች ተጋደሉ። የሰይጣን ተንኮል ደካማ ነውና።" (ሱረቱ-ኒሳእ 4፡76)፡፡
2ኛ/ ሰው ነጻ ፈቃድ ያለው ፍጡር ነው፡፡ እንደ ሮቦት በተሞላው ነገር ብቻ የሚንቀሳቀስ ግኡዝ ፍጥረት አይደለም፡፡ ነጻ ፈቃድም ስላለው ከአምላኩ ዘንድ፡- ይህንን አድርግ! ይህንን ደግሞ አትቅረብ! የሚል መለኮታዊ ትእዛዝን በኃላፊነት ተቀብሏል፡፡ በኃላፊቱም ልክ፡ ነገ በጌታው ዘንድ ይጠየቃል፡፡ ግዳጁን በአግባቡ ተወጥቶ እንደኾን የጌታውን እዝነት ጀነትን ይጎናጸፋል፡፡ ግዳጁን ችላ ብሎ የሸይጧንን መስመር ተከትሎ እንደኾን የጌታውን የቁጣው መገለጫ የኾነውን ጀሀነም እሳትን ይገባል፡፡
እንግዲያውስ ሸይጧን በሰው ነጻ ፈቃድ ላይ ጣልቃ በመግባት፡ ሰዎችን ከመልካም ሥራ በማገድ እንቅፋት መሆን ከቻለ፡ የኛ ነጻ ፈቃድ ትርጉ
በአቡ ሀይደር
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው
ክብርና ምስጋና ለዓለማቱ ጌታ ለአላህ የተገባ ይሁን (አል-ፋቲሓ 2)፡፡ የአላህ ሰላምና ውዳሴ የሰው ዘር ታላቅ መሪ ለሆኑት ለነቢዩ ሙሐመድ (አል-አሕዛብ 56) ለመላው የአላህ መልክተኞች (አል-ሷፍፋት 181) የሐቅንም መንገድ በተከተለ ሁሉ ላይ ይሁን (ጣሀ 47)፡፡
አንዱ ክርስቲያን ነው ይህን ጥያቄ ያቀረበው፡፡ እናንተ ሙስሊሞች እንደምትሉት በረመዷን ወር ሰይጣናት የሚታሰሩ ከሆነ፡ አሁን የሚያሳስተን የለምና፡ ለምን እኛ ክርስቲያኖች ሙስሊም አልሆንም ታዲያ? የሚል፡፡ ለዚህ ጥያቄም መጠነኛ ምላሹ እንዲህ ይቀርባል፡-
ጥቅላዊ ምላሽ፡-
ወገናችን! ሰዎችን ኹሉ ያከፈረው (ከሀዲ ያደረገው) ሸይጧን ነው ማን አለህ ቀድሞውኑ? እንደዛ ተብሎ ቢሆን ኖሮ፡ በታሰረ ጊዜ የከፈሩት በጠቅላላ ለምን ተመልሰው አልሰለሙም? የሚል ጤናማ ጥያቄ ማቅረቡ ተገቢ ይኾን ነበር፡፡ ግን ባልተባለ ነገር ላይ ቆሞ ጥያቄ ማቅረብ ትልቅ የአስተሳሰብ መዛባት ነው፡፡ ሸይጧን ለሰዎች ክህደትና አመጽ ጎትጓች በመሆኑ፡ የጥፋት ሰበብ ተደርጎ ይወሰዳል እንጂ፡ በሰዎች ልብ ላይ ተሹሞ፡ በልባቸውና በእምነት መካከል ጣልቃ በመግባት እንዳያምኑ ይጋርዳል አልተባለም፡፡ ይህን የማድረግ ስልጣንም አልተሰጠውም፡፡ እሱ ወደ ኃጢአት ይጣራል እንጂ፡ ኃጢአቱን የሚፈጽመው ሰውየው እራሱ ነው፡፡ ስለሆነም ስለ ሥራው ይጠየቃል፡፡ አንተም በሸይጧን መታሰር ሰበብ እኔ ለምን አልሰለምኩም ታዲያ? ላልከው፡ እውን ለመስለምና አላህን ብቻ ለማምለክ እራስህን አዘጋጅተህ ነበርን? ከሸይጧን የከፋውን ጠላትህንስ (ነፍሲያህን) መከተል አቁመህ ነበርን? በማለት ልንጠይቅህ እንወዳለን፡፡ እስኪ አንተም ውስጥህን መርምረውና የዚያኔ መልሱን ታገኘዋለህ፡፡
ዝርዝር ምላሽ፡-
1ኛ/ ከሁሉ በፊት ሊታወቅ የሚገባው ጉዳይ ቢኖር፡- ለማመንም ሆነ ለመካድ ሰበቡ ሰውየው እራሱ መሆኑን ነው፡፡ በእምነትና በክህደት ጉዳይ ላይ አንዱን በመምረጥ ቁርጥ ውሳኔ ለማድረግ የኛ ፈቃድ ሚናውን ይጫወታል፡፡ ሸይጣን ይህንን ውሳኔአችንን ለማስቀየር ወይንም ለመቀልበስ ምንም ስልጣን አልተሰጠውም፡፡ የሱ ድርሻው መጎትጎትና በኃጢአት ባሕር ላይ ዋኝተን እንድንቀር፡ በተውበት (ንሰሀ) ወደ አላህ መንገድ እንዳንመለስ፡ መጥፎውን ጥሩ በማስመሰል የማታለያ መንገዶችን መጠቀም ነው እንጂ፡ በፍጹም ሰው ከልቡ ወስኖ ለመስራት ያቀደውን ነገር (ጥሩም ሆነ መጥፎ) ለማገድና ለመቀየር የሚያስችል ስልጣን አልተሰጠውም! የለውምም፡፡
ያ ቢሆን ኖሮ፡ ስለኛ ኃጢአት የሚጠየቀው እሱ በኾነ ነበር፡፡ ስለዚህ አንተም ሙስሊም ያልኾንከው በተሰጠህ ነጻ-ፈቃድ የአላህን መንገድ ለመከተል ባለመምረጥህ ሰበብ እንጂ፡ ባንተ ፍላጎትና ፈቃድ ላይ ሸይጧን ተሸሞብህ ከልክሎህ አይደለም፡፡ ያ በመኾኑም የሸይጧን መታሰርም ሆነ መፈታት ባንተ ውሳኔ ላይ ምንም የሚያመጣው ለውጥ የለም፡፡ እሱ ከእውነት መንገድ ሰዎችን ለማገድ ከመጎትጎትና ወደ ጥፋት መንገድ ከመጥራት ውጭ ሌላ አቅም አልተሰጠውምና፡፡ የአላህ ቃል በትንሳኤው ዕለት (የውሙል ቂያም) በሸይጧንና በተከታዮቹ መካከል ስለሚደረገው የቃላት ምልልስ እንዲህ ይነግረናል፡-
" وَقَالَ الشَّيْطَانُ لَمَّا قُضِيَ الْأَمْرُ إِنَّ اللَّهَ وَعَدَكُمْ وَعْدَ الْحَقِّ وَوَعَدْتُكُمْ فَأَخْلَفْتُكُمْ وَمَا كَانَ لِيَ عَلَيْكُمْ مِنْ سُلْطَانٍ إِلَّا أَنْ دَعَوْتُكُمْ فَاسْتَجَبْتُمْ لِي فَلَا تَلُومُونِي وَلُومُوا أَنْفُسَكُمْ مَا أَنَا بِمُصْرِخِكُمْ وَمَا أَنْتُمْ بِمُصْرِخِيَّ إِنِّي كَفَرْتُ بِمَا أَشْرَكْتُمُونِ مِنْ قَبْلُ إِنَّ الظَّالِمِينَ لَهُمْ عَذَابٌ أَلِيمٌ " سورة إبراهيم 22
"ነገሩም በተፈጸመ ጊዜ፣ ሰይጣን ይላቸዋል፦ አላህ እውነተኛውን ቃል ኪዳን ገባላችሁ፤ ቃል ኪዳንም ገባሁላችሁ፤ አፈረስኩባችሁም፣ ለኔም በናንተ ላይ ምንም ሥልጣን አልነበረኝም ግን ጠራኋችሁ፤ ለኔም ታዘዛችሁ ስለዚህ አትውቀሱኝ፤ ነፍሶቻችሁንም ውቀሱ እኔ የምረዳችሁ አይደለሁም፤ እናንተም የምትረዱኝ አይደላችሁም፤ እኔ ከአሁን በፊት ለአላህ ተጋሪ በአደረጋችሁት ነገር ካድኩ፤ በዳዮቹ ለነርሱ በእርግጥ አሳማሚ ቅጣት አልላቸው።" (ሱረቱ ኢብራሂም 14፡22)፡፡
ይህ አንቀጽ የሚያስረዳው፡- አላህ በባሮቹ መካከል ፍትሐዊ ዳኝነትን በመዳኘት፡ የጀነቱም ወደ ጀነት፣ የጀሀነሙም ወደ ጀሀነም እንዲገባ ፍርድንና ውሳኔን ባስተላለፈ ወቅት፡ ሸይጧንም ለከሀዲያን፡- አላህ መቀስቀስና ከሞት መነሳት፡ ከዛም በእኔ ዘንድ ቆማችሁ መዳኘትና፡ ለሥራችሁ ተገቢ የኾነን ክፍያ እከፍላችኋለሁ በማለት፡ በነቢያቱ አንደበትና በመለኮታዊ መጽሐፍቱ አማካኝነት እውነተኛ ቃል ኪዳንን ገብቶላችሁ ነበር፡፡ እኔ ደግሞ፡ ሞቶ መቀስቀስ የሚባል ነገር የለም፡፡ ጀነት እና ጀሀነም የሚባለውን ዓለምም ማንም ሄዶ ያየው የለም፡ ስለዚህ በዚህቹ ምድራዊ ህይወታችሁ እንዳሻችሁ ሁኑ፡ ምንም አትሆኑም አይዟችሁ! በማለት የሀሰት ቃልን ገብቼላችሁ አፈረስኩ፡፡ ቢሆንም እናንተ እኔን መውቀስ አትችሉም!፡፡ ምክንያቱም እኔ ስጠራችሁ እሺ ብላችሁ የታዘዛችሁኝ እናንተው ናችሁ እንጂ፡ እኔ እናንተን ለማስገደድ ስልጣን አልነበረኝምና፡፡ ያ በመሆኑም የገዛ ነፍሳችሁን ውቀሱ እንጂ፡ እኔን አትውቀሱ! አሁን እኔ እናንተን የምረዳችሁ፡ ወይም እናንተ እኔን የምትረዱ አይደላችሁምና፡ በምድራዊ ህይወታችሁ ከአላህ ሌላ በማምለክ ባጋራችሁበት ነገር ሁሉ ክጃለሁ አላውቃችሁም! እንደሚላቸው ነው፡፡
እኛም የአላህን ቃል ተከትለን የምንለው፡- ሰዎች ኢስላምን እንዳይቀበሉ ሸይጧን ጉትጎታ ከማቅረብ ውጭ ሌላ ሚና የለውም፡፡ ኃይሉን ተጠቅሞ ማስቆምም አይችልም ነው፡፡ ደግሞም የሸይጧን ተንኮሉ ደካማ ነውና፡ በአላህ ኃይልና እገዛ ኃይሉንና ተንኮሉን መና ማስቀረት ይቻላል፡፡ የአላህ ቃል እንዲህ ይላል፡-
" الَّذِينَ آمَنُوا يُقَاتِلُونَ فِي سَبِيلِ اللَّهِ وَالَّذِينَ كَفَرُوا يُقَاتِلُونَ فِي سَبِيلِ الطَّاغُوتِ فَقَاتِلُوا أَوْلِيَاءَ الشَّيْطَانِ إِنَّ كَيْدَ الشَّيْطَانِ كَانَ ضَعِيفًا " سورة النساء 76
"እነዚያ ያመኑት ሰዎች፣ በአላህ መንገድ ይጋደላሉ፤ እነዛ የካዱትም በጣዖት መንገድ ይጋደላሉ፤ የሰይጣንንም ጭፍሮች ተጋደሉ። የሰይጣን ተንኮል ደካማ ነውና።" (ሱረቱ-ኒሳእ 4፡76)፡፡
2ኛ/ ሰው ነጻ ፈቃድ ያለው ፍጡር ነው፡፡ እንደ ሮቦት በተሞላው ነገር ብቻ የሚንቀሳቀስ ግኡዝ ፍጥረት አይደለም፡፡ ነጻ ፈቃድም ስላለው ከአምላኩ ዘንድ፡- ይህንን አድርግ! ይህንን ደግሞ አትቅረብ! የሚል መለኮታዊ ትእዛዝን በኃላፊነት ተቀብሏል፡፡ በኃላፊቱም ልክ፡ ነገ በጌታው ዘንድ ይጠየቃል፡፡ ግዳጁን በአግባቡ ተወጥቶ እንደኾን የጌታውን እዝነት ጀነትን ይጎናጸፋል፡፡ ግዳጁን ችላ ብሎ የሸይጧንን መስመር ተከትሎ እንደኾን የጌታውን የቁጣው መገለጫ የኾነውን ጀሀነም እሳትን ይገባል፡፡
እንግዲያውስ ሸይጧን በሰው ነጻ ፈቃድ ላይ ጣልቃ በመግባት፡ ሰዎችን ከመልካም ሥራ በማገድ እንቅፋት መሆን ከቻለ፡ የኛ ነጻ ፈቃድ ትርጉ
ሙ ምኑ ላይ ነው? አንድ አባት በጠዋቱ ማልዶ ይነሳና ልጁን፡- ከሰአት ለምሳ ቤት እስክመለስ ድረስ ከገበያ ወጥተህ እነዚህን ነገራት ገዝተህ ጠብቀኝ! በማለት ትእዛዝ ይሰጠውና፡ ልጁን ከበሩ ማገር ጋር እንዳይንቀሳቀስ ጥፍር አድርጎ አስሮት ወደ ስራው ይኼዳል፡፡ ይህ አባት ከሰዓት ላይ ለምሳ ወደቤቱ ሲመለስ፡ ልጁን እዛው የታሰረበት በሩ ላይ ያገኘውና፡ የላክሁህን እቃ ለምን አላመጣህም? በማለት ይቀጣዋል፡፡ አሁን የዚህ አባት እርምጃ ትክክለኛ ነበር! ብሎ የሚያስብ ሰው ይኖራልን? በፍፁም የለም! ከተባለ ደግሞ፡- እንግዲያውስ አባት ለልጁ ከሚያዝነው በላይ፡ ለባሮቹ የሚራራው አምላክስ፡ የሱን ትእዛዛት እንዳናከብር ሰይጣን በኃይሉ እንቅፋት ሲሆንብን፡ እያየና እየሰማ በዝምታ በማለፍ፡ ከዚያም የቂያም ቀን፡ ለምን ትእዛዜን አላከበራችሁም በማለት ይቀጣናል ብሎ ማሰብስ እንዴት ይቻላል?
ለምን ሰው የገዛ ነፍሱን ድክመት በሸይጧን ጉትጎታ ያሳብባል? አላህም እኮ ነጻ ፈቃድ የሰጠን፡ አመስጋኝ ሆነን የእምነትን መንገድ እንድንከተል፡ ወይንም ከሀዲ ሆነን የጥመትን መንገድ በመከተል በፈቃዳችን እንድንወስን ነው፡፡ የአላህ ቃል ሲናገር እንዲህ ይላል፡-
" إِنَّا خَلَقْنَا الْإِنْسَانَ مِنْ نُطْفَةٍ أَمْشَاجٍ نَبْتَلِيهِ فَجَعَلْنَاهُ سَمِيعًا بَصِيرًا (2) إِنَّا هَدَيْنَاهُ السَّبِيلَ إِمَّا شَاكِرًا وَإِمَّا كَفُورًا " سورة الإنسان 3-2
"እኛ ሰዉን፥ (በሕግ ግዳጅ) የምንሞክረዉ ስንሆን፥ ቅልቅሎች ከሆኑ የፍትወት ጠብታ ፈጠርነዉ፤ ሰሚ ተመልካችም አደረግነዉ። እኛ፥ ወይ አመስጋኝ ወይም ከሐዲ ሲሆን መንገዱን መራነዉ፤ (ገለጽንለት)።" (ሱረቱል ኢንሳን 76፡2-3)፡፡
3ኛ/ ሌላው ወገናችን ያልተረዳው ነጥብ፡ ሸይጧናት ይታሰራሉ ሲባል፡ ሁሉንም አለመሆኑን ነው፡፡ በነቢያዊ ትምሕርቱ ላይ እንደተብራራው፡ እነዚህ በረመዷን ወር የሚታሰሩት ሸይጧናት እጅግ አመጸኞቹን አስቸጋሪዎቹን እንደሆነ ነው፡፡ ቀጣዩ ሐዲሥም ይህን እውነት እንዲህ ይገልጸዋል፡-
عن أبي هريرة رضي الله عنه قال : قال رسول الله صلى الله عليه وسلم: ( إِذَا كَانَ أَوَّلُ لَيْلَةٍ من شَهْرِ رَمَضَانَ صُفِّدَتِ الشَّيَاطِينُ وَمَرَدَةُ الْجِنِّ ، وَغُلِّقَتْ أَبْوَابُ النَّارِ فلم يُفْتَحْ منها بَابٌ ، وَفُتِّحَتْ أَبْوَابُ الْجَنَّةِ فلم يُغْلَقْ منها بَابٌ ...) الحديث ، رواه الترمذي (682) ، وابن ماجه (1642) ، وحسَّنه الألباني في " صحيح الجامع " (759).
ከአቢ ሁረይራህ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንደተላለፈው የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- "የረመዷን ወር የመጀመሪያው ለሊት ሲገባ፡ ሸይጧናትና አመጸኛ ጂንኒዎች ይታሰራሉ፡፡ የጀሀነም በሮች አንድም ሳይቀር ይከረቸማሉ፡፡ የጀነት በሮች አንድም ሳይቀር ይከፈታሉ…" (ቲርሚዚይ 682፣ ኢብኑ ማጀህ 1642፣ አልባኒይ ሶሒሑል ጃሚዕ 759)፡፡)
ከዚህ ሐዲሥ በመነሳት፡ በረመዷን የሚታሰሩት፡ ለሰዎች አስቸጋሪና አመጸኛ የሆኑ ሸይጧናት መሆናቸውን መረዳት እንችላለን፡፡ አቅመ ደካማዎቹና ሽሜዎቹ ደግሞ የጉትጎታ ሥራቸውን ይቀጥላሉ ማለት ነው፡፡ ወላሁ አዕለም፡፡
4ኛ/ በተጨማሪም ይህ ወገናችን የሳተው ነገር፡ ሰዎቹን ከአላህ መንገድ ለማደናቀፍ ያላሰለሰ ጥረት የሚያደርገው ከጂንኒ ወገን የኾነው ሸይጧንን ብቻ አድርጎ መሳሉ ነው፡፡ የገዛ ነፍሲያችንም (ስሜት) እጅግ አደገኛ ጠላት ነው፡፡ ሰው የሸይጧንን ጉትጎታ ማሸነፍ የሚችለው፡ በነፍሲያው ላይ ድልን ከተቀዳጀ በኋላ ነው፡፡ ነፍሲያችን ትእዛዝን አትወድም፡፡ ስሜትንና ዝንባሌን እንድንከተል ትመክረናለች፡፡ ከአላህ መንገድና እሱን ከማምለክ ታዘናጋናለች፡፡ ስለዚህ የሸይጧን ጉትጎታ ብቻ ሳይሆን የገዛ ነፍሲያችንም ከኛው ጋር ትግል ውስጥ መሆኗን ማወቅ አለብህ፡፡ አንተንም ለመስለም የሚከለክልህ ይህ የነፍሲያህ እምቢተኝነት መሆኑን አስተውለሀልን?
5ኛ/ በመጨረሻም ለዚህ ወገናችን የምናስተላልፈው መልእክት፡ ሂዳያ (ቅኑን ጎዳና ማግኘት) የአላህ ተውፊቅ (መልካሙን ዕድል እንድታገኝ መግጠም) እንጂ፡ የገዛ ሥራችን ውጤት አይደለም፡፡ እኛ መሆን የምንችለው ነገር ቢኖር ሰበብ መሆን ብቻ ነው፡፡ ውጤቱ ግን ከአላህ ዘንድ ብቻ የሚሰጥ ነው፡፡ ስለዚህ ዕድሜህን ሙሉ ከአላህ መንገድ ወጥተህ፡ የነፍሲያህና የሸይጧን መጫወቻ ለመሆን ፈቅደህ ስታበቃ፡ ሸይጧን ነው ከመንገድ ያስወጣኝ ማለት አያዋጣም፡፡ ቅድሚያ ነፍሲያህንና ሸይጧንን ታግለህ በአላህ መንገድ ለመታገል ከወሰንክ አላህም ቅኑን ጎዳና እንደሚመራህ በመግለጽ ቃልን ገብቷልና፡ አንተም ለማመን እራስህን አዘጋጅ፡ ሸይጧን ስለታሰረ የሚሰልም፡ ስለተፈታ ደግሞ የሚክድ ሰው የለምና፡፡ የአላህ ቃል እንዲህ ይላል፡-
" وَالَّذِينَ جَاهَدُوا فِينَا لَنَهْدِيَنَّهُمْ سُبُلَنَا وَإِنَّ اللَّهَ لَمَعَ الْمُحْسِنِينَ " سورة العنكبوت 69
"እነዚያም በኛ መንገድ የታገሉ መንገዳችንን በእርግጥ እንመራቸዋለን፤ አላህም በእርግጥ ክበጎ ሠሪዎች ጋር ነው።" (ሱረቱል ዐንከቡት 29፡69)፡፡
Join us➤ t.me/abuhyder
Click and Like ➤➤ https://www.facebook.com/Ustaz.Abuhyder
Join us➤ t.me/abuhyder
ለምን ሰው የገዛ ነፍሱን ድክመት በሸይጧን ጉትጎታ ያሳብባል? አላህም እኮ ነጻ ፈቃድ የሰጠን፡ አመስጋኝ ሆነን የእምነትን መንገድ እንድንከተል፡ ወይንም ከሀዲ ሆነን የጥመትን መንገድ በመከተል በፈቃዳችን እንድንወስን ነው፡፡ የአላህ ቃል ሲናገር እንዲህ ይላል፡-
" إِنَّا خَلَقْنَا الْإِنْسَانَ مِنْ نُطْفَةٍ أَمْشَاجٍ نَبْتَلِيهِ فَجَعَلْنَاهُ سَمِيعًا بَصِيرًا (2) إِنَّا هَدَيْنَاهُ السَّبِيلَ إِمَّا شَاكِرًا وَإِمَّا كَفُورًا " سورة الإنسان 3-2
"እኛ ሰዉን፥ (በሕግ ግዳጅ) የምንሞክረዉ ስንሆን፥ ቅልቅሎች ከሆኑ የፍትወት ጠብታ ፈጠርነዉ፤ ሰሚ ተመልካችም አደረግነዉ። እኛ፥ ወይ አመስጋኝ ወይም ከሐዲ ሲሆን መንገዱን መራነዉ፤ (ገለጽንለት)።" (ሱረቱል ኢንሳን 76፡2-3)፡፡
3ኛ/ ሌላው ወገናችን ያልተረዳው ነጥብ፡ ሸይጧናት ይታሰራሉ ሲባል፡ ሁሉንም አለመሆኑን ነው፡፡ በነቢያዊ ትምሕርቱ ላይ እንደተብራራው፡ እነዚህ በረመዷን ወር የሚታሰሩት ሸይጧናት እጅግ አመጸኞቹን አስቸጋሪዎቹን እንደሆነ ነው፡፡ ቀጣዩ ሐዲሥም ይህን እውነት እንዲህ ይገልጸዋል፡-
عن أبي هريرة رضي الله عنه قال : قال رسول الله صلى الله عليه وسلم: ( إِذَا كَانَ أَوَّلُ لَيْلَةٍ من شَهْرِ رَمَضَانَ صُفِّدَتِ الشَّيَاطِينُ وَمَرَدَةُ الْجِنِّ ، وَغُلِّقَتْ أَبْوَابُ النَّارِ فلم يُفْتَحْ منها بَابٌ ، وَفُتِّحَتْ أَبْوَابُ الْجَنَّةِ فلم يُغْلَقْ منها بَابٌ ...) الحديث ، رواه الترمذي (682) ، وابن ماجه (1642) ، وحسَّنه الألباني في " صحيح الجامع " (759).
ከአቢ ሁረይራህ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንደተላለፈው የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ፡- "የረመዷን ወር የመጀመሪያው ለሊት ሲገባ፡ ሸይጧናትና አመጸኛ ጂንኒዎች ይታሰራሉ፡፡ የጀሀነም በሮች አንድም ሳይቀር ይከረቸማሉ፡፡ የጀነት በሮች አንድም ሳይቀር ይከፈታሉ…" (ቲርሚዚይ 682፣ ኢብኑ ማጀህ 1642፣ አልባኒይ ሶሒሑል ጃሚዕ 759)፡፡)
ከዚህ ሐዲሥ በመነሳት፡ በረመዷን የሚታሰሩት፡ ለሰዎች አስቸጋሪና አመጸኛ የሆኑ ሸይጧናት መሆናቸውን መረዳት እንችላለን፡፡ አቅመ ደካማዎቹና ሽሜዎቹ ደግሞ የጉትጎታ ሥራቸውን ይቀጥላሉ ማለት ነው፡፡ ወላሁ አዕለም፡፡
4ኛ/ በተጨማሪም ይህ ወገናችን የሳተው ነገር፡ ሰዎቹን ከአላህ መንገድ ለማደናቀፍ ያላሰለሰ ጥረት የሚያደርገው ከጂንኒ ወገን የኾነው ሸይጧንን ብቻ አድርጎ መሳሉ ነው፡፡ የገዛ ነፍሲያችንም (ስሜት) እጅግ አደገኛ ጠላት ነው፡፡ ሰው የሸይጧንን ጉትጎታ ማሸነፍ የሚችለው፡ በነፍሲያው ላይ ድልን ከተቀዳጀ በኋላ ነው፡፡ ነፍሲያችን ትእዛዝን አትወድም፡፡ ስሜትንና ዝንባሌን እንድንከተል ትመክረናለች፡፡ ከአላህ መንገድና እሱን ከማምለክ ታዘናጋናለች፡፡ ስለዚህ የሸይጧን ጉትጎታ ብቻ ሳይሆን የገዛ ነፍሲያችንም ከኛው ጋር ትግል ውስጥ መሆኗን ማወቅ አለብህ፡፡ አንተንም ለመስለም የሚከለክልህ ይህ የነፍሲያህ እምቢተኝነት መሆኑን አስተውለሀልን?
5ኛ/ በመጨረሻም ለዚህ ወገናችን የምናስተላልፈው መልእክት፡ ሂዳያ (ቅኑን ጎዳና ማግኘት) የአላህ ተውፊቅ (መልካሙን ዕድል እንድታገኝ መግጠም) እንጂ፡ የገዛ ሥራችን ውጤት አይደለም፡፡ እኛ መሆን የምንችለው ነገር ቢኖር ሰበብ መሆን ብቻ ነው፡፡ ውጤቱ ግን ከአላህ ዘንድ ብቻ የሚሰጥ ነው፡፡ ስለዚህ ዕድሜህን ሙሉ ከአላህ መንገድ ወጥተህ፡ የነፍሲያህና የሸይጧን መጫወቻ ለመሆን ፈቅደህ ስታበቃ፡ ሸይጧን ነው ከመንገድ ያስወጣኝ ማለት አያዋጣም፡፡ ቅድሚያ ነፍሲያህንና ሸይጧንን ታግለህ በአላህ መንገድ ለመታገል ከወሰንክ አላህም ቅኑን ጎዳና እንደሚመራህ በመግለጽ ቃልን ገብቷልና፡ አንተም ለማመን እራስህን አዘጋጅ፡ ሸይጧን ስለታሰረ የሚሰልም፡ ስለተፈታ ደግሞ የሚክድ ሰው የለምና፡፡ የአላህ ቃል እንዲህ ይላል፡-
" وَالَّذِينَ جَاهَدُوا فِينَا لَنَهْدِيَنَّهُمْ سُبُلَنَا وَإِنَّ اللَّهَ لَمَعَ الْمُحْسِنِينَ " سورة العنكبوت 69
"እነዚያም በኛ መንገድ የታገሉ መንገዳችንን በእርግጥ እንመራቸዋለን፤ አላህም በእርግጥ ክበጎ ሠሪዎች ጋር ነው።" (ሱረቱል ዐንከቡት 29፡69)፡፡
Join us➤ t.me/abuhyder
Click and Like ➤➤ https://www.facebook.com/Ustaz.Abuhyder
Join us➤ t.me/abuhyder
Audio
ለምን ተፈጠርን!?
ሁሉንም የሰው ልጆች የሚመለከት ጥሪ በዋልታ ቲቪ የቀረበ
🎙 አዘጋጅ⇊
➤ ኡስታዝ አቡ ሐይደር
Join us➤ t.me/abuhyder
https://youtu.be/a4BHwoHLWXo
ሁሉንም የሰው ልጆች የሚመለከት ጥሪ በዋልታ ቲቪ የቀረበ
🎙 አዘጋጅ⇊
➤ ኡስታዝ አቡ ሐይደር
Join us➤ t.me/abuhyder
https://youtu.be/a4BHwoHLWXo