AAU - Muslim Students Union
7.94K subscribers
2.95K photos
186 videos
57 files
840 links
This is the official channel of AAU-MSU.

Group: @aaumsu_discussion
Youtube: youtube.com/@aaumsu
Twitter: x.com/aaumsu12
Facebook: facebook.com/profile.php?id=100087931837303

Contact us: @Aaumuslimstudentsunion1
Email: aaumsu12@gmail.com
Download Telegram
እውነትም፣ እስልምና ሰላምን የሚያስተምር፣ በጽናት ለእውነትና ለፍትሕ መቆምን የሚያስተምር እምነት ነው!!

ጂማ ዩኒቨርሲቲ ብዙ የመስዋትነትን ታሪኮችን ከጀርባው ያዘለውን ውዱን የሙስሊም ሴት ሂጃብ ለተማሪዎቹ አጀንዳ ካደረገ ረጅም ጊዜን አስቆጥሯል። በነዚህ ሁሉ ጊዜያት ሰላምን መንገዳቸው ጽናትን መለያቸው ያደረጉ የግቢው ሙስሊም ተማሪዎች እስልምና የሰላም እምነት መሆኑ በ ተግባር ከኖሩት ውስጥ ተጠቃሾቹ ናቸው••

የአባጂፋር ሀገር ጂማ ስትጠራ፣ ሙስሊሙ ማህበረሰብ በስፋት የሚኖርባት አካባቢ መሆኗ ከሚገልጿት ቀዳሚ መገለጫዎቿ አንዱ ነው። ታዲያ ሂጃብን አንዱ የ ሂወቱ ክፍል አድርጎ ሚኖር ማህበረሰብ ውስጥ
🎯ሂጃብ ለ ትምርት ስኬታማነት እንቅፋት
🎯ሂጃብ ለ ግቢውና ለማህበረሰቡ የ ደህንነት ስጋት ሆኖ ሊቀርብ የቻለው በምን አግባብ ነው ?
!

እንዴትስ ሂጃብን የ ሕይወት መርህ ብሎ ልጁን ያስያዘ ማህበረሰብ ውስጥ በሂጃብ ጥያቄ ምክንያት ተማሪዎችን ማግለል፣ ማንከራተት፣ ማሰር አልፎም ከግቢው ማባረር ጋር መድረስ ተቻለ ?!

ሕያው ምስክር ~2~ የጂማ ዩኒቨርሲቲ የ ነጻነት ጉዞ!

ተጋባዥ እንግዶች
አብዲ ኮርማ ~ በጊዜው የጂማ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አግሪ ካምፓስ አሚር
ሱደይሲ አብዱረሕማን~ የጂማ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር


🗓መስከረም-1 የፊታችን ጁምዐ!
🕞ከምሽቱ 3:00 ጀምሮ!

@aaumsu
🔥21👏52
ምስሉን ፕሮፋይል እናድርግ
በስቶሪዎቻችን ላይ እናጋራ
ቻናል እና ግሩፕ ያላችሁ መልዕክቱን በዚያ በኩል አድርሱ
ኢንቦክስ በመግባትም ለምናውቃቸው ሁሉ እንላክ!

ጁምዓ (መስከረም 1) ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ እንገናኝ !

የአባ ጅፋር ልጆች የሰሩትን ትግል፤ የከፈሉትን መስዕዋትነትን ሕያው ምስክር ሆኖ እንቃኛለን። በደልን አንቀበልም ብለው እስር ቤት እስከማደር ስለደረሱት የጁማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ትግል እንቃኛለን።

ቻለንጁን እንቀላቀል !

@aaumsu
🔥30👏53👍3
🔥ከሙተነቂቦች መንደር ~ 1
ጂማ ዩኒቨርሲቲ!🔥


“...ከዚህ በላይ ስማቸው የተጠቀሱ ተማሪዎች የሃይማኖት መግለጫ በሆነው አለባበስ፣ ከሚከለከሉት አንዱ ጀለቢያ፣ ጥምጣም እና ማንነታቸውን በማይገልጽ አለባበስ ኢቃም ፊታቸውን ሸፍነው ግቢ ውስጥ በመንቀሳቀስ፣ እንዲሁም የተማሪዎች መመገቢያ ካፌ ለመመገብ ሲሄዱ መያዛቸውን አሳውቀውናል። ስለዚህ ሦስቱ ተማሪዎች የአለባበስ የዲሲፕሊን መመሪያ ጥሰው ስለተገኙ፣ የተከለከሉ ተግባራትን ለሚያከናውኑ ተማሪዎች መማሪያ ይሆን ዘንድ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መመሪያ ቁጥር 002/012 መሠረት በተማሪዎች ዲሲፕሊን ታይቶ እንዲቀጡ…”


🍂ኒቃብ የለበስኩት የግቢ ተማሪ እያለው ነበር በሰዓቱ ግቢው ኒቃብ ካለመፍቀዱም በላይ ማስክ ለብሰው ያገኟቸውን ልጆች እንኳ ID በመቀማት የሚያስተጓጉሉበት ወቅት ነበር።

ከኒቃብ ጋር ተያይዞ ብዙ አይነት ፈተናዎች ይኖራሉ እኔም ጋር ከነበሩት ውስጥ አንዱ በክፍል ውስጥ ከ አስተማሪ ጋር የነበረ የ እለተእለት ማስጠንቀቂያ ነበር••• አስተማሪው attendance ለመሙላት የሁሉንም ስም በሚጠራበት ጊዜ ሁሌም ስሜን ከጠራ ቡሃላ ጠቋሚ ጣቱን እያወዛወዘ "ይሄ ነገርሽን ዝቅ አድርጊ ብያለው " ይል ነበር ወደ ለበስኩት ማስክ እያመላከተ... አንዳንዴም ብቻዬን እየጠራኝ አለባበሴን እንዳስተካክል ይነግረኝ ነበር

ከሁሉም በላይ ግን እኔ ዘንድ ላይረሳ በደማቁ የተፃፈው "ኒቃብ ለብሳችሁ በመገኘት" ተብሎ ከ 2 ጓደኞቼ ጋር ከ ዲስፕሊን ቢሮ ቀርቦብን የነበረው ክስ ነው!! መጀመርያ ID ሲቀሙን እንደሌላ ጊዜው በነጋታው ይመልሱልናል ብለን ስንጠብቅ ነገሩ ከሮ ከጥበቃና የደህንነት ክፍል ለጂማ technology institute ተማሪዎች discipline ኮሚቴ ለሌሎች ተማሪዎች መማርያ በሚሆን መልኩ እንድንታረም ሚጠይቅ የክስ ደብዳቤ ገባ..


🗓መስከረም - 1 ከምሽቱ 3:00! ሰዓት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ቴሌግራም ገጽ እንገናኝ!"

@aaumsu
🔥184👏1
💫ልዩ የዳእዋ ፕሮግራም ለእህቶች💫

ሂጃብ እና የዘመኑ ፈተና

አላህ ሱ.ወ ሴትን ልጅ ካላቀበት እና ካከበረበት ነገሮች ውስጥ ሂጃብ አንዱ እና ትልቁ ነገር ነው።የተስተካከለ አለባበስ የአንዲት ሙስሊም ሴት ጥብቅነት መገለጫም ጭምር እንደሆነ ተቀምጦልናል። ታድያ አለባበሳችን ምን መምሰል አለበት...ምንድነው ሂጃብ መስፈርቶቹ እንዲሁም ምንድነው የተፈለገበት .....እሚለውን እና ሌሎችንም ለማውራት ቀጠሯችንን የፊታችን ቅዳሜ በታላቁ ሁዘይፋ መስጂድ አድርገናል።

ምን እሱ ብቻ ..

ከሂጃብ ጋር እየመጡ ያሉ ትምህርት ላይ እንቅፋት የሆኑ ክልከላዎች እና ዘመን አመጣሽ ውጣውረዶች ምንድናቸው ? በምን መልክ ማለፍ እንችላለን ? ለሚመጣውስ ትውልድ ምን ማበርከት እንችላለን ? የሚለውንም የምናነሳ ይሆናል።

ቦታ፡- ሁዘይፋ መስጂድ (የሺ ደበሌ ከፍ ብሎ)
ቀን ፡- የፊታችን ቅዳሜ
ሰአት ፡-3፡00-6፡00
ተጋባዥ ፡- ሁሏም እህት ሁሏም እናት ሁሏም ተማሪ (አዲስ ግቢ የምትገቡ ተማሪዎች ብትመጡ በደንብ ትጠቀማላቹ)

@aaumsu
👌18🔥7👍41🥰1
ጥቂት ሰዓታት ብቻ ይቀሩታል!

ምስሉን ፕሮፋይል እናድርግ

በስቶሪዎቻችን ላይ እናጋራ
ቻናል እና ግሩፕ ያላችሁ መልዕክቱን በዚያ በኩል አድርሱ
ኢንቦክስ በመግባትም ለምናውቃቸው ሁሉ እንላክ!

ዛሬ ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ እንገናኝ !

@aaumsu
🔥12🥰1👌1
ብዙ ያልተነኩና የልተዳሰሱ አሻራዎች ያሉበት መንገድ!

ሕያው ምስክር ~ 2 ~ ጅማ ዩኒቨርስቲ የነፃነት ትግል!!

🗓 ዛሬ ከ ምሽቱ 3:00 እንገናኝ!


@aaumsu
🔥11👍2🥰1
ሕያው ምስክር - 2 - 3:00 ላይ ይጀመራል!

ከ2 ሰዓት ያነሰ ጊዜ ቀረን ማለት ነው። ስለ አባጅፋሯ ጅማ፤ ስለአባጅፋር ልጆች የመብት ጥያቄ ሂደት ከሕያው ምስክሮች ጋር ልዩ ቆይታ ይኖራል። መልዕክቱን ለሁሉም አድርሱ። ሰከንድ ሳያልፍ በሰዓቱ እንገኝ።

የጥያቄ አለን ትውልድ የሚዘነጋው ትግል የለም!

@aaumsu
🔥113👏1
1 ሰዓት ብቻ ቀረው!

ዝግጁ?

@aaumsu
🔥7🫡21👍1
Live stream scheduled for
Live stream started
ለእንግዶች ማንኛውም ጥያቄ እና አስተያየት ካላችሁ በ @Niqab_issueBot መላክ ትችላላችሁ።

@aaumsu
7🥰2👍1
"የጀመዓ ትልቁ ኃላፊነት የተማሪዎችn መብት እና ደህንነት ማስጠበቅ ነው።"

- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)

@aaumsu
👌351
ችግሩን እንፈታለን ብለው ቃል የገቡ አካላት መጨረሻ ላይ ፈሩ፤ ችግሩን መፍታት አልቻሉም።

- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)

@aaumsu
🔥221
እንደ ኃገር አቀፍ ደረጃ ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆኑ ግለሰቦች፤ ሽማግሌዎች ከጀመዓው ጋር ተወያዩ፤ ለችግሩም መፍትሄ እንደሚያመጡ ቃል ገቡ። ነገር ግን ይህ ሳይሆን ቀረ።

- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)

@aaumsu
👌11😭5🔥31
ዩኒቨርሲቲው ከሁለት ሳምንት በኃላ ፈታለሁ ብሎ ቃል ከገባ በኃላ እንደገና ቃሉን በማጠፍ "እንደዚህ አይነት ነገር አላልኩም" በማለት ቃሉን አጠፈ።

- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)

@aaumsu
😡21
2017 ዓ.ል ረመዳን ሲደርስ ተማሪው ከኒቃብ ጨምሮ ያሉትን ጥያቄዎች ሰብስቦ ቢያቀርብም ዩኒቨርሲቲው ምንም የተነሳ ጥያቄ እንደሌለ አድርጎ አቀረበ። ይህ ሲሆን ተማሪው ሙሉ ትኩረቱን ወደ ኒቃቡ ጉዳይ ሙሉ ትኩረቱን አዞረ።

- ሱደይስ አብዱረህማን (የጂማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሚር)

@aaumsu
🔥173