AAU - Muslim Students Union
7.85K subscribers
2.91K photos
185 videos
56 files
836 links
This is the official channel of AAU-MSU.

Group: @aaumsu_discussion
Youtube: youtube.com/@aaumsu
Twitter: x.com/aaumsu12
Facebook: facebook.com/profile.php?id=100087931837303

Contact us: @Aaumuslimstudentsunion1
Email: aaumsu12@gmail.com
Download Telegram
#ሕያው_ምስክር_2

በ ቅርብ ቀን ይጠብቁን!

@aaumsu
🔥16👏6
AAU - Muslim Students Union
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ለዩኒቨርሲቲው የUAT ፈተና፣ መመዝገቢያ እና ትራንስፖርት ወጪ ሽፋን በለቀቀው ፎርም መሰረት በቂ አመልካቾችን አጊኝተናል። በአሁኑ ሰዓት የተላኩልንን መረጃዎች የማጣራት እና የማረጋገጥ ስራ እየሰራን የምንገኝ ሲሆን፤ መረጃቸውን አጣርተን ላፀደቅናቸው ተማሪዎች ነገ ኢንሻአላህ የምናሳውቅ ይሆናል። በተጨማሪም የሌሎች ተማሪዎችን ወጪ ለመሸፈን የሚያስችል…
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ለዩኒቨርሲቲው የUAT ፈተና፣ መመዝገቢያ እና ትራንስፖርት ወጪ መሸፈን የማይችሉ ልጆችን ለመደገፍ በለቀቀው ፎርም ተመዝግባችሁ እስካሁን ያልተደወለላችሁ ወንድም እና እህቶች፤ ስልካችሁን ማግኘት ስላልቻለን በ @Aaumuslimstudentsunion1 እንድታናግሩን እንጠይቃለን።

@aaumsu
5🔥2👍1🥰1
በአባጂፋሯ ጅማ የተገፈፈ ክብር፤ የተከለከለ ሒጃብ ... በአባጂፋር ልጆች የተደረገ ትግል፤ የተከፈለ መስዋዕትነት፤ የተረጋገጠ ክብር --- በጅማ ዩኒቨርስቲ !

ሕያው ምስክር - 2

አባጂፋር (ረህመቱላሂ ዐለይሂ) ከጅማ መምለካ ተሻግረው፤ ሐበሻንም አቋርጠው ስለሙስሊሞች መብት የሚብሰለሰሉ፤ የሚታገሉ፤ መስዋዕትነት የከፈሉ ታላቅ እና ፍትሐዊ ንጉስ ነበሩ። ሆኖም ግን ከአመታት ቡሃላ፤ በጅማ ከተማ፤ በጅማ ዩኒቨርስቲ ቅጥር ግቢ ውስጥ ሙስሊም ተማሪዎች ባይተዋር ሆኑ። ሙስሊም ስለሆኑ ሊለብሱት ግዴታ የሆነውን ሒጃብ (ኒቃብ) ከመልበስ ተከለከሉ። ለተከታታይ አስር አመታት ያክል በተለያየ ጊዜ፤ በተለያዩ ሰዎች ክብራቸው ተደፈረ።

ይህ እየሆነ ባለበት በ2017 ዓ.ል የአባጂፋር ልጆች መብታቸውን ያስከብሩ ዘንድ የአላህ ፍቃድ ሆነ። በወርሐ ረመዷን ከተራዊህ መልስ ኒቃቢስት ተማሪዎች ወደ ግቢ ካልገቡ እኛም አንገባም በማለት ለተከታታይ አራት ቀናት ታገሉ። መሪዎቻቸው ቢታሰሩም ፀንተው ቆሙ። በአላህ ፈቃድም በፍትሐዊው ንጉስ ሐገር የተነፈገው ነፃነት ተከብሮ ፍትሕ ፀና።

የነበረውን ሂደት፤ የተፈጠሩትን ክስተቶች፤ የመጣውን ውጤት በሕያው ምስክር - 2 የምንዳስስ ይሆናል።

መስከረም - 1
ጁምዓ ከምሽቱ 3:00 ጀምሮ !


በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ (@aaumsu) እንገናኝ። መልዕክቱ ለሁሉም ይደርስ ዘንድ share ያድርጉ።

@aaumsu
🔥255👏3
"የተማሪዎችን እርካታ አስመልክቶ በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ፖሊስ ምርምር፤ የአመራር ልማት መርሐግብር እና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የ2018 አፈፃፀም ዙሪያ በተዘጋጀው መድረክ ላይ የቀረበው ጥናት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን ሁኔታ በግልፅ ያሳየ ነው።" - የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት

ሸገር FM ባወጣው ዘገባ እንዳስቀመጠው የተማሪዎች እርካታን አስመልክቶ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ 47 ዩኒቨርስቲዎች በመጨረሻው ደረጃ ላይ ተቀምጧል። ይህ ውጤት ባለፉት ሁለት አመታት ዩኒቨርስቲው የተማሪዎችን ሐይማኖታዊ እና ሰብዓዊ መብቶች የሚጥሱ መመሪያዎችን በማውጣት፤ በሐይማኖታቸው ጣልቃ ገብቶ ሒጃብ መልበስን በመከልከል፤ ተማሪዎች ትኩረታቸውን ወደ መብት ጥያቄ እንዲያደርጉ በማድረግ የፈፀመውን የአመራር ውድቀት በግልፅ ያሳያል። የተፈጠሩ ችግሮችን በውይይት ከመፍታት ይልቅ ለተማሪዎች ምላሽን በመንፈግ ውጪ እንዲያድሩ በማድረግ፤ በምርቃት ቀናቸው ከእስር ቤት እንዲውሉ በማድረግ፤ ከተመረቁም ቡሃላ መብታቸውን የጠየቁ ተማሪዎችን ዲግሪ በመከልከል የፈፀማቸው አንጋፋ የመብት ጥሰቶች ተጠቃሽ ናቸው።

መሠል ስህተቶች እንደ ሀገር አርዓያ ሊሆን የሚገባው ተቋም ሀገር ውስጥ ከሚገኙ ተቋማት ጭራ እንዲሆን ከማድረጋቸው ባሻገር የመጪውን ትውልድ ተስፋ የሚያቀጭጩ በመሆናቸው ውጤቱን ከመገምገም ባሻገር መሬት ላይ ያለውን ችግር በመፍታት እና ይህንን አንጋፋ ቅሌት ያመጡ አካላትን ተጠያቂ በማድረግ የሚመለከተው አካል ሁሉ እንዲረባረብ እንጠይቃለን።

@aaumsu
🔥327👌5💯4
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ የሐሩን ሚዲያ ምላሽ ምንድን ነበር? https://vt.tiktok.com/ZSq85g9u5/ ያዳምጡ፤ ሪፖስትም ያድርጉ።

@aaumsu
👍15👌3
ኢማን ሬድዋን እንኳን ደስ አለሽ!

በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የ4ተኛ አመት ፋርማሲ ተመሪ የሆነችው እህታችን ኢማን ሬድዋን እንደ አፍሪካ በተደረገ የጤና ስርዓት ኢንተርፕረይነሮች ውድድር ላይ በመሳተፍ አሸናፊ ሆና 2500 ዶላር ተሸላሚ ሆናለች። ይህ ስኬት የትጋቷ እና ጥረቷ ውጤት ነው። ከሷ አልፎ ለሁሉም ተማሪዎች አርአያ በመሆን ሙስሊሙ ጠንክሮ መማርና የሆነ አስተዋጽኦ ለማህበረሰቡ ማበርከት እንዳለበት መልእክት ያስተላልፋል ።

አላህ ይባርክልሽ! ከላቁ ስኬቶችም ደጋግሞ ያድርስሽ!!!! መብሩክክክክክክ!!!

@aaumsu
👏53🎉149🔥7🥰5
ወደ ዩኒቨርስቲዎች በተለይም ጂማ እና ሐረማያ ለመግባት ላሰባችሁ በዘንድሮ ኢንትራንስ ላለፋችሁ ተማሪዎች፦

ዩኒቨርስቲዎቹ ምን ይመስላሉ? ምን ምን አይነት ዲፓርትመንቶቹ አሉ? በየትኞቹ ዘርፎችስ የተሻሉ ናቸው? ከእኛስ ምን ይጠበቃል በሚሉ እና በሌሎች ነጥቦች ዙሪያ ጥልቅ ውይይት ለማድረግ ቀጠሮ ይዘናል። ስለ ሁሉም ዩኒቨርስቲዎች ጠቅለል ያለ መረጃ ይሰጣል።

ተጋባዥ እንግዶች፦

፨ Muhammaddin Muhidin (በጅማ ዩኒቨርስቲ የ5ተኛ አመት ሜዲስን ተማሪ እና የጀመዓው ምክትል አሚር)

፨ Faris Mustefa (የሐረማያ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ ምክትል አሚር)

የፕሮግራሙ አስተባባሪ፦ ሚፍታህ ኢብራሒም ነው።

ፕሮግራሙ፦ ነገ ማለትም እሁድ ጷጉሜ 1 / 2018 ዓ.ል ከምሽቱ 3:00 ጀምሮ @MohammadamminKassaw ይሰጣል። በፕሮግራሙ ላይ መመለስ አለባቸው የምትሏቸውን ጥያቄዎች @MOHAMMADAMMINM ላኩልን። መረጃውን ለሁሉም ይደርስ ዘንድም Share አድርጉት።

@aaumsu
👍62👏1
1_UAT_Test_Taker_Schedule_–_AAU_Test_Site_–_September_7–8,_2026.xlsx
574.7 KB
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቅድመ ምረቃ አዲስ ገቢ ተማሪዎች መግቢያ ፈተና ጷጉሜ 2 እና 3 ይሰጣል። የተፈተኞች ዝርዝር እና የመፈተኛ ቦታ፣ እንዲሁም የፈተና ሰዓት ከላይ ተያይዟል።

@aaumsu
7
ለግፍ ያላጐነበሰው ንጉሥ 👑

ክፍል 4

ነጃሺ ኢስላምን መቀበሉን ግልጽ አድርጎ ለነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) ዳብዳቤ ጻፈ::
ደብዳቤው የሚከተለው ነበር ፡-

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩኅ በጣም አዛኝ በሆነውይድረስ ለሙሐመድ-የአላህ መልዕክተኛ-ከነጃሺ አስሐማ፡፡

“ከአላህ የሆነ ሰላምታ በእርስዎ ላይ ይሁን-የአላህ ነቢይ፤እዝነቱና በረከቱም ይሁንብዎ፤ ወደ ኢስላም ከመራኝ አላህ በቀር ሌላ ሊገዙት የሚገባ አምላክ እንደሌለ እመሰክራለሁ::
ከዚህም በመቀጠል የአላህ መልዕክተኛ ደብዳቤዎ ደርሶኛል። በሰማይና በምድር ጌታ እምላለሁ፡፡ ስለማርያም ልጅ ዒሳ (ኢየሱስ) የጠቀሱልኝን በተመለከተ ራሱ ዒሳም ቢሆን እርስዎ ካሉት የጨመረው ነገር የለም:: ወደኛ የተላኩበትን ምክንያት አውቀናል፡፡ እርስዎም የአላህ መልዕክተኛ መሆንዎን፣ እውነተኛ እና በሐቅ መስካሪ (ሊተማመኑብዎት የሚገባዎ) መሆንዎን ተገንዝበናል፡፡ ለዚህም ቃል ኪዳን ገብቻለሁ:: የአጎትዎን ልጅ ቃል ኪዳን ፈጽሜለታለሁ:: የዓለማት ጌታ ለሆነው ለአላህም እጅ ሰጥቻለሁ።”

ነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) ኡሙ ሐቢባን (ረምላ ቢንት አቢ ሱፍያንን) ለማግባት በሁለተኛው ደብዳቤያቸው ነጃሺን ጠየቁ፡፡ ነጃሺም ነቢዩን (ሰ.ዐ.ወ)ወክሎ ኒካሁን አስፈጽሟል፡፡
ለኢስላም ስትል ወደ ሐበሻ ከነባሏ የተሰደደችው ኡሙ ሐቢባ ቢንት አቢ ሱፍያን ባሏ እምነቱን በመቀየሩና በመሞቱ ነቢዩ እጅግ አዘኑ፡፡
ልቧ ክፉኛ የተሰበረውን ኡሙ ሐቢባን ራሳቸው ለማግባት ወሰኑ፡፡ ለዚህም ነበር በዐምር ኢብኑ ዑመያ አል-ደሚሪይ አማካኝነት መልዕክት ወደ ነጃሺ የላኩት:: ነጃሺም መልዕክቱ ሲደርሰው ለኡሙ ሐቢባ ቢንት አቢ ሱፍያን በቤተ መንግሥቱ አገልጋይ በነበረችው አብረኸት መልዕክት ላከባት:: ልቧ ተሰብሮ የነበረው ኡሙ ሐቢባ ዜናው በአብረኸት አማካኝነት ሲደርሳት እጅግ ተደሰተች፡፡ ጋብቻው ይፈጸም ዘንድ ኻሊድ ቢን ሰዒድን ወከለች:: እጅግ ከመደሰቷ የተነሳም የምሥራቹን ለነገረቻት አብረኸት የተለያዩ የብር ጌጣጌጦችን ሰጠቻት::
ይህ ውቡ ታሪካችን ነው ከራስ አልፎ ለሌላው አለም መትረፍን የምንማርበት ፤ንጉስ ነጃሺም ከራሳቸው አልፈው ሌሎች በሃቅ ጎዳና ላይ እንዲገኙ ሚናቸውን በሚገባ ተወጥተዋል።

ነገር ግን የነጃሺ መስለም ዛሬም ድረስ ሲተረክ ለመቀበል የማይፈልጉ አካላት አሉ::
በእርግጥ እነኚህ ወገኖች አንድ የክርስቲያን ንጉሥ ሊሰልም የማይችልበትን ሁኔታ ማሳየት አልቻሉም።

ያለ መረጃ እንዲሁ ማጣጣልን መርጠዋል::
ነጃሺ ኢስላምን መቀበሉ ብቻ ሳይሆን ዳዕዋ በማድረግ ያስለማቸው ግለሰቦችም ነበሩ።

ከነዚህ መካከል ዐምር ኢብኑል ዓስ ይገኝበታል። ዐምር ሶሓቦችን
ወደ መካ ለማስመለስ ተልኮ ሳይሳካለት ከተመለሰው የቁረይሽ ልዑክ አንዱ እንደነበር ይታወሳል።
በበርካታ ጥንታዊ ኢስላማዊ መዛግብት ላይ እንደተዘገበው ዐምር ኢብኑል ዓስ ኢስላምን የተቀበለው በንጉሥ ነጃሺ እጅ ነበር።
ይህ ሊሆን የቻለው ዳግም ወደ አክሱም በተመለሰበት ጊዜ ነበር፡፡ ዐምር ኢብኑል ዓስ እንዲህ ይተርክልናል፡-
ከኸንደቅ ጦርነት በኋላ ከቁረይሽ ጎሳ መካከል ንግግሬን የሚሰሙኝንና የሚያከብሩኝን ሰዎች ሰበሰብኩ፡፡
“እንደምታዩት የሙሐመድ ነገር (ለኛ) ከቀን ወደ ቀን በሚያስጠላ ሁኔታ እያየለና እየበረታ ሄደ። እኔ አንድ ሐሳብ አለኝ::
በርሱ ላይ ምን ትላላችሁ? ስል ጠየቅኳቸው:: ‹‹ምን አሰብክ?›› አሉኝ፡፡
‹‹ወደ ነጃሺ እንሂድና ከእርሱ ዘንድ እንሁን፡፡ ሕዝባችንን ሙሐመድ ካሸነፈ በነጃሺ ግዛት ስር ሆንን ማለት ነው፡፡ ከርሱ ዘንድ መሆናችን በሙሐመድ ሥር ከመሆን ይልቅ ለኛ የተወደደ ነው:: ሕዝቦቻችን ካሸነፉ ደግሞ በእርግጥ በነርሱ ዘንድ ስለምንታወቅ መልካም ሁኔታ እንጂ አይገጥመንም›› አልኳቸው::
‹‹መልካም ነው› በማለት ከኔ ሐሳብ ጋር ተስማሙ:: ለነጃሺ የሚሰጡትን ስጦታዎች እንዲያሰባስቡ ነግሬያቸው ወደርሱ አገር ተጓዝን::

የነቢዩ መልዕክተኛ ዐምር ኢብኑ ዑመያ አል ደሚሪይ በነ ጃዕፈርና በሶሓባዎች ጉዳይ ከነጃሺ ዘንድ ገብቶ ሲወጣ አየነው::

ለወዳጆቼ “ይህ ዐምር ኢብኑ ዑመያ አል-ደሚሪይ ነው:: ከነጃሺ ዘንድ ገብቼ ስጦታዎችን ሰጥቼው የዚህን ሰው አንገት እንድቆርጥ (እንድገድለው) ጠይቄ ቢፈቅድልኝና ይህን ባደርግ የሙሐመድን መልዕክተኛ በመግደሌ ቁረይሾች ትልቅ ውለታ እንደዋልኩላቸው (ምንዳ እንደከፈልኳቸው) ይቆጥሩ ነበር›› አልኳቸው:: ነጃሺ ዘንድ ገባሁ:: ከዚህ በፊት እንደማደርገው ለርሱ (ለሰላምታ) አጎነበስኩ፡፡

ነጃሺም ‹እንኳን ደህና መጣህ ወዳጄ›› አለኝ:: በርካታ ስጦታም ሰጠሁት:: (በኋላ ላይም) ዐምር ‹‹የጠላታችን ሙሐመድ መልዕክተኛ ከአንተ ዘንድ ገብቶ ሲወጣ አየሁት:: (ከቁረይሽ) ታላላቆቹና ምርጦቹ ተገደሉ፡፡
ስጠኝና ይህን ሰው ልግደለው›› ስል ጠየቅሁት::
ነጃሺ በጥያቄው ክፉኛ ተናደደ።
ዐምርም በነጃሺ አኳኋን ተደናገጠ፡፡
‹‹ምናለ መሬት ተቀዳ በዋጠችኝ!›› እስኪል ድረስ የቁጭት ስሜት ተሰማው፡፡

‹‹ንጉሥ ሆይ! ይህ ጉዳይ እንዲህ የሚያናድድዎ መሆኑን ባውቅ አልጠይቆትም ነበር›› ሲል ተናገረ፡፡

ነጃሺም ‹‹ለሙሴ ይመጣ የነበረው መልአኩ ገብርኤል (ጂብሪል) የሚመጣለትን ሰው መልዕክተኛ ልትገድል ትጠይቀኛለህን?›› ሲል በቁጣ ተናገረ፤ገሰጸው፡፡
ዐምርም ‹‹ንጉሥ ሆይ! እንደዚያ ነው እንዴ?›› ሲል ጠየቀ።
ነጃሺም ‹‹ወየውልህ ዐምር! እኔን ታዘዘኝና እርሳቸውን (ነቢዩ ሙሐመድን) ተከተላቸው፡፡ በአላህ እምላለሁ! ሙሴ በፊርዓውንና ሠራዊቱ ላይ ድል እንዳደረገ ሁሉ
ሙሐመድም በእውነት በተቃዋሚዎቹ ላይ ድል ማድረጉ የማይቀር ነው› አለ፡፡

ዐምር ‹‹በኢስላም ላይ ቃል ኪዳን ተጋባኝ›› ሲል ነጃሺን ጠየቀ። ነጃሺም “መልካም›› በማለት እጁን ዘርግቶ ከዐምር ኢብኑል ዓስ ጋር በኢስላም ላይ ቃል ኪዳን ተጋባ። በነጃሺ ግሳጼና ዳዕዋ የተማረከው ዐምርም ኢስላምን በነጃሺ እጅ ተቀበለ።

ዐምር ትረካውን ይቀጥላል፡- “እጄን ዘርግቼ በኢስላም ላይ ቃል ኪዳን ተጋባሁ:: ከርሱ ዘንድ ስወጣ መስለሜን ከወዳጆቼ ደበቅሁ:: ወደ ነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) ተጓዝኩ:: ጊዜው ከፈትህ (hመካ በድል መከፈት) በፊት ነበር፤ወደ መዲና ስሄድ በመንገድ ላይ ኻሊድ ኢብኑ ወሊድን አገኘሁት::

የሱለይማን አባት ወዴት ነው?› ስል ጠየቅኩት:: ሊሰልም እንደሚሄድ ነገረኝ። «በአላህ ይሁንብኝ! እኔም ለእስልምና ስል ነው የመጣሁት› ስል ገለጽኩለት::
መንገድ ላይም ዑስማን ቢን ጠልሀን አግኝተው ተያይዘው ሄዱ፡፡
ዐምርም ሙስሊምነቱን ይፋ አድርጎ ከነቢዩ ጋር ቃል ተጋባ፡፡
ነቢዩን (ሶ.ዐ.ወ) አገኛቸውና ‹‹የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! እኔ ያለፈው ወንጀሌ እንዲማርልኝ  መስፈርት በማድረግ ከርስዎ ጋር ቃል ኪዳን ልጋባ›› አላቸው፡፡ ነቢዩም (ሶ.ዐ.ወ) ‹‹ዐምር ሆይ! ቃል ኪዳን ተጋባኝ! ኢስላም ከርሱ በፊት የነበረውን ኃጢአት ያብሳል:: ስደትም ከርሱ በፊት የነበረውን ያብሳልና›› አሉ::

በነጃሺ እጅ የሰለመው ዐምር ኢብኑል ዓስ ያለፈው ወንጀሉና ጥፋቱ እንዲማርለት ከነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) ጋር ቃል ኪዳን ተጋባ፡፡
በዚህም ሐበሻዊው ሙስሊም ንጉሥ ነጃሺ ዐምርን ማስለም ቻለ፤
ዐምርም በ640 ግብጽን በመክፈት ከእስላማዊው የኸሊፋ ግዛት ጋር የቀላቀለ ታላቅ ሳሃባ ነበር።
በእርግጥም ኋላችን ትግል ያዋዛው፣ መማሪያ፣ መገሰጫ እና መንቂያ ደዉል መሆን በሚችል መልኩ ሰፍሯል።
እኛስ?ለወደፊቱ ትውልድ መቅረቡ ግድ የሆነውን ታሪካችንን በምን መልኩ እየጻፍነው ይሁን?

የመጨረሻው ክፍል ይቀጥላል…

@aaumsu
🥰112