AAU - Muslim Students Union
7.85K subscribers
2.91K photos
184 videos
54 files
835 links
This is the official channel of AAU-MSU.

Group: @aaumsu_discussion
Youtube: youtube.com/@aaumsu
Twitter: x.com/aaumsu12
Facebook: facebook.com/profile.php?id=100087931837303

Contact us: @Aaumuslimstudentsunion1
Email: aaumsu12@gmail.com
Download Telegram
"ምንም ነገር ቢፈጠር ወደኃላ አንመለስም። ትምህርታችንንም አንተውም"

- በጊዜው በዲላ ዩኒቨርሲቲ የነበሩ ሙስሊም ተማሪዎች

@aaumsu
🫡2152🥰2
"በሰላማዊ መንገድ መጓዝን ምርጫችን አድርገን እየተንቀሳቀሰን ሳለ እነሱ ግን ወደ ማስፈራራት፤ መረበሽ፤ ልጆችን አትመረቁም በማለት፣ ቤተሰብን በመጥቀስ ለማስፈራራት ሞክረዋል።"

@aaumsu
🔥181
«ኢማን ባይሆን! የአኺራ ጉዳይ ባይሆን ኖሮ ለማለፍ አስቸጋሪ ነበር!»

ሊከለክሉን የሞከሩት ሰዎች ያልገባቸውና እኛ ብቻ የሚገባን ቁልፍ ነገር ይህ ነው።

ሁሉ የሆነው ለዚያ ነው። ... ኢማን ስለሆነ!!!

@aaumsu
🔥20👌74💯2🤗2
"የእናንተ ክብር ማለት የኡማ ክብር ነው!"

- የዲላ ዩኒቨርሲቲ ወንድ ሙስሊም ተማሪዎች

@aaumsu
🔥28👌5🥰32👍2🏆1
"ጭራሽ ሊያግዙን ይችላሉ ብለን ያልገመትናቸው እህትና ወንድሞች፣ መምህራን፣ ሰራተኞች አብረውን ተሰልፈው ነበር።"

@aaumsu
19🔥11👏6🤗2
Live stream finished (2 hours)
الحمد لله الذي بنعمته تتم الصالحات

ፕሮግራማችን ባማረ ሁኔታ ተጠናቋል።

የዲላ ዩኒቨርሲቲን ታሪካዊ የመብት ትግል ላጋሩን፤ እንደ ታላቅ ወንድም፤ እንደ አሚር እና እንደ ኡስታዝ ሆነው ምክራቸውን ላካፈሉን የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ የቀድሞ አሚር ኡስታዝ ኑረዲን አብደላህ ከልብ እናመሰግናለን።

እንዲሁምፕሮግራሙ እንዲሳካ ለተነቀሳቀሱ እህት እና ወንድሞች ሁሉ ጀዛኩሙሏሁ ኸይራ ማለት እንወዳለን!

መጀመሪያ አካባቢ ስለነበረው የኔትዎርክ መቆራረጥ ይቅርታ እየጠየቅን፤ በቀጥታ መከታተል ላልቻላችሁ ሪከርድ የሚለቀቅ ይሆናል።

ህያው ምስክር ፕሮግራማችን በቀጣይም ከሌላ እንግዳና ሌላ አስተማሪ የትግል ታሪክ ጋር በቅርቡ የሚመለስ ይሆናል።

@aaumsu
21🔥11👏2🫡2🥰1👌1
በአላህ ስም እጅግ በጣም ርኅሩኅ በጣም አዛኝ በሆነው!

በመጀመሪያ ጥሪያችንን አክብራችሁ ስለተገኛችሁ ኡስታዝ ኑረዲን፣ እንዲሁም መላው ተሳታፊ ወንድምና እህቶች በአላህ ስም እጅግ አድርገን እናመሰግናለን። ለተፈጠረው የኔትወርክ ችግርም ይቅርታ እንጠይቃለን።

በመቀጠል፤ ከዲላ ዩኒቨርሲቲ ትግል ብዙ የተማርናቸው ትምህርቶች አሉ። የነበረው ወኔ፣ ጥንካሬ እና ህብረት እጅግ የሚያስደንቅ ነበር። አላህ በሰማነው ተጠቃሚ ያድርገን፤ ምክራቸውንም ተቀብለናል። በአላህ ፈቃድ "ከትግል በኋላ ድል እንደሚመጣ" የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ጀማ ሕያው ምስክር ሆኖ ቀርቦልናል።

ይህንንም ተከተሎ ጀማችን ወይም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት፤ ዲላ ላይ ጀግንነት እና ቁርጠኝነት ላሳዩት ወንድምና እህቶች፣ እንዲሁም በጀማቸው ስም ስጦታ ማበርከት ይፈልጋል። ስጦታውንም በሚመጣው ዓመት የWelcome Program ላይ ኡስታዝ መጥተው ይቀበሉን ዘንድ በአክብሮት እንጠይቃለን።

ሙሀመድ ኢድሪስ (የአአዩሙተህ ፕሬዝዳንት)

@aaumsu
🔥193👏1
ሀሳን ኢብኑ ሳቢት ልዩ የስነ-ፅሁፍ ውድድር !

በተደረገው ጥሪ መሠረት ብዙዎች ብዕራቸውን አንስተው ስንኞችን በመቋጠር፤ ሐሳቦችንም በመደርደር በውድድሩ ላይ ተሳትፈዋል። ውድድሩ ስለሕዝበ ሙስሊም የመብት ጥያቄ፤ ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጉዳይ፤ ስለክብራችን፤ ስለነፃነታችን የመክተብ ነው። በግጥምም ሆነ በዝርው፤ ገጠመኝም ሆነ ማንኛውንም ሐሳብ ማቅረብ ይቻላል።

ከ1-3 የሚወጡ ተሸላሚ የሚሆኑ ይሆናል።

1ኛ፦ 1500 ብር፤ የምስክር ወረቀት እና ተጨማሪ ልዩ ስጦታዎች

2ኛ፦ 1000 ብር፤ የምስክር ወረቀት እና ተጨማሪ ልዩ ስጦታዎች

3ኛ፦ 500 ብር፤ የምስክር ወረቀት እና ተጨማሪ ልዩ ስጦታዎች

የጥበብ ውጤቶቻችሁን @Niqab_issueBot ላኩልን።

@aaumsu
🔥93
ለግፍ ያላጐነበሰው ንጉሥ 👑

ክፍል 1

ከዘመናት በኋላ በታሪክ ውስጥ አሻራውን ጥሎ ያለፈ አንድ ታላቅ ሰው ወዳፈራችዉ ምድር እንሻገር…………

በዙሪያው ያለው ኃይል ሁሉ በእጁ በነበረበት ጊዜ በምሕረቱ፣

ማንም ሊገዳደረው በማይችልበትና ሊበድል ቢፈልግ አንዲት ስራው በቂ በነበረችበት ሰዓት ደግሞ በፍትሑና በዕኩልነቱ የታወቀ ንጉሥ።

ዓለም በሩን የከፈተለት፣ ተግባሩ ምንም ኃይልና አቅም የሌላቸውን ምስኪን እንግዶች ዕጣ ፈንታ መቀየር የቻለ ታላቅ ሰው።


ከዚህም ጋር እንግዶቹ በመጡ ጊዜ ስለ ኃይላቸው፣ ስለ ብዛታቸው ወይም ለእርሱ ሊያበረክቱት ስለሚችሉት ነገር አንዳችም ጥቅማ ጥቅምን አልጠየቀም።

ይልቁንም አዳመጣቸው፤
ከዚያም ቀላል የማይባል፣ የታሪክ ሚዛኑን ሙሉ በሙሉ የቀየረና ያስዋበን ፤እስከ ዛሬ ድረስ በዚች ምድር ላይ አሻራውን ያኖረ ቆራጥ ውሳኔን ወሰነ።

የታሪክ መጻሕፍት በፍትሕ የመሰከሩለት፣

በሙስሊሞች ልብ ውስጥም ስሙ ከትልልቅ የፍትሕና የሰላም ምዕራፎች ጋር ተያይዞ የሚነሣ ታላቅ ስብዕና።

ታዲያ ይህ ንጉሥ ማን ነው?

ወደ ምድሩ የተሰደዱትስ እነማን ናቸው?

ከሐበሻ ምድር ታሪክ ውስጥስ የእርሱ አቋም ለምን ትልቁን ቦታ ያዘ?

ይህ ሰውስ እንዴት የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ታሪክ ዋና አካል ሊሆን ቻለ?

የዛሬው ትግላችን ሊጀምር ሚገባው ከትላንቱ ታሪካችን ከዚህ ነው።

💫ዉዱ ንጉሣችን…………
💫አርአያችን ……..
💫የፍትህ ምሳሌያችን……..
💫ዉቡ ታሪካችን…….

ስንታገል ርቀታች እኛው ለእኛው ከመሆን አልፎ ለሌላው እስከመድረስ  ጭምር  እንዲሆን ተምሰሌት የሆነን መሪ

ይህ ታላቅ ስብዕና👇

ንጉሥ አል-አስሐማ ቢን አብጀር (ነጃሺ) ነው።

የኢስለም አሀዳዊ ጥሪን ፈጽሞ መስማት ያልፈለጉት የመካ ቁራይሾች በሙስሊሞች ላይ የቅጣት በትራቸውን አሳረፉ።

አማኞች ግፍና መከራን አስተናገዱ። ችግርና እንግልት ተከተላቸው። ከእምነታቸው በመመለስ እንደነርሱ የጣኦት አምልኮን ይከተሉ ዘንድ ማዕቀብ ስቃይና ጥቃት ተፈጸመባቸው።


ነብዩ ሙሀመድ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ) በባልደረቦቻቸው ላይ የሚፈጸመውን ጥቃት ሊከላከሉ እንደማይችሉ ሲገነዘቡ ወደ ሀበሻ ምድር እንዲሰደዱ መከሯቸው። እንዲህም አሏቸው :-

“ወደ ሀበሻ ተሰደዱ። በእርሷ ዘንድ አንድንጉስ አለ። ከእርሱ ፊት ማንም ተበዳይ አይሆንም፣ስለዚህ ተሰደዱ። አላህ ካላችሁበት ሁኔታ አውጥቶ ድልን እስክንጎናጸፍ ድረስ። “

በዚህም መሰረት የነብያቸውን ትእዛዝ ተቀብለው በ5ኛው የነብይነት አመት የመጀመሪያውን ስደት 12 ሆነው በጀልባ ለ1 ሰው ግማሽ ዲናር ከፍለው ወደ ሀበሻ ተጓዙ።

በገዛ ሀገራቸው ያጡትን የአምልኮ ነጻነት በሀበሻው መሪ አስሃማ ወይም ነጃሺ አገዛዝ ስርም ተጎናጸፉ።

የነብዩ ሙሀመድ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ባልደረቦች በሀበሻ የገጠማቸውን እንዲህ ሲሉ መስክረዋል:-


……..ክፍል 2 ይቀጥላል

@aaumsu
11👍6🔥2
ሕያው ምስክር - 1
Ustaz Nureddin Abdellah
ሕያው ምስክር - 1

በ11 ብርሃናማ ሌሊቶች መፍትሔ የተገኘለት የ11 አመታት የመብት ጥያቄ --- በዲላ ዩኒቨርስቲ !

አቅራቢ፦ ኡስታዝ ኑረዲን አብደላህ (የዲላ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት የቀድሞ አሚር)

አዘጋጅ፦ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት !!

@aaumsu
🔥14🏆32👌21
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
Haqni hawaasa tokkoof dhabame, hawaasa hundaaf balaadha. Gaaffiin barattoota Muslimaa AAU gaaffii mirga namummaa ti malee dhimma amantii qofa miti!

Sagaleen keenya namoota dabalataatiin akka gahuuf viidiyoo kana share godhaa: https://www.tiktok.com/@aaumsu/video/7677097862420811029

@aaumsu
🔥17
ጀመዓችን የኢንስታግራም አካውንት በከፈተ አንድ ወር ውስጥ

፨ ከ3000 በላይ ተከታዮች
፨ 259,355 View
፨ 19,769 Like

ማግኘት ተችሏል። በመድረኩ የተለያዩ ይዘቶችን በማጋራት ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥሰት ድምፅ ለመሆን፤ ስለተለያዩ ጉዳዮች ግንዛቤ ለመፍጠር ተሞክሯል። ሚዲያ ሀሳቦቻችንን የምንሸጥበት፤ መልዕክታችንን የምናስተላልፍበት ብሎም አጀንዳዎቻችንን የሁሉም አጀንዳ የምናደርግበት መድረክ ነውና https://www.instagram.com/p/DcYr4y-jfXo/?img_index=3&igsi=dmc1d3VnbGg5OHg5 በመግባት አካውንታችንን Follow አድርጉ። ለሁሉም ተደራሽ ይሆን ዘንድም አሰራጩ።

እንኳን ደስ አለን 🎉🎉🎉 !!!

@aaumsu
🎉324🔥1🤩1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ሒጃቧ እምነቷ !

ለሁሉም ይደርስ ዘንድ በቲክቶክ https://vt.tiktok.com/ZSVHmXxjj/ በመግባት ኮፒሊንክ ሪፖስት ያድርጉ።

@aaumsu
🔥15👏2🫡2
UG_Extension_Program.pdf
1.3 MB
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መቀላቀል የምትፈልጉ የዘንድሮ 12ኛ ክፍል ተፈታኞች የማመልከቻ ጊዜ ከነገ ጀምሮ ለተከታታይ 10 ቀናት ክፍት እንደሚሆን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

ዝርዝር መረጃ ከላይ የተያያዙት ፋይሎች ላይ ማግኘት የምትችሉ ሲሆን ማንኛውም የሚያስፈልጋችሁ መረጃ ወይም እገዛ የሚኖር ከሆነ https://t.me/Aaumuslimstudentsunion1 ላይ ጻፉልን።

@aaumsu
👍101🥰1
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የሒጅራ ካላንደር ከነባሩ ካላንደር ጎን ለጎን እውቅና ተሰጥቶት ተግባራዊ እንዲደረግ መወሰነ በምክክር ፍትሕ ሊመጣ እንደሚችል ያመላከተ ነው !

ቪድዮው ለሁሉም ይደርስ ዘንድ https://vt.tiktok.com/ZSVxo8NXc/ በቲክቶክ በመግባት ኮፒሊንክ ሪፖስት አድርጉ።

@aaumsu
🔥71