ታድለን ቢሆን . . .
የሙስሊሙን ተማሪ መብት ማስከበር የሙስሊሙ ተማሪ ሀላፊነት ብቻ አልነበረም። ታድለን ቢሆን የተማሪዎቹን መብት አክብሮ ማስተማር የዩኒቨርስቲው ሀላፊነት ነበር። ግን አልሆነም! ታድለን ቢሆን ዩኒቨርስቲው መብታችንን ሲጥሱ መብታችንን የማስከበሩ ሀላፊነት የትምህርት ሚኒስቴር ነበር። ግን አልሆነም! ታድለን ቢሆን መብታችን ሲጣስ የማስከበሩ ሀላፊነት የሰላም ሚኒስቴር፣ የፍትሕ ሚኒስቴር፣ የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር ነበር። ግን አልሆነም! ታድለን ቢሆን እንደ ሙስሊም መብቶቻችንን የማስከበር ሀላፊነቱ የመጅሊስ ነበር። ግን አልሆነም!
አልሆነምና ተስፋ ቁረጡ የሚሉም አልጠፉም። ለሁሉም ግን አላህ በቅዱስ ቃሉ ያስቀመጠውን ድንቅ አንቀፅ አንብቡላቸው።
" الَّذِينَ قَالَ لَهُمُ النَّاسُ إِنَّ النَّاسَ قَدْ جَمَعُوا لَكُمْ فَاخْشَوْهُمْ فَزَادَهُمْ إِيمَانًا وَقَالُوا حَسْبُنَا اللَّهُ وَنِعْمَ الْوَكِيلُ
እነዚያ ሰዎቹ ለእነርሱ፡- «ሰዎች ለእናንተ (ጦርን) አከማችተዋልና ፍሩዋቸው» ይሉዋቸውና (ይህም) እምነትን የጨመረላቸው «በቂያችንም አላህ ነው ምን ያምርም መጠጊያ!» ያሉ ናቸው፡፡" [3:173]
ለሁሉም በቂ የሆነው አላህ መጠጊያችን ነው። ከእርሱ ወጪስ መጠጊያ አለን? ምንኛ ያማረ መጠጊያ ነው።
@aaumsu
የሙስሊሙን ተማሪ መብት ማስከበር የሙስሊሙ ተማሪ ሀላፊነት ብቻ አልነበረም። ታድለን ቢሆን የተማሪዎቹን መብት አክብሮ ማስተማር የዩኒቨርስቲው ሀላፊነት ነበር። ግን አልሆነም! ታድለን ቢሆን ዩኒቨርስቲው መብታችንን ሲጥሱ መብታችንን የማስከበሩ ሀላፊነት የትምህርት ሚኒስቴር ነበር። ግን አልሆነም! ታድለን ቢሆን መብታችን ሲጣስ የማስከበሩ ሀላፊነት የሰላም ሚኒስቴር፣ የፍትሕ ሚኒስቴር፣ የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር ነበር። ግን አልሆነም! ታድለን ቢሆን እንደ ሙስሊም መብቶቻችንን የማስከበር ሀላፊነቱ የመጅሊስ ነበር። ግን አልሆነም!
አልሆነምና ተስፋ ቁረጡ የሚሉም አልጠፉም። ለሁሉም ግን አላህ በቅዱስ ቃሉ ያስቀመጠውን ድንቅ አንቀፅ አንብቡላቸው።
" الَّذِينَ قَالَ لَهُمُ النَّاسُ إِنَّ النَّاسَ قَدْ جَمَعُوا لَكُمْ فَاخْشَوْهُمْ فَزَادَهُمْ إِيمَانًا وَقَالُوا حَسْبُنَا اللَّهُ وَنِعْمَ الْوَكِيلُ
እነዚያ ሰዎቹ ለእነርሱ፡- «ሰዎች ለእናንተ (ጦርን) አከማችተዋልና ፍሩዋቸው» ይሉዋቸውና (ይህም) እምነትን የጨመረላቸው «በቂያችንም አላህ ነው ምን ያምርም መጠጊያ!» ያሉ ናቸው፡፡" [3:173]
ለሁሉም በቂ የሆነው አላህ መጠጊያችን ነው። ከእርሱ ወጪስ መጠጊያ አለን? ምንኛ ያማረ መጠጊያ ነው።
@aaumsu
🔥21❤10⚡2
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
"አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ 2 ሶስት ቀን ኒቃብ አይከለከልም ቢል መፍትሔ መጣ አንልም። ምን ማለት ነው? እኛ የምንፈልገው በመመሪያ የፀና መብት ነው። ነገ የት ነው የምታስጮሁን ብለን ልንጠይቅ ነው?!" -
@aaumsu
@aaumsu
🔥24💯2
አልሐምዱሊላህ __ ታድለናል !
ገና ባልጠና ጉልበታችን፥ የብዙዎች ያልተሰራ የቤት ሥራ በጫንቃችን ላይ ተጣለብን።
ታድለን ...
የትውልድን ክብር በመጠበቅ ላይ ኃላፊነት ወሰድን።
ታድለን...
የእህታቸው ክብር እየተነካ፥ በሰላም ተኝተው የማያድሩ ዓይኖች ተሰጡን።
ታድለን...
ፍትሕ ስትቀበር «በእኔን ከተመቸኝ ይሁንታ» የማይቀበል አዕምሮ ተሰጠን።
ታድለን...
ቀን እስኪያልፍ የሚጎድልን ክብር የማይታገስ ልብ ተቸርን።
ታድለን...
ሌሎች የፈሩበትን ነገር በድፍረት የመጋፈጥ ወኔ ተሰጠን።
ታድለን...
«አዳኝ» እስኪመጣ ሳንጠብቅ፥ ኃላፊነታችንን የምንወጣበት ተቆርቋሪነት ተሰጠን።
እንደኛ የታደለ አለ እንዴ?!
ታድለን...
ፍትሕ መጓደል አመመን።
የመብታችን መጣስ ቆረቆረን።
ጭቆና አንገሸገሸን።
ደግሞ እንደኛ የታደለ አለ እንዴ?!
ታድለንማ'ኮ...
ታሪክ "ካላጎነበሱት" መካከል መዘገበን።
መስዋዕትነት ከገባቸው፤
ትውልዳቸውን ለመታደግ ቁርጠኛ ከሆኑት መሃል መዘገበን።
ደግሞ እንደኛ የታደለ አለ እንዴ?!
ታድለንማ'ኮ...
በአላህ ላይ ከሚመኩት፣
ለመንገዱ ከሚታመኑት፤
ድልንም ከርሱ ብቻ ከሚጠብቁት ሰራዊቶቹ መሃል አደረገን።
ደግሞ እንደኛ የታደለ አለ እንዴ?!
ለኛ የተሰጠው ለማን ተሰጥቷል?! - ዙሪያችሁን አትመለከቱምን?!
በህይወታችን ካየናቸው ብዙ ብዙ ብቸኝነቶች ውስጥ፥ በዚህ የትግል መንገድ ላይ ያለ ብቸኝነትን ያህል ዋጋ ያለው ብቸኝነት የት እናገኛለን?!
አላህ የሚያየው፣ የሚመሰክርለት ብቸኝነት!
ወደ ድል እንጂ የማይደርስ፣ ውድቀት የሌለበት ብቸኝነት!!
ትርጉሙ ጥልቅ፣ ክፍያው ብዙ ብቸኝነት!!!
ይህ እንደዋዛ 'ሚገኝ ነው እንዴ 'ሚመስለን?! በፍጹም።
ለዚህ ብቸኝነት መመረጥ ያሻዋል።
ይህ'ኮ ታላቅ ጸጋ እንጂ ሌላ አይደለም።
አልሐምዱሊላህ!!!
ሐስቡነላህ ወኒዕመል ወኪል!!!
@aaumsu
ገና ባልጠና ጉልበታችን፥ የብዙዎች ያልተሰራ የቤት ሥራ በጫንቃችን ላይ ተጣለብን።
ታድለን ...
የትውልድን ክብር በመጠበቅ ላይ ኃላፊነት ወሰድን።
ታድለን...
የእህታቸው ክብር እየተነካ፥ በሰላም ተኝተው የማያድሩ ዓይኖች ተሰጡን።
ታድለን...
ፍትሕ ስትቀበር «በእኔን ከተመቸኝ ይሁንታ» የማይቀበል አዕምሮ ተሰጠን።
ታድለን...
ቀን እስኪያልፍ የሚጎድልን ክብር የማይታገስ ልብ ተቸርን።
ታድለን...
ሌሎች የፈሩበትን ነገር በድፍረት የመጋፈጥ ወኔ ተሰጠን።
ታድለን...
«አዳኝ» እስኪመጣ ሳንጠብቅ፥ ኃላፊነታችንን የምንወጣበት ተቆርቋሪነት ተሰጠን።
እንደኛ የታደለ አለ እንዴ?!
ታድለን...
ፍትሕ መጓደል አመመን።
የመብታችን መጣስ ቆረቆረን።
ጭቆና አንገሸገሸን።
ደግሞ እንደኛ የታደለ አለ እንዴ?!
ታድለንማ'ኮ...
ታሪክ "ካላጎነበሱት" መካከል መዘገበን።
መስዋዕትነት ከገባቸው፤
ትውልዳቸውን ለመታደግ ቁርጠኛ ከሆኑት መሃል መዘገበን።
ደግሞ እንደኛ የታደለ አለ እንዴ?!
ታድለንማ'ኮ...
በአላህ ላይ ከሚመኩት፣
ለመንገዱ ከሚታመኑት፤
ድልንም ከርሱ ብቻ ከሚጠብቁት ሰራዊቶቹ መሃል አደረገን።
ደግሞ እንደኛ የታደለ አለ እንዴ?!
ለኛ የተሰጠው ለማን ተሰጥቷል?! - ዙሪያችሁን አትመለከቱምን?!
በህይወታችን ካየናቸው ብዙ ብዙ ብቸኝነቶች ውስጥ፥ በዚህ የትግል መንገድ ላይ ያለ ብቸኝነትን ያህል ዋጋ ያለው ብቸኝነት የት እናገኛለን?!
አላህ የሚያየው፣ የሚመሰክርለት ብቸኝነት!
ወደ ድል እንጂ የማይደርስ፣ ውድቀት የሌለበት ብቸኝነት!!
ትርጉሙ ጥልቅ፣ ክፍያው ብዙ ብቸኝነት!!!
ይህ እንደዋዛ 'ሚገኝ ነው እንዴ 'ሚመስለን?! በፍጹም።
ለዚህ ብቸኝነት መመረጥ ያሻዋል።
ይህ'ኮ ታላቅ ጸጋ እንጂ ሌላ አይደለም።
አልሐምዱሊላህ!!!
ሐስቡነላህ ወኒዕመል ወኪል!!!
@aaumsu
🔥34❤8
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ይህ ዛሬ 6 ሰዓት ከ50 ላይ በአምስት ኪሎ በር ላይ የተከሰተ ነው!
ኒቃቢስት ተማሪዎችን ኒቃባችሁን ካላወለቃችሁ አትገቡም በማለት መልሰዋል። መታዎቂያ አሳይተን እንግባ ቢሉም እምቢ ተብለው ተከልክለዋል።
መብታችንን በግልፅ የሚጥስ መመሪያ አወጡ፤ ኒቃቢስቶችን የሚያገል እና ምቹ ያልሆነ የቴክኖሎጂ ስርዓት ዘረጉ፤ ይህ ግልፅ የሆነ መዋቅራዊ ጭቆና ነው። ያሉበትን መዋቅር ሙስሊም ጠል ለሆነው አስተሳሰባቸው ማስፈፀሚያ እያደረጉት ነው።
የዚህ ሁሉ ምንጭ ለሐይማኖት ነፃነት መብታችን እውቅና መንፈግ ነውና በሁሉም መንገድ ልንጠይቃቸው ግድ ነው። በጋራ ሀገር በጋራ ሀብት በገነባነው ተቋም ውስጥ እኛን ያገለለ መመሪያ እና ስርዓት ለምን እንዳወጡ ልንጠይቃቸው ግድ ነው። በመመሪያ የጣሱትን መብት በመመሪያ ከለላ እስኪሰጡት፤ ለፈፀሙብን በደል በሕግ አግባብ እስኪጠየቁ ድረስ ልንታገላቸው ግድ ነው።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
@aaumsu
ኒቃቢስት ተማሪዎችን ኒቃባችሁን ካላወለቃችሁ አትገቡም በማለት መልሰዋል። መታዎቂያ አሳይተን እንግባ ቢሉም እምቢ ተብለው ተከልክለዋል።
መብታችንን በግልፅ የሚጥስ መመሪያ አወጡ፤ ኒቃቢስቶችን የሚያገል እና ምቹ ያልሆነ የቴክኖሎጂ ስርዓት ዘረጉ፤ ይህ ግልፅ የሆነ መዋቅራዊ ጭቆና ነው። ያሉበትን መዋቅር ሙስሊም ጠል ለሆነው አስተሳሰባቸው ማስፈፀሚያ እያደረጉት ነው።
የዚህ ሁሉ ምንጭ ለሐይማኖት ነፃነት መብታችን እውቅና መንፈግ ነውና በሁሉም መንገድ ልንጠይቃቸው ግድ ነው። በጋራ ሀገር በጋራ ሀብት በገነባነው ተቋም ውስጥ እኛን ያገለለ መመሪያ እና ስርዓት ለምን እንዳወጡ ልንጠይቃቸው ግድ ነው። በመመሪያ የጣሱትን መብት በመመሪያ ከለላ እስኪሰጡት፤ ለፈፀሙብን በደል በሕግ አግባብ እስኪጠየቁ ድረስ ልንታገላቸው ግድ ነው።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
@aaumsu
😡60❤2
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
Sarbama mirgaafii cunqursa barattoota yuniversitii Finfinnee irra gahaa jiru, afaan niqaabistoota irraa. Dhaggeeffadhaa, hunduu akka dhagahuufis tamsaasaa.
Gaaffii qabna_ deebiin haqaa hanga kennamutti !
@aaumsu
Gaaffii qabna_ deebiin haqaa hanga kennamutti !
@aaumsu
🔥16❤3
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
በአዲስ አበበ ዩምበረስቲ በኒቃቢስት ደረሳሶ ኢጄጅ ናረይ ምካት ተገግኒሙ ቲሰሙይ። አጥናቡይ! ለበለ ሰብ ኢጄጃምነኮ አሱይ
ሱል አለነ_ ኣዲል ጀዋብ ኢመጫን ጃንጎ!!!
@aaumsu
ሱል አለነ_ ኣዲል ጀዋብ ኢመጫን ጃንጎ!!!
@aaumsu
🔥19❤5😭5👌1
"ዝምታው ይሰበር!
ጭቆናው ይብቃ!" - ወንድም ሙራድ ታደሰ
የሚከተለውን መልዕክትም አስተላልፏል፦
"መንግስት አለ» በምንልበት፣ የሀገሪቱ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የዲፕሎማሲ ማዕከል በሆነችው አዲስ አበባ፣ 4 ኪሎ እና 6 ኪሎ
(AAU) ላይ የሙስሊም እህቶቻችንን መብት ማስከበር ካልቻልን፤ የመንግስት አማጺ እና ጽንፈኛ በነገሰበት አክሱም ከተማ ላይ ሙስሊሙ መብት ያገኛል ብሎ ማሰብ ዘበት ነው! ይህ በዋና ከተማችን፣ በመንግስት አፍንጫ ስር እየሆነ ያለ ግልጽ መዋቅራዊ ጭቆና ነው! በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሙስሊም ሴቶችን ክብር እና መብት ማስከበር ያቃተው ኡማ፣ አክሱም ላይ ሄዶ መብት አስከብራለሁ ቢል ቀልድ ነው።"
ኢንሻአላህ _ መብቶቻችንን ለምነን ሳይሆን ታግለን እናስከብራለን። ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ !
@aaumsu
ጭቆናው ይብቃ!" - ወንድም ሙራድ ታደሰ
የሚከተለውን መልዕክትም አስተላልፏል፦
"መንግስት አለ» በምንልበት፣ የሀገሪቱ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የዲፕሎማሲ ማዕከል በሆነችው አዲስ አበባ፣ 4 ኪሎ እና 6 ኪሎ
(AAU) ላይ የሙስሊም እህቶቻችንን መብት ማስከበር ካልቻልን፤ የመንግስት አማጺ እና ጽንፈኛ በነገሰበት አክሱም ከተማ ላይ ሙስሊሙ መብት ያገኛል ብሎ ማሰብ ዘበት ነው! ይህ በዋና ከተማችን፣ በመንግስት አፍንጫ ስር እየሆነ ያለ ግልጽ መዋቅራዊ ጭቆና ነው! በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሙስሊም ሴቶችን ክብር እና መብት ማስከበር ያቃተው ኡማ፣ አክሱም ላይ ሄዶ መብት አስከብራለሁ ቢል ቀልድ ነው።"
ኢንሻአላህ _ መብቶቻችንን ለምነን ሳይሆን ታግለን እናስከብራለን። ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ !
@aaumsu
🔥19❤9👌6
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
في جامعة أديس أبابا، تعرضت الطالبات المنتقبات لانتهاكات تمس حقوقهن. يجب أن يصل هذا الأمر للجميع، ويجب اتخاذ خطوات لتحقيق العدالة.
استمعوا لرسالتهن وانشروها أمانةً لوجه الله، وسنستمر في طرح السؤال حتى نصل إلى إجابة عادلة.
@aaumsu
استمعوا لرسالتهن وانشروها أمانةً لوجه الله، وسنستمر في طرح السؤال حتى نصل إلى إجابة عادلة.
@aaumsu
🔥17💔13❤5👍4
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ቦርድ
ሙስሊም ተማሪዎች ዩኒቨርስቲው እያደረሰ ያለውን የመብት ጥሰት በመግለፅ መፍትሔ ያመጣ ዘንድ ለቦርዱ ደብዳቤ ይዘው የሄዱት ከወራት በፊት ነበር። ደብዳቤውን ለማስገባት ለሄዱት ተወካዮች "ቦርድ የዩኒቨርስቲው የመጨረሻ አካል ስለሆነ እስከዛሬ የሄዳችሁበትን መንገድ በደንብ በሚገልፅ መልኩ፤ ለተቋማት ሁሉ ያስገባችሗቸውን ደብዳቤ እንዲሁም የሰጡትን ምላሽ አጠናቅራችሁ አምጡ።" - የሚልን ምላሽ ሰጠ። መስፈርታቸውን በመቀበልም በብዙ ቀናት ዶክመንቶች ተዘጋጅተው ካለቁ ቡሃላ ተወካዮች ደብዳቤውን ከእነ ዶክመንቶቹ ለማስገባት ሲሄዱ "እኛ ከእናንተ ደብዳቤ አንቀበልም!" - በማለት መልሰዋል።
የዩኒቨርስቲው አመራሮችየተማሪዎችን ጥያቄ በማፈን እና መብታቸውን በመጣስ የጀመሩት የቁልቁለት ጉዞ ከቦርድ መድረሱ በጣም የሚያሳዝን ነው። ጥያቄያችንን በደብዳቤ ስናስገባ መቀበል፤ ችግሮቻችንን በውይይት እንፈታ ዘንድ ስንጠይቅም ማስተናገድ ግዴታም ስልጣኔም ቢሆንም አሻፈረኝ እንዳሉ ነው።
ያም ሆነ ይህ ግን መብቶቻችን መከበራቸው አይቀሬ ነው። በሁሉም መንገድ ጠይቀን የነጠቁንን መብት እናስከብራለን፤ በደል የፈፀሙብን አካላትም ተጠያቂ ይሆናሉ።
"ንቁ! የአላህ እርዳታ በእርግጥ ቅርብ ነው (ተባሉም)፡፡" [2:214]
@aaumsu
ሙስሊም ተማሪዎች ዩኒቨርስቲው እያደረሰ ያለውን የመብት ጥሰት በመግለፅ መፍትሔ ያመጣ ዘንድ ለቦርዱ ደብዳቤ ይዘው የሄዱት ከወራት በፊት ነበር። ደብዳቤውን ለማስገባት ለሄዱት ተወካዮች "ቦርድ የዩኒቨርስቲው የመጨረሻ አካል ስለሆነ እስከዛሬ የሄዳችሁበትን መንገድ በደንብ በሚገልፅ መልኩ፤ ለተቋማት ሁሉ ያስገባችሗቸውን ደብዳቤ እንዲሁም የሰጡትን ምላሽ አጠናቅራችሁ አምጡ።" - የሚልን ምላሽ ሰጠ። መስፈርታቸውን በመቀበልም በብዙ ቀናት ዶክመንቶች ተዘጋጅተው ካለቁ ቡሃላ ተወካዮች ደብዳቤውን ከእነ ዶክመንቶቹ ለማስገባት ሲሄዱ "እኛ ከእናንተ ደብዳቤ አንቀበልም!" - በማለት መልሰዋል።
የዩኒቨርስቲው አመራሮችየተማሪዎችን ጥያቄ በማፈን እና መብታቸውን በመጣስ የጀመሩት የቁልቁለት ጉዞ ከቦርድ መድረሱ በጣም የሚያሳዝን ነው። ጥያቄያችንን በደብዳቤ ስናስገባ መቀበል፤ ችግሮቻችንን በውይይት እንፈታ ዘንድ ስንጠይቅም ማስተናገድ ግዴታም ስልጣኔም ቢሆንም አሻፈረኝ እንዳሉ ነው።
ያም ሆነ ይህ ግን መብቶቻችን መከበራቸው አይቀሬ ነው። በሁሉም መንገድ ጠይቀን የነጠቁንን መብት እናስከብራለን፤ በደል የፈፀሙብን አካላትም ተጠያቂ ይሆናሉ።
"ንቁ! የአላህ እርዳታ በእርግጥ ቅርብ ነው (ተባሉም)፡፡" [2:214]
@aaumsu
🔥18❤5
🔥26🥰5❤2😍1
የአላህ እርዳታ በእርግጥ ቅርብ ነው!
ፍትህን ለማስፈንና መብቶቻችንን ለማስከበር በምናደርገው ጉዞ ውስጥ የሚገጥሙን መሰናክሎች የጥንካሬያችን መለኪያ እንጂ የውድቀታችን ምልክቶች አይደሉም። ጨለማው በጣም የሚበረታው ሊነጋ ሲል እንደሆነ ሁሉ፣ ፈተናውም የሚከብደው ድሉ ሊመጣ ሲቃረብ ነው።
ታላቁ ጌታችን በተከበረው ቃሉ እንዲህ ይለናል፦
ይህ የጽናት ጊዜ ነው። ይህ የተወኩል ወቅት ነው። የሐቅ መንገድ መቼም ቢሆን ቢጠነክር እንጂ አይበጠስም። በጌታችን በአላህ ቃል ኪዳን ላይ ሙሉ እምነት አለን፤ እርሱ ፍትሃዊ ነውና የተገፉትን አይጥልም፣ የደጋጎችንም ስራ አያጠፋም።
📌 ጥንካሬያችን የሚመነጨው ከልባችን እምነት እንጂ ከሁኔታዎች መለዋወጥ አይደለም።
📌 እጅ ለእጅ ተያይዘን፣ በዱዓ ተጠናክረን ወደፊት እንጓዛለን።
📌 ትዕግስት የድል ሁሉ ቁልፍ ናት።
📌 ለእውነት የቆመ ማንም ይሁን ማን፣ መጨረሻው ስኬት ነው። እውነትና ፍትህ አሸናፊ መሆናቸው የማይቀር ሃቅ ነው።
ጌታችን ሆይ! በጽናት አጽናን፤ ድልህንም ቅርብ አድርግልን።
@aaumsu
ፍትህን ለማስፈንና መብቶቻችንን ለማስከበር በምናደርገው ጉዞ ውስጥ የሚገጥሙን መሰናክሎች የጥንካሬያችን መለኪያ እንጂ የውድቀታችን ምልክቶች አይደሉም። ጨለማው በጣም የሚበረታው ሊነጋ ሲል እንደሆነ ሁሉ፣ ፈተናውም የሚከብደው ድሉ ሊመጣ ሲቃረብ ነው።
ታላቁ ጌታችን በተከበረው ቃሉ እንዲህ ይለናል፦
"የአላህ እርዳታ መቼ ነው? ይሉ ዘንድ (ተጨነቁ)። ንቁ! የአላህ እርዳታ በእርግጥ ቅርብ ነው።" (አል-በቀራህ፡ 214)
ይህ የጽናት ጊዜ ነው። ይህ የተወኩል ወቅት ነው። የሐቅ መንገድ መቼም ቢሆን ቢጠነክር እንጂ አይበጠስም። በጌታችን በአላህ ቃል ኪዳን ላይ ሙሉ እምነት አለን፤ እርሱ ፍትሃዊ ነውና የተገፉትን አይጥልም፣ የደጋጎችንም ስራ አያጠፋም።
📌 ጥንካሬያችን የሚመነጨው ከልባችን እምነት እንጂ ከሁኔታዎች መለዋወጥ አይደለም።
📌 እጅ ለእጅ ተያይዘን፣ በዱዓ ተጠናክረን ወደፊት እንጓዛለን።
📌 ትዕግስት የድል ሁሉ ቁልፍ ናት።
📌 ለእውነት የቆመ ማንም ይሁን ማን፣ መጨረሻው ስኬት ነው። እውነትና ፍትህ አሸናፊ መሆናቸው የማይቀር ሃቅ ነው።
ጌታችን ሆይ! በጽናት አጽናን፤ ድልህንም ቅርብ አድርግልን።
@aaumsu
❤15🔥5
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
"ለእኛ አጀንዳ ሰጥተው ከትምህርት ያዘናጉን አካላት ቀጣዩን ትውልድ፤ የእኛን ልጆች፤ የእኛን ወንድም እህቶች በተመሳሳይ ጥያቄ ከትምህርት እንዲያዘናጓቸው አንፈልግም። እኛ እየተሳቀቅን የኖርንበትን፤ እኛ እየተሳቀቅን የተማርንበትን፤ ማንም አካል በክብራችን እየተረማመደ ያለበትን ሁኔታ በእኛ ልጆች ላይ እንዲደገም አንፈቅድም።"
@aaumsu
@aaumsu
🔥17💯6❤3
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
"አሁን አሸባሪ እንደዚህ ሆኖ ቢገባና ጉዳት ቢያደርስ ራሳችሁን አይጸጽታችሁም?"
ኒቃብ የለበሱ ተማሪዎችን ላይብረሪ አትገቡም ብሎ ከልክሎ ምክንያቱን ሲያብራራ ከተናገረው ነው። ሙስሊም ጠልነታቸው በዚህ ልክ አግጥጦ ነው የሚታየው። እነዚህን አካላት ደፍሮ ከመጠየቅ፣ ከመታገል እና በሕግ ተጠያቂ ከማድረግ ውጪ አማራጭ የለንም።
By any means necessary መብታችን ሊከበር ግድ ነው። በመመሪያ የከለከሉትን መብት በመመሪያ ከለላ እስኪሰጡት መጠየቅ ግድ ነው። መብታችንን የጣሱ አካላት ተጠያቂ ሊደረጉ ግድ ነው።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ !
@aaumsu
ኒቃብ የለበሱ ተማሪዎችን ላይብረሪ አትገቡም ብሎ ከልክሎ ምክንያቱን ሲያብራራ ከተናገረው ነው። ሙስሊም ጠልነታቸው በዚህ ልክ አግጥጦ ነው የሚታየው። እነዚህን አካላት ደፍሮ ከመጠየቅ፣ ከመታገል እና በሕግ ተጠያቂ ከማድረግ ውጪ አማራጭ የለንም።
By any means necessary መብታችን ሊከበር ግድ ነው። በመመሪያ የከለከሉትን መብት በመመሪያ ከለላ እስኪሰጡት መጠየቅ ግድ ነው። መብታችንን የጣሱ አካላት ተጠያቂ ሊደረጉ ግድ ነው።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ !
@aaumsu
😡22🔥2💔2❤1
አላሁ አክበር!!! አላሁ አክበር!!!
ከ19 ወራት በላይ፤ ከ620 ቀናት በላይ ጥያቄ አለን! ሲሉ የነበሩት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ለጥያቄ መልስ እንፈልጋለን! በማለት በአሁኑ ሰዓት ከፕሬዝዳንት ጽ/ቤቱ ጋር ይገኛሉ!!
@aaumsu
ከ19 ወራት በላይ፤ ከ620 ቀናት በላይ ጥያቄ አለን! ሲሉ የነበሩት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ለጥያቄ መልስ እንፈልጋለን! በማለት በአሁኑ ሰዓት ከፕሬዝዳንት ጽ/ቤቱ ጋር ይገኛሉ!!
@aaumsu
🔥45❤5⚡1👏1👌1
ፕሬዝዳንቱ ሳይመጡ የትም አንሄድም! ጥያቄያችን ምላሽ ሳያገኝ ወደኃላ ማለት የለም ያሉት የግቢያችን ሙስሊም ተማሪዎች በአሁን ሰዓት በፕሬዝዳንቱ ጽ/ቤት በገፍ ተሰባሰበዋል!
@aaumsu
@aaumsu
❤28🔥18💯2⚡1👌1