4_60262876053629905171_1.mp4
15.5 MB
ባለፈው ሳምንት _ በወሎ ዩኒቨርስቲ ከተደረገ የጁምዓ ኹጥባ !
"የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲን ፕሮጀክት ተመልከቱ። መራቆትን ባህል አድርገው እንደ ምዕራባውያን ካልሆናችሁ እያሉ ነው። ጉዳዩ የባህል ከሆነ ለምን የአፋር እና ሶማሌን ባህል አያከብሩም? ኒቃብ ለአፋር ባህሉ ነው። ኒቃብ ለሶማሌ ባህሉ ነው።"
@aaumsu
"የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲን ፕሮጀክት ተመልከቱ። መራቆትን ባህል አድርገው እንደ ምዕራባውያን ካልሆናችሁ እያሉ ነው። ጉዳዩ የባህል ከሆነ ለምን የአፋር እና ሶማሌን ባህል አያከብሩም? ኒቃብ ለአፋር ባህሉ ነው። ኒቃብ ለሶማሌ ባህሉ ነው።"
@aaumsu
🔥12💯4❤2
"የሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ ከትውልድ ትውልድ እየተሸጋገረ በሁሉም የሚደረስ ታዚያ መሆን የለበትም። በዚህ ዘመን በዚህ ትውልድ የሚቋጭ እንጂ።"
@aaumsu
@aaumsu
💯26❤8🔥6👌4⚡2
وَلَا تَهِنُوا(አትድከሙ/አትስነፉ)፦
የሰበሰባችሁት 1,141 ፊርማ በ "X" ሲሰረዝ፣ የተወካዮቻችሁ ድምፅ "አናውቃችሁም" ተብሎ ሲናቅ፣ በሩ ላይ ያሉት ጥበቆች መንገዱን ሲዘጉባችሁ... አትድከሙ! የእናንተ ጥንካሬ የሚለካው በሮች በመከፈታቸው ሳይሆን፣ በሮች ተዘግተውባችሁም ለቆማችሁለት አላማ ባለመደላደላችሁ (resilience) ነው።
وَلَا تَحْزَنُوا(አትዘኑ)፦
ርቦሽ ከካፌ ስትባረሪ፣ ታመሽ ከክሊኒክ ስትገፊ፣ ወይም መምህራን ማርክሽን ቀንሰው ሊያሸማቅቁሽ ሲጥሩ... አትዘኚ! ይህ የአጭር ጊዜ እንግልት ነው። እነሱ 'እየቀጣናችሁ ነው' ብለው ቢያስቡ፣ አላህ ግን በሰማይ ቤቱ ለአንቺ የክብር ማዕድ 🍱 እያዘጋጀ ነው። ውጤትሽን በወረቀት ላይ ቢቀንሱትም፣ በእርሱ ዘንድ ያለሽ ደረጃ ግን ከፍ ያለ ነው።
وَأَنتُمُ الْأَعْلَوْنَ(እናንተ የበላይ ናችሁ)፦
ሀቅ ነው! ኒቃብሽን እንደ "ስጋት" ለሚቆጥሩት፣ ክብራቸውን ለዲግሪ ለሸጡትና የሌላውን ጥላ ለሚከተሉት ሰዎች አትሸማቀቂ። "በጥላ ውስጥ የሚቆይ ሰው ጥላ የለውም!" እንደሚባለው፣ ማንነታቸውን ደብቀውና የሌላውን ቀለም ለብሰው የሚሄዱት እነርሱ እንጂ፣ በፀሐይ ተቃጥለሽም ቢሆን የራስሽን የፅናት ጥላ ይዘሽ የቆምሽው አንቺ የበላይ ነሽ! ዲግሪ ካንቺ በታች ነው፤ ኒቃብሽ ግን የፈጣሪሽ አደራ በመሆኑ ካንቺ ጋር ከፍ ያለ ነው።
ባርነት ወይስ ዕውቀት?
ዛሬ ላይ ባለመማር ሊቀጡሽ የወሰኑ አካላት አንድ ነገር ሊረዱ ይገባል፤ ጥያቄሽ አንድና ግልፅ ነው— "መማር እፈልጋለሁ!" ነገር ግን ስትማሪ ክብርሽን፣ ሞገስሽንና ኒቃብሽን ጠብቀሽ ነው። ያለ ዲንሽ ሕይወት የለሽም፤ ያለ ተቅዋ ትምህርት ትርጉም አይሰጥሽም። የታላቁ ነቢያችን (ሰ.ዐ.ወ) አደራ የሆነውን ዲን አጥፍተሽ የምታመጪው ዲግሪ ለቤትሽም ለሀገርሽም በረካ አይሆንም። አንገትሽን አስደፍተው፣ በራስሽ ማንነት እንድትሸማቀቂ አድርገው የሚሰጡሽ እውቀት እውቀት ሳይሆን 'ባርነት' ነው።
አብሽሪ! አንቺ አትሰበሪም!
ለካፌና ለክሊኒክ ስትከለከዪ፣ በሩ ላይ ስትገፊና ስትገለዪ "ተሰበረች" ብለው ለገመቱ ሁሉ የምንለው፤ ይሄ ጫና የሚጨምረው ጥንካሬሽን እንጂ ድካምሽን አይደለም። ዛሬ በሩን ቢዘጉብሽ፣ ተቅዋን በልብሽ ካኖርሽ..
ረቡና በውብ ንግግሩ እንዲህ ሲል አብሽር ይልሻል፦
وَمَن يَتَّقِ اللَّهَ يَجْعَل لَّهُ مَخْرَجًا ۞ وَيَرْزُقْهُ مِنْ حَيْثُ لَا يَحْتَسِب
...አንቺ ብቻ እኔን ፍሪ እንጂ ላለሽበት ጭንቀት እና ጫና መውጫን አደርግልሻለሁ፤ ምን እሱ ብቻ ባላሰብሽው በኩልም ሪዝቄን እረዝቅሻለሁ ይልሻል። አንገትሽን ሊያስደፉሽ በሞከሩ ሰዎች ፊት፣ በኩራት ቀና ብለሽ የምትሄጂበት ቀን ደግሞ እሩቅ አይደለም። Inshallah ❤️
.... أَلَا إِنَّ نَصْرَ اللَّهِ قَرِيبٌ
(እውቁ! የአላህ እርዳታ ቅርብ ነው) ፦
የእርሱ እርዳታ በቢሮክራሲና በሰው ፍቃድ የታጠረ አይደለም። ለጊዜው ነገራቶችን እያየ ዝም ያለው አንቺ እንድትሰበሪ or ሊቀጣሽ ሳይሆን፣ በፅናትሽ ታሪክ ሰርተሽ ለድል እንድትበቂ ነው።
ሀስቡነላህ ወኒእመል ወኪል!
ሰዎች "ተከታታይ ክስ መስርተንባችኋል፣ አናውቃችሁም፣ ዲግሪ የላችሁም" ብለው ሊያስፈራሯችሁ ሲሞክሩ፣ ቁርአን የሚሰጣችሁ 'ወኔ' ግን ፍፁም የተለየ ነው ፦
الَّذِينَ قَالَ لَهُمُ النَّاسُ إِنَّ النَّاسَ قَدْ جَمَعُوا لَكُمْ فَاخْشَوْهُمْ فَزَادَهُمْ إِيمَانًا وَقَالُوا حَسْبُنَا اللَّهُ وَنِعْمَ الْوَكِيلُ
Look... እነሱ 1,141 ፊርማን ሲንቁ፣ አንቺ ግን "አላህ በቂዬ ነው" ስትይ፣ ሰማይና ምድር ካንቺ ጋር ይቆማሉ። ዲግሪ ወረቀት ነው፤ ኒቃብሽ ግን 'ሞገስ' ነው። ዛሬ አንገትሽን ሊያስደፉሽ የሞከሩ ሁሉ፣ ነገ በፅናትሽ ብርሃን አይናቸው ሲታወር ታያለሽ።
አብሽሪ እህቴ! አንቺ የአላህ እንግዳ እንጂ የካምፓስ ስደተኛ አይደለሽም። ዛሬ በካፌው በር ብትከለከዪም፣ ነገ በጀነት በር 'ያለምንም ሂሳብ' የምትገቢው አንቺ ነሽ!
"ኒቃቧንም ትለብሳለች... ትምህርቷንም ትማራለች!"
©ከቁርአን አያህ
#AAUMuslimStudents #DignityOverEverything #KeQuranAyah #JusticeForNiqabis #Ethiopia
@aaumsu
የሰበሰባችሁት 1,141 ፊርማ በ "X" ሲሰረዝ፣ የተወካዮቻችሁ ድምፅ "አናውቃችሁም" ተብሎ ሲናቅ፣ በሩ ላይ ያሉት ጥበቆች መንገዱን ሲዘጉባችሁ... አትድከሙ! የእናንተ ጥንካሬ የሚለካው በሮች በመከፈታቸው ሳይሆን፣ በሮች ተዘግተውባችሁም ለቆማችሁለት አላማ ባለመደላደላችሁ (resilience) ነው።
وَلَا تَحْزَنُوا(አትዘኑ)፦
ርቦሽ ከካፌ ስትባረሪ፣ ታመሽ ከክሊኒክ ስትገፊ፣ ወይም መምህራን ማርክሽን ቀንሰው ሊያሸማቅቁሽ ሲጥሩ... አትዘኚ! ይህ የአጭር ጊዜ እንግልት ነው። እነሱ 'እየቀጣናችሁ ነው' ብለው ቢያስቡ፣ አላህ ግን በሰማይ ቤቱ ለአንቺ የክብር ማዕድ 🍱 እያዘጋጀ ነው። ውጤትሽን በወረቀት ላይ ቢቀንሱትም፣ በእርሱ ዘንድ ያለሽ ደረጃ ግን ከፍ ያለ ነው።
وَأَنتُمُ الْأَعْلَوْنَ(እናንተ የበላይ ናችሁ)፦
ሀቅ ነው! ኒቃብሽን እንደ "ስጋት" ለሚቆጥሩት፣ ክብራቸውን ለዲግሪ ለሸጡትና የሌላውን ጥላ ለሚከተሉት ሰዎች አትሸማቀቂ። "በጥላ ውስጥ የሚቆይ ሰው ጥላ የለውም!" እንደሚባለው፣ ማንነታቸውን ደብቀውና የሌላውን ቀለም ለብሰው የሚሄዱት እነርሱ እንጂ፣ በፀሐይ ተቃጥለሽም ቢሆን የራስሽን የፅናት ጥላ ይዘሽ የቆምሽው አንቺ የበላይ ነሽ! ዲግሪ ካንቺ በታች ነው፤ ኒቃብሽ ግን የፈጣሪሽ አደራ በመሆኑ ካንቺ ጋር ከፍ ያለ ነው።
ባርነት ወይስ ዕውቀት?
ዛሬ ላይ ባለመማር ሊቀጡሽ የወሰኑ አካላት አንድ ነገር ሊረዱ ይገባል፤ ጥያቄሽ አንድና ግልፅ ነው— "መማር እፈልጋለሁ!" ነገር ግን ስትማሪ ክብርሽን፣ ሞገስሽንና ኒቃብሽን ጠብቀሽ ነው። ያለ ዲንሽ ሕይወት የለሽም፤ ያለ ተቅዋ ትምህርት ትርጉም አይሰጥሽም። የታላቁ ነቢያችን (ሰ.ዐ.ወ) አደራ የሆነውን ዲን አጥፍተሽ የምታመጪው ዲግሪ ለቤትሽም ለሀገርሽም በረካ አይሆንም። አንገትሽን አስደፍተው፣ በራስሽ ማንነት እንድትሸማቀቂ አድርገው የሚሰጡሽ እውቀት እውቀት ሳይሆን 'ባርነት' ነው።
አብሽሪ! አንቺ አትሰበሪም!
ለካፌና ለክሊኒክ ስትከለከዪ፣ በሩ ላይ ስትገፊና ስትገለዪ "ተሰበረች" ብለው ለገመቱ ሁሉ የምንለው፤ ይሄ ጫና የሚጨምረው ጥንካሬሽን እንጂ ድካምሽን አይደለም። ዛሬ በሩን ቢዘጉብሽ፣ ተቅዋን በልብሽ ካኖርሽ..
ረቡና በውብ ንግግሩ እንዲህ ሲል አብሽር ይልሻል፦
وَمَن يَتَّقِ اللَّهَ يَجْعَل لَّهُ مَخْرَجًا ۞ وَيَرْزُقْهُ مِنْ حَيْثُ لَا يَحْتَسِب
...አንቺ ብቻ እኔን ፍሪ እንጂ ላለሽበት ጭንቀት እና ጫና መውጫን አደርግልሻለሁ፤ ምን እሱ ብቻ ባላሰብሽው በኩልም ሪዝቄን እረዝቅሻለሁ ይልሻል። አንገትሽን ሊያስደፉሽ በሞከሩ ሰዎች ፊት፣ በኩራት ቀና ብለሽ የምትሄጂበት ቀን ደግሞ እሩቅ አይደለም። Inshallah ❤️
.... أَلَا إِنَّ نَصْرَ اللَّهِ قَرِيبٌ
(እውቁ! የአላህ እርዳታ ቅርብ ነው) ፦
የእርሱ እርዳታ በቢሮክራሲና በሰው ፍቃድ የታጠረ አይደለም። ለጊዜው ነገራቶችን እያየ ዝም ያለው አንቺ እንድትሰበሪ or ሊቀጣሽ ሳይሆን፣ በፅናትሽ ታሪክ ሰርተሽ ለድል እንድትበቂ ነው።
ሀስቡነላህ ወኒእመል ወኪል!
ሰዎች "ተከታታይ ክስ መስርተንባችኋል፣ አናውቃችሁም፣ ዲግሪ የላችሁም" ብለው ሊያስፈራሯችሁ ሲሞክሩ፣ ቁርአን የሚሰጣችሁ 'ወኔ' ግን ፍፁም የተለየ ነው ፦
الَّذِينَ قَالَ لَهُمُ النَّاسُ إِنَّ النَّاسَ قَدْ جَمَعُوا لَكُمْ فَاخْشَوْهُمْ فَزَادَهُمْ إِيمَانًا وَقَالُوا حَسْبُنَا اللَّهُ وَنِعْمَ الْوَكِيلُ
Look... እነሱ 1,141 ፊርማን ሲንቁ፣ አንቺ ግን "አላህ በቂዬ ነው" ስትይ፣ ሰማይና ምድር ካንቺ ጋር ይቆማሉ። ዲግሪ ወረቀት ነው፤ ኒቃብሽ ግን 'ሞገስ' ነው። ዛሬ አንገትሽን ሊያስደፉሽ የሞከሩ ሁሉ፣ ነገ በፅናትሽ ብርሃን አይናቸው ሲታወር ታያለሽ።
አብሽሪ እህቴ! አንቺ የአላህ እንግዳ እንጂ የካምፓስ ስደተኛ አይደለሽም። ዛሬ በካፌው በር ብትከለከዪም፣ ነገ በጀነት በር 'ያለምንም ሂሳብ' የምትገቢው አንቺ ነሽ!
"ኒቃቧንም ትለብሳለች... ትምህርቷንም ትማራለች!"
❤️🩹ከ ቁርአን አያህ...
©ከቁርአን አያህ
#AAUMuslimStudents #DignityOverEverything #KeQuranAyah #JusticeForNiqabis #Ethiopia
@aaumsu
❤59🥰5🏆2👍1
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
ጥያቄ አለን ማለት ከጀመርን 624 ቀናት ሞላ። መመሪያው በረቂቅነት ደረጃ ሳለ በመስከረም 15, 2017 ዓ.ል ነበር ጥያቄ አለን በማለት በአምስት ኪሎ ግቢ ድምፃችንን ከፍ አድርገን ያሰማነው። የዚያኔ ለጥያቄያችን ምላሽ ላለመስጠት መድረኩን ረግጠው ቢሄዱም ቢሯቸው ድረስ ተሰብስበን በመሄድ ደጋግመን ጠይቀናቸው ነበር። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ለ20 ወራት እና 19 ቀናት ብንጠይቅም በውይይት አምኖ ለጥያቄያችን ምላሽ ለመስጠት ከጠረጴዛ በአግባቡ የተቀመጠ አካል የለም። ለጥያቄያችን የተነፈገው ትኩረት እና በሂደቱ የተሰጠው ግብረመልስ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ያለውን ውይይት ጠል እና ሙስሊም ጠል አካሄዶችን የሚያሳይ ነው። ምንም ቢሆን ምን መብቶቻችንን በመጣሳቸው ፍትሕን ለመጠየቅ የጀመርነው ጉዞ አይቋጭም። በሰላማዊ መንገድ በአስቸኳይ መፍትሔ ይመጣ ዘንድ ዳግም እንጠይቃለን።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ !
@aaumsu
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ !
@aaumsu
🔥20👍8💯6❤1
ሒጃቧ - ማንነቷ!
መገለጫዋ ነው
ማንነት ምስጢሩ፥ የተወጠነበት፣
የሴትነት ሀሁ
የተፈጥሮ ሚዛን፥ ጸንቶ የቆመበት።
እሷነት ነው ሒጃብ
ጥንት የተሰጠችው፥ የገጿ ላይ አርማ፣
በወቅት አይደበዝዝ
አረጀብኝ ብላ፥ እትጥለው ከርማ።
እቃዋም አይደለም
ሲያሻት የምትጥለው፥ ደግሞ 'ምታነሳው፥
የመኖር ምሷ ነው
ከራሷ ተገምዶ፥ እሷው የምትለብሰው።
ማንነት ነውና
ነፍስና ስጋዋን፥ ተዋሕዶ ያለ፣
እሷን ከሂጃቧ
የምትነጥልበት፥ ጉልበት ወዴት አለ?
©EHEMSU
@aaumsu
መገለጫዋ ነው
ማንነት ምስጢሩ፥ የተወጠነበት፣
የሴትነት ሀሁ
የተፈጥሮ ሚዛን፥ ጸንቶ የቆመበት።
እሷነት ነው ሒጃብ
ጥንት የተሰጠችው፥ የገጿ ላይ አርማ፣
በወቅት አይደበዝዝ
አረጀብኝ ብላ፥ እትጥለው ከርማ።
እቃዋም አይደለም
ሲያሻት የምትጥለው፥ ደግሞ 'ምታነሳው፥
የመኖር ምሷ ነው
ከራሷ ተገምዶ፥ እሷው የምትለብሰው።
ማንነት ነውና
ነፍስና ስጋዋን፥ ተዋሕዶ ያለ፣
እሷን ከሂጃቧ
የምትነጥልበት፥ ጉልበት ወዴት አለ?
©EHEMSU
@aaumsu
🔥20👏4❤2
60 ቀናት ሞላ
በዚህ ምሽት ዩኒቨርስቲው ካዘጋጀው የኢፍጣር መድረክ የተገኙ ሒጃቢስቶች "ጥያቄ አለን! መልስ ስጡን!" - በማለት ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ማሰማታቸውን ታሪክ በወርቃማ ብዕር ከትቦ አልፏል። ሒጃቢስቷ "ከምግቡ በፊት ነፃነቴ ይቀድማል። ካከበራችሁኝ መብቴን አክብሩ።" - በማለት ተናግራ ነበር። ምሽቱን የነበሩ የግቢው አካላት በማግስቱ ፕሬዚዳንቱ ባሉበት ውይይት ተደርጎ መፍትሔ እንደሚመጣ ቢገልፁም ጁምዓ ሲደረስ ደግሞ ከአዲስ አበባ ከተማ ፀጥታ እና ብልፅግና ቢሮ የመጡ አካላት ቀጠሮው ለሰኞ ይዛወር ብለው መድረክ እንደሚዘጋጅ ቃል ገብተው ነበር።
ሆኖም ይህ ቀን ካለፈ ዛሬ 60 ቀናት ሞላ። ጥያቄያችንን እንመልሳለን ያሉ አካላት ሳይመልሱ፤ ውይይት ይካሄዳል ብለው ቃል የገቡት ቃላቸውን ሳያከብሩ 60 ቀናት ሞላ። በሒጃብ ምክንያት ሰብዓዊ መብቷ ለተገፈፈው እህት ፍትሕ ይሰጥ ዘንድ፤ ችግሮች በውይይት ተፈተው የዩኒቨርስቲው ስም ይመለስ ዘንድ፤ አጥፊዎች ይቀጡ ዘንድ መድረክ ይዘጋጃል ተብሎ ሳይዘጋጅ 60 ቀናት አለፉ።
ቀናት አለፉ ማለት ግን ጥያቄውም አለፈ ማለት አይደለም። ውይይትን ተመራጭ መንገድ አድርጎ መፍትሔን መሻት ፍርሃት ሳይሆን ብስለት ነው። ሆኖም ግን ለውይይት የተጋበዙ እና እንደሚካሄድ ቃል የገቡ አካላት ቃላቸውን ባለማክበራቸው መፍትሔ ሳይመጣ ቀርቷል። ስለሆነም መፍትሔው ይመጣ ዘንድ ጠንከር ብሎ መጠየቅ፤ ጠንከር ብሎ ድምፅን ማሰማት፤ ተቀናጅቶ እና ተናቦ መንቀሳቀስ ግድ ነው። ይህ ይሆናል። ሲሆንም መፍትሔው በቅርቡ ይመጣል። ኢንሻአላህ!
ጥያቄ አለን _ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ !
@aaumsu
በዚህ ምሽት ዩኒቨርስቲው ካዘጋጀው የኢፍጣር መድረክ የተገኙ ሒጃቢስቶች "ጥያቄ አለን! መልስ ስጡን!" - በማለት ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ማሰማታቸውን ታሪክ በወርቃማ ብዕር ከትቦ አልፏል። ሒጃቢስቷ "ከምግቡ በፊት ነፃነቴ ይቀድማል። ካከበራችሁኝ መብቴን አክብሩ።" - በማለት ተናግራ ነበር። ምሽቱን የነበሩ የግቢው አካላት በማግስቱ ፕሬዚዳንቱ ባሉበት ውይይት ተደርጎ መፍትሔ እንደሚመጣ ቢገልፁም ጁምዓ ሲደረስ ደግሞ ከአዲስ አበባ ከተማ ፀጥታ እና ብልፅግና ቢሮ የመጡ አካላት ቀጠሮው ለሰኞ ይዛወር ብለው መድረክ እንደሚዘጋጅ ቃል ገብተው ነበር።
ሆኖም ይህ ቀን ካለፈ ዛሬ 60 ቀናት ሞላ። ጥያቄያችንን እንመልሳለን ያሉ አካላት ሳይመልሱ፤ ውይይት ይካሄዳል ብለው ቃል የገቡት ቃላቸውን ሳያከብሩ 60 ቀናት ሞላ። በሒጃብ ምክንያት ሰብዓዊ መብቷ ለተገፈፈው እህት ፍትሕ ይሰጥ ዘንድ፤ ችግሮች በውይይት ተፈተው የዩኒቨርስቲው ስም ይመለስ ዘንድ፤ አጥፊዎች ይቀጡ ዘንድ መድረክ ይዘጋጃል ተብሎ ሳይዘጋጅ 60 ቀናት አለፉ።
ቀናት አለፉ ማለት ግን ጥያቄውም አለፈ ማለት አይደለም። ውይይትን ተመራጭ መንገድ አድርጎ መፍትሔን መሻት ፍርሃት ሳይሆን ብስለት ነው። ሆኖም ግን ለውይይት የተጋበዙ እና እንደሚካሄድ ቃል የገቡ አካላት ቃላቸውን ባለማክበራቸው መፍትሔ ሳይመጣ ቀርቷል። ስለሆነም መፍትሔው ይመጣ ዘንድ ጠንከር ብሎ መጠየቅ፤ ጠንከር ብሎ ድምፅን ማሰማት፤ ተቀናጅቶ እና ተናቦ መንቀሳቀስ ግድ ነው። ይህ ይሆናል። ሲሆንም መፍትሔው በቅርቡ ይመጣል። ኢንሻአላህ!
ጥያቄ አለን _ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ !
@aaumsu
🔥20💔10❤4😭4
ይህ የወልቂጤ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ድምፅ ነው። አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ያወጣውን ጨቋኝ መመሪያ አስመልክቶ ጥያቄ አለን በማለት ድምፃቸውን አሰምተዋል። ሙስሊሙ ተማሪ ከጫፍ እስከ ጫፍ በሚያሰማው ድምፅ ለጥያቄው መልስ ያገኛል።
መብቶቻችንን የሚጥሱ አካላት በሕግ ይጠየቁ!
Qaamonni mirga keenya sarban seeraan haa gaafataman!
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ !
@aaumsu
መብቶቻችንን የሚጥሱ አካላት በሕግ ይጠየቁ!
Qaamonni mirga keenya sarban seeraan haa gaafataman!
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ !
@aaumsu
🔥25❤10👌1
አስራ አምስት ወራት አለፉ
ሰላም ሚኒስቴር
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ያወጣው ጨቋኝ መመሪያ እያደረሰ ያለው የመብት ጥሰት በዝርዝር ተጠቅሶ የመፍትሔው አካል እንዲሆኑ በመግለፅ የመጀመሪያው ደብዳቤ ከገባላቸው አስራ አምስት ወራት አልፈዋል። በ2017 በነበረ አንድ ግንኙነት በጉዳዩ ላይ ከመጅሊስ አካላት ጋር ተወያይተው መፍትሔ እንደሚያመጡ ቢገልፁም መፍትሔው ሳይመጣ አመቱ ተጠናቀቀ። መመሪያውም ጭቆናውም በ2018 መቀጠላቸውን ተከትሎ ከ6 ወራት በፊት ዳግም ደብዳቤ ቢገባላቸውም ምንም አይነት ምላሽም ሆነ መፍትሔ ሳይሰጡ እስካሁን አሉ።
ሙስሊሙ ተማሪ ተቋሜ ብሎ በሄደበት ተቋም አገልግሎት ሊያገኝና መብቱን ሊያስጠብቁለት የተገባ ቢሆንም ፍሬው የታዬ ስራ ባለመሰራቱ መመሪያው ሳይሻሻል እስካሁን አለ። ይህ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለሙስሊሙ ተማሪ ጥያቄ የሰጠውን ቦታ የሚያሳይ እና በጥልቁ ቅሬታ የፈጠረ ተግባር ነው።
ሆኖም ግን በሁሉም መንገድ፣ የሚመለከተው ሁሉ ዘንድ በመሄድ ስንጠይቅ የነበረው ጥያቄ የእኛ ትውልድ ሀላፊነት ነውና የማስከበሩ ሀላፊነት የእኛው ነው። በአላህ ፈቃድ በትብብር፣ በቅንጅት፣ በመናበብ፣ ለአንድ አላማ በአንድነት በመቆም ስለመብታችን እንጠይቃለን፤ መብታችንም እስኪከበር ድረስ ጥያቄ አለን እንላለን።
ጥያቄ አለን እንላለን _ በሚዲያም በአካልም _ በቢሮም በአደባባይም _ በጋራ በአንድነት ጥያቄ አለን እንላለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ !
@aaumsu
ሰላም ሚኒስቴር
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ያወጣው ጨቋኝ መመሪያ እያደረሰ ያለው የመብት ጥሰት በዝርዝር ተጠቅሶ የመፍትሔው አካል እንዲሆኑ በመግለፅ የመጀመሪያው ደብዳቤ ከገባላቸው አስራ አምስት ወራት አልፈዋል። በ2017 በነበረ አንድ ግንኙነት በጉዳዩ ላይ ከመጅሊስ አካላት ጋር ተወያይተው መፍትሔ እንደሚያመጡ ቢገልፁም መፍትሔው ሳይመጣ አመቱ ተጠናቀቀ። መመሪያውም ጭቆናውም በ2018 መቀጠላቸውን ተከትሎ ከ6 ወራት በፊት ዳግም ደብዳቤ ቢገባላቸውም ምንም አይነት ምላሽም ሆነ መፍትሔ ሳይሰጡ እስካሁን አሉ።
ሙስሊሙ ተማሪ ተቋሜ ብሎ በሄደበት ተቋም አገልግሎት ሊያገኝና መብቱን ሊያስጠብቁለት የተገባ ቢሆንም ፍሬው የታዬ ስራ ባለመሰራቱ መመሪያው ሳይሻሻል እስካሁን አለ። ይህ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለሙስሊሙ ተማሪ ጥያቄ የሰጠውን ቦታ የሚያሳይ እና በጥልቁ ቅሬታ የፈጠረ ተግባር ነው።
ሆኖም ግን በሁሉም መንገድ፣ የሚመለከተው ሁሉ ዘንድ በመሄድ ስንጠይቅ የነበረው ጥያቄ የእኛ ትውልድ ሀላፊነት ነውና የማስከበሩ ሀላፊነት የእኛው ነው። በአላህ ፈቃድ በትብብር፣ በቅንጅት፣ በመናበብ፣ ለአንድ አላማ በአንድነት በመቆም ስለመብታችን እንጠይቃለን፤ መብታችንም እስኪከበር ድረስ ጥያቄ አለን እንላለን።
ጥያቄ አለን እንላለን _ በሚዲያም በአካልም _ በቢሮም በአደባባይም _ በጋራ በአንድነት ጥያቄ አለን እንላለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ !
@aaumsu
🔥24❤4
በሁዳ መልቲሚዲያ
2000 ላይ ሒጃብን የሚከለክለው የመጀመሪያው መመሪያ ሲወጣ የነበረው ትንቅንቅ ተዳሷል። ከዚያ በፊት በሙስሊም ተማሪዎች ላይ ሲደርሱ የነበሩት፤ አሁን ላይ እየደረሰ ያለው ተጠቅሷል። የአዲስ የአበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለው የመብት ጥሰትም የተዳሰሰ ሲሆን ብቸኛ መፍትሔውም በዝርዝር ተቀምጧል።
ሊንኩ https://youtu.be/eM0omRXNjIM?si=lKtxA0iK3NW96kMO ነው። በደንብ ያዳምጡ። የቤት ስራዎንም ይውሰዱ። ለሌሎችም ያሰራጩ።
@aaumsu
2000 ላይ ሒጃብን የሚከለክለው የመጀመሪያው መመሪያ ሲወጣ የነበረው ትንቅንቅ ተዳሷል። ከዚያ በፊት በሙስሊም ተማሪዎች ላይ ሲደርሱ የነበሩት፤ አሁን ላይ እየደረሰ ያለው ተጠቅሷል። የአዲስ የአበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለው የመብት ጥሰትም የተዳሰሰ ሲሆን ብቸኛ መፍትሔውም በዝርዝር ተቀምጧል።
ሊንኩ https://youtu.be/eM0omRXNjIM?si=lKtxA0iK3NW96kMO ነው። በደንብ ያዳምጡ። የቤት ስራዎንም ይውሰዱ። ለሌሎችም ያሰራጩ።
@aaumsu
🔥17❤5🥰2👌1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ኒቃቢስቷ፦ እምነቴን መተው አለብኝ?
የAAU ጥበቆች፦ እምነት ብሔር የሚባል ነገር የለም። እምነት በልብ ነው።
ይህ ኒቃቢስት እህት ላይ በር ያለች ጥበቃ አትገቢም ብላ ካቆመቻት ቡሃላ የተናገሩት ንግግር ነው። እዚህ እምነት የሚባል ነገር አይሰራም በማለት የእምነቷ ክፍል የሆነን አለባበስ ከበር ጥላ እንድትገባ ጠይቋታል። እርሷም "እና እምነቴን መተው አለብኝ?" - በማለት እየጠየቀች ነው። እምነቷን መተው አለባት? እምነታችንን መተው አለብን? ገብተን እንማር ዘንድ እስልምናችንን ከበር ጥለን መግባት አለብን? ይህ ድፍረትን የቀላቀለ የሙስሊም ተማሪዎችን መብት የሚጥስ ንግግር ነው። እስልምና ከዩኒቨርስቲ በር ተጥሎ የሚገባ ሐይማኖት አይደለም።
ኒቃብን በመመሪያ በመከልከል መብታችን የሆነን አለባበስ ከመከልከል ጀምሮ ጥላቻ አዘል ንግግሮች እንዲደርሱብን እየሆነ ነው። ይህ ለምን እንደተፈለገ አሁንም ጥያቄ አለን። መመሪያው ይሻሻል ዘንድ በሁሉም መንገድ ስንጠይቅ እንደነበረውም መመሪያው ተሻሽሎ መብታችን ይጠበቅ ዘንድ በትብብር፣ በአንድነት፣ በጋራ እና በሕብረት ድምፃችንን ማሰማት፤ ስለመብታችን መጠየቅ፤ የእኛ ስለሆነውም መሞገት ግዴታችን ሆኗል። በአላህ ፈቃድ ይህ እሮሮ በእኛ ትውልድ ይቋጫል። መብታችን ተከብሮም ፍትሕ የሚሰፍን ይሆናል። ኢንሻ አላህ!
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ !
@aaumsu
የAAU ጥበቆች፦ እምነት ብሔር የሚባል ነገር የለም። እምነት በልብ ነው።
ይህ ኒቃቢስት እህት ላይ በር ያለች ጥበቃ አትገቢም ብላ ካቆመቻት ቡሃላ የተናገሩት ንግግር ነው። እዚህ እምነት የሚባል ነገር አይሰራም በማለት የእምነቷ ክፍል የሆነን አለባበስ ከበር ጥላ እንድትገባ ጠይቋታል። እርሷም "እና እምነቴን መተው አለብኝ?" - በማለት እየጠየቀች ነው። እምነቷን መተው አለባት? እምነታችንን መተው አለብን? ገብተን እንማር ዘንድ እስልምናችንን ከበር ጥለን መግባት አለብን? ይህ ድፍረትን የቀላቀለ የሙስሊም ተማሪዎችን መብት የሚጥስ ንግግር ነው። እስልምና ከዩኒቨርስቲ በር ተጥሎ የሚገባ ሐይማኖት አይደለም።
ኒቃብን በመመሪያ በመከልከል መብታችን የሆነን አለባበስ ከመከልከል ጀምሮ ጥላቻ አዘል ንግግሮች እንዲደርሱብን እየሆነ ነው። ይህ ለምን እንደተፈለገ አሁንም ጥያቄ አለን። መመሪያው ይሻሻል ዘንድ በሁሉም መንገድ ስንጠይቅ እንደነበረውም መመሪያው ተሻሽሎ መብታችን ይጠበቅ ዘንድ በትብብር፣ በአንድነት፣ በጋራ እና በሕብረት ድምፃችንን ማሰማት፤ ስለመብታችን መጠየቅ፤ የእኛ ስለሆነውም መሞገት ግዴታችን ሆኗል። በአላህ ፈቃድ ይህ እሮሮ በእኛ ትውልድ ይቋጫል። መብታችን ተከብሮም ፍትሕ የሚሰፍን ይሆናል። ኢንሻ አላህ!
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ !
@aaumsu
🔥10🤬8😭2❤1👌1😡1
ሒጃቧ - መብቷ!
እኩል ግብር ከፍሎ
እኩል ደሙን ሰጥቶ፥ ባጸናት ሐገሩ
ልጄን ላስተምር ሲል
አይሆንም ሲባል ግን፥ አለመታፈሩ?!
የነጻነት ምድር
ቀበርኩት ብትልም፥ ጭቆናን ምድሯ ላይ
አይኗ ተሸፍኗል
ልማር የምትላት፥ ልጇን ዞራ እንዳታይ።
ለስሙ እኩልነት
ሲሰበክ ቢውልም፥ መድረክ ተፈልጎ
የታለ እኩልነት
ያ'ገሪቷን ግማሽ፥ ወደ ጎን አድርጎ?!
ትዝብት እንጂ ትርፉ
ፍትሕ ስሟ ቀርቶ፥ ግብሯ ቢሆን ኦና፣
ሀገር አትሰራም
ከግለሰቦች ደጅ፥ መብት እየተጠና።
ሌሎች እኩዮቿን
መብት እንደሆናቸው፥ ትምህርትና ስራ፣
እሷም ትማራለች
(እሷም ትሰራለች)
እምነቷን አክብራ፥ መብቷን አስከብራ።
©️EHEMSU
@aaumsu
እኩል ግብር ከፍሎ
እኩል ደሙን ሰጥቶ፥ ባጸናት ሐገሩ
ልጄን ላስተምር ሲል
አይሆንም ሲባል ግን፥ አለመታፈሩ?!
የነጻነት ምድር
ቀበርኩት ብትልም፥ ጭቆናን ምድሯ ላይ
አይኗ ተሸፍኗል
ልማር የምትላት፥ ልጇን ዞራ እንዳታይ።
ለስሙ እኩልነት
ሲሰበክ ቢውልም፥ መድረክ ተፈልጎ
የታለ እኩልነት
ያ'ገሪቷን ግማሽ፥ ወደ ጎን አድርጎ?!
ትዝብት እንጂ ትርፉ
ፍትሕ ስሟ ቀርቶ፥ ግብሯ ቢሆን ኦና፣
ሀገር አትሰራም
ከግለሰቦች ደጅ፥ መብት እየተጠና።
ሌሎች እኩዮቿን
መብት እንደሆናቸው፥ ትምህርትና ስራ፣
እሷም ትማራለች
(እሷም ትሰራለች)
እምነቷን አክብራ፥ መብቷን አስከብራ።
©️EHEMSU
@aaumsu
🔥17❤3👌3
70 ቀናት ሞላ
ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት
አስቸኳይ የሆነ የፖለቲካ አመራር እና ውሳኔ በማሳለፍ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን ስልታዊ የመብት ጥሰት እና ማግለል ያስቆም ዘንድ ለብልፅግና ጽ/ቤት ደብዳቤ ከገባ 70 ቀናት ሞልቷል። ሆኖም ግን እስካሁን ባለው ጊዜ ተማሪዎች ላስገቡት ደብዳቤ የተሰጠ ምላሽም ሆነ የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት የተወሰደ ቁርጠኛ እርምጃ አልታየም።
መሠል ምላሾች አግባብነት የሌላቸው እንደሆኑ እናምናለን። ተማሪዎች የደረሰባቸው በደል ተሰምቶ መፍትሔ ይመጣ ዘንድ ሁሉንም አማራጭ ተጠቅመዋል። ቅሬታዎችን ሰምቶ አጥፊዎችን በመቅጣት መፍትሔ መስጠት የመንግስት ሀላፊነት ቢሆንም መፍትሔው ሳይመጣ እስካሁን አለ።
መመሪያው ይስተካከል ዘንድ ዳግም እንጠይቃለን። መመሪያው እስኪስተካከልም ጥያቄ አለን እንላለን። የደረሰብንን በደል አሳውቀን ምላሽ ላልሰጡን ስለምን ምላሽ እንዳልሰጡ ጥያቄ አለን። መፍትሔ እንደሚያመጡ ቀጠሮ ሰጥተው ቃላቸውን ላጠፉ አካላት ስለምን ቃላቸውን እንዳጠፉ ጥያቄ አለን። መመሪያውን ሳያሻሽሉ በደላቸውን ለቀጠሉ አካላት ስለምን በበዳይነታቸው ለመቀጠል እንደቆረጡ ጥያቄ አለን።
ጥያቄያችንንም ሳንሰለች ሳንደክም ሳንፈራ ሳናፍር በቢሮ ውስጥም ሆነ በአደባባይ እናቀርባለን። በሚዲያም ሆነ በአካል እናሰማለን። ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ!
@aaumsu
ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት
አስቸኳይ የሆነ የፖለቲካ አመራር እና ውሳኔ በማሳለፍ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን ስልታዊ የመብት ጥሰት እና ማግለል ያስቆም ዘንድ ለብልፅግና ጽ/ቤት ደብዳቤ ከገባ 70 ቀናት ሞልቷል። ሆኖም ግን እስካሁን ባለው ጊዜ ተማሪዎች ላስገቡት ደብዳቤ የተሰጠ ምላሽም ሆነ የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት የተወሰደ ቁርጠኛ እርምጃ አልታየም።
መሠል ምላሾች አግባብነት የሌላቸው እንደሆኑ እናምናለን። ተማሪዎች የደረሰባቸው በደል ተሰምቶ መፍትሔ ይመጣ ዘንድ ሁሉንም አማራጭ ተጠቅመዋል። ቅሬታዎችን ሰምቶ አጥፊዎችን በመቅጣት መፍትሔ መስጠት የመንግስት ሀላፊነት ቢሆንም መፍትሔው ሳይመጣ እስካሁን አለ።
መመሪያው ይስተካከል ዘንድ ዳግም እንጠይቃለን። መመሪያው እስኪስተካከልም ጥያቄ አለን እንላለን። የደረሰብንን በደል አሳውቀን ምላሽ ላልሰጡን ስለምን ምላሽ እንዳልሰጡ ጥያቄ አለን። መፍትሔ እንደሚያመጡ ቀጠሮ ሰጥተው ቃላቸውን ላጠፉ አካላት ስለምን ቃላቸውን እንዳጠፉ ጥያቄ አለን። መመሪያውን ሳያሻሽሉ በደላቸውን ለቀጠሉ አካላት ስለምን በበዳይነታቸው ለመቀጠል እንደቆረጡ ጥያቄ አለን።
ጥያቄያችንንም ሳንሰለች ሳንደክም ሳንፈራ ሳናፍር በቢሮ ውስጥም ሆነ በአደባባይ እናቀርባለን። በሚዲያም ሆነ በአካል እናሰማለን። ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ!
@aaumsu
🔥15❤2👌2
🫡19❤3💯3
በኢትዮጵያ የሚኖሩ ሙስሊሞች ይባል ነበር _ ቀደምቶቻችን በከፈሉት ዋጋ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች ተባልን
ኢትዮጵያ የክርስቲያን ደሴት ነች ይባል ነበር _ አባቶቻችን ባደረጉት ትግል ኢትዮጵያ የሁሉም የሆነች ሴኩላር ሀገር ነች እንዲባል ሆነ
በሁለቱ ዒዶች የመንግስት መስሪያ ቤት ክፍት ሆኖ ይውል፤ ትምህርት ቤትም ሆን ተብሎ የፈተና ቀን ይሆን ነበር _ ታሪካቸውን በወርቅ ብዕር ከትበው ባለፉ ትውልዶች ዒዶቻችን ብሔራዊ በዓል ሆኑ
ስለ እስልምና _ የሐይማኖት ነፃነት መብት በሕገ- መንግስት እንዲፀና _ የሐይማኖት እኩልነት መብት በሕግ እንዲቀመጥ ያልተከፈለ መስዋዕትነት የለም። ሆኖም በሕገ- መንግስት እንዲፀና የተደረገው መብት የትምህርት ሚኒስቴርን አጥር መሻገር ተስኖታል። ዋጋ ተከፍሎበት በሕግ እንዲፀና የሆነው መብት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲን አጥር መሻገር ተስኖት በመመሪያ ተጥሷል።
ሆኖም ቀደምት አባት እናቶች ታግለው ያፀኑትን ታግሎ ማስከበሩ የእኔ፣ የአንተ የአንቺ፣ የሁላችን ሀላፊነት ሆኗል። ዋጋ ለተከፈለበት ዋጋ መክፈል ግድ ነው።
@aaumsu
ኢትዮጵያ የክርስቲያን ደሴት ነች ይባል ነበር _ አባቶቻችን ባደረጉት ትግል ኢትዮጵያ የሁሉም የሆነች ሴኩላር ሀገር ነች እንዲባል ሆነ
በሁለቱ ዒዶች የመንግስት መስሪያ ቤት ክፍት ሆኖ ይውል፤ ትምህርት ቤትም ሆን ተብሎ የፈተና ቀን ይሆን ነበር _ ታሪካቸውን በወርቅ ብዕር ከትበው ባለፉ ትውልዶች ዒዶቻችን ብሔራዊ በዓል ሆኑ
ስለ እስልምና _ የሐይማኖት ነፃነት መብት በሕገ- መንግስት እንዲፀና _ የሐይማኖት እኩልነት መብት በሕግ እንዲቀመጥ ያልተከፈለ መስዋዕትነት የለም። ሆኖም በሕገ- መንግስት እንዲፀና የተደረገው መብት የትምህርት ሚኒስቴርን አጥር መሻገር ተስኖታል። ዋጋ ተከፍሎበት በሕግ እንዲፀና የሆነው መብት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲን አጥር መሻገር ተስኖት በመመሪያ ተጥሷል።
ሆኖም ቀደምት አባት እናቶች ታግለው ያፀኑትን ታግሎ ማስከበሩ የእኔ፣ የአንተ የአንቺ፣ የሁላችን ሀላፊነት ሆኗል። ዋጋ ለተከፈለበት ዋጋ መክፈል ግድ ነው።
@aaumsu
🔥20❤5💯3👍2
23 ቀናት ሞላ
የፌደራል መጅሊስ ፕሬዚዳንት
ሸይኽ ሐጂ ኢብራሒም ቱፋ ከዶክተር ሳሙኤል እና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እንደተነጋገሩና የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በኒቃባቸው ምክንያት ሳይሳቀቁ እንዲማሩ እንደሚያደርጉ ከ23 ቀናት በፊት በአዲስ አበባ መጅሊስ ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ገልፀው ነበር። ይህንንም ተከትሎ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ተወካዮች ከመጅሊሱ ፕሬዚዳንት እና ምክትል ፕሬዚዳንቶች ጋር የዚያኑ ቀን ውይይት ያደረጉ ሲሆን መጅሊሱ መመሪያው ይስተካከል ዘንድ የሚጠይቅ ደብዳቤ እንዲያስገባ፤ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ የመብት ጥሰት የፈፀሙ የዩኒቨርስቲው አካላትን ሊከስ፤ ከዩኒቨርስቲው ጋር ለዘላቂው መፍትሔ ውይይት ሊደረግ እንዲሁም በሀገር አቀፍ ደረጃ የመጨረሻ መፍትሔ ይመጣ ዘንድ ከተቋቋመው 17 ኮሚቴ ጋር ተማሪዎች በቅርበት እንዲሰሩ ከስምምነት ተደርሶ ነበር።
ቃል በተገባ ማግስት ጀምሮ የመብት ጥሰቶቹ የቀጠሉ እና መመሪያውም ያልተሻሻለ ቢሆንም ባለፉት 23 ቀናት ውስጥ ከተጠቀሱት አራት ነጥቦች ውስጥ ወደ ተግባር የተለወጠ አንድም ነጥብ የለም። መጅሊስ የሙስሊሙን መብት ሊያስጠብቅ የሚገባ ግንባር ቀደም ተቋም እንደመሆኑ በዚህ ሁሉ ቀናት ውስጥ ትኩረት ተሰጥቶ ቁርጠኛ የሆነ አቋም ተወስዶ መፍትሔ አለመምጣቱ በተማሪው ዘንድ ቅሬታ ፈጥሯል።
ጥያቄያችን መብቶቻችን በመመሪያ ተፅፈው እና በሕግ ፀንተው እንዲመለሱልን ነው። ነፃነታችንን ገፍፎ ሙስሊም ጠልነቱን ሲያንፀባርቅ እና በደል ሲፈፅም የነበረ ሁሉ በሕግ አግባብ ይጠየቅ ዘንድም ግድ ነው።
ጥያቄ አለን እንላለን። ቢሮ ውስጥም በአደባባይም _ በሚዲያም በአካልም _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ!
@aaumsu
የፌደራል መጅሊስ ፕሬዚዳንት
ሸይኽ ሐጂ ኢብራሒም ቱፋ ከዶክተር ሳሙኤል እና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እንደተነጋገሩና የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በኒቃባቸው ምክንያት ሳይሳቀቁ እንዲማሩ እንደሚያደርጉ ከ23 ቀናት በፊት በአዲስ አበባ መጅሊስ ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ገልፀው ነበር። ይህንንም ተከትሎ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ተወካዮች ከመጅሊሱ ፕሬዚዳንት እና ምክትል ፕሬዚዳንቶች ጋር የዚያኑ ቀን ውይይት ያደረጉ ሲሆን መጅሊሱ መመሪያው ይስተካከል ዘንድ የሚጠይቅ ደብዳቤ እንዲያስገባ፤ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ የመብት ጥሰት የፈፀሙ የዩኒቨርስቲው አካላትን ሊከስ፤ ከዩኒቨርስቲው ጋር ለዘላቂው መፍትሔ ውይይት ሊደረግ እንዲሁም በሀገር አቀፍ ደረጃ የመጨረሻ መፍትሔ ይመጣ ዘንድ ከተቋቋመው 17 ኮሚቴ ጋር ተማሪዎች በቅርበት እንዲሰሩ ከስምምነት ተደርሶ ነበር።
ቃል በተገባ ማግስት ጀምሮ የመብት ጥሰቶቹ የቀጠሉ እና መመሪያውም ያልተሻሻለ ቢሆንም ባለፉት 23 ቀናት ውስጥ ከተጠቀሱት አራት ነጥቦች ውስጥ ወደ ተግባር የተለወጠ አንድም ነጥብ የለም። መጅሊስ የሙስሊሙን መብት ሊያስጠብቅ የሚገባ ግንባር ቀደም ተቋም እንደመሆኑ በዚህ ሁሉ ቀናት ውስጥ ትኩረት ተሰጥቶ ቁርጠኛ የሆነ አቋም ተወስዶ መፍትሔ አለመምጣቱ በተማሪው ዘንድ ቅሬታ ፈጥሯል።
ጥያቄያችን መብቶቻችን በመመሪያ ተፅፈው እና በሕግ ፀንተው እንዲመለሱልን ነው። ነፃነታችንን ገፍፎ ሙስሊም ጠልነቱን ሲያንፀባርቅ እና በደል ሲፈፅም የነበረ ሁሉ በሕግ አግባብ ይጠየቅ ዘንድም ግድ ነው።
ጥያቄ አለን እንላለን። ቢሮ ውስጥም በአደባባይም _ በሚዲያም በአካልም _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ!
@aaumsu
🔥15❤5👍2💔2