ፍትሕ ሚኒስቴር ፍትሕን የሚያጓድል ረቂቅ መመሪያ አውጥቶ ተወያዩበት ብሏል!
2005 ዓ.ል ላይ በዘመነ ኢሕአዴግ የሙስሊሙን ማህበረሰብ ከመንግስት ተቋማት "ውጡ!" ማለት ብቻ የቀረው መመሪያ ወጥቶ እስከ አሁኗ ሰዓት ድረስ በመንግስት ተቋማት ውስጥ በተለይም በትምህርት ተቋማት ውስጥ ሙስሊሙ ማህበረሰብ ብዙ እንግልት እንዲደርስበት ሆኗል:: ለአብነትም ብዙ ሳንርቅ በሒጃባቸው ምክንያት ከትምህርት ገበታ የተገለሉት የጉንችሬ ሙስሊም ተማሪዎች ህያው ምስክር ናቸው:: ከዚያም ባለፈ በየዩኒቨርሲቲው ሒጃብና ጀለብያ በተለበሰ ወይም ሶላት በተሰገደ ቁጥር የሚፈጠረው አምባጓሮ የደረሰውን መገፋት ስፋት ያሳያል::
አሁንም ፍትሕ ሚኒስቴር ያወጣው ረቂቅ ደንብ ከሴኩላሪዝም መሰረታዊ መርሆ ያፈነገጠ : የሃይማኖት ነፃነት መብትን የሚጋፋና ሙስሊም ተማሪዎች በሃይማኖታቸውና በትምህርታቸው መካከል እንዲመርጡ የሚያስገድድ ነው::
በዚህ ረገድ የፌደራል መጅሊስ ያወጣው መግለጫ እንደ ተቋም ተቋሙን የሚመጥንና ያለውን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያሳይ ነው:: እኛም እንደ ሙስሊም ተማሪ ህግና ስርዓትን ተከትለን በቃን ልንል ይገባል:: ኢ-ፍትሐዊነትን የምንሸከምበት ትከሻ እንደሌለን ልናሳይ ግድ ነው::
ሶላት ህይዎት ነው:: ሒጃብ ከእምነት ነው:: እስልምናችን ከዩኒቨርሲቲ ሲገባ የሚወልቅ የውጭ ዩኒፎርም አይደለም:: አለቀ!
@aaumsu
2005 ዓ.ል ላይ በዘመነ ኢሕአዴግ የሙስሊሙን ማህበረሰብ ከመንግስት ተቋማት "ውጡ!" ማለት ብቻ የቀረው መመሪያ ወጥቶ እስከ አሁኗ ሰዓት ድረስ በመንግስት ተቋማት ውስጥ በተለይም በትምህርት ተቋማት ውስጥ ሙስሊሙ ማህበረሰብ ብዙ እንግልት እንዲደርስበት ሆኗል:: ለአብነትም ብዙ ሳንርቅ በሒጃባቸው ምክንያት ከትምህርት ገበታ የተገለሉት የጉንችሬ ሙስሊም ተማሪዎች ህያው ምስክር ናቸው:: ከዚያም ባለፈ በየዩኒቨርሲቲው ሒጃብና ጀለብያ በተለበሰ ወይም ሶላት በተሰገደ ቁጥር የሚፈጠረው አምባጓሮ የደረሰውን መገፋት ስፋት ያሳያል::
አሁንም ፍትሕ ሚኒስቴር ያወጣው ረቂቅ ደንብ ከሴኩላሪዝም መሰረታዊ መርሆ ያፈነገጠ : የሃይማኖት ነፃነት መብትን የሚጋፋና ሙስሊም ተማሪዎች በሃይማኖታቸውና በትምህርታቸው መካከል እንዲመርጡ የሚያስገድድ ነው::
በዚህ ረገድ የፌደራል መጅሊስ ያወጣው መግለጫ እንደ ተቋም ተቋሙን የሚመጥንና ያለውን ኢ-ፍትሐዊነት የሚያሳይ ነው:: እኛም እንደ ሙስሊም ተማሪ ህግና ስርዓትን ተከትለን በቃን ልንል ይገባል:: ኢ-ፍትሐዊነትን የምንሸከምበት ትከሻ እንደሌለን ልናሳይ ግድ ነው::
ሶላት ህይዎት ነው:: ሒጃብ ከእምነት ነው:: እስልምናችን ከዩኒቨርሲቲ ሲገባ የሚወልቅ የውጭ ዩኒፎርም አይደለም:: አለቀ!
@aaumsu
🔥13❤8👌4👏2🫡1
🥀 Daily Reminder 112🥀
يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ ٱرۡكَعُواْ وَٱسۡجُدُواْۤ وَٱعۡبُدُواْ رَبَّكُمۡ وَٱفۡعَلُواْ ٱلۡخَيۡرَ لَعَلَّكُمۡ تُفۡلِحُونَ۩
"እናንተ ያመናችሁ ሰዎች ሆይ! (በስግደታችሁ) አጎንብሱ፣ በግንባራችሁም ተደፉ፣ ጌታችሁንም ተገዙ፣ በጎንም ነገር ሥሩ፣ ልትድኑ ይከጀልላችኋልና!"
Surah Al-Hajj; 77
@aaumsu
يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ ٱرۡكَعُواْ وَٱسۡجُدُواْۤ وَٱعۡبُدُواْ رَبَّكُمۡ وَٱفۡعَلُواْ ٱلۡخَيۡرَ لَعَلَّكُمۡ تُفۡلِحُونَ۩
"እናንተ ያመናችሁ ሰዎች ሆይ! (በስግደታችሁ) አጎንብሱ፣ በግንባራችሁም ተደፉ፣ ጌታችሁንም ተገዙ፣ በጎንም ነገር ሥሩ፣ ልትድኑ ይከጀልላችኋልና!"
Surah Al-Hajj; 77
@aaumsu
👍6
- لا أحد يدرك كم أنت تجاهد نفسك
لا أحد يرى تحطمك الداخلي
لا أحد يعي كيف تدور الحياة في جوفك
لا أحد يحسب كم انهيار رافق تشكلك
لذلك توخّى الحذر فحسب.
@aaumsu
لا أحد يرى تحطمك الداخلي
لا أحد يعي كيف تدور الحياة في جوفك
لا أحد يحسب كم انهيار رافق تشكلك
لذلك توخّى الحذر فحسب.
@aaumsu
👍5
Abu bakr and Omar knew they were promised Jannah but acted like they weren't, We aren't even promised
Jannah but act like we are.
@aaumsu
Jannah but act like we are.
@aaumsu
👍5
የሃይማኖት ጉዳይን አስመልክቶ በተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ ላይ የም/ቤታችንን አቋም ስለማሳወቅ፤
🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴 🔴🔴🔴🔴🔴
ሀገራችን ኢትዮጵያ የብዝሀ ሃይማኖት መገኛ ሆና ሳለ ለዘመናት የሃይማኖቶች እኩልነትና የሐገር ባለቤትነት ጉዳይ ከሙስሊሙ አንፃር ሳይረጋገጥ በመኖሩ እስልምና እንደ ሃይማኖት ሙስሊሙ ማህበረሰብም እንደ ዜጋ ከፍ ያለ ዋጋ ሲከፍሉ ኖረዋል፡፡ በዚህም ምክንያት ህዝበ ሙስሊሙ ከንጉሳዊው የአስተዳደር ዘመን ጀምሮ መንግሰትና ሃይማኖት የተለያዩ እንዲሆኑና የሃይማኖት እኩልነትና ነፃነት እንዲከበር መራር ትግል ሲያደርግ ቆይቷል።
ከዚህም በመነሳት ሙስሊሙ በታላቁ የኢትዮጲያ ህዝባዊ አብዮት ዋነኛ ተሳታፊ ነበር። አብዮቱ ካስገኛቸው ድሎች አንዱ ለመጀመሪያ ጊዜ መንግስትና የሃይማኖት የተለያዩ መሆናቸው የተደነገገበት የደርግ ዘመን 1979 ህገ መንግሰት ተጠቃሽ ነው። ይሁን እንጂ መብቱ በህገመንግሰት ይካተት እንጂ በተግባር ስራ ላይ ሳይውል ጭቆናው ቀጥሎ ቆይቷል። በአንፃራዊነት በ1983 የነበረውን የመንግስት ለውጥ ተከትሎ የመንግስትና የሃይማኖት መለያየት በ1987 ፀድቆ እስከ አሁንም በስራ ላይ የሚገኘው የኢፊዴሪ ህገ-መንግስት በግልፅ በመቀመጡ ከቀድሞ የተሻለ ጊዜ ነበር ማለት ይቻላል፡፡
ነገር ግን ህገ-መንግስቱ ውስጥ በመርህ ደረጃ የተቀመጡትን የመንግሰትና ሐይማኖት መለያየት እንዲሁም የሃይማኖት እኩልነትና ነፃነት መብቶችና መሰረታዊ መርሆዎችና ድንጋጌዎች ለማስፈፀም የሚውሉ ዝርዝር ህጎች ሳይወጡ በመቆየቱ ምክንያት መብቶቹን በምሉዕነት መጠቀም አልተቻለም። ይባስ ብሎም አንዳንድ ተቋማት ህገመንግሰታዊ የሆነውን የመንግሰትና ሃይማኖት መለያየት መርህ ያልተገባ ትርጉም በመስጠት ለአድሏዊ አሰራር ሲያዉሉት ተስተውለዋል። አንዳንድ ተቋማትም የህገ-መንግስቱን ግልፅ ድንጋጌዎች የሚቃረኑ፤እንዲሁም በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የሙስሊሙን ማህበረሰብ ኢላማ ያደረጉ ደንቦች፤መመሪያዎችንና አሰራሮችን በመዘርጋት ህዝባችን ላይ ጥቃቶችና በደሎች ሲያደርሱበት በስፋት ተስተውለዋል ፡፡
የኢትዮጵያ ሙስሊም ማህበረሰብም በተለያዩ ጊዜያት እነዚህ በደሎችና ጥቃቶች በዘላቂነት ሊያስቆሙለት የሚያስችሉና ህገ መንግስተዊ መብቱን በምሉዕነት እንዲገለገልባቸው የሚያስችሉ ዝርዝር ህጎች በአግባቡ እንዲወጡና ስርዓት ያለው ወጥ አሰራር እንዲኖር ሲወተውቱ ቆይተዋል፡፡
ከዚህም በመነሳት የኢትዮጲያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ህገመንግስታዊውን የመንግስትና ሃይማኖት መለያየት መርህን እንዲሁም የሃይማኖት እኩልነትና ነፃነትን በዝርዝር ለማስፈፀም አዋጅ መውጣቱን በመርህ ደረጃ ይደግፈዋል። ይሁን እንጂ ከአዋጁ ረቂቅ ዝግጅት ጀምሮ ህጉን ለማውጣት እየተኬደበት ያለው ሂደትና ፤የረቂቅ አዋጁ ይዘትን አስመልክቶ ከሰሞኑ እየተስተዋለ ያለውን የህዝበ ሙስሊሙን ፍላጎትና ስጋት በእጅጉ ይጋራል።
ምክር ቤታችን መንግስት ሊያወጣው ያሰበው ረቂቅ አዋጅ እንደ ሙስሊም ማህበረሰብ ወኪልነቱ እንደዚ ያሉ መመሪያዎች ባለመኖራቸው የተነሳ በሙስሊሙ ላይ ይደርሱ የነበሩትን ያልተማከሉ ነገር ግን የተቀናጁ የሚመስሉ ጥቃቶችን በወጥነት ያስቆማል ብሎ ስለሚያምን ለአዋጁ ያለውን ድጋፍ ከወዲሁ መግለፅ ይፈልጋል። በአዋጁ ላይ ያሉንን አስተያየቶችና ስጋቶች የምንገልፀውም የመንግስትን ፍላጎት ወይም አላማ በመጥፎ በመረዳት ሳይሆን በሀገራችን የህግና የአዋጆች መውጣት ታሪክ የሙስሊሙ ማህበረሰብ ጥያቄዎችና ጥቅሞች የማይገናዘቡበት የቆየ አሰራር በመኖሩ አንዳንድ ለኛ ወሳኝ የሆኑ ነገሮችን አንድም ባለማወቅ ወይን ደግሞ በግለሰቦች የተለየ ፍላጎት የተነሳ ቸል ሲባሉ እና ሙስሊሙን ተጎጂ ሲያደርጉ በመኖራችን ስጋት ስላለን መሆኑን ማስገንዘብ እንፈልጋለን።
ይህ የአማኞች ሀገር በምትባለው ሀገራችን ሊወጣ እየተዘጋጀ የሚገኘው አዋጅም የሃይማኖትን እኩልነት፣ የመንግስትና የሃይማኖትን መለያየት በተለያዩ ጊዜያት በሙስሊሙ ማህበረሰብ በተለይም ደግሞ በትምህርት ቤቶችና በተለያዩ የመንግስት ተቋማት የሚገኙ ሙስሊም ሰራተኞችና ባለስልጣናት ላይ ይደርስ የነበረውን ግልጽ የሆነ ተቋማዊና ግለሰባዊ የሆነ የበደልና የጥቃት ተግባራትን ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ የሚቀርፍ መሆን እንዳለበት ም/ቤታችን ያምናል፡፡
ከዚህ አንፃር በረቂቅ አዋጁ ዙሪያ እየተነሱ ካሉ የህዝባችን ሃሳቦች በመነሳት ምክር ቤታችን በተወሰነ መልኩ ለማጣራት ባደረገው ጥረት ረቂቅ አዋጁ እነዚህን ነባር ችግሮች ከመቅረፍ ይልቅ የሚያባብሱና ተጨማሪ ችግሮችን የሚያስከትሉ አንዳንድ ድንጋጌዎች እንዳሉበት ለመገንዘብ ችሏል።
በመሆኑም በዚህ ጉዳይ ላይ ከሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ጋር በተደረገው ውይይት መሠረት ሰፋ ያለ የሙስሊሙን መብት የሚመለከቱ ጉዳዮችን በዝርዝር የሚያቀርብ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ ጠቅላይ ምክር ቤታችን ከዚህ በታች የተዘረዘሩ ጉዳዮች ላይ ያለውን ጥብቅ አቋምና ስጋት ለማቅረብ ይወዳል፡-
1. ምንም እንኳን ህግ መውጣቱ የምንፈልገውና የቆየ የህዝባችን ጥያቄ ቢሆንም የእምነታችንን የተለዩ የአምልኮ ባህሪያት ግምት ውስጥ ሳያስገባ በስመ እኩልነት ብቻ ከሌሎች ሃይማኖቶች የአምልኮ ስርዓት ጋር በማነፃፀር እዚህም እዚያም ከልክለናል በሚል የተሳሳተ መነሻ የተቀረፀው እንዲሁም በእምነታችን የአምልኮ ስርዓት ውስጥ በመግባት አንድ ሙስሊም በእምነቱ የታዘዘውን የአምልኮ ተግባር እንዴት ማከናወን እንዳለበት እሰከመምረጥ ድረስ ገደብ ለመጣል በሚሞክሩ አናቅፅ የተሞላ ረቂቅ አዋጅ መሆኑ ተገቢ ስላልሆነ ፣
2. የሃይማኖትና የአማኞች ሃገር ናት የምትባለውን ሃገራችንን ሃይማኖታዊ እሴቶች ከማጎልበትና ሃይማኖቶችን ለሃገራዊ አንድነትና እድገት በአዎንታዊነት ከመጠቀም ይልቅ የሀገራችንን ተጨባጭ ባለማገናዘብና ወደጐን በመተው እምነቶችን በበማዳከም ለሃገር ከሚያበረክቱት ገንቢ አስተዋፅኦ የማግለል ባህሪ ያለው በመሆኑ ፣
3. ሃገራችን ህብረ ብሄራዊ የፌዴራል ስርዓት የምትከተል እንደመሆንዋ በተለያዩ ክልሎች በመሬት ላይ ያለውን እውነታ በፍፁም ከግምት ውስጥ ያልከተተና ተፈፃሚነት የሌለው ህግ እንዳይሆን የሚያሰጋ በመሆኑ፣
4. ረቂቅ አዋጁ በመሠረቱ አንድ ህግ ለሀገርና ለህዝብ ጥቅም ሲባል የሚወጣበትን መርህ በመጣስ በህገ መንግስቱ የተረጋገጠውን የእምነት መብትና ነፃነትን ከማስፈፀም ይልቅ መገደብ ላይ በማተኮር የአለም አቀፍ ህጐችንና ህገ መንግስታችንን የሚቃንኑ ሀሳቦች ያሉበት በመሆኑ ፣
5. የመንግሰትና ሃይማኖት መለያየት መርህ ዋና አስኳል የሆነውን የመንግስትን በሃይማኖት ውስጥ ጣልቃ የመግባት ሁኔታ ከመገደብ ይልቅ፤ያለአግባብ መንግሰት በሃይማኖት ጉዳዮች ጣልቃ መግባትን የሚያበረታታና መንግስት የሀይማኖቶች ተቆጣጠሪ የማድረግ ባህሪ ያለው በመሆኑ ፣
6. ሕገመንግስታዊውን የሃይማኖት ነፃነትን ከማስከበር አንፃር የእምነታችንን ልዩ የአምልኮ ባህሪያት በመረዳት ለዚያ የሚመች ሁኔታዎችን ከማመቻቸት ይልቅ አምልኮዎችን መከልከል ላይ ማተኮሩ፣
ለምሳሌ፡- በት/ት ቤቶች እና በመንግስት ተቋማት አካባቢ ሙስሊሙ ግዴታ የሆነበትን ሰላትና የሴቶች አለባበስ ሁኔታ የመከልከልን ባህሪያት የተሞላ መሆኑ ፣
7. የመንግስትና የሃይማኖትን መለያየት አስመልክቶ ለረቂቅ አዋጁ ግብዓት ተደርገው የነበሩ ጥናቶችን ውጤትና ምክረ ሃሳቦች ወደጐን በመተው ህግ አርቃቂዎቹ አካላት በተቃራኒው ለመሄድ የመረጡበት አግባብ ትክክል አለመሆኑ ፣
🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴 🔴🔴🔴🔴🔴
ሀገራችን ኢትዮጵያ የብዝሀ ሃይማኖት መገኛ ሆና ሳለ ለዘመናት የሃይማኖቶች እኩልነትና የሐገር ባለቤትነት ጉዳይ ከሙስሊሙ አንፃር ሳይረጋገጥ በመኖሩ እስልምና እንደ ሃይማኖት ሙስሊሙ ማህበረሰብም እንደ ዜጋ ከፍ ያለ ዋጋ ሲከፍሉ ኖረዋል፡፡ በዚህም ምክንያት ህዝበ ሙስሊሙ ከንጉሳዊው የአስተዳደር ዘመን ጀምሮ መንግሰትና ሃይማኖት የተለያዩ እንዲሆኑና የሃይማኖት እኩልነትና ነፃነት እንዲከበር መራር ትግል ሲያደርግ ቆይቷል።
ከዚህም በመነሳት ሙስሊሙ በታላቁ የኢትዮጲያ ህዝባዊ አብዮት ዋነኛ ተሳታፊ ነበር። አብዮቱ ካስገኛቸው ድሎች አንዱ ለመጀመሪያ ጊዜ መንግስትና የሃይማኖት የተለያዩ መሆናቸው የተደነገገበት የደርግ ዘመን 1979 ህገ መንግሰት ተጠቃሽ ነው። ይሁን እንጂ መብቱ በህገመንግሰት ይካተት እንጂ በተግባር ስራ ላይ ሳይውል ጭቆናው ቀጥሎ ቆይቷል። በአንፃራዊነት በ1983 የነበረውን የመንግስት ለውጥ ተከትሎ የመንግስትና የሃይማኖት መለያየት በ1987 ፀድቆ እስከ አሁንም በስራ ላይ የሚገኘው የኢፊዴሪ ህገ-መንግስት በግልፅ በመቀመጡ ከቀድሞ የተሻለ ጊዜ ነበር ማለት ይቻላል፡፡
ነገር ግን ህገ-መንግስቱ ውስጥ በመርህ ደረጃ የተቀመጡትን የመንግሰትና ሐይማኖት መለያየት እንዲሁም የሃይማኖት እኩልነትና ነፃነት መብቶችና መሰረታዊ መርሆዎችና ድንጋጌዎች ለማስፈፀም የሚውሉ ዝርዝር ህጎች ሳይወጡ በመቆየቱ ምክንያት መብቶቹን በምሉዕነት መጠቀም አልተቻለም። ይባስ ብሎም አንዳንድ ተቋማት ህገመንግሰታዊ የሆነውን የመንግሰትና ሃይማኖት መለያየት መርህ ያልተገባ ትርጉም በመስጠት ለአድሏዊ አሰራር ሲያዉሉት ተስተውለዋል። አንዳንድ ተቋማትም የህገ-መንግስቱን ግልፅ ድንጋጌዎች የሚቃረኑ፤እንዲሁም በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የሙስሊሙን ማህበረሰብ ኢላማ ያደረጉ ደንቦች፤መመሪያዎችንና አሰራሮችን በመዘርጋት ህዝባችን ላይ ጥቃቶችና በደሎች ሲያደርሱበት በስፋት ተስተውለዋል ፡፡
የኢትዮጵያ ሙስሊም ማህበረሰብም በተለያዩ ጊዜያት እነዚህ በደሎችና ጥቃቶች በዘላቂነት ሊያስቆሙለት የሚያስችሉና ህገ መንግስተዊ መብቱን በምሉዕነት እንዲገለገልባቸው የሚያስችሉ ዝርዝር ህጎች በአግባቡ እንዲወጡና ስርዓት ያለው ወጥ አሰራር እንዲኖር ሲወተውቱ ቆይተዋል፡፡
ከዚህም በመነሳት የኢትዮጲያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ህገመንግስታዊውን የመንግስትና ሃይማኖት መለያየት መርህን እንዲሁም የሃይማኖት እኩልነትና ነፃነትን በዝርዝር ለማስፈፀም አዋጅ መውጣቱን በመርህ ደረጃ ይደግፈዋል። ይሁን እንጂ ከአዋጁ ረቂቅ ዝግጅት ጀምሮ ህጉን ለማውጣት እየተኬደበት ያለው ሂደትና ፤የረቂቅ አዋጁ ይዘትን አስመልክቶ ከሰሞኑ እየተስተዋለ ያለውን የህዝበ ሙስሊሙን ፍላጎትና ስጋት በእጅጉ ይጋራል።
ምክር ቤታችን መንግስት ሊያወጣው ያሰበው ረቂቅ አዋጅ እንደ ሙስሊም ማህበረሰብ ወኪልነቱ እንደዚ ያሉ መመሪያዎች ባለመኖራቸው የተነሳ በሙስሊሙ ላይ ይደርሱ የነበሩትን ያልተማከሉ ነገር ግን የተቀናጁ የሚመስሉ ጥቃቶችን በወጥነት ያስቆማል ብሎ ስለሚያምን ለአዋጁ ያለውን ድጋፍ ከወዲሁ መግለፅ ይፈልጋል። በአዋጁ ላይ ያሉንን አስተያየቶችና ስጋቶች የምንገልፀውም የመንግስትን ፍላጎት ወይም አላማ በመጥፎ በመረዳት ሳይሆን በሀገራችን የህግና የአዋጆች መውጣት ታሪክ የሙስሊሙ ማህበረሰብ ጥያቄዎችና ጥቅሞች የማይገናዘቡበት የቆየ አሰራር በመኖሩ አንዳንድ ለኛ ወሳኝ የሆኑ ነገሮችን አንድም ባለማወቅ ወይን ደግሞ በግለሰቦች የተለየ ፍላጎት የተነሳ ቸል ሲባሉ እና ሙስሊሙን ተጎጂ ሲያደርጉ በመኖራችን ስጋት ስላለን መሆኑን ማስገንዘብ እንፈልጋለን።
ይህ የአማኞች ሀገር በምትባለው ሀገራችን ሊወጣ እየተዘጋጀ የሚገኘው አዋጅም የሃይማኖትን እኩልነት፣ የመንግስትና የሃይማኖትን መለያየት በተለያዩ ጊዜያት በሙስሊሙ ማህበረሰብ በተለይም ደግሞ በትምህርት ቤቶችና በተለያዩ የመንግስት ተቋማት የሚገኙ ሙስሊም ሰራተኞችና ባለስልጣናት ላይ ይደርስ የነበረውን ግልጽ የሆነ ተቋማዊና ግለሰባዊ የሆነ የበደልና የጥቃት ተግባራትን ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ የሚቀርፍ መሆን እንዳለበት ም/ቤታችን ያምናል፡፡
ከዚህ አንፃር በረቂቅ አዋጁ ዙሪያ እየተነሱ ካሉ የህዝባችን ሃሳቦች በመነሳት ምክር ቤታችን በተወሰነ መልኩ ለማጣራት ባደረገው ጥረት ረቂቅ አዋጁ እነዚህን ነባር ችግሮች ከመቅረፍ ይልቅ የሚያባብሱና ተጨማሪ ችግሮችን የሚያስከትሉ አንዳንድ ድንጋጌዎች እንዳሉበት ለመገንዘብ ችሏል።
በመሆኑም በዚህ ጉዳይ ላይ ከሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ጋር በተደረገው ውይይት መሠረት ሰፋ ያለ የሙስሊሙን መብት የሚመለከቱ ጉዳዮችን በዝርዝር የሚያቀርብ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ ጠቅላይ ምክር ቤታችን ከዚህ በታች የተዘረዘሩ ጉዳዮች ላይ ያለውን ጥብቅ አቋምና ስጋት ለማቅረብ ይወዳል፡-
1. ምንም እንኳን ህግ መውጣቱ የምንፈልገውና የቆየ የህዝባችን ጥያቄ ቢሆንም የእምነታችንን የተለዩ የአምልኮ ባህሪያት ግምት ውስጥ ሳያስገባ በስመ እኩልነት ብቻ ከሌሎች ሃይማኖቶች የአምልኮ ስርዓት ጋር በማነፃፀር እዚህም እዚያም ከልክለናል በሚል የተሳሳተ መነሻ የተቀረፀው እንዲሁም በእምነታችን የአምልኮ ስርዓት ውስጥ በመግባት አንድ ሙስሊም በእምነቱ የታዘዘውን የአምልኮ ተግባር እንዴት ማከናወን እንዳለበት እሰከመምረጥ ድረስ ገደብ ለመጣል በሚሞክሩ አናቅፅ የተሞላ ረቂቅ አዋጅ መሆኑ ተገቢ ስላልሆነ ፣
2. የሃይማኖትና የአማኞች ሃገር ናት የምትባለውን ሃገራችንን ሃይማኖታዊ እሴቶች ከማጎልበትና ሃይማኖቶችን ለሃገራዊ አንድነትና እድገት በአዎንታዊነት ከመጠቀም ይልቅ የሀገራችንን ተጨባጭ ባለማገናዘብና ወደጐን በመተው እምነቶችን በበማዳከም ለሃገር ከሚያበረክቱት ገንቢ አስተዋፅኦ የማግለል ባህሪ ያለው በመሆኑ ፣
3. ሃገራችን ህብረ ብሄራዊ የፌዴራል ስርዓት የምትከተል እንደመሆንዋ በተለያዩ ክልሎች በመሬት ላይ ያለውን እውነታ በፍፁም ከግምት ውስጥ ያልከተተና ተፈፃሚነት የሌለው ህግ እንዳይሆን የሚያሰጋ በመሆኑ፣
4. ረቂቅ አዋጁ በመሠረቱ አንድ ህግ ለሀገርና ለህዝብ ጥቅም ሲባል የሚወጣበትን መርህ በመጣስ በህገ መንግስቱ የተረጋገጠውን የእምነት መብትና ነፃነትን ከማስፈፀም ይልቅ መገደብ ላይ በማተኮር የአለም አቀፍ ህጐችንና ህገ መንግስታችንን የሚቃንኑ ሀሳቦች ያሉበት በመሆኑ ፣
5. የመንግሰትና ሃይማኖት መለያየት መርህ ዋና አስኳል የሆነውን የመንግስትን በሃይማኖት ውስጥ ጣልቃ የመግባት ሁኔታ ከመገደብ ይልቅ፤ያለአግባብ መንግሰት በሃይማኖት ጉዳዮች ጣልቃ መግባትን የሚያበረታታና መንግስት የሀይማኖቶች ተቆጣጠሪ የማድረግ ባህሪ ያለው በመሆኑ ፣
6. ሕገመንግስታዊውን የሃይማኖት ነፃነትን ከማስከበር አንፃር የእምነታችንን ልዩ የአምልኮ ባህሪያት በመረዳት ለዚያ የሚመች ሁኔታዎችን ከማመቻቸት ይልቅ አምልኮዎችን መከልከል ላይ ማተኮሩ፣
ለምሳሌ፡- በት/ት ቤቶች እና በመንግስት ተቋማት አካባቢ ሙስሊሙ ግዴታ የሆነበትን ሰላትና የሴቶች አለባበስ ሁኔታ የመከልከልን ባህሪያት የተሞላ መሆኑ ፣
7. የመንግስትና የሃይማኖትን መለያየት አስመልክቶ ለረቂቅ አዋጁ ግብዓት ተደርገው የነበሩ ጥናቶችን ውጤትና ምክረ ሃሳቦች ወደጐን በመተው ህግ አርቃቂዎቹ አካላት በተቃራኒው ለመሄድ የመረጡበት አግባብ ትክክል አለመሆኑ ፣
👍5❤1
ባለፉት 29 ዓመታት የህገ-መንግስቱን ግልጽ ድንጋጌዎች ሆንብሎ ያለአግባብ በመተርጐም ሙስሊሙ ማህበረሰብ በልዩነት ሲጠቃባቸው የነበሩና ማህበረሰቡም ከፍተኛ ተቃውሞ ሲያቀርብባቸው የነበሩ መመሪያዎችና አሰራሮች መወገድ ሲገባቸው በዚህ ረቂቅ አዋጅ ውስጥ በድጋሚ ተካተው መገኘታቸው በህዝብ ዘንድ ከወዲሁ እየፈጠረ ያለው ከፍተኛ የስጋት ስሜት ለወደፊቱም ከሀገር ደህንነትና ሰላም አንፃር የሚያመጣውን ውጥረት ከግምት ውስጥ በማስገባት፣
አዋጁ በብስለትና በስክነት ታይቶ ተጨባጭ የሆኑ የጥናት ውጤቶች ተንፀባርቀውበት፣ ከገዳቢነት ይልቅ መብት ማስከበርን መርሁ ያደረገ አዋጅ እንዲሆን እንደገና እንዲከለስና ተጨማሪ ሰፊ ጊዜ ተወስዶበት እንዲወጣ ያለንን አቋምና ስጋት እየገለፅን ም/ቤታችን ከዚህ አንፃር የሙስሊሙን ማህበረሰብ ፍላጎትና መብት እንዲሁም በረቂቅ አዋጁ ላይ ቢካተቱ የሚላቸውን ገንቢ ሀሳቦች በዝርዝር በአጭር ጊዜ ውስጥ ለሚመለከታቸው አካላት ሁሉ የሚያቀርብ መሆኑን እያሳወቀ ለዚህም ይረዳ ዘንድ ረቂቅ አዋጁ እንደ ተቋም በፅሁፍ እንዲደርሰን ለመጠየቅ እንወዳለን፡፡
“ከሰላምታ ጋር”
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት
አዋጁ በብስለትና በስክነት ታይቶ ተጨባጭ የሆኑ የጥናት ውጤቶች ተንፀባርቀውበት፣ ከገዳቢነት ይልቅ መብት ማስከበርን መርሁ ያደረገ አዋጅ እንዲሆን እንደገና እንዲከለስና ተጨማሪ ሰፊ ጊዜ ተወስዶበት እንዲወጣ ያለንን አቋምና ስጋት እየገለፅን ም/ቤታችን ከዚህ አንፃር የሙስሊሙን ማህበረሰብ ፍላጎትና መብት እንዲሁም በረቂቅ አዋጁ ላይ ቢካተቱ የሚላቸውን ገንቢ ሀሳቦች በዝርዝር በአጭር ጊዜ ውስጥ ለሚመለከታቸው አካላት ሁሉ የሚያቀርብ መሆኑን እያሳወቀ ለዚህም ይረዳ ዘንድ ረቂቅ አዋጁ እንደ ተቋም በፅሁፍ እንዲደርሰን ለመጠየቅ እንወዳለን፡፡
“ከሰላምታ ጋር”
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት
👍10🥰3
⏳ Only One Day Left to Register! ⏳
Tomorrow is the final day to secure your spot in the AAiT Quran Competition. Don't miss your chance to showcase your talent and connect with the Holy Quran. Whether you're a seasoned reciter or just starting your journey, there's a category for everyone! From Recitation with Eyes to mastering 30 Juz’, this competition celebrates dedication and skill.
🎉 With a grand total prize pool of 50,000+ ETB, there are exciting prizes up for grabs! 💰
⏰ Register now through the links below and secure your spot:
For brothers: https://forms.gle/htC6qbVDc5Pk3hzH8
For sisters: https://forms.gle/iW82H3VyJRMYN4aJ8
Deadline: Tomorrow, May 10, 2024
🌿🤝 Open to all students of AAU, Male and Female, regardless of campus. Don't miss out - register now and embark on a journey of spiritual growth!
#AAiTQuranCompetition #QuranExcellence #SpiritualEnrichment
Verily the one who recites the Qur'an beautifully, smoothly, and precisely, he will be in the company of the noble and obedient angels.
Tomorrow is the final day to secure your spot in the AAiT Quran Competition. Don't miss your chance to showcase your talent and connect with the Holy Quran. Whether you're a seasoned reciter or just starting your journey, there's a category for everyone! From Recitation with Eyes to mastering 30 Juz’, this competition celebrates dedication and skill.
🎉 With a grand total prize pool of 50,000+ ETB, there are exciting prizes up for grabs! 💰
⏰ Register now through the links below and secure your spot:
For brothers: https://forms.gle/htC6qbVDc5Pk3hzH8
For sisters: https://forms.gle/iW82H3VyJRMYN4aJ8
Deadline: Tomorrow, May 10, 2024
🌿🤝 Open to all students of AAU, Male and Female, regardless of campus. Don't miss out - register now and embark on a journey of spiritual growth!
#AAiTQuranCompetition #QuranExcellence #SpiritualEnrichment
👍2
📢 Attention All 6 Kilo Muslim Students! 📢
Assalamu Alaikum Warahmatullahi Wabarakatuh !
Praise be to Allah! Our special program is happening next Saturday just for you! Join us for a day filled with learning and excitement.
🎓 Listen to senior students as they talk about different departments, helping you figure out your path.
❓ Ask questions and get answers from students who've been there before, making learning super fun!
🏆 Plus, we'll be giving awards to our top students! Your hard work will be recognized!
🌟 And don't forget, we'll also be honoring the winners and participants of the Qalam Question and Answer Competition! Get ready to be inspired!
Don't miss out! Come and be part of this awesome event! See you there!
📆Date :- Saturday, May 11
⏰Time:- 2:30 LT in the morning
📍Location: Al-Aqsa Mesjid
@aaumsu
Assalamu Alaikum Warahmatullahi Wabarakatuh !
Praise be to Allah! Our special program is happening next Saturday just for you! Join us for a day filled with learning and excitement.
🎓 Listen to senior students as they talk about different departments, helping you figure out your path.
❓ Ask questions and get answers from students who've been there before, making learning super fun!
🏆 Plus, we'll be giving awards to our top students! Your hard work will be recognized!
🌟 And don't forget, we'll also be honoring the winners and participants of the Qalam Question and Answer Competition! Get ready to be inspired!
Don't miss out! Come and be part of this awesome event! See you there!
📆Date :- Saturday, May 11
⏰Time:- 2:30 LT in the morning
📍Location: Al-Aqsa Mesjid
@aaumsu
🔥3🥰3👌1
በ 6 Kilo Academic Award ላይ ተወዳድራችሁ መሸለም የምትፈልጉ ተማሪዎች ለመመዝገብ እስከ ምሽቱ 5 ሰዓት ድረስ ግዜ አላችሁ። የመመዝገቢያ ፎርሙ ከታች ያለው ነው👇👇👇
https://surveyheart.com/form/66340e5e448f481596f27bda
Barattoonni 6 Kilo Academic Award irratti dorgomuun badhaafamu barbaaddan galmeedhaaf hanga halkan sa'aatii 5tti yeroo qabduu. Formiin galmee kan armaan gadiitti argamudha👇👇👇
https://surveyheart.com/form/66340e5e448f481596f27bda
@aau6kilojemea
https://surveyheart.com/form/66340e5e448f481596f27bda
Barattoonni 6 Kilo Academic Award irratti dorgomuun badhaafamu barbaaddan galmeedhaaf hanga halkan sa'aatii 5tti yeroo qabduu. Formiin galmee kan armaan gadiitti argamudha👇👇👇
https://surveyheart.com/form/66340e5e448f481596f27bda
@aau6kilojemea
👍1
ፍትሕ ሚኒስቴር እንዴት መስገድ እንዳለብንና ምን መልበስ እንዳለብን ጭምር የሚነግር ረቂቅ ደንብ አውጥቶ ለማፅደቅ ሽር ጉድ ላይ ነው:: ይህንን ረቂቅ መመሪያ ማውጣቱ የንቀቱን ልክ ቢያሳይም ማህበረሰቡ የሰጠው በዝምታ የተዋጠ መልስ ደግሞ ያስደነግጣል:: ለምን ቸል ተባለ የሚለው ጥያቄ ምላሽ ያሻል:: ህዝቡ መንቃት አለበት:: ሴኩላር በሆነች ሀገር ውስጥ ስለ አምልኮ ተግባራችሁ ልወቅላችሁ እስከ ማለት ድረስ የደረሰ መመሪያ እምቢኝ ሊባል ይገባል:: የሃይማኖት ነፃነት መብት ሲደፈር ዝም ተብሎ ሊታይ አይገባም::
ከዚያ ባሻገር መመሪያው ተሻሽሎ የዜጎችን የሃይማኖት ነፃነት መብት ባከበረና የሴኩላሪዝምን መሰረታዊ መርሆ በጠበቀ መልኩ ሊፀድቅ ግድ ይላል::
@aaumsu
ከዚያ ባሻገር መመሪያው ተሻሽሎ የዜጎችን የሃይማኖት ነፃነት መብት ባከበረና የሴኩላሪዝምን መሰረታዊ መርሆ በጠበቀ መልኩ ሊፀድቅ ግድ ይላል::
@aaumsu
👍6🔥5
ከሰሞኑ በአወዛጋቢነቱ አጀንዳ ሁኖ የቆየው በፍትሕ ሚንስትር የተዘጋጀው "የሀይማኖት ጉዳዮች አዋጅ"ከዩንቨርሲቲ ተወካዮች ጋር በአዳማ ከተማ ውይይት ማድረጉ ተሰምቷል።
...
ውይይቱ የተዘጋጀው በሰላም ሚኒስትር ሲሆን በውይይቱ ላይ ከዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንትና አንድ መምህር በአጠቃላይ ከአንድ ዩኒቨርስቲ ሁለት (2)ተወካዮች ያካተተ መሆኑን ለሀሩን ሚዲያ ምንጮች ገልጸዋል።በውይይቱ ሁሉንም ሀይማኖቶች የሚመለከቱ ጉዳዮች የተነሱ ሲሆን በረቂቅ አዋጁ ከተካተቱት መካከል በተለይ ኢስላምን የተመለከቱ ህጎች "በቡድን ማምለክ"እና "ማንነትን የሚያሳይ አለበባስ"ብቻ መፍቀዱ በጋራ ሰላት መስገድን እና ኒቃብ መለበስ የሚከለክል በመሆኑ አንድ ሀይማኖት ላይ ብቻ ያነጣጠረ ለአፈፃም የሚችግር መሆኑን ከምሁራኑ ተነስቷል።
...
ከኦዲት ሪፖርት ከፋይናንስ ቁጥጥር መንግስት በሃይማኖት ያለውን ጣልቃ ገብነት በተመለከተ ፣የሀይማኖት ተቋማት ግንባታ ሊሎር የሚገባ እርቀት ፣የመቃብር ቦታዎች እና ሌሎችም ሰፊ ሀሳቦች መነሳታቸው ተገልጿል።በውይይቱ የጅግጅጋ ዩኒቨርስቲ ሰመራ እና መዳወላቡ ዩኒቨርስቲ አለመሳተፋቸውም ተነስቷል።
..
በመጨረሻም ውይይት ሲመሩ የነበሩ አካላት የተነሱ ሀሳቦች ላይ ምላሽ የሰጡ ሲሆን በተለይ በቡድን አምልኮ እና ማንነት የተመለከተ አልባሳት ላይ በድጋሜ ከሀይማኖት አባቶች ጋር ውይይት እንደሚያደርጉበት መናገራቸውን የሀሩን ሚዲያ ምንጮች ገልጸዋል።ውይይቱ በተመሳሳይ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጋር ደግሞ ቅዳሜ ውይይት እንደሚደረግ ለማወቅ ተችሏል። በረቂቅ አዋጁ ዙሪያ ከእስልምና ሀይማኖት ተከታዮች በተጨማሪ ሙስሊም ያልሆኑ አካላትም ቅሬታቸውን እያቀረቡ ሲሆን አዋጁ ከመጽደቁ በፊት የህዝብ ቅሬታዎችን ባማከለ መልኩ እንዲስተካከል የተለያዩ ሀይማኖታዊ ተቋማት በየፊናቸው ጥሪ በማቅረብ ላይ ይገኛ
harun media
...
ውይይቱ የተዘጋጀው በሰላም ሚኒስትር ሲሆን በውይይቱ ላይ ከዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንትና አንድ መምህር በአጠቃላይ ከአንድ ዩኒቨርስቲ ሁለት (2)ተወካዮች ያካተተ መሆኑን ለሀሩን ሚዲያ ምንጮች ገልጸዋል።በውይይቱ ሁሉንም ሀይማኖቶች የሚመለከቱ ጉዳዮች የተነሱ ሲሆን በረቂቅ አዋጁ ከተካተቱት መካከል በተለይ ኢስላምን የተመለከቱ ህጎች "በቡድን ማምለክ"እና "ማንነትን የሚያሳይ አለበባስ"ብቻ መፍቀዱ በጋራ ሰላት መስገድን እና ኒቃብ መለበስ የሚከለክል በመሆኑ አንድ ሀይማኖት ላይ ብቻ ያነጣጠረ ለአፈፃም የሚችግር መሆኑን ከምሁራኑ ተነስቷል።
...
ከኦዲት ሪፖርት ከፋይናንስ ቁጥጥር መንግስት በሃይማኖት ያለውን ጣልቃ ገብነት በተመለከተ ፣የሀይማኖት ተቋማት ግንባታ ሊሎር የሚገባ እርቀት ፣የመቃብር ቦታዎች እና ሌሎችም ሰፊ ሀሳቦች መነሳታቸው ተገልጿል።በውይይቱ የጅግጅጋ ዩኒቨርስቲ ሰመራ እና መዳወላቡ ዩኒቨርስቲ አለመሳተፋቸውም ተነስቷል።
..
በመጨረሻም ውይይት ሲመሩ የነበሩ አካላት የተነሱ ሀሳቦች ላይ ምላሽ የሰጡ ሲሆን በተለይ በቡድን አምልኮ እና ማንነት የተመለከተ አልባሳት ላይ በድጋሜ ከሀይማኖት አባቶች ጋር ውይይት እንደሚያደርጉበት መናገራቸውን የሀሩን ሚዲያ ምንጮች ገልጸዋል።ውይይቱ በተመሳሳይ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጋር ደግሞ ቅዳሜ ውይይት እንደሚደረግ ለማወቅ ተችሏል። በረቂቅ አዋጁ ዙሪያ ከእስልምና ሀይማኖት ተከታዮች በተጨማሪ ሙስሊም ያልሆኑ አካላትም ቅሬታቸውን እያቀረቡ ሲሆን አዋጁ ከመጽደቁ በፊት የህዝብ ቅሬታዎችን ባማከለ መልኩ እንዲስተካከል የተለያዩ ሀይማኖታዊ ተቋማት በየፊናቸው ጥሪ በማቅረብ ላይ ይገኛ
harun media
🔥9👌3
Q. What makes a man lose his honor?
Imam shafi'i: talking too much, exposing people's secrets and placing his hopes and trust in every single person.
@aaumsu
Imam shafi'i: talking too much, exposing people's secrets and placing his hopes and trust in every single person.
@aaumsu
👍15❤6
🌟 Friendly Reminder for Tomorrow! 🌟
Assalamu Alaikum, dear 6 Kilo Muslim Students!
Just a gentle nudge to remind you about our special program happening tomorrow! Get ready to embark on a journey of enlightenment with your fellow students.
📆Date :- Tomorrow, May 11
⏰Time:- 2:30 LT in the morning
📍Location: Al-Aqsa Mesjid
Join us as we delve into discussions about various departments, seek guidance, and recognize the achievements of our top-performing students. Plus, don't miss the exciting awards ceremony honoring the winners of the Qalam Question and Answer Competition!
@aau6kilojemea
Assalamu Alaikum, dear 6 Kilo Muslim Students!
Just a gentle nudge to remind you about our special program happening tomorrow! Get ready to embark on a journey of enlightenment with your fellow students.
📆Date :- Tomorrow, May 11
⏰Time:- 2:30 LT in the morning
📍Location: Al-Aqsa Mesjid
Join us as we delve into discussions about various departments, seek guidance, and recognize the achievements of our top-performing students. Plus, don't miss the exciting awards ceremony honoring the winners of the Qalam Question and Answer Competition!
@aau6kilojemea
👌6👍3❤1
🥀 Daily Reminder 113🥀
يَٰٓأَيُّهَا ٱلۡإِنسَٰنُ مَا غَرَّكَ بِرَبِّكَ ٱلۡكَرِيمِ(6)
"አንተ ሰው ሆይ! በቸሩ ጌታህ ምን አታለለህ( አዘናጋህ)??"
Surah Al-Infitar; 6
@aaumsu
يَٰٓأَيُّهَا ٱلۡإِنسَٰنُ مَا غَرَّكَ بِرَبِّكَ ٱلۡكَرِيمِ(6)
"አንተ ሰው ሆይ! በቸሩ ጌታህ ምን አታለለህ( አዘናጋህ)??"
Surah Al-Infitar; 6
@aaumsu
🥰9👍2
Imagine that after all this the supporters of such criminality come to talk to you about children's rights and women's rights, criticizing Sharia laws because they claim that they contradict these rights, and impose the curricula they want for the children of Muslims in schools.
Copied
@aaumsu
Copied
@aaumsu
😭17😡2❤1
የኦዳ ቡልቱም ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ ክብር ይገባቸዋል!!
ከላይ በምስሉ ላይ የሚታዬው አብርሐም የተባለ የሪሜድያል ተማሪ በቲክቶክ ስለ ቁርዓን ቁርዓን ላይ የሌለ ቃልን በመጠቀም በኦሮምኛ ቋንቋ ለ4 ደቂቃ የዘለቀ መልዕክት አስተላልፎ ነበር:: ከዚህ ክስተት ቡሃላ ጀመዓው ባደረገው እንቅስቃሴ ተማሪው በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን ከዩኒቨርሲቲው ጋር በነበረ ንግግር ተማሪው ተማሪዎችን ወደ ሃይማኖት ግጭት ሊያስገባ የሚችል ንግግር በመናገር ወንጀል ተከሶ ለ2 አመት ከትምህርት እንዲታገድ ተወስኖበታል::
የኦዳቡልቱም ጀመዓ ስለ ትጋታችሁ ምስጋና ይገባችሗል:: የኦዳቡልቱም አካባቢ ፖሊስና የዩኒቨርሲቲው አካላት ስለ አፋጣኝ ምላሻችሁ ምስጋና ይገባችሗል::
@MohammadamminKassaw
ከላይ በምስሉ ላይ የሚታዬው አብርሐም የተባለ የሪሜድያል ተማሪ በቲክቶክ ስለ ቁርዓን ቁርዓን ላይ የሌለ ቃልን በመጠቀም በኦሮምኛ ቋንቋ ለ4 ደቂቃ የዘለቀ መልዕክት አስተላልፎ ነበር:: ከዚህ ክስተት ቡሃላ ጀመዓው ባደረገው እንቅስቃሴ ተማሪው በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን ከዩኒቨርሲቲው ጋር በነበረ ንግግር ተማሪው ተማሪዎችን ወደ ሃይማኖት ግጭት ሊያስገባ የሚችል ንግግር በመናገር ወንጀል ተከሶ ለ2 አመት ከትምህርት እንዲታገድ ተወስኖበታል::
የኦዳቡልቱም ጀመዓ ስለ ትጋታችሁ ምስጋና ይገባችሗል:: የኦዳቡልቱም አካባቢ ፖሊስና የዩኒቨርሲቲው አካላት ስለ አፋጣኝ ምላሻችሁ ምስጋና ይገባችሗል::
@MohammadamminKassaw
👍40👌8👏3❤1🔥1
❤16👌4👍1
የፍትሕ ሚኒስቴር ረቂቅ መመሪያ- ግልፅ ለማድረግ !
የህዝቡ ዝምታ ወይ ጥልቅ ከሆነ ቁጣ ወይ ደግሞ ጥልቅ ከሆነ የግንዛቤ እጥረት ሊሆን ይችላል:: ከቁጣ ከሆነ ይበል የሚያስብል ሆኖ ሲፈነዳ የሚታይ ይሆናል:: ከግንዛቤ እጥረት የመሆን እድሉ ሰፊ ነውና የረቂቅ መመሪያው አንደምታው ምንድን ነው የሚለውን እንደሚከተለው እንመልከት::
አይበለውና ከፀደቀ በየትኛውም የትምህርት ተቋማት ኒቃብ ለብሶ መማር ይከለከላል:: ይህ ከሆነ ለአመታት ሲደረጉ የነበሩ ትግሎች አፈር ከመልበሳቸው ባሻገር የትምህርት ተቋሞቻችን ህጋዊ ስልጣን ኖሯቸው ኒቃቢስቶችን አንቀበልም የማለት ሙሉ ስልጣን ይኖራቸዋል:: "ለምን?" ሲባሉም መመሪያው ስለሚያዝ ነው የሚል ምላሽን ይሰጣሉ:: "ሕገ-መንግስቱስ?" ከተባሉም ውይይት ተደርጎበት ከሕገ-መንግስት ጋር ምንም አይነት መጣረስ እንደሌለበት ታምኖ የፀደቀ ነው የማለት መብቱ አላቸው:: በዚህ ውስጥ ወትሮውንም በትምህርት ስርዓቱ ያልታቀፈው ሙስሊም በዚህ ሳቢያ ይገፋል:: ትምህርትን እየጠላ ከማዕቀፉ በሲስተም ይወጣል:: በሁለተኛ ደረጃ በትምህርት ተቋማት ውስጥ ሶላት በጀመዓ መስገድ ይከለክላል:: ወንድምህ ወይም እህትሽ እየሰገዱ ሄዶ ተከትሎ መስገድ ሊያስቀጣ ማለት ነው:: በዚህም ሂደት ከሚቀጣው ተማሪ ባሻገር በሙስሊሙ ዘንድ የባለቤትነት ስሜት እየጠፋ የትምህርት ስርዓቱን በቋሚነት ችላ የሚልበት ስርዓት ይዘረጋል::
በሌላ አውድ ገልብጠን ስንመለከተው ደግሞ ሰፊ የሆነ እድል እናገኛለን:: መመሪያው አሉታዊ ይዘት ባላቸው አንቀፆች እንደተሞላ የተገለፀ ቢሆንም በረቂቅ ደረጃ ያለ ስለሆነ ከላይ እስከ ታች ያለው የህብረተሰብ ክፍል ተፅዕኖ በመፍጠር ከሕገ-መንግስቱ በማይጣረስ መልኩ እንዲፀድቅ ማድረግ ይቻላል:: በዚያ ሂደት ውስጥ የሃይማኖት ነፃነት መብታችንና ሴኩላሪዝም በአግባቡ እንዲከበሩ ማድረግ ከቻልን እስከ ዛሬ በተለያየ ምክንያት አንዴ ሒጃብ ለበሳችሁ ሌላ ጊዜ ሶላት ሰገዳችሁ እያሉ ሲበጠብጡ የነበሩ ሁሉ ተጠያቂ ይሆናሉ ማለት ነው::
ስለሆነም ችላ ሊባል አይገባም:: የዚህ ትውልድ ትልቁ ሀላፊነት ይህንን ፈተና በድል መወጣት ነው:: ሁሉም ትኩረት ሰጥቶ awareness ከመፍጠር ጀምሮ ባሉት እንቅስቃሴዎች ላይ በመሳተፍ ለዘመናት የጭቃ እሾህ ሆኖ ሲነዘንዘን የነበረውን እንቅፋት ማስወገድ ግድ ይለናል::
@aaumsu
የህዝቡ ዝምታ ወይ ጥልቅ ከሆነ ቁጣ ወይ ደግሞ ጥልቅ ከሆነ የግንዛቤ እጥረት ሊሆን ይችላል:: ከቁጣ ከሆነ ይበል የሚያስብል ሆኖ ሲፈነዳ የሚታይ ይሆናል:: ከግንዛቤ እጥረት የመሆን እድሉ ሰፊ ነውና የረቂቅ መመሪያው አንደምታው ምንድን ነው የሚለውን እንደሚከተለው እንመልከት::
አይበለውና ከፀደቀ በየትኛውም የትምህርት ተቋማት ኒቃብ ለብሶ መማር ይከለከላል:: ይህ ከሆነ ለአመታት ሲደረጉ የነበሩ ትግሎች አፈር ከመልበሳቸው ባሻገር የትምህርት ተቋሞቻችን ህጋዊ ስልጣን ኖሯቸው ኒቃቢስቶችን አንቀበልም የማለት ሙሉ ስልጣን ይኖራቸዋል:: "ለምን?" ሲባሉም መመሪያው ስለሚያዝ ነው የሚል ምላሽን ይሰጣሉ:: "ሕገ-መንግስቱስ?" ከተባሉም ውይይት ተደርጎበት ከሕገ-መንግስት ጋር ምንም አይነት መጣረስ እንደሌለበት ታምኖ የፀደቀ ነው የማለት መብቱ አላቸው:: በዚህ ውስጥ ወትሮውንም በትምህርት ስርዓቱ ያልታቀፈው ሙስሊም በዚህ ሳቢያ ይገፋል:: ትምህርትን እየጠላ ከማዕቀፉ በሲስተም ይወጣል:: በሁለተኛ ደረጃ በትምህርት ተቋማት ውስጥ ሶላት በጀመዓ መስገድ ይከለክላል:: ወንድምህ ወይም እህትሽ እየሰገዱ ሄዶ ተከትሎ መስገድ ሊያስቀጣ ማለት ነው:: በዚህም ሂደት ከሚቀጣው ተማሪ ባሻገር በሙስሊሙ ዘንድ የባለቤትነት ስሜት እየጠፋ የትምህርት ስርዓቱን በቋሚነት ችላ የሚልበት ስርዓት ይዘረጋል::
በሌላ አውድ ገልብጠን ስንመለከተው ደግሞ ሰፊ የሆነ እድል እናገኛለን:: መመሪያው አሉታዊ ይዘት ባላቸው አንቀፆች እንደተሞላ የተገለፀ ቢሆንም በረቂቅ ደረጃ ያለ ስለሆነ ከላይ እስከ ታች ያለው የህብረተሰብ ክፍል ተፅዕኖ በመፍጠር ከሕገ-መንግስቱ በማይጣረስ መልኩ እንዲፀድቅ ማድረግ ይቻላል:: በዚያ ሂደት ውስጥ የሃይማኖት ነፃነት መብታችንና ሴኩላሪዝም በአግባቡ እንዲከበሩ ማድረግ ከቻልን እስከ ዛሬ በተለያየ ምክንያት አንዴ ሒጃብ ለበሳችሁ ሌላ ጊዜ ሶላት ሰገዳችሁ እያሉ ሲበጠብጡ የነበሩ ሁሉ ተጠያቂ ይሆናሉ ማለት ነው::
ስለሆነም ችላ ሊባል አይገባም:: የዚህ ትውልድ ትልቁ ሀላፊነት ይህንን ፈተና በድል መወጣት ነው:: ሁሉም ትኩረት ሰጥቶ awareness ከመፍጠር ጀምሮ ባሉት እንቅስቃሴዎች ላይ በመሳተፍ ለዘመናት የጭቃ እሾህ ሆኖ ሲነዘንዘን የነበረውን እንቅፋት ማስወገድ ግድ ይለናል::
@aaumsu
👍17🔥5🫡3❤1