AAU - Muslim Students Union
6.45K subscribers
2.68K photos
149 videos
51 files
765 links
This is the official channel of AAU-MSU.

Group: @aaumsu_discussion
Youtube: youtube.com/@aaumsu
Twitter: x.com/aaumsu12
Facebook: facebook.com/profile.php?id=100087931837303

Contact us: @Aaumuslimstudentsunion1
Email: aaumsu12@gmail.com
Download Telegram
"በእኔና በአላህ መካከል ሀጃ አለና እንዲሳካ ዱዓ አድርጉልኝ!" በማለት ለሐዋሳው መስጂድ 200 ብር ገቢ አድርገዋል :: አላህ ሐጃቸውን ባማረ መልኩ ይሙላላቸው :: በዱንያም በአኼራም የሚያማምሩ ነገሮችን ይስጣቸው ::
6👍2
እህታችን ለሐዋሳ ወንድም እህቶች መስጂድ 200 ብር አስገብታለች :: አላህ ህይዎቷን በብርሃን ይሙላ :: የዱንያ ህይዎቷን በብርሃን ይሙላ :: የቀብር ህይዎቷን በብርሃን ይሙላ :: የአኼራ ህይዎቷን በብርሃን ይሙላ ::
👍5
Reading makes you a better person !

@aaumsu
👌62👍2
የአሉባልታ እድሜ ከብልህ ሰው ጆሮ እስኪደርስ ብቻ ነው ::

@aaumsu
🥰8👏4
Very soon !
inshallah !


@aaumsu
20🥰2👍1
✔️ የሸዋል ፆም

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦

﴿مَن صامَ رَمَضانَ ثُمَّ أتْبَعَهُ سِتًّا مِن شَوّالٍ، كانَ كَصِيامِ الدَّهْرِ.﴾

“ረመዳንን ፆሞ የሸዋልን ስድስት ቀናት ፆምን ያስከተለ አመቱን ሙሉ እንደፆመ ይቆጠራል።”

📚 ሙስሊም ዘግበውታል

@aaumsu
👍111
100 ቀን እና መሰል የተመራቂ ተማሪዎችን ፕሮግራም የምትሳተፉ እህት ወንድሞች:- ፕሮግራሞቹ ላይ የሚከናወኑ ተግባራት ማለትም ከጭፈራ  ጀምሮ ያሉ ክንውኖች ከሀይማኖታችን መሰረታዊ መርሆ ያፈነገጡና ከአላህ ጋር የሚያጣሉ ስለሆነ አላህን ፈርታችሁ መሰል ፕሮግራሞች ላይ ከመሳተፍ ተቆጠቡ ::

@aaumsu
👍18👌2
Overthinking -> istigfar
Anxious = Istigfar
Depressed -> istigfar
Angry -> istigfar
Lazy to get up and pray -> istigfar
Losing your iman-> istigfar
Broke-> istigfar

@aaumsu
👌22👍85🔥3
🥀 Daily Reminder 86🥀

ٱلۡحَمۡدُ لِلَّهِ رَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ(2)

"ምስጋና የዓለማት ጌታ ለኾነው ለአላህ ይገባው!!"

Surah Al-Fatiha; 2

@aaumsu
10🥰3🔥1
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ለሐዋሳ ሪፈራል ካምፓስ ሙስሊም ተማሪዎች መስጂድ ግንባታ 60000 ብር አበርክቷል።

   ለ5 ቀናት በተደረገ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ-ግብር ለሐዋሳ ሪፈራል ካምፓስ ሙስሊም ተማሪዎች መስጂድ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪወች 60000 ብር የተሰበሰበ ሲሆን በዛሬው እለት ገቢ ተደርጓል። በመጀመሪያ ደረጃ ይህንን ለፈቀደልን አምላካችን አላህ ላቅ ያለ ምስጋና ይድረስ። በመቀጠል በዚህ ንቅናቄ ላይ በእጅጉ የተሳተፋችሁን ሁሉ በተለይም የጀመዓችን እንቁ የሆናችሁ ተማሪዎች : አልሙናይ እንዲሁም የሌላ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እና የሀይስኩል ተማሪዎችን በአላህ ስም እናመሠግናለን:: አላህ ያክብርልን::

በመጨረሻም ይህ ከችግራችን አንድ ከአላማችን በማንኪያ መሆኑን አውቃችሁ በህብረት በምንሰራቸው ስራዎች ላይ በንቃት ትሳተፉ ዘንድ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን::

AAU MUSLIM STUDENTS UNION !

@aaumsu
👏244👌3👍2
ችግርን ተከፋፍሎ መሸከም መቻል ፀጋም ድልም ነው።

@aaumsu
👍143
የሐዋሳ ሪፈራል ካምፓስ ሙስሊም ተማሪዎች መስጂድን በጋራ እንገንባ!

   የሐዋሳ ሪፈራል ካምፓስ ሙስሊም ተማሪዎች ከሁለት አመት በፊት በነበረ ንቅናቄ 2 ሚልዬን ብር ከማህበረሰቡ አሰባስበን ለመስጅድ መስሪያ የሚሆን 350 ካሬ መሬት ገዝተናል :: ከዚያ ቡሃላ አነስተኛ ቤቶችን ሰርተን እየሰገድንና ዲናችንን እየተማርን ቢሆንም አሁን ላይ ቤቶቹ ለመፍረስ ጥቂት ብቻ ነው የቀራቸው :: ቦታውም ማስፋፊያ ይፈልጋል ::

   በአካባቢው ያለው መስጂድ እሱ ብቻ መሆኑ : አካባቢው ለአክፍሮት ሀይላት ተጋላጭ መሆኑ እንዲሁም ተማሪውና ማ/ሰቡ የአቅም ማነስ ውስጥ መግባታቸው መስጂዳችንን አብረን እንገነባ ዘንድ ጥሪ እንድናስተላልፍላችሁ አስገድዶናል ::

ለዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች መስጂድን ገንብቶ ያለምንም ተፅዕኖ እንዲሰግዱና ዲናቸውን እንዲማሩ ማድረግ ተማሪውን በዲኑ እንዲጠነክር መሰረት መጣል ነውና ሁላችሁም ተረባርባችሁ ትገነቡት ዘንድ እንጠይቃለን ::

የአካውንት ስም:- ሀዋሳ ሪፈራል ተማሪዎች መስጂድ

📌 Commercial Bank of Ethiopia - 1000412678854
📌 Cooperative Bank of Oromia - 1006700037551
📌 Awash Bank - 01425493086500

ለትውልድ የሚተላለፍ ተቋም በመገንባት ውስጥ የአኼራ ቤታችንን እንገንባ !

የሀዋሳ ሪፈራል ካምፓስ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ !

@aaumsu
👍6
AAU - Muslim Students Union
Photo
ለሐዋሳ ሪፈራል ካምፓስ ሙስሊም ተማሪዎች መስጂድ ማስገንቢያ ማስገባት የምትፈልጉ ከላይ ባሉት አማራጮች አስገቡላቸው :: መልዕክቱንም ለሌሎች በማጋራትና ተደራሽ እንዲሆን በማድረግ ቀና ተብብራችሁን አድርጉ ::
👍4
   ቀብር ውስጥ ምን ያህል ጊዜ እንደምታሳልፍ ታውቃለህ? እኔም አላውቅም :: ግን ዱንያ ላይ ከምታሳልፈው እንደሚልቅ እርግጥ ነው :: ቀንህ ደርሶ እንደምትሞተው ቀኑ ደርሶ ስትቀሰቀስ የጌታህን ውሳኔ ብቻ ለመጠበቅ 50000 አመታትን ትቆማለህ :: ከዚያ ቡሃላ ውሳኔው ሲፀና ደግሞ እስከ ዘላለሙ ወይ በጀነት ወይ ደግሞ በጀሃነም ውስጥ ትኖራለህ ::

   የእኔ ጥያቄ "ዛሬ ላይ ቆመህ ነገ ላይ እንደምትኖረው እርግጠኛ ላልሆንክለት የዱንያ ህይዎት ላይ ታች እያልክ ለረዢሙ የአኼራ ህይዎት ስለምን ዘነጋህ?" የሚል ነው:: ካልሆነማ ለዛሬ የምትኖርበትኮ አለህ :: ካልሆነማ ዛሬን እንደምንም ለብሰህ ጠጥተህ ታልፋለህ :: ብቻ ለማለፍ እስከሆነ ድረስ ባትበላ ባትጠጣ እንኳ ታልፈዋለህ :: ግን የዱንያ ልፋትህ እንደምትኖረው እርግጠኛ ላልሆንከው ነገ ነው :: የምትሰበስበው እንደምትበላው እርግጠኛ ያልሆንከውን ምግብ ነው :: የምታግበሰብሰው እንደምትጠቀምበት እርግጠኛ ያልሆንከውን ገንዘብ ነው ::

   እርግጠኛ ለሆንከው የአኼራ ህይዎትስ ? እየሰበሰብከው ያለኸው ነገር አለህ? የሸመትከው ነገር አለህ) የሰራኸው ነገር አለህ ? ለቀብርህ ማለቴ ነው :: ከጌታህ ፊት ስትቆም የምትናገረውን ማለቴ ነው :: ከሌለህ ሞኝ ሆነሃልና በብልጠት አስወግደው :: ብልጥ ማለት ነፍሱን ተቆጣጥሮ ከሞት ቡሃላ ላለው የሰራ ነውና ::

@MohammadamminKassaw
👌9👍6
ወደ ቀጣይ ደረጃ መሸጋገር ከፈለክ አፍህን ሰብሰብ አድርገው !

ወደፊት እንዳትራመድ እያደረገህ ያለው ምላስህ ሊሆን ይችላል !

"በአላህና በመጨረሻው ቀን ያመነ መልካምን ይናገር ወይም ዝም ይበል ::" ተብሎስ የል ?

@aaumsu
👍18