AAU - Muslim Students Union
6.48K subscribers
2.76K photos
151 videos
51 files
767 links
This is the official channel of AAU-MSU.

Group: @aaumsu_discussion
Youtube: youtube.com/@aaumsu
Twitter: x.com/aaumsu12
Facebook: facebook.com/profile.php?id=100087931837303

Contact us: @Aaumuslimstudentsunion1
Email: aaumsu12@gmail.com
Download Telegram
AAU - Muslim Students Union
Photo
ረመዷን2️⃣9️⃣
(ወደ ጽናት)⓶
፨፨፨
<<እንደታዘዝከውም ቀጥ በል፡፡>>[አ'ሹራ፡15]
፨፨፨
ጊዜ ይሄዳል፤ቀናት ተደማምረው ወራት ይተካሉ፤አላህ ድጋሚ ከሚያገኙት ያድርገንና ረመዷንም ተመልሶ ይመጣል፤ታዲያ...የሚመጣው ረመዷን የዘንድሮው የጨመረልንን መልካም ነገር እንደ መሠረት ተጠቅሞ ወደ ሌላ የተሻለ ከፍታ የሚያደርሰን ይሆን ዘንድ ከአሁኑ አቋማችን ሳንመለስ ተዘጋጅተን ልንጠብቀው ይገባል።"አንድ ዓመት ግን ሩቅ አይደለም?"
.
*
ታዲያ!መጭው ጊዜ በጽናት እንዴት ይለፍ?
.
፨፨፨
<<አላህን ከባሮቹ ውስጥ የሚፈሩት ዐዋቂዎቹ ብቻ ናቸው፡፡ አላህ አሸናፊ መሓሪ ነው፡፡>>[ፋጢር:28]
፨፨፨
.
ብዙዎቻችን ስለሶላት አሰጋገድና መሠረታዊ ነገሮች ከቤተሰብ የወረስነው ተለምዷዊ ዕውቀት ይኖረን ይሆናል።ይህ መሠረታዊ ዕውቀት ጥሩ ቢሆንም፣ በአላህ መንገድ ላይ ለመጽናት ግን ዋስትና አይሆንም።አላህን ይበልጥ ስታውቀው ይበልጥ ትጠነቀቀዋለህ።የሱን ኃያልነት ስትረዳ በፍርሀት፣የእዝነቱ ስፋት ሲገባህ ደግሞ በተስፋ እየተገዛኸው ትኖራለህ።የተፈጠርክበትን ዓላማ የምታሳካው በደነገገልህ ሸሪዓ ብቻ ነውና ዲኑን ይበልጥ ማወቅ ለመጽናት ይረዳሀል።
*
አላህ የሚወሳባቸው፣ የሱ ዲን የሚማርባቸው ስብስቦች ላይ ስትዘወትር ያለህ ላይ እየጨመርክ ትሄዳለህ እንጅ መንገድ አትስትም።ያላወቁትን በማወቅ፤ያወቁትን በማስፋት ወደ አላህ ይበልጥ መቅረብ፣የጽናት ሰው መሆን ይቻላል።የወንጀልን አስከፊነት፣የኸይር ስራን ምንዳ በደንብ ስናውቅ ዓመቱን ሙሉ የዒባዳ ዓመት ማድረግ እንችላለን።
*
ከዲን አንፃር ስናየው፣ትላንትና ዛሬያችንን አንድ አድርገን እየኖርን ያለነው ጥቂት አይደለንም።ትላንትም ዛሬም ቁርኣንን ማንበብ አንችልም፤ወይም አነባበባችንን እስከዛሬ አልተስተካከለም።ስለ ዐቂዳችን ብንጠየቅ መልስ የለንም፤ሶላታችንና ጾማችንም ተለምዶ እንጅ በትክክል ከአላህ ሒሳብን በመፈለግ የሚፈፀሙ አይደሉም።
*
ትምህርትን እያጠኑና እየተረዱ፣ቀኑን በክላስ፣ሌሊቱን በንባብ እያሳለፉ  ቁርኣንን ማንበብ አለመቻልንና፣የሶላትን ደንብ በሚገባ አለማወቅን ከምንም አለመቁጠር ከተማረና የተሻለ አረዳድን አዳብሯል ከሚባል ሰው የሚጠበቅ ተግባር አይደለም።እርግጥ ግቢ የተገኘንበት የመጀመሪያ ዓላማ ዓለማዊ ትምህርትን ፍለጋ ነው።ከዚህም ፈጽሞ ልንዘናጋ አይገባም።የቤተሰብ አማና ብሎም የዚህችን ዓለም ስንቅ የምንሰንቅበት ትልቅ መሣሪያ ነውና።
*
ይህ ማለት ግን ሙሉ ነገራችንን እሱ ላይ ማጥፋት አለብን ማለት አይደለም።በሁለቱም ስኬታማ ሆኖ መመረቅ እንደሚቻል በማመን ለሁለቱም መትጋት ይገባል።ለዚህም የሚያግዘው በማይጠቅሙ ነገሮች ላይ የሚባክንን ጊዜ ቀንሶ ሰዓትን በአግባቡ መጠቀም ይሆናል።
*
ከረመዷን በኋላ የዕውቀት ቦታዎች ላይ አለመገኘት ረመዷን ላይ የሸመትነውን መልካም ነገር እንድናጣና ወደቀድሞው ማንነታችን እንድንመለስ የሚያደርግ ሌላኛው ምክንያት ነው።
.
ዲንን በአግባቡ አለመረዳትና በደንብ አለማወቅ ያለው መጥፎ ውጤት በኛ እንደማይገደብ መገንዘብ መቻል አለብን።ኢስላም በኛ በኩል ለቀጣዩ ትውልድ እንደሚተላለፍ መዘንጋት የለብንም።

ወንድሜ ሆይ!ሩቅ ሊመስለህ ቢችልም የቤተሰብ አስተዳዳሪ፣የልጆች አባት መሆንህ የማይቀር ነው።አሁን ያለህበት ሁኔታ ለዛ የሚመጥን ነው?
ለልጆችህ የምታወርሰው ኢስላማዊ ዕውቀትና ስነ-ምግባር ይበልጥ የምታዳብረውስ መቼ ነው?ከአሁኑ  አይደለምን?

እህቴ ሆይ! እየተማርሽ ይሆናል።ሆኖም ግን ትክክለኛ ሚናሽና ክብርሽ ኢስላማዊ ቤተሰብ መገንባት ላይ እንደሆነ አትዘንጊ።ለዛ የሚሆን ስንቅ አለሽ?የምትውይውስ ስንቅሽን የምትሰንቂበት ቦታ ነው ወይስ ልጆችሽን ልታይበት የማትፈልጊበት ቦታ?ከጊዜሽ ቀንሰሽ ለዋናው ዓላማሽ መዘጋጀትስ የለብሽም?
.
‼️ጊዜው ከምንም ጊዜውም በላይ ዲንን ለመማር የሚጠቅሙ ዕድሎች የተመቻቹበት ጊዜ ነው።ስልክ፣ኢንተርኔትና ሌሎቹን ለዚህ ብንጠቀማቸው ከጽናት ባለቤቶች የመሆን ዕድላችን ሰፊ ነውና ጸጋዎችን በመጠቀም ላይ አደራ!
፨፨፨
«ጌታዬ ሆይ! ዕውቀትንም ጨምርልኝ» በል፡፡[ጧሀ:114]
፨፨፨
🌱አላህ ሆይ!ረመዷንን በኛ ላይ መላልስልን!...አሚን!

⭕️የዕለቱ ቻሌንጅ⭕️
.
1️⃣በዕውቀት ወደ ጽናት ለመጓዝ መወሰን
.
2️⃣ የአንድ ዓመት የዒልም ዕቅድ ማውጣት፤የሚመጣውን ክረምትም በደንብ ለመጠቀም በመወሰን ከአሁኑ ዕቅድ ማውጣት፣
.
3️⃣ የጀመዓ ደርሶችና፣ፕሮግራሞች ላይ ለመገኘት መወሰን

🍀Principle of The Year🍀
A year of "firmness through Seeking Knowledge!"

🌱 አሏሁ'መ ኢነከ ዐፉውን ቱሒቡል ዐፍዎ ፈዕፉ ዐና!

#AAiTJemeaRamadanReminders2
@aaumsu
👍1
80-81ኛ - 300 ብር - SSC and FBE

እህቶቻችንን አላህ ይቀበላቸው :: ይውዳቸው :: የሚወዱትን የሚያስደስታቸውንና እሱ አላህ የሚወደውን ነገር ሁሉ ይስጣቸው :: የአኼራ ቤታቸውን በጀነተል-ፊርደውስ ይገንባ ::
👍2🔥2
82ኛ-100 ብር - ከ4ኪሎ

አላህ ይቀበላቸው :: ኸይር ጀዛቸውን ይክፈል :: ዱንያቸውን ያሳምር :: አኼራቸውን ይሙላ ::

ተነቃቁ !
ተነቃነቁ !

እስከ ማታ 50K እንሙላ !!
እንረባረብ !!!
👍6👌21
ለሐዋሳ ሪፈራል ካምፓስ ሙስሊም ተማሪዎች መስጂድ ግንባታ 45500 ብር ደርሰናል !

መስጂድን የገነባ አላህ በጀነት ቤት ይገነባለታል :: መስጂዱ እንዲሰራ ሰበብ ሆንን ማለት የነገ ተስፋ የሆኑ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ዲናቸውን በነፃነት የሚማሩበት ማዕከል አገኙ ማለት ነው ::

ተልዕኳችን ትልቅ ነውና እንረባረብ :: ከAAUMSU በትንሹ 50ሺ እንሰብስብ :: ለዚያ ደግሞ 4500 ብር ብቻ ይቀረናል :: 1 ሰው መሸፈን ይችላል :: 45 ሰውም 100 ብር ቢሰጥ ይሞላዋል ::

ኸይር ነውና እንረባረብ :: ወደ አኼራ ቀድሞን የሚሄድ ሀብት ነውና እንሽቀዳደም ::

የማስገቢያ አካውንት :- 1000485306432
AAU Muslim students union :: ማስገባታችሁን screenshot በማድረግ @MOHAMMADAMMINM ላኩልኝ ::

Let us do it my beloved ones !
👍84
83-86ኛ - 450 ብር !

ከንግድ ኮሌጅ 150 ብር : ከመሐንዲሶች ሰፈር 100 ብር : ከሰላሙ ሰፈር (ዶክተሮች) 100 ብር እንዲሁም ከቤተ-መንግስት አቅራቢያ (100 ብር) ለሐዋሳ ወንድሞቻችን መስጂድ ግንባታ አስገብተዋል ::

አላህ ይቀበላቸው :: ህይዎታቸውን ብርሃን በብርሃን ያድርግ :: ችግራቸውን ያስወግድ :: ድሎታቸውን ያብዛ :: ጥሩ ትዳርና መልካም ልጆችን ይስጣቸው :: ሰፊ ሐብትና ሙሉ ጠና ይወፍቃቸው :: ረጂም እድሜና ኢማን ይለግሳቸው :: የእርሱን ቤት ለመገንብት እንደተረባረቡት ቤታቸውን በጀነተል-ፊርደውስ ይገንባ ::

ልደታ : ጥቁር አንበሳ : main campus and... አለን በሉሉሉሉሉ !!!!
👏6👍3
87ኛ - 300 ብር - ከCommerce

ንግድ ኮሌጆች አሁንም ከፊት ናቸው:: ለሐዋሳ ወንድሞቻቸው መስጂድ እየተረባረቡ ነው :: አላህ ይቀበላቸው :: ኸይራትን አከታትሎ ይወፍቃቸው :: በሚወዱት በሚያስደስትና በሚወደው ነገር ይሸልማቸው :: ቤታቸውን በጀነት ይገንባ ::

መሐንዲሶች አለን በሉሉ!
ህንፃ ኮሌጆች አለንን በሉሉ !
ዶክተሮች አለን በሉሉሉ !!
Social ኢንጂነሪንግ ውስጥ ያላችሁም ተረባረቡ !!!
👍7
Challenge 50K - up to megrib!

Let us challenge ourselves to challenge 50K for our brothers mesjid (Hawassa referral campus Muslim students Mesjid) !
We are at 46250 !!
Left with 3750 !!!

Let us do it my beloved brothers and sisters in Islam !
Let us show our unity and strength with in fulfilling our responsibility!

The account is 1000485306432
AAU Muslim students union
. Send me the screenshot of your slip via @Mohammadamminm .
👌5😡1
ቻሌንጅ 50K በ100 ብር ተጀምሯል!

አላህ ሁልጊዜም ቢሆን ለኸይር ነገር ተሽቀዳዳሚና ቀዳሚ ያድርገው :: በዱንያም በአኼራም የሚያስደስት ነገር ይወፍቀው ::

Challenge 50K !
left with 3650 !
Challenge your account to challenge 50K!
👍4
1100 ብር - አላሁ አክበርርርር !

አላህ ይቀበላቸው :: ኸይር ጀዛቸውን ይክፈል :: የዱንያ ቤታቸውን ያሳምር :: የአኼራ ቤታቸውን በጀነተል-ፊርደውስ ውስጥ ይገንባ ::

ለ50ሺ 2550 ብር ብቻ ይቀረናል!

"እሳትን በተምር ክፋይ እንኳ ቢሆን ተጠንቀቋት!" ብለዋልና አነሰ በዛ ሳትሉ ስጡ ::
👏8👍5🔥1
100 ብር - ከሰፈረሰላም !

አላህ ይቀበላቸው :: ኸይር ጀዛቸውን ይክፈል :: ረጂም እድሜ ከሰፊ ሲሳይ እውቀትና ኢማን ጋር ይወፍቃቸው :: የአኼራ ቤታቸውን በጀነተል-ፊርደውስ ይገንባ ::

50ሺ ልንሞላ 2450 ይቀረናል!
let us do it ya-ahababi !!
👍41
91ኛ - 250 ብር !

አላህ ይቀበላቸው :: ያስደስታቸው :: ይውደዳቸው :: ያስወድዳቸው :: ሰፊ ሀብት ከረጂም እድሜ ሙሉ ጤናና ኢማን ጋር ይስጣቸው :: የአኼራ ቤታቸውንም በጀነተል-ፊርደውስ ይገንባ ::

ለ50ሺ 2200 ይቀረናል!!
እንሙላው !!
👏4👍1
92ኛ - 100 ብር - ከሰፈረሰላም

አላህ ይቀበላቸው :: የሚወደድ ነገርን በዱንያም በአኼራም ይስጣቸው ::

ለ50ሺ 2100 ብር ይቀረናል!
ተሳተፉ!!
እንሙላው !!!
👍1👏1
ኢድ አል-ፊጥር ረቡዕ እንደሆነ ተረጋግጧል!

   እንኳን አደረሰን !

@aaumsu
👌18👍74
በመስጂደል ሀረም ዛሬ ምሽት የሚሰደገደውን የ1445 ረመዳን የመጨረሻ ተራዊህ ሰላት ተወዳጁ ሸይኽ ያሲር አድ-ደውሰሪ እና ሸይኽ ጁሃኒ እንደሚመሩት ታውቋል። ፕሮግራሙን ከታች ያለውን ሊንክ በመጠቀም በቀጥታ መከታተል ትችላላችሁ።
👇👇👇
https://www.youtube.com/live/moQtMet7F7w?si=tGzhUtTt_3eDzNt6

@aaumsu
@aaumsu
🔥5🥰2👍1
93ኛ - 100 ብር

"እናቴን አላህ እንዲያስደስታት ዱዓ አድርጉልኝ!" ብላለች :: የእናት ደስታ የልጅ ስኬት ነውና ስኬትሽን አብዝቶ ደስታዋን ያብዛ:: ችግርሽን አስወግዶ ደስታዋን ያብዛ :: ዱንያችሁን ያሳምር :: በአኼራ እስከ ዘላለሙ በጀነተል-ፊርደውስ ይሰብስባችሁ ::
👍2