ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ
30.6K subscribers
122 photos
3 videos
61 files
4 links
Philosophy For Higher Consciousness
Download Telegram
2.መጽሐፍ ቅዱስ ከህዋ አንፃር የሰው ልጅ ምንድን ነው? በማለት ይጠይቃል?

“የጣቶችህን ሥራ ሰማዮችን ባየሁ ጊዜ፣
ጨረቃንና ከዋክብትን አንተ የሠራሃቸውን፣
ታስበው ዘንድ ሰው ምንድን ነው?
ትጐበኘውም ዘንድ የሰው ልጅ ምንድን ነው?”

በማለት መዝሙረኛው ንጉስ ዳዊት ይጠይቃል፡፡
መዝሙረኛው ያነሳው ጥያቄ የዚህ ምዕራፍ ርዕስ ጉዳይ ነው፡፡ ሰው ተፈጥሯዊ የሆነ የአጋጣሚ ክስተት ውጤት ነው ወይስ ታላቅ አላማ ለማሳካት የተፈጠረ ልዩ ፍጥረት? ሰው በተፈጥሮ ሂደት በአጋጣሚ የተገኘ ቢሆንና የፍጥረታት ሁሉ የበላይና የመጨረሻ ግብ ሁኖ ሊወሰድ ይችላልን? ከፀሐይና ከጨረቃ-ከህዋ-አንፃር ሲታይስ እዚህ ግባ የማይባል ተፈጥሯዊ ማንነት ያለው ከብናኝ አፈር፣ በእግራችን ረግጠን እንደምንገድላቸው ትናንሽ ነፍሳት አይነት የሆነ ተራ ፍጥረት ነውን ወይስ በህዋ ውስጥ ያሉትን ነገሮች እንደፍላጐቱ ማድረግ የሚችል ኃያል ፍጥረት? ህዋ ለሰው ጥቅምና መልካም ግልጋሎት ተብሎ የተፈጠረ ነገር ነውን ወይስ መጥፋያው? መጽሐፍ ቅዱስ ለእነዚህ አይነት ጥያቄዎች የሚሰጠው መልስ ሁለት አይነት ነው፡፡ በአንድ በኩል የሰውን ኃያልነት ሲያጐላ በሌላ በኩል ተራ ፍጥረት መሆኑን ይነግረናል፡፡ መለኮታዊ ማንነት ያለውና በፍጥረታት ሁሉ ላይ ገዥነቱን የሚነግረን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል እንዳለ ሁሉ በሌሎች ክፍሎች ደግሞ ሰውን አዋርዶና አቅልሎ ይነግረናል፡፡ የሰውን ልዩ ማንነትና ገዥነቱን መዝሙረኛው ዳዊት እንዲህ በማለት ይገልፀዋል፡፡

“ከመላዕክት እጅግ ጥቂት አሳነስኸው፣
በክብርና በምስጋና ዘውድ ከለልኸው፣
በእጆችህም ሥራ ሁሉ ላይ ሾምኸው፣
ሁሉን ከእግሮቹ በታች አስገዛህለት፣.."

ከጥቅሱ መረዳት እንደሚቻለው ሰው ከመላዕክት አንሶ የማያንስ በፍጥረታት ሁሉ ላይ ተሹሞ ዘውድ የደፋ ታላቅ ፍጥረት ነው፡፡ የሰው ታላቅነት ከአፈጣጠሩ ልዩ መሆን ይጀምራል፤ በእግዚአብሔር መልክ (በልጁ መልክ) የተፈጠረና የመለኮት ባህሪ ተካፋይ የሆነ ነው፡፡ በተቃራኒው ደግሞ መጽሐፍ ቅዱስ ለሰው ልጅ ሌላ ማንነት ይሰጠዋል፡፡ ከሌሎች ፍጥረታት የማይለይ ይባስ ብሎ ከሌሎች ፍጥረታት አሣንሶ ሰውን ይገልፀዋል፡፡ መጽሐፈ መክብብ እንዲህ ይላል፡፡

“እኔ በልቤ ስለሰው ልጆች እንደ እንስሳ መሆናቸውን እንዲያዩ እግዚአብሔር ይፈትናቸዋል አልሁ፡፡ የሰው ልጆችና የእንስሳ እድል ፈንታ አንድ ነው፣ ድርሻቸውም ትክክል ነው፡፡ አንዱ እንደሚሞት ሌላውም እንዲሁ ይሞታል፣ የሁለም እስትንፋስ አንድ ነው፣ ሁሉም ከንቱ ነውና ሰው ከእንስሳ ብልጫ የለውም፡፡”

መጽሐፈ ኢዮብ ደግሞ የሰውን ማንነት ከዚህ በባሰ መልኩ ይገልፀዋል፡፡

“እነሆ፣ ጨረቃ እንኳ ብሩህ አይደሉም፣
ክዋክብትም በፊቱ ንጹሀን አይደሉም፣
ይልቁንስ ብስብስ የሆነ ሰው
ትልም የሆነ የሰው ልጅ ምንኛ ያንስ፡፡”

ፍልስፍናስ ምን ይላል? ፍልስፍና ትኩረት ከሚሰጥባቸው ጉዳዮች አንዱና ዋናው የሰውና የህዋ ጉዳይ ነው፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ፍልስፍና ሰፋፊ፣ ጥልቀትና ብዛት ያላቸው አስተሳሰቦችን አቅርቧል። በቀጣይ እናያለን....

@zephilosophy
👍40🤔74👏1
ሰው ከህዋ አንፃር ያለው ቦታ እና ግንዛቤ በጥንታዊ እና በመካከላኛ ዘመን የነበሩ ፈላስፋዎች እይታ

ራሳቸውን ጥበበኞች እያሉ የሚጠሩ አንደበተኛና ጠርጣሪ (Sophist) ፈላስፋዎች እስከመጡበት ጊዜ የነበሩ ከቴለስ ጀምሮ የነበሩ ፈላስፋዎች ሰውን የተፈጥሮ አካል አድርገው ነው የተመለከቱት፤ ለሰው የተለዬ ማንነት አልሰጡትም፡፡ እንዲያውም ሰው የተፈጥሮ ህግ ተገዥና የበታች እንደሆነ ገልፀዋል፡፡

የዚህ አይነት አመለካከት በግሪክ ፈላስፋዎች ዘንድ የዘለቀው ራሳቸውን ጥበበኞች እያሉ የሚጠሩ አንደበታዊያን (Sophist) ፈላስፋዎች እስከመጡበት ጊዜ ድረስ ብቻ ነው፡፡ ከበፊተኞቹ ፈላስፋዎች በተቃራኒው አንደበታዊያን ፈላስፋዎች ሰው የተለዬ ማንነት ያለው መሆኑን በፍልስፍናቸው አበሠሩ፡፡ አንደበታዊያን ሰውን ከተፈጥሮ በመለየት የራሱን እጣፈንታ በራሱ መወሰን የሚችል ፍጥረት እንደሆነ ያምናሉ፡፡ ሰው ምን ያህል የተፈጥሮን ሥርዓት ሊያወቅና ሊቆጣጠር እንደሚችል ባይረዱትም ሰው ለራሱ ጥቅም ማስገኘት እስኪችል ድረስ ተፈጥሮን መቅረጽ ወይም መለወጥ እንደሚችል ያምናሉ፡፡

ፕሮታጐራስ የተባለው ታዋቂው አንደበታዊ ፈላስፋ “ለሁሉም ነገር ወሳኙ (ዳኛው) ሰው ነው- Man is the measure of everything” የሚል አባባል አለው፡፡ ይህ አባባል ሁለት ትርጉሞች አሉት፡፡ የመጀመሪያው እውነት ወይም ሀሰት፣ ጥሩ ወይም መጥፎ  የምንላቸው ነገሮች እንደ ሰው እይታ ነው ማለት ነው፡፡ ሌላው ትርጉሙ በሁሉም ነገር ላይ መወሰን የሚችለው ሰው ነው፤ ከሰው በላይ የሆነ ምንም ነገር የለም ማለት ነው፡፡ ከሁሉም በላይ ማለት ከተፈጥሮም እንዲሁም ከአማልክትም በላይ ማለት ነው፡፡ በዚህ መልኩ በፍልስፍና ታሪክ ውስጥ ሰው የፍጥረታት ሁሉ ማዕከልና የበላይ የሆነ ክብር ለመጀመሪያ ጊዜ ያገኘው በአንደበታዊያን ፈላስፋዎች ነው፡፡

ከአንደበታዊያን በኋላ የመጡ እንደ ፕሌቶና አሪስቶትል ያሉ ፈላስፋዎች ከቁስ አካላትና ከህያዊያን ፍጥረታት ሁሉ በላይ የሚያደርገው በሰው ውስጥ የተለዬ ነገር አለ ብለው ያምናሉ፡፡ ሰው ተፈጥሮን ብቻ አይደለም ፍጹም የሆኑ ሃሳባዊያን ነገሮችን ጨምሮ መረዳት ይችላል፡፡ ይህ በሰው ዘንድ ያለ የተለዬ ነገር ነው፤ በዚህ የተለዬ ማንነት ሰው ከተፈጥሮ በላይ መሆን ብቻ ሣይሆን ከመለኰት ጋር ተመሣሣይ ያደርገዋል፡፡ ስለዚህ ሰው በግዙፉ ህሊና ቢስ ህዋ ውስጥ የሚሆነው ነገር ጠፍቶት የሚንገዋለል ፍጥረት ሣይሆን የተፈጥሮን ሥርዓት አሸንፎ ወደ መለኮት ራሱን ከፍ ከፍ የሚያደርግ ፍጥረት መሆኑን ፕሌቶና አሪስቶትል ያምናሉ፡፡

ከፕሌቶና አሪስቶትል በኋላ የመጡ ስቶይክ (Stoic) ፈላስፋዎች ደግሞ የተለዬ አመለካከት ነው ያላቸው፡፡ ለስቶይኮች ሰው የግዙፉ ህዋ ቅጅ ነው፡፡ በሰው ውስጥ ያለው በህዋ ውስጥ አስቀድሞ ያለው ነው፡፡ ሰው በህሊናው እንደሚመራው ሁሉ ተፈጥሮ በአጠቃላይ የሚመራው በስቶይኮች ቃል (logos) ብለው በሚጠሩት ህዋዊ ህሊና ነው፡፡ ሰው የሚኖረው ተፈጥሮ በሰጠችው ልክ በመሆኑ ተፈጥሮ እንዳደረገችው ሁኖ መኖር አለበት፡፡

ተፈጥሮ በህሊናዊ ኃይል ስለምትመራ ተፈጥሮን መቃወም ስህተት ነው፡፡ ይህ አመለካከት ሰውን ከተፈጥሮ በታች የሚያደርግ ብቻ ሣይሆን የሰው ህይወት አስቀድሞ የተወሰነና መቀየር የማይቻል መሆኑን ይሣየናል፡፡

የመካከለኛው ዘመን የነበሩ ክርስቲያን ፈላስፋዎች በመካከላቸው ልዩነት ይኑር እንጅ ዙሮ ዙሮ እግዚአብሔርን የህዋ ፈጣሪ መሆንና ሰውም የእግዚአብሔር ምርጡ የሥራ ውጤት መሆኑን ይስማሙበታል፡፡ ነገር ግን አካላዊ (ቁሳዊ) ማንነቱ ለሰው ጥቅም አልሰጠውም፤ ምኞትን፣ ሀጢዓትንና ሞትን አመጣበት፡፡ ሁለን ነገር በበላይነት ገዝቶ እንዲኖርበት የተሰጠው ዓለምም መከበሪያው ሣይሆን መቀበሪያው ሆነ፡፡ በመሆኑም አካላዊ (ቁሳዊ) ማንነቱና ምድራዊ ኑሮው አስፈላጊ አይደለም፤

ከሞት ነፃ ሁኖ የሚኖርበት ሌላ ማንነትና ሌላ ዓለም ያስፈልገዋል፡፡ ይህን ዓለም ሰው ንቆ መኖር አለበት፤ ይህ ዓለም ክብርና ዋጋ የሚሰጠው አይደለም፡፡ ጥቅም አለው ከተባለም ወደ ሌላኛው ዓለም ለመድረስ ለመሸጋገሪያነት ማገልገሉ ነው፡ ስለዚህ ሰው መሻት ያለበት እየኖረበት ያለውን ዓለም ሣይሆን ሌላኛውን (ከላይ) ያለውን ዓለም ነው፡፡

ዓለም ንቆ መኖር ካለበት በህዋ ላይ ሊጫወተው የሚችለው ሚናም ሆነ በህዋ የራሱን ቦታ ምን ሊሆን እንደሚችል ማወቅ አያስፈልገውም፡፡ ይህ አመለካከት ሰውንና ህዋን፣ ህሊና እና ቁስን መንፈስንና አካልን የሚለያይ ነው፡፡ ሰውን ከሚኖርበት ዓለም የሚለያይ አመለካከት ደግሞ ሰው በዚህ ዓለም ሊያደርግ የሚችለው ነገር ቢኖር እንኳ ጥቅም (ዋጋ) እንደሌለው ያመለክታል፡፡ ሰው ዓለምን ለመግዛት ቢፈጠርም የራሱን አካል እንኳ መግዛት ስለተሳነው በዚህ ዓለም ሊያገኝ የሚችለው ዘላለማዊ ክብርን አጥቶታል፡፡ ስለዚህ ሰው ማሰብ ያለበት ከሞት በኋላ ስለሚኖረው ህይወት እንጅ ከሞት በፊት ስላለው ሊሆን አይገባም፡፡

ዋናው ነገር ይህ ዓለም ለሰው መልካም እንዳይደለ መታመኑ ነው፡፡ ይህ ዓለም መጥፎና የሥቃይ ሁሉ ምክንያት ነው፡፡ የሐጢዓት ምክንያት በመሆኑ ይህ ዓለም ለሰው ልጅ ጠላቱ ነው፡፡ የላይኛው መንፈሳዊ ዓለም ግን የጽድቅና የዘላለም በረከት የሚገኝበት ነው፡፡ የመልካም ነገሮች ሁሉ መኖሪያ ቤትና የመለኮት ማረፊያ በመሆኑ የሰው ልጅ አላማ ሊሆን የሚገባው ቁሳዊ (ምድራዊ) ዓለምን መተውና መንፈሳዊ የሆነውን ዓለም ማግኘት ነው።

ዘመናዊ ፍልስፍና ስለ ህዋ ምን ይላል??

ረ/ፕርፌሰር ዋለልኝ እምሩ

@zephilosophy
@zephilosophy
👍492🔥1
5.የህዋ ግንዛቤ በዘመናዊ ፍልስፍና ታሪክ ውስጥ

የህዳሴውን ዘመንን ተከትሎ በሣይንሱም ሆነ በፍልስፍናው ብዙ አይነት አስተሳሰቦችና ትምህርቶች ይራመዱ ጀመር፡፡

ፍልስፍና “የሰውን ህይወት እጣፈንታ የሚወስን ኃይል አለ” ከሚል እምነት በመላቀቅ ሰው የራሱን ህይወት በራሱ ፈቃድና እውቀት መምራት ይችላል ወደሚል እምነት ተሸጋገረ፡፡

በመካከለኛው ዘመን ሰው ተስፋውን በአምላክ ጥሎ የራሱን ማንነት ረስቶ ነበር፡፡ በዚያ ዘመን ሰው ስለራሱ ማንነት ያንቀላፋበት ጊዜ ነበር፡፡ ከህዳሴው ዘመን ጀምሮ ግን ሰው ለረጅም ዘመን ከአንቀላፋበት ነቃ - ራሱን ማስተዋል ጀመረ፡፡ ወደራሱ በተመለከተ ቁጥር በሌላ ኃይል ከመተማመን ይልቅ የራሱ ኃይል ከምንም ነገር በላይ ሊያደርገው እንደሚችል አሰበ፡፡ በሳይንሳዊ እውቀት ምስጢሩን የተረዳውን ተፈጥሯዊ ሥርዓት በራሱ አቅም መግዛትና ለራሱ ጥቅም ማዋል እንደሚችል ድፍሩቱን ማሳየት ጀመረ፡፡

ይህ የህዳሴው ዘመን መንፈስ ነበር - በራሱ የመተማመን መንፈስ! የህዳሴው ዘመን ፍልስፍና የዘመናዊ ፍልስፍና መግቢያ በር ነው፡፡ ሙሉ ትኩረት የሰጠውም የሰው ልጅ ተፈጥሮን የመለወጥ አቅም ላይ ነበር፡፡ በዚህ ምክንያት የህዳሴው ዘመን ፍልስፍና ሰባዊነት - Humanism የሚል መጠሪያ አገኘ፡፡ እንደ ሉዶቪቾ ቫይቪስ (Ludovico Vives) ፣ ፔትሪስ ራመስ (Petrus Ramus) እና በርናርዲኖ ቴሎሶ (Bernardino Telesio) የመሳሰሉት ሰባዊ አስተሳሰብን በቀደምትነት ያራመዱ ፈላስፋዎች ናቸው፡፡ እነዚህ ፈላስፋዎች የሰው ልጅ አጋዥ ሣያስፈልገው በራሱ አቅም የተፈጥሮን ኃይል ቀልብሶ ራሱን የበላይ አድርጐ መኖር ይችላል የሚል ከፍተኛ እምነት ነበራቸው፡፡ በዚህ አቋማቸው ሰውን አቅመ - ቢስ ያደረጉ እምነቶች ላይ አመጽ የጀመሩ ፈላስፋዎች ለመሆን ቻሉ፡፡ ሳይንስ ያመጣውን መነቃቃት ተከትሎ ሰባዊያን ያመጡት ፍልስፍና ለጨለማው ዘመን ማብቂያና የብርሃን ዘመን መምጣት የተበሠረበት ፍልስፍና ለመሆን ቻለ፡፡

ሳይንስ በፈጠረላቸው መደላድል ላይ ተመሥርተው ፍራንሲስ ቤከንና ቶማስ ሆብስ የተባሉ ፈላስፋዎች ሰው ከህዋ ጋር ያለውን ግንኙነት በእውቀት ላይ የተመሠረተ ሊሆን እንደሚገባው በማስገንዘብ የተፈጥሮን እንቅስቃሴና አጠቃላይ ሥርዐተ - ህጉን ማወቅ የሰው ልጅ ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡በተለይ ለሆብስ የተፈጥሮ ህግ መታወቅ ከተቻለ ሰው ህጉን እንደፈቃዱ እያስተካከለ መኖር እንደሚችል እምነቱን ገለፀ፡፡

እነ ቶማስ ሆብስ ሁሉን ነገር ቁሳዊ አደረጉት፡፡ ህሊና-ሀሳብ - በእንቅስቃሴ ላይ ያለ ቁስ ነው፤ እግዚአብሔርም ቢሆን ቁስአካላዊ ነው፤ መንፈሳዊ የሚባል ነገር የለም የሚል እምነት ማራመድ ጀመሩ፡፡

በእንደዚህ አይነት አመለካከቶች ተጋግሎ የነበረው የሰባዊነት ፍልስፍና ሳይታሰብ መቀዝቀዝ ጀመረ፡፡

ለምን ??? ይቀጥላል..

@zephilosophy
👍274🎄1
የዘመናዊ ፍልስፍና ሙግቶች

የቀጠለ
....የዳሳሽነት (empiricism) ፍልስፍናን ያራመዱ የብሪታንያ ፈላስፋዎች ሰውን የሁሉ ነገር ማዕከል አድርገው የተረዱ ቢሆንም ከሰው አሳቤ ውጭ ህዋ የራሱ የሆነ ህልውና የለውም በማለት ህዋንና ሰውን ያስተሳሰረውን ገመድ ቆርጠው ጣሉት፡፡ በርክሌይ የተባለው ፈላስፋ ቁሳዊ ነገሮች ከሰው ህሳቤ ውጭ ህልውና የላቸውም ማለቱና የስሜት ህዋሳቶች መረጃዎች መገኛቸው ቁሳዊ ነገሮች ሣይሆኑ እግዚአብሔር ነው ማለቱ የሳይንስን መሠረት የሆነውንና ሰው ማንነቱ ሊገለጽበት የሚችለው ቁስ አካል ከንቱ (ዋጋ የሌለው) ነገር ሁኖ እነዲታሰብ አደረገው፡፡ ይባስ ብሎ ዴቭድ ሂዩም የሰው ልጅ የስሜቶችና የሀሳቦች መንሸራሸሪያ መንገድ ከመሆን ውጭ ሌላ ማንነት የለውም፤ የህዋን (የቁስ አካላት) ህልውናንም ማረጋገጥ አይቻልም በማለቱ በፍልስፍና ተሟሙቆ የነበረው የሰውን ኃያልነት የማሳየት አስተሳሰብ ላይ ቀዝቃዛ ውሃ ቸለሰበት፡፡

ሌሎች ደግሞ የህዋን ህልውና ሙሉ በሙሉ ሀሳባዊ አደረጉት፡፡  እንጀ ሜልብራንች ያሉ ፈላስፋዎች (Malebranche) እኛ የምናውቀው እግዚአብሔር የገለፀልንን ነው፤ እርሱ ከሰጠን ሃሳብ ውጭ ምንም የምናውቀው ነገር የለም የሚል እምነት ያዙ፡፡  ሜልብራንች ሲናገር “እግዚአብሔር ዓለምን ቢያጠፋና አሁን እንዲሰማኝ እንዳዳረገኝ ወደፊትም እንዲሰማኝ ቢያደረገኝ ወደፊት የማየው አሁን የማየውን ነው፡፡” በሌላ አገላለጽ ይህ ማለት “እግዚአብሔር ዓለምን ቢያጠፋ ነገር ግን ልክ አሁን እንደሚሰማኝ (እንዳልጠፋች አድርጐ እንዳስብ ቢያደርገኝ) የማስበው ወይም የምረዳው መጥፋቷን ሣይሆን መኖሯን ነው፡፡የሚል ራሱን ሙሉ በሙሉ  የእግዚአብሔር ሀሳብ ብቻ እንደሆነ አድርጐ እንዲያስብ የሚያስችል አመለካከት ያራምድ ነበር።

በዘመናዊ ፍልስፍና የታዩ አንዳንድ ፈላስፋዎች ደግሞ ከጊዜው ነባራዊ ሁኔታ ውጭ ሆነውና የሣይንስን መንገድ ስተው የሰውን ልጅ ወደ ጥንታዊ ኑሮው ለመመለስ የሚከጅል ሀሳብ ማራመድ ጀመሩ፡፡ ለዚህ ጥሩ ማሳያ የሚሆነው የዣን -ዣክ ሩሶ (Rousseau) ፍልስፍና ነው፡፡ ሩሶ እንደሚለው ሣይንስ የተፈጥሮ ህግ እውቀት ነው፤ ሳይንስ የሰውን ልጅ ኑሮ ይምራ ማለት ሰው በህግ ይመራ ማለት ነው፡፡ ሳይንስ ሰውን በህግ አስሮ መያዝ ይፈልጋል፡፡ ሰው ግን እንደፈቃዱና ስሜቱ መኖር የሚሻ ፍጥረት ነው፡፡ ሳይንስና ሳይንስ ያመጣቸው ስልጣኔዎች ግን የሰውን ልጅ ነፃነት የሚጋፉ በመሆናቸው አያስፈልጉም የሚል እምነት ማራመድ ጀመረ፡፡

ከላይ የተመለከትናቸውን ፍልስፍናዎች አጠቃለን ስናያቸው ዘመናዊ ፍልስፍና መስመር ይዞ መራመድና ወጥ የሆነ አቋም መያዝ እንደተሳነው መረዳት እንችላለን፡፡ በአንድ በኩል የሰውን ልጅ የበላይ አድርጐ ሲመለከት በሌላ በኩል ደግሞ እግዚአብሔርን በሰው ዘር ህሊና ላይ ይሾማል፤ አንዳንዴ ደግሞ ሰው ስለራሱም ሆነ ስለሚኖርበት ዓለም እንዲጠራጠር ሲያደርግ በሌላ በኩል ደግሞ ሰውን የራሱ የሥራ ውጤት ከሆነው ሥልጣኔ አርቆ ተፈጥሯዊ ኑሮ ብቻ መኖር ወደ ሚችልበት ወደ ተፈጥሮአዊነት ኑሮ መመለስ ይሻለዋል የሚል ሙግት ውስጥ ገባ፡፡

ኢማኑየል ካንት እንደብሪታንያ ፈላስፋዎች ሁሉ ሰው የሚረዳው የራሱን ሃሳብ ነው የሚል እምነት ቢኖረውም በምክንያታዊ አስተሳሰብ ሰው ከራሱ ውጭ የሆነ ቁሳዊ ዓለም መኖሩን፣ የእግዚአብሔርን ህልውናም ሆነ ዘላለማዊነት እና ነፃነት አለ ብሎ እንዲያምን አስችሎታል በማለት አሣወቀ፡፡ እነዚህ እምነቶች ደግሞ ተግባራዊ የሆነ ሥነ ምግባራዊ ኑሮና ሌላም አይነት ማኀበራዊ ህይወት እንዲኖርና ራሱንም ከተፈጥሮ በላይ አድርጐ እንዲያስብ አስችሎታል የሚል መደምደሚያ ሃሳብ ላይ ደረሰ፡፡ ይህን የመሰለው የካንት አስተሳሰብ በተወሰነ ደረጃም ቢሆን የሰውን በህዋ ላይ ያለውን የበላይነትና ክብር የመመለስ አስተሳሰብ ሁኖ ተወሰደ፡፡

በካንት መጫሚያ እግራቸውን ያስገቡ ሌሎች የጀርመን ፈላስፋዎች የሰውን ልጅ በህዋ ውስጥ ያለው መንፈሳዊና ህሊናዊ ኃይል ወራሽ በማድረግ ከቁስ አካላትና ከሌሎችም ፍጥረታት ሁሉ በላይ የሆነ ማንነት ያለው መሆኑን የሚያመለክት ጥልቅና ረቂቅ የሆነ ሀሳባዊ ፍልስፍና አቀረቡ፡፡ ካንትን ተከትለው የመጡ እንደ ሩዶልፍ ኸርማን ሎዝ፣ ሼልንግና ሄግል አይነት ፈላስፋዎች ህዋና ሰውን በአንድ አይናቸው የተመለከቱ ፈላስፋዎች ናቸው፡፡ ህዋ ለእነዚህ ፈላስፋዎች ህያው ነው፤ ህሊናዊ ነው፤ ሁልጊዜ ከፍ ወዳለ ደረጃ ለመሸጋገር የሚንቀሳቀስ ነገር ነው፡፡ በዚህ ህሊናዊ የለውጥ ሂደት ህዋ የራሱን የመጨረሻ የዕድገት ደረጃ የደረሰው በሰው ነው፡፡ ህዋ ሙሉ የሚሆነውና ራሱን የሚያውቀው በሰው ነው፡፡ ለእነዚህ ፈላስፋዎች ሰው ማለት ትንሽ ህዋ ነው፡፡


ከብዙ ፍልስፍና ሀሳቦች በጥቂቱ ስንቃኘው የህዋና የሰው ግንኙነት በፈላስፋዎች ዘንድ ይኼን የመሰለ አስተሳሰብ ፈጥሯል፡፡ በእኛም ላይ የሚፈጥረው ተጽዕኖ ቀላል አይሆንም፡፡ በህዋ ውስጥ ሰው ያለው ቦታ ለመወሰንና በሰውና በህዋ መካከል ያለውን ግንኙነት በተመለከተ ከውዝግብ የፀዳና የማያሻማ መልስ  ማግኘት ባንችልም ርዕሰ ጉዳዩን ከተለያዩ አቅጣጫዎች ሰፋ አድርገን እንድንመለከተው የሚያስችል ሃሳቦችን አግኝተናል ።

ረ/ፕርፌሰር ዋለልኝ እምሩ

@zephilosophy
@zephilosophy
👍38👏106
ብቸኛው ባለቅኔ
ካህሊል ጂብራን

ለጋስነት በልቤ ውስጥ ተዘርታለች። ክምር ስንዴ አመረትኩ ፤ ለተራቡም አካፈልኩ። ነብሴ ለወይን ፍሬ ትሰጣለች፡፡ ወይኑን ጨምቄ ለተጠሙ አጠጣሁ። ፋኖሴን ዘይት ሞልቼ መስኮቴ ጋር አኖርኩኝ። በጭለማ ለሚጓዙ እንግዶች መንገዱን አበራሁ፡፡ ይህንን ሁሉ የማደርገው በእነዚህ ድርጊቶቼ ውስጥ ስለምኖር ነው። የሕይወት እጣ ለጋስ እጆቼን ብታስርበኝ ሞትን እመርጣለሁ። ገጣሚ ነኝና መለገስ ካልቻልኩ ፈፅሞ አልቀበልም። የሰው ልጅ ቁጣ እንደ አውሎ ነፋስ ያጓራል። እኔ ግን በዝምታ እተነፍሳለሁ፡፡ ምክንያቱም ትንፋሼ ፈጣሪ ጋር ሲደርስ ወጀቡ በሙሉ ይቆማልና። ሰዎች ምድራዊ ነገሮች ላይ ይንጠለጠላሉ፡፡ የኔ መሻት ግን የፍቅር ችቦ ናት። በብርሃኗ የልቤን ሰብአዊነት ታነፃልኛለች፡፡ ሰዎች በዘር ፣ በቀለም በሃይማኖት ተከፋፍለዋል። እኔ ደግሞ በሁሉም አገር እንግዳ ነኝ – የየትኛውም ወገን አይደለሁም፡፡ ሥነ-ፍጥረት (ዩኒቨርስ) አገሬ ስትሆን ጉሳዬ ደግሞ ሁሉም የሰው ልጅ ነው፡፡ የሰው ልጅ አቅመቢስ ሆነውም የተከፋፈሉ ናቸው። በየጊዜው የምትጠበውን ምድር በግዛትና አገራት መሰነጣጠቅ አላዋቂነት ነው። የሰው ልጆች እጅ ለእጅ የሚያያዙት የነፍስን ቤተ መቅደስ ለማፍረስና ምድራዊ ድልድይ ለመገንባት ብቻ ነው። ብቻየን ቆሜ እንዲህ የሚል የውስጥ ድምፄ ተሰማኝ ፡
#ፍቅር  ለሰው ልብ ሕይወት እንደምትሰጥ ሁሉ አለማወቅን ማወቅ ደግሞ የእውቀትን መንገድ ያሳየዋል። ፍቅርና አለማወቅን መረዳት ወደ ታላቅ ደስታ ይመራሉ– ምክንያቱም ፈጣሪ ከፀሀይ በታች ለሰው ልጅ መከራን አልፈጠረምና።

@Zephilosophy
@Zephilosophy
👍6625🥰9👏4
ስለ ፍቅር ብጠይቅ ጥያቄዎቼን መመለስ የሚችል ማን አለ?
✍️ካህሊል ጂብራን

ፍቅር ምንድን ነው? ስለ ፍቅር ብላችሁ ንገሩኝ፣ በልቤ የሚነደው እሳት ምንድን ነው ጉልበቴን የሚያልፈሰፍሰው እና ምኞቴን የሚያከስመው ምንድነው?

ነፍሴን የሚጨብጧት እነዚያ የተደበቁ ለስላሳ እና ሻካራ እጆች ምንድናቸው?

ልቤን የሞላት ከመራር ደስታ እና ከጣፋጭ ህመም የተቀየጠ ወይን ምንድነው?

አይኖቼን የተከልኩበት የማይታይ ነገር የማሰላስለው ለመረዳት የሚያስቸግር ነገር፣ ልረዳው ያልቻልኩት ስሜት ምንድነው?

በትካዜ ውስጥ ከሳቅ ድምቀት የበለጠ ውብ፣ ከደስታ በላቀ የሚያስደስት ሃዘን አለ?
እስኪነጋ ድረስ አስተኝቶ በህይወት ለሚያቆየኝና መላ እኔነቱን በብርሃን ለሚሞላው ሃያል ራሴን የማስገዛው ለምንድን ነው?

እኛ ፍቅር የምንለው ነገር ምንድነው? ንገሩኝ፣ ህሊናን በሙሉ የሚገዛው በዘመናት ውስጥ የተደበቀው ሚስጥር ምንድነው?

ይህ በአንድ ወቅት የሁሉም ነገር መነሻና ውጤት የነበረው ፍቅር ምንድነው?
ይህ ከህይወትና ሞት የመነጨው፣ ከህይወት ይበልጥ አስገራሚ፣ ከሞት በላቀ ጥልቅ የሆነው ንቃት ምንድነው?

ንገሩኝ ጓደኞቼ፣ ፍቅር በጣቱ ጫፍ ነፍሱን ነክቶት ከህይወት እንቅልፍ የማይነቃ ከእናንተ መሃል አለ?

ነፍሱ የመረጠቻት ፍቅሩ ጠርታው እናትና አባቱን ትቶ የማይሄድ ከእናንተ መሃል ማነው?

ነፍሱ በልጃገረድ ጥዑም ትንፋሽ፣ ጣፋጭ ድምፅ እና ትንግርታዊ ለስላሳ እጆች ተማርካ ልቡ እስከ ዓለም ዳርቻ የማትሰደድ ወጣት ማን አለ?

ከልቡ የሚወደውን ሰው ለማግኘት ውቅያኖስ የማይሰነጥቅ፣ በረሃ የማያቋርጥ፡ ተራራ የማይቧጥጥ ከእናንተ መሃል ማነው?

ንስሃውን ከሚሰማው፣ ምህላውን ከሚቀበለው አምላክ ፊት እንደሚቀርብ የዕጣን መስዋዕት ልቡን የማያነደው ማን አለ?

ፍቅር ማለት...
ይቀጥላል...

@Zephilosophy

ንገሩኝ ጓደኞቼ ፍቅር ለናንተ ምንድነው ? ስለ ፍቅር ብላችሁ ንገሩኝ...✍️leave comment
49👍35🥰1
ፍቅር ማለት
....የቀጠለ

ትናንት ከመቅደሱ በራፍ ቆሜ መንገደኞቹን ስለ ፍቅር ተዓምራቶችና ጥቅሞች ያውቁ እንደሆነ በጥያቄ ሳደርቃቸው ዋልኩ፡፡

አንድ የደከመና የገረጣ ፊት ያላቸው በዕድሜ የገፉ አዛውንት በአጠገቤ እያለፉ እንዲህ አሉኝ፡-
«ፍቅር ከመጀመሪያው ሰው የተሽለምነው ተፈጥሯዊ ድክመት ነው፡፡»
ይሁን እንጂ አንድ ጎበዝ ወጣት በንዴት መልስ ሰጠ፡- .. «ፍቅር ዛሬን ከትናንት እና ከነገ ጋር የሚያገናኝ ድልድይ ነው።»


አንዲት ሃዘን የተላበሰ ፊት ያላት ሴት አቃስታ እንዲህ  አለች «ፍቅር በገሃነም የሚድሁ ጥቋቁር እፉኝቶች የሚወጉን ገዳይ መርዝ ነው መርዙ እንደ ጤዛ ትኩስ ስለሚመስል የተራበች ነፍስ ተስገብግባ ትጠጣዋለች ከመጀመሪያው ስካር በኋላ ግን ጠጪው ይታመምና ቀስ በቀስ ይሞታል፡፡»

ከዚያም አንዲት ውብ ጉንጮቿ እንደ ፀሃይ የሚያበሩ ልጃገረድ ፈገግ ብላ እንዲህ አለች፡
«ፍቅር በንጋት ሙሽሮች የሚቀርብ ጠንካራ ነፍሶችን የሚያጠነክርና ወደ ከዋክብት እንዲመጥቁ የሚያስችላቸው ወይን ነው፡፡»

ከእሷ በኋላ አንድ ጥቁር ካባ የደረበ ፂማም ሰው አይኖቹን አፍጥጦ ተናገረ፡
«ፍቅር ወጣትነት የሚጀምርበትና የሚያበቃበት የታወረ ድንቁርና ነው፡፡»
ሌላኛው ፈገግ ብሎ ቀጠለ፡«ፍቅር ሰው የአምላካቱን ያህል እንዲያይ የሚያስችል ሰማያዊ ዕውቀት ነው፡፡»

አንድ አይነ - ስውር መንገዱን በበትር እየፈለገ እንዲህ አለ፡
«ፍቅር ነፍስ የህያውነትን ሚስጥር እንዳታሳይ የሚከልላት፣ በዚህም ልብ ከኮረብቶች መሃል የሚንቀጠቀጡትን ጣዕረ - ሞቶች ፍላጎት ብቻ እንዲያይ እና የድምፅ አልባዎቹን ሸለቆዎች የመስተጋባት ጩኸት ብቻ እንዲሰማ የሚያደርግ የጉም መጋረጃ ነው፡፡»

አንድ ወጣት ክራሩን እየመታ እንዲህ ሲል ዘመረ-
«ፍቅር ከሚነደው የነፍስ ጉድጓድ በመመንጨት ምድሪቱን በብርሃን የሚሞላ አስማታዊ ጨረር ነው፡፡ ፍቅር ህይወትን በንቃትና ባለመንቃት መሃል እንዳለ ቆንጆ ህልም እንድናየው የሚያስችለን ነው፡፡»

አንድ ሽማግሌ ሰው እግሮቻቸውን እንደ ቡትቶ ጨርቅ እየጉተቱ
በሚንቀጠቀጥ ድምፅ እንዲህ አሉ፡
«ፍቅር በፀጥታማ መቃብር ያረፈ እስክሬን፣ በዘላለማዊነት ውስጥ
የሰጠመች ነፍስ ነው፡፡»

ከዚያም አንድ የአምስት ዓመት ህፃን እንዲህ አለ፡
«ፍቅር እናትና አባቴ ናቸው:: ከእናትና ከአባቴ በቀር ደግሞ ፍቅርን የሚያውቀው የለም።»

እናም ያለፉት በሙሉ ፍቅር የተስፋቸውና የተስፋ መቁረጫቸው ነፀብራቅ እንደሆነ በመግለፅ ሚስጥርነቱን የበለጠ አጎሉት።

ከዚያም በመቅደሱ ውስጥ አንድ ድምፅ ሰማሁ፡
« ህይወት እኩል ሁለት ቦታ ትከፈላለች፣ አንዱ በረዶ እና ሌላኛው እሳት፤ የሚፋጀው ግማሽ ፍቅር ነው፡፡»

በመጨረሻ ወደ መቅደሱ ገባሁና ተንበርክኬ ደስ እያለኝ ፀለይኩ፡- «ጌታዬ ሆይ፣ የነበልባሉ ራት አድርገኝ ... ጌታዬ ሆይ፣ የተከበረው እሳት ምግብ አድርገኝ ... አሜን፡፡»

ምንጭ- የጥበብ መንገድ
ደራሲ - ካህሊል ጂብራን

@Zephilosophy
@Zephilosophy
👍5527🥰1
ኦሾ ስለ ፍቅር

ፍቅር ከጥልቁ ውስጣችን የሚመጣ ነው።በጥያቄ ልናመጣው አንችልም ሲመጣም ዝም ማሰኘት አይቻልም። ፍቅር እኛ የምናደርገው ምርጫ አይደለም።

በሰው ህይወት ውስጥ ታላቁ ሙዚቃ ሊፈልቅ የሚችለው ልብ በአግባቡ የተቃኙ ክሮች ሲኖሩት ነው፡፡ ልቡን ያጣ ማህበረሰብ ጥሩ፣ እውተኛና ውብ የሆኑትን ክሮች ሁሉ አጥቷል፡፡ እውነት፣ ውበትና አምላካዊ ባህሪያት ወደ ህይወታችን እንዲገቡ ከፈለግን የልብን ሙዚቃ አፍላቂ የሆኑትን ክሮች በአግባቡ ከመቃኘት ውጪ ሌላ መንገድ የለም፡፡

እነዚህን የልብ ሙዚቃ አፍላቂ ክሮች በአግባቡ ለመቃኘት የሚያስችለው መንገድ ፍቅር ነው፡፡ ፍቅርን “ፀሎት ወይም እግዜርን የማግኛው መንገድ” ብዬ የምጠራውም ለዚህ ነው፡፡ ከፍቅር ያልሆነ ፀሎት ውሸትና የማይጠቅም ነው፡፡ ፍቅር አልባ የፀሎት ቃላት ዋጋ የላቸውም፡፡ ወደ አምላክ ለመጓዝ የፈለገ ሰው ያለ ፍቅር ሊሳካለት አይችልም፡፡ ልባዊ ሙዚቃን የሚያፈልቀው ፍቅር ነው፡፡

@Zephilosophy
82👍35🔥7👏4
Audio
ስምንት ድንቅ ያልተሰሙ ታሪኮች

ተራኪ - ግሩም ተበጀ

@zephilosophy
👍50🙏11👏5🥰2
ውስጣዊ ምሽጋችንን ከፍርሃት መጠበቅ

"ከፍርሃት ከራሱ በስተቀር   ምንም አትፍራ ፍርሃቶቻችን ልቀው እንዲገኙ የምንፈቅድ ከሆነ፣ ለመኖር ምንም ምክንያት፣ ለሀዘኖቻችንም ምንም ገደብ የለንም።”
- ሴኔካ

“መፍራት ያለብን ብቸኛ ነገር ማፈግፈግን ነው።መፍራት ያለብን ወደ ፊት  ለመገስገስ እና ለመለወጥ የሚያስፈልጉትን ጥረቶች ሽባ የሚያደርገውን ስም የለሽ፣ ምክንያት የለሽ፣ ተገቢ ያልሆነ ፍርሃትን ራሱን ነው።”

ስቶይኮች ፍርሃት የሚፈራ የሚሆነው በሚፈጥራቸው ችግሮች እንደ ሆነ ያውቃሉ፡፡ ሳናስበው ልናስወግዳቸው ስንነሳ፣ የምንፈራቸው ነገሮች በራሳችንና በሌሎች ላይ ከምንፈጥረው ጉዳት ጋር ሲነፃፀሩ ይደበዝዛሉ፡፡ ጦርነት መጥፎ ነው፤ ፍርሃት ደግሞ የበለጠ መጥፎ ነው። ከባድ ሁኔታ ፍርሃት የበለጠ እንዲጠነክር ያደርገዋል እንጂ አያግዘውም፡፡ ይህንን ሁኔታ መለወጥ የምንፈልግ ከሆነ ልንቋቋመውና ልናስወግደው ይገባል።

“ፍርሃትን የሚያመጡት ሁኔታዎች ናቸው፤ እኛ በጠላታችን ላይ ኃይል ሊኖረን ወይም ልንከላከለው ስንችል እኛ ግን እሱ በሚፈጥራቸው ሀሳቦች በፍርሃት ምሽግ ውስጥ ተሸብበናል ። ምሽጉ የሚጠፋው እንዴት ነው? በመሳሪያ ወይም በእሳት ብቻ ሳይሆን በአስተዋይነትም ነው ..... መጀመር ያለብን ከእዚሁ  ከአእምሯችን ነው፤ ምሽጉን መያዝና ጨቋኙን ማስወገድ ያለብን ከዚሁ ግንባር ነው።”
- ኤፒክቴተስ

ስቶይኮች “ውስጣዊ ምሽግ” የሚል አስደናቂ ሀሳብ ይሰጡናል።
ነፍሳችንን ይከላከላል ብለው የሚያምኑትም ይህንን ምሽግ ነው። .! በአካላዊ ሁኔታችን ተጠቂ ብንሆንም፣ በብዙ መንገዶች በመከራ ውስጥ
ልንሆን ብንችልም፣ ውስጣዊ ግዛታችን ግን መታለፍ የማይቻል መሆን አለበት።

ነገር ግን ታሪክ እንደሚያስተምረን፣ መታለፍ የማይቻሉ ምሽጎች #ከውስጥ ተላልፈው ከተሰጡ ሊሰበሩ ይችላሉ። በግንቦቹ ውስጥ የሚኖሩት ዜጎች በፍርሃት፣ በስግብግብነት ወይም በጥቅመኝነት ሲወድቁ፣ በሮቹን ሊከፍቱና ጠላትን እንዲገባ ሊያደርጉ ይችላሉ። ብዙዎቻችን ድፍረታችንን ስናጣና ለፍርሃት የተሰጠን ስንሆን የምናደርገውም ይህንን ነው፡፡

ጠንካራ ምሽግ ተቀብለሃል እና አሳልፈህ አትስጠው!!

📚የእለት ፍልስፍና

@Zephilosophy
@Zephilosophy
👍7116🔥2👏1
"ዝምታን የተማርኩት ከለፍላፊ፤ ትግስትን የተማርኩት ደግሞ ትግስት ከሌለው እንዲሁም ደግሞ ደግነትን የተማርኩት ከክፉ ቢሆንም በጣም የሚገርመዉ ነገር ለነዚህ መምህሮቼ ምስጋና ቢስ መሆኔ ነዉ።"
ካህሊል ጅብራን

Join👇👇👇
@zephilosophy
@zephilosophy
@zephilosophy
144👍56😁11🥰5
የትኩረት መዛባት

በዚህ ማህረሰብ ውስጥ  “ተመልከት የእኔ ሕይወት ከአንተ ሕይወት የበለጠ ያማረ ነው” በሚሉ በማህበራዊ ድረ- ገፆች በሚተላለፉ መልዕክቶች በኩል ጭንቀት፣ ፍርሃት፣ የጥፋተኝነት ስሜት ወዘተ... የመሳሰሉት አሉታዊ ልምዶች ያሉት ትውልድ እየፈራ ነው፡፡

ሰዎችም ሆነ የቲቪ ማስታወቂያዎች የመልካም ሕይወት ቁልፉ አሪፍ ስራ ማግኘት፣ ወይም ዘናጭ መኪና ወይም ቆንጆ ሴት ጓደኛ ያለህ መሆን እንደሆነ እንድታምን ይፈልጋሉ፡፡ አለም ያለማቋረጥ የሚነግርህ ነገር፣ የተሻለ የሕይወት መንገድ የሚባለው ብዙ መግዛት፣ ብዙ ማግኘት ፣ ብዙ መዋብ እንደሆነ ነው፡፡ ስለዚህ ሁልጊዜ በተደጋጋሚ ስለሁሉም ነገር ግድ እንዲኖርህ በሚነገሩ መልዕክቶች ስለምትጨናነቅ ያለማቋረጥ አዲስ ቅንጡ ነገሮችን ስለመግዛት፤ የእረፍት ጊዜህን ውድ በሆኑ ቦታዎች ስለማሳለፍ የምታስብ ትሆናለህ ወይም ፋሽን ልብሶች እና ኮስሞቲክሶችን ስለመግዛት የምታስቢ ትሆኛለሽ።

  እነዚህ ነገሮች ከባድ የበታችነት እና የጭንቀት ስሜት ከመፍጠራቸውም በላይ በማይገባ አይነት የማይረቡና የውሸት ከሆኑ ነገሮች ጋር የተጣበቅክ እንድትሆንና ሕይወትህን ሙሉ የማይጨበጥ ደስታና እርካታ ስታሳድድ እንድትኖር ያደርግሃል፡፡ የመልካም ሕይወት ቁልፍ ስለ ብዙ ነገሮች መጨነቅ ሳይሆን፣ ስለ ትንሽ ለዚያውም እውነት፣ አስቸኳይና አስፈላጊ ስለሆነው ነገር ብቻ መጨነቅ ነው፡፡

Mark Manson

@zephilosophy
👍12623🔥9👏1
ሟች ከመሆንህ እውነታ ጋር መጋፈጥ በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ ምክንያቱም ሁሉንም የማይረቡ፣ አቅም የሌላቸውና ጥልቀት የሌላቸውን እሴቶች ሁሉ ጠራርጎ የሚያስወግድ ነገር ነው፡፡ ብዙ ሰዎች ቀኖቻቸውን ተጨማሪ ገንዘብ ወይም ትንሽ ተጨማሪ ዝናና ትኩረት ወይም ትክክል ወይም ተወዳጅ በመሆናቸው ትንሽ ተጨማሪ ማረጋገጫ በማሳደድ ሲያሳልፉ፣ ሞት ግን ሁላችንንም በጣም በሚያሰቃይና አሰፈላጊ ጥያቄ ያፋጥጠናል፡፡
"ውርስህ ምንድነው? አንተ ስትሞት አለም የተለየችና የተሻለች የምትሆነው እንዴት ነው? ምን አሻራ ትተሀል? ምን ተፅእኖ ታመጣለህ?"

@Zephilosophy
👍81🔥107🥰4
ቅናት

ምንጭ ፦ ነፃ ስሜቶች (ኦሾ)
ትርጉም፦ ዩሐንስ አዳም

ቅናትውድድር/ንጽጽር ነው፡፡ እንድናወዳደር እና እንድናነጻጽር ተምረናል፡፡ ሁሌም እንድናነጻጽር ተገርተናል፡፡

አንድ ሰው የተሻለ ቤት አለው፡፡

አንድ የሆነ ሰው ያማረ አካል አለው፡፡

አንድ ሌላ ሰው ብዙ ገንዘብ አለው፡፡

አንድ ሰው ማራኪ ሰብእና አለው፡፡

ራሳችሁን ከአላፊ አግዳሚው ጋር አነጻጽሩ እናም ታላቅ ቅናት የሚያንሰራራ ይሆናል፡፡ ቅናት የንጽጽር መገራት ውጤት ነው፡፡ ንጽጽርን እና ውድድርን የምታስወግዱ ከሆነ ቅናት ይጠፋል፡፡ ከዚያም ራሳችሁን እንደሆናችሁት ብቻ ታውቁታላችሁ፡፡ እናንተ ማንንም አይደላችሁም፡፡ ማንንም መሆን አያስፈልጋችሁም፡፡ ራሳችሁን ከዛፎች ጋር አለማወዳደራችሁ ጥሩ አለበለዚያ በእነሱም ቅናት ይሰማችሁ ነበር፡፡ ለምን አረንጓዴ አልሆናችሁም? ለምን ይሆን እግዚአብሔር የጨከነባችሁ? ለምን አበባዎችን
አልሆናችሁም? ራሳችሁን ከአዋፋት ፣ ከወንዞች ፣ ከተራሮች ጋር አለማወዳደራችሁ ጥሩ ነው፡፡ አለበለዚያማ ትሰቃዮ ነበር። የምትወዳደሩት ከሰው ልጆች ጋር ብቻ ነው፡፡ ምክንያቱም እንድትወዳደሩ የተገራችሁት ከሰዎች ጋር ብቻ ስለሆነ ነው፡፡ ከፒኮኮች እና ከበቀቀኖች ጋር አትወዳደሩም፡፡

አለበለዚያማ ቅናት በጣም እና በጣም ይጨምር እና መኖር እስከሚያቅታችሁ ድረስ የቅናት ሸክም ይጫናችሁ ነበር፡፡ ውድድር እና ንጽጽር በጣም ቂላቂል አመላካከት ነው ምክንያቱም እያንዳንዱ ሰው ልዮ እና የማይነጻጸር በመሆኑ ነው።

ይህ ግንዛቤ አንድ ጊዜ በውስጣችሁ ከሰፈነ ቅናት ይጠፋል፡፡

እያንዳንዱ ሰው ልዮ እና የማይወዳደር ነው፡፡

እናንተ ራሳችሁንብቻ ናችሁ፡፡

ማንም ፈጽሞ እናንተን አይመስልም፡፡

እናንተ ፈጽሞ ማንንም መምሰል አትችሉም፡፡

አንድን ሰው/ሴት በምትወዱ ጊዜ ወደሌላ ሴት/ሰው ዘንድ ሊሄድ/ልትሄድ እንደማይችል/ትችል ታምናላችሁ፡፡ ግን ከሄደ/ከሄደች ምንም ማድረግ አይቻልም፡፡ ፍቅር ይህንን ግንዛቤ ያመጣል፡፡ ምንም ቅናት አይኖርም፡፡ ስለሆነም ቅናት የሚኖር ከሆነ ፍቅር እንደሌለ ጠንቅቃችሁ እወቁ፡፡ ቅናት ባለበት ግንኙነት ውስጥ ካላችሁ ጨዋታ እየተጫወታችሁ ነው ፤ ከፍቅር በስተጀርባ ወሲብን እየደበቃችሁ ነው ማለት ነው፡፡ ፍቅር ምንም ሳይሆን የተቀባ/ያጌጠ ቃል ብቻ ነው ማለት ነው፡፡

ቅናትን በጣም በቅርበት ተመልከቱት፡፡ ቅናት ምንድን ነው? ቅናት ማለት በውድድር ውስጥ መኖር ማለት ነው፡፡ አንድ ከእናንተ የበላይ የሆነ ሰው አለ፡፡ ከእናንተ በታች የሆነ ሰው አለ፡፡ እናንተ ሁሌም የመሰላሉ መሃል ላይ ናችሁ፡፡ ምናልባትም መሰላሉም ማንም መጨረሻውን የማያገኘው ክብ ሊሆንም ይችላል፡፡ እያንዳንዱ ሰው መሃል ላይ ተወስኖ ቀርቷል፡፡ እንዳንዱም ሰው መሃል ላይ ነው፡፡ መሰላሉ በክብ የሚሽከረከር ይመስላል፡፡

አንድ ሰው ከበላያችሁ ነው- ያ... ይጎዳል፡፡ ያም በጦርነት፣ በትግል ፣ በሚቻለው የትኛውም መንገድ ትንቀሣቀሱ ዘንዳ ያደርጋችኋል፡፡ ምክንያቱም የሚሳካላችሁ ከሆነ በትክክለኛው ይሁን በተሣሣተው መንገድ ማንም ግድ አይኖረውም፡፡ ስኬት ትክክለኛ ያደርጋችኋል፡፡ ውድቀት የተሣሣታችሁ እንደሆነ ያረጋግጣል፡፡ ስለዚህ ዋናው ጉዳይ ስኬት ነው፡፡ ስለዚህ ለስኬት የትኛውም መንገድ መጠቀም ይቻላል፡፡ መጨረሻው መንገዱን ትክክል ያደርገዋል፡፡ ስለዚህ ስለ መንገዱ ምንም መጨነቅ አያስፈልጋችሁም፡፡ ማንም ስለ መንገዱ ማንም አይጨንቀውም፡፡ መላው ጥያቄ እንዴት ነው መሰላሉን መውጣት የሚቻለው የሚለው ጥያቄ ነው፡፡ ግን የመሰላሉ መጨረሻ ላይ ፈጽሞ መምጣት አትችሉም፡፡ እናም ከእናንተ በላይ የሆነው ሰው ቅናትን በውስጣችሁ ይፈጥርባችኋል፡፡ እሱ ተሳክቶለታል
እናንተ ወድቃችኋል፡፡

ከምክንያት ወደ ውጤት የሚያመሩ መደምደሚያዎች አማኞች እንጂ ሳይንቲስቶች አያደርጓችሁም፡፡ “በቅናት ላይ ተመሰጡበት” ስላችሁ ይህንን ስሜት ታዘቡት ማለቴ ነው፡፡ በውስጣዊ አለማችሁ ውስጥ ሣይንቲስቶች ሁኑ፡፡ አእምሯችሁን ላብራቶሪ አድርጉት እና ያለምንም ውግዘት ተመለከቱ፡፡ “ቅናት መጥፎ ነው” አትበሉ፡፡ ማን ያውቃል “ቁጣ መጥፎ ነው” አትበሉ፡፡ ማን ያውቃል? አዎ ....ቅናት መጥፎ እንደሆነ ተነግሯችኋል፡፡ ያ....ግን በሌሎች የተነገረ ነገር ነው፡፡ ይህ የእናንተ ልምድ አይደለም፡፡ ህልውናዊ መሆን አለባችሁ፡፡ መከራችሁ የቅናትን መጥፎነት ካላረጋገጠ በስተቀር ለምንም ነገር "ነው” ወይም “አይደለም” አትበሉ፡፡ ፍጹም በሆነ መንገድ ከብያኔ ነጻ መሆን አለባችሁ፡፡ እናም ቅናትን ፣ ቁጣን ወይ፤ ወሲብን መታዘብ ደግሞ ታዓምር ነው።

ከማንኛውም ብያኔ ውጭ ሆናችሁ ስትታዘቡ ምን ይከሰታል? በቅናት ውስጥ የበለጠ በተመለከታችሁ ቁጥር ቅናት የበለጠ ግልጽ ይሆናል፡፡ የቅናትን ቂልነት ታያላችሁ፡፡ ቅናት ቂላቂል ነገር መሆኑን ቀድማችሁ ስለወሰናችሁ ሳይሆን በራሣችሁ ልምድ ተመርኩዛችሁ ቅናት ሞኝነት እንደሆነ ይገባችኋል፡፡ ግን ቀድሞውኑ ቅናት ሞኝነት እንደሆነ ከወሰናችሁ መላውን ነጥብ የምታጡት ይሆናል፡፡ ቀድሞ አለመበየናችሁን አስታውሱ፡፡ ቀድሞውኑ የምትወስኑ ከሆናችሁ መላውን ትርጉም ታጡታላችሁ፡፡ ከማንኛውም ውሳኜ ውጪ ተንቀሳቀሱ እናም ቅናት ምን እንደሆነ ተመልከቱ፡፡

@Zephilosophy
@Zephilosophy
👍5512
[የሕሊና ጸሎት]
___
ደምስ ሰይፉ

'አንዳንዶች' ሆይ...
.
.
.
'ሕዝብ' 'ሕዝብ' በሚለው አንደበታችሁ ውስጥ በሕዝብነት ስፍር በምላሳችሁ የምላመጥ ስም የለሽ መሆኔን...
___
ልባችሁ ቅንጣት ፍቅር ሳይኖራት ስለኔ መሰዋታችሁን በመለፈፍ በስሜ የምትነግዱ መሆኑን...
___
ከገዛ ክፋታችሁ አገዛዝ ነፃ ሳትወጡ 'ነፃ አውጭ ነን' ስብከታችሁን በየ አጋጣሚው ስትሰብኩ የማያቀረሻችሁ መሆኑን...
___
ወገኔ ሰው ነው ብዬ ከምኖርበት ቀዬ በመንደርተኛነት ጥንወት ታውራችሁ እንደ አውሬ አሳዳችሁኝ ስታበቁ ስለ ሰብዓዊ መብት ስታወሩ የማያቅለሸልሻችሁ መሆኑን...
___
'ዲሞክራሲ' በማስፈን ስም አገዛዝ ለማንበር እንደምታሴሩና ለዚህ ክፋታችሁ እኔኑ ጭዳ ከማድረግ የማትመለሱ መሆኑን...
___
ያለፈውን 'ጨለማ' የምትተቹት የተሻለ ቀን ለማምጣት ሳይሆን የተረኝነት አዙሪት ለማንበር መሆኑን...
___
ከሰላሜ ይልቅ ወንበራችሁ እያስጨነቃችሁ እንኳ 'የዜጎች መብት ይከበር' የምትሉት በአስመሳይነት መሆኑን...
___



.
.
.





.
.
.
ግና
.
.
.
ዛሬም ተስፋ ሳልቆርጥ የፍትህ ጸሐይ እስክትወጣ የምጠብቀው "የማይነጋ ለሊት የለም" ያሉኝን አምኜ ነው...
___

@Zephilosophy
@Zephilosophy
👍5612🥰4
እውነተኛ ማንነትን ማግኘት

ህይወታቸውን ሙሉ በኢጎ የተያዙ፣ የማያስተውሉና የማያስተውሉ ሆነው የቀሩ ሠዎች፣ ስለማንነታቸው ሲያወሩ ወዲያውኑ ስማቸውን፣ ስራቸውን፣ ግላዊ ታሪካቸውን፣ የሰውነታቸውን ቅርፅና ሁኔታ፣ ሌሎች ሊዛመዷቸው የሚችሉትን ሁኔታዎች ይነግሩሀል። ሌሎች ደግሞ እራሳቸውን ዘላለማዊ ነፍስ ወይም ህያው መንፈስ አድርገው እንደሚያስቡ በመናገር የተሻሉ መስለው ሊቀርቡ ይሞክራሉ። ነገር ግን በእውነት እራሳቸውን አውቀውት ነው ወይስ በአእምሮአቸው ውስጥ መንፈሳዊ-ቀመስ ፅንሰ ሐሳብ እየከተቱ ነው? እራስን ማወቅ፣ የተወሰኑ ሃሳቦችን ወይም እምነቶችን ከመቀበል በላይ ጥልቅ ነው። መንፈሳዊ ሃሳቦችም ሆኑ እምነቶች ጠቋሚ ቢሆኑ እንጂ፣ የሰው አእምሮአዊ ቅኝት አካል የሆነውን ቀድሞ የተገነባውን ጠንካራ የማንነት ፅንሰ ሃሳብ የሚያመክን ሃይል እምብዛም  የላቸውም። እራስህን በጥልቀት ማወቅ፣ በአእምሮህ ዙሪያ ከሚመላለስ ምንም አይነት ሃሳብ ጋር፣ አንዳች ግንኙነት የለውም። እራስን ማወቅ፣ እራስህን በአእምሮህ ውስጥ ከማጣት ይልቅ፣ በህላዌህ ውስጥ መትከል ነው።

👉ማንነቴ ብለህ የምታስበው ማንነት

የማንነት ስሜትህ በህይወትህ ያስፈልገኛል የምትለውንና ቦታ የምትሰጠውን ነገር የሚወስን ይሆናል። ለአንተ ቦታ ያለው ነገር ደግሞ፣ ሊረብሽህም ሆነ ሊያበሳጭህ አቅም አለው። እራስህን ምን ያህል በጥልቀት እንደምታውቀው ለመመዘንም፣ ይኽንኑ መስፈርት ልትጠቀም ትችላለህ። ቦታ የምትሰጣቸው ነገሮች የሚገለፁት በምትናገረውና በምታምነው ብቻ ሳይሆን በድርጊቶችህና በምትወስዳቸው አፀፋዊ ምላሾች ላይ አስፈላጊ እና ቁምነገር መስለው የሚገለጡትንም ያካትታል። እራስህን እንዲህ 'የሚያበሳጩኝና የሚረብሹኝ ነገሮች ምንድን ናቸው?' ብለህ ልትጠይቅ ትችላለህ። ትንንሽ ነገሮች አንተን የመረበሽ አቅም ካላቸው ማንነትህ በትክክል እንደዛ ነው፤ ትንሽ ነህ። ሳታስተውል የምታምነውም ይህንን ነው።

የምር የምትፈልገው ነገር ሰላምን ከሆነ፣ ሰላምን ትመርጣለህ። ከምንም ነገር በላይ ቦታ የምትሰጠው ለሰላም ከሆነ እና እራስህን ከትንሽ " እኔነት" ይልቅ መንፈስ እንደሆንክ በእውነት የምታውቅ ከሆነ፣ ከፈታኝ ሰዎች እና ሁኔታዎች ጋር ስትገናኝ ፍፁም አስተዋይና የረጋህ ሆነህ ትቆያለህ። የተፈጠረውን ሁኔታ ወዲያው ተቀብለህ፣ እራስህን ከማግለል ይልቅ ከሁኔታው ጋር አንድ ታደርጋለህ። እና ከዚያ አርምሞ ውስጥ የሚመጣ መልስ ታገኛለህ። መልሱን የሚሰጠውም ማንነትህ (ጥልቁ ተፈጥሮህ) እንጂ፣ ማንነቴ ብለህ ያሰብከው (ትንሹ እኔ) አየሸደለም። ምላሹም ሀያልና የተሳለጠ ሲሆን፣ የትኛውንም ሠውም ሆነ ሁኔታ ጠላት አያደርግም።

አንተ ኢጎህን አይደለህም፤ ስለዚህ በውስጥህ ያለውን ኢጎ ስታውቅ እራስህን አወቅክ ማለት ሳይሆን፣ ማንነተህ ያልሆነውን አወቅክ ማለት ነው። ነገር ግን በትክክል እራስህን ለማወቅ እንዳትችል ያደረገህን ትልቅ መሰናክል የምታስወግደው ማንነትህ ያልሆነውን ስታውቅ ነው።

ማንነትህን ማንም ሊነግርህ አይችልም። ማንነትህ ምንም አይነት ሀሳብ አይፈልግም። እንዲያውም እያንዳንዱ እምነት መሰናክል ይፈጥርብሀል። ምክንያቱም ሲጀመር የተፈጠርከውን ነህ። ነገር ግን መረዳት ከሌለ፣ ማንነትህ ወደ አለም ብርሀን መምጣት አይችልም።

👉  መትረፍረፍ

የምትረፍረፍ ምንጩ በውጪ የለም። የማንነትህ አካል ነው እንጂ። ነገር ግን ውጪ ያለዉን መትረፍረፍ በማወቅና በማመስገን መጀመር ትችላለህ። በዙሪያህ ያለውን የህይወትን ሙላት ተመልከት። ምነም እንኳን መትረፍረፍ ከተሰማህ ነገሮች ወደ አንተ መምጣታቸው አይቀሬ ቢሆንም፣ መትረፍረፍ እንዲሰማህ፣ ንብረት መያዝ አይጠበቅብህም። መትረፍረፍ፣ ላለው የሚመጣ ነገር ነው። ይህ የዩኒቨርስ ህግ ነው። መትረፍረፍም ሆነ ጎዶሎነት የሚገለጡ የውስጥህ እውነታዎች ናቸው።

👉 መልካም አና መጥፎ

ብዙ ሰዎች በህይወታቸው የሆነ ወቅት ላይ ከመወለድ፣ ከማደግ፣ ከስኬት ከመልካም ጤንነት፣ ከእርካታ እና ከማሸነፍ በተጨማሪ እጦት፣ ውድቀት፣ ህመም፣ እርጅና፣ መጃጀት፣ ስቃይና ሞትም እንዳለ ያውቃሉ። እነዚህም በስምምነት "መልካም" እና "መጥፎ" ፣ "የሰመረ" እና "ያልሰመረ" ተደርገው ይወሰዳሉ። የሰዎች ህይወት "ትርጉም" የሚኖረው መልካም ከተባለው ጋር ሲያያዝ ሲሆን፣ ይህም መልካም የተባለው ነገር ደግሞ ሁልጊዜ የመንኮታኮት፣ የመሰባበር፣ የመበጥበጥ አደጋ ይጋረጥበታል። ህይወት ትርጉም ስታጣና የሚገልፃት ነገር ሁሉ ስታጣ፣ ትርጉም የለሽና መጥፎ በሆነው አደጋ ውስጥ ገብታለች። ፈጥኖም ሆነ ዘግይቶ፣ የትኛውንም የኢንሹራንስ ፖሊሲ ብንገባ ህይወትን የሚያምስ ነገር መምጣቱ በማንም ላይ አይቀሬ ነው። አመጣጡ፣ በእጦት ወይም በአደጋ፣ በህመም፣ በአካል ጉዳት፣ በእርጅና ወይም ሞት ሊሆን ይችላል። ነገር ግን በሰውየው ህይወት ውስጥ የመጣው እክል እና ይሄን ተከትሎ የሚፈጠረው አእምሮ የፈጠረው ትርጉም መንኮታኮቱ፣ ለመለኮታዊው ስርአት በር ከፋች ሊሆን ይችላል።

ሃሳብ፣ ሁኔታዎችና ክስተቶች ልክ የግላቸው ተፈጥሮ ያላቸው ይመስል፣መልካም እና መጥፎ እያልን እንሰይማቸዋለን። በሃሳብ ላይ ባለን ቅጥ ያጣ አመኔታ ምክንያት እውነታ ይሰነጣጠቃል። ይህ መሰነጣጠቅ ወዥንብር ቢሆንም፣ በውዥንብሩ እስከተጠመድክ ድረስ ግን እውነት ይመስላል። ቢሆንም፣ ዓለም ግን እርስ በእርሱ የተሳሰረ፣ አንድም ነገር የብቻው ህልውና የሌለው፣ የማይከፋፈል ህብር ነው። የሁሉም ነገሮችና ክስተቶች በጥልቀት መተሳሰር የሚያመለክተውም "መልካም" እና "መጥፎ" የሚባሉት አእምሮአዊ ስያሜዎች፣ በተጨባጭ ውዥንብር እንደሆኑ ነው። እጅግ የተገደቡ ምልከታዎች ሲሆኑ እውነት መሆን የሚችሉትም በአንፃራዊነትና በጊዜያዊነት ነው። ይሄ በሎተሪ እጣ ውድ መኪና በገዛው አስተዋይ ሰው ታሪክ ውስጥ ውብ ሆኖ ተብራርቷል። ጓደኞቹና ቤተሰቦቹ ስለርሱ ተደስተው በዚያውም ደስታውን ለማክበር መጡ። "በጣም አይገርምም!። እድለኛ ነህ" አሉት። ሰውየውም ፈገግ ብሎ "ይሆናል" አለ። መኪናዋን በመንዳት የተወሰኑ ሳምንታት አጣጣመ። አንድ ቀን ግን፣ የሰከረ አሽከርካሪ በመንገድ መገናኛ ላይ ገጨውና በከፍተኛ ጉዳት ሆስፒታል ገባ። ጓደኞቹና ቤተሰቦቹ ሊጠይቁት መጡ " እንዴት አይነት ክፉ አጋጣሚ ነው?" አሉ። ሰውየው በድጋሚ ፈገግ ብሎ "ይሆናል" አለ። በሆስፒታል በነበረበት ጊዜም፣ በምሽት የመሬት መንሸራተት ተከስቶ መኖርያ ቤቱን ባህር ውስጥ ከተተው። እንደገና በሚቀጥለው ቀን ጓደኞቹና ቤተሰቦቹ መጥተው " ሆስፒታል ውስጥ በመሆንህ እድለኛ አይደለህም ታዲያ?" አሉት። እርሱም መልሶ "ይሆናል" አላቸው።

የአስተዋዩ ሰው "ይሆናል" የሚለው አባባል፣ የሚከሰተውን ሁሉ ለመፈረጅ አለመፈለጉን ያመለክታል። ከመፈረጅ ይልቅ፣ የሆነውን ሁሉ በመቀበል ከመለኮታዊዉ ስርዓት ጋር ንቁ አንድነት ይፈጥራል። ተራ የሚመስል ክስተት በህብሩ ሸማ ውስጥ ምን አይነት ስፍራ ሊኖረው እንደሚችል አእምሮ በፍፁም እንደማይረዳ አውቋል። ነገር ግን ድንገተኛ የሚባል ክስተት የለም፤ በራሱ እና ስለራሱ ብቻ በብቸኝነት የሚኖር ክስተትም ሆነ ሁኔታ የለም። አካልህን የገነቡ አተምች በውስጥህ የሚገኙ ከዋክብት ይመስላሉ፤ እናም የትንሽ ክስተት መንስኤው ወሰን የለሽ እና በማይጨበጥ መልኩ ከህብሩ ጋር የተሳሰረ ነው። የማንኛውንም ክስተት መነሻ ወደ ሗላ ሄደህ መመርመር ከፈለግክ፣ እስከ ፍጥረት መጀመሪያ ድረስ መጓዝ ይኖርብሀል። 

ምንጭ ፦ አዲስ ምድር
ፀሀፊ :-ኤካሀርት ቶሌ

ይቀጥላል

@Zephilosophy
@Zephilosophy
👍5421🔥5
ኢጎ እና የአሁኑ ቅፅበት

የአሁኑ ቅፅበት ወዳጅህ አድርገህ መወሰን የኢጎ ፍፃሜ ነው። ኢጎ በአሁኑ ቅፅበት ማለትም ከህይወት ጋር አንድ መሆን አይችልም። ምክንያቱም የኢጎ ተፈጥሮ እራሱ አሁንን ቸል የማለት፣ የመቃወምና፣ ዋጋ ያለመስጠት ነው። ኢጎ የሚኖረው በጊዜ ውስጥ ነው። ኢጎ ብርቱ ከሆነ፣ በህይወት ውስጥ ብዙ ጊዜ ይወስዳል። እናም አብዛኛው የምታስበው ሃሳብ ካለፈው ጊዜ እና ከመፃኢው ጊዜ ጋር የተገናኘ ይሆናል። በዚህም የማንነት ስሜትህ፣ ማንነትህን ካለፈው ጊዜ ይቀዳል። ሙላትህን ደግሞ ከመፃኢው ጊዜ ይጠብቃል። ፍርሀት፣ ድብርት፣ ጥበቃ፣ ቁጭት፣ ፀፀት፣ ንዴት በጊዜ የተገደበው ህላዌ ብልሹነቶች ናቸው።

ኢጎ የአሁኑን ቅፅበት የሚያስተናግድበት ሶስት መንገዶች አሉት። እነዚህም፣ ለሆነ ግብ እንደ መረማመጃ፣ እንደ እንቅፋት ወይም እንደ ጠላት ናቸው። እነዚህ ልምዶች ሲነሱ እንድታስተውልና መልሰህም መወሰን እንድትችል፣ እያንዳንዳቸውን እንፈትሻቸው።

1.ለኢጎ የአሁኑ ቅፅበት የተሻለ ከተባለ፣ ሊሆን የሚችለው ለሆነ ግብ እንደ መረማመጃ ሲሆን ነው። ምንም እንኳን መፃኢ ጊዜ እራሱ በአእምሮ ውስጥ ከሃሳብነት ያልዘለለ፣ ሲመጣም የአሁን ቅፅበት ሆኖ ከመምጣት ውጪ መሆን የማይችል ቢሆንም፣ የአሁኑ ቅፅበት ግን በጣም አስፈላጊ ተደርጎ ለሚወሰደው መፃኢ ጊዜ እንደመረማመጃ ተደርጎ ይወሰዳል። በሌላ አገላለፅ ሌላ ጊዜ ላይ ለመሆን በጣም ከመጣደፍ የተነሳ፣ አሁንን በደንብ መኖር አትችልም።

2.ይህ ልምድ እጅግ ሲጎላ ደግሞ (የተለመደም ነው) ፣ የአሁኑ ቅፅበት ሊቀረፍ እንደሚገባ እንቅፋት ተደርጎ ይወሰዳል። በዘመናችን አኗኗር፣ በየሰው የእለት ኑሮ ውስጥ ጥድፊያ፣ ሰቀቀን እና ጭንቀት የሚነሱትና መደበኛ ሁኔታ የሆኑትም ለዚሁ ነዉ። ህይወት ማለትም አሁን እንደ "ችግር" ታይቷል፣ እናም ከመደሰትህ፣ በትክክል መኖር ከመጀመርህ በፊት ልትፈታቸው የሚገቡ ብዙ ችግሮችን ማኖር ትጀምራለህ። ችግሩ ግን ፣ አንድ ችግር በፈታህ ቁጥር ፣ ሌላ ችግር ደግሞ ብቅ ይላል። የአሁኑ ቅፅበት እንደ እክል እስከታየ ድረስ፣ ችግሮች ፍፃሜ አይኖራቸውም።

3.ሌላው በጣም የከፋና በጣም የተለመደው ደግሞ፣ የአሁኑን ቅፅበት እንደ ጠላት ማየት ነው። የምትሰራውን ስራ ስትጠላ፣ አካባቢህን ስታማርር፣ የሚከሰተውንና የተከሰተውን ነገር ስትረግም፣ ወይም ከራስህ ጋር የምታወራው ነገር በነበርና ባልነበር ሲሞላ፣ ስትወቅስና ስትወነጅል፣ ከሚከሰተው ነገር ጋር ስትጣላ፣ ሁሌም ቢሆን ከዚያ ውጪ መሆን ከማይችለው ክስተት ጋር ስትጣላ፤ ህይወትን ጠላት እያደረክ ነው፤ ህይወትም "የምትፈልገው ጦርነት ነው፣ የምታገኘውም ጦርነት ነው" ትልሀለች።

ከአሁኑ ቅፅበት ጋር ያለህን ብልሹ ግንኙነት እንዴት መቀየር ትችላለህ? በጣም አስፈላጊው ነገር፣ ራስህን፣ ሃሳቦችህንና ድርጊቶችህን መመልከት ነው። በምትመለከትበት ጊዜ፣ ከአሁን ጋር ያለህ ግንኙነት ብልሹ እንደሆነ በምታስተውልበት ጊዜ፣ ህላዌህ ውስጥ ነህ። ተመልካቹ፣ በውስጥህ የሚያንሰራራው ህላዌ ነው። ብልሹነቱን ባየህበት ቅፅበት፣ ብልሹነቱ መክሰም ይጀምራል።

👉 ከወሰን ባሻገር መሆን

ንቁ ከሆንክ፣ ትኩረትህ በአሁን ላይ ብቻ ከሆነ፣ ያ ህላዌ በምትሰራው ስራ ላይ ይፈስና ለውጥ ይፈጥራል። በዚያ ውስጥ ጥራትና ሀይል አለ። የምትሰራው ነገር፣ በዋናነት ለሆነ ግብ (ገንዘብ፣ ክብር፣ አሸናፊነት) መረማመጃ ካልሆነ፤ ይልቁንም በራሱ ምሉዕ ከሆነ፣ በምትሰራው ላይ ሀሴት እና ህያዉነት አለ፤ በህላዌህ ውስጥ ነህ። እንዲሁም ከአሁኑ ቅፅበት ጋር ወዳጅነት ካልፈጠርክ በቀር፣ ህላዌ ውስጥ አትሆንም። የተፈጠርነው ገደብን ለመኖር ብቻ ሳይሆን ከገደብ ባሻገር በመጓዝ በሕላዌያችን እንድናብብ ጭምር ነው።

መፅሀፍ፦ አዲስ ምድር
ደራሲ፦ ኤክሀርት ቶሌ

@Zephilosophy
@Zephilosophy
👍5210👏10🥰1
ደስታ

ምንጭ ፦ ከፍስሀ ጋር መወለድ (ኦሾ)
ተርጓሚ፦ በዩሐንስ አዳም

መደሰት አስቸጋሪ የሆነው ደስታ መጥፋት እንዳለበት ስለሚታሰብ ነው፡፡ መደሰት የሚቻለው ራሳችሁን ሳትሆኑ ነው፡፡ አናንተ እና ደስታ በአንድ ላይ ልትኖሩ አትችሉም፡፡ ደስታ እዚያ ሲኖር አናንተ ቀሪ ናችሁ፡፡ አናንተ እዚያ ስትኖኑ ደስታ ቀሪ ይሆናል፡፡ ደስታ እና አናንተ ልክ እንደ ብርሃን እና ጨለማ ናችሁ፡፡ ሁለታችሁም ተመሳሳይ ቦታ ላይ መከሰት አችትሉም፡፡

በዚህ ምክንያት የተነሳ መደሰት አስቸጋሪ ነው፡፡ ደስታ ቀላል አይደለም፤ ምክንያቱም መሞት አስቸጋሪ ነው፡፡ እናም በእያንዳንዷ ቅፅበት እንዴት መሞት እንዳለባቸው የሚያውቁ ብቻ ናቸው እንዴት መደሰት እንዳለባቸው የሚያውቁት፡፡ ብዙ የመሞት ብቃት በኖራችሁ ቁጥር ደስታችሁ የጠለቀ፣ የፍስሃችሁ ነበልባልም በጣም ታላቅ ይሆናል፡፡

መደሰት አስቸጋሪ ነው ፦ ምክንያቱም መከረኛ ሆናችሁ እንድትቀሩ የሚያደርጉ በጣም በርካታ ኢንቨስትመንቶች አሉ ይህንን ሁኔታ ካላያችሁት በስተቀር ለመደሰት መሞከራችሁን መቀጠል ብትችሉም ቅሉ በጭራሽ ደስተኛ አትሆኑም፡፡ እነዚህ በመከራችሁ ውስጥ የሚያገኙት ኢንቨስትመንቶቻችሁ መወገድ አለባቸው፡፡ እናም እያንዳንዱ ሰው ከልጅነቱ ጀምሮ መከራ ሊከፍል የሚችል መሆኑን ተምሯል፡፡ አናንተ ደስተኛ እና ጤነኛ ከሆናችሁ ማንም ስለ አናንተ ደንታ የለውም፡፡ ጥሞናን አታገኙም፤ እናም ጥሞና የእኔነት ዋናው እስትንፋስ ነው፡፡ ልክ አካል ኦክስጂን እንደሚያስፈልገው እኔነት ጥሞና /ትኩረት/ ያስፈልገዋል፡፡

ጤነኛ ፣ ደስተኛ ስትሆኑ ሰዎች ጥሞና አይቸሩዋችሁም፡፡ ጥሞና አያስፈልግም፡፡ ዳሩ ስትታመሙ፣ መከረኛ ስትሆኑ፣ ስታለቅሱ፣ ስታስቡ ግን ሁሉም ቤተሰብ ወደ ፍላጎቶቻችሁ ትኩረትን ይሰጣሉ፡፡ ልክ ድንገተኛ አደጋ እንደ ደረሰባችሁ ስራቸውን ያቆማሉ፡፡ እናት ከማዕድ ቤት እየሮጠች ትመጣለች ፤ አባትም ጋዜጣውን ያሽቀነጥራል፡፡ እናም ሁሉም ሰው ትኩረቱን ከእናንተ ጋር ያደርጋል፡፡ ይህ ሁኔታ ታላቅ የእኔነት እርካታን ያጎናፅፋል፡፡ እናም ቀስበቀስ የእኔነትን መንገድ ትማራላችሁ፡፡ መከረኛ ሆኖ መቅረት... እናም ሰዎች ለእናንተ ጥሞና ይሰጣሉ፡፡ መከረኛ ሆናችሁ ቅሩ እናም እነሱ ለእናንተ ያዝኑላችኃል፤ ደስተኛ ስትሆኑ ማንም ያንን ስሜታችሁን አይካፈልም፡፡ ለዚያ ነው ሰዎች ለባህታዊዎች ትኩረትን የሚሰጡት፡፡ አንድ ሰው ይፆማል እናም ሰዎች ተመልከቱት እንዴት ያለ ቅዱስ ነው" ይላሉ፡፡

ክብረ በዓልን ብታከብሩ ማንም ያንን ስሜት ከአናንተ ጋር አይቋደስም:: ከአንድ ሰው ጋር በፍቅር ውስጥ ብትሆኑ ማን ነው ከአናንተ ጋር ስሜታችሁን የሚጋራው? በተቃራኒው ሰዎች በጣም ቀናተኛ ይሆናሉ፡፡ አናንተ ተወዳዳሪ ሆናችኃል፡፡ እነዚህ ሰዎች አንድ ዓይነት ሰውን ለራሳቸው ይፈልጋሉ፤ አናንተ ጠላት ናችሁ።

እኛ የተወለድነው ከፍስሐ ጋር ነው፤ ፍስሐ የኛ ዋናው ፍጥረት ነው፤ ደስተኛ ለመሆን ምንም ነገር አያስፈልግም፤ አንድ ሰው ዝም ብሎ ብቻውን በመቀመጥ ደስተኛ መሆን ይችላል፡፡ ደስታ ተፈጥሯዊ ሲሆን - መከራ ደግሞ ተፈጥሮዊ ያልሆነ ነው:: ግን መከራ ትርፋማ ያደርጋል፡፡ እናም ደስታ ዓላማ - ቢስ ነው፡፡ ማንኛውንም ትርፍ አያመጣላችሁም፡፡

ስለሆነም አንድ ሰው መወሰን መቻል አለበት፡፡ ደስተኛ መሆንን ከፈለጋችሁ ተራ ሰው መሆን መቻል አለባችሁ፡፡ ይህ ነው እንግዲህ ውሳኔው፡፡ ደስተኛ መሆን ከፈለጋችሁ ማንንም ያልሆናችሁ መሆን ይኖርባችኃል፡፡ ምክንያቱም እንዳችም ጥሞና አታገኙም፡፡ በተቃራኒው ሰዎች ቅናት ይሰማቸዋል። ሰዎች ከእናንተ
በተቃራኒ ውስጥ ይሆናሉ፡፡ ሰዎች አይወዱአችሁም፡፡ ሰዎች የሚወዱአችሁ በመከራ ውስጥ ከሆናችሁ ብቻ ነው:: ከዚያም ያዝኑላችኃል፤ ችግራችሁን ይካፈሏችኃል፤ በሁኔታው የእናንተ እኔነት ይረካል፤ እናም የእነርሱም እኔነት ጨምሮ ይረካል፡፡ ከአንድ ሰው ሀዘኑን ሲጋሩ እነሱ የበላይ እናም አናንተ የበታች ናችሁ፡፡ እነርሱ ወሳኝ እጆች ናቸው፡፡ የመተዛዘን የበላይነት ጨዋታ ደስ ያሰኛቸዋል፡፡

ዝም ብላችሁ ታዘቡ-አናንተም ራሳችሁ እነዚህን ታደርጋላችሁ፡፡ አንድ ሰው የእሾህ አልጋ ላይ ቢተኛ ሰውየው ለሰው ልጅ የተወሰነ ደስታን ይዞ የመጣ ይመስል፣ ታላቅ ድርጊትን የፈጸመ ይመስል- ወዲያውኑ ትሰግዱለታላችሁ፡፡ እሱ እኮ ዝም ብሎ ራሱን ማሰቃየት የሚወድ ሰው ነው፡፡ ነገር ግን ትወዱታላችሁ ፤ ታከብሩታላችሁም፤ አክብሮታችሁ ግን ጤናማ ያልሆነ ነው፡፡ ይህ ሰው የአናንተን ጥሞና ይፈልጋል፡፡ እናም ይህ መንገድ ደግሞ የአናንተን ጥሞናን ለማግኘት በጣም ቀላሉ መንገድ ነው፡፡ የእርሱ እኔነት ይሟላል፤ ይረካል፡፡ ስለዚህ በእነዚያ እሾሆች ላይ ለመተኛት እና ለመሰቃየት ዝግጁ ነው፡፡

ይህ ነገር ሁሉም ቦታ በትንሽም ሆነ በትልቅ መጠን እየተከሰተ ነው፡፡ ልብ በሉት! ይህ በጣም ጥንታዊ ወጥመድ ነው፡፡ እናም ከዚያ በኋላ መደሰት ትችላላችሁ፡፡ ከደስታ በቀር ምንም የለም፤ ማንንም ላለመሆን ዝግጁ ከሆናችሁ፣ የሌሎችን ጥሞና የማትሹ ከሆነ ከናካቴው ምንም ዓይነት ችግር አይኖርም ደስተኛ መሆን፣ ዘና ማለት ትችላላችሁ፡፡ በጣም ትናንሽ ነገሮች የሚቻለውን ታላቅ ፍስሐ ሊሰጡአችሁ ይችላሉ፡፡

@Zephilosophy
@Zephilosophy
👍4413😁2
ራስን ከፍ አድርጎ የማየት ኢጎ

በህይወት ስቃይ ና ችግሮች ውስጥ  ስንሆን  በችግሮቻችን የበለጠ አቅመቢስነት የሚሰማን እንሆናለን፡፡ በዚህም ከእነዚያ ችግሮች ለማምለጥና ያንን ለማካካስ ራሳችንን ከፍ አድርጎ ማየት እናዳብራለን፡፡ ይህ ራስን ከፍ አድርጎ ማየት ከእነዚህ በአንዱ መንገድ ይሰራል፡፡

1. እኔ በጣም አሪፍ ነኝ ሌሎቻችሁ ግን ደባሪዎች ናችሁ ስለዚህ የተለየ እንክብካቤ ያስፈልገኛል፡፡
2. እኔ የምረባ አይደለሁም ሌሎቻችሁ
ግን አሪፎች ስለሆናችሁ የተለየ እንክብካቤ ያስፈልገኛል የሚሉ ናቸው፡፡

እነዚህ ሀሳቦች በውጪ ሲታዩ ተቃራኒ አስተሳሰብ፣ ውስጡ ግን ተመሳሳይ ራስ ወዳድነት ያለባቸው ናቸው፡፡ በእርግጥ ራሳቸውን ከፍ አድርገው የሚያዩ ሰዎች በሁለቱ መካከል ሲዋዥቁ ይታያሉ፡፡ ወይ እነርሱ ከአለም ሁሉ በላይ ናቸው አለዚያም ደግሞ አለም ሁሉ ከእነርሱ በላይ ነው፡፡ ይህም መዋዠቅ የሚከሰተው የሆነ ቀን ወይም ያለባቸውን ሱስ እያስታገሱ ባሉባት ቅጽበት ይሆናል፡፡

ብዙ ሰዎች ከንቱ በሆነው ለራሳቸው በሚሰጡት ከፍተኛ ክብር የተነሳ በራሳቸው ፍቅር የወደቁ እንዲሁም በጣም ለፍላፊ በመሆናቸው ከሌላው ሰው በቀላሉ መለየት ይችላሉ።በቀላሉ መለየት የማይችሉት ለራሳቸው ከፍተኛ ክብር የሚሰጡ ሆነው ነገር ግን ዝቅተኛ እንደሆኑና ለአለም የማይጠቅሙ እንደሆኑ የሚሰማቸውን ነው፡፡

በሕይወት ውስጥ ሁሉም ነገር አንተን ለመጉዳት የሚደረግና ያለማቋረጥ ተጠቂ የሚያደርግህ አድርጎ መተርጎም ልክ ተቃራኒውን እንደማድረግ ያህል ራስ ወዳድነት ነው፡፡ አንደኛው ምንም አይነት ችግር የሌለበት ሆኖ አንደኛው ደግሞ ሊቀረፍ የማይችል ችግር አለበት የሚል እምነት ማዳበር የዚያኑ ያህል በከፍተኛ ደረጃ ከንቱ የሆነ ራስን ከፍ አድርጎ የማየት ነገር ይፈልጋል፡፡ እውነታው በሕይወት ውስጥ የግል ችግር የሚባል ነገር አለመኖሩ ነው፡፡ የሆነ ችግር ካለብህ፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሌሎች ሰዎችም ከዚህ ቀደም የዚያ አይነት ችግር ነበረባቸው ወይም አሁን አለባቸው አለበለዚያም ወደፊት ይኖርባቸዋል፡፡ የዚያ ችግር ተጠቂዎች ምናልባትም አንተ የምታውቃቸው ሰዎች ሊሆኑም ይችላሉ፡፡ ይህ መሆኑ ግን ችግሩን አያሳንሰውም ወይም የሚጎዳ የመሆኑን መጠን አይቀንሰውም፡፡ ይህ ማለት በአንዳንድ ሁኔታዎች ተጠቂ ላትሆን ትችላለህ ማለትም ሳይሆን ይህ ማለት አንተ የተለየህ አይደለህም ማለት ነው፡፡

በአብዛኛው ችግሮችን ለመፍታት የመጀመሪያውና በጣም አስፈላጊ የሆነው እርምጃ፣ አንተና የአንተ ችግሮች በችግሮቹ ከባድነት ወይም በሚያስከትሉት ስቃይ ተጠቃሚዎች አለመሆናችሁን መረዳት ነው፡፡

ራስን ከፍ አድርጎ የማየት ችግር

አንድ ጊዜ ሰዎች በዙሪያቸው የሚከናወነው ሁሉ ራስን ትልቅ አድርጎ የሚያሳይ እንደሆነ ያለማቋረጥ እንዲገምቱ የሚያደርግ አስተሳሰብ ካዳበሩ፣ እነርሱን ከዚያ ውስጥ ሰብሮ ማውጣት በጣም አስቸጋሪ ነው፡፡ እነርሱን ለማስረዳት የሚደረግ ሙከራ ሁሉ ለእነርሱ የእነርሱን ታላቅነት፣ ምን ያህል ጎበዝ፣ ተሰጥኦ ያላቸው፣ መልከ መልካሞችና ስኬታማ መሆናቸውን መሸከም ባለመቻል የሚመጣ ጥቃት ተደርጎ ይታያል፡፡

ራሳቸውን ከፍ ያሉ እንደሆኑ የሚሰማቸው ሰዎች፣ በሕይወት ውስጥ ያሉት ሁኔታዎች ሁሉ ለእነርሱ ታላቅነት ወይ አድናቆት ወይ ጥቃት የተሰሩ ናቸው ብለው ያምናሉ፡፡ የሆነ ጥሩ ነገር ካጋጠማቸው እነርሱ በሰሩት አሪፍ ነገር ምክንያት ነው፡፡ መጥፎ ነገር ካጋጠማቸው የሆነ ሰው ቀንቶ ሊጎዳቸው ሞክሮ ነው፡፡ ራስን ከፍ አድርጎ ማየት ዘላቂነት የለውም፡፡ እንደዚህ አይነት ሰዎች የእነርሱን የበላይነት ስሜት በሚያጠናክር በየትኛውም ነገር ራሳቸውን ያሞኛሉ፡፡ ምንም ያህል ዋጋ ቢያስከፍልም፣ አንዳንድ ጊዜ በዙሪያቸው ላሉ ሰዎች አካላዊና ስሜታዊ ጉዳት የሚያስከትል ቢሆንም የአእምሮ እይታቸውን ይከላከላሉ፡፡

ለራሳቸው ከንቱ የሆነ ከፍተኛ ግምት የሚሰጡ ሰዎች  ለራሳቸው ችግሮች በግልፅና በታማኝነት እውቅና መስጠት ስለማይችሉ ህይወታቸውን ዘላቂ ወይም ትርጉም ባለው ሁኔታ ማሻሻል አይችሉም፡፡ እንደዚህ ያሉ ከፍተኛ ክህደት እያሳደዱና ታላላቅ የክህደት ደረጃዎች እያከማቹ ለመኖር የተተው ናቸው፡፡

ግን በመጨረሻ እውነቱ ይወጣና የተቀበሩት ችግሮች ሁሉ እንደገና ራሳቸውን ግልፅ ሲያደረጉ ከባድ የህይወት ምስቅልቅል ውስጥ ይገባሉ።

📚- The subtle art of not giving a f*ck
✍️ - Mark manson

@Zephilosophy
👍4611😭2
#Moral_Philosophy
በዚህ ዓለም ላይ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ጥሩ የሆነ ነገር ምንድን ነው?
___
#Repost

በሥነ
ምግባር የፍልስፍና ታሪክ ውስጥ እንደ አብሪ ኮኮብ ሆነው ከሚታዩ ፈላስፋዎች መካከል አንዱ ጀርመናዊው ፈላስፋ ኢማኑኤል ካንት ነው። በዚህ የፍልስፍና ዘውግ ውስጥ "ደስታ" እና "ጥቅም" ለረጅም ጊዜ የህልዮቱ ማንፀሪያዎች ሆነው አገልግለዋል።

ካንት ግን በ18ኛው ክ/ዘ መጨረሻ ላይ አዲስ የሥነ ምግባር ማንፀሪያ ይዞ መጣ። ይሄንንም ማንፀሪያ ለማሳየት በቅድሚያ አንድ ወሳኝ የሥነ ምግባር ጥያቄ ያነሳል፤ እንዲህ የሚል፦

"በዚህ ምድር ላይ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ (ያለምንም Qualification) ጥሩ የሆነ ነገር ምንድን ነው?"

እስቲ እንገምት መልሱ ምን ሊሆን ይችላል?

#ገንዘብ!? አይደለም፤ ገንዘብ ጥሩ የሚሆነው ለጥሩ ነገር ስናውለው እንጂ ገንዘብ በራሱ በተፈጥሮው ጥሩነት የለውም፡፡

#ዕውቀት!? ዕውቀትም አይደለም፤ እውቀት ጥሩ የሚሆነው መልካም ሰው ሲያገኝ ነው፡፡

#ጉብዝና (Courage)!? እሱም አይደለም፤ ጉብዝና ጥሩ የሚሆነው ለጥሩ ዓላማ ሲሆን ነው፡፡ ለምሳሌ፣ ሂትለር ጎበዝ (Couragous) ነው፡፡ ሆኖም ግን፣ የእሱ ጉብዝና መጥፎ ጉብዝና ነው፡፡

እና ታዲያ ምንድን ነው? ለካንት መልሱ ቀላል ነው - በዚህ ዓለም ላይ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በራሱ መልካም የሆነ ነገር አንድ ብቻ ነው፤ እሱም "ቅንነት/Good will" ነው፡፡ ዕውቀት፣ ገንዘብና ጉብዝና ቅንነት ላይ ካላረፉ አደገኛ ይሆናሉ፡፡

ይሄም ማለት በካንት የሥነምግባር አስተምህሮ
(Deontological Ethics) መሰረት አንድ ነገር ጥሩነቱ የሚለካው በውጤቱ (ጥቅም ወይም ደስታ ስለሚሰጥ) ሳይሆን በዓላማው (በሞቲቩ) ነው፡፡ እስቲ አንድ ምሳሌ እናንሳ፦

#ለምሳሌ፣ ኤልሳ የምትባል ልጅ ዋና እየተለማመደች እያለች ውሃ ውስጥ ስትሰምጥ ሄለን አየቻት፡፡ ወዲያውም ሄለን የኤልሳን ህይወት ለማዳን ውሃው ውስጥ ዘላ ገባች፡፡ ውጤቱ ግን በጣም የሚያሳዝን ሆነ ― ኤልሳ በሄለን እጅ ላይ ሞተች፡፡ ይሄንን የሄለንን ተግባር በምንድን ነው የምንመዝነው/ የምንዳኘው?

* በውጤቱ ይሆን?! ውጤቱማ ሄለንን ወንጀለኛ ያደርጋታል፡፡

* በዓላማው (በሄለን ሞቲቭ) ማለትም "ነፍስ የማዳን" ዓላማ ይሆን?! ይሄ ጥሩ መለኪያ ይመስላል፡፡ ሆኖም ግን፣ በዚህ የሄለን ዓላማ ላይ ራሱ ጥያቄዎች ይነሳሉ፦

የሄለን "ነፍስ የማዳን" ዓላማ (motive) መነሻው ምንድን ነው?! ለካንት ወሳኙ ጥያቄ ይሄ ነው፡፡ የአንድን ድርጊት ጥሩነትና መጥፎነት የምንለካው በውጤቱ ሳይሆን በሐሳቡ/ በዓላማው ቢሆንም፣ የዓላማውስ መነሻ ምንድን ነው?! የሚለው ጥያቄ በጣም ወሳኝ ነው፡፡ ስለዚህ፣ የሄለን "ነፍስ የማዳን" ዓላማ (motive) መነሻው ምንድን ነው?! አራት መላምቶችን እናስቀምጥ፦

* የሄለን "ነፍስ የማዳን" ዓላማ ኤልሳን ስለምታውቃት (የጎረቤት ልጅ ስለሆነች ወይም የብሄሯ ልጅ ስለሆነች) ከሆነ፣ የሄለን ተግባር መልካም ሥራ አያስብለውም፤ ያ "የሞራል ተግባር" አያስብለውም፡፡ ምክንያቱም፣ የሞቲቩ መነሻ Inclination ነው፡፡

* የሄለን "ነፍስ የማዳን" ዓላማ መነሻው "ማንኛውም ሰው በሞት አፋፍ ላይ ያለን ሌላ ሰው የመርዳትና የማዳን ግዴታ አለበት" የሚለውን የመንግስት ህግ ለማክበር ከሆነ፣ አሁንም የሄለን ተግባር መልካም ሥራ አያስብለውም፡፡ ምክንያቱም፣ የሞቲቩ መነሻ ውጫዊ (in accordance with Duty) ነው፡፡

የሄለን "ነፍስ የማዳን" ዓላማ መነሻው "ባልንጀራህን እንደራስህ አድርገህ ውደድ" የሚለውን ሃይማኖታዊ ህግ ለማክበርና ገነት ለመግባት ከሆነ፣ አሁንም የሄለን ተግባር መልካም ሥራ አያስብለውም፡፡ ምክንያቱም፣ የሞቲቩ መነሻ አሁንም ውጫዊና ቅድመ ሁኔታ ላይ የተመሰረተ ነው፡፡

የሄለን "ነፍስ የማዳን" ዓላማ መነሻው "በሞት አፋፍ ላይ ያለን ሰው የመርዳትና የማዳን ውስጣዊ የሞራል ግዴታ አለብኝ" ከሚል ከሆነ ትክክል ነች፤ ይሄም ሄለንን "መልካም ሰው" ያስብላታል፡፡ ምክንያቱም፣ የሞቲቩ መነሻ ምንም ዓይነት ቅድመ ሁኔታ ላይ ያልተመረኮዘ ንፁህ ውስጣዊ የቅንነት ግዴታ (motive from Duty/the moral law within) ስለሆነ፡፡

ካንት በዚህ ቅንነት (Good Will) ላይ በተመሰረተው ውስጣዊ የሞራል ግዴታ አብዝቶ ይመሰጣል፡፡ ለዚህም ነው ካንት እንዲህ በሚል ንግግሩ ይበልጥ የሚታወቀው፦

"ሁልጊዜ በህይወቴ የሚያስደምሙኝ ሁለት ነገሮች አሉ፤ እነሱም ከላይ በከዋክብት የተንቆጠቆጠው ሰማይና በውስጤ ደግሞ ያለው የሞራል ህግ the moral law within me!! ናቸው።"

@Zephilosophy
@Zephilosophy
👍9120👏7🔥2🤔1
ተመስጦ (meditation)

ብዙ ሰው ከራሱ ጋር የግል ጊዜ ስለማይወስድ ሂወቱ የተረጋጋ አይደለም!


የሰው ልጅ ዕለት ተዕለት በሚኖረው ኑሮ ውስጥ ሲደክመው ዕረፍት ማድረግን ፤ የሰውነት ክፍሎቹን ለማፍታታት መንጠራራትንና ማፍታታትን ፤ የድብርት ስሜት ሲሰማው ማፋሸግንና ሲጨንቀው ስሜቱን ለማረጋጋት ዓየር በደንብ ወደ ውስጥ አስገብቶና ወደ ውጭ በረጅሙ መተንፈስን በተፈጥሮ የታደላቸው ገጸ በረከቶች ናቸው፡፡ ከፍ ሲልም መንፈሱን ወደ ትልቁ ማማ ሰማየ ሰማይ በመውሰድና በመመሰጥ አእምሮውንና መንፈሱን ያድስበታል፡፡

ተመስጦ ሰዎች ከጥንት ጊዜ ጀምሮ አእምሯቸውንና ህይወታቸውን የሚቆጣጠሩበት እንዲሁም እራሳቸውን ፈልገው የሚያገኙበት የአእምሮ ፤የአካልና የመንፈስ እንቅስቃሴ ነው፡፡ በተጨማሪም ተመስጦ ሰዎች አእምሯቸውን እንደ ኤሌክትሪክ ማብሪያና ማጥፊያ ባሻቸው ሰዓት ማሰብ የሚፈልጉትን እንዲያስቡ ማሰብ የማይፈልጉትን ደግሞ ከአእምሮአቸው ውስጥ በቀላሉ የሚያጠፉበት ተፈጥሯዊ የአእምሮ ቁልፍ ነው፡፡

በአንድም ይሁን በሌላ መልኩ በዓለም ላይ በሚገኙ ባህሎች ውስጥ ተመስጦና መመሰጥ አለ፡፡ ነገር ግን ተመስጦ በተደራጀና በተዋቀረ መልኩ የተጀመረው በሂንዱ ሸለቆ ውስጥ ከክርስቶስ ልደት በፊት ከ5000 እስከ 3500 ዓመተ ዓለም አካባቢ መሆንኑን የአርኪዮሎጂ ጥናቶችና ግኝቶች ያስረዳሉ፡፡ በሂንዱ ሸለቆች የተገኙ የግርግዳ ላይ ስዕሎች ከላይ ከተጠቀሰው ዓመተ ዓለም ጀምሮ ሰዎች ቁጭ ብለው እግራቸውን አመሳቀለው ተመስጦን ሲያከናውኑ እንደነበር ማስረጃዎች ያስረዳሉ፡፡ እንዲሁም በህንድ መጻሕፍት ውስጥ ከ3000 ዓመታት በፊት የተመስጦና መመሰጥ ዘዴዎች ተመዝግበው እንደሚገኙ የታሪክ ድርሳናት ያሳያሉ፡፡

ሁሉም ሃይማኖታዊ ክንዋኔዎች በውስጣቻው ተመስጦን ይዘው ይገኛሉ፡፡ በሃይማኖታዊ ስርዓት ምዕመናን ሲጸልዩ ፤ ሲያመሰግኑና ሲሰግዱ ወደ አምላካቸው ይመሰጣሉ፡፡ ነገር ግን አብዛኛውን ጊዜ ስለተመስጦና መመሰጥ ሲነሳ ሰዎች ወደ አእምሮአቸው የሚመጣው የቡድሃ ወይም የሂንዱ እምነት ነው፡፡ ምንም እንኳን እነኚህ ሃይማኖቶች በሃይማኖታዊ ክንዋኔአቸው ለተመስጦ ትልቅ ትኩረት ቢሰጡም በዘመናዊው እይታ ተመስጦና መመሰጥ ከየትኛውም ሃይማኖት ጋር አይያያዝም አልያም ዘውትር መመሰጥንና ተመስጦን ማከናወን የቡድሃ ወይም የሂንዱ እምነት ተከታይ መሆን ማለት አይደለም፡፡ ለመነሻ ያህል ይህን ካልን የመመሰጥና የተመስጦን ጥቅም ከብዙ በጥቂቱ እንመለከታለን

1.ውጥረትን ይቀንሳል

መመሰጥና ተመስጦ ከማንኛውም አካላዊ እንቅስቃሴ በላይ ውጥረትን የመቀነስ አቅሙ ከፍተኛ ነው፡፡ መመሰጥ ውጥረትን መቀነስ ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ በነርቭ ስርዓት ላይ ውጥረትን የሚያመጣውን ኮርቲሶል የሚባለውን ኬሚካል በመቀነስ በምትኩ ሰዎች ጥሩ ስሜት እንዲሰማቸው የሚያደርገውን ሴሮቶኒን የተባለውን ኬሚካል አንጎላችን እንዲያመነጭ ያነሳሳል፡፡

2.ጤናን ያሻሽላል

ተመስጦ የበሽታ መከላከል ኃይልን በማደርጀት፤ የደም ግፊትና የኮለስትሮል መጠንን  በመቀነስ ጤናን ያሻሽላል፡፡ በተለይ በማይድን ጽኑ ህመም የሚሰቃዩ ሰዎች ህመማቸውን ለማስታገስና ለማገገም ከተመስጦ ብዙ ጥቅም ያገኛሉ፡፡ በእርግጥ ተመስጦን ለመጠቀም የግድ ጽኑ ህሙማን መሆን አይጠበቅብንም ከጉንፋንና እራስ ምታት ለመታቀብና ለመዳን ትልቅ አስተዋጽኦ ያደርጋል፡፡

3.ለእንቅልፍ

በስራ ጫና ብዛትና በውጥረት ምክንያት አንዳንድ ጊዜ ሰዎች እንቅልፍ ላይዛቸውና በቶሎ በመተኛት ከድካማቸው ፋታ ለማግኘት ይቸገራሉ፡፡ ይህ በሚሆንበት ወቅት መመሰጥት ችግራቸውን  ተፈጥሮአዊ በሆነ መንገድ በቀላል እንዲፈቱ ይረዳቸዋል፡፡

4.እርጅናን ይከላከላል

ጥናቶች እንደሚያመለክቱት አዘውትረው የሚመሰጡ ሰዎች ከማይመሰጡት ጋር ሲወዳደሩ ቀናቸውን በተመስጦ የሚያሳልፉ ሰዎች ከዕድሜቸው አንጻር ቶሎ የማያረጁና ረጅም ዕድሜ የሚኖሩ ሆነው ተገኝተው፡፡ ይህም የሚሆንበት ምክንያት መመሰጥና ተመስጦ እርጅና የሚያስከትሉ ቲሹዎችንና በሽታዎችን መግታት በመቻሉ ነው፡፡

5. ለውስጠ ስሜት መረጋጋትና አወንታዊ አስተሳሰብ

መመሰጥ ጭንቀት ውስጥ ለገቡ፤ በቶሎ ለሚናደዱ፤ ስሜታቸውን መቆጣጠር ለሚቸገሩና ድብርት ለሚያጠቃቸው ሰዎች እንደ ተፈጥሯዊ መከላከያ መድኃኒት ተደርጎ በባለሙያዎች ይታዘዝላቸዋል፡፡ በተጨማሪም መመሰጥ የአሉታዊ አስተሳሰቦችንና ስሜቶችን ከሰዎች አእምሮና አካላት ውስጥ አጥርቶ በማውጣት በአወንታዊ አስተሳሰብ እንዲገነቡ ትልቅ ሚና ይጫወታል፡፡ በአጠቃላይ ከጭንቀትና ተያያዥ ጉዳዮች ባሻገር ተመስጦን የሚያዘወትሩ ሰዎች ጥሩ ስሜት የሚሰማቸውና ደስተኞች ናቸው፡፡

ለተመስጦ የሚረዱ ጥቆማዎች

.ዘውትርና በተመሳሳይ ሰዓት መመሰጥን ልምድ ማድረግ ይመከራል

.ከመመሰጥ በፊት የማነቃቃት ባህሪይ ያላቸውን ትኩስ ነገሮች አለመውሰድ

.ከምግብ በኋላ አለመመሰጥና በቀን ውስጥ ሙሉ ኃይል የለኝም ብለው በሚያስቡበት ሰዓት መመሰጥ

.መመሰጥ የሚፈልጉበትን ስፍራ ማዘጋጀትና በቂ ዓየር እንዲገባው መስኮት መክፈት

.በጣም ደማቅ ብርሃን የሌለውን ስፋራ መምረጥና ሰፋ ያለ ልብስ መልበስ

.ጸጥ ያለ አካባቢን መምረጥና በተመስጦ ጊዜ ሊረብሹ የሚችሉ ነገሮችን እንደ ስልክ ፤ ሬዲዮ ፤ ቴሌቪዥንና የመሳሰሉ ነገሮን ድምጽ ማጥፋት

.በረጅሙ ዓየር ወደ ውስጥ ማስገባት

.ያስገቡትን ዓየር ለጥቂት ሰከንዶች ሳይተነፍሱ ማቆየት

.ከዚያም በረጅሙ መተንፈስ

.በሚተነፍሱበት ወቅት ለሚሰማዎት ስሜት ትኩረት መስጠት፤ ዓየር በአፍንጫ ቀዳዳዎ ሲገባ ፤ ዓየሩን ለተወሰኑ ሰከንዶች ሲይዙት በመላ አካላቶ እየተሰራጨ እንደሆነና ሰውነቶን አዝናንቶ በአፍዎ እንደሚወጣ ማሰብ በቀላሉ የተረጋጋ ስሜትንና መዝናናትን አእምሮአችንና አካላችን እንዲሰማው ያደርጋል፡፡

@Zephilosophy
@Zephilosophy
👍8319🥰2👏2