🙏ስለ መልካም አስተያየታችሁ ሁላችሁንም ከልብ እናመሰግናለን።ፍቅራችሁን ያለስስት ገልፃችሁልናልና እውነት ከልብ እንወዳችኋለን። ከዚህ በላይ እንድንሰራ ትልቅ ሀላፊነት ጥላችሁብናል።
ይህ የቻናል የተፈጠረው ምክንያታዊ ና ሚዛናዊ አስተሳሰብ እንዲኖረን የሚያስችሉ ፍልስፍናዎችን ና እውቀቶችን ለማጋራት ነው።በተጨማሪም አካልን፣ ስሜትን እና አእምሮን የማስገዛት ጥበብን በማስተማር ንቁ፣ በሳል እና ብልህ ሰው እንድንሆን ማገዝ ነው። እስካሁን በዚህ ቻናል የህይወት ልማድችንንና እምነታችንን የሚጠይቁ፤ የንቃት ሀይል የሚጨምሩ ፤ ፍቅር እና መንፈሳዊነትን የሚሰብኩ ሀሳቦችን አጋርተናል።
ሆናም ግን ካነበብናቸው እና ካወቅናቸው ብዙ መፅሀፍትና ልምምዶች ጥቂቱን ብቻ ነው የጋራናችሁ። ከዚህ በኋለ በብዛት እንድናጋራችሁ ዘንድ ፈጣሪ የማይዋዥቅ ሞራልና የማይደበዝዝ ትጋት ይሰጠን ዘንድ እንመኛለን!!
ብዙ ሰው ጋር ተደራሽ በመሆን ትጋታችን ይጨመር ዘንድ እያንዳንዱን ፁሁፍ #ሼር ማድረግ እንዳትዘነጉ!!
@zephilosophy
ይህ የቻናል የተፈጠረው ምክንያታዊ ና ሚዛናዊ አስተሳሰብ እንዲኖረን የሚያስችሉ ፍልስፍናዎችን ና እውቀቶችን ለማጋራት ነው።በተጨማሪም አካልን፣ ስሜትን እና አእምሮን የማስገዛት ጥበብን በማስተማር ንቁ፣ በሳል እና ብልህ ሰው እንድንሆን ማገዝ ነው። እስካሁን በዚህ ቻናል የህይወት ልማድችንንና እምነታችንን የሚጠይቁ፤ የንቃት ሀይል የሚጨምሩ ፤ ፍቅር እና መንፈሳዊነትን የሚሰብኩ ሀሳቦችን አጋርተናል።
ሆናም ግን ካነበብናቸው እና ካወቅናቸው ብዙ መፅሀፍትና ልምምዶች ጥቂቱን ብቻ ነው የጋራናችሁ። ከዚህ በኋለ በብዛት እንድናጋራችሁ ዘንድ ፈጣሪ የማይዋዥቅ ሞራልና የማይደበዝዝ ትጋት ይሰጠን ዘንድ እንመኛለን!!
ብዙ ሰው ጋር ተደራሽ በመሆን ትጋታችን ይጨመር ዘንድ እያንዳንዱን ፁሁፍ #ሼር ማድረግ እንዳትዘነጉ!!
@zephilosophy
👍39❤2
👍Reaction released
የምንለቃቸውን ፁሁፎች በላይክ ብዛት እያወዳደራችሁ እንዳታነቡ በሚል ምክንያት reaction አናበራም ነበር።የቴሌግራም monitazation ለመጠቀም ስንል አብርተነዋል። የምናቀርባቸው ፁሁፎች በክብደትም ሆነ በጥልቀት እየጨመሩ ስለሚመጡ እያንዳንዱን ሀሳብ ሳትመርጡ ብታነቡ መልካም ነው። ምክንያቱም የምናቀርባቸው ሀሳቦች መጀመሪያውኑም ከተመረጡ መፅሀፎች የተመረጡ እና የተጨመቁ ሀሳባች ስለሆኑ ...
የምንለቃቸውን ፁሁፎች በላይክ ብዛት እያወዳደራችሁ እንዳታነቡ በሚል ምክንያት reaction አናበራም ነበር።የቴሌግራም monitazation ለመጠቀም ስንል አብርተነዋል። የምናቀርባቸው ፁሁፎች በክብደትም ሆነ በጥልቀት እየጨመሩ ስለሚመጡ እያንዳንዱን ሀሳብ ሳትመርጡ ብታነቡ መልካም ነው። ምክንያቱም የምናቀርባቸው ሀሳቦች መጀመሪያውኑም ከተመረጡ መፅሀፎች የተመረጡ እና የተጨመቁ ሀሳባች ስለሆኑ ...
👍184👏6🔥2❤1
💬ሰለ ጥያቆቻችሁ
🤝ግሩፕ ስለመክፈት
የቻናላችን ግሩፕ ለማታውቁት 👇👇
https://t.me/+XgPfefgVVvRhZjk0
በዚህ ግሩፕ በምናነሳቸው ሀሳቦች ላይ መወያየት፤ ተጨማሪ ሀሳብ መስጠት፤ መሞገትና መተቸት ትችላላችሁ።ወደፊት ደግሞ ብዙዎቻችሁን የሚያሳትፍ የውይይት እና የክርክር መድረክ ይኖረናል!!
📚soft copy መፅሀፍ ስለማጋራት
⭐️ብዙ pdf መፅሀፎች ቢኖሩንም ገብያ ላይ ካልጠፉና ደግመው የማይታተሙ ካልሆኑ በስተቀር የደራሲዎችን ጥቅም ስለሚጎዳ ያለ ደራሲዎች ፍቃድ መለጠፍ አንችልም።ምን ቢወደድ መፅሀፍ ከምንበላው ምግብ አያንስምና እየገዛችሁ የማንበብ ልምድን ማዳበር አለባችሁ።
🤝ግሩፕ ስለመክፈት
የቻናላችን ግሩፕ ለማታውቁት 👇👇
https://t.me/+XgPfefgVVvRhZjk0
በዚህ ግሩፕ በምናነሳቸው ሀሳቦች ላይ መወያየት፤ ተጨማሪ ሀሳብ መስጠት፤ መሞገትና መተቸት ትችላላችሁ።ወደፊት ደግሞ ብዙዎቻችሁን የሚያሳትፍ የውይይት እና የክርክር መድረክ ይኖረናል!!
📚soft copy መፅሀፍ ስለማጋራት
⭐️ብዙ pdf መፅሀፎች ቢኖሩንም ገብያ ላይ ካልጠፉና ደግመው የማይታተሙ ካልሆኑ በስተቀር የደራሲዎችን ጥቅም ስለሚጎዳ ያለ ደራሲዎች ፍቃድ መለጠፍ አንችልም።ምን ቢወደድ መፅሀፍ ከምንበላው ምግብ አያንስምና እየገዛችሁ የማንበብ ልምድን ማዳበር አለባችሁ።
👏33👍11❤4
ሰው ከህዋ አንፃር ያለው ቦታ እና ግንዛቤ
ከግዙፉ ህዋ አንፃር የሰው ማንነት እንዴት ሊገለጽ ይችላል?
ሰው - ራሱን ከግዙፉ ህዋ ጋር እያስተያዬ ስለራሱ ማንነት ያስባል፣ የህይወቱን ትርጉም ፍለጋ ይኳትናል፣ ይጨነቃል፣ ተስፋ የሚሆነው ነገር ይፈልጋል፡፡ እነዚህን ስሜቶቹ፣ ፍላጐቶቹ፣ ተስፋዎቹ፣ እምነቶቹ. .. ወዴት ያደርሱታል ?
ሰው ከህዋ አንፃር ያለው ግንዛቤን ከጥንታዊ ሰው ታሪክ፤ ከመፅሀፍ ቅዱስ ፤ከትላልቅ ፈላስፎች እይታ አንፃር እናየዋለን።
1.ጥንታዊው ሰው ስለ ህዋ ያለው ግንዛቤ
የሰውና የህዋን ግንኙነት ምን እንደሚመስል ለመረዳት ከጥንታዊ ሰው ኑሮና አስተሳሰብ እንጀምር ካልን በአንድ በኩል ከላይ እንደተገለፀው ሰው ከተፈጥሮ በላይ የመሆን ማንነት ሲታይበት በተቃራኒው ደግሞ በዛን ዘመን ይኖር የነበረው ስው ተፈጥሮን ሌትም ቀንም በመፍራት ራሱን ከተፈጥሮ በታች የጣለበት ጊዜ ሁኖ እናገኘዋለን፡፡ በዘመኑ ሰው ነገሮች ሁሉ ነፍስ አላቸው ብሎ ያምን ነበር፤ ይህ ማለት ሰው በዘመኑ ነፍሳዊ (animist) ነበር፡፡ በሰማይ በምድር ያሉትን ሁሉ ሰውአዊ (antoropomorphic) ማንነት የሰጠበት ጊዜ ነበር፤ ከፍ ሲልም መንፈሳዊ ትርጉም በመስጠት ተፈጥሮን ያመለከበት ጊዜ ነበር።
የጥንቱ ዘመን የሰው ልጅ ታሪክ በእንደዚህ አይነት ሁለት የተለያዩ ስሜቶችና እምነቶች (በፍርሃትና በድፍረት፣ በሽንፈትና አሸናፊነት፣ በበታችነትና የበላይነት) ውስጥ ሰው ግራ ተጋብቶ የሚንገዋለል ማንነት ይዞ ይኖር የነበረበት ዘመን እንደነበር ያሳየናል፡፡ የጥንት ግብፃዊያን የምድር ህይወታቸውን በአባይም በፀሐይም ይመስሉት ነበር፡፡ አባይ ይሞላል - ይጐድላልም፤ ፀሐይ ትወጣለች ትጠልቃለችም፡፡ የሰው ህይወትም እንደዚያው ነው፡- ይወለዳል - ያድጋል፤ ይሞታል-ከሞትም ይነሳል፡፡ የተፈጥሮን የድግግሞሽ ሥርዓት መሠረት አድርገው ጥንታዊ ግብፃዊያን ሞተው እንደማይቀሩ - ከሞት እንደሚነሱ ያምኑ ነበር፡፡ የፀሐይ የሰማይ ላይ ጉዞ በምድር ላይ የሰው ጉዞ ነው፡፡ፀሐይ ስትጠልቅ ጠፍታ አትቀርም፤ በክብር ደግሞ ትወለዳለች፡፡ ይህም የሰው እጣፈንታው አንደፀሐይ የሆነና የሚሞት ገላው እንደሚነሳ የተስፋ ቃል የሚሰጠው ሆነ፡፡ በዚህ ምክንያትም ፀሐይን አምላክ ነሽ አሏት፤ መሪዎቻቸውንም በፀሐይ መሠሏቸው፡፡
ሥልጣኔ የሰውን ልጅ መጐብኘት ሲጀምር ተፈጥሮን የሚመለከትበት አይኑ እየሰፋ መጣ፤ ራሱንም በሰማያት ካሉት ፍጥረታት ጋር ያስተያይ ጀመር፡፡ ተፈጥሮን በማሸነፍ ማንነቱን ለማሳየትም ልቡ የበለጠ ተነሳሳ፤ ድንጋይ በድንጋይ እየደራረበ ራሱን ወደሰማይ ከፍ ያደርግ ጀመር፡፡ ከፍ አድርጐ በሠራው የድንጋይ ማማ ቁሞ መሬትን ቁልቁል ሲመለከታት እያነሰችበት መጣች፤ የእርሱ የበላይነት ግን ከሁሉ በልጦ ታየው፡፡
ከዚህ በመቀጠል ደግሞ መፅሀፍ ቅዱስ የሰው ልጅ ከህዋ አንፃር ያለውን ሁለት ምልከታ እናያለን...
ረ/ፕርፌሰር ዋለልኝ እምሩ
@zephilosophy
ከግዙፉ ህዋ አንፃር የሰው ማንነት እንዴት ሊገለጽ ይችላል?
ሰው - ራሱን ከግዙፉ ህዋ ጋር እያስተያዬ ስለራሱ ማንነት ያስባል፣ የህይወቱን ትርጉም ፍለጋ ይኳትናል፣ ይጨነቃል፣ ተስፋ የሚሆነው ነገር ይፈልጋል፡፡ እነዚህን ስሜቶቹ፣ ፍላጐቶቹ፣ ተስፋዎቹ፣ እምነቶቹ. .. ወዴት ያደርሱታል ?
ሰው ከህዋ አንፃር ያለው ግንዛቤን ከጥንታዊ ሰው ታሪክ፤ ከመፅሀፍ ቅዱስ ፤ከትላልቅ ፈላስፎች እይታ አንፃር እናየዋለን።
1.ጥንታዊው ሰው ስለ ህዋ ያለው ግንዛቤ
የሰውና የህዋን ግንኙነት ምን እንደሚመስል ለመረዳት ከጥንታዊ ሰው ኑሮና አስተሳሰብ እንጀምር ካልን በአንድ በኩል ከላይ እንደተገለፀው ሰው ከተፈጥሮ በላይ የመሆን ማንነት ሲታይበት በተቃራኒው ደግሞ በዛን ዘመን ይኖር የነበረው ስው ተፈጥሮን ሌትም ቀንም በመፍራት ራሱን ከተፈጥሮ በታች የጣለበት ጊዜ ሁኖ እናገኘዋለን፡፡ በዘመኑ ሰው ነገሮች ሁሉ ነፍስ አላቸው ብሎ ያምን ነበር፤ ይህ ማለት ሰው በዘመኑ ነፍሳዊ (animist) ነበር፡፡ በሰማይ በምድር ያሉትን ሁሉ ሰውአዊ (antoropomorphic) ማንነት የሰጠበት ጊዜ ነበር፤ ከፍ ሲልም መንፈሳዊ ትርጉም በመስጠት ተፈጥሮን ያመለከበት ጊዜ ነበር።
የጥንቱ ዘመን የሰው ልጅ ታሪክ በእንደዚህ አይነት ሁለት የተለያዩ ስሜቶችና እምነቶች (በፍርሃትና በድፍረት፣ በሽንፈትና አሸናፊነት፣ በበታችነትና የበላይነት) ውስጥ ሰው ግራ ተጋብቶ የሚንገዋለል ማንነት ይዞ ይኖር የነበረበት ዘመን እንደነበር ያሳየናል፡፡ የጥንት ግብፃዊያን የምድር ህይወታቸውን በአባይም በፀሐይም ይመስሉት ነበር፡፡ አባይ ይሞላል - ይጐድላልም፤ ፀሐይ ትወጣለች ትጠልቃለችም፡፡ የሰው ህይወትም እንደዚያው ነው፡- ይወለዳል - ያድጋል፤ ይሞታል-ከሞትም ይነሳል፡፡ የተፈጥሮን የድግግሞሽ ሥርዓት መሠረት አድርገው ጥንታዊ ግብፃዊያን ሞተው እንደማይቀሩ - ከሞት እንደሚነሱ ያምኑ ነበር፡፡ የፀሐይ የሰማይ ላይ ጉዞ በምድር ላይ የሰው ጉዞ ነው፡፡ፀሐይ ስትጠልቅ ጠፍታ አትቀርም፤ በክብር ደግሞ ትወለዳለች፡፡ ይህም የሰው እጣፈንታው አንደፀሐይ የሆነና የሚሞት ገላው እንደሚነሳ የተስፋ ቃል የሚሰጠው ሆነ፡፡ በዚህ ምክንያትም ፀሐይን አምላክ ነሽ አሏት፤ መሪዎቻቸውንም በፀሐይ መሠሏቸው፡፡
ሥልጣኔ የሰውን ልጅ መጐብኘት ሲጀምር ተፈጥሮን የሚመለከትበት አይኑ እየሰፋ መጣ፤ ራሱንም በሰማያት ካሉት ፍጥረታት ጋር ያስተያይ ጀመር፡፡ ተፈጥሮን በማሸነፍ ማንነቱን ለማሳየትም ልቡ የበለጠ ተነሳሳ፤ ድንጋይ በድንጋይ እየደራረበ ራሱን ወደሰማይ ከፍ ያደርግ ጀመር፡፡ ከፍ አድርጐ በሠራው የድንጋይ ማማ ቁሞ መሬትን ቁልቁል ሲመለከታት እያነሰችበት መጣች፤ የእርሱ የበላይነት ግን ከሁሉ በልጦ ታየው፡፡
ከዚህ በመቀጠል ደግሞ መፅሀፍ ቅዱስ የሰው ልጅ ከህዋ አንፃር ያለውን ሁለት ምልከታ እናያለን...
ረ/ፕርፌሰር ዋለልኝ እምሩ
@zephilosophy
🔥19👍18❤7
2.መጽሐፍ ቅዱስ ከህዋ አንፃር የሰው ልጅ ምንድን ነው? በማለት ይጠይቃል?
“የጣቶችህን ሥራ ሰማዮችን ባየሁ ጊዜ፣
ጨረቃንና ከዋክብትን አንተ የሠራሃቸውን፣
ታስበው ዘንድ ሰው ምንድን ነው?
ትጐበኘውም ዘንድ የሰው ልጅ ምንድን ነው?”
በማለት መዝሙረኛው ንጉስ ዳዊት ይጠይቃል፡፡
መዝሙረኛው ያነሳው ጥያቄ የዚህ ምዕራፍ ርዕስ ጉዳይ ነው፡፡ ሰው ተፈጥሯዊ የሆነ የአጋጣሚ ክስተት ውጤት ነው ወይስ ታላቅ አላማ ለማሳካት የተፈጠረ ልዩ ፍጥረት? ሰው በተፈጥሮ ሂደት በአጋጣሚ የተገኘ ቢሆንና የፍጥረታት ሁሉ የበላይና የመጨረሻ ግብ ሁኖ ሊወሰድ ይችላልን? ከፀሐይና ከጨረቃ-ከህዋ-አንፃር ሲታይስ እዚህ ግባ የማይባል ተፈጥሯዊ ማንነት ያለው ከብናኝ አፈር፣ በእግራችን ረግጠን እንደምንገድላቸው ትናንሽ ነፍሳት አይነት የሆነ ተራ ፍጥረት ነውን ወይስ በህዋ ውስጥ ያሉትን ነገሮች እንደፍላጐቱ ማድረግ የሚችል ኃያል ፍጥረት? ህዋ ለሰው ጥቅምና መልካም ግልጋሎት ተብሎ የተፈጠረ ነገር ነውን ወይስ መጥፋያው? መጽሐፍ ቅዱስ ለእነዚህ አይነት ጥያቄዎች የሚሰጠው መልስ ሁለት አይነት ነው፡፡ በአንድ በኩል የሰውን ኃያልነት ሲያጐላ በሌላ በኩል ተራ ፍጥረት መሆኑን ይነግረናል፡፡ መለኮታዊ ማንነት ያለውና በፍጥረታት ሁሉ ላይ ገዥነቱን የሚነግረን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል እንዳለ ሁሉ በሌሎች ክፍሎች ደግሞ ሰውን አዋርዶና አቅልሎ ይነግረናል፡፡ የሰውን ልዩ ማንነትና ገዥነቱን መዝሙረኛው ዳዊት እንዲህ በማለት ይገልፀዋል፡፡
“ከመላዕክት እጅግ ጥቂት አሳነስኸው፣
በክብርና በምስጋና ዘውድ ከለልኸው፣
በእጆችህም ሥራ ሁሉ ላይ ሾምኸው፣
ሁሉን ከእግሮቹ በታች አስገዛህለት፣.."
ከጥቅሱ መረዳት እንደሚቻለው ሰው ከመላዕክት አንሶ የማያንስ በፍጥረታት ሁሉ ላይ ተሹሞ ዘውድ የደፋ ታላቅ ፍጥረት ነው፡፡ የሰው ታላቅነት ከአፈጣጠሩ ልዩ መሆን ይጀምራል፤ በእግዚአብሔር መልክ (በልጁ መልክ) የተፈጠረና የመለኮት ባህሪ ተካፋይ የሆነ ነው፡፡ በተቃራኒው ደግሞ መጽሐፍ ቅዱስ ለሰው ልጅ ሌላ ማንነት ይሰጠዋል፡፡ ከሌሎች ፍጥረታት የማይለይ ይባስ ብሎ ከሌሎች ፍጥረታት አሣንሶ ሰውን ይገልፀዋል፡፡ መጽሐፈ መክብብ እንዲህ ይላል፡፡
“እኔ በልቤ ስለሰው ልጆች እንደ እንስሳ መሆናቸውን እንዲያዩ እግዚአብሔር ይፈትናቸዋል አልሁ፡፡ የሰው ልጆችና የእንስሳ እድል ፈንታ አንድ ነው፣ ድርሻቸውም ትክክል ነው፡፡ አንዱ እንደሚሞት ሌላውም እንዲሁ ይሞታል፣ የሁለም እስትንፋስ አንድ ነው፣ ሁሉም ከንቱ ነውና ሰው ከእንስሳ ብልጫ የለውም፡፡”
መጽሐፈ ኢዮብ ደግሞ የሰውን ማንነት ከዚህ በባሰ መልኩ ይገልፀዋል፡፡
“እነሆ፣ ጨረቃ እንኳ ብሩህ አይደሉም፣
ክዋክብትም በፊቱ ንጹሀን አይደሉም፣
ይልቁንስ ብስብስ የሆነ ሰው
ትልም የሆነ የሰው ልጅ ምንኛ ያንስ፡፡”
ፍልስፍናስ ምን ይላል? ፍልስፍና ትኩረት ከሚሰጥባቸው ጉዳዮች አንዱና ዋናው የሰውና የህዋ ጉዳይ ነው፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ፍልስፍና ሰፋፊ፣ ጥልቀትና ብዛት ያላቸው አስተሳሰቦችን አቅርቧል። በቀጣይ እናያለን....
@zephilosophy
“የጣቶችህን ሥራ ሰማዮችን ባየሁ ጊዜ፣
ጨረቃንና ከዋክብትን አንተ የሠራሃቸውን፣
ታስበው ዘንድ ሰው ምንድን ነው?
ትጐበኘውም ዘንድ የሰው ልጅ ምንድን ነው?”
በማለት መዝሙረኛው ንጉስ ዳዊት ይጠይቃል፡፡
መዝሙረኛው ያነሳው ጥያቄ የዚህ ምዕራፍ ርዕስ ጉዳይ ነው፡፡ ሰው ተፈጥሯዊ የሆነ የአጋጣሚ ክስተት ውጤት ነው ወይስ ታላቅ አላማ ለማሳካት የተፈጠረ ልዩ ፍጥረት? ሰው በተፈጥሮ ሂደት በአጋጣሚ የተገኘ ቢሆንና የፍጥረታት ሁሉ የበላይና የመጨረሻ ግብ ሁኖ ሊወሰድ ይችላልን? ከፀሐይና ከጨረቃ-ከህዋ-አንፃር ሲታይስ እዚህ ግባ የማይባል ተፈጥሯዊ ማንነት ያለው ከብናኝ አፈር፣ በእግራችን ረግጠን እንደምንገድላቸው ትናንሽ ነፍሳት አይነት የሆነ ተራ ፍጥረት ነውን ወይስ በህዋ ውስጥ ያሉትን ነገሮች እንደፍላጐቱ ማድረግ የሚችል ኃያል ፍጥረት? ህዋ ለሰው ጥቅምና መልካም ግልጋሎት ተብሎ የተፈጠረ ነገር ነውን ወይስ መጥፋያው? መጽሐፍ ቅዱስ ለእነዚህ አይነት ጥያቄዎች የሚሰጠው መልስ ሁለት አይነት ነው፡፡ በአንድ በኩል የሰውን ኃያልነት ሲያጐላ በሌላ በኩል ተራ ፍጥረት መሆኑን ይነግረናል፡፡ መለኮታዊ ማንነት ያለውና በፍጥረታት ሁሉ ላይ ገዥነቱን የሚነግረን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል እንዳለ ሁሉ በሌሎች ክፍሎች ደግሞ ሰውን አዋርዶና አቅልሎ ይነግረናል፡፡ የሰውን ልዩ ማንነትና ገዥነቱን መዝሙረኛው ዳዊት እንዲህ በማለት ይገልፀዋል፡፡
“ከመላዕክት እጅግ ጥቂት አሳነስኸው፣
በክብርና በምስጋና ዘውድ ከለልኸው፣
በእጆችህም ሥራ ሁሉ ላይ ሾምኸው፣
ሁሉን ከእግሮቹ በታች አስገዛህለት፣.."
ከጥቅሱ መረዳት እንደሚቻለው ሰው ከመላዕክት አንሶ የማያንስ በፍጥረታት ሁሉ ላይ ተሹሞ ዘውድ የደፋ ታላቅ ፍጥረት ነው፡፡ የሰው ታላቅነት ከአፈጣጠሩ ልዩ መሆን ይጀምራል፤ በእግዚአብሔር መልክ (በልጁ መልክ) የተፈጠረና የመለኮት ባህሪ ተካፋይ የሆነ ነው፡፡ በተቃራኒው ደግሞ መጽሐፍ ቅዱስ ለሰው ልጅ ሌላ ማንነት ይሰጠዋል፡፡ ከሌሎች ፍጥረታት የማይለይ ይባስ ብሎ ከሌሎች ፍጥረታት አሣንሶ ሰውን ይገልፀዋል፡፡ መጽሐፈ መክብብ እንዲህ ይላል፡፡
“እኔ በልቤ ስለሰው ልጆች እንደ እንስሳ መሆናቸውን እንዲያዩ እግዚአብሔር ይፈትናቸዋል አልሁ፡፡ የሰው ልጆችና የእንስሳ እድል ፈንታ አንድ ነው፣ ድርሻቸውም ትክክል ነው፡፡ አንዱ እንደሚሞት ሌላውም እንዲሁ ይሞታል፣ የሁለም እስትንፋስ አንድ ነው፣ ሁሉም ከንቱ ነውና ሰው ከእንስሳ ብልጫ የለውም፡፡”
መጽሐፈ ኢዮብ ደግሞ የሰውን ማንነት ከዚህ በባሰ መልኩ ይገልፀዋል፡፡
“እነሆ፣ ጨረቃ እንኳ ብሩህ አይደሉም፣
ክዋክብትም በፊቱ ንጹሀን አይደሉም፣
ይልቁንስ ብስብስ የሆነ ሰው
ትልም የሆነ የሰው ልጅ ምንኛ ያንስ፡፡”
ፍልስፍናስ ምን ይላል? ፍልስፍና ትኩረት ከሚሰጥባቸው ጉዳዮች አንዱና ዋናው የሰውና የህዋ ጉዳይ ነው፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ፍልስፍና ሰፋፊ፣ ጥልቀትና ብዛት ያላቸው አስተሳሰቦችን አቅርቧል። በቀጣይ እናያለን....
@zephilosophy
👍40🤔7❤4👏1
ሰው ከህዋ አንፃር ያለው ቦታ እና ግንዛቤ በጥንታዊ እና በመካከላኛ ዘመን የነበሩ ፈላስፋዎች እይታ
ራሳቸውን ጥበበኞች እያሉ የሚጠሩ አንደበተኛና ጠርጣሪ (Sophist) ፈላስፋዎች እስከመጡበት ጊዜ የነበሩ ከቴለስ ጀምሮ የነበሩ ፈላስፋዎች ሰውን የተፈጥሮ አካል አድርገው ነው የተመለከቱት፤ ለሰው የተለዬ ማንነት አልሰጡትም፡፡ እንዲያውም ሰው የተፈጥሮ ህግ ተገዥና የበታች እንደሆነ ገልፀዋል፡፡
የዚህ አይነት አመለካከት በግሪክ ፈላስፋዎች ዘንድ የዘለቀው ራሳቸውን ጥበበኞች እያሉ የሚጠሩ አንደበታዊያን (Sophist) ፈላስፋዎች እስከመጡበት ጊዜ ድረስ ብቻ ነው፡፡ ከበፊተኞቹ ፈላስፋዎች በተቃራኒው አንደበታዊያን ፈላስፋዎች ሰው የተለዬ ማንነት ያለው መሆኑን በፍልስፍናቸው አበሠሩ፡፡ አንደበታዊያን ሰውን ከተፈጥሮ በመለየት የራሱን እጣፈንታ በራሱ መወሰን የሚችል ፍጥረት እንደሆነ ያምናሉ፡፡ ሰው ምን ያህል የተፈጥሮን ሥርዓት ሊያወቅና ሊቆጣጠር እንደሚችል ባይረዱትም ሰው ለራሱ ጥቅም ማስገኘት እስኪችል ድረስ ተፈጥሮን መቅረጽ ወይም መለወጥ እንደሚችል ያምናሉ፡፡
ፕሮታጐራስ የተባለው ታዋቂው አንደበታዊ ፈላስፋ “ለሁሉም ነገር ወሳኙ (ዳኛው) ሰው ነው- Man is the measure of everything” የሚል አባባል አለው፡፡ ይህ አባባል ሁለት ትርጉሞች አሉት፡፡ የመጀመሪያው እውነት ወይም ሀሰት፣ ጥሩ ወይም መጥፎ የምንላቸው ነገሮች እንደ ሰው እይታ ነው ማለት ነው፡፡ ሌላው ትርጉሙ በሁሉም ነገር ላይ መወሰን የሚችለው ሰው ነው፤ ከሰው በላይ የሆነ ምንም ነገር የለም ማለት ነው፡፡ ከሁሉም በላይ ማለት ከተፈጥሮም እንዲሁም ከአማልክትም በላይ ማለት ነው፡፡ በዚህ መልኩ በፍልስፍና ታሪክ ውስጥ ሰው የፍጥረታት ሁሉ ማዕከልና የበላይ የሆነ ክብር ለመጀመሪያ ጊዜ ያገኘው በአንደበታዊያን ፈላስፋዎች ነው፡፡
ከአንደበታዊያን በኋላ የመጡ እንደ ፕሌቶና አሪስቶትል ያሉ ፈላስፋዎች ከቁስ አካላትና ከህያዊያን ፍጥረታት ሁሉ በላይ የሚያደርገው በሰው ውስጥ የተለዬ ነገር አለ ብለው ያምናሉ፡፡ ሰው ተፈጥሮን ብቻ አይደለም ፍጹም የሆኑ ሃሳባዊያን ነገሮችን ጨምሮ መረዳት ይችላል፡፡ ይህ በሰው ዘንድ ያለ የተለዬ ነገር ነው፤ በዚህ የተለዬ ማንነት ሰው ከተፈጥሮ በላይ መሆን ብቻ ሣይሆን ከመለኰት ጋር ተመሣሣይ ያደርገዋል፡፡ ስለዚህ ሰው በግዙፉ ህሊና ቢስ ህዋ ውስጥ የሚሆነው ነገር ጠፍቶት የሚንገዋለል ፍጥረት ሣይሆን የተፈጥሮን ሥርዓት አሸንፎ ወደ መለኮት ራሱን ከፍ ከፍ የሚያደርግ ፍጥረት መሆኑን ፕሌቶና አሪስቶትል ያምናሉ፡፡
ከፕሌቶና አሪስቶትል በኋላ የመጡ ስቶይክ (Stoic) ፈላስፋዎች ደግሞ የተለዬ አመለካከት ነው ያላቸው፡፡ ለስቶይኮች ሰው የግዙፉ ህዋ ቅጅ ነው፡፡ በሰው ውስጥ ያለው በህዋ ውስጥ አስቀድሞ ያለው ነው፡፡ ሰው በህሊናው እንደሚመራው ሁሉ ተፈጥሮ በአጠቃላይ የሚመራው በስቶይኮች ቃል (logos) ብለው በሚጠሩት ህዋዊ ህሊና ነው፡፡ ሰው የሚኖረው ተፈጥሮ በሰጠችው ልክ በመሆኑ ተፈጥሮ እንዳደረገችው ሁኖ መኖር አለበት፡፡
ተፈጥሮ በህሊናዊ ኃይል ስለምትመራ ተፈጥሮን መቃወም ስህተት ነው፡፡ ይህ አመለካከት ሰውን ከተፈጥሮ በታች የሚያደርግ ብቻ ሣይሆን የሰው ህይወት አስቀድሞ የተወሰነና መቀየር የማይቻል መሆኑን ይሣየናል፡፡
የመካከለኛው ዘመን የነበሩ ክርስቲያን ፈላስፋዎች በመካከላቸው ልዩነት ይኑር እንጅ ዙሮ ዙሮ እግዚአብሔርን የህዋ ፈጣሪ መሆንና ሰውም የእግዚአብሔር ምርጡ የሥራ ውጤት መሆኑን ይስማሙበታል፡፡ ነገር ግን አካላዊ (ቁሳዊ) ማንነቱ ለሰው ጥቅም አልሰጠውም፤ ምኞትን፣ ሀጢዓትንና ሞትን አመጣበት፡፡ ሁለን ነገር በበላይነት ገዝቶ እንዲኖርበት የተሰጠው ዓለምም መከበሪያው ሣይሆን መቀበሪያው ሆነ፡፡ በመሆኑም አካላዊ (ቁሳዊ) ማንነቱና ምድራዊ ኑሮው አስፈላጊ አይደለም፤
ከሞት ነፃ ሁኖ የሚኖርበት ሌላ ማንነትና ሌላ ዓለም ያስፈልገዋል፡፡ ይህን ዓለም ሰው ንቆ መኖር አለበት፤ ይህ ዓለም ክብርና ዋጋ የሚሰጠው አይደለም፡፡ ጥቅም አለው ከተባለም ወደ ሌላኛው ዓለም ለመድረስ ለመሸጋገሪያነት ማገልገሉ ነው፡ ስለዚህ ሰው መሻት ያለበት እየኖረበት ያለውን ዓለም ሣይሆን ሌላኛውን (ከላይ) ያለውን ዓለም ነው፡፡
ዓለም ንቆ መኖር ካለበት በህዋ ላይ ሊጫወተው የሚችለው ሚናም ሆነ በህዋ የራሱን ቦታ ምን ሊሆን እንደሚችል ማወቅ አያስፈልገውም፡፡ ይህ አመለካከት ሰውንና ህዋን፣ ህሊና እና ቁስን መንፈስንና አካልን የሚለያይ ነው፡፡ ሰውን ከሚኖርበት ዓለም የሚለያይ አመለካከት ደግሞ ሰው በዚህ ዓለም ሊያደርግ የሚችለው ነገር ቢኖር እንኳ ጥቅም (ዋጋ) እንደሌለው ያመለክታል፡፡ ሰው ዓለምን ለመግዛት ቢፈጠርም የራሱን አካል እንኳ መግዛት ስለተሳነው በዚህ ዓለም ሊያገኝ የሚችለው ዘላለማዊ ክብርን አጥቶታል፡፡ ስለዚህ ሰው ማሰብ ያለበት ከሞት በኋላ ስለሚኖረው ህይወት እንጅ ከሞት በፊት ስላለው ሊሆን አይገባም፡፡
ዋናው ነገር ይህ ዓለም ለሰው መልካም እንዳይደለ መታመኑ ነው፡፡ ይህ ዓለም መጥፎና የሥቃይ ሁሉ ምክንያት ነው፡፡ የሐጢዓት ምክንያት በመሆኑ ይህ ዓለም ለሰው ልጅ ጠላቱ ነው፡፡ የላይኛው መንፈሳዊ ዓለም ግን የጽድቅና የዘላለም በረከት የሚገኝበት ነው፡፡ የመልካም ነገሮች ሁሉ መኖሪያ ቤትና የመለኮት ማረፊያ በመሆኑ የሰው ልጅ አላማ ሊሆን የሚገባው ቁሳዊ (ምድራዊ) ዓለምን መተውና መንፈሳዊ የሆነውን ዓለም ማግኘት ነው።
ዘመናዊ ፍልስፍና ስለ ህዋ ምን ይላል??
ረ/ፕርፌሰር ዋለልኝ እምሩ
@zephilosophy
@zephilosophy
ራሳቸውን ጥበበኞች እያሉ የሚጠሩ አንደበተኛና ጠርጣሪ (Sophist) ፈላስፋዎች እስከመጡበት ጊዜ የነበሩ ከቴለስ ጀምሮ የነበሩ ፈላስፋዎች ሰውን የተፈጥሮ አካል አድርገው ነው የተመለከቱት፤ ለሰው የተለዬ ማንነት አልሰጡትም፡፡ እንዲያውም ሰው የተፈጥሮ ህግ ተገዥና የበታች እንደሆነ ገልፀዋል፡፡
የዚህ አይነት አመለካከት በግሪክ ፈላስፋዎች ዘንድ የዘለቀው ራሳቸውን ጥበበኞች እያሉ የሚጠሩ አንደበታዊያን (Sophist) ፈላስፋዎች እስከመጡበት ጊዜ ድረስ ብቻ ነው፡፡ ከበፊተኞቹ ፈላስፋዎች በተቃራኒው አንደበታዊያን ፈላስፋዎች ሰው የተለዬ ማንነት ያለው መሆኑን በፍልስፍናቸው አበሠሩ፡፡ አንደበታዊያን ሰውን ከተፈጥሮ በመለየት የራሱን እጣፈንታ በራሱ መወሰን የሚችል ፍጥረት እንደሆነ ያምናሉ፡፡ ሰው ምን ያህል የተፈጥሮን ሥርዓት ሊያወቅና ሊቆጣጠር እንደሚችል ባይረዱትም ሰው ለራሱ ጥቅም ማስገኘት እስኪችል ድረስ ተፈጥሮን መቅረጽ ወይም መለወጥ እንደሚችል ያምናሉ፡፡
ፕሮታጐራስ የተባለው ታዋቂው አንደበታዊ ፈላስፋ “ለሁሉም ነገር ወሳኙ (ዳኛው) ሰው ነው- Man is the measure of everything” የሚል አባባል አለው፡፡ ይህ አባባል ሁለት ትርጉሞች አሉት፡፡ የመጀመሪያው እውነት ወይም ሀሰት፣ ጥሩ ወይም መጥፎ የምንላቸው ነገሮች እንደ ሰው እይታ ነው ማለት ነው፡፡ ሌላው ትርጉሙ በሁሉም ነገር ላይ መወሰን የሚችለው ሰው ነው፤ ከሰው በላይ የሆነ ምንም ነገር የለም ማለት ነው፡፡ ከሁሉም በላይ ማለት ከተፈጥሮም እንዲሁም ከአማልክትም በላይ ማለት ነው፡፡ በዚህ መልኩ በፍልስፍና ታሪክ ውስጥ ሰው የፍጥረታት ሁሉ ማዕከልና የበላይ የሆነ ክብር ለመጀመሪያ ጊዜ ያገኘው በአንደበታዊያን ፈላስፋዎች ነው፡፡
ከአንደበታዊያን በኋላ የመጡ እንደ ፕሌቶና አሪስቶትል ያሉ ፈላስፋዎች ከቁስ አካላትና ከህያዊያን ፍጥረታት ሁሉ በላይ የሚያደርገው በሰው ውስጥ የተለዬ ነገር አለ ብለው ያምናሉ፡፡ ሰው ተፈጥሮን ብቻ አይደለም ፍጹም የሆኑ ሃሳባዊያን ነገሮችን ጨምሮ መረዳት ይችላል፡፡ ይህ በሰው ዘንድ ያለ የተለዬ ነገር ነው፤ በዚህ የተለዬ ማንነት ሰው ከተፈጥሮ በላይ መሆን ብቻ ሣይሆን ከመለኰት ጋር ተመሣሣይ ያደርገዋል፡፡ ስለዚህ ሰው በግዙፉ ህሊና ቢስ ህዋ ውስጥ የሚሆነው ነገር ጠፍቶት የሚንገዋለል ፍጥረት ሣይሆን የተፈጥሮን ሥርዓት አሸንፎ ወደ መለኮት ራሱን ከፍ ከፍ የሚያደርግ ፍጥረት መሆኑን ፕሌቶና አሪስቶትል ያምናሉ፡፡
ከፕሌቶና አሪስቶትል በኋላ የመጡ ስቶይክ (Stoic) ፈላስፋዎች ደግሞ የተለዬ አመለካከት ነው ያላቸው፡፡ ለስቶይኮች ሰው የግዙፉ ህዋ ቅጅ ነው፡፡ በሰው ውስጥ ያለው በህዋ ውስጥ አስቀድሞ ያለው ነው፡፡ ሰው በህሊናው እንደሚመራው ሁሉ ተፈጥሮ በአጠቃላይ የሚመራው በስቶይኮች ቃል (logos) ብለው በሚጠሩት ህዋዊ ህሊና ነው፡፡ ሰው የሚኖረው ተፈጥሮ በሰጠችው ልክ በመሆኑ ተፈጥሮ እንዳደረገችው ሁኖ መኖር አለበት፡፡
ተፈጥሮ በህሊናዊ ኃይል ስለምትመራ ተፈጥሮን መቃወም ስህተት ነው፡፡ ይህ አመለካከት ሰውን ከተፈጥሮ በታች የሚያደርግ ብቻ ሣይሆን የሰው ህይወት አስቀድሞ የተወሰነና መቀየር የማይቻል መሆኑን ይሣየናል፡፡
የመካከለኛው ዘመን የነበሩ ክርስቲያን ፈላስፋዎች በመካከላቸው ልዩነት ይኑር እንጅ ዙሮ ዙሮ እግዚአብሔርን የህዋ ፈጣሪ መሆንና ሰውም የእግዚአብሔር ምርጡ የሥራ ውጤት መሆኑን ይስማሙበታል፡፡ ነገር ግን አካላዊ (ቁሳዊ) ማንነቱ ለሰው ጥቅም አልሰጠውም፤ ምኞትን፣ ሀጢዓትንና ሞትን አመጣበት፡፡ ሁለን ነገር በበላይነት ገዝቶ እንዲኖርበት የተሰጠው ዓለምም መከበሪያው ሣይሆን መቀበሪያው ሆነ፡፡ በመሆኑም አካላዊ (ቁሳዊ) ማንነቱና ምድራዊ ኑሮው አስፈላጊ አይደለም፤
ከሞት ነፃ ሁኖ የሚኖርበት ሌላ ማንነትና ሌላ ዓለም ያስፈልገዋል፡፡ ይህን ዓለም ሰው ንቆ መኖር አለበት፤ ይህ ዓለም ክብርና ዋጋ የሚሰጠው አይደለም፡፡ ጥቅም አለው ከተባለም ወደ ሌላኛው ዓለም ለመድረስ ለመሸጋገሪያነት ማገልገሉ ነው፡ ስለዚህ ሰው መሻት ያለበት እየኖረበት ያለውን ዓለም ሣይሆን ሌላኛውን (ከላይ) ያለውን ዓለም ነው፡፡
ዓለም ንቆ መኖር ካለበት በህዋ ላይ ሊጫወተው የሚችለው ሚናም ሆነ በህዋ የራሱን ቦታ ምን ሊሆን እንደሚችል ማወቅ አያስፈልገውም፡፡ ይህ አመለካከት ሰውንና ህዋን፣ ህሊና እና ቁስን መንፈስንና አካልን የሚለያይ ነው፡፡ ሰውን ከሚኖርበት ዓለም የሚለያይ አመለካከት ደግሞ ሰው በዚህ ዓለም ሊያደርግ የሚችለው ነገር ቢኖር እንኳ ጥቅም (ዋጋ) እንደሌለው ያመለክታል፡፡ ሰው ዓለምን ለመግዛት ቢፈጠርም የራሱን አካል እንኳ መግዛት ስለተሳነው በዚህ ዓለም ሊያገኝ የሚችለው ዘላለማዊ ክብርን አጥቶታል፡፡ ስለዚህ ሰው ማሰብ ያለበት ከሞት በኋላ ስለሚኖረው ህይወት እንጅ ከሞት በፊት ስላለው ሊሆን አይገባም፡፡
ዋናው ነገር ይህ ዓለም ለሰው መልካም እንዳይደለ መታመኑ ነው፡፡ ይህ ዓለም መጥፎና የሥቃይ ሁሉ ምክንያት ነው፡፡ የሐጢዓት ምክንያት በመሆኑ ይህ ዓለም ለሰው ልጅ ጠላቱ ነው፡፡ የላይኛው መንፈሳዊ ዓለም ግን የጽድቅና የዘላለም በረከት የሚገኝበት ነው፡፡ የመልካም ነገሮች ሁሉ መኖሪያ ቤትና የመለኮት ማረፊያ በመሆኑ የሰው ልጅ አላማ ሊሆን የሚገባው ቁሳዊ (ምድራዊ) ዓለምን መተውና መንፈሳዊ የሆነውን ዓለም ማግኘት ነው።
ዘመናዊ ፍልስፍና ስለ ህዋ ምን ይላል??
ረ/ፕርፌሰር ዋለልኝ እምሩ
@zephilosophy
@zephilosophy
👍49❤2🔥1
5.የህዋ ግንዛቤ በዘመናዊ ፍልስፍና ታሪክ ውስጥ
የህዳሴውን ዘመንን ተከትሎ በሣይንሱም ሆነ በፍልስፍናው ብዙ አይነት አስተሳሰቦችና ትምህርቶች ይራመዱ ጀመር፡፡
ፍልስፍና “የሰውን ህይወት እጣፈንታ የሚወስን ኃይል አለ” ከሚል እምነት በመላቀቅ ሰው የራሱን ህይወት በራሱ ፈቃድና እውቀት መምራት ይችላል ወደሚል እምነት ተሸጋገረ፡፡
በመካከለኛው ዘመን ሰው ተስፋውን በአምላክ ጥሎ የራሱን ማንነት ረስቶ ነበር፡፡ በዚያ ዘመን ሰው ስለራሱ ማንነት ያንቀላፋበት ጊዜ ነበር፡፡ ከህዳሴው ዘመን ጀምሮ ግን ሰው ለረጅም ዘመን ከአንቀላፋበት ነቃ - ራሱን ማስተዋል ጀመረ፡፡ ወደራሱ በተመለከተ ቁጥር በሌላ ኃይል ከመተማመን ይልቅ የራሱ ኃይል ከምንም ነገር በላይ ሊያደርገው እንደሚችል አሰበ፡፡ በሳይንሳዊ እውቀት ምስጢሩን የተረዳውን ተፈጥሯዊ ሥርዓት በራሱ አቅም መግዛትና ለራሱ ጥቅም ማዋል እንደሚችል ድፍሩቱን ማሳየት ጀመረ፡፡
ይህ የህዳሴው ዘመን መንፈስ ነበር - በራሱ የመተማመን መንፈስ! የህዳሴው ዘመን ፍልስፍና የዘመናዊ ፍልስፍና መግቢያ በር ነው፡፡ ሙሉ ትኩረት የሰጠውም የሰው ልጅ ተፈጥሮን የመለወጥ አቅም ላይ ነበር፡፡ በዚህ ምክንያት የህዳሴው ዘመን ፍልስፍና ሰባዊነት - Humanism የሚል መጠሪያ አገኘ፡፡ እንደ ሉዶቪቾ ቫይቪስ (Ludovico Vives) ፣ ፔትሪስ ራመስ (Petrus Ramus) እና በርናርዲኖ ቴሎሶ (Bernardino Telesio) የመሳሰሉት ሰባዊ አስተሳሰብን በቀደምትነት ያራመዱ ፈላስፋዎች ናቸው፡፡ እነዚህ ፈላስፋዎች የሰው ልጅ አጋዥ ሣያስፈልገው በራሱ አቅም የተፈጥሮን ኃይል ቀልብሶ ራሱን የበላይ አድርጐ መኖር ይችላል የሚል ከፍተኛ እምነት ነበራቸው፡፡ በዚህ አቋማቸው ሰውን አቅመ - ቢስ ያደረጉ እምነቶች ላይ አመጽ የጀመሩ ፈላስፋዎች ለመሆን ቻሉ፡፡ ሳይንስ ያመጣውን መነቃቃት ተከትሎ ሰባዊያን ያመጡት ፍልስፍና ለጨለማው ዘመን ማብቂያና የብርሃን ዘመን መምጣት የተበሠረበት ፍልስፍና ለመሆን ቻለ፡፡
ሳይንስ በፈጠረላቸው መደላድል ላይ ተመሥርተው ፍራንሲስ ቤከንና ቶማስ ሆብስ የተባሉ ፈላስፋዎች ሰው ከህዋ ጋር ያለውን ግንኙነት በእውቀት ላይ የተመሠረተ ሊሆን እንደሚገባው በማስገንዘብ የተፈጥሮን እንቅስቃሴና አጠቃላይ ሥርዐተ - ህጉን ማወቅ የሰው ልጅ ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡በተለይ ለሆብስ የተፈጥሮ ህግ መታወቅ ከተቻለ ሰው ህጉን እንደፈቃዱ እያስተካከለ መኖር እንደሚችል እምነቱን ገለፀ፡፡
እነ ቶማስ ሆብስ ሁሉን ነገር ቁሳዊ አደረጉት፡፡ ህሊና-ሀሳብ - በእንቅስቃሴ ላይ ያለ ቁስ ነው፤ እግዚአብሔርም ቢሆን ቁስአካላዊ ነው፤ መንፈሳዊ የሚባል ነገር የለም የሚል እምነት ማራመድ ጀመሩ፡፡
በእንደዚህ አይነት አመለካከቶች ተጋግሎ የነበረው የሰባዊነት ፍልስፍና ሳይታሰብ መቀዝቀዝ ጀመረ፡፡
ለምን ??? ይቀጥላል..
@zephilosophy
የህዳሴውን ዘመንን ተከትሎ በሣይንሱም ሆነ በፍልስፍናው ብዙ አይነት አስተሳሰቦችና ትምህርቶች ይራመዱ ጀመር፡፡
ፍልስፍና “የሰውን ህይወት እጣፈንታ የሚወስን ኃይል አለ” ከሚል እምነት በመላቀቅ ሰው የራሱን ህይወት በራሱ ፈቃድና እውቀት መምራት ይችላል ወደሚል እምነት ተሸጋገረ፡፡
በመካከለኛው ዘመን ሰው ተስፋውን በአምላክ ጥሎ የራሱን ማንነት ረስቶ ነበር፡፡ በዚያ ዘመን ሰው ስለራሱ ማንነት ያንቀላፋበት ጊዜ ነበር፡፡ ከህዳሴው ዘመን ጀምሮ ግን ሰው ለረጅም ዘመን ከአንቀላፋበት ነቃ - ራሱን ማስተዋል ጀመረ፡፡ ወደራሱ በተመለከተ ቁጥር በሌላ ኃይል ከመተማመን ይልቅ የራሱ ኃይል ከምንም ነገር በላይ ሊያደርገው እንደሚችል አሰበ፡፡ በሳይንሳዊ እውቀት ምስጢሩን የተረዳውን ተፈጥሯዊ ሥርዓት በራሱ አቅም መግዛትና ለራሱ ጥቅም ማዋል እንደሚችል ድፍሩቱን ማሳየት ጀመረ፡፡
ይህ የህዳሴው ዘመን መንፈስ ነበር - በራሱ የመተማመን መንፈስ! የህዳሴው ዘመን ፍልስፍና የዘመናዊ ፍልስፍና መግቢያ በር ነው፡፡ ሙሉ ትኩረት የሰጠውም የሰው ልጅ ተፈጥሮን የመለወጥ አቅም ላይ ነበር፡፡ በዚህ ምክንያት የህዳሴው ዘመን ፍልስፍና ሰባዊነት - Humanism የሚል መጠሪያ አገኘ፡፡ እንደ ሉዶቪቾ ቫይቪስ (Ludovico Vives) ፣ ፔትሪስ ራመስ (Petrus Ramus) እና በርናርዲኖ ቴሎሶ (Bernardino Telesio) የመሳሰሉት ሰባዊ አስተሳሰብን በቀደምትነት ያራመዱ ፈላስፋዎች ናቸው፡፡ እነዚህ ፈላስፋዎች የሰው ልጅ አጋዥ ሣያስፈልገው በራሱ አቅም የተፈጥሮን ኃይል ቀልብሶ ራሱን የበላይ አድርጐ መኖር ይችላል የሚል ከፍተኛ እምነት ነበራቸው፡፡ በዚህ አቋማቸው ሰውን አቅመ - ቢስ ያደረጉ እምነቶች ላይ አመጽ የጀመሩ ፈላስፋዎች ለመሆን ቻሉ፡፡ ሳይንስ ያመጣውን መነቃቃት ተከትሎ ሰባዊያን ያመጡት ፍልስፍና ለጨለማው ዘመን ማብቂያና የብርሃን ዘመን መምጣት የተበሠረበት ፍልስፍና ለመሆን ቻለ፡፡
ሳይንስ በፈጠረላቸው መደላድል ላይ ተመሥርተው ፍራንሲስ ቤከንና ቶማስ ሆብስ የተባሉ ፈላስፋዎች ሰው ከህዋ ጋር ያለውን ግንኙነት በእውቀት ላይ የተመሠረተ ሊሆን እንደሚገባው በማስገንዘብ የተፈጥሮን እንቅስቃሴና አጠቃላይ ሥርዐተ - ህጉን ማወቅ የሰው ልጅ ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡በተለይ ለሆብስ የተፈጥሮ ህግ መታወቅ ከተቻለ ሰው ህጉን እንደፈቃዱ እያስተካከለ መኖር እንደሚችል እምነቱን ገለፀ፡፡
እነ ቶማስ ሆብስ ሁሉን ነገር ቁሳዊ አደረጉት፡፡ ህሊና-ሀሳብ - በእንቅስቃሴ ላይ ያለ ቁስ ነው፤ እግዚአብሔርም ቢሆን ቁስአካላዊ ነው፤ መንፈሳዊ የሚባል ነገር የለም የሚል እምነት ማራመድ ጀመሩ፡፡
በእንደዚህ አይነት አመለካከቶች ተጋግሎ የነበረው የሰባዊነት ፍልስፍና ሳይታሰብ መቀዝቀዝ ጀመረ፡፡
ለምን ??? ይቀጥላል..
@zephilosophy
👍27❤4🎄1
የዘመናዊ ፍልስፍና ሙግቶች
የቀጠለ
....የዳሳሽነት (empiricism) ፍልስፍናን ያራመዱ የብሪታንያ ፈላስፋዎች ሰውን የሁሉ ነገር ማዕከል አድርገው የተረዱ ቢሆንም ከሰው አሳቤ ውጭ ህዋ የራሱ የሆነ ህልውና የለውም በማለት ህዋንና ሰውን ያስተሳሰረውን ገመድ ቆርጠው ጣሉት፡፡ በርክሌይ የተባለው ፈላስፋ ቁሳዊ ነገሮች ከሰው ህሳቤ ውጭ ህልውና የላቸውም ማለቱና የስሜት ህዋሳቶች መረጃዎች መገኛቸው ቁሳዊ ነገሮች ሣይሆኑ እግዚአብሔር ነው ማለቱ የሳይንስን መሠረት የሆነውንና ሰው ማንነቱ ሊገለጽበት የሚችለው ቁስ አካል ከንቱ (ዋጋ የሌለው) ነገር ሁኖ እነዲታሰብ አደረገው፡፡ ይባስ ብሎ ዴቭድ ሂዩም የሰው ልጅ የስሜቶችና የሀሳቦች መንሸራሸሪያ መንገድ ከመሆን ውጭ ሌላ ማንነት የለውም፤ የህዋን (የቁስ አካላት) ህልውናንም ማረጋገጥ አይቻልም በማለቱ በፍልስፍና ተሟሙቆ የነበረው የሰውን ኃያልነት የማሳየት አስተሳሰብ ላይ ቀዝቃዛ ውሃ ቸለሰበት፡፡
ሌሎች ደግሞ የህዋን ህልውና ሙሉ በሙሉ ሀሳባዊ አደረጉት፡፡ እንጀ ሜልብራንች ያሉ ፈላስፋዎች (Malebranche) እኛ የምናውቀው እግዚአብሔር የገለፀልንን ነው፤ እርሱ ከሰጠን ሃሳብ ውጭ ምንም የምናውቀው ነገር የለም የሚል እምነት ያዙ፡፡ ሜልብራንች ሲናገር “እግዚአብሔር ዓለምን ቢያጠፋና አሁን እንዲሰማኝ እንዳዳረገኝ ወደፊትም እንዲሰማኝ ቢያደረገኝ ወደፊት የማየው አሁን የማየውን ነው፡፡” በሌላ አገላለጽ ይህ ማለት “እግዚአብሔር ዓለምን ቢያጠፋ ነገር ግን ልክ አሁን እንደሚሰማኝ (እንዳልጠፋች አድርጐ እንዳስብ ቢያደርገኝ) የማስበው ወይም የምረዳው መጥፋቷን ሣይሆን መኖሯን ነው፡፡የሚል ራሱን ሙሉ በሙሉ የእግዚአብሔር ሀሳብ ብቻ እንደሆነ አድርጐ እንዲያስብ የሚያስችል አመለካከት ያራምድ ነበር።
በዘመናዊ ፍልስፍና የታዩ አንዳንድ ፈላስፋዎች ደግሞ ከጊዜው ነባራዊ ሁኔታ ውጭ ሆነውና የሣይንስን መንገድ ስተው የሰውን ልጅ ወደ ጥንታዊ ኑሮው ለመመለስ የሚከጅል ሀሳብ ማራመድ ጀመሩ፡፡ ለዚህ ጥሩ ማሳያ የሚሆነው የዣን -ዣክ ሩሶ (Rousseau) ፍልስፍና ነው፡፡ ሩሶ እንደሚለው ሣይንስ የተፈጥሮ ህግ እውቀት ነው፤ ሳይንስ የሰውን ልጅ ኑሮ ይምራ ማለት ሰው በህግ ይመራ ማለት ነው፡፡ ሳይንስ ሰውን በህግ አስሮ መያዝ ይፈልጋል፡፡ ሰው ግን እንደፈቃዱና ስሜቱ መኖር የሚሻ ፍጥረት ነው፡፡ ሳይንስና ሳይንስ ያመጣቸው ስልጣኔዎች ግን የሰውን ልጅ ነፃነት የሚጋፉ በመሆናቸው አያስፈልጉም የሚል እምነት ማራመድ ጀመረ፡፡
ከላይ የተመለከትናቸውን ፍልስፍናዎች አጠቃለን ስናያቸው ዘመናዊ ፍልስፍና መስመር ይዞ መራመድና ወጥ የሆነ አቋም መያዝ እንደተሳነው መረዳት እንችላለን፡፡ በአንድ በኩል የሰውን ልጅ የበላይ አድርጐ ሲመለከት በሌላ በኩል ደግሞ እግዚአብሔርን በሰው ዘር ህሊና ላይ ይሾማል፤ አንዳንዴ ደግሞ ሰው ስለራሱም ሆነ ስለሚኖርበት ዓለም እንዲጠራጠር ሲያደርግ በሌላ በኩል ደግሞ ሰውን የራሱ የሥራ ውጤት ከሆነው ሥልጣኔ አርቆ ተፈጥሯዊ ኑሮ ብቻ መኖር ወደ ሚችልበት ወደ ተፈጥሮአዊነት ኑሮ መመለስ ይሻለዋል የሚል ሙግት ውስጥ ገባ፡፡
ኢማኑየል ካንት እንደብሪታንያ ፈላስፋዎች ሁሉ ሰው የሚረዳው የራሱን ሃሳብ ነው የሚል እምነት ቢኖረውም በምክንያታዊ አስተሳሰብ ሰው ከራሱ ውጭ የሆነ ቁሳዊ ዓለም መኖሩን፣ የእግዚአብሔርን ህልውናም ሆነ ዘላለማዊነት እና ነፃነት አለ ብሎ እንዲያምን አስችሎታል በማለት አሣወቀ፡፡ እነዚህ እምነቶች ደግሞ ተግባራዊ የሆነ ሥነ ምግባራዊ ኑሮና ሌላም አይነት ማኀበራዊ ህይወት እንዲኖርና ራሱንም ከተፈጥሮ በላይ አድርጐ እንዲያስብ አስችሎታል የሚል መደምደሚያ ሃሳብ ላይ ደረሰ፡፡ ይህን የመሰለው የካንት አስተሳሰብ በተወሰነ ደረጃም ቢሆን የሰውን በህዋ ላይ ያለውን የበላይነትና ክብር የመመለስ አስተሳሰብ ሁኖ ተወሰደ፡፡
በካንት መጫሚያ እግራቸውን ያስገቡ ሌሎች የጀርመን ፈላስፋዎች የሰውን ልጅ በህዋ ውስጥ ያለው መንፈሳዊና ህሊናዊ ኃይል ወራሽ በማድረግ ከቁስ አካላትና ከሌሎችም ፍጥረታት ሁሉ በላይ የሆነ ማንነት ያለው መሆኑን የሚያመለክት ጥልቅና ረቂቅ የሆነ ሀሳባዊ ፍልስፍና አቀረቡ፡፡ ካንትን ተከትለው የመጡ እንደ ሩዶልፍ ኸርማን ሎዝ፣ ሼልንግና ሄግል አይነት ፈላስፋዎች ህዋና ሰውን በአንድ አይናቸው የተመለከቱ ፈላስፋዎች ናቸው፡፡ ህዋ ለእነዚህ ፈላስፋዎች ህያው ነው፤ ህሊናዊ ነው፤ ሁልጊዜ ከፍ ወዳለ ደረጃ ለመሸጋገር የሚንቀሳቀስ ነገር ነው፡፡ በዚህ ህሊናዊ የለውጥ ሂደት ህዋ የራሱን የመጨረሻ የዕድገት ደረጃ የደረሰው በሰው ነው፡፡ ህዋ ሙሉ የሚሆነውና ራሱን የሚያውቀው በሰው ነው፡፡ ለእነዚህ ፈላስፋዎች ሰው ማለት ትንሽ ህዋ ነው፡፡
ከብዙ ፍልስፍና ሀሳቦች በጥቂቱ ስንቃኘው የህዋና የሰው ግንኙነት በፈላስፋዎች ዘንድ ይኼን የመሰለ አስተሳሰብ ፈጥሯል፡፡ በእኛም ላይ የሚፈጥረው ተጽዕኖ ቀላል አይሆንም፡፡ በህዋ ውስጥ ሰው ያለው ቦታ ለመወሰንና በሰውና በህዋ መካከል ያለውን ግንኙነት በተመለከተ ከውዝግብ የፀዳና የማያሻማ መልስ ማግኘት ባንችልም ርዕሰ ጉዳዩን ከተለያዩ አቅጣጫዎች ሰፋ አድርገን እንድንመለከተው የሚያስችል ሃሳቦችን አግኝተናል ።
ረ/ፕርፌሰር ዋለልኝ እምሩ
@zephilosophy
@zephilosophy
የቀጠለ
....የዳሳሽነት (empiricism) ፍልስፍናን ያራመዱ የብሪታንያ ፈላስፋዎች ሰውን የሁሉ ነገር ማዕከል አድርገው የተረዱ ቢሆንም ከሰው አሳቤ ውጭ ህዋ የራሱ የሆነ ህልውና የለውም በማለት ህዋንና ሰውን ያስተሳሰረውን ገመድ ቆርጠው ጣሉት፡፡ በርክሌይ የተባለው ፈላስፋ ቁሳዊ ነገሮች ከሰው ህሳቤ ውጭ ህልውና የላቸውም ማለቱና የስሜት ህዋሳቶች መረጃዎች መገኛቸው ቁሳዊ ነገሮች ሣይሆኑ እግዚአብሔር ነው ማለቱ የሳይንስን መሠረት የሆነውንና ሰው ማንነቱ ሊገለጽበት የሚችለው ቁስ አካል ከንቱ (ዋጋ የሌለው) ነገር ሁኖ እነዲታሰብ አደረገው፡፡ ይባስ ብሎ ዴቭድ ሂዩም የሰው ልጅ የስሜቶችና የሀሳቦች መንሸራሸሪያ መንገድ ከመሆን ውጭ ሌላ ማንነት የለውም፤ የህዋን (የቁስ አካላት) ህልውናንም ማረጋገጥ አይቻልም በማለቱ በፍልስፍና ተሟሙቆ የነበረው የሰውን ኃያልነት የማሳየት አስተሳሰብ ላይ ቀዝቃዛ ውሃ ቸለሰበት፡፡
ሌሎች ደግሞ የህዋን ህልውና ሙሉ በሙሉ ሀሳባዊ አደረጉት፡፡ እንጀ ሜልብራንች ያሉ ፈላስፋዎች (Malebranche) እኛ የምናውቀው እግዚአብሔር የገለፀልንን ነው፤ እርሱ ከሰጠን ሃሳብ ውጭ ምንም የምናውቀው ነገር የለም የሚል እምነት ያዙ፡፡ ሜልብራንች ሲናገር “እግዚአብሔር ዓለምን ቢያጠፋና አሁን እንዲሰማኝ እንዳዳረገኝ ወደፊትም እንዲሰማኝ ቢያደረገኝ ወደፊት የማየው አሁን የማየውን ነው፡፡” በሌላ አገላለጽ ይህ ማለት “እግዚአብሔር ዓለምን ቢያጠፋ ነገር ግን ልክ አሁን እንደሚሰማኝ (እንዳልጠፋች አድርጐ እንዳስብ ቢያደርገኝ) የማስበው ወይም የምረዳው መጥፋቷን ሣይሆን መኖሯን ነው፡፡የሚል ራሱን ሙሉ በሙሉ የእግዚአብሔር ሀሳብ ብቻ እንደሆነ አድርጐ እንዲያስብ የሚያስችል አመለካከት ያራምድ ነበር።
በዘመናዊ ፍልስፍና የታዩ አንዳንድ ፈላስፋዎች ደግሞ ከጊዜው ነባራዊ ሁኔታ ውጭ ሆነውና የሣይንስን መንገድ ስተው የሰውን ልጅ ወደ ጥንታዊ ኑሮው ለመመለስ የሚከጅል ሀሳብ ማራመድ ጀመሩ፡፡ ለዚህ ጥሩ ማሳያ የሚሆነው የዣን -ዣክ ሩሶ (Rousseau) ፍልስፍና ነው፡፡ ሩሶ እንደሚለው ሣይንስ የተፈጥሮ ህግ እውቀት ነው፤ ሳይንስ የሰውን ልጅ ኑሮ ይምራ ማለት ሰው በህግ ይመራ ማለት ነው፡፡ ሳይንስ ሰውን በህግ አስሮ መያዝ ይፈልጋል፡፡ ሰው ግን እንደፈቃዱና ስሜቱ መኖር የሚሻ ፍጥረት ነው፡፡ ሳይንስና ሳይንስ ያመጣቸው ስልጣኔዎች ግን የሰውን ልጅ ነፃነት የሚጋፉ በመሆናቸው አያስፈልጉም የሚል እምነት ማራመድ ጀመረ፡፡
ከላይ የተመለከትናቸውን ፍልስፍናዎች አጠቃለን ስናያቸው ዘመናዊ ፍልስፍና መስመር ይዞ መራመድና ወጥ የሆነ አቋም መያዝ እንደተሳነው መረዳት እንችላለን፡፡ በአንድ በኩል የሰውን ልጅ የበላይ አድርጐ ሲመለከት በሌላ በኩል ደግሞ እግዚአብሔርን በሰው ዘር ህሊና ላይ ይሾማል፤ አንዳንዴ ደግሞ ሰው ስለራሱም ሆነ ስለሚኖርበት ዓለም እንዲጠራጠር ሲያደርግ በሌላ በኩል ደግሞ ሰውን የራሱ የሥራ ውጤት ከሆነው ሥልጣኔ አርቆ ተፈጥሯዊ ኑሮ ብቻ መኖር ወደ ሚችልበት ወደ ተፈጥሮአዊነት ኑሮ መመለስ ይሻለዋል የሚል ሙግት ውስጥ ገባ፡፡
ኢማኑየል ካንት እንደብሪታንያ ፈላስፋዎች ሁሉ ሰው የሚረዳው የራሱን ሃሳብ ነው የሚል እምነት ቢኖረውም በምክንያታዊ አስተሳሰብ ሰው ከራሱ ውጭ የሆነ ቁሳዊ ዓለም መኖሩን፣ የእግዚአብሔርን ህልውናም ሆነ ዘላለማዊነት እና ነፃነት አለ ብሎ እንዲያምን አስችሎታል በማለት አሣወቀ፡፡ እነዚህ እምነቶች ደግሞ ተግባራዊ የሆነ ሥነ ምግባራዊ ኑሮና ሌላም አይነት ማኀበራዊ ህይወት እንዲኖርና ራሱንም ከተፈጥሮ በላይ አድርጐ እንዲያስብ አስችሎታል የሚል መደምደሚያ ሃሳብ ላይ ደረሰ፡፡ ይህን የመሰለው የካንት አስተሳሰብ በተወሰነ ደረጃም ቢሆን የሰውን በህዋ ላይ ያለውን የበላይነትና ክብር የመመለስ አስተሳሰብ ሁኖ ተወሰደ፡፡
በካንት መጫሚያ እግራቸውን ያስገቡ ሌሎች የጀርመን ፈላስፋዎች የሰውን ልጅ በህዋ ውስጥ ያለው መንፈሳዊና ህሊናዊ ኃይል ወራሽ በማድረግ ከቁስ አካላትና ከሌሎችም ፍጥረታት ሁሉ በላይ የሆነ ማንነት ያለው መሆኑን የሚያመለክት ጥልቅና ረቂቅ የሆነ ሀሳባዊ ፍልስፍና አቀረቡ፡፡ ካንትን ተከትለው የመጡ እንደ ሩዶልፍ ኸርማን ሎዝ፣ ሼልንግና ሄግል አይነት ፈላስፋዎች ህዋና ሰውን በአንድ አይናቸው የተመለከቱ ፈላስፋዎች ናቸው፡፡ ህዋ ለእነዚህ ፈላስፋዎች ህያው ነው፤ ህሊናዊ ነው፤ ሁልጊዜ ከፍ ወዳለ ደረጃ ለመሸጋገር የሚንቀሳቀስ ነገር ነው፡፡ በዚህ ህሊናዊ የለውጥ ሂደት ህዋ የራሱን የመጨረሻ የዕድገት ደረጃ የደረሰው በሰው ነው፡፡ ህዋ ሙሉ የሚሆነውና ራሱን የሚያውቀው በሰው ነው፡፡ ለእነዚህ ፈላስፋዎች ሰው ማለት ትንሽ ህዋ ነው፡፡
ከብዙ ፍልስፍና ሀሳቦች በጥቂቱ ስንቃኘው የህዋና የሰው ግንኙነት በፈላስፋዎች ዘንድ ይኼን የመሰለ አስተሳሰብ ፈጥሯል፡፡ በእኛም ላይ የሚፈጥረው ተጽዕኖ ቀላል አይሆንም፡፡ በህዋ ውስጥ ሰው ያለው ቦታ ለመወሰንና በሰውና በህዋ መካከል ያለውን ግንኙነት በተመለከተ ከውዝግብ የፀዳና የማያሻማ መልስ ማግኘት ባንችልም ርዕሰ ጉዳዩን ከተለያዩ አቅጣጫዎች ሰፋ አድርገን እንድንመለከተው የሚያስችል ሃሳቦችን አግኝተናል ።
ረ/ፕርፌሰር ዋለልኝ እምሩ
@zephilosophy
@zephilosophy
👍38👏10❤6
ብቸኛው ባለቅኔ
ካህሊል ጂብራን
ለጋስነት በልቤ ውስጥ ተዘርታለች። ክምር ስንዴ አመረትኩ ፤ ለተራቡም አካፈልኩ። ነብሴ ለወይን ፍሬ ትሰጣለች፡፡ ወይኑን ጨምቄ ለተጠሙ አጠጣሁ። ፋኖሴን ዘይት ሞልቼ መስኮቴ ጋር አኖርኩኝ። በጭለማ ለሚጓዙ እንግዶች መንገዱን አበራሁ፡፡ ይህንን ሁሉ የማደርገው በእነዚህ ድርጊቶቼ ውስጥ ስለምኖር ነው። የሕይወት እጣ ለጋስ እጆቼን ብታስርበኝ ሞትን እመርጣለሁ። ገጣሚ ነኝና መለገስ ካልቻልኩ ፈፅሞ አልቀበልም። የሰው ልጅ ቁጣ እንደ አውሎ ነፋስ ያጓራል። እኔ ግን በዝምታ እተነፍሳለሁ፡፡ ምክንያቱም ትንፋሼ ፈጣሪ ጋር ሲደርስ ወጀቡ በሙሉ ይቆማልና። ሰዎች ምድራዊ ነገሮች ላይ ይንጠለጠላሉ፡፡ የኔ መሻት ግን የፍቅር ችቦ ናት። በብርሃኗ የልቤን ሰብአዊነት ታነፃልኛለች፡፡ ሰዎች በዘር ፣ በቀለም በሃይማኖት ተከፋፍለዋል። እኔ ደግሞ በሁሉም አገር እንግዳ ነኝ – የየትኛውም ወገን አይደለሁም፡፡ ሥነ-ፍጥረት (ዩኒቨርስ) አገሬ ስትሆን ጉሳዬ ደግሞ ሁሉም የሰው ልጅ ነው፡፡ የሰው ልጅ አቅመቢስ ሆነውም የተከፋፈሉ ናቸው። በየጊዜው የምትጠበውን ምድር በግዛትና አገራት መሰነጣጠቅ አላዋቂነት ነው። የሰው ልጆች እጅ ለእጅ የሚያያዙት የነፍስን ቤተ መቅደስ ለማፍረስና ምድራዊ ድልድይ ለመገንባት ብቻ ነው። ብቻየን ቆሜ እንዲህ የሚል የውስጥ ድምፄ ተሰማኝ ፡
#ፍቅር ለሰው ልብ ሕይወት እንደምትሰጥ ሁሉ አለማወቅን ማወቅ ደግሞ የእውቀትን መንገድ ያሳየዋል። ፍቅርና አለማወቅን መረዳት ወደ ታላቅ ደስታ ይመራሉ– ምክንያቱም ፈጣሪ ከፀሀይ በታች ለሰው ልጅ መከራን አልፈጠረምና።
@Zephilosophy
@Zephilosophy
ካህሊል ጂብራን
ለጋስነት በልቤ ውስጥ ተዘርታለች። ክምር ስንዴ አመረትኩ ፤ ለተራቡም አካፈልኩ። ነብሴ ለወይን ፍሬ ትሰጣለች፡፡ ወይኑን ጨምቄ ለተጠሙ አጠጣሁ። ፋኖሴን ዘይት ሞልቼ መስኮቴ ጋር አኖርኩኝ። በጭለማ ለሚጓዙ እንግዶች መንገዱን አበራሁ፡፡ ይህንን ሁሉ የማደርገው በእነዚህ ድርጊቶቼ ውስጥ ስለምኖር ነው። የሕይወት እጣ ለጋስ እጆቼን ብታስርበኝ ሞትን እመርጣለሁ። ገጣሚ ነኝና መለገስ ካልቻልኩ ፈፅሞ አልቀበልም። የሰው ልጅ ቁጣ እንደ አውሎ ነፋስ ያጓራል። እኔ ግን በዝምታ እተነፍሳለሁ፡፡ ምክንያቱም ትንፋሼ ፈጣሪ ጋር ሲደርስ ወጀቡ በሙሉ ይቆማልና። ሰዎች ምድራዊ ነገሮች ላይ ይንጠለጠላሉ፡፡ የኔ መሻት ግን የፍቅር ችቦ ናት። በብርሃኗ የልቤን ሰብአዊነት ታነፃልኛለች፡፡ ሰዎች በዘር ፣ በቀለም በሃይማኖት ተከፋፍለዋል። እኔ ደግሞ በሁሉም አገር እንግዳ ነኝ – የየትኛውም ወገን አይደለሁም፡፡ ሥነ-ፍጥረት (ዩኒቨርስ) አገሬ ስትሆን ጉሳዬ ደግሞ ሁሉም የሰው ልጅ ነው፡፡ የሰው ልጅ አቅመቢስ ሆነውም የተከፋፈሉ ናቸው። በየጊዜው የምትጠበውን ምድር በግዛትና አገራት መሰነጣጠቅ አላዋቂነት ነው። የሰው ልጆች እጅ ለእጅ የሚያያዙት የነፍስን ቤተ መቅደስ ለማፍረስና ምድራዊ ድልድይ ለመገንባት ብቻ ነው። ብቻየን ቆሜ እንዲህ የሚል የውስጥ ድምፄ ተሰማኝ ፡
#ፍቅር ለሰው ልብ ሕይወት እንደምትሰጥ ሁሉ አለማወቅን ማወቅ ደግሞ የእውቀትን መንገድ ያሳየዋል። ፍቅርና አለማወቅን መረዳት ወደ ታላቅ ደስታ ይመራሉ– ምክንያቱም ፈጣሪ ከፀሀይ በታች ለሰው ልጅ መከራን አልፈጠረምና።
@Zephilosophy
@Zephilosophy
👍66❤25🥰9👏4
❤ስለ ፍቅር ብጠይቅ ጥያቄዎቼን መመለስ የሚችል ማን አለ?
✍️ካህሊል ጂብራን
ፍቅር ምንድን ነው? ስለ ፍቅር ብላችሁ ንገሩኝ፣ በልቤ የሚነደው እሳት ምንድን ነው ጉልበቴን የሚያልፈሰፍሰው እና ምኞቴን የሚያከስመው ምንድነው?
ነፍሴን የሚጨብጧት እነዚያ የተደበቁ ለስላሳ እና ሻካራ እጆች ምንድናቸው?
ልቤን የሞላት ከመራር ደስታ እና ከጣፋጭ ህመም የተቀየጠ ወይን ምንድነው?
አይኖቼን የተከልኩበት የማይታይ ነገር የማሰላስለው ለመረዳት የሚያስቸግር ነገር፣ ልረዳው ያልቻልኩት ስሜት ምንድነው?
በትካዜ ውስጥ ከሳቅ ድምቀት የበለጠ ውብ፣ ከደስታ በላቀ የሚያስደስት ሃዘን አለ?
እስኪነጋ ድረስ አስተኝቶ በህይወት ለሚያቆየኝና መላ እኔነቱን በብርሃን ለሚሞላው ሃያል ራሴን የማስገዛው ለምንድን ነው?
እኛ ፍቅር የምንለው ነገር ምንድነው? ንገሩኝ፣ ህሊናን በሙሉ የሚገዛው በዘመናት ውስጥ የተደበቀው ሚስጥር ምንድነው?
ይህ በአንድ ወቅት የሁሉም ነገር መነሻና ውጤት የነበረው ፍቅር ምንድነው?
ይህ ከህይወትና ሞት የመነጨው፣ ከህይወት ይበልጥ አስገራሚ፣ ከሞት በላቀ ጥልቅ የሆነው ንቃት ምንድነው?
ንገሩኝ ጓደኞቼ፣ ፍቅር በጣቱ ጫፍ ነፍሱን ነክቶት ከህይወት እንቅልፍ የማይነቃ ከእናንተ መሃል አለ?
ነፍሱ የመረጠቻት ፍቅሩ ጠርታው እናትና አባቱን ትቶ የማይሄድ ከእናንተ መሃል ማነው?
ነፍሱ በልጃገረድ ጥዑም ትንፋሽ፣ ጣፋጭ ድምፅ እና ትንግርታዊ ለስላሳ እጆች ተማርካ ልቡ እስከ ዓለም ዳርቻ የማትሰደድ ወጣት ማን አለ?
ከልቡ የሚወደውን ሰው ለማግኘት ውቅያኖስ የማይሰነጥቅ፣ በረሃ የማያቋርጥ፡ ተራራ የማይቧጥጥ ከእናንተ መሃል ማነው?
ንስሃውን ከሚሰማው፣ ምህላውን ከሚቀበለው አምላክ ፊት እንደሚቀርብ የዕጣን መስዋዕት ልቡን የማያነደው ማን አለ?
ፍቅር ማለት...
ይቀጥላል...
@Zephilosophy
ንገሩኝ ጓደኞቼ ፍቅር ለናንተ ምንድነው ? ስለ ፍቅር ብላችሁ ንገሩኝ...✍️leave comment
✍️ካህሊል ጂብራን
ፍቅር ምንድን ነው? ስለ ፍቅር ብላችሁ ንገሩኝ፣ በልቤ የሚነደው እሳት ምንድን ነው ጉልበቴን የሚያልፈሰፍሰው እና ምኞቴን የሚያከስመው ምንድነው?
ነፍሴን የሚጨብጧት እነዚያ የተደበቁ ለስላሳ እና ሻካራ እጆች ምንድናቸው?
ልቤን የሞላት ከመራር ደስታ እና ከጣፋጭ ህመም የተቀየጠ ወይን ምንድነው?
አይኖቼን የተከልኩበት የማይታይ ነገር የማሰላስለው ለመረዳት የሚያስቸግር ነገር፣ ልረዳው ያልቻልኩት ስሜት ምንድነው?
በትካዜ ውስጥ ከሳቅ ድምቀት የበለጠ ውብ፣ ከደስታ በላቀ የሚያስደስት ሃዘን አለ?
እስኪነጋ ድረስ አስተኝቶ በህይወት ለሚያቆየኝና መላ እኔነቱን በብርሃን ለሚሞላው ሃያል ራሴን የማስገዛው ለምንድን ነው?
እኛ ፍቅር የምንለው ነገር ምንድነው? ንገሩኝ፣ ህሊናን በሙሉ የሚገዛው በዘመናት ውስጥ የተደበቀው ሚስጥር ምንድነው?
ይህ በአንድ ወቅት የሁሉም ነገር መነሻና ውጤት የነበረው ፍቅር ምንድነው?
ይህ ከህይወትና ሞት የመነጨው፣ ከህይወት ይበልጥ አስገራሚ፣ ከሞት በላቀ ጥልቅ የሆነው ንቃት ምንድነው?
ንገሩኝ ጓደኞቼ፣ ፍቅር በጣቱ ጫፍ ነፍሱን ነክቶት ከህይወት እንቅልፍ የማይነቃ ከእናንተ መሃል አለ?
ነፍሱ የመረጠቻት ፍቅሩ ጠርታው እናትና አባቱን ትቶ የማይሄድ ከእናንተ መሃል ማነው?
ነፍሱ በልጃገረድ ጥዑም ትንፋሽ፣ ጣፋጭ ድምፅ እና ትንግርታዊ ለስላሳ እጆች ተማርካ ልቡ እስከ ዓለም ዳርቻ የማትሰደድ ወጣት ማን አለ?
ከልቡ የሚወደውን ሰው ለማግኘት ውቅያኖስ የማይሰነጥቅ፣ በረሃ የማያቋርጥ፡ ተራራ የማይቧጥጥ ከእናንተ መሃል ማነው?
ንስሃውን ከሚሰማው፣ ምህላውን ከሚቀበለው አምላክ ፊት እንደሚቀርብ የዕጣን መስዋዕት ልቡን የማያነደው ማን አለ?
ፍቅር ማለት...
ይቀጥላል...
@Zephilosophy
ንገሩኝ ጓደኞቼ ፍቅር ለናንተ ምንድነው ? ስለ ፍቅር ብላችሁ ንገሩኝ...✍️leave comment
❤49👍35🥰1
❤ፍቅር ማለት
....የቀጠለ
ትናንት ከመቅደሱ በራፍ ቆሜ መንገደኞቹን ስለ ፍቅር ተዓምራቶችና ጥቅሞች ያውቁ እንደሆነ በጥያቄ ሳደርቃቸው ዋልኩ፡፡
አንድ የደከመና የገረጣ ፊት ያላቸው በዕድሜ የገፉ አዛውንት በአጠገቤ እያለፉ እንዲህ አሉኝ፡-
«ፍቅር ከመጀመሪያው ሰው የተሽለምነው ተፈጥሯዊ ድክመት ነው፡፡»
ይሁን እንጂ አንድ ጎበዝ ወጣት በንዴት መልስ ሰጠ፡- .. «ፍቅር ዛሬን ከትናንት እና ከነገ ጋር የሚያገናኝ ድልድይ ነው።»
አንዲት ሃዘን የተላበሰ ፊት ያላት ሴት አቃስታ እንዲህ አለች «ፍቅር በገሃነም የሚድሁ ጥቋቁር እፉኝቶች የሚወጉን ገዳይ መርዝ ነው መርዙ እንደ ጤዛ ትኩስ ስለሚመስል የተራበች ነፍስ ተስገብግባ ትጠጣዋለች ከመጀመሪያው ስካር በኋላ ግን ጠጪው ይታመምና ቀስ በቀስ ይሞታል፡፡»
ከዚያም አንዲት ውብ ጉንጮቿ እንደ ፀሃይ የሚያበሩ ልጃገረድ ፈገግ ብላ እንዲህ አለች፡
«ፍቅር በንጋት ሙሽሮች የሚቀርብ ጠንካራ ነፍሶችን የሚያጠነክርና ወደ ከዋክብት እንዲመጥቁ የሚያስችላቸው ወይን ነው፡፡»
ከእሷ በኋላ አንድ ጥቁር ካባ የደረበ ፂማም ሰው አይኖቹን አፍጥጦ ተናገረ፡
«ፍቅር ወጣትነት የሚጀምርበትና የሚያበቃበት የታወረ ድንቁርና ነው፡፡»
ሌላኛው ፈገግ ብሎ ቀጠለ፡«ፍቅር ሰው የአምላካቱን ያህል እንዲያይ የሚያስችል ሰማያዊ ዕውቀት ነው፡፡»
አንድ አይነ - ስውር መንገዱን በበትር እየፈለገ እንዲህ አለ፡
«ፍቅር ነፍስ የህያውነትን ሚስጥር እንዳታሳይ የሚከልላት፣ በዚህም ልብ ከኮረብቶች መሃል የሚንቀጠቀጡትን ጣዕረ - ሞቶች ፍላጎት ብቻ እንዲያይ እና የድምፅ አልባዎቹን ሸለቆዎች የመስተጋባት ጩኸት ብቻ እንዲሰማ የሚያደርግ የጉም መጋረጃ ነው፡፡»
አንድ ወጣት ክራሩን እየመታ እንዲህ ሲል ዘመረ-
«ፍቅር ከሚነደው የነፍስ ጉድጓድ በመመንጨት ምድሪቱን በብርሃን የሚሞላ አስማታዊ ጨረር ነው፡፡ ፍቅር ህይወትን በንቃትና ባለመንቃት መሃል እንዳለ ቆንጆ ህልም እንድናየው የሚያስችለን ነው፡፡»
አንድ ሽማግሌ ሰው እግሮቻቸውን እንደ ቡትቶ ጨርቅ እየጉተቱ
በሚንቀጠቀጥ ድምፅ እንዲህ አሉ፡
«ፍቅር በፀጥታማ መቃብር ያረፈ እስክሬን፣ በዘላለማዊነት ውስጥ
የሰጠመች ነፍስ ነው፡፡»
ከዚያም አንድ የአምስት ዓመት ህፃን እንዲህ አለ፡
«ፍቅር እናትና አባቴ ናቸው:: ከእናትና ከአባቴ በቀር ደግሞ ፍቅርን የሚያውቀው የለም።»
እናም ያለፉት በሙሉ ፍቅር የተስፋቸውና የተስፋ መቁረጫቸው ነፀብራቅ እንደሆነ በመግለፅ ሚስጥርነቱን የበለጠ አጎሉት።
ከዚያም በመቅደሱ ውስጥ አንድ ድምፅ ሰማሁ፡
« ህይወት እኩል ሁለት ቦታ ትከፈላለች፣ አንዱ በረዶ እና ሌላኛው እሳት፤ የሚፋጀው ግማሽ ፍቅር ነው፡፡»
በመጨረሻ ወደ መቅደሱ ገባሁና ተንበርክኬ ደስ እያለኝ ፀለይኩ፡- «ጌታዬ ሆይ፣ የነበልባሉ ራት አድርገኝ ... ጌታዬ ሆይ፣ የተከበረው እሳት ምግብ አድርገኝ ... አሜን፡፡»
ምንጭ- የጥበብ መንገድ
ደራሲ - ካህሊል ጂብራን
@Zephilosophy
@Zephilosophy
....የቀጠለ
ትናንት ከመቅደሱ በራፍ ቆሜ መንገደኞቹን ስለ ፍቅር ተዓምራቶችና ጥቅሞች ያውቁ እንደሆነ በጥያቄ ሳደርቃቸው ዋልኩ፡፡
አንድ የደከመና የገረጣ ፊት ያላቸው በዕድሜ የገፉ አዛውንት በአጠገቤ እያለፉ እንዲህ አሉኝ፡-
«ፍቅር ከመጀመሪያው ሰው የተሽለምነው ተፈጥሯዊ ድክመት ነው፡፡»
ይሁን እንጂ አንድ ጎበዝ ወጣት በንዴት መልስ ሰጠ፡- .. «ፍቅር ዛሬን ከትናንት እና ከነገ ጋር የሚያገናኝ ድልድይ ነው።»
አንዲት ሃዘን የተላበሰ ፊት ያላት ሴት አቃስታ እንዲህ አለች «ፍቅር በገሃነም የሚድሁ ጥቋቁር እፉኝቶች የሚወጉን ገዳይ መርዝ ነው መርዙ እንደ ጤዛ ትኩስ ስለሚመስል የተራበች ነፍስ ተስገብግባ ትጠጣዋለች ከመጀመሪያው ስካር በኋላ ግን ጠጪው ይታመምና ቀስ በቀስ ይሞታል፡፡»
ከዚያም አንዲት ውብ ጉንጮቿ እንደ ፀሃይ የሚያበሩ ልጃገረድ ፈገግ ብላ እንዲህ አለች፡
«ፍቅር በንጋት ሙሽሮች የሚቀርብ ጠንካራ ነፍሶችን የሚያጠነክርና ወደ ከዋክብት እንዲመጥቁ የሚያስችላቸው ወይን ነው፡፡»
ከእሷ በኋላ አንድ ጥቁር ካባ የደረበ ፂማም ሰው አይኖቹን አፍጥጦ ተናገረ፡
«ፍቅር ወጣትነት የሚጀምርበትና የሚያበቃበት የታወረ ድንቁርና ነው፡፡»
ሌላኛው ፈገግ ብሎ ቀጠለ፡«ፍቅር ሰው የአምላካቱን ያህል እንዲያይ የሚያስችል ሰማያዊ ዕውቀት ነው፡፡»
አንድ አይነ - ስውር መንገዱን በበትር እየፈለገ እንዲህ አለ፡
«ፍቅር ነፍስ የህያውነትን ሚስጥር እንዳታሳይ የሚከልላት፣ በዚህም ልብ ከኮረብቶች መሃል የሚንቀጠቀጡትን ጣዕረ - ሞቶች ፍላጎት ብቻ እንዲያይ እና የድምፅ አልባዎቹን ሸለቆዎች የመስተጋባት ጩኸት ብቻ እንዲሰማ የሚያደርግ የጉም መጋረጃ ነው፡፡»
አንድ ወጣት ክራሩን እየመታ እንዲህ ሲል ዘመረ-
«ፍቅር ከሚነደው የነፍስ ጉድጓድ በመመንጨት ምድሪቱን በብርሃን የሚሞላ አስማታዊ ጨረር ነው፡፡ ፍቅር ህይወትን በንቃትና ባለመንቃት መሃል እንዳለ ቆንጆ ህልም እንድናየው የሚያስችለን ነው፡፡»
አንድ ሽማግሌ ሰው እግሮቻቸውን እንደ ቡትቶ ጨርቅ እየጉተቱ
በሚንቀጠቀጥ ድምፅ እንዲህ አሉ፡
«ፍቅር በፀጥታማ መቃብር ያረፈ እስክሬን፣ በዘላለማዊነት ውስጥ
የሰጠመች ነፍስ ነው፡፡»
ከዚያም አንድ የአምስት ዓመት ህፃን እንዲህ አለ፡
«ፍቅር እናትና አባቴ ናቸው:: ከእናትና ከአባቴ በቀር ደግሞ ፍቅርን የሚያውቀው የለም።»
እናም ያለፉት በሙሉ ፍቅር የተስፋቸውና የተስፋ መቁረጫቸው ነፀብራቅ እንደሆነ በመግለፅ ሚስጥርነቱን የበለጠ አጎሉት።
ከዚያም በመቅደሱ ውስጥ አንድ ድምፅ ሰማሁ፡
« ህይወት እኩል ሁለት ቦታ ትከፈላለች፣ አንዱ በረዶ እና ሌላኛው እሳት፤ የሚፋጀው ግማሽ ፍቅር ነው፡፡»
በመጨረሻ ወደ መቅደሱ ገባሁና ተንበርክኬ ደስ እያለኝ ፀለይኩ፡- «ጌታዬ ሆይ፣ የነበልባሉ ራት አድርገኝ ... ጌታዬ ሆይ፣ የተከበረው እሳት ምግብ አድርገኝ ... አሜን፡፡»
ምንጭ- የጥበብ መንገድ
ደራሲ - ካህሊል ጂብራን
@Zephilosophy
@Zephilosophy
👍55❤27🥰1
ኦሾ ስለ ፍቅር
ፍቅር ከጥልቁ ውስጣችን የሚመጣ ነው።በጥያቄ ልናመጣው አንችልም ሲመጣም ዝም ማሰኘት አይቻልም። ፍቅር እኛ የምናደርገው ምርጫ አይደለም።
በሰው ህይወት ውስጥ ታላቁ ሙዚቃ ሊፈልቅ የሚችለው ልብ በአግባቡ የተቃኙ ክሮች ሲኖሩት ነው፡፡ ልቡን ያጣ ማህበረሰብ ጥሩ፣ እውተኛና ውብ የሆኑትን ክሮች ሁሉ አጥቷል፡፡ እውነት፣ ውበትና አምላካዊ ባህሪያት ወደ ህይወታችን እንዲገቡ ከፈለግን የልብን ሙዚቃ አፍላቂ የሆኑትን ክሮች በአግባቡ ከመቃኘት ውጪ ሌላ መንገድ የለም፡፡
እነዚህን የልብ ሙዚቃ አፍላቂ ክሮች በአግባቡ ለመቃኘት የሚያስችለው መንገድ ፍቅር ነው፡፡ ፍቅርን “ፀሎት ወይም እግዜርን የማግኛው መንገድ” ብዬ የምጠራውም ለዚህ ነው፡፡ ከፍቅር ያልሆነ ፀሎት ውሸትና የማይጠቅም ነው፡፡ ፍቅር አልባ የፀሎት ቃላት ዋጋ የላቸውም፡፡ ወደ አምላክ ለመጓዝ የፈለገ ሰው ያለ ፍቅር ሊሳካለት አይችልም፡፡ ልባዊ ሙዚቃን የሚያፈልቀው ፍቅር ነው፡፡
@Zephilosophy
ፍቅር ከጥልቁ ውስጣችን የሚመጣ ነው።በጥያቄ ልናመጣው አንችልም ሲመጣም ዝም ማሰኘት አይቻልም። ፍቅር እኛ የምናደርገው ምርጫ አይደለም።
በሰው ህይወት ውስጥ ታላቁ ሙዚቃ ሊፈልቅ የሚችለው ልብ በአግባቡ የተቃኙ ክሮች ሲኖሩት ነው፡፡ ልቡን ያጣ ማህበረሰብ ጥሩ፣ እውተኛና ውብ የሆኑትን ክሮች ሁሉ አጥቷል፡፡ እውነት፣ ውበትና አምላካዊ ባህሪያት ወደ ህይወታችን እንዲገቡ ከፈለግን የልብን ሙዚቃ አፍላቂ የሆኑትን ክሮች በአግባቡ ከመቃኘት ውጪ ሌላ መንገድ የለም፡፡
እነዚህን የልብ ሙዚቃ አፍላቂ ክሮች በአግባቡ ለመቃኘት የሚያስችለው መንገድ ፍቅር ነው፡፡ ፍቅርን “ፀሎት ወይም እግዜርን የማግኛው መንገድ” ብዬ የምጠራውም ለዚህ ነው፡፡ ከፍቅር ያልሆነ ፀሎት ውሸትና የማይጠቅም ነው፡፡ ፍቅር አልባ የፀሎት ቃላት ዋጋ የላቸውም፡፡ ወደ አምላክ ለመጓዝ የፈለገ ሰው ያለ ፍቅር ሊሳካለት አይችልም፡፡ ልባዊ ሙዚቃን የሚያፈልቀው ፍቅር ነው፡፡
@Zephilosophy
❤82👍35🔥7👏4
ውስጣዊ ምሽጋችንን ከፍርሃት መጠበቅ
"ከፍርሃት ከራሱ በስተቀር ምንም አትፍራ ፍርሃቶቻችን ልቀው እንዲገኙ የምንፈቅድ ከሆነ፣ ለመኖር ምንም ምክንያት፣ ለሀዘኖቻችንም ምንም ገደብ የለንም።”
- ሴኔካ
“መፍራት ያለብን ብቸኛ ነገር ማፈግፈግን ነው።መፍራት ያለብን ወደ ፊት ለመገስገስ እና ለመለወጥ የሚያስፈልጉትን ጥረቶች ሽባ የሚያደርገውን ስም የለሽ፣ ምክንያት የለሽ፣ ተገቢ ያልሆነ ፍርሃትን ራሱን ነው።”
ስቶይኮች ፍርሃት የሚፈራ የሚሆነው በሚፈጥራቸው ችግሮች እንደ ሆነ ያውቃሉ፡፡ ሳናስበው ልናስወግዳቸው ስንነሳ፣ የምንፈራቸው ነገሮች በራሳችንና በሌሎች ላይ ከምንፈጥረው ጉዳት ጋር ሲነፃፀሩ ይደበዝዛሉ፡፡ ጦርነት መጥፎ ነው፤ ፍርሃት ደግሞ የበለጠ መጥፎ ነው። ከባድ ሁኔታ ፍርሃት የበለጠ እንዲጠነክር ያደርገዋል እንጂ አያግዘውም፡፡ ይህንን ሁኔታ መለወጥ የምንፈልግ ከሆነ ልንቋቋመውና ልናስወግደው ይገባል።
“ፍርሃትን የሚያመጡት ሁኔታዎች ናቸው፤ እኛ በጠላታችን ላይ ኃይል ሊኖረን ወይም ልንከላከለው ስንችል እኛ ግን እሱ በሚፈጥራቸው ሀሳቦች በፍርሃት ምሽግ ውስጥ ተሸብበናል ። ምሽጉ የሚጠፋው እንዴት ነው? በመሳሪያ ወይም በእሳት ብቻ ሳይሆን በአስተዋይነትም ነው ..... መጀመር ያለብን ከእዚሁ ከአእምሯችን ነው፤ ምሽጉን መያዝና ጨቋኙን ማስወገድ ያለብን ከዚሁ ግንባር ነው።”
- ኤፒክቴተስ
ስቶይኮች “ውስጣዊ ምሽግ” የሚል አስደናቂ ሀሳብ ይሰጡናል።
ነፍሳችንን ይከላከላል ብለው የሚያምኑትም ይህንን ምሽግ ነው። .! በአካላዊ ሁኔታችን ተጠቂ ብንሆንም፣ በብዙ መንገዶች በመከራ ውስጥ
ልንሆን ብንችልም፣ ውስጣዊ ግዛታችን ግን መታለፍ የማይቻል መሆን አለበት።
ነገር ግን ታሪክ እንደሚያስተምረን፣ መታለፍ የማይቻሉ ምሽጎች #ከውስጥ ተላልፈው ከተሰጡ ሊሰበሩ ይችላሉ። በግንቦቹ ውስጥ የሚኖሩት ዜጎች በፍርሃት፣ በስግብግብነት ወይም በጥቅመኝነት ሲወድቁ፣ በሮቹን ሊከፍቱና ጠላትን እንዲገባ ሊያደርጉ ይችላሉ። ብዙዎቻችን ድፍረታችንን ስናጣና ለፍርሃት የተሰጠን ስንሆን የምናደርገውም ይህንን ነው፡፡
ጠንካራ ምሽግ ተቀብለሃል እና አሳልፈህ አትስጠው!!
📚የእለት ፍልስፍና
@Zephilosophy
@Zephilosophy
"ከፍርሃት ከራሱ በስተቀር ምንም አትፍራ ፍርሃቶቻችን ልቀው እንዲገኙ የምንፈቅድ ከሆነ፣ ለመኖር ምንም ምክንያት፣ ለሀዘኖቻችንም ምንም ገደብ የለንም።”
- ሴኔካ
“መፍራት ያለብን ብቸኛ ነገር ማፈግፈግን ነው።መፍራት ያለብን ወደ ፊት ለመገስገስ እና ለመለወጥ የሚያስፈልጉትን ጥረቶች ሽባ የሚያደርገውን ስም የለሽ፣ ምክንያት የለሽ፣ ተገቢ ያልሆነ ፍርሃትን ራሱን ነው።”
ስቶይኮች ፍርሃት የሚፈራ የሚሆነው በሚፈጥራቸው ችግሮች እንደ ሆነ ያውቃሉ፡፡ ሳናስበው ልናስወግዳቸው ስንነሳ፣ የምንፈራቸው ነገሮች በራሳችንና በሌሎች ላይ ከምንፈጥረው ጉዳት ጋር ሲነፃፀሩ ይደበዝዛሉ፡፡ ጦርነት መጥፎ ነው፤ ፍርሃት ደግሞ የበለጠ መጥፎ ነው። ከባድ ሁኔታ ፍርሃት የበለጠ እንዲጠነክር ያደርገዋል እንጂ አያግዘውም፡፡ ይህንን ሁኔታ መለወጥ የምንፈልግ ከሆነ ልንቋቋመውና ልናስወግደው ይገባል።
“ፍርሃትን የሚያመጡት ሁኔታዎች ናቸው፤ እኛ በጠላታችን ላይ ኃይል ሊኖረን ወይም ልንከላከለው ስንችል እኛ ግን እሱ በሚፈጥራቸው ሀሳቦች በፍርሃት ምሽግ ውስጥ ተሸብበናል ። ምሽጉ የሚጠፋው እንዴት ነው? በመሳሪያ ወይም በእሳት ብቻ ሳይሆን በአስተዋይነትም ነው ..... መጀመር ያለብን ከእዚሁ ከአእምሯችን ነው፤ ምሽጉን መያዝና ጨቋኙን ማስወገድ ያለብን ከዚሁ ግንባር ነው።”
- ኤፒክቴተስ
ስቶይኮች “ውስጣዊ ምሽግ” የሚል አስደናቂ ሀሳብ ይሰጡናል።
ነፍሳችንን ይከላከላል ብለው የሚያምኑትም ይህንን ምሽግ ነው። .! በአካላዊ ሁኔታችን ተጠቂ ብንሆንም፣ በብዙ መንገዶች በመከራ ውስጥ
ልንሆን ብንችልም፣ ውስጣዊ ግዛታችን ግን መታለፍ የማይቻል መሆን አለበት።
ነገር ግን ታሪክ እንደሚያስተምረን፣ መታለፍ የማይቻሉ ምሽጎች #ከውስጥ ተላልፈው ከተሰጡ ሊሰበሩ ይችላሉ። በግንቦቹ ውስጥ የሚኖሩት ዜጎች በፍርሃት፣ በስግብግብነት ወይም በጥቅመኝነት ሲወድቁ፣ በሮቹን ሊከፍቱና ጠላትን እንዲገባ ሊያደርጉ ይችላሉ። ብዙዎቻችን ድፍረታችንን ስናጣና ለፍርሃት የተሰጠን ስንሆን የምናደርገውም ይህንን ነው፡፡
ጠንካራ ምሽግ ተቀብለሃል እና አሳልፈህ አትስጠው!!
📚የእለት ፍልስፍና
@Zephilosophy
@Zephilosophy
👍71❤16🔥2👏1
"ዝምታን የተማርኩት ከለፍላፊ፤ ትግስትን የተማርኩት ደግሞ ትግስት ከሌለው እንዲሁም ደግሞ ደግነትን የተማርኩት ከክፉ ቢሆንም በጣም የሚገርመዉ ነገር ለነዚህ መምህሮቼ ምስጋና ቢስ መሆኔ ነዉ።"
ካህሊል ጅብራን
Join👇👇👇
@zephilosophy
@zephilosophy
@zephilosophy
ካህሊል ጅብራን
Join👇👇👇
@zephilosophy
@zephilosophy
@zephilosophy
❤144👍56😁11🥰5
የትኩረት መዛባት
በዚህ ማህረሰብ ውስጥ “ተመልከት የእኔ ሕይወት ከአንተ ሕይወት የበለጠ ያማረ ነው” በሚሉ በማህበራዊ ድረ- ገፆች በሚተላለፉ መልዕክቶች በኩል ጭንቀት፣ ፍርሃት፣ የጥፋተኝነት ስሜት ወዘተ... የመሳሰሉት አሉታዊ ልምዶች ያሉት ትውልድ እየፈራ ነው፡፡
ሰዎችም ሆነ የቲቪ ማስታወቂያዎች የመልካም ሕይወት ቁልፉ አሪፍ ስራ ማግኘት፣ ወይም ዘናጭ መኪና ወይም ቆንጆ ሴት ጓደኛ ያለህ መሆን እንደሆነ እንድታምን ይፈልጋሉ፡፡ አለም ያለማቋረጥ የሚነግርህ ነገር፣ የተሻለ የሕይወት መንገድ የሚባለው ብዙ መግዛት፣ ብዙ ማግኘት ፣ ብዙ መዋብ እንደሆነ ነው፡፡ ስለዚህ ሁልጊዜ በተደጋጋሚ ስለሁሉም ነገር ግድ እንዲኖርህ በሚነገሩ መልዕክቶች ስለምትጨናነቅ ያለማቋረጥ አዲስ ቅንጡ ነገሮችን ስለመግዛት፤ የእረፍት ጊዜህን ውድ በሆኑ ቦታዎች ስለማሳለፍ የምታስብ ትሆናለህ ወይም ፋሽን ልብሶች እና ኮስሞቲክሶችን ስለመግዛት የምታስቢ ትሆኛለሽ።
እነዚህ ነገሮች ከባድ የበታችነት እና የጭንቀት ስሜት ከመፍጠራቸውም በላይ በማይገባ አይነት የማይረቡና የውሸት ከሆኑ ነገሮች ጋር የተጣበቅክ እንድትሆንና ሕይወትህን ሙሉ የማይጨበጥ ደስታና እርካታ ስታሳድድ እንድትኖር ያደርግሃል፡፡ የመልካም ሕይወት ቁልፍ ስለ ብዙ ነገሮች መጨነቅ ሳይሆን፣ ስለ ትንሽ ለዚያውም እውነት፣ አስቸኳይና አስፈላጊ ስለሆነው ነገር ብቻ መጨነቅ ነው፡፡
Mark Manson
@zephilosophy
በዚህ ማህረሰብ ውስጥ “ተመልከት የእኔ ሕይወት ከአንተ ሕይወት የበለጠ ያማረ ነው” በሚሉ በማህበራዊ ድረ- ገፆች በሚተላለፉ መልዕክቶች በኩል ጭንቀት፣ ፍርሃት፣ የጥፋተኝነት ስሜት ወዘተ... የመሳሰሉት አሉታዊ ልምዶች ያሉት ትውልድ እየፈራ ነው፡፡
ሰዎችም ሆነ የቲቪ ማስታወቂያዎች የመልካም ሕይወት ቁልፉ አሪፍ ስራ ማግኘት፣ ወይም ዘናጭ መኪና ወይም ቆንጆ ሴት ጓደኛ ያለህ መሆን እንደሆነ እንድታምን ይፈልጋሉ፡፡ አለም ያለማቋረጥ የሚነግርህ ነገር፣ የተሻለ የሕይወት መንገድ የሚባለው ብዙ መግዛት፣ ብዙ ማግኘት ፣ ብዙ መዋብ እንደሆነ ነው፡፡ ስለዚህ ሁልጊዜ በተደጋጋሚ ስለሁሉም ነገር ግድ እንዲኖርህ በሚነገሩ መልዕክቶች ስለምትጨናነቅ ያለማቋረጥ አዲስ ቅንጡ ነገሮችን ስለመግዛት፤ የእረፍት ጊዜህን ውድ በሆኑ ቦታዎች ስለማሳለፍ የምታስብ ትሆናለህ ወይም ፋሽን ልብሶች እና ኮስሞቲክሶችን ስለመግዛት የምታስቢ ትሆኛለሽ።
እነዚህ ነገሮች ከባድ የበታችነት እና የጭንቀት ስሜት ከመፍጠራቸውም በላይ በማይገባ አይነት የማይረቡና የውሸት ከሆኑ ነገሮች ጋር የተጣበቅክ እንድትሆንና ሕይወትህን ሙሉ የማይጨበጥ ደስታና እርካታ ስታሳድድ እንድትኖር ያደርግሃል፡፡ የመልካም ሕይወት ቁልፍ ስለ ብዙ ነገሮች መጨነቅ ሳይሆን፣ ስለ ትንሽ ለዚያውም እውነት፣ አስቸኳይና አስፈላጊ ስለሆነው ነገር ብቻ መጨነቅ ነው፡፡
Mark Manson
@zephilosophy
👍126❤23🔥9👏1
ሟች ከመሆንህ እውነታ ጋር መጋፈጥ በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ ምክንያቱም ሁሉንም የማይረቡ፣ አቅም የሌላቸውና ጥልቀት የሌላቸውን እሴቶች ሁሉ ጠራርጎ የሚያስወግድ ነገር ነው፡፡ ብዙ ሰዎች ቀኖቻቸውን ተጨማሪ ገንዘብ ወይም ትንሽ ተጨማሪ ዝናና ትኩረት ወይም ትክክል ወይም ተወዳጅ በመሆናቸው ትንሽ ተጨማሪ ማረጋገጫ በማሳደድ ሲያሳልፉ፣ ሞት ግን ሁላችንንም በጣም በሚያሰቃይና አሰፈላጊ ጥያቄ ያፋጥጠናል፡፡
"ውርስህ ምንድነው? አንተ ስትሞት አለም የተለየችና የተሻለች የምትሆነው እንዴት ነው? ምን አሻራ ትተሀል? ምን ተፅእኖ ታመጣለህ?"
@Zephilosophy
"ውርስህ ምንድነው? አንተ ስትሞት አለም የተለየችና የተሻለች የምትሆነው እንዴት ነው? ምን አሻራ ትተሀል? ምን ተፅእኖ ታመጣለህ?"
@Zephilosophy
👍81🔥10❤7🥰4
ቅናት
ምንጭ ፦ ነፃ ስሜቶች (ኦሾ)
ትርጉም፦ ዩሐንስ አዳም
ቅናትውድድር/ንጽጽር ነው፡፡ እንድናወዳደር እና እንድናነጻጽር ተምረናል፡፡ ሁሌም እንድናነጻጽር ተገርተናል፡፡
አንድ ሰው የተሻለ ቤት አለው፡፡
አንድ የሆነ ሰው ያማረ አካል አለው፡፡
አንድ ሌላ ሰው ብዙ ገንዘብ አለው፡፡
አንድ ሰው ማራኪ ሰብእና አለው፡፡
ራሳችሁን ከአላፊ አግዳሚው ጋር አነጻጽሩ እናም ታላቅ ቅናት የሚያንሰራራ ይሆናል፡፡ ቅናት የንጽጽር መገራት ውጤት ነው፡፡ ንጽጽርን እና ውድድርን የምታስወግዱ ከሆነ ቅናት ይጠፋል፡፡ ከዚያም ራሳችሁን እንደሆናችሁት ብቻ ታውቁታላችሁ፡፡ እናንተ ማንንም አይደላችሁም፡፡ ማንንም መሆን አያስፈልጋችሁም፡፡ ራሳችሁን ከዛፎች ጋር አለማወዳደራችሁ ጥሩ አለበለዚያ በእነሱም ቅናት ይሰማችሁ ነበር፡፡ ለምን አረንጓዴ አልሆናችሁም? ለምን ይሆን እግዚአብሔር የጨከነባችሁ? ለምን አበባዎችን
አልሆናችሁም? ራሳችሁን ከአዋፋት ፣ ከወንዞች ፣ ከተራሮች ጋር አለማወዳደራችሁ ጥሩ ነው፡፡ አለበለዚያማ ትሰቃዮ ነበር። የምትወዳደሩት ከሰው ልጆች ጋር ብቻ ነው፡፡ ምክንያቱም እንድትወዳደሩ የተገራችሁት ከሰዎች ጋር ብቻ ስለሆነ ነው፡፡ ከፒኮኮች እና ከበቀቀኖች ጋር አትወዳደሩም፡፡
አለበለዚያማ ቅናት በጣም እና በጣም ይጨምር እና መኖር እስከሚያቅታችሁ ድረስ የቅናት ሸክም ይጫናችሁ ነበር፡፡ ውድድር እና ንጽጽር በጣም ቂላቂል አመላካከት ነው ምክንያቱም እያንዳንዱ ሰው ልዮ እና የማይነጻጸር በመሆኑ ነው።
ይህ ግንዛቤ አንድ ጊዜ በውስጣችሁ ከሰፈነ ቅናት ይጠፋል፡፡
እያንዳንዱ ሰው ልዮ እና የማይወዳደር ነው፡፡
እናንተ ራሳችሁንብቻ ናችሁ፡፡
ማንም ፈጽሞ እናንተን አይመስልም፡፡
እናንተ ፈጽሞ ማንንም መምሰል አትችሉም፡፡
አንድን ሰው/ሴት በምትወዱ ጊዜ ወደሌላ ሴት/ሰው ዘንድ ሊሄድ/ልትሄድ እንደማይችል/ትችል ታምናላችሁ፡፡ ግን ከሄደ/ከሄደች ምንም ማድረግ አይቻልም፡፡ ፍቅር ይህንን ግንዛቤ ያመጣል፡፡ ምንም ቅናት አይኖርም፡፡ ስለሆነም ቅናት የሚኖር ከሆነ ፍቅር እንደሌለ ጠንቅቃችሁ እወቁ፡፡ ቅናት ባለበት ግንኙነት ውስጥ ካላችሁ ጨዋታ እየተጫወታችሁ ነው ፤ ከፍቅር በስተጀርባ ወሲብን እየደበቃችሁ ነው ማለት ነው፡፡ ፍቅር ምንም ሳይሆን የተቀባ/ያጌጠ ቃል ብቻ ነው ማለት ነው፡፡
ቅናትን በጣም በቅርበት ተመልከቱት፡፡ ቅናት ምንድን ነው? ቅናት ማለት በውድድር ውስጥ መኖር ማለት ነው፡፡ አንድ ከእናንተ የበላይ የሆነ ሰው አለ፡፡ ከእናንተ በታች የሆነ ሰው አለ፡፡ እናንተ ሁሌም የመሰላሉ መሃል ላይ ናችሁ፡፡ ምናልባትም መሰላሉም ማንም መጨረሻውን የማያገኘው ክብ ሊሆንም ይችላል፡፡ እያንዳንዱ ሰው መሃል ላይ ተወስኖ ቀርቷል፡፡ እንዳንዱም ሰው መሃል ላይ ነው፡፡ መሰላሉ በክብ የሚሽከረከር ይመስላል፡፡
አንድ ሰው ከበላያችሁ ነው- ያ... ይጎዳል፡፡ ያም በጦርነት፣ በትግል ፣ በሚቻለው የትኛውም መንገድ ትንቀሣቀሱ ዘንዳ ያደርጋችኋል፡፡ ምክንያቱም የሚሳካላችሁ ከሆነ በትክክለኛው ይሁን በተሣሣተው መንገድ ማንም ግድ አይኖረውም፡፡ ስኬት ትክክለኛ ያደርጋችኋል፡፡ ውድቀት የተሣሣታችሁ እንደሆነ ያረጋግጣል፡፡ ስለዚህ ዋናው ጉዳይ ስኬት ነው፡፡ ስለዚህ ለስኬት የትኛውም መንገድ መጠቀም ይቻላል፡፡ መጨረሻው መንገዱን ትክክል ያደርገዋል፡፡ ስለዚህ ስለ መንገዱ ምንም መጨነቅ አያስፈልጋችሁም፡፡ ማንም ስለ መንገዱ ማንም አይጨንቀውም፡፡ መላው ጥያቄ እንዴት ነው መሰላሉን መውጣት የሚቻለው የሚለው ጥያቄ ነው፡፡ ግን የመሰላሉ መጨረሻ ላይ ፈጽሞ መምጣት አትችሉም፡፡ እናም ከእናንተ በላይ የሆነው ሰው ቅናትን በውስጣችሁ ይፈጥርባችኋል፡፡ እሱ ተሳክቶለታል
እናንተ ወድቃችኋል፡፡
ከምክንያት ወደ ውጤት የሚያመሩ መደምደሚያዎች አማኞች እንጂ ሳይንቲስቶች አያደርጓችሁም፡፡ “በቅናት ላይ ተመሰጡበት” ስላችሁ ይህንን ስሜት ታዘቡት ማለቴ ነው፡፡ በውስጣዊ አለማችሁ ውስጥ ሣይንቲስቶች ሁኑ፡፡ አእምሯችሁን ላብራቶሪ አድርጉት እና ያለምንም ውግዘት ተመለከቱ፡፡ “ቅናት መጥፎ ነው” አትበሉ፡፡ ማን ያውቃል “ቁጣ መጥፎ ነው” አትበሉ፡፡ ማን ያውቃል? አዎ ....ቅናት መጥፎ እንደሆነ ተነግሯችኋል፡፡ ያ....ግን በሌሎች የተነገረ ነገር ነው፡፡ ይህ የእናንተ ልምድ አይደለም፡፡ ህልውናዊ መሆን አለባችሁ፡፡ መከራችሁ የቅናትን መጥፎነት ካላረጋገጠ በስተቀር ለምንም ነገር "ነው” ወይም “አይደለም” አትበሉ፡፡ ፍጹም በሆነ መንገድ ከብያኔ ነጻ መሆን አለባችሁ፡፡ እናም ቅናትን ፣ ቁጣን ወይ፤ ወሲብን መታዘብ ደግሞ ታዓምር ነው።
ከማንኛውም ብያኔ ውጭ ሆናችሁ ስትታዘቡ ምን ይከሰታል? በቅናት ውስጥ የበለጠ በተመለከታችሁ ቁጥር ቅናት የበለጠ ግልጽ ይሆናል፡፡ የቅናትን ቂልነት ታያላችሁ፡፡ ቅናት ቂላቂል ነገር መሆኑን ቀድማችሁ ስለወሰናችሁ ሳይሆን በራሣችሁ ልምድ ተመርኩዛችሁ ቅናት ሞኝነት እንደሆነ ይገባችኋል፡፡ ግን ቀድሞውኑ ቅናት ሞኝነት እንደሆነ ከወሰናችሁ መላውን ነጥብ የምታጡት ይሆናል፡፡ ቀድሞ አለመበየናችሁን አስታውሱ፡፡ ቀድሞውኑ የምትወስኑ ከሆናችሁ መላውን ትርጉም ታጡታላችሁ፡፡ ከማንኛውም ውሳኜ ውጪ ተንቀሳቀሱ እናም ቅናት ምን እንደሆነ ተመልከቱ፡፡
@Zephilosophy
@Zephilosophy
ምንጭ ፦ ነፃ ስሜቶች (ኦሾ)
ትርጉም፦ ዩሐንስ አዳም
ቅናትውድድር/ንጽጽር ነው፡፡ እንድናወዳደር እና እንድናነጻጽር ተምረናል፡፡ ሁሌም እንድናነጻጽር ተገርተናል፡፡
አንድ ሰው የተሻለ ቤት አለው፡፡
አንድ የሆነ ሰው ያማረ አካል አለው፡፡
አንድ ሌላ ሰው ብዙ ገንዘብ አለው፡፡
አንድ ሰው ማራኪ ሰብእና አለው፡፡
ራሳችሁን ከአላፊ አግዳሚው ጋር አነጻጽሩ እናም ታላቅ ቅናት የሚያንሰራራ ይሆናል፡፡ ቅናት የንጽጽር መገራት ውጤት ነው፡፡ ንጽጽርን እና ውድድርን የምታስወግዱ ከሆነ ቅናት ይጠፋል፡፡ ከዚያም ራሳችሁን እንደሆናችሁት ብቻ ታውቁታላችሁ፡፡ እናንተ ማንንም አይደላችሁም፡፡ ማንንም መሆን አያስፈልጋችሁም፡፡ ራሳችሁን ከዛፎች ጋር አለማወዳደራችሁ ጥሩ አለበለዚያ በእነሱም ቅናት ይሰማችሁ ነበር፡፡ ለምን አረንጓዴ አልሆናችሁም? ለምን ይሆን እግዚአብሔር የጨከነባችሁ? ለምን አበባዎችን
አልሆናችሁም? ራሳችሁን ከአዋፋት ፣ ከወንዞች ፣ ከተራሮች ጋር አለማወዳደራችሁ ጥሩ ነው፡፡ አለበለዚያማ ትሰቃዮ ነበር። የምትወዳደሩት ከሰው ልጆች ጋር ብቻ ነው፡፡ ምክንያቱም እንድትወዳደሩ የተገራችሁት ከሰዎች ጋር ብቻ ስለሆነ ነው፡፡ ከፒኮኮች እና ከበቀቀኖች ጋር አትወዳደሩም፡፡
አለበለዚያማ ቅናት በጣም እና በጣም ይጨምር እና መኖር እስከሚያቅታችሁ ድረስ የቅናት ሸክም ይጫናችሁ ነበር፡፡ ውድድር እና ንጽጽር በጣም ቂላቂል አመላካከት ነው ምክንያቱም እያንዳንዱ ሰው ልዮ እና የማይነጻጸር በመሆኑ ነው።
ይህ ግንዛቤ አንድ ጊዜ በውስጣችሁ ከሰፈነ ቅናት ይጠፋል፡፡
እያንዳንዱ ሰው ልዮ እና የማይወዳደር ነው፡፡
እናንተ ራሳችሁንብቻ ናችሁ፡፡
ማንም ፈጽሞ እናንተን አይመስልም፡፡
እናንተ ፈጽሞ ማንንም መምሰል አትችሉም፡፡
አንድን ሰው/ሴት በምትወዱ ጊዜ ወደሌላ ሴት/ሰው ዘንድ ሊሄድ/ልትሄድ እንደማይችል/ትችል ታምናላችሁ፡፡ ግን ከሄደ/ከሄደች ምንም ማድረግ አይቻልም፡፡ ፍቅር ይህንን ግንዛቤ ያመጣል፡፡ ምንም ቅናት አይኖርም፡፡ ስለሆነም ቅናት የሚኖር ከሆነ ፍቅር እንደሌለ ጠንቅቃችሁ እወቁ፡፡ ቅናት ባለበት ግንኙነት ውስጥ ካላችሁ ጨዋታ እየተጫወታችሁ ነው ፤ ከፍቅር በስተጀርባ ወሲብን እየደበቃችሁ ነው ማለት ነው፡፡ ፍቅር ምንም ሳይሆን የተቀባ/ያጌጠ ቃል ብቻ ነው ማለት ነው፡፡
ቅናትን በጣም በቅርበት ተመልከቱት፡፡ ቅናት ምንድን ነው? ቅናት ማለት በውድድር ውስጥ መኖር ማለት ነው፡፡ አንድ ከእናንተ የበላይ የሆነ ሰው አለ፡፡ ከእናንተ በታች የሆነ ሰው አለ፡፡ እናንተ ሁሌም የመሰላሉ መሃል ላይ ናችሁ፡፡ ምናልባትም መሰላሉም ማንም መጨረሻውን የማያገኘው ክብ ሊሆንም ይችላል፡፡ እያንዳንዱ ሰው መሃል ላይ ተወስኖ ቀርቷል፡፡ እንዳንዱም ሰው መሃል ላይ ነው፡፡ መሰላሉ በክብ የሚሽከረከር ይመስላል፡፡
አንድ ሰው ከበላያችሁ ነው- ያ... ይጎዳል፡፡ ያም በጦርነት፣ በትግል ፣ በሚቻለው የትኛውም መንገድ ትንቀሣቀሱ ዘንዳ ያደርጋችኋል፡፡ ምክንያቱም የሚሳካላችሁ ከሆነ በትክክለኛው ይሁን በተሣሣተው መንገድ ማንም ግድ አይኖረውም፡፡ ስኬት ትክክለኛ ያደርጋችኋል፡፡ ውድቀት የተሣሣታችሁ እንደሆነ ያረጋግጣል፡፡ ስለዚህ ዋናው ጉዳይ ስኬት ነው፡፡ ስለዚህ ለስኬት የትኛውም መንገድ መጠቀም ይቻላል፡፡ መጨረሻው መንገዱን ትክክል ያደርገዋል፡፡ ስለዚህ ስለ መንገዱ ምንም መጨነቅ አያስፈልጋችሁም፡፡ ማንም ስለ መንገዱ ማንም አይጨንቀውም፡፡ መላው ጥያቄ እንዴት ነው መሰላሉን መውጣት የሚቻለው የሚለው ጥያቄ ነው፡፡ ግን የመሰላሉ መጨረሻ ላይ ፈጽሞ መምጣት አትችሉም፡፡ እናም ከእናንተ በላይ የሆነው ሰው ቅናትን በውስጣችሁ ይፈጥርባችኋል፡፡ እሱ ተሳክቶለታል
እናንተ ወድቃችኋል፡፡
ከምክንያት ወደ ውጤት የሚያመሩ መደምደሚያዎች አማኞች እንጂ ሳይንቲስቶች አያደርጓችሁም፡፡ “በቅናት ላይ ተመሰጡበት” ስላችሁ ይህንን ስሜት ታዘቡት ማለቴ ነው፡፡ በውስጣዊ አለማችሁ ውስጥ ሣይንቲስቶች ሁኑ፡፡ አእምሯችሁን ላብራቶሪ አድርጉት እና ያለምንም ውግዘት ተመለከቱ፡፡ “ቅናት መጥፎ ነው” አትበሉ፡፡ ማን ያውቃል “ቁጣ መጥፎ ነው” አትበሉ፡፡ ማን ያውቃል? አዎ ....ቅናት መጥፎ እንደሆነ ተነግሯችኋል፡፡ ያ....ግን በሌሎች የተነገረ ነገር ነው፡፡ ይህ የእናንተ ልምድ አይደለም፡፡ ህልውናዊ መሆን አለባችሁ፡፡ መከራችሁ የቅናትን መጥፎነት ካላረጋገጠ በስተቀር ለምንም ነገር "ነው” ወይም “አይደለም” አትበሉ፡፡ ፍጹም በሆነ መንገድ ከብያኔ ነጻ መሆን አለባችሁ፡፡ እናም ቅናትን ፣ ቁጣን ወይ፤ ወሲብን መታዘብ ደግሞ ታዓምር ነው።
ከማንኛውም ብያኔ ውጭ ሆናችሁ ስትታዘቡ ምን ይከሰታል? በቅናት ውስጥ የበለጠ በተመለከታችሁ ቁጥር ቅናት የበለጠ ግልጽ ይሆናል፡፡ የቅናትን ቂልነት ታያላችሁ፡፡ ቅናት ቂላቂል ነገር መሆኑን ቀድማችሁ ስለወሰናችሁ ሳይሆን በራሣችሁ ልምድ ተመርኩዛችሁ ቅናት ሞኝነት እንደሆነ ይገባችኋል፡፡ ግን ቀድሞውኑ ቅናት ሞኝነት እንደሆነ ከወሰናችሁ መላውን ነጥብ የምታጡት ይሆናል፡፡ ቀድሞ አለመበየናችሁን አስታውሱ፡፡ ቀድሞውኑ የምትወስኑ ከሆናችሁ መላውን ትርጉም ታጡታላችሁ፡፡ ከማንኛውም ውሳኜ ውጪ ተንቀሳቀሱ እናም ቅናት ምን እንደሆነ ተመልከቱ፡፡
@Zephilosophy
@Zephilosophy
👍55❤12
[የሕሊና ጸሎት]
___
ደምስ ሰይፉ
'አንዳንዶች' ሆይ...
.
.
.
'ሕዝብ' 'ሕዝብ' በሚለው አንደበታችሁ ውስጥ በሕዝብነት ስፍር በምላሳችሁ የምላመጥ ስም የለሽ መሆኔን...
___
ልባችሁ ቅንጣት ፍቅር ሳይኖራት ስለኔ መሰዋታችሁን በመለፈፍ በስሜ የምትነግዱ መሆኑን...
___
ከገዛ ክፋታችሁ አገዛዝ ነፃ ሳትወጡ 'ነፃ አውጭ ነን' ስብከታችሁን በየ አጋጣሚው ስትሰብኩ የማያቀረሻችሁ መሆኑን...
___
ወገኔ ሰው ነው ብዬ ከምኖርበት ቀዬ በመንደርተኛነት ጥንወት ታውራችሁ እንደ አውሬ አሳዳችሁኝ ስታበቁ ስለ ሰብዓዊ መብት ስታወሩ የማያቅለሸልሻችሁ መሆኑን...
___
'ዲሞክራሲ' በማስፈን ስም አገዛዝ ለማንበር እንደምታሴሩና ለዚህ ክፋታችሁ እኔኑ ጭዳ ከማድረግ የማትመለሱ መሆኑን...
___
ያለፈውን 'ጨለማ' የምትተቹት የተሻለ ቀን ለማምጣት ሳይሆን የተረኝነት አዙሪት ለማንበር መሆኑን...
___
ከሰላሜ ይልቅ ወንበራችሁ እያስጨነቃችሁ እንኳ 'የዜጎች መብት ይከበር' የምትሉት በአስመሳይነት መሆኑን...
___
ወ
ዘ
ተ
.
.
.
አ
ው
ቃ
ለ
ሁ
.
.
.
ግና
.
.
.
ዛሬም ተስፋ ሳልቆርጥ የፍትህ ጸሐይ እስክትወጣ የምጠብቀው "የማይነጋ ለሊት የለም" ያሉኝን አምኜ ነው...
___
@Zephilosophy
@Zephilosophy
___
ደምስ ሰይፉ
'አንዳንዶች' ሆይ...
.
.
.
'ሕዝብ' 'ሕዝብ' በሚለው አንደበታችሁ ውስጥ በሕዝብነት ስፍር በምላሳችሁ የምላመጥ ስም የለሽ መሆኔን...
___
ልባችሁ ቅንጣት ፍቅር ሳይኖራት ስለኔ መሰዋታችሁን በመለፈፍ በስሜ የምትነግዱ መሆኑን...
___
ከገዛ ክፋታችሁ አገዛዝ ነፃ ሳትወጡ 'ነፃ አውጭ ነን' ስብከታችሁን በየ አጋጣሚው ስትሰብኩ የማያቀረሻችሁ መሆኑን...
___
ወገኔ ሰው ነው ብዬ ከምኖርበት ቀዬ በመንደርተኛነት ጥንወት ታውራችሁ እንደ አውሬ አሳዳችሁኝ ስታበቁ ስለ ሰብዓዊ መብት ስታወሩ የማያቅለሸልሻችሁ መሆኑን...
___
'ዲሞክራሲ' በማስፈን ስም አገዛዝ ለማንበር እንደምታሴሩና ለዚህ ክፋታችሁ እኔኑ ጭዳ ከማድረግ የማትመለሱ መሆኑን...
___
ያለፈውን 'ጨለማ' የምትተቹት የተሻለ ቀን ለማምጣት ሳይሆን የተረኝነት አዙሪት ለማንበር መሆኑን...
___
ከሰላሜ ይልቅ ወንበራችሁ እያስጨነቃችሁ እንኳ 'የዜጎች መብት ይከበር' የምትሉት በአስመሳይነት መሆኑን...
___
ወ
ዘ
ተ
.
.
.
አ
ው
ቃ
ለ
ሁ
.
.
.
ግና
.
.
.
ዛሬም ተስፋ ሳልቆርጥ የፍትህ ጸሐይ እስክትወጣ የምጠብቀው "የማይነጋ ለሊት የለም" ያሉኝን አምኜ ነው...
___
@Zephilosophy
@Zephilosophy
👍56❤12🥰4
እውነተኛ ማንነትን ማግኘት
ህይወታቸውን ሙሉ በኢጎ የተያዙ፣ የማያስተውሉና የማያስተውሉ ሆነው የቀሩ ሠዎች፣ ስለማንነታቸው ሲያወሩ ወዲያውኑ ስማቸውን፣ ስራቸውን፣ ግላዊ ታሪካቸውን፣ የሰውነታቸውን ቅርፅና ሁኔታ፣ ሌሎች ሊዛመዷቸው የሚችሉትን ሁኔታዎች ይነግሩሀል። ሌሎች ደግሞ እራሳቸውን ዘላለማዊ ነፍስ ወይም ህያው መንፈስ አድርገው እንደሚያስቡ በመናገር የተሻሉ መስለው ሊቀርቡ ይሞክራሉ። ነገር ግን በእውነት እራሳቸውን አውቀውት ነው ወይስ በአእምሮአቸው ውስጥ መንፈሳዊ-ቀመስ ፅንሰ ሐሳብ እየከተቱ ነው? እራስን ማወቅ፣ የተወሰኑ ሃሳቦችን ወይም እምነቶችን ከመቀበል በላይ ጥልቅ ነው። መንፈሳዊ ሃሳቦችም ሆኑ እምነቶች ጠቋሚ ቢሆኑ እንጂ፣ የሰው አእምሮአዊ ቅኝት አካል የሆነውን ቀድሞ የተገነባውን ጠንካራ የማንነት ፅንሰ ሃሳብ የሚያመክን ሃይል እምብዛም የላቸውም። እራስህን በጥልቀት ማወቅ፣ በአእምሮህ ዙሪያ ከሚመላለስ ምንም አይነት ሃሳብ ጋር፣ አንዳች ግንኙነት የለውም። እራስን ማወቅ፣ እራስህን በአእምሮህ ውስጥ ከማጣት ይልቅ፣ በህላዌህ ውስጥ መትከል ነው።
👉ማንነቴ ብለህ የምታስበው ማንነት
የማንነት ስሜትህ በህይወትህ ያስፈልገኛል የምትለውንና ቦታ የምትሰጠውን ነገር የሚወስን ይሆናል። ለአንተ ቦታ ያለው ነገር ደግሞ፣ ሊረብሽህም ሆነ ሊያበሳጭህ አቅም አለው። እራስህን ምን ያህል በጥልቀት እንደምታውቀው ለመመዘንም፣ ይኽንኑ መስፈርት ልትጠቀም ትችላለህ። ቦታ የምትሰጣቸው ነገሮች የሚገለፁት በምትናገረውና በምታምነው ብቻ ሳይሆን በድርጊቶችህና በምትወስዳቸው አፀፋዊ ምላሾች ላይ አስፈላጊ እና ቁምነገር መስለው የሚገለጡትንም ያካትታል። እራስህን እንዲህ 'የሚያበሳጩኝና የሚረብሹኝ ነገሮች ምንድን ናቸው?' ብለህ ልትጠይቅ ትችላለህ። ትንንሽ ነገሮች አንተን የመረበሽ አቅም ካላቸው ማንነትህ በትክክል እንደዛ ነው፤ ትንሽ ነህ። ሳታስተውል የምታምነውም ይህንን ነው።
የምር የምትፈልገው ነገር ሰላምን ከሆነ፣ ሰላምን ትመርጣለህ። ከምንም ነገር በላይ ቦታ የምትሰጠው ለሰላም ከሆነ እና እራስህን ከትንሽ " እኔነት" ይልቅ መንፈስ እንደሆንክ በእውነት የምታውቅ ከሆነ፣ ከፈታኝ ሰዎች እና ሁኔታዎች ጋር ስትገናኝ ፍፁም አስተዋይና የረጋህ ሆነህ ትቆያለህ። የተፈጠረውን ሁኔታ ወዲያው ተቀብለህ፣ እራስህን ከማግለል ይልቅ ከሁኔታው ጋር አንድ ታደርጋለህ። እና ከዚያ አርምሞ ውስጥ የሚመጣ መልስ ታገኛለህ። መልሱን የሚሰጠውም ማንነትህ (ጥልቁ ተፈጥሮህ) እንጂ፣ ማንነቴ ብለህ ያሰብከው (ትንሹ እኔ) አየሸደለም። ምላሹም ሀያልና የተሳለጠ ሲሆን፣ የትኛውንም ሠውም ሆነ ሁኔታ ጠላት አያደርግም።
አንተ ኢጎህን አይደለህም፤ ስለዚህ በውስጥህ ያለውን ኢጎ ስታውቅ እራስህን አወቅክ ማለት ሳይሆን፣ ማንነተህ ያልሆነውን አወቅክ ማለት ነው። ነገር ግን በትክክል እራስህን ለማወቅ እንዳትችል ያደረገህን ትልቅ መሰናክል የምታስወግደው ማንነትህ ያልሆነውን ስታውቅ ነው።
ማንነትህን ማንም ሊነግርህ አይችልም። ማንነትህ ምንም አይነት ሀሳብ አይፈልግም። እንዲያውም እያንዳንዱ እምነት መሰናክል ይፈጥርብሀል። ምክንያቱም ሲጀመር የተፈጠርከውን ነህ። ነገር ግን መረዳት ከሌለ፣ ማንነትህ ወደ አለም ብርሀን መምጣት አይችልም።
👉 መትረፍረፍ
የምትረፍረፍ ምንጩ በውጪ የለም። የማንነትህ አካል ነው እንጂ። ነገር ግን ውጪ ያለዉን መትረፍረፍ በማወቅና በማመስገን መጀመር ትችላለህ። በዙሪያህ ያለውን የህይወትን ሙላት ተመልከት። ምነም እንኳን መትረፍረፍ ከተሰማህ ነገሮች ወደ አንተ መምጣታቸው አይቀሬ ቢሆንም፣ መትረፍረፍ እንዲሰማህ፣ ንብረት መያዝ አይጠበቅብህም። መትረፍረፍ፣ ላለው የሚመጣ ነገር ነው። ይህ የዩኒቨርስ ህግ ነው። መትረፍረፍም ሆነ ጎዶሎነት የሚገለጡ የውስጥህ እውነታዎች ናቸው።
👉 መልካም አና መጥፎ
ብዙ ሰዎች በህይወታቸው የሆነ ወቅት ላይ ከመወለድ፣ ከማደግ፣ ከስኬት ከመልካም ጤንነት፣ ከእርካታ እና ከማሸነፍ በተጨማሪ እጦት፣ ውድቀት፣ ህመም፣ እርጅና፣ መጃጀት፣ ስቃይና ሞትም እንዳለ ያውቃሉ። እነዚህም በስምምነት "መልካም" እና "መጥፎ" ፣ "የሰመረ" እና "ያልሰመረ" ተደርገው ይወሰዳሉ። የሰዎች ህይወት "ትርጉም" የሚኖረው መልካም ከተባለው ጋር ሲያያዝ ሲሆን፣ ይህም መልካም የተባለው ነገር ደግሞ ሁልጊዜ የመንኮታኮት፣ የመሰባበር፣ የመበጥበጥ አደጋ ይጋረጥበታል። ህይወት ትርጉም ስታጣና የሚገልፃት ነገር ሁሉ ስታጣ፣ ትርጉም የለሽና መጥፎ በሆነው አደጋ ውስጥ ገብታለች። ፈጥኖም ሆነ ዘግይቶ፣ የትኛውንም የኢንሹራንስ ፖሊሲ ብንገባ ህይወትን የሚያምስ ነገር መምጣቱ በማንም ላይ አይቀሬ ነው። አመጣጡ፣ በእጦት ወይም በአደጋ፣ በህመም፣ በአካል ጉዳት፣ በእርጅና ወይም ሞት ሊሆን ይችላል። ነገር ግን በሰውየው ህይወት ውስጥ የመጣው እክል እና ይሄን ተከትሎ የሚፈጠረው አእምሮ የፈጠረው ትርጉም መንኮታኮቱ፣ ለመለኮታዊው ስርአት በር ከፋች ሊሆን ይችላል።
ሃሳብ፣ ሁኔታዎችና ክስተቶች ልክ የግላቸው ተፈጥሮ ያላቸው ይመስል፣መልካም እና መጥፎ እያልን እንሰይማቸዋለን። በሃሳብ ላይ ባለን ቅጥ ያጣ አመኔታ ምክንያት እውነታ ይሰነጣጠቃል። ይህ መሰነጣጠቅ ወዥንብር ቢሆንም፣ በውዥንብሩ እስከተጠመድክ ድረስ ግን እውነት ይመስላል። ቢሆንም፣ ዓለም ግን እርስ በእርሱ የተሳሰረ፣ አንድም ነገር የብቻው ህልውና የሌለው፣ የማይከፋፈል ህብር ነው። የሁሉም ነገሮችና ክስተቶች በጥልቀት መተሳሰር የሚያመለክተውም "መልካም" እና "መጥፎ" የሚባሉት አእምሮአዊ ስያሜዎች፣ በተጨባጭ ውዥንብር እንደሆኑ ነው። እጅግ የተገደቡ ምልከታዎች ሲሆኑ እውነት መሆን የሚችሉትም በአንፃራዊነትና በጊዜያዊነት ነው። ይሄ በሎተሪ እጣ ውድ መኪና በገዛው አስተዋይ ሰው ታሪክ ውስጥ ውብ ሆኖ ተብራርቷል። ጓደኞቹና ቤተሰቦቹ ስለርሱ ተደስተው በዚያውም ደስታውን ለማክበር መጡ። "በጣም አይገርምም!። እድለኛ ነህ" አሉት። ሰውየውም ፈገግ ብሎ "ይሆናል" አለ። መኪናዋን በመንዳት የተወሰኑ ሳምንታት አጣጣመ። አንድ ቀን ግን፣ የሰከረ አሽከርካሪ በመንገድ መገናኛ ላይ ገጨውና በከፍተኛ ጉዳት ሆስፒታል ገባ። ጓደኞቹና ቤተሰቦቹ ሊጠይቁት መጡ " እንዴት አይነት ክፉ አጋጣሚ ነው?" አሉ። ሰውየው በድጋሚ ፈገግ ብሎ "ይሆናል" አለ። በሆስፒታል በነበረበት ጊዜም፣ በምሽት የመሬት መንሸራተት ተከስቶ መኖርያ ቤቱን ባህር ውስጥ ከተተው። እንደገና በሚቀጥለው ቀን ጓደኞቹና ቤተሰቦቹ መጥተው " ሆስፒታል ውስጥ በመሆንህ እድለኛ አይደለህም ታዲያ?" አሉት። እርሱም መልሶ "ይሆናል" አላቸው።
የአስተዋዩ ሰው "ይሆናል" የሚለው አባባል፣ የሚከሰተውን ሁሉ ለመፈረጅ አለመፈለጉን ያመለክታል። ከመፈረጅ ይልቅ፣ የሆነውን ሁሉ በመቀበል ከመለኮታዊዉ ስርዓት ጋር ንቁ አንድነት ይፈጥራል። ተራ የሚመስል ክስተት በህብሩ ሸማ ውስጥ ምን አይነት ስፍራ ሊኖረው እንደሚችል አእምሮ በፍፁም እንደማይረዳ አውቋል። ነገር ግን ድንገተኛ የሚባል ክስተት የለም፤ በራሱ እና ስለራሱ ብቻ በብቸኝነት የሚኖር ክስተትም ሆነ ሁኔታ የለም። አካልህን የገነቡ አተምች በውስጥህ የሚገኙ ከዋክብት ይመስላሉ፤ እናም የትንሽ ክስተት መንስኤው ወሰን የለሽ እና በማይጨበጥ መልኩ ከህብሩ ጋር የተሳሰረ ነው። የማንኛውንም ክስተት መነሻ ወደ ሗላ ሄደህ መመርመር ከፈለግክ፣ እስከ ፍጥረት መጀመሪያ ድረስ መጓዝ ይኖርብሀል።
ምንጭ ፦ አዲስ ምድር
ፀሀፊ :-ኤካሀርት ቶሌ
✍ይቀጥላል✍
@Zephilosophy
@Zephilosophy
ህይወታቸውን ሙሉ በኢጎ የተያዙ፣ የማያስተውሉና የማያስተውሉ ሆነው የቀሩ ሠዎች፣ ስለማንነታቸው ሲያወሩ ወዲያውኑ ስማቸውን፣ ስራቸውን፣ ግላዊ ታሪካቸውን፣ የሰውነታቸውን ቅርፅና ሁኔታ፣ ሌሎች ሊዛመዷቸው የሚችሉትን ሁኔታዎች ይነግሩሀል። ሌሎች ደግሞ እራሳቸውን ዘላለማዊ ነፍስ ወይም ህያው መንፈስ አድርገው እንደሚያስቡ በመናገር የተሻሉ መስለው ሊቀርቡ ይሞክራሉ። ነገር ግን በእውነት እራሳቸውን አውቀውት ነው ወይስ በአእምሮአቸው ውስጥ መንፈሳዊ-ቀመስ ፅንሰ ሐሳብ እየከተቱ ነው? እራስን ማወቅ፣ የተወሰኑ ሃሳቦችን ወይም እምነቶችን ከመቀበል በላይ ጥልቅ ነው። መንፈሳዊ ሃሳቦችም ሆኑ እምነቶች ጠቋሚ ቢሆኑ እንጂ፣ የሰው አእምሮአዊ ቅኝት አካል የሆነውን ቀድሞ የተገነባውን ጠንካራ የማንነት ፅንሰ ሃሳብ የሚያመክን ሃይል እምብዛም የላቸውም። እራስህን በጥልቀት ማወቅ፣ በአእምሮህ ዙሪያ ከሚመላለስ ምንም አይነት ሃሳብ ጋር፣ አንዳች ግንኙነት የለውም። እራስን ማወቅ፣ እራስህን በአእምሮህ ውስጥ ከማጣት ይልቅ፣ በህላዌህ ውስጥ መትከል ነው።
👉ማንነቴ ብለህ የምታስበው ማንነት
የማንነት ስሜትህ በህይወትህ ያስፈልገኛል የምትለውንና ቦታ የምትሰጠውን ነገር የሚወስን ይሆናል። ለአንተ ቦታ ያለው ነገር ደግሞ፣ ሊረብሽህም ሆነ ሊያበሳጭህ አቅም አለው። እራስህን ምን ያህል በጥልቀት እንደምታውቀው ለመመዘንም፣ ይኽንኑ መስፈርት ልትጠቀም ትችላለህ። ቦታ የምትሰጣቸው ነገሮች የሚገለፁት በምትናገረውና በምታምነው ብቻ ሳይሆን በድርጊቶችህና በምትወስዳቸው አፀፋዊ ምላሾች ላይ አስፈላጊ እና ቁምነገር መስለው የሚገለጡትንም ያካትታል። እራስህን እንዲህ 'የሚያበሳጩኝና የሚረብሹኝ ነገሮች ምንድን ናቸው?' ብለህ ልትጠይቅ ትችላለህ። ትንንሽ ነገሮች አንተን የመረበሽ አቅም ካላቸው ማንነትህ በትክክል እንደዛ ነው፤ ትንሽ ነህ። ሳታስተውል የምታምነውም ይህንን ነው።
የምር የምትፈልገው ነገር ሰላምን ከሆነ፣ ሰላምን ትመርጣለህ። ከምንም ነገር በላይ ቦታ የምትሰጠው ለሰላም ከሆነ እና እራስህን ከትንሽ " እኔነት" ይልቅ መንፈስ እንደሆንክ በእውነት የምታውቅ ከሆነ፣ ከፈታኝ ሰዎች እና ሁኔታዎች ጋር ስትገናኝ ፍፁም አስተዋይና የረጋህ ሆነህ ትቆያለህ። የተፈጠረውን ሁኔታ ወዲያው ተቀብለህ፣ እራስህን ከማግለል ይልቅ ከሁኔታው ጋር አንድ ታደርጋለህ። እና ከዚያ አርምሞ ውስጥ የሚመጣ መልስ ታገኛለህ። መልሱን የሚሰጠውም ማንነትህ (ጥልቁ ተፈጥሮህ) እንጂ፣ ማንነቴ ብለህ ያሰብከው (ትንሹ እኔ) አየሸደለም። ምላሹም ሀያልና የተሳለጠ ሲሆን፣ የትኛውንም ሠውም ሆነ ሁኔታ ጠላት አያደርግም።
አንተ ኢጎህን አይደለህም፤ ስለዚህ በውስጥህ ያለውን ኢጎ ስታውቅ እራስህን አወቅክ ማለት ሳይሆን፣ ማንነተህ ያልሆነውን አወቅክ ማለት ነው። ነገር ግን በትክክል እራስህን ለማወቅ እንዳትችል ያደረገህን ትልቅ መሰናክል የምታስወግደው ማንነትህ ያልሆነውን ስታውቅ ነው።
ማንነትህን ማንም ሊነግርህ አይችልም። ማንነትህ ምንም አይነት ሀሳብ አይፈልግም። እንዲያውም እያንዳንዱ እምነት መሰናክል ይፈጥርብሀል። ምክንያቱም ሲጀመር የተፈጠርከውን ነህ። ነገር ግን መረዳት ከሌለ፣ ማንነትህ ወደ አለም ብርሀን መምጣት አይችልም።
👉 መትረፍረፍ
የምትረፍረፍ ምንጩ በውጪ የለም። የማንነትህ አካል ነው እንጂ። ነገር ግን ውጪ ያለዉን መትረፍረፍ በማወቅና በማመስገን መጀመር ትችላለህ። በዙሪያህ ያለውን የህይወትን ሙላት ተመልከት። ምነም እንኳን መትረፍረፍ ከተሰማህ ነገሮች ወደ አንተ መምጣታቸው አይቀሬ ቢሆንም፣ መትረፍረፍ እንዲሰማህ፣ ንብረት መያዝ አይጠበቅብህም። መትረፍረፍ፣ ላለው የሚመጣ ነገር ነው። ይህ የዩኒቨርስ ህግ ነው። መትረፍረፍም ሆነ ጎዶሎነት የሚገለጡ የውስጥህ እውነታዎች ናቸው።
👉 መልካም አና መጥፎ
ብዙ ሰዎች በህይወታቸው የሆነ ወቅት ላይ ከመወለድ፣ ከማደግ፣ ከስኬት ከመልካም ጤንነት፣ ከእርካታ እና ከማሸነፍ በተጨማሪ እጦት፣ ውድቀት፣ ህመም፣ እርጅና፣ መጃጀት፣ ስቃይና ሞትም እንዳለ ያውቃሉ። እነዚህም በስምምነት "መልካም" እና "መጥፎ" ፣ "የሰመረ" እና "ያልሰመረ" ተደርገው ይወሰዳሉ። የሰዎች ህይወት "ትርጉም" የሚኖረው መልካም ከተባለው ጋር ሲያያዝ ሲሆን፣ ይህም መልካም የተባለው ነገር ደግሞ ሁልጊዜ የመንኮታኮት፣ የመሰባበር፣ የመበጥበጥ አደጋ ይጋረጥበታል። ህይወት ትርጉም ስታጣና የሚገልፃት ነገር ሁሉ ስታጣ፣ ትርጉም የለሽና መጥፎ በሆነው አደጋ ውስጥ ገብታለች። ፈጥኖም ሆነ ዘግይቶ፣ የትኛውንም የኢንሹራንስ ፖሊሲ ብንገባ ህይወትን የሚያምስ ነገር መምጣቱ በማንም ላይ አይቀሬ ነው። አመጣጡ፣ በእጦት ወይም በአደጋ፣ በህመም፣ በአካል ጉዳት፣ በእርጅና ወይም ሞት ሊሆን ይችላል። ነገር ግን በሰውየው ህይወት ውስጥ የመጣው እክል እና ይሄን ተከትሎ የሚፈጠረው አእምሮ የፈጠረው ትርጉም መንኮታኮቱ፣ ለመለኮታዊው ስርአት በር ከፋች ሊሆን ይችላል።
ሃሳብ፣ ሁኔታዎችና ክስተቶች ልክ የግላቸው ተፈጥሮ ያላቸው ይመስል፣መልካም እና መጥፎ እያልን እንሰይማቸዋለን። በሃሳብ ላይ ባለን ቅጥ ያጣ አመኔታ ምክንያት እውነታ ይሰነጣጠቃል። ይህ መሰነጣጠቅ ወዥንብር ቢሆንም፣ በውዥንብሩ እስከተጠመድክ ድረስ ግን እውነት ይመስላል። ቢሆንም፣ ዓለም ግን እርስ በእርሱ የተሳሰረ፣ አንድም ነገር የብቻው ህልውና የሌለው፣ የማይከፋፈል ህብር ነው። የሁሉም ነገሮችና ክስተቶች በጥልቀት መተሳሰር የሚያመለክተውም "መልካም" እና "መጥፎ" የሚባሉት አእምሮአዊ ስያሜዎች፣ በተጨባጭ ውዥንብር እንደሆኑ ነው። እጅግ የተገደቡ ምልከታዎች ሲሆኑ እውነት መሆን የሚችሉትም በአንፃራዊነትና በጊዜያዊነት ነው። ይሄ በሎተሪ እጣ ውድ መኪና በገዛው አስተዋይ ሰው ታሪክ ውስጥ ውብ ሆኖ ተብራርቷል። ጓደኞቹና ቤተሰቦቹ ስለርሱ ተደስተው በዚያውም ደስታውን ለማክበር መጡ። "በጣም አይገርምም!። እድለኛ ነህ" አሉት። ሰውየውም ፈገግ ብሎ "ይሆናል" አለ። መኪናዋን በመንዳት የተወሰኑ ሳምንታት አጣጣመ። አንድ ቀን ግን፣ የሰከረ አሽከርካሪ በመንገድ መገናኛ ላይ ገጨውና በከፍተኛ ጉዳት ሆስፒታል ገባ። ጓደኞቹና ቤተሰቦቹ ሊጠይቁት መጡ " እንዴት አይነት ክፉ አጋጣሚ ነው?" አሉ። ሰውየው በድጋሚ ፈገግ ብሎ "ይሆናል" አለ። በሆስፒታል በነበረበት ጊዜም፣ በምሽት የመሬት መንሸራተት ተከስቶ መኖርያ ቤቱን ባህር ውስጥ ከተተው። እንደገና በሚቀጥለው ቀን ጓደኞቹና ቤተሰቦቹ መጥተው " ሆስፒታል ውስጥ በመሆንህ እድለኛ አይደለህም ታዲያ?" አሉት። እርሱም መልሶ "ይሆናል" አላቸው።
የአስተዋዩ ሰው "ይሆናል" የሚለው አባባል፣ የሚከሰተውን ሁሉ ለመፈረጅ አለመፈለጉን ያመለክታል። ከመፈረጅ ይልቅ፣ የሆነውን ሁሉ በመቀበል ከመለኮታዊዉ ስርዓት ጋር ንቁ አንድነት ይፈጥራል። ተራ የሚመስል ክስተት በህብሩ ሸማ ውስጥ ምን አይነት ስፍራ ሊኖረው እንደሚችል አእምሮ በፍፁም እንደማይረዳ አውቋል። ነገር ግን ድንገተኛ የሚባል ክስተት የለም፤ በራሱ እና ስለራሱ ብቻ በብቸኝነት የሚኖር ክስተትም ሆነ ሁኔታ የለም። አካልህን የገነቡ አተምች በውስጥህ የሚገኙ ከዋክብት ይመስላሉ፤ እናም የትንሽ ክስተት መንስኤው ወሰን የለሽ እና በማይጨበጥ መልኩ ከህብሩ ጋር የተሳሰረ ነው። የማንኛውንም ክስተት መነሻ ወደ ሗላ ሄደህ መመርመር ከፈለግክ፣ እስከ ፍጥረት መጀመሪያ ድረስ መጓዝ ይኖርብሀል።
ምንጭ ፦ አዲስ ምድር
ፀሀፊ :-ኤካሀርት ቶሌ
✍ይቀጥላል✍
@Zephilosophy
@Zephilosophy
👍54❤21🔥5