Zehabesha
61.1K subscribers
4.84K photos
478 videos
14 files
6.42K links
Ethiopian News
Download Telegram
ሃሰተኛ 200 ብር ተሰራጭቷል ተጠንቀቁ ብለናል፤ ተጠንቀቁ።
በደብረብርሃን ከሃያ ሺህ በላይ፣ በዋግ ሕምራ ሰቆጣ ከ65 ሺህ በላይ፣ በቆቦና አካቢው ከ60 ሺህ በላይ በዳባት እንዲሁ በሺዎች የሚቆግጠሩ፣ በደቡብ ክልል የተለያዩ ከተሞች እንዲሁ በሺዎች የሚቆጠሩ ተፈናቃዮች ይገኛሉ። አነሰም በዛም እነዚህ ተፈናቃዮች ቢያንስ ትንሽም ነገር አግኝተዋል፤ በሚዲያም ተዘግቦላቸዋል። በቂ ባይሆንም። ሆኖም በጎጃም ፍኖተ ሰላም የሚገኙ ከመቶ ሺህ በላይ የሚሆኑት ተፈናቃዮች ግን የሚጮህካቸው አክቲቪስትም፣ የሚያስታውሳቸው ወገንም፣ ዞር ብሎ የሚያያቸው ባለስልጣን የለም። ከዚህ ቀደም ተማረው ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ከጎጃም ፍኖተሰላም እና ቡሬ ተነስተው ወደ ባህርዳር የ እግር ጉዞ ቢጀምሩም በጥብቃ ኃይሎች እንዲመለሱ ተደርገዋል። ድምጻቸውም አልተሰማም። የዘ-ሐበሻ ባልደረባ ተዋቸው ደርሶ ለነዚህ ወገኖች ድምጽ ከመሆን ፍኖተ ሰላም በመሄድ ተፈናቃዮቹን እነጋግሯቸዋል፤ አብዛኛዎቹ ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና ከወለጋ የተፈናቀሉ ናቸው፤ ድምጻቸውን እንስማ። ቪድዮውን በየቦታው በማጋራት ትኩርት እንዲያገኙ እናድርግ።
https://www.youtube.com/watch?v=k2RN9TPWKKA
በአሸባሪው ሕወሓት የተፈጸሙ በወልቃይት ጠገዴ ጠለምት የተገኙ የጅምላ መቃብሮች በፎቶ።