Yop Poem ️
7.78K subscribers
83 photos
7 videos
25 files
58 links
፨Yop Poem
አዳዲስ እና የቆዩ ግጥሞችና ወጎችን በቀላሉ ያገኙበታል። 🤲
እርስዎም የግጥም ተሰጥዖ ካልዎት መልቀቅ ይችላሉ።👐
Our main channale :- @Utophiainfo

ቻናላችንን #share ያድርጉ👍

for promo & cross 👉 @Yared642
Download Telegram
'ለምን አልፈጠርክም.. ?'

(ኤፍሬም ስዩም)

ሳይደምን ሳይዘንብ ሳይጨልም ሳይነጋ ፤
ምድርና አርያምን ቀድሞ ሳትዘረጋ ፤
ፊተኛው ኋለኛው አልፋና ኦሜጋ ፤
እንዴት ነበር ኑሮህ ስፍራህስ ምኑጋ ?
ምንት ሳይኖር በፊት ኢምንት እያለ ፤
ያሁኑ ዙፋንህ ኪሩቤል ከሌለ ፤
ያኔ ያንተ ሀገር ከየት ነበር ያለ ?
ሀገርህ እንዳልል ያኔ ሀገር የለም ፤
ምንም ሳይኖር በፊት ስትኖር በምንም ፤
በእግዚአብሔርነትህ እግዜር ከሌለብህ ፤
ሁሉንም አዋቂ አንተ ብቻ ከሆንህ ፤
ስንት ዘመን ሆነህ ሆነህ ከተገኘህ ?
ፍጥረትስ ነበረ ከመፍጠርህ በፊት ?
ቀድመው የተሰሩ ከሰው ከመላዕክት ?
ካልነበረም ፍጥረት ፤
የዘመናት አምላክ የዘመናት ንጉስ ጥያቄዬን መልስ ፤
ለምን አልፈጠርክም እስክትፈጥር ድረስ ?
.



@Yoppoem
ፍቃዱ ግርማ

    አያድርስ ከቶ

እማታገኝውን ሺህ ግዜ መናፈቅ
ለማይሆነው ነገር ሺህ ግዜ መጨነቅ
እራስክን ከማጣት ምንም አታተርፍም
ዝብርቅርቅ ባለበት በዚህ ከንቱ አለም
አይጣልብህ እንጂ አያድርስ ከቶ
በዚች አለም ኑሮ ማንስ ያቃል ረክቶ ። ?
  
        ማንም

@Yoppoem
Messages in this channel will no longer be automatically deleted
Asmarino
Dawit Tsige
❤️❤️❤️
@Yoppoem
ማያልፍ የመሰለኝ ዳምኖ ህይዎቴ
ባዘነብኩት እንባ ታጥቦ ማንነቴ
ግርዶሹ በርትቶ ነገየን ጋርዶብኝ
ፍፁም አንዳልጓጓ ህመም በርትቶብኝ
ዛሬ ነገ እያልኩኝ ሞቴን ሲጠባበቅ
ህመሜን ሳዳምጥ ስሜቶቼን ሳረቅ
.
.
.
         መኖር ማለት ስቃይ
         መኖር ምለት ህመም
         መኖር ማለት ጭንቀት
         መኖር ማለት ድካም....

ወደ ተስፋ መንደር እልፍ ጊዜ ባመራ
የ እድሌን ልሻማ ከ እኩዮቼ ጋራ
ብፈልግ... ብጠብቅ ድርሻ የለኝ ሁኖ
ጠብታ እንኳን ሳይቀር ከ እኔነቴ ተኖ
ፀሐይ የለኝ ሁና ሕይዎቴ ዳምኖ
.
.
.
       ትላንት በመኖሬ ተስፋ እንኳን ሳይኖረኝ
       ምንም ያህል ባዝን የሚያልፍ ባይመስለኝ
       ቀን እየቆጠረ ቀን እየጨመረ
       የደመናው ጥቁረት መጠኑ ቀንሶ
       የስቃይ ዉርጅብኝ ከነበረው አንሶ
       ከ ሕይወቴ ጠፋ ቀስ በቀስ ጨርሶ...
.
.
.
የ ፀሐይ ዉበቷ
የፀሐይ ድምቀቷ
የዉበት ፍካቷ
ዛሬ ላይ ብሸፈን
ደመናው ሲገፈፍ ወደጎን ሲበተን....
.
.
.
       ህመም ብርድ ሁኖ ያገረጣው ትናንት
       ተንፏቆ እየዳሀ ዛሬን በመጠጋት
       አንድ ቀን ልጨምር ብዬ በመኖሬ
       ተስፋ ፀሐይ ሁኖ ከች አለልኝ ዛሬ!!
           
           @Yoppoem
አባቶች እናቶች
በፍቅር ተጋግዘው ፣ ያቆሙልን እውነት
በዘመን ጠልሽቶ...
ለእኛ ለልጆች ፣ ይመስለናል ተረት፡፡
።።።።።።
የኛ ትልቅ ችግር ፣ የኛ ትልቅ ህመም
"ተረት ተረት"ሲባል
መሰረት ሳንይዝ
"የመሰረት" ብሎ ፣" እሺ" እያሉ ማዝገም፡፡
።።።።።።፣
ተረት ተረት
"የመሰረት"
አንድ ሀገር ነበረች
"እሺ"
እምነትን ከፍቅር ፣ ገምዳ ያስተማረች፡፡
"እሺ"
አናም በዚች ሀገር...
ሙስሊሞች በእምነት ፣ መስጅድ ሲገነቡ
ክርስቲያኖች በፍቅር...
ይታዩ ነበረ ፣ ምሶሶ ሲያቀርቡ፡፡
"እሺ"
፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እናም በዚች ሀገር...
ክርስቲያኖች በምነት ፣ ቤተስኪያን ሲያንፁ
ሙስሊሞች በፍቅር...
ይታዩ ነበረ ፣ ጉልላት ሲቀርፁ፡፡
"እሺ"
እናም በዚ መልኩ ፣ ሲኖሩ ሰኖሩ
እንደተዋደዱ እንደተፋቀሩ
እንደተጋገዙ እንደተባበሩ
መሰረት እንድናይ...
አንዋር ከራጉኤል ፣ ተጎራብተው ቀሩ
"እሺ"
"እሺ" ማለት ጥሩ
መሰረት ሳይዙ ...
የመሰረት ብሎ ፣ መኖር ነው ችግሩ!!!
።።።።።

By Belay Bekele Weya

@Yoppoem
Forwarded from Yop Poem ️ (Death💀)
አባቶች እናቶች
በፍቅር ተጋግዘው ፣ ያቆሙልን እውነት
በዘመን ጠልሽቶ...
ለእኛ ለልጆች ፣ ይመስለናል ተረት፡፡
።።።።።።
የኛ ትልቅ ችግር ፣ የኛ ትልቅ ህመም
"ተረት ተረት"ሲባል
መሰረት ሳንይዝ
"የመሰረት" ብሎ ፣" እሺ" እያሉ ማዝገም፡፡
።።።።።።፣
ተረት ተረት
"የመሰረት"
አንድ ሀገር ነበረች
"እሺ"
እምነትን ከፍቅር ፣ ገምዳ ያስተማረች፡፡
"እሺ"
አናም በዚች ሀገር...
ሙስሊሞች በእምነት ፣ መስጅድ ሲገነቡ
ክርስቲያኖች በፍቅር...
ይታዩ ነበረ ፣ ምሶሶ ሲያቀርቡ፡፡
"እሺ"
፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እናም በዚች ሀገር...
ክርስቲያኖች በምነት ፣ ቤተስኪያን ሲያንፁ
ሙስሊሞች በፍቅር...
ይታዩ ነበረ ፣ ጉልላት ሲቀርፁ፡፡
"እሺ"
እናም በዚ መልኩ ፣ ሲኖሩ ሰኖሩ
እንደተዋደዱ እንደተፋቀሩ
እንደተጋገዙ እንደተባበሩ
መሰረት እንድናይ...
አንዋር ከራጉኤል ፣ ተጎራብተው ቀሩ
"እሺ"
"እሺ" ማለት ጥሩ
መሰረት ሳይዙ ...
የመሰረት ብሎ ፣ መኖር ነው ችግሩ!!!
።።።።።

By Belay Bekele Weya

@Yoppoem
በዚህ ሙቅ ከተማ
በዚህ ደማቅ መንገድ
ሺ አምፖል በበራበት
ፀሐይ ቀንና ሌት ፥ በማትጠልቅበት
ለሰው የማይታይ
አለ ብቸኝነት ።

አለ ብቸኝነት
በስንት እግሮች መሐል
ያደፈ ኮት ለብሶ
አይኑ ማዶ ፈዞ
የታክሲ ጥሩንባ የሚያደነቁረው
ሰው ገፍትሮት እንኳን
"ይቅርታ" የማይለው
ስሙ ፥ ማይነሳ
መኖሩ ፥ የተረሳ
ቢሞት ፥ ልብ የማይባል
አለ ብቸኝነት
እዚሁ ፥ እኛው መሐል ።

አለ ብቸኝነት
አንድ ጊዜ ተራምዶ
ብዙ ጊዜ የሚቆም
በፋሲካ በአል ፥ ብቻውን የሚጾም ።

አለ ብቸኝነት
ቢያውቀው ወይ ባያውቀው
የሚገላምጠው
(ወይ በመተያየት)
ፈገግታ 'ሚሰጠው
አንድ አይን የናፈቀው ።

አለ ብቸኝነት
ዕንባውን የዋጠ
ሳቁን የመጠጠ
ስሜቱን ያፈናት ፥ ልውጣ ባለች ቁጥር
ልቡ እንደ ድመት ሆድ ፥ ትር ትር የምትል ።

አለ ብቸኝነት
ወዴትም የማይሄድ ፥ ዝም ብሎ የሚራመድ
እንኳንስ ሰውና ፥ ልቡ ያልሆነው ዘመድ
ጭር ያለ ባይተዋር
በሰው ጎርፍ መሐል
ትንፋሹ የሚታየው
እርምጃ የሚመትር
ጠብታ የሚቆጥር
ወዴትም ሳንርቅ ፥ እዚሁ አፍንጫችን
እዚሁ ልባችን ስር
አለ ብቸኝነት ።

@Yoppoem
Messages in this channel will no longer be automatically deleted
ተመልሰናል ቤተሰብ 😊😊
ጥቁር ነጭ ግራጫ
(ነብይ መኮንን)

...ሰው እያለ አጠገባችን
ቅንነቱን ማየት ሲያመን
ከኛ አብሮ በሕይወት ቆሞ ፤ መልካሙን ስምን
መጥራት ሲያንቀን
"ሰው ካልሞተ ወይ ካልሄደ አይነሳም" እንላለን
እንዲህ እያልን፤
ስንቱን ጠቢብ እየሸኘን፤
አበባውን ቀጥፈን ጥለን፤ አበባ (እ)ናስቀምጣለን።



@Yoppoem
አድሚኖች ፖስት ካደረጋችሁ በኋላ የፖሰታችሁትን እራሳችሁ አጥፉ🙏🙏
Yop Poem ️ pinned «አድሚኖች ፖስት ካደረጋችሁ በኋላ የፖሰታችሁትን እራሳችሁ አጥፉ🙏🙏»