የገጣሚያን ማኅበር
18.6K subscribers
210 photos
11 videos
10 files
372 links
እዚህ ማኅበር ውስጥ የሚካተቱ የስነ-ጽሁፍ ይዘቶች፦
👉መንፈሳዊ ግጥም
፦ስለ ሀገር ፦ስለ እግዚአብሔር ፍቅር ፦ስለ ወንጌል ፦ስለቤተክርስቲያን👉መነባነብ
👉ግጥማዊ ትረካ
ይቀላቀሉን
Channel👉 @Ye_Getamian_Mahiber
Group👉 @yegetamianmahiber
YouTube https://www.youtube.com/channel/UCu6J21bKGYAwu8GxXoywbmA
Download Telegram
ሁሉም እኔን ይመስላሉ!


ለምሳሌ
ትላንት ጮኾ የጠራው ዓይነ ስውሩ
ጠርቶት ሲጨነቅ በግርግሩ
"ዝምበል" እያሉት ከእሱ የደረሰው
እኔን ይመስላል ያ ለማኝ ሰው
በእርግጥ...
ዓይን ነበረኝ እንደ ምልክት ያገለገለኝ
አምኜው ስጓዝ ገደል ሚጥለኝ
ያላስመለጠኝ ስንቴ ስሰበር
እንዲያይ ተፈጥሮ አያይም ነበር።
ደግሞም

የልብ ብርሃን ተስፋ ሚዝበት
ለጨለማዬ ፋና ሞጋበት
አልነበረኝም ብርሃን ለቤቴ
ዘይት አልባ ነው ሸክላ ማኅቶቴ
የለኝም ለእግሬ ጭላንጭል መብራት
መርቶ ሚያደርሰኝ ለንጉስ እራት
አልነበረኝም የመንገድ መብራት።


በርግጥ...
ዓይን ነበረኝ እንደ ምልክት ያገለገለኝ
አምኜው ስጓዝ ገደል ሚጥለኝ
አልጠቀሙኝም ማቃጭላቸው ሳንቲሞች እንኳን
መቼ አስገቡኝ ከህይወት ድንኳን
አልነበረኝም የተስፋ ፋኖስ
እየሱስ ብሎ የዳነው ለማኝ
እኔን ይመስላል በርጠለሚሆስ
   ለካስ...
ለእውር መነፅር ስውር ቃል አለች
ሰው እየሱስ ሲል ዓለም ታንሳለች
ፈጣሪያቸውን ፍጥረት ያውቁታል
አፍ እየሱስ ሲል ዓለም መስህቧ ይረቋቆታል።
ለካስ ሰው ያያል...

ሰው ያያል ለካ እየሱስ ብሎ
ማምለጥ ይቻላል እየሱስ ብሎ
ፍቅሩ የነካው ሰው ይከተለዋል
          መረቡን ጥሎ
መረብ ኑሮዬ ፤ መረብ ትዳሬ ፤መረብ ህይወቴ
የህይወት ተስፋዬ ፤ምድር ላይ መክበር፤ ነበር ስለቴ

መረበኛ ነኝ ዘውትር የምውል በአጢአት ማህበል
እድፌን ነክተ እንዳትቆሽሽ ፤ ከእኔ ራቅ በል

ያለው ጴጥሮስ ልቡን ሲያየው ልቡ ተስቦት
ቃል ደማ ካፉ ፤የነፍሱን ደምስር፤ ፍቅር አልቦት

ስለቆሻሻው የሚነቅፈውን ሊሰማ ቢጥር እሱን ሊያደምጠው
እርሱ ግን መልሱ "ተከተለኝ ነው ሰው ሊያስጠምደው"

ነጥቆ ሊያወጣው፤ ከሞት ከተማ ፤ ከሙታን ግርግም
ምርጫ ተወለት ፤ ልዝቡን ቀንበር ፤ ቀሊሉን ሸክም

ማራኪው ፍቅሩ ፤ ጥልቁ ትህትናው፤ ልቡን ቢስበው
   መረቡን ጥሎ ፤
    ኑሮውን ጥሎ
ትዳሩን ጥሎ ፤ ተከትሎታል ጴጥሮስ አበው
ደግ አረገ...
ይኖር የነበር ፤ በማረፊያ አልባ ፤ የኑሮ እንጥልጥል
በሕያው መዝገብ ፤ አይሰፍርም ነበር ፤ መረቡን ባይጥል
ትላንት በእሱ..
ከአጢሀት ውቂያኖስ ፤ ሰማይ የገባው፤ በህይወት መሰላል
ፃድቁ አባቴ አበው ጴጥሮስ እኔን ይመስላል ።
ይኸው
እንካቸው ደካሞች ብሎ ፤ የነገረኝ ቅዱስ ቃሉ
ቆም ብዬ ሳጤናቸው ፤ ሁሉም እኔን ይመስላሉ ።

ደግሞ ያ የቄሳር አስገባሪው ...ጠፊ ጣዖት ገንዘብን ሰርሳሪው

ጦጣ የመሰለው የዛፍ ላይ ሯጭ
እኔን ይመስላል ዘኪዮስ ቀራጭ
በአርባ ቀን ዕድል የተበደለው
የሀጢአት ሰው ተብሎ የተገለለው
መሲሕ ነው ሲሉት ከሩቅ ልይ ብሎ
ጦጣ የመሰለው ዛፍ ላይ ተሰቅሎ
ተስፋን ናፋቂው ቁመተ አጭሩ
እኔን ይመስላል ሁሉ ነገሩ

ጥቀርሻ ኑሮውን ነክቶ.......ካመድ ከትቢያ አንስቶ
አዚሙን አባርሮለት.........የመገበው ዕለት ዕለት
እያራቀው  ከአጢሃት ግፊት......ያከበረው በናቁት ፊት
ስንት የሰው ፊት እንዳላየ......ሊያየው ወጥቶ በሱ የታየ
ጦጣ መሳይ ዛፍ ላይ ሯጭ
                    እኔ ነኝ ዘኪዮስ ቀራጭ

ገብሬሃለው የአጢሀት ግብር......ሮጫለው ለራስ ክብር
የልብ ጭንቄን ሚሰማ..........አብሮኝ በልቶ የማያማ
እየሳመ የማይከዳ.......ናፍቅ ነበር ንፁህ እንግዳ
አገኘሁ አገኘኸኝ
አገኘሁ አንተን ጌታ..........ልቤ ጮቤ እየመታ
            አነባሁኝ መንታ መንታ
አስገረምከኝ ስሜን ጠርተኽ አወረድከኝ ከዛፌም ላይ
         ....................    ልታስገባኝ ያንተ ሰማይ
ልታደርገኝ የምድር ጨው......አልጫነቴን ልትፈጨው
በጥዑም አጅህ አንኳክተኸው የልቤን በር
ባትገባብኝ እኔ እኔን አልሆንም ነበር
እንኳን መጣክ !
እንኳን መጣክ ቤተ ሳይዳ
ከመፃጉዎች ስብሰባ ከዲዊያኖች መደዳ
በገል መንደር ለቁሰለቴ ማከኪያዎቼን ሰንቄ
ቁስሌ የውሻ አሎን ብሎኝ ስላልሻረ ተጨንቄ
ወድቄ ነበር ደቅቄ.......ጭንቄን አዳማጭ ናፍቄ
ባለሁበት ሰፈር መጥተህ.....ቁም ስትለኝ አበርትተህ
ተገረመች ቤተ-ሳይዳ
ተገረመች ቤተ-ሳይዳ ፤ እኔም አለሁ ተገርሜ
ነፍሴን ፍሰሓ ያስናፈቃት ፤ የት ገባ ያመታት እርሜ
ይገርማል...
አመራረጡ የገረመው ፤ልቤ አውንም ይገረማል፤
እንዴት የኔ ደዌ ታየው ፤ ከዛ ሁሉ ደዌ መሀል ።
ይገርማል ...
ሰማይ ሰማያት ዙፋኑ፤ምድር ማትበቃው ለተረከዙ፤
በቁም ነገር ቆጥሮኝ መጣ ፤ እኔን ሊያደርግ ደመወዙ።
ብቻ መዳኔ ግሩም ነው፤ አደራረጉም ይደንቃል፤
ማን እንደ እሱ ለእኔ ይወድቃል
ማን እንደ እሱ ለእኔ ይደቅቃል
ማን እንደ እሱ ለእኔ ይደርቃል
ማን እንደ እሱ ለእኔ ይጎዳል
ማን እንደ እሱ እኔን ይወዳል
ያሉት ሁሉ.....እኔን ይመስላሉ ።

ይኸው
እንካቸው ደካሞች ብሎ ፤ የነገረኝ ቅዱስ ቃሉ
ቆም ብዬ ሳጤናቸው ፤ ሁሉም እኔን ይመስላሉ።

የሱ መልስ

Subscribe Our YouTube Channel
https://www.youtube.com/@Poetscouncil8394
👆👆👆👆
No reaction
There is
No post ☹️
ከንቱ ከንቱ አረገኝ

ሰው በምድር ኑሮው
በዚች አጭር ጊዜው
ያተረፈው ምን አለ
ይልቁን አጎደለ
ይቺ አለም መኖራ
እኛን ማማረሯ
                                   አባቶቻችን ሄዱ
                                   አሉ የተባሉ ሄዱ
                                   የተከበሩ ሄዱ
                                   ያደጉ ሄዱ
                                   የቆዩ ሄዱ
                                ድል ሠሪዎች ሄዱ
                                 የተዋረዱ ሄዱ
                                ለአለም የኖሩ ሄዱ
እኛስ ግን
ሞቱ ልንባል
ወይንስ ቀሩ
ወይንስ ተቀበሩ
ወይንስ አረጉ
ወይንስ ታረዱ
                    ይቺ አለም ከንቱ
                    የከንቱም ከንቱ
                    ለካ ያለው ሰባኪው
                    የፊቱን አይቶ ነው
                    ምን የፊቱን ብቻ
                    የዋላውንም ዛቻ
                    አይቶ ተመልክቶ
                    በደንብም አጣርቶ
                    አስተውሎም ጭምር
                    ካየውም ግርግር
ኸረ ይቺ አለም ከንቱ አረገቺኝ
ስለሷ እንዳስብ ተቆጣጠረችኝ
ከንቱ ከንቱ አረገኝ ያልኩት ወዳጄ ነው
ተገድጄ እንጂ ይህን አለም ሳየው

ገጣሚ ፡ ህይወት ነክር
ቀን፡ መጋቢት 25

Subscribe Our YouTube Channel
https://www.youtube.com/@Poetscouncil8394
እስቲ እንወያይ


ቅዱሳን ክርስቲያን
Betting መጫወት
ይፈቀዳል?
HAPPY MOTHER DAY !ዛሬ የእናቶች ቀን ነው  ።

በአጭሩ ለእናቶ ያለውን ቃል ግለፁልን?
😍😍
ቤዛዬ
ካንተ ፊት የጠፋው ከእጅ የተጣልኩ
ልቅረብህ እንኳን ብል የማልችል የተከትኩ
ድነትን አገኝ ብዬ ፈፅሞ ማላስብ
ፃድቅ ነኝ ብዬ ራሴን ልክብ
እንድም ስንኳ የለም በኔ ላይ ፅድቅ
አንተ ሆነህ ነው እንጂ ፃዲቅ
የድነት ተስፋ እንዳይደርስ እኔ ጋር
በዘር ሃረጌ የለም የሆነ ለእግዚአብሔር
እሱ ወዶኝ እንጂ እሱ ወዶኝ እንጂ
ልጣል ማይገባኝ በቅዱሱ ደጅ
ርቄ የቆምኩኝ ማልገባ መቅደስ
የሰራውት በደል ሁሌም ሚከስ
በማመኔ እንጂ ያልሆነ በስራ
የእርሱ ስም በኔ ሊጠራ
አላፋረብኝም ቅዱስ እግዚአብሔር
በዘመኔ ላይ አንተ ብቻ ክበር


ማስረሻ
REACT 🥰❤️


Subscribe Our YouTube Channel
https://www.youtube.com/@Poetscouncil8394
16k loading.. 🥳🤩🥳🤩
"፤ የሥጋ ሕይወት በደሙ ውስጥ ነውና፤ ደሙም ከሕይወቱ የተነሣ ያስተሰርያልና በመሠዊያው ላይ ለነፍሳችሁ ማስተስረያ ይሆን ዘንድ እኔ ለእናንተ ሰጠሁት።"

        (ኦሪት ዘሌዋውያን 17: 11)

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇

መድቀቁና መሠቃየቱ ግን የእግዚአብሔር ፈቃድ ነበር፤ እግዚአብሔር ነፍሱን የኀጢአት መሥዋዕት ቢያደርገውም እንኳ፣ ዘሩን ያያል፤ ዕድሜውም ይረዝማል፤ የእግዚአብሔርም ፈቃድ በእጁ ይከናወናል።

            ኢሳይያስ 53:10

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇

የሰው ልጅ እንዲያገለግሉት ሳይሆን፣ ለማገልገልና ነፍሱንም ለብዙዎች ቤዛ አድርጎ ለመስጠት መጥቶአልና።

         ማቴዎስ 20:28

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇

ራሱንም ለሰዎች ሁሉ ቤዛ አድርጎ ሰጠ፤ ይህም በትክክለኛው ጊዜ ተመስክሮለታል።

             1 ጢሞቴዎስ 2:6

Subscribe Our YouTube Channel
https://www.youtube.com/@Poetscouncil8394
# ቃልህን ልኑረው

ቃልህን ልኑረው፣ አዳኜ ኢየሱስ
ለዚያች ለመዳን ቀን፣ ወዳንተ እንድደርስ
ፈቃድህን ልኑር ፣ አንተን ደስ ላሰኝ
ተቀይጦ መኖር፣ይኸው አሁን ይብቃኝ
ለምን ጥቂት እያልኩ፣እርሾ እጠቀማለሁ
ሊጡን እንዲያቦካ፣በርግጥ እኮ አቃለሁ

አሮጌን ማንነት፣በጥቂት ወስዳለሁ
ደሞ ለስህተቱ ፣ጥቅስ እፈልጋለሁ
ፈቃድህ እንዳልሆነ፣ ልቤ እያወቀው
መታዘዝ የሚለው፣ እየተናነቀው
ፈቃድህ ነው ፣ እያልኩ ሁሌ ናገራለው
ደግሜ ለራሴ ፣ ለልቤ አወራለሁ
አቤት እኔ ስገርም፣ደግሞ ፀልያለሁ
ፈቃድህን አስታውቀኝ፣እያልኩ እጮሀለሁ

ከእንተ ፈቃድ ጋር፣ታዲያ እንዴት ላስታርቀው
ያንተን ፈቃድናየራሴን ፍላጎት፣አንድላይ አድርጌው
አሮጌውን እርሾ፣ ከቤቴ አስቀምጬ
ፈቃድህን እያወኩ፣ አለመመለሴ
ምን ይሉታል አሁን፣ እያወቁ አላውቅም
ቀናው መንገድ ሳለ፣ሁልጊዜ መጣመም

ሲናገር ሲናገር፣ እኔኮ አልስማ
እኔ ምፈልገው፣እኔኑ ልሰማ
በውስጤ ያለዉን፣ካሳቤ ሚስማማ
ኢየሱስ እባክህ😭፣ፈቃድህን ልኑረው
የማውቀውን ሁሉ፣ልፈፅም ላድርገው
የማውቀውን ያክል፣ሳልቀይጥ ልኑረው
ጌታዬ ኢየሱስ፣ ቃልህን ልኑረው።

@Meta_01234

📥Group :  @yegetamianmahiber
📥Channel : @Ye_Getamian_Mahiber
👆👆👆👆👆👆👆👆👆
      🔺🀄️🀄️ሉን🔺
           Join us
         🎯     ♡         ❍ㅤ    ⌲ 
ʲᵒᶦⁿ    ˡᶦᵏᵉ  ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ   ˢʰᵃʳᵉ
ሰላም ጥያቄና መልስ ዛሬ ይኖረናል እንደተለመደው 3:00 ለይ ሁላችሁም ተሳተፉ ማንም እንዳይቀር እናም ደግሞ የጥያቄና መልስ ውድድር አሸናፊ ለመሆን ማድረግ የሚጠበቅባችሁ ጥያቄ ሲጠየቅ ትክክለኛውን መልስ ቀድሞ መመለስ ነው እንዲሁም ደግሞ መልሱን ኤዲት ማድረግ አይቻልም🤗 በዚህ መሰረት አሸናፊውን የምሸልም ይሆናል መልካም ዕድል መልካም ቆይታ👍👍🙏🙏🙏🙏🙏😍😍😍😍😍❤️❤️❤️❤️❤️❤️


Subscribe Our YouTube Channel
https://www.youtube.com/@Poetscouncil8394
የገጣሚያን ማኅበር pinned «ሰላም ጥያቄና መልስ ዛሬ ይኖረናል እንደተለመደው 3:00 ለይ ሁላችሁም ተሳተፉ ማንም እንዳይቀር እናም ደግሞ የጥያቄና መልስ ውድድር አሸናፊ ለመሆን ማድረግ የሚጠበቅባችሁ ጥያቄ ሲጠየቅ ትክክለኛውን መልስ ቀድሞ መመለስ ነው እንዲሁም ደግሞ መልሱን ኤዲት ማድረግ አይቻልም🤗 በዚህ መሰረት አሸናፊውን የምሸልም ይሆናል መልካም ዕድል መልካም ቆይታ👍👍🙏🙏🙏🙏🙏😍😍😍😍😍❤️❤️❤️❤️❤️❤️ Subscribe Our…»
ሠላም ቅዱሳን እንደት አመሻችሁ 🙌🙌


የዕለቱ ፕሮግራም በጸሎት እንጀምራለን🙏


ቅዱስ እግዚአብሔር ሆይ እናመሰግናለን
ስምህ ለዘላለም የተመሰገነ ይሁን።ካለላችን ስለሆንክ ለነፍሳችን ሠላም ስለሆንክ ለዘላለም እናከብራለን ክብር በሠማይ በምድር ለአንተ ብቻ ይሁኔ🙏🙏🙏🙏



አባቱ አሁን የዕለቱ ፕሮግራም አንተን በማስቀደም ጀምረናል እስከ ፍጻሜ  ድረስ አንተ ብቻ ምራን በመንፈስ ቅዱስ ኃይል አብርታን 🙏🙏🙏 በጌታ ስም መገኘትህን በመካከላችን አሳየን ኃይልን ግለጥልን🙏🙏🙏🙏 በመንፈስ ቅዱስ እሳት ንካን🙏🙏🙏🙏 ሁሉ እንደ በጎ ፈቃህ ይሁን አሜን አሜን

🙏🙏🙏🙏
16k Followers  🔥🔥
Thank You Everyone🥰❤️

   እስቲ ምን ተጠቀማችሁ ከዝህ ቻኔል?
አጭር መልዕክት በComment መስጫ
ላይ አስቀምጡ።😊
ጥያቄ አንድ
ጥያቄ አንድ

ጳውሎስ “እናንተ ክብራችን ደስታችንም ናችሁና” ብሎ የተናገረው እነማንን ነው?

ሀ/ የቲቶ ሰዎችን
ለ/ የተሰሎንቄ ሰዎችን
ሐ/ የቆላሲያይ ሰዎችን
መ/ የፊልጵስዩስ ሰዎችን
መልስ



“እናንተ ክብራችን ደስታችንም ናችሁና።”
  — 1ኛ ተሰሎንቄ 2፥20
ጥያቄ ሁለት
ጥያቄ፡ ሁለት


የኢየሱስን አስከሬን እንዲቀብር የጠየቀው ሰው ስሙ ማን ነበር?
ሀ)ጴጥሮሰ
ለ)የአርማትያሱ ዮሴፍ
ሐ)ይሁዳ
መ)የአስቀሮጡ ይሁዳ
መልስ፡-

ለ/ የአርማትያሱ ዮሴፍ
ጥያቄ ሶስት
ጥያቄ፡- ሶስት

ከ9ኙ የመንፈስ ፍሬዎች ያልሆነዉ አንዱ የቱ ነዉ?
ሀ)ፍቅር
ለ)አዛኝነት
ሐ)ደግነት
መ)ጥሩነት