በኦላይን መድረክ 50 የሚጠጉ ህጻናት ላይ ጾታዊ ጥቃት የፈጸመው አየርላዳዊ በእስራት ተቀጣ።
በሰሜናዊ አየርላንድ የሚኖረው የ55 ዓመቱ ዴቪድ ጆን አንድሪውስ በ130 የወሲብ ጥቃቶች ተከሶ የ27 ዓመት እስራት ተፈርዶበታል።
ከዚህ ውስጥ 46ቱ ህፃናት ናቸው ተብሏል። ጥቃት ካደረሰባቸው ህፃናትም ውስጥ በዕድሜ ትንሿ የ8 ዓመት ህፃን ናት።
ወንጀለኛው ጥቃቱን የፈጸመው እንዴት ነው ?
ጥቃት አድራሹ እራሱን በ አስራዎቹ እንደሚገኝ ታዳጊ አስመስሎ በ snapchat እና በ instagram ገፅ ላይ ለጥፎ 50 የሚደርሱ ህፃናት ላይ ጥቃት በማድረስ ነው ጥቃቱን ሲያደርስ የነበረው።
በተደረገው ምርመራም መርማሪዎቹ 10,000 የሚጠጉ ህገ-ወጥ የህፃናት ምስሎችን በአንድሪውስ የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያው ላይ ያገኙ ሲሆን በአስራዎቹ እንዳለ ታዳጊ መስሎ ለመለጠፍ የተጠቀመባቸውን 40 የሚሆኑ የመለያ ስሞችም (user names) ተገኝቷል።
አብዛኛዎቹ ወንጀሎች "ካትፊሺንግ" ማለትም አንድ ሰው የሌላን ሰውን ምስል እንደራሱ አድርጎ ማቅረብ ጋር የሚያያዝ ነው።
ወንጀሎቹ በፍርድ ቤቱ ሲቀርቡ የአስገድዶ መድፈር ሙከራ ፣ከ13 ዓመት በታች የሆነን ልጅ ወሲባዊ ተግባር እንዲፈፅም ማድረግ ወይም መገፋፋት፣ ወሲብ ነክ የሆኑ መልዕክቶችን ወይም ንግግሮችን ማድረግ፣ ማስፈራራት ይገኙበታል።
በተጨማሪም ህፃናት የወሲብ አገልግሎቶችን እንዲፈፅሙ ገንዘብ ለመክፈል ሙከራ ማድረግ፣ የህፃናትን የወሲብ ንግድ ወይም ፖርኖግራፌን ማዘጋጀት ወይም ማመቻቸት፣ ተገቢ ያልሆኑ ምስሎችን መያዝ ይገኙበታል።
በዳውንፓትሪክ ክራውን ፍርድ ቤት የተሰየሙት ዳኛ ጂኦፍሪ ሚለር "እሱ ራሱ ልጅ ነው በሚል የተሳሳተ እምነት ልጆቹን አታሏቸዋል ... ይህን ካደረገ በኋላ በጣም ጥንቃቄ በተሞላበት ሁኔታ ከሱ ጋር በማህበራዊ ሚዲያ ምስል እንዲያጋሩት የተለያዮ ማስፈራሪያዎችንና ማሳመኛ መንገዶችን ይጠቀም ነበር" ሲሉ ይገልጻሉ።
"ከእያንዳንዱ ልጅ ጋር የተለዋወጠው መልዕክት የይዘቱ አፀያፊነት የተከሳሹን መጥፎና አስፈሪ የሆነ አስተሳሰቡን ያሳያል" ያሉት ዳኛዋ አንድሪውስ ተበዳዮቹ የሰጡትን ምስል በማሰራጨት ለእሱ ደስታ የሚሆኑ ተጨማሪ ነገሮችንም እንዲልኩለት እነሱንና ጓደኞቻቸውንም ያስፈራራ እንደነበር ተናግረዋል።
የተጠቂዎቹ ቁጥር እየጨመረ በሄደ ቁጥር እሱም የወንጀል ዱካዉን ለመሸፈን ጥረት ሲያደርግ እየሞከረ መቆየቱን አክለዋል።
የሚፈጸምበት መንገድ ይለያይ እንጂ በእኛም ሀገር ተመሳሳይ ጥቃቶች ይፈጸማሉ። ቤተሰብ ከልጆቹ ጋር ያለውን ቅርበት በማጠናከር ከተመሳሳይ ጥቃት ልጆችን መጠበቅ፤ የጥቃቱ ሰለባ የሆኑ ልጆችን ከዚህ ሂደት እንዲወጡ ከባለሞያ ጋር ማገዝ ከምንም በላይ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነው።
Source : Sky News
@TikvahethMagazine
በሰሜናዊ አየርላንድ የሚኖረው የ55 ዓመቱ ዴቪድ ጆን አንድሪውስ በ130 የወሲብ ጥቃቶች ተከሶ የ27 ዓመት እስራት ተፈርዶበታል።
ከዚህ ውስጥ 46ቱ ህፃናት ናቸው ተብሏል። ጥቃት ካደረሰባቸው ህፃናትም ውስጥ በዕድሜ ትንሿ የ8 ዓመት ህፃን ናት።
ወንጀለኛው ጥቃቱን የፈጸመው እንዴት ነው ?
ጥቃት አድራሹ እራሱን በ አስራዎቹ እንደሚገኝ ታዳጊ አስመስሎ በ snapchat እና በ instagram ገፅ ላይ ለጥፎ 50 የሚደርሱ ህፃናት ላይ ጥቃት በማድረስ ነው ጥቃቱን ሲያደርስ የነበረው።
በተደረገው ምርመራም መርማሪዎቹ 10,000 የሚጠጉ ህገ-ወጥ የህፃናት ምስሎችን በአንድሪውስ የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያው ላይ ያገኙ ሲሆን በአስራዎቹ እንዳለ ታዳጊ መስሎ ለመለጠፍ የተጠቀመባቸውን 40 የሚሆኑ የመለያ ስሞችም (user names) ተገኝቷል።
አብዛኛዎቹ ወንጀሎች "ካትፊሺንግ" ማለትም አንድ ሰው የሌላን ሰውን ምስል እንደራሱ አድርጎ ማቅረብ ጋር የሚያያዝ ነው።
ወንጀሎቹ በፍርድ ቤቱ ሲቀርቡ የአስገድዶ መድፈር ሙከራ ፣ከ13 ዓመት በታች የሆነን ልጅ ወሲባዊ ተግባር እንዲፈፅም ማድረግ ወይም መገፋፋት፣ ወሲብ ነክ የሆኑ መልዕክቶችን ወይም ንግግሮችን ማድረግ፣ ማስፈራራት ይገኙበታል።
በተጨማሪም ህፃናት የወሲብ አገልግሎቶችን እንዲፈፅሙ ገንዘብ ለመክፈል ሙከራ ማድረግ፣ የህፃናትን የወሲብ ንግድ ወይም ፖርኖግራፌን ማዘጋጀት ወይም ማመቻቸት፣ ተገቢ ያልሆኑ ምስሎችን መያዝ ይገኙበታል።
በዳውንፓትሪክ ክራውን ፍርድ ቤት የተሰየሙት ዳኛ ጂኦፍሪ ሚለር "እሱ ራሱ ልጅ ነው በሚል የተሳሳተ እምነት ልጆቹን አታሏቸዋል ... ይህን ካደረገ በኋላ በጣም ጥንቃቄ በተሞላበት ሁኔታ ከሱ ጋር በማህበራዊ ሚዲያ ምስል እንዲያጋሩት የተለያዮ ማስፈራሪያዎችንና ማሳመኛ መንገዶችን ይጠቀም ነበር" ሲሉ ይገልጻሉ።
"ከእያንዳንዱ ልጅ ጋር የተለዋወጠው መልዕክት የይዘቱ አፀያፊነት የተከሳሹን መጥፎና አስፈሪ የሆነ አስተሳሰቡን ያሳያል" ያሉት ዳኛዋ አንድሪውስ ተበዳዮቹ የሰጡትን ምስል በማሰራጨት ለእሱ ደስታ የሚሆኑ ተጨማሪ ነገሮችንም እንዲልኩለት እነሱንና ጓደኞቻቸውንም ያስፈራራ እንደነበር ተናግረዋል።
የተጠቂዎቹ ቁጥር እየጨመረ በሄደ ቁጥር እሱም የወንጀል ዱካዉን ለመሸፈን ጥረት ሲያደርግ እየሞከረ መቆየቱን አክለዋል።
የሚፈጸምበት መንገድ ይለያይ እንጂ በእኛም ሀገር ተመሳሳይ ጥቃቶች ይፈጸማሉ። ቤተሰብ ከልጆቹ ጋር ያለውን ቅርበት በማጠናከር ከተመሳሳይ ጥቃት ልጆችን መጠበቅ፤ የጥቃቱ ሰለባ የሆኑ ልጆችን ከዚህ ሂደት እንዲወጡ ከባለሞያ ጋር ማገዝ ከምንም በላይ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነው።
Source : Sky News
@TikvahethMagazine
👏50❤16😨4😡3🕊2
በኦሮሚያ ክልል ባሉ ከተሞች የኤች አይ ቪ ኤድስ ሥርጭት ከ2 -3 % እንደሚደርስ ተገለጸ።
በኦሮሚያ ክልል ያለውን የኤች አይ ቪ ኤድስ ሥርጭትን በተመለከተ በዛሬው ዕለት የክልሉ ጤና ቢሮ በሰጠው መግለጫ ላይ ተነስቷል።
መግለጫውን የቢሮው ምክትል ኃላፊ ዶ/ር ጉሻ ባላኮ የሰጡ ሲሆን በክልሉ 157,226 ሰዎች ከቫይረሱ ጋር አብረው እንደሚኖሩና 131,278 የሚሆኑ ዜጎች መድኃኒት መጠቀም መጀመራቸውን ጠቅሰዋል።
በተጨማሪም፦
- በ2016 ሦስት ሚሊዮን ሰዎች የኤች አይ ቪ ምርመራ አድርገው 10,267 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን ማወቃቸውን፤
- ባለፉት አምስት አመታት 44,993 የሚሆኑ ዜጎች አዲስ ቫይረሱ እንዳለባቸው አውቀው መድኃኒት መጀመራቸውን፤
- 7,703 የሚሆኑ ዜጎች ባለፉት 5 ዓመታት በቫይረሱ ሳቢያ ህይወታቸው ማለፉን ገልጸዋል።
ዶ/ር ጉሻ አክለውም፥ በክልሉ ያለው አጠቃላይ የቫይረሱ የሥርጭት መጠን 0.6% መሆኑን አንስተው፥ ይህ ቁጥር በከተሞች ሲሆን ወደ 2-3% ከፍ እንደሚል ነው የተናገሩት።
የኤችአይቪ ስርጭት በጣም የከፋው ሰሜን ሸዋ፣ ምዕራብ ጉጂ፣ ሆሮሮ ጉዱሩ ወለጋ፣ ጉጂ፣ ምስራቅ ሸዋ እና ደቡብ ምዕራብ ሸዋ አከባቢዎች መሆኑንም ተናግረዋል።
በክልሉ የትኞቹ ከተሞች የኤችአይቪ ሥርጭት በስፋት ታይቶባቸዋል?
እንደ ምክትል ኃላፊው ገለጻ የሥርጭት መጠኑ ከፍተኛ ብለው ያስቀመጧቸው፦
- ሞጆ
- አሰላ
- አዳማ
- ቢሾፍቱ
- አምቦ
- መቱ
- ነቃምቴ
- ሻኪሶ
- ሮቤ
- ሸገር
- ጅማ ናቸው።
ኤች አይ ቪ ከእናት ወደ ልጅ የሚተላለፍበት መጠን በሀገር አቀፍ ደረጃ 8.64% ሲሆን በክልሉ ደግሞ 7.48% መሆኑን ዶ/ር ጉሾ ባላኮ በመግለጫው ወቅት የተናገሩት።
መረጃው የኦሮሚያ ኮሚኒኬሽን ቢሮ ነው።
@TikvahethMagazine
በኦሮሚያ ክልል ያለውን የኤች አይ ቪ ኤድስ ሥርጭትን በተመለከተ በዛሬው ዕለት የክልሉ ጤና ቢሮ በሰጠው መግለጫ ላይ ተነስቷል።
መግለጫውን የቢሮው ምክትል ኃላፊ ዶ/ር ጉሻ ባላኮ የሰጡ ሲሆን በክልሉ 157,226 ሰዎች ከቫይረሱ ጋር አብረው እንደሚኖሩና 131,278 የሚሆኑ ዜጎች መድኃኒት መጠቀም መጀመራቸውን ጠቅሰዋል።
በተጨማሪም፦
- በ2016 ሦስት ሚሊዮን ሰዎች የኤች አይ ቪ ምርመራ አድርገው 10,267 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውን ማወቃቸውን፤
- ባለፉት አምስት አመታት 44,993 የሚሆኑ ዜጎች አዲስ ቫይረሱ እንዳለባቸው አውቀው መድኃኒት መጀመራቸውን፤
- 7,703 የሚሆኑ ዜጎች ባለፉት 5 ዓመታት በቫይረሱ ሳቢያ ህይወታቸው ማለፉን ገልጸዋል።
ዶ/ር ጉሻ አክለውም፥ በክልሉ ያለው አጠቃላይ የቫይረሱ የሥርጭት መጠን 0.6% መሆኑን አንስተው፥ ይህ ቁጥር በከተሞች ሲሆን ወደ 2-3% ከፍ እንደሚል ነው የተናገሩት።
የኤችአይቪ ስርጭት በጣም የከፋው ሰሜን ሸዋ፣ ምዕራብ ጉጂ፣ ሆሮሮ ጉዱሩ ወለጋ፣ ጉጂ፣ ምስራቅ ሸዋ እና ደቡብ ምዕራብ ሸዋ አከባቢዎች መሆኑንም ተናግረዋል።
በክልሉ የትኞቹ ከተሞች የኤችአይቪ ሥርጭት በስፋት ታይቶባቸዋል?
እንደ ምክትል ኃላፊው ገለጻ የሥርጭት መጠኑ ከፍተኛ ብለው ያስቀመጧቸው፦
- ሞጆ
- አሰላ
- አዳማ
- ቢሾፍቱ
- አምቦ
- መቱ
- ነቃምቴ
- ሻኪሶ
- ሮቤ
- ሸገር
- ጅማ ናቸው።
ኤች አይ ቪ ከእናት ወደ ልጅ የሚተላለፍበት መጠን በሀገር አቀፍ ደረጃ 8.64% ሲሆን በክልሉ ደግሞ 7.48% መሆኑን ዶ/ር ጉሾ ባላኮ በመግለጫው ወቅት የተናገሩት።
መረጃው የኦሮሚያ ኮሚኒኬሽን ቢሮ ነው።
@TikvahethMagazine
❤40😢13😡6🤔1
2023 SY20 የተሰኘው አስትሮይድ በ18 ኢትዮጵያዊያን ተማሪዎች ግኝትነት ተመዘገበ።
በኢትዮጵያ የስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ የማኅበረሰብ አቀፍ ሳይንስ ፕሮጀክት ሥር የሚገኘው የኢትዮ-አስቴሮይድ አዳኞች ክለብ አዲስ 2023 SY20 የተባለ የምልምል አስቴሮይድ ግኝት ማግኘቱን ይፋ አድርጓል።
ይኸው ግኝት 18 የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች የአስትሮይዱን እንቅስቃሴ ከዓመት በፊት በማስተዋል ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን ከቀናት በፊት የዓለም አቀፉ የሥነ-ፈለካዊ ፍለጋ ትብብር ( IASC ) ግኝቱን አጽድቋል።
ይህም በኢትዮጵያውያን ዜጋ ሳይንቲስቶች የተገኘ የመጀመሪያው የአስትሮይድ ግኝት ያደርገዋል ተብሏል።
ምልምል አስቴሮይዱ ሊገኝ የቻለው በPan-STARRS የሕዋ ምልከታ ጣቢያ በተነሱ ምስሎች ሲሆን ፤ ተማሪዎቹ እነዚህን ምስሎች በመጠቀም እና ልየታ በማካሄድ ይህን ምልምል ምልምል አስቴሮይድ ሊያገኙ ችለዋል ሲል የኢትዮጵያ የስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ ለቲክቫህ በላከው መግለጫ አስታውቋል።
ይህ ፕሮግራም በዓለም አቀፉ የሥነፈለካዊ ፍለጋ ትብብር ( IASC ) የፓን-አፍሪካን የአስቴሮይድ ፍለጋ ንቅናቄ አማካኝነት የሚተገበር ነው።
በሌሎች አፍሪካ ሀገራት የሚገኙ ወጣቶችም በግልም ይሁን በጋራ ተመሳሳይ የአስትሮይድ ፍለጋ ፕሮጀክቱ ላይ ተሳታፊ ሲሆኑ ከአንድ በላይ ያስመዘገቡም እንደሚገኙ መረጃዎች ያሳያሉ።
@TikvahethMagazine
በኢትዮጵያ የስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ የማኅበረሰብ አቀፍ ሳይንስ ፕሮጀክት ሥር የሚገኘው የኢትዮ-አስቴሮይድ አዳኞች ክለብ አዲስ 2023 SY20 የተባለ የምልምል አስቴሮይድ ግኝት ማግኘቱን ይፋ አድርጓል።
ይኸው ግኝት 18 የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች የአስትሮይዱን እንቅስቃሴ ከዓመት በፊት በማስተዋል ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን ከቀናት በፊት የዓለም አቀፉ የሥነ-ፈለካዊ ፍለጋ ትብብር ( IASC ) ግኝቱን አጽድቋል።
ይህም በኢትዮጵያውያን ዜጋ ሳይንቲስቶች የተገኘ የመጀመሪያው የአስትሮይድ ግኝት ያደርገዋል ተብሏል።
ምልምል አስቴሮይዱ ሊገኝ የቻለው በPan-STARRS የሕዋ ምልከታ ጣቢያ በተነሱ ምስሎች ሲሆን ፤ ተማሪዎቹ እነዚህን ምስሎች በመጠቀም እና ልየታ በማካሄድ ይህን ምልምል ምልምል አስቴሮይድ ሊያገኙ ችለዋል ሲል የኢትዮጵያ የስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ ለቲክቫህ በላከው መግለጫ አስታውቋል።
ይህ ፕሮግራም በዓለም አቀፉ የሥነፈለካዊ ፍለጋ ትብብር ( IASC ) የፓን-አፍሪካን የአስቴሮይድ ፍለጋ ንቅናቄ አማካኝነት የሚተገበር ነው።
በሌሎች አፍሪካ ሀገራት የሚገኙ ወጣቶችም በግልም ይሁን በጋራ ተመሳሳይ የአስትሮይድ ፍለጋ ፕሮጀክቱ ላይ ተሳታፊ ሲሆኑ ከአንድ በላይ ያስመዘገቡም እንደሚገኙ መረጃዎች ያሳያሉ።
@TikvahethMagazine
👏201❤28🤔4😡4😨3👍1😢1
𝐍𝐞𝐰 𝐓𝐫𝐚𝐢𝐧𝐢𝐧𝐠 𝐏𝐫𝐨𝐠𝐫𝐚𝐦 𝐀𝐧𝐧𝐨𝐮𝐧𝐜𝐞𝐦𝐞𝐧𝐭 📣📣📣
"National Customs Procedure" Second Round Training
For More Information join our channel @EFFSAAtrainingcenter
and Registration,
📱 +251 903 182525
📞 +251 115 589045
📍 Kazanchis, Nigist Towers Hotel and Apartments, 4th floor (In front of Elilly Hotel)
"National Customs Procedure" Second Round Training
For More Information join our channel @EFFSAAtrainingcenter
and Registration,
📱 +251 903 182525
📞 +251 115 589045
📍 Kazanchis, Nigist Towers Hotel and Apartments, 4th floor (In front of Elilly Hotel)
❤1
TIKVAH-MAGAZINE
ኢትዮጵያ አሁን ላይ ከ1ሚሊዮን በላይ ፍልሰተኞችን እያስተናገደች ትገኛለች። ኢትዮጵያ አሁን ላይ ከ1ሚሊዮን ሰባ አንድ ሺ በላይ ፍልሰተኞችንና ጥገኝነት ጠያቂዎችን እያስተናገደች ያለች መሆኑን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ከፍተኛው የሥደተኞች ኮሚሽን (UNHCR) ቁጥራዊ መረጃዎች ያሳያሉ። ከዚህ ውስጥ 80 በመቶ የሚሆኑት ሴቶች እና ህጻናት መሆናቸው ሲገለጽ 54 በመቶ የሚሆኑት ደግሞ እድሜያቸው 0-…
#Update
° "ኤርትራውያን ስደተኞችና ጥገኝነት ጠያቂዎች ለእስርና እንግልት እየተዳረጉ ነው በሚል የሚሰራጨው መረጃ ትክክል አይደለም" - የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ከፍተኛው የሥደተኞች ኮሚሽን (UNHCR) በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል ትግራይና አፋር ክልል በኩል ከኤርትራ የሚገቡ ስደተኞች ጥበቃ እና ከለላ ያስፈልጋቸዋል ሲል በሪፖርቱ ጠቅሶ እንደነበር ይታወሳል።
ቢቢሲ በሰራው ዘገባም በአዲስ አበባ የሚገኙ ኤርትራውያን ስደተኞች መጠነ ሰፊ እስራት እየተፈጸመባቸው ፖሊስ የሚወስደው ርምጃ እየተጠናከረ መምጣቱን ዘግቦ ነበር።
ይህን ተከትሎም የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት በጉዳዩ ላይ ከደቂቃዎች በፊት መግለጫ አውጥቷል።
አገልግሎቱ በመግለጫው፥ የሚዲያዎቹን ዘገባ ተከትሎ አደረኩት ባለው ማጣራት፣ ሕጋዊ የስደተኝነት ዕውቅና ኖሯቸው ለእስርና እንግልት የተዳረጉ ስደተኞች በሀገሪቱ አለመኖራቸውን አረጋግጫለሁ ብሏል።
በዚህም በሀገሪቱ የሚገኙ ኤርትራውያን ስደተኞችና ጥገኝነት ጠያቂዎች ላይ ያነጣጠረ የዘፈቀደ እስርና እንግልት እየተከናወነ ነው በሚል በሀገር ውስጥና በውጭ ሚዲያ አውታሮች የተሰሩ ዘገባዎችን ተቋሙ "መሠረተ ቢስ" ሲል አጣጥሎታል።
አክሎም፥ ስደተኞች የሀገሪቱን ሕግና ሥርዓት ጥሰው ለእስር የተዳረጉበት ሁኔታ የሚኖር ከሆነ፣ አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት የሚከታተለው ይሆናል ሲል አክሎ ገልጿል፡፡
በተጨማሪም የስደተኞች ምዝገባ ቆሟል በሚል ሚዲያው የሚያሰራጨው መረጃም ከእውነት የራቀ ነው ያለው አገልግሎቱ፥ "የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት የስደተኝነት መስፈርትን ለሚያሟሉ አካላት ምንም ልዩነት ሳያደርግ የምዝገባ አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቷል፤ እየሰጠም ይገኛል" ብሏል፡፡
የወሳኝ ኩነት ምዝገባና የምስክር ወረቀት አገልግሎትን ጨምሮ የስደተኝነት መታወቂያ የመስጠት ተግባር ከበፊቱ በተጠናከረና በተደራጀ መልኩ እየተከናወነ መሆኑንም ተቋሙ ገልጿል።
ኢትዮጵያ ከ26 ሀገራት ከለላና ጥበቃ ፈልገው ለመጡ ከ1.1 ሚሊዮን በላይ ስደተኞችና ጥገኝነት ጠያቂዎች ከለላና ጥበቃ እየሰጠች ትገኛለች፡፡ ከነዚህ ውስጥ አብዛኛውን ቁጥር የሚይዙት ከጎረቤት ደቡብ ሱዳን፣ ሶማሊያ፣ ሱዳንና ኤርትራ የሚመጡ ስደተኞች ናቸው፡፡
#Ethiopia
#Eritrea
#Refugees
@TikvahethMagazine
° "ኤርትራውያን ስደተኞችና ጥገኝነት ጠያቂዎች ለእስርና እንግልት እየተዳረጉ ነው በሚል የሚሰራጨው መረጃ ትክክል አይደለም" - የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ከፍተኛው የሥደተኞች ኮሚሽን (UNHCR) በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል ትግራይና አፋር ክልል በኩል ከኤርትራ የሚገቡ ስደተኞች ጥበቃ እና ከለላ ያስፈልጋቸዋል ሲል በሪፖርቱ ጠቅሶ እንደነበር ይታወሳል።
ቢቢሲ በሰራው ዘገባም በአዲስ አበባ የሚገኙ ኤርትራውያን ስደተኞች መጠነ ሰፊ እስራት እየተፈጸመባቸው ፖሊስ የሚወስደው ርምጃ እየተጠናከረ መምጣቱን ዘግቦ ነበር።
ይህን ተከትሎም የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት በጉዳዩ ላይ ከደቂቃዎች በፊት መግለጫ አውጥቷል።
አገልግሎቱ በመግለጫው፥ የሚዲያዎቹን ዘገባ ተከትሎ አደረኩት ባለው ማጣራት፣ ሕጋዊ የስደተኝነት ዕውቅና ኖሯቸው ለእስርና እንግልት የተዳረጉ ስደተኞች በሀገሪቱ አለመኖራቸውን አረጋግጫለሁ ብሏል።
በዚህም በሀገሪቱ የሚገኙ ኤርትራውያን ስደተኞችና ጥገኝነት ጠያቂዎች ላይ ያነጣጠረ የዘፈቀደ እስርና እንግልት እየተከናወነ ነው በሚል በሀገር ውስጥና በውጭ ሚዲያ አውታሮች የተሰሩ ዘገባዎችን ተቋሙ "መሠረተ ቢስ" ሲል አጣጥሎታል።
አክሎም፥ ስደተኞች የሀገሪቱን ሕግና ሥርዓት ጥሰው ለእስር የተዳረጉበት ሁኔታ የሚኖር ከሆነ፣ አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት የሚከታተለው ይሆናል ሲል አክሎ ገልጿል፡፡
በተጨማሪም የስደተኞች ምዝገባ ቆሟል በሚል ሚዲያው የሚያሰራጨው መረጃም ከእውነት የራቀ ነው ያለው አገልግሎቱ፥ "የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት የስደተኝነት መስፈርትን ለሚያሟሉ አካላት ምንም ልዩነት ሳያደርግ የምዝገባ አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቷል፤ እየሰጠም ይገኛል" ብሏል፡፡
የወሳኝ ኩነት ምዝገባና የምስክር ወረቀት አገልግሎትን ጨምሮ የስደተኝነት መታወቂያ የመስጠት ተግባር ከበፊቱ በተጠናከረና በተደራጀ መልኩ እየተከናወነ መሆኑንም ተቋሙ ገልጿል።
ኢትዮጵያ ከ26 ሀገራት ከለላና ጥበቃ ፈልገው ለመጡ ከ1.1 ሚሊዮን በላይ ስደተኞችና ጥገኝነት ጠያቂዎች ከለላና ጥበቃ እየሰጠች ትገኛለች፡፡ ከነዚህ ውስጥ አብዛኛውን ቁጥር የሚይዙት ከጎረቤት ደቡብ ሱዳን፣ ሶማሊያ፣ ሱዳንና ኤርትራ የሚመጡ ስደተኞች ናቸው፡፡
#Ethiopia
#Eritrea
#Refugees
@TikvahethMagazine
😡19❤6👏5
#የሥራ_ማስታወቂያ
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በ81 የሥራ መደቦች በዜሮ ዓመት የሥራ ልምድ ከ800 በላይ እንዲሁም የሥራ ልምድ በሚጠይቁ 41 የሥራ መደቦች ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር እንደሚፈልግ አስታውቋል።
አመልካቾች ከታህሳስ 9 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ቅዳሜን ጨምሮ ባሉት 15(አስራ አምስት) ተከታታይ የሥራ ቀናት አስፈላጊ የትምህርትና የሥራ ልምድ ማስረጃችሁን ዋናውንና የማይመለስ ፎቶ ኮፒ በመያዝ፦
📍 በአዲስ አበባ ከተማ ፒያሳ እናት ህንፃ አጠገብ በሚገኘው የተቋሙ ቢሮ፣
📍 በድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት፣
እንዲሁም በሁሉም ክልሎች የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት በአካል ቀርባችሁ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን ተቋሙ ገልጿል።
ስራ ልምድ ለሚጠይቁ የሥራ መደቦች አመልካቾች አግባብነት ያለው የሥራ ልምድ ማቅረብ የሚጠበቅባቸው ሲሆን ዜሮ ዓመት ዲግሪ የትምህርት ደረጃ ለሚጠይቁ ስራ መደቦች ላይ ደግሞ የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተና (Exit Exam) ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
እንዲሁም የዩኒቨርስቲ መመረቂያ ውጤት ለወንድ 2.5 እና ለሴት 2.00 መሆን አለበት። የትምህርት ደረጃ /Level/ ለሚጠይቁ ስራ መደቦች የCOC ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባችኋልም ተብሏል።
ዜሮ ዓመት ለሚጠይቁ ስራ መደቦች ላይ የሚያመለክቱ ተወዳደሪዎች ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ የተመረቁ መሆን አለባቸው የተባለ ሲሆን መስፈርቱን አሟልተው ለሚመረጡ ተወዳዳሪዎች ተቋሙ የሚሰጠውን ስልጠና ለመውሰድ ፍቃደኛ መሆንና ተቋሙ በሚመድብበት ቦታ ለመስራት ፈቃደኛ መሆን ይጠበቅባቸዋል።
የተለያዩ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ሀገር ቋንቋ ክህሎት ያላቸው እንዲሁም መሠረታዊ የኮምፒዩተር ክህሎት (Basic computer skill) ያላቸው ተወዳዳሪዎች ይበረታታሉ ተብሏል።
❗️ ተቋሙ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ማስታወቂያውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ ሊሰርዝው እንደሚችል ጠቁሟል።
ዝርዝሩን ይመልከቱ https://ics.gov.et/job/national-job-opening
#Share
@TikvahethMagazine
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በ81 የሥራ መደቦች በዜሮ ዓመት የሥራ ልምድ ከ800 በላይ እንዲሁም የሥራ ልምድ በሚጠይቁ 41 የሥራ መደቦች ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር እንደሚፈልግ አስታውቋል።
አመልካቾች ከታህሳስ 9 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ቅዳሜን ጨምሮ ባሉት 15(አስራ አምስት) ተከታታይ የሥራ ቀናት አስፈላጊ የትምህርትና የሥራ ልምድ ማስረጃችሁን ዋናውንና የማይመለስ ፎቶ ኮፒ በመያዝ፦
እንዲሁም በሁሉም ክልሎች የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት በአካል ቀርባችሁ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን ተቋሙ ገልጿል።
ስራ ልምድ ለሚጠይቁ የሥራ መደቦች አመልካቾች አግባብነት ያለው የሥራ ልምድ ማቅረብ የሚጠበቅባቸው ሲሆን ዜሮ ዓመት ዲግሪ የትምህርት ደረጃ ለሚጠይቁ ስራ መደቦች ላይ ደግሞ የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተና (Exit Exam) ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
እንዲሁም የዩኒቨርስቲ መመረቂያ ውጤት ለወንድ 2.5 እና ለሴት 2.00 መሆን አለበት። የትምህርት ደረጃ /Level/ ለሚጠይቁ ስራ መደቦች የCOC ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባችኋልም ተብሏል።
ዜሮ ዓመት ለሚጠይቁ ስራ መደቦች ላይ የሚያመለክቱ ተወዳደሪዎች ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ የተመረቁ መሆን አለባቸው የተባለ ሲሆን መስፈርቱን አሟልተው ለሚመረጡ ተወዳዳሪዎች ተቋሙ የሚሰጠውን ስልጠና ለመውሰድ ፍቃደኛ መሆንና ተቋሙ በሚመድብበት ቦታ ለመስራት ፈቃደኛ መሆን ይጠበቅባቸዋል።
የተለያዩ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ሀገር ቋንቋ ክህሎት ያላቸው እንዲሁም መሠረታዊ የኮምፒዩተር ክህሎት (Basic computer skill) ያላቸው ተወዳዳሪዎች ይበረታታሉ ተብሏል።
ዝርዝሩን ይመልከቱ https://ics.gov.et/job/national-job-opening
#Share
@TikvahethMagazine
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
👏55❤27😡9😨4👍2😢2
𝐍𝐞𝐰 𝐓𝐫𝐚𝐢𝐧𝐢𝐧𝐠 𝐏𝐫𝐨𝐠𝐫𝐚𝐦 𝐀𝐧𝐧𝐨𝐮𝐧𝐜𝐞𝐦𝐞𝐧𝐭 📣📣📣
"National Customs Procedure" Second Round Training
For More Information join our channel @EFFSAAtrainingcenter
and Registration,
📱 +251 903 182525
📞 +251 115 589045
📍 Kazanchis, Nigist Towers Hotel and Apartments, 4th floor (In front of Elilly Hotel)
"National Customs Procedure" Second Round Training
For More Information join our channel @EFFSAAtrainingcenter
and Registration,
📱 +251 903 182525
📞 +251 115 589045
📍 Kazanchis, Nigist Towers Hotel and Apartments, 4th floor (In front of Elilly Hotel)
❤2
TIKVAH-MAGAZINE
#Update ° "ኤርትራውያን ስደተኞችና ጥገኝነት ጠያቂዎች ለእስርና እንግልት እየተዳረጉ ነው በሚል የሚሰራጨው መረጃ ትክክል አይደለም" - የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ከፍተኛው የሥደተኞች ኮሚሽን (UNHCR) በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል ትግራይና አፋር ክልል በኩል ከኤርትራ የሚገቡ ስደተኞች ጥበቃ እና ከለላ ያስፈልጋቸዋል ሲል በሪፖርቱ ጠቅሶ እንደነበር ይታወሳል። ቢቢሲ…
#Update
° "ቁጥራቸው ቀላል የማይባል የውጭ አገር ሰዎች ባልተፈቀደላቸው የሥራ መስክ ተሰማርተው ይገኛሉ"
° "ማንኛውም የውጭ አገር ዜጋ የአገራችንን ህግ ተላልፎ ከተገኘ በህግ ተጠያቂ ይሆናል" - የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት
ኤርትራውያን ስደተኞችና ጥገኝነት ጠያቂዎች ለእስርና እንግልት እየተዳረጉ ነው በሚል የተሰሩ ዘገባዎችን አስመልክቶ በትላንትናው ዕለት የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት "ሕጋዊ የስደተኝነት ዕውቅና ኖሯቸው ለእስርና እንግልት የተዳረጉ ስደተኞች በሀገሪቱ የሉም" የሚል መግለጫ ማውጣቱ ይታወሳል።
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በበኩሉ በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ የህግ ጥሰት የፈፀሙ የውጭ ዜጎችን የተመለከተ ማብራሪያ ሰጥቷል።
በመግለጫውም ከጎረቤት አገራት ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ ዜጎች ለ9ዐ ቀናት ያለ ቪዛ ክፍያ በቀን ማህተም ገብተው እንዲቆዩ መፈቀዱን አስታውሷል።
ቁጥራቸው ቀላል የማይባል የውጭ አገር ሰዎች የስራ ፈቃድና መኖሪያ ፈቃድ ሳይኖራቸው ባልተፈቀደላቸው የሥራ መስክና ህገወጥ የማዕድን፣ የገንዘብ፣ አደገኛ እፅ፣ የሰዎች ዝውውርና መሰል ህገወጥ ተግባራት ላይ ተሰማርተው ይገኛሉ ብሏል።
በተለይ በርካታ ኤርትራዊያን ወደ ሀገር የሚገቡት በህገወጥ መንገድ ነው ያለው መግለጫው ከተፈቀደላቸው የጊዜ ገደብ በላይ በመቆየት በህገ-ወጥ መንገድ እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ ሲል ከሷል።
በዚህም
- ለውጭ አገር ዜጎች ባልተፈቀዱ የስራ መስኮች በመሰማራት በህገወጥ መንገድ ከትንሸ ሱቅ ችርቻሮ እስከ ያልተፈቀዱ ትላልቅ ስራዎች ተሰማርተው ሳለ፤
- በርካታ የኤርትራዊ ዜግነት ያላቸው ዘመድ ለመጠየቅ በማስመስል ከዱባይ፣ ከኤርትራ፣ ከኡጋንዳ በመመላለስ የኮንትሮባንድ እና ሌሎች ህገወጥ ተግባራት ሲያከናውኑ፤
- በተለያዩ አገራት ከሚገኙ ሌሎች ህገ-ወጥ ደላሎች ጋር በመተሳሰር ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ሲሳተፉ፤
- ለተለያዩ ሕገወጥ ተግባራት የሚያገለገሉ ሐሰተኛና የተጭበረበሩ የጉዞና የይለፍ ሰነዶች፣ ማህተሞች፣ የባንክ ቡኮች በማዘጋጀትና በመጠቀም ህገ-ወጥ ተግባራት ሲፈጽሙ ተገኝተዋል ብሏል።
መግለጫው አክሎም ማንኛውም የውጭ አገር ዜጋ የአገራችንን ህግ ተላልፎ ከተገኘ በህግ ተጠያቂ ይሆናል። ይህ ግን በአንድ ሀገር ዜጋ ብቻ ተፈጻሚ የሚደርግ አሰራር ተደርጎ በአንድ አንድ ሚድያዎች መዘገቡ ስህተት ነው ብሏል።
በተጨማሪም በስደተኝነት የተመዘገበ ማንኛውም የኤርትራዊ ዜግነት ያለው ሰው ያለ ፈቃዱ ከአገር እንዲወጣ እና ተገቢነት የሌለው ክፍያ እንዲክፍል የተደርግ ሰው የለም ብሏል።
ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል።
@TikvahethMagazine
° "ቁጥራቸው ቀላል የማይባል የውጭ አገር ሰዎች ባልተፈቀደላቸው የሥራ መስክ ተሰማርተው ይገኛሉ"
° "ማንኛውም የውጭ አገር ዜጋ የአገራችንን ህግ ተላልፎ ከተገኘ በህግ ተጠያቂ ይሆናል" - የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት
ኤርትራውያን ስደተኞችና ጥገኝነት ጠያቂዎች ለእስርና እንግልት እየተዳረጉ ነው በሚል የተሰሩ ዘገባዎችን አስመልክቶ በትላንትናው ዕለት የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት "ሕጋዊ የስደተኝነት ዕውቅና ኖሯቸው ለእስርና እንግልት የተዳረጉ ስደተኞች በሀገሪቱ የሉም" የሚል መግለጫ ማውጣቱ ይታወሳል።
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በበኩሉ በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ የህግ ጥሰት የፈፀሙ የውጭ ዜጎችን የተመለከተ ማብራሪያ ሰጥቷል።
በመግለጫውም ከጎረቤት አገራት ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ ዜጎች ለ9ዐ ቀናት ያለ ቪዛ ክፍያ በቀን ማህተም ገብተው እንዲቆዩ መፈቀዱን አስታውሷል።
ቁጥራቸው ቀላል የማይባል የውጭ አገር ሰዎች የስራ ፈቃድና መኖሪያ ፈቃድ ሳይኖራቸው ባልተፈቀደላቸው የሥራ መስክና ህገወጥ የማዕድን፣ የገንዘብ፣ አደገኛ እፅ፣ የሰዎች ዝውውርና መሰል ህገወጥ ተግባራት ላይ ተሰማርተው ይገኛሉ ብሏል።
በተለይ በርካታ ኤርትራዊያን ወደ ሀገር የሚገቡት በህገወጥ መንገድ ነው ያለው መግለጫው ከተፈቀደላቸው የጊዜ ገደብ በላይ በመቆየት በህገ-ወጥ መንገድ እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ ሲል ከሷል።
በዚህም
- ለውጭ አገር ዜጎች ባልተፈቀዱ የስራ መስኮች በመሰማራት በህገወጥ መንገድ ከትንሸ ሱቅ ችርቻሮ እስከ ያልተፈቀዱ ትላልቅ ስራዎች ተሰማርተው ሳለ፤
- በርካታ የኤርትራዊ ዜግነት ያላቸው ዘመድ ለመጠየቅ በማስመስል ከዱባይ፣ ከኤርትራ፣ ከኡጋንዳ በመመላለስ የኮንትሮባንድ እና ሌሎች ህገወጥ ተግባራት ሲያከናውኑ፤
- በተለያዩ አገራት ከሚገኙ ሌሎች ህገ-ወጥ ደላሎች ጋር በመተሳሰር ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ሲሳተፉ፤
- ለተለያዩ ሕገወጥ ተግባራት የሚያገለገሉ ሐሰተኛና የተጭበረበሩ የጉዞና የይለፍ ሰነዶች፣ ማህተሞች፣ የባንክ ቡኮች በማዘጋጀትና በመጠቀም ህገ-ወጥ ተግባራት ሲፈጽሙ ተገኝተዋል ብሏል።
መግለጫው አክሎም ማንኛውም የውጭ አገር ዜጋ የአገራችንን ህግ ተላልፎ ከተገኘ በህግ ተጠያቂ ይሆናል። ይህ ግን በአንድ ሀገር ዜጋ ብቻ ተፈጻሚ የሚደርግ አሰራር ተደርጎ በአንድ አንድ ሚድያዎች መዘገቡ ስህተት ነው ብሏል።
በተጨማሪም በስደተኝነት የተመዘገበ ማንኛውም የኤርትራዊ ዜግነት ያለው ሰው ያለ ፈቃዱ ከአገር እንዲወጣ እና ተገቢነት የሌለው ክፍያ እንዲክፍል የተደርግ ሰው የለም ብሏል።
ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል።
@TikvahethMagazine
👏42❤18😡2🤔1
ከደቡብ ሱዳን ተነስተዉ በሱርማ ወረዳ ከብት ለመዝረፍ የሞከሩ አርብቶአደሮች በቁጥጥር ስር ዋሉ።
ከደቡብ ሱዳን መነሻቸዉን አድርገዉ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በሚገኘዉ ምዕራብ ኦሞ ዞን ሱሪ ወረዳ የአርብቶ አደሮችን ከብቶችን ዘርፈዉ ለመሄድ የሞከሩ 46 የደቡብ ሱዳን አርብቶ አደሮች በቁጥጥር ስር መዋላቸዉን የሠላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ
የኢፌዲሪ የሀገር መከላከያ ሠራዊት፣ የፌዴራል ፖሊስ እና የክልልና የአካባቢዉ ፖሊስ በመቀናጀት በቁጥጥር ስር ማዋላቸዉን የክልሉ ሠላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አንድነት አሸናፊው ገልጸዋል።
የተዘረፉ 250 ከብቶች እና 21 የተለያዩ ጦር መሳሪያዎች መያዛቸዉንና የተመለሱ ከብቶችም ለባለቤቶች የተሰጡ መሆኑን ተናግረዋል።
ዘራፊዎቹ አሁን ላይ በፌደራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር እንደሚገኙ አቶ አንድነት አሸናፊ ገልጸዋል።
መረጃው የክልሉ ኮሚኒኬሽን ቢሮ ነው።
@TikvahethMagazine
ከደቡብ ሱዳን መነሻቸዉን አድርገዉ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በሚገኘዉ ምዕራብ ኦሞ ዞን ሱሪ ወረዳ የአርብቶ አደሮችን ከብቶችን ዘርፈዉ ለመሄድ የሞከሩ 46 የደቡብ ሱዳን አርብቶ አደሮች በቁጥጥር ስር መዋላቸዉን የሠላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ
የኢፌዲሪ የሀገር መከላከያ ሠራዊት፣ የፌዴራል ፖሊስ እና የክልልና የአካባቢዉ ፖሊስ በመቀናጀት በቁጥጥር ስር ማዋላቸዉን የክልሉ ሠላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አንድነት አሸናፊው ገልጸዋል።
የተዘረፉ 250 ከብቶች እና 21 የተለያዩ ጦር መሳሪያዎች መያዛቸዉንና የተመለሱ ከብቶችም ለባለቤቶች የተሰጡ መሆኑን ተናግረዋል።
ዘራፊዎቹ አሁን ላይ በፌደራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር እንደሚገኙ አቶ አንድነት አሸናፊ ገልጸዋል።
መረጃው የክልሉ ኮሚኒኬሽን ቢሮ ነው።
@TikvahethMagazine
👏98❤8🤔3😢2
ቀጣዩ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን የሊቀ-መንበር ማን ይሆናል ?
አፍሪካ ህብረት የሊቀ-መንበርነት ምርጫ በወርሀ የካቲት በ አዲስ አበባ ይካሄዳል። ይህ ምርጫ በየአራት አመቱ የሚካሄድ ሲሆን፣ ተመራጩም የአፍሪካ ህብረት ህጋዊ ተወካይና ዋና የአፍሪካ ህብረት ዋና ሥራ አስፈፃሚ እንዲሁም ኮሚሽኑ የገንዘብ ነክ ጉዳይ የበላይ ሀላፊ ይሆናል።
በ2025 አ.ም በአዲስ አበባ በሚካሄደው 38ተኛው ጉባኤ አዲስ ሊቀ-መንበር ይመረጣል ተመራጩም ሊቀመንበር የአሁኑን የአፍሪካ ህብረት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሙሳ ፋኪ ማህማትን የሚተካ ይሆናል።
በዚህ የምርጫ ፉክክር የቀድሞው የኬንያ ጠቅላይ ሚንስትር ራይላ ኦዲንጋ ለዘንድሮም ምርጫ ከፍተኛ ግምት አግኝተዋል።
ራይላ የአፍሪካ ህብረት የመሰረተ- ልማት ልዩ መልክተኛ ( special Envoy) ሆነው ከ 2018 እስከ 2024 አገልግለዋል።
ራይላ ለአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበነት ቦታ ከሌሎች ተወዳዳሪዎች ከፍተኛ ፉክክር ይገጥማቸዋል ተብሎ ይታሰባል።
ከዚህም መካከለሰ የ59 ዓመቱ የጅቡቲው የውጪ ጉዳይ ሚንስትር መሀሙድ አሊ የሱፍ ሌላው ለምርጫው ከፍተኛ ግምት የተሰጣቸው ናቸው።
የ55 ዓመቱ የ ቀድሞው የማዳጋስካር ሪቻርድ ራንድሪያ ማናድራቶ የኢኮኖሚና የፋይናንስ ሚኒስቴር ለዋና ሥራ አስፈፃሚነት በምርጫው ይወዳደራሉ።
እነዚህ ተወዳዳሪዎች ዛሬ በአፍሪካ ዋና መቀመጫ በአዲስ አበባ አፍሪካን በሚመለከት ያላቸውን እቅድ የፖሊሲ ጉዳዎች እና ቅድሚያ የሚሰጡዋቸው ሀሳቦች ላይ ክርክር ያካሂዳሉ።
የምርጫ ክርክሩ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴሌቪዥን እንዲሁም በሌሎች የኦላይን እና የቀጥታ ስርጭት አማራጮች ከምሽት 1 ሰዓት እስከ 3 ሰዓት ድረስ የሚተላለፍ ይሆናል።
#Mjadala
#TheAfricaWeWant
#AddisAbaba
@TikvahethMagazine
አፍሪካ ህብረት የሊቀ-መንበርነት ምርጫ በወርሀ የካቲት በ አዲስ አበባ ይካሄዳል። ይህ ምርጫ በየአራት አመቱ የሚካሄድ ሲሆን፣ ተመራጩም የአፍሪካ ህብረት ህጋዊ ተወካይና ዋና የአፍሪካ ህብረት ዋና ሥራ አስፈፃሚ እንዲሁም ኮሚሽኑ የገንዘብ ነክ ጉዳይ የበላይ ሀላፊ ይሆናል።
በ2025 አ.ም በአዲስ አበባ በሚካሄደው 38ተኛው ጉባኤ አዲስ ሊቀ-መንበር ይመረጣል ተመራጩም ሊቀመንበር የአሁኑን የአፍሪካ ህብረት ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሙሳ ፋኪ ማህማትን የሚተካ ይሆናል።
በዚህ የምርጫ ፉክክር የቀድሞው የኬንያ ጠቅላይ ሚንስትር ራይላ ኦዲንጋ ለዘንድሮም ምርጫ ከፍተኛ ግምት አግኝተዋል።
ራይላ የአፍሪካ ህብረት የመሰረተ- ልማት ልዩ መልክተኛ ( special Envoy) ሆነው ከ 2018 እስከ 2024 አገልግለዋል።
ራይላ ለአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበነት ቦታ ከሌሎች ተወዳዳሪዎች ከፍተኛ ፉክክር ይገጥማቸዋል ተብሎ ይታሰባል።
ከዚህም መካከለሰ የ59 ዓመቱ የጅቡቲው የውጪ ጉዳይ ሚንስትር መሀሙድ አሊ የሱፍ ሌላው ለምርጫው ከፍተኛ ግምት የተሰጣቸው ናቸው።
የ55 ዓመቱ የ ቀድሞው የማዳጋስካር ሪቻርድ ራንድሪያ ማናድራቶ የኢኮኖሚና የፋይናንስ ሚኒስቴር ለዋና ሥራ አስፈፃሚነት በምርጫው ይወዳደራሉ።
እነዚህ ተወዳዳሪዎች ዛሬ በአፍሪካ ዋና መቀመጫ በአዲስ አበባ አፍሪካን በሚመለከት ያላቸውን እቅድ የፖሊሲ ጉዳዎች እና ቅድሚያ የሚሰጡዋቸው ሀሳቦች ላይ ክርክር ያካሂዳሉ።
የምርጫ ክርክሩ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴሌቪዥን እንዲሁም በሌሎች የኦላይን እና የቀጥታ ስርጭት አማራጮች ከምሽት 1 ሰዓት እስከ 3 ሰዓት ድረስ የሚተላለፍ ይሆናል።
#Mjadala
#TheAfricaWeWant
#AddisAbaba
@TikvahethMagazine
❤20🕊3👍1
TIKVAH-MAGAZINE
Photo
#Update
በሊባኖስ በተከሰተው ጦርነት ምክንያት የተፈናቀሉ እንዲሁም ከዚያ በፊት ወደ አገር ለመመለስ ጠይቀው የመውጫ ቪዛ ሲጠባበቁ የነበሩ 316 ዜጎች ወደ አገራቸው መመለሳቸውን በቤይሩት-ሊባኖስ የኢትዮጵያ ቆንጽላ ጀነራል ጽ/ቤት አስታውቋል።
ከተመለሱት ዜጎች ውስጥ 167 ዜጎች በሊባኖስ በተከሰተው ጦርነት ምክንያት የተፈናቀሉና በሊባኖስ ከአለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት(IOM) ጋር በመተባበር ረቡዕ ታህሳስ 2 ቀን ወደ አገር እንዲመለሱ የተደረጉ ሲሆኑ 17 እናቶችና 22 ህፃናት ይገኙበታል ተብሏል፡፡
በተለያዩ ምክንያቶች የመኖሪያና የሥራ ፈቃድ ሳይኖራቸው በሊባኖስ ረዥም ዓመታት ሲኖሩ የነበሩ ሰነድ አልባ ዜጎቻችን ወደ አገራቸው ለመመለስ ባቀረቡት በጥያቄያቸው መሠረትት ደግሞ 149 የሚሆኑት ወደ ሀገር ቤት ተመልሰዋል።
@TikvahethMagazine
በሊባኖስ በተከሰተው ጦርነት ምክንያት የተፈናቀሉ እንዲሁም ከዚያ በፊት ወደ አገር ለመመለስ ጠይቀው የመውጫ ቪዛ ሲጠባበቁ የነበሩ 316 ዜጎች ወደ አገራቸው መመለሳቸውን በቤይሩት-ሊባኖስ የኢትዮጵያ ቆንጽላ ጀነራል ጽ/ቤት አስታውቋል።
ከተመለሱት ዜጎች ውስጥ 167 ዜጎች በሊባኖስ በተከሰተው ጦርነት ምክንያት የተፈናቀሉና በሊባኖስ ከአለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት(IOM) ጋር በመተባበር ረቡዕ ታህሳስ 2 ቀን ወደ አገር እንዲመለሱ የተደረጉ ሲሆኑ 17 እናቶችና 22 ህፃናት ይገኙበታል ተብሏል፡፡
በተለያዩ ምክንያቶች የመኖሪያና የሥራ ፈቃድ ሳይኖራቸው በሊባኖስ ረዥም ዓመታት ሲኖሩ የነበሩ ሰነድ አልባ ዜጎቻችን ወደ አገራቸው ለመመለስ ባቀረቡት በጥያቄያቸው መሠረትት ደግሞ 149 የሚሆኑት ወደ ሀገር ቤት ተመልሰዋል።
@TikvahethMagazine
👏46❤9😨1