TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#TPLF #SHANE

በ19 የህወሓት ቡድን አመራር እና አባላት በአዲስ አበባ የሚገኙ ቋሚ ንብረቶቻቸው ላይ እገዳ መጣሉን የደህንነትና ፀጥታ የጋራ ግብረ ሃይል አስታወቀ፡፡

ንብረታቸውን እንዳያንቀሳቅሱ እና እንዲታገድ የተደረገባቸው የህወሓት ቡድን አመራርና አባላት ፦

- ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ በቅፅል ስማቸው ወዲ ወረደ፣
- ሌተናል ጀነራል ፍስሃ ኪዳኑ በቅፅል ስማቸድ ፍስሃ ማንጁስ ፣
- ሜጀር ጀነራል አበበ ተ/ሀይማኖት በቅፅል ስማቸው ጆቤ፣
- ሜጀር ጀነራል ሀልፎም እጅጉ በቅፅል ስማቸው ወዲ እጅጉ፣
- ሜጀር ጀነራል ተስፋዬ ግደይ፣
- ብርጋዴር ጀነራል ሃ/ስላሴ ግርማይ በቅፅል ስማቸው ወዲ እንቤተይ፣
- ብርጋዴር ጀነራል ምግበ ሀይለ፣
- ብርጋዴር ጀነራል ተክላይ አሸብር በቅፅል ስማቸው ወዲ አሸብር
- አቶ ኢሳያስ ወ/ጊዮርጊስ
- አቶ ሀሰን ሽፋ ሲሆኑ በአጠቃላይ በድምሩ 19 ናቸው።

በሌላ በኩል መቐለ ሆነው ለህወሓት ቡድን መረጃ ሲሰጡ ፤ የፋይናንስ እና የሎጀስቲክስ ድጋፎችን በድብቅ ሲያቀርቡ እንዲሁም የመከላከያ ሰራዊት የደንብ ልብሶችን በመልበስ በጊዜያዊ አስተዳደሩ አመራሮችና ሰራተኞች ላይ ተመሳስለው ጥቃት ሲፈጽሙ ከነበሩ ግለሰቦች መካከል 14 የቡድኑ አባላት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ገልጿል።

ተጠርጣሪዎቹ ለሰብአዊ ድጋፍ በመጓጓዝ ላይ የነበሩና እያንዳንዳቸው 20 ሌትር የምግብ ዘይት የያዙ 2,200 ጄሪካኖችን የጫነ አንድ ተሽከርካሪ ከእነ ተሳቢው አስገድደው አቅጣጫውን እንዲቀይር በማድረግ በድብቅ ለህወሓት ለመላክ ሲሞክሩ ነው በቁጥጥር ስር የዋሉት።

በተጨማሪ ግብረ ሃይሉ የሼኔን ቡድን ሲደግፉ የነበሩ 141 ተጠርጣሪ ግለሰቦች የፋይናስ ስርአት እንዲቋረጥ እና ገንዘባቸው እንዲታገድ ተደርጓል፡፡

ዝርዝር መግለጫው : telegra.ph/ETH-05-31

@tikvahethiopia