TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Ventilators

ደቡብ ሱዳን 5 ምክትል ፕሬዘዳንቶች ያላት ቢሆንም ለ11 ሚሊዮን ህዝብ የሚሆን 4 የኦክስጅን መስጫ ማሽኖች አላት ሲል ዘ ኒው ዮርክ ታይምስ ዘግቧል፡፡

ምንም እንኳን ለኮሮና ቫይረስ ህመምተኞች ለመተንፈስ የሚያግዛቸው ቬንትሌተር ማሽን በደቡብ ሱዳን ካሉ ምክትል ፕሬዘዳንቶች እኩል ባይሆንም አንድም እንኳን ከሌላት ሱማሊያ በቁጥር ልቆ ታይቷል፡፡ በሱማሊያ ምንም አይነት የመተንፈሻ መሳሪያ እንደሌለ ዘገባው ያስረዳል፡፡

ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ 5 ሚሊዮን ህዝብ ያላት ሲሆን 3 ቬንትሌተር ብቻ ነው ያላት ፤ ላይቤሪያም በተመሳሳይ ከ6ቱ 3ቱ ብቻ ናቸው የሚሰሩት።

ቡርኪና ፋሶ ለ20 ሚሊየን ህዝብ 11 ነው ያላት ፤ በኬኒያ 257 ፤ በጋና 200 ፤ ሱዳን 80 አላቸው፡፡ በሀገራችንም 575 ቬንትለተሮች እንዳሉ ዘገባው ጠቁሟል፡፡

በአፍሪካ በአሁን ሰዓት በአጠቃላይ 2,000 ቬንትለተሮች ያሉ ሲሆን ከ46 ሺህ በላይ ሰዎች በሞቱባት በአሜሪካ ብቻ 17 ሺህ ቬንትሌተሮች እንዳሉ ነው ዘ ኒዉ ዮርክ ታይምስ በዘገባው ያስረዳው፡፡

#ETHIOFM #DERESEAMARE
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia