በ yesuf Ibrahim
የወልቃይት ጉዳይ በአማራ ህዝብ ትግል ውስጥ ጉልህ ስፍራ ካላቸው አጀንዳዎች መካከል ግንባር ቀደም ሆኖ የሚጠቀስ ነው።
በገፊ ምክንያትነትና በቀጣይ ግብዓትነት!
ወልቃይት ማለት የሆነ የመሬት ወርድ × ቁመት ጉዳይ አይደለም! የትህነግ ስብስብ ለግማሽ ምዕተአመት ያክል ሳያቋርጥ ጥርሱን አግጥጦና አይኑን አፍጥጦ በወልቃይት ላይ የሚያማትረው ለምን እንደሆነ በትክክል መረዳት ያስፈልጋል።
በዋናነት ወልቃይት ማንነቱን በግፍ የተነጥቀና የዘር ጭፍጨፋዎች ሰለባ የሆነ ሰፊ ማህበረሰብ ጉዳይ ነው። ይህ ከሁሉም በላይ የወልቃይትን ጉዳይ automatically የመላው አማራ ህዝብ አጀንዳ አድርጎታል።
"ወልቃይት" የፍትህ፣ የማንነት፣ የክብርና የታሪክ ጉዳይ ነው! የወልቃይትን ፋይዳ በደላላ ቀመር መረዳት አይቻልም። የወልቃይትን ጉዳይ "በሰሊጥ ፖለቲካ" ፈርጀው የሚያራክሱ አካላት እንደሁኔታው አስገራሚና አሳዛኝ ናቸው። ግን— የትህነግ ስብስብ ሊጥ በሚሰርቅበት ዘመን ሰሊጥስ ቢሆን እንደት ርካሽ ሊሆን ይቻላል?
ለማንኛውም—
በወልቃይት ታሪክ፣ መልክዓምድር፣ ከርሰምድርና መልከዓ-ፖለቲካ ዙሪያ ዝርዝርና ተጨባጭ ግንዛቤ ለመፍጠር— ለአማራ ተማሪዎችና ወጣቶች ሲወርድ ሲዋረድ በቀጠለው "የወልቃይት" ጉዳይ ዙሪያ የተሻለ ግንዛቤ ለማስጨበጥ በሚል የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል።
በተመሳሳይ በሌሎች የአማራ ህዝብ ነባርና መሰረታዊ ጥያቄች ዙሪያም ተገቢውን ግንዛቤ በመፍጠርና አስቻይ የትግል ስልቶችን በመንደፍ መንቀሳቀስ ያስፈልጋል። የአማራ አጀንዳዎች እርስበርስ ተደጋጋፊ በመሆናቸው ለአንዱ የምንሰጠው እልባት ለቀሪዎቹ ትልቅ ግብዓት እንደሚሆን ሊሰመርበት ይገባል!
ማስታወሻ
------
ወያኔ በግፍ ጨፈጭፎ ጅምላ መቃብሮች ውስጥ የጣላቸውን ወገኖች አፅም የማውጣትና በክብር የማሳረፉ ስራዎች ሲከናወኑ በተቻለ መጠን ታዋቂ የሆኑ የሀገር ውስጥና የዓለማቀፍ የሚዲያዎችና የሰብዓዊ መብት ተቋማት እንዲታዘቧቸውና እንዲዘግቧቸው ማድረግ ያስፈልጋል።
የወልቃይት ጉዳይ በአማራ ህዝብ ትግል ውስጥ ጉልህ ስፍራ ካላቸው አጀንዳዎች መካከል ግንባር ቀደም ሆኖ የሚጠቀስ ነው።
በገፊ ምክንያትነትና በቀጣይ ግብዓትነት!
ወልቃይት ማለት የሆነ የመሬት ወርድ × ቁመት ጉዳይ አይደለም! የትህነግ ስብስብ ለግማሽ ምዕተአመት ያክል ሳያቋርጥ ጥርሱን አግጥጦና አይኑን አፍጥጦ በወልቃይት ላይ የሚያማትረው ለምን እንደሆነ በትክክል መረዳት ያስፈልጋል።
በዋናነት ወልቃይት ማንነቱን በግፍ የተነጥቀና የዘር ጭፍጨፋዎች ሰለባ የሆነ ሰፊ ማህበረሰብ ጉዳይ ነው። ይህ ከሁሉም በላይ የወልቃይትን ጉዳይ automatically የመላው አማራ ህዝብ አጀንዳ አድርጎታል።
"ወልቃይት" የፍትህ፣ የማንነት፣ የክብርና የታሪክ ጉዳይ ነው! የወልቃይትን ፋይዳ በደላላ ቀመር መረዳት አይቻልም። የወልቃይትን ጉዳይ "በሰሊጥ ፖለቲካ" ፈርጀው የሚያራክሱ አካላት እንደሁኔታው አስገራሚና አሳዛኝ ናቸው። ግን— የትህነግ ስብስብ ሊጥ በሚሰርቅበት ዘመን ሰሊጥስ ቢሆን እንደት ርካሽ ሊሆን ይቻላል?
ለማንኛውም—
በወልቃይት ታሪክ፣ መልክዓምድር፣ ከርሰምድርና መልከዓ-ፖለቲካ ዙሪያ ዝርዝርና ተጨባጭ ግንዛቤ ለመፍጠር— ለአማራ ተማሪዎችና ወጣቶች ሲወርድ ሲዋረድ በቀጠለው "የወልቃይት" ጉዳይ ዙሪያ የተሻለ ግንዛቤ ለማስጨበጥ በሚል የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል።
በተመሳሳይ በሌሎች የአማራ ህዝብ ነባርና መሰረታዊ ጥያቄች ዙሪያም ተገቢውን ግንዛቤ በመፍጠርና አስቻይ የትግል ስልቶችን በመንደፍ መንቀሳቀስ ያስፈልጋል። የአማራ አጀንዳዎች እርስበርስ ተደጋጋፊ በመሆናቸው ለአንዱ የምንሰጠው እልባት ለቀሪዎቹ ትልቅ ግብዓት እንደሚሆን ሊሰመርበት ይገባል!
ማስታወሻ
------
ወያኔ በግፍ ጨፈጭፎ ጅምላ መቃብሮች ውስጥ የጣላቸውን ወገኖች አፅም የማውጣትና በክብር የማሳረፉ ስራዎች ሲከናወኑ በተቻለ መጠን ታዋቂ የሆኑ የሀገር ውስጥና የዓለማቀፍ የሚዲያዎችና የሰብዓዊ መብት ተቋማት እንዲታዘቧቸውና እንዲዘግቧቸው ማድረግ ያስፈልጋል።
አማራ የሕልውና አደጋ እንዳለበት እየለፈፉ ነገር ግን ወያኔ የሚወደውን እየወደዱ ወያኔ የሚጠላውን እየጠሉ "የአማራ የሕልውና የቅርብ ተጠሪ ነን" ባይ የወያኔ የቁርጥ ቀን ጠበቆች ከሆኑት ይልቅ በወልቃይት ጉዳይ የትግራይ ተወላጅ የሆነችው ሔርሜላ ሐረገወይን የአማራ አልፎም የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ መሆኗን በግብር አስመስክራለች።
አማራን እንወቅ በሚል ወደወልቃይት የተደረገውን ጉዞ በብአዴንነት በለመዱት የትርጉም አሰጣጥ ለማጣጣል እየተሞከረ ነው። ወልቃይትን አጀንዳ ያደረጉትን አካላት የአብይ ተላላኪ የብአዴን ተከፋይ እያሉ ነው። የነቁ የሚመስሉት የወያኔ የቁርጥ ቀን ጠበቆች ደግሞ ለምን ወልቃይት ብቻ ደራስ መተከልስ ራያስ አጀንዳ አይሆንም በማለት ለሁሉም አማራ ወይም ለአማራ አንድነት የሚቆረቆሩና የሚገዳቸው መስለው የወልቃይት ጉዳይ የሁሉም አማራ ጉዳይ እንዳልሆነ ወይም የጉዞው አላማ ትኩረት አግኝቶ ገዥ እንዳይኖረው ተግተው ሲሰሩ እንደማየት አሳዛኝ ነገር የለም። ደግሞ እኮ ተፅዕኖው ከትዝብት የሚያልፍም አይደለም።
ይህ የወያኔ የቁርጥ ቀን ጠበቃ አቅም አለመኖሩ በጀን እንጅ ከወያኔ ቀድሞ ማጥፋት ቢችል ለደስታው ወደር አይኖረውም። አቅሙ መቼም ማደግ የማይችልና የወያኔን መዳከም ተከትሎ የሚከስም ስለሆነ ትዝብታችንን የእየመዘገብን ወደፊት እየሰነጠቅን በድል መገስገሳችን ላይ ትኩረታችንን እናነጣጥራለን።
ወያኔ መሩ የሳይበር አማራ የግለሰቦችን ስም በማጥፋት ዘመቻ መሰማራትን፣ መሳደብን፣ መራገምን፣ የምድጃ ዳር ወሬ ማመላለስን፣እንደ ፖለቲካ አዋቂነት እንደ ሴራ ሊቀ-ጠበብነት በመቁጠር የሚደረገውን የዘወትር የግብር መገለጫን ከዚህ በኋላ እንዲያስተካክል በመወትወት የምናጠፋው ጊዜ የምንገባው ሰጣ ገባ አይኖርም(አላማዬ ብሎ የያዘው በመሆኑ) በስራው ራሱን በደንብ እንዲገልጥ እንቅፋት ባለመሆን ከእኛ የሚጠበቀውን ስራ መስራትን ያስቀደመ ይሆናል ።
ነውርን ጌጥ ማድረግን እንደክብር፣ ባንዳነት መላበስን እንደ አዋቂነት የሚቆጥር የእናት ጡት ነካሽ የእፍኝት ልጆች ባሕሪይ በደንብ ጎልቶ እንዲወጣ ባላየና ባልሰማ ማለፍ በአንድ በኩል እንደ አዋጭ መንገድ ሊታይም የሚችል ነው። ይህ በአማራ ስም የሚንቀሳቀስ ለአማራ ሕልውና ቁጥር አንድ ስጋት የሆነ ወያኔ መሩ የሳይበር ሃይል አላማው ምን እንደሆነ አሁን አሁን በብዙሃኑ አማራ ዘንድ እየተገለጠ መምጣቱ ትልቅ ተስፋ የሚሰጥም ነው።
ሔርሜላ ሐረገወይን ወያኔ በአደባባይ አዋጅ አገርን ለማፍረስ ሲኦልም ድረስ እገባለሁ ከአማራ ጋርም ሂሳብ አወራርዳለሁ ብሎ ጦርነት ሲከፍት ከአማራም ሆነ ከኢትዮጵያዊን ጎን ቆመሽ እስካሁን እያሳየሽ ያለውን የፀና አቋም እናደንቃለን። ስላደረግሽው ሁሉም ከልብ እናመሰግናለን‼️
አማራን እንወቅ በሚል ወደወልቃይት የተደረገውን ጉዞ በብአዴንነት በለመዱት የትርጉም አሰጣጥ ለማጣጣል እየተሞከረ ነው። ወልቃይትን አጀንዳ ያደረጉትን አካላት የአብይ ተላላኪ የብአዴን ተከፋይ እያሉ ነው። የነቁ የሚመስሉት የወያኔ የቁርጥ ቀን ጠበቆች ደግሞ ለምን ወልቃይት ብቻ ደራስ መተከልስ ራያስ አጀንዳ አይሆንም በማለት ለሁሉም አማራ ወይም ለአማራ አንድነት የሚቆረቆሩና የሚገዳቸው መስለው የወልቃይት ጉዳይ የሁሉም አማራ ጉዳይ እንዳልሆነ ወይም የጉዞው አላማ ትኩረት አግኝቶ ገዥ እንዳይኖረው ተግተው ሲሰሩ እንደማየት አሳዛኝ ነገር የለም። ደግሞ እኮ ተፅዕኖው ከትዝብት የሚያልፍም አይደለም።
ይህ የወያኔ የቁርጥ ቀን ጠበቃ አቅም አለመኖሩ በጀን እንጅ ከወያኔ ቀድሞ ማጥፋት ቢችል ለደስታው ወደር አይኖረውም። አቅሙ መቼም ማደግ የማይችልና የወያኔን መዳከም ተከትሎ የሚከስም ስለሆነ ትዝብታችንን የእየመዘገብን ወደፊት እየሰነጠቅን በድል መገስገሳችን ላይ ትኩረታችንን እናነጣጥራለን።
ወያኔ መሩ የሳይበር አማራ የግለሰቦችን ስም በማጥፋት ዘመቻ መሰማራትን፣ መሳደብን፣ መራገምን፣ የምድጃ ዳር ወሬ ማመላለስን፣እንደ ፖለቲካ አዋቂነት እንደ ሴራ ሊቀ-ጠበብነት በመቁጠር የሚደረገውን የዘወትር የግብር መገለጫን ከዚህ በኋላ እንዲያስተካክል በመወትወት የምናጠፋው ጊዜ የምንገባው ሰጣ ገባ አይኖርም(አላማዬ ብሎ የያዘው በመሆኑ) በስራው ራሱን በደንብ እንዲገልጥ እንቅፋት ባለመሆን ከእኛ የሚጠበቀውን ስራ መስራትን ያስቀደመ ይሆናል ።
ነውርን ጌጥ ማድረግን እንደክብር፣ ባንዳነት መላበስን እንደ አዋቂነት የሚቆጥር የእናት ጡት ነካሽ የእፍኝት ልጆች ባሕሪይ በደንብ ጎልቶ እንዲወጣ ባላየና ባልሰማ ማለፍ በአንድ በኩል እንደ አዋጭ መንገድ ሊታይም የሚችል ነው። ይህ በአማራ ስም የሚንቀሳቀስ ለአማራ ሕልውና ቁጥር አንድ ስጋት የሆነ ወያኔ መሩ የሳይበር ሃይል አላማው ምን እንደሆነ አሁን አሁን በብዙሃኑ አማራ ዘንድ እየተገለጠ መምጣቱ ትልቅ ተስፋ የሚሰጥም ነው።
ሔርሜላ ሐረገወይን ወያኔ በአደባባይ አዋጅ አገርን ለማፍረስ ሲኦልም ድረስ እገባለሁ ከአማራ ጋርም ሂሳብ አወራርዳለሁ ብሎ ጦርነት ሲከፍት ከአማራም ሆነ ከኢትዮጵያዊን ጎን ቆመሽ እስካሁን እያሳየሽ ያለውን የፀና አቋም እናደንቃለን። ስላደረግሽው ሁሉም ከልብ እናመሰግናለን‼️
ከሁሉም የአማራ ክልል አካባቢዎች የተውጣጡ ወንድሞቻችን የአማራ የዕዳ ደብዳቤ በተቀበረባትና በተቀደደባት ወልቃይት አዲረመጥ ከፍተኛ የሆነ አቀባበል እየተደረገላቸው ይገኛል። ውድ ወንድሞቻችን ቆይታችሁ ያማረ እንዲሆን እንመኛለን!
ወልቃይት ከነዓናችን ነች‼️
ወልቃይት ከነዓናችን ነች‼️
ከአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የተሰጠ መግለጫ
****
ፍትሕ በሐሰት ትርክትና የጥላቻ ስሜት የጅምላ ጭፍጨፋ ሰለባ ለሆኑ ወገኖቻችን!
አሸባሪውና ዘረኛው ትሕነግ የሽምቅ ተዋጊ በነበረበት ጊዜ ጀምሮ ወልቃይትና ጠገዴ አካባቢ ያለውን ስትራቴጅያዊ ጠቀሜታና ሀብት በመገንዘብ አካባቢውን ለመቆጣጠር ወጣ ገባ ማለት ከጀመረበት 1972 ዓ.ም ጀምሮ በተለይም አካባቢውን ሙሉ በሙሉ ከተቆጣጠረበት 1983 ዓ.ም ጀምሮ በወልቃይት-ጠገዴ ሰቲት ሁመራ የአማራ ሕዝብ ላይ መጠነ ሰፊ ግድያ፣ ማፈናቀልና አፈና ሲፈፅም ቆይቷል:: በዚህም በአስር ሺህዎች የሚቆጠሩ የአማራ ተወላጆች ማንነታቸው ወንጀል ሆኖባቸው እንደወጡ ቀርተዋል፡፡ በጥቅሉ፣ ባለፉት ሠላሳ ዓመታት ዓለም ጀሮ የነፈገው የዘር ማጥፋት ወንጀል በወልቃይት ጠገዴ የአማራ ሕዝብ ላይ ተፈጽሟል፡፡
ጥቅምት 24/ 2013 ዓ.ም አሸባሪውና ዘረኛው ትሕነግ በሰሜን ዕዝ ልዩ ልዩ የጦር ሰፈሮች ላይ ጥቃት ማድረሱን እና በሁለት አቅጣጫ ደግሞ አማራ ክልል ላይ የጦር ወረራ መፈፀሙን ተከትሎ በሕግ ማስከበር ዘመቻው በደረሰበት የመልስ ምት፣ ቡድኑ አካባቢውን ለቆ እንዲሄድ የተደረገ ሲሆን፤ በሚያፈገፍግበት ወቅት ጥቅምት 30/2013 ዓ.ም. በማይካድራ ከተማ በሺህ የሚቆጠሩ አማሮችን፤ በተመሳሳይ ሕዳር 03/ 2013 ከሁመራ ከተማ አርባ ኪሎ ሜትር በምትርቀው ‹እድሪስ› የተባለች የገጠር ቀበሌ/ከተማ ላይ የተመረጡ የአማራ ባለሀብቶችን ጨፍጭፎ መሄዱ የሁሉንም ልብ የሰበረ ክስተት እንደነበር ይታወሳል፡፡
አሸባሪው ቡድን ከወልቃይት፣ ጠገዴና ሁመራ አካባቢ ተመትቶ መልቀቁን ተከትሎ የሁመራ ኤርፖርት በቁጥጥር ስር ሲውል በዙሪያው የጅምላ መቃብሮች የተገኙ ሲሆን፤ በዚሁ ቀጠና በተለያየ ጊዜ የተለያየ ቦታ ላይም በርካታ የጀምላ መቃብሮች ተገኝተዋል:: ከሰሞኑ በወልቃይት-ጠገዴ ሰቲት ሁመራ አካባቢ ለአስራ ስድስት ወራት ጥናት ሲሰራ የቆየው የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የጥናት ቡድን የአካባቢው ማኅበረሰብ "ገሃነም" እያለ በሚጠራው የትሕነግ ድብቅ የማሳቃያ፣ መግደያና ማሰሪያ ቦታ እጅግ አስደንጋጭ የሆነ የጅምላ መቃብር ተገኝቷል:: ትህነግ በሐሰት ትርክት ከቆመበት ተፈጥሯዊ የጭካኔ ባህሪውና በአካባቢው ሲፈጽማቸው ከኖሩ ዓለማቀፍ ወንጀሎች አኳያ ተጨማሪ ምርመራ ቢደረግ አያሌ የጅምላ መቃብሮች እንደሚገኙ አያጠራጥርም::
ስለሆነም:-
፩. የፌደራል መንግሥቱ በተለይም የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን፣ የአማራ ክልል መንግሥት ጥናቱን ቀድመ ብሎ ከጀመረው የጎንደር ዩኒቨርሲቲና መሰል የምርምር ተቋማት ጋር በመተባበር ይኸን መዋቅራዊ ሆኖ ለሦስት አስርት ዓመታት የዘለቀ የዘር ማጥፋት ወንጀል እንዲጣራ እንዲያደርጉ፣ ይህን ዓለማቀፍ ወንጀል የፈፀሙ የትህነግ ፖለቲካዊና ወታደራዊ አመራሮች ላይ ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ ሁሉን አቀፍ (ሙያዊና ተቋማዊ) ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ አብን አጥብቆ ይጠይቃል::
፪. የአማራ ሕዝብ አሁንም በተለይ በምዕራብ ኦሮሚያ (ወለጋና አካባቢው) የጅምላ ፍጅት ሰለባ ሆኖ የቀጠለ ስለሆነ መንግሥት የጅምላ ፍጅቱን እንዲያስቆም እየጠየቅን፣ የወንጀሉ ተባባሪና አቀናባሪ የሆኑ በየደረጃው ያሉ የመንግሥት ኃላፊዎችን ጨምሮ ወንጀል ፈፃሚዎችን ተገቢውን ምርመራ በማድረግ ለሕግ እንዲያቀርብ በጥብቅ እንጠይቃለን:: የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽንን ጨምሮ በዜጎች የሰብዓዊ መብት ዙሪያ የሚሰሩ ሀገር በቀልና የውጭ ተቋማት በእነዚህ አካባቢዎች የተፈፀሙ መጠነ ሰፊ ጭፍጨፋዎችን እንዲያጣሩና ተጠያቂነትም እንዲሰፍን የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ እንጠይቃለን::
ፍትሕ በሐሰት ትርክትና የጥላቻ ስሜት የጅምላ ጭፍጨፋ ሰለባ ለሆኑ ወገኖቻችን!
መጋቢት 26/ 2014
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
****
ፍትሕ በሐሰት ትርክትና የጥላቻ ስሜት የጅምላ ጭፍጨፋ ሰለባ ለሆኑ ወገኖቻችን!
አሸባሪውና ዘረኛው ትሕነግ የሽምቅ ተዋጊ በነበረበት ጊዜ ጀምሮ ወልቃይትና ጠገዴ አካባቢ ያለውን ስትራቴጅያዊ ጠቀሜታና ሀብት በመገንዘብ አካባቢውን ለመቆጣጠር ወጣ ገባ ማለት ከጀመረበት 1972 ዓ.ም ጀምሮ በተለይም አካባቢውን ሙሉ በሙሉ ከተቆጣጠረበት 1983 ዓ.ም ጀምሮ በወልቃይት-ጠገዴ ሰቲት ሁመራ የአማራ ሕዝብ ላይ መጠነ ሰፊ ግድያ፣ ማፈናቀልና አፈና ሲፈፅም ቆይቷል:: በዚህም በአስር ሺህዎች የሚቆጠሩ የአማራ ተወላጆች ማንነታቸው ወንጀል ሆኖባቸው እንደወጡ ቀርተዋል፡፡ በጥቅሉ፣ ባለፉት ሠላሳ ዓመታት ዓለም ጀሮ የነፈገው የዘር ማጥፋት ወንጀል በወልቃይት ጠገዴ የአማራ ሕዝብ ላይ ተፈጽሟል፡፡
ጥቅምት 24/ 2013 ዓ.ም አሸባሪውና ዘረኛው ትሕነግ በሰሜን ዕዝ ልዩ ልዩ የጦር ሰፈሮች ላይ ጥቃት ማድረሱን እና በሁለት አቅጣጫ ደግሞ አማራ ክልል ላይ የጦር ወረራ መፈፀሙን ተከትሎ በሕግ ማስከበር ዘመቻው በደረሰበት የመልስ ምት፣ ቡድኑ አካባቢውን ለቆ እንዲሄድ የተደረገ ሲሆን፤ በሚያፈገፍግበት ወቅት ጥቅምት 30/2013 ዓ.ም. በማይካድራ ከተማ በሺህ የሚቆጠሩ አማሮችን፤ በተመሳሳይ ሕዳር 03/ 2013 ከሁመራ ከተማ አርባ ኪሎ ሜትር በምትርቀው ‹እድሪስ› የተባለች የገጠር ቀበሌ/ከተማ ላይ የተመረጡ የአማራ ባለሀብቶችን ጨፍጭፎ መሄዱ የሁሉንም ልብ የሰበረ ክስተት እንደነበር ይታወሳል፡፡
አሸባሪው ቡድን ከወልቃይት፣ ጠገዴና ሁመራ አካባቢ ተመትቶ መልቀቁን ተከትሎ የሁመራ ኤርፖርት በቁጥጥር ስር ሲውል በዙሪያው የጅምላ መቃብሮች የተገኙ ሲሆን፤ በዚሁ ቀጠና በተለያየ ጊዜ የተለያየ ቦታ ላይም በርካታ የጀምላ መቃብሮች ተገኝተዋል:: ከሰሞኑ በወልቃይት-ጠገዴ ሰቲት ሁመራ አካባቢ ለአስራ ስድስት ወራት ጥናት ሲሰራ የቆየው የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የጥናት ቡድን የአካባቢው ማኅበረሰብ "ገሃነም" እያለ በሚጠራው የትሕነግ ድብቅ የማሳቃያ፣ መግደያና ማሰሪያ ቦታ እጅግ አስደንጋጭ የሆነ የጅምላ መቃብር ተገኝቷል:: ትህነግ በሐሰት ትርክት ከቆመበት ተፈጥሯዊ የጭካኔ ባህሪውና በአካባቢው ሲፈጽማቸው ከኖሩ ዓለማቀፍ ወንጀሎች አኳያ ተጨማሪ ምርመራ ቢደረግ አያሌ የጅምላ መቃብሮች እንደሚገኙ አያጠራጥርም::
ስለሆነም:-
፩. የፌደራል መንግሥቱ በተለይም የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን፣ የአማራ ክልል መንግሥት ጥናቱን ቀድመ ብሎ ከጀመረው የጎንደር ዩኒቨርሲቲና መሰል የምርምር ተቋማት ጋር በመተባበር ይኸን መዋቅራዊ ሆኖ ለሦስት አስርት ዓመታት የዘለቀ የዘር ማጥፋት ወንጀል እንዲጣራ እንዲያደርጉ፣ ይህን ዓለማቀፍ ወንጀል የፈፀሙ የትህነግ ፖለቲካዊና ወታደራዊ አመራሮች ላይ ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ ሁሉን አቀፍ (ሙያዊና ተቋማዊ) ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ አብን አጥብቆ ይጠይቃል::
፪. የአማራ ሕዝብ አሁንም በተለይ በምዕራብ ኦሮሚያ (ወለጋና አካባቢው) የጅምላ ፍጅት ሰለባ ሆኖ የቀጠለ ስለሆነ መንግሥት የጅምላ ፍጅቱን እንዲያስቆም እየጠየቅን፣ የወንጀሉ ተባባሪና አቀናባሪ የሆኑ በየደረጃው ያሉ የመንግሥት ኃላፊዎችን ጨምሮ ወንጀል ፈፃሚዎችን ተገቢውን ምርመራ በማድረግ ለሕግ እንዲያቀርብ በጥብቅ እንጠይቃለን:: የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽንን ጨምሮ በዜጎች የሰብዓዊ መብት ዙሪያ የሚሰሩ ሀገር በቀልና የውጭ ተቋማት በእነዚህ አካባቢዎች የተፈፀሙ መጠነ ሰፊ ጭፍጨፋዎችን እንዲያጣሩና ተጠያቂነትም እንዲሰፍን የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ እንጠይቃለን::
ፍትሕ በሐሰት ትርክትና የጥላቻ ስሜት የጅምላ ጭፍጨፋ ሰለባ ለሆኑ ወገኖቻችን!
መጋቢት 26/ 2014
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን እንኳን ደስ አለን‼️
HR6600 እና S3199 ባሉበት እንዲቆሙ መወሰኑ ለእናት አገር ኢትዮጵያ ድምፅ ለሆናችሁ የምንጊዜም አለኝታ ኢትዮጵያዊያን ትልቅ ብስራት ለባንዳዎች ደግሞ የመርዶ ዜና ነው።
ኢትዮጵያ ዛሬም ልክ እንደትናንቱ የቱንም ያህል በፈተናዎች ብትከበብም በድል መሻገሯ ለአፍታም የሚያጠራጥር አይሆንም!
ቀሪውን ፈተና በድል ለመወጣት በተለመደው ቁርጠኝነት መቀጠል ያስፈልጋል!
አላስፈላጊ መስዋዕትነት ለመቀነስ እንጅ በአንድነት በፀና አላማ ቆመን የማናሸንፈዉ ምንም አይነት ምድራዊ ሃይል አለመኖሩን የመጣንባቸው ወይም የተጓዝንባቸው ምዕራፎች ሕያው ምስክር ናቸው‼️
HR6600 እና S3199 ባሉበት እንዲቆሙ መወሰኑ ለእናት አገር ኢትዮጵያ ድምፅ ለሆናችሁ የምንጊዜም አለኝታ ኢትዮጵያዊያን ትልቅ ብስራት ለባንዳዎች ደግሞ የመርዶ ዜና ነው።
ኢትዮጵያ ዛሬም ልክ እንደትናንቱ የቱንም ያህል በፈተናዎች ብትከበብም በድል መሻገሯ ለአፍታም የሚያጠራጥር አይሆንም!
ቀሪውን ፈተና በድል ለመወጣት በተለመደው ቁርጠኝነት መቀጠል ያስፈልጋል!
አላስፈላጊ መስዋዕትነት ለመቀነስ እንጅ በአንድነት በፀና አላማ ቆመን የማናሸንፈዉ ምንም አይነት ምድራዊ ሃይል አለመኖሩን የመጣንባቸው ወይም የተጓዝንባቸው ምዕራፎች ሕያው ምስክር ናቸው‼️
ወንድም ተስፋዬ ወርቁ በተወለደበት ተንታ ወረዳ አጅባር ከተማ ስለአማራ ህዝብ ትግል ሲጨነቅ በጉልህ የሚታወቅ ጀግና ወንድም ነው። ተስፋዬ የአብን አባል ሲሆን ባለፈው ሰኔ በተደረገው ምርጫ ድርጅቱን ወክሎ ተንታ ላይ ከተወዳደሩት እጩዎች አንዱ ነበር። ከምርጫው መጠናቀቅ ብዙም ሳይቆይ ህወሓት የአማራን ግዛቶች ወርሮ ኢትዮጵያን ለማፍረስ ሲገስግስ የአማራ ክልል መንግሥት ያደረገውን የክተት ጥሪ በጀግንነት ተቀብለው በሁለት ሳምንት ስልጠና ብቻ ጠላትን ለመፋለም ጦር ግንባር ከገቡት በታሪክ ሲወደሱ ከሚኖሩ ጀግኖች ኢትዮጵያዊያን መካከል አማራውን በኩራት ከሚወክሉት ጥቂት ቆራጦች የሚጠቀስ ነው። ጀግናው ተስፋዬ ወርቁ ግዳጁን በድል አጠናቆ ከኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ክላሽ ተሸልሞ በክብር ወደ ቤተሰቡ የተመለሰ ለአሳየው አኩሪ ተጋድሎም በተንታ ከተማ ደማቅ አቀባበል የተደረገለት ወጣት ነው።
ዛሬ የተስፋዬን ጉዳይ ያነሳሁት ተንታ ወረዳን ወክሎ ወደ "አማራዊቷን ከንዓን" ወልቃይትን ለመጎብኘት ከተጓዙት ወጣቶች መካከል እንዳለ በማየቴ ነው። አማራነትን በቃል ሳይሆን በተግባር የኖረ እንደ ተስፋዬ ወርቁ ያለ ለብዙዎች አርአያ የሚሆንን ወጣት ማክበር ስለሚገባ እንኳን ለኢትዮጵያ ህልውና ተስፋ ወደሆነችው ወልቃይት "ከንዓን" በሰላም መጣህ ማለት እፈልጋለሁ።
የፕሮግራሙ አስተባባሪዎች ለተስፋዬ ወርቁ እና ከእርሱ ጋር ዘምተው በድል የተመለሱ ጀግኖች ካሉ ልዩ እንክብካቤ እንድታደርጉላቸው በትህትና እጠይቃለሁ።
ዛሬ የተስፋዬን ጉዳይ ያነሳሁት ተንታ ወረዳን ወክሎ ወደ "አማራዊቷን ከንዓን" ወልቃይትን ለመጎብኘት ከተጓዙት ወጣቶች መካከል እንዳለ በማየቴ ነው። አማራነትን በቃል ሳይሆን በተግባር የኖረ እንደ ተስፋዬ ወርቁ ያለ ለብዙዎች አርአያ የሚሆንን ወጣት ማክበር ስለሚገባ እንኳን ለኢትዮጵያ ህልውና ተስፋ ወደሆነችው ወልቃይት "ከንዓን" በሰላም መጣህ ማለት እፈልጋለሁ።
የፕሮግራሙ አስተባባሪዎች ለተስፋዬ ወርቁ እና ከእርሱ ጋር ዘምተው በድል የተመለሱ ጀግኖች ካሉ ልዩ እንክብካቤ እንድታደርጉላቸው በትህትና እጠይቃለሁ።
መያዣና መጨበጫ የሌለው፤ ከተራ ጩኸትና መፎክር የማያልፍ፤ግልጽ የሆነ ራዕይና ግብ ባለቤት ያልሆነ፤ የተዘበራረቀና የተምታታበት የ herd mentality ተጠቂ አይደለም ሰፊውን ሕዝብ ለአንድ ዓላማ ሊያሰልፍ፣ ሊያሳምንና አግባብቶም ከጎኑ ሊያስከትል ይቅርና እስከ ምፅዓት ድረስ ጊዜ ቢሰጠው እንኳን እርስ በርስ ሊስማማና ሊደማመጥ ፈፅሞ አይችልም።
በተለያዩ ምክንያቶች የሚነሱ ጊዜያዊ ኃይማኖታዊና ማኅበራዊ ጥያቄዎችንና አለመግባባቶችን በተረትና ምሳሌ ወይም በእንካ ስላንትያ ሊፈታ የሚችል አይደለም። ችግሩን በመናቅ ለማዳፈን ወይም በችግሩ ላይ ቤንዚል በማርከፍከፍ ሐገር በማቃጠል ሊፈታ የሚችል የሕዝብ ጥያቄ የለም። አሉ የሚባሉ ችግሮቻችን የሚቀረፉት በሰከነ መንገድ በሚደረጉ ውይይቶች እና በጥበብ መራመድ ስንችል እንጅ እግርና እጅ በሌለው ስሜት ወለድ የጃስ በለው ፖለቲካ በማቀንቀን አይደለም። ከምንም በላይ ሕዝቡን የማይወክሉ ብቻ ሳይሆን ጠላት በሆኑ ሰዎች ጭምር ጥያቄው ሲዘወር ሌላ ጥያቄ ከመፍጠር ውጭ መፍትሄው ይርቃል።
በተጨማሪም የምድጃ ዳር ወሬ ለሚቃርሙ አሉባልተኞች እና የሕልውና መሰረታቸውን ግጭት ላይ ላደረጉ ለአቀሳሳሪ የደም ነጋዴዎች ጆሮ ከመስጠት ካልተሻገርን የሕዝብ ጥያቄ መልኩን ቀይሮ ነገረ-ስራችንም ወደራስ መተኮስ ብቻ የመሆን እድሉን ያሰፋዋል።
አንድን ጉዳይ ውጤቱን ሳያሰሉ አጀንዳ አድርጎ መታገል ደመ-ነብሳዊነት ነው‼️
በተለያዩ ምክንያቶች የሚነሱ ጊዜያዊ ኃይማኖታዊና ማኅበራዊ ጥያቄዎችንና አለመግባባቶችን በተረትና ምሳሌ ወይም በእንካ ስላንትያ ሊፈታ የሚችል አይደለም። ችግሩን በመናቅ ለማዳፈን ወይም በችግሩ ላይ ቤንዚል በማርከፍከፍ ሐገር በማቃጠል ሊፈታ የሚችል የሕዝብ ጥያቄ የለም። አሉ የሚባሉ ችግሮቻችን የሚቀረፉት በሰከነ መንገድ በሚደረጉ ውይይቶች እና በጥበብ መራመድ ስንችል እንጅ እግርና እጅ በሌለው ስሜት ወለድ የጃስ በለው ፖለቲካ በማቀንቀን አይደለም። ከምንም በላይ ሕዝቡን የማይወክሉ ብቻ ሳይሆን ጠላት በሆኑ ሰዎች ጭምር ጥያቄው ሲዘወር ሌላ ጥያቄ ከመፍጠር ውጭ መፍትሄው ይርቃል።
በተጨማሪም የምድጃ ዳር ወሬ ለሚቃርሙ አሉባልተኞች እና የሕልውና መሰረታቸውን ግጭት ላይ ላደረጉ ለአቀሳሳሪ የደም ነጋዴዎች ጆሮ ከመስጠት ካልተሻገርን የሕዝብ ጥያቄ መልኩን ቀይሮ ነገረ-ስራችንም ወደራስ መተኮስ ብቻ የመሆን እድሉን ያሰፋዋል።
አንድን ጉዳይ ውጤቱን ሳያሰሉ አጀንዳ አድርጎ መታገል ደመ-ነብሳዊነት ነው‼️