Thomas Jejaw Molla - ቶማስ ጀጃው ሞላ
6.42K subscribers
2.98K photos
371 videos
1 file
31 links
No pain No gain
Download Telegram
By Getenet Almaw
ሰበር ዜና ለባንዳዎች በሙሉ

<>

በኢትዮጵያ ላይ ሊጣል የታቀደውን #HR6600 የኢኮኖሚ ማዕቀብ ለደገፉ በነውራቸው አጊጠው በድንቁርናቸው ለተኩራሩ ባንዳዎች በሙሉ መቀመጫውን ዋሽንግተን ዲሲ ያደረገው Von Batten-Montague-York, L.C. አዲስ ብስራት አለኝ እያለ ነው።

ይህ የፖሊሲ አማካሪ እና ጉዳይ አስፈጻሚ/ወትዋች/ ሆኖ የሚሰራ ቡድን (policy advisory and advocacy group) በውጭ የሚኖሩ ዲያስፖራ ኢትዮጵያዊያን ወደ አገር ቤት የሚልኩትንገንዘብ ለመገደብ ከዩናይትድ ስቴትስ የገንዘብ ሚኒስቴር ጋር በጋራ መስራት መጀመሩን ይፋ አድርጓል!!

#HR6600 ይጽደቅ” እያለ የሚሞላፈጥ ሰው አንድ በውጭ የሚኖር ኢትዮጵያዊ አገር ቤት ያለ ጅምር ቤቱን ለማስጨረስ፣ የጀመረውን ንግድ ለማስፋፋትና ለማቀላጠፉ፣ ቤተሰብቹን በተለያዩ መንገዶች ለመደገፍ (በማስተማር፣ በመጦር፣ የንግድ መነሻ ካፒታል በመስጠት፣...) ብሎም በሰው ሰራሽ አደጋና (ጦርነትን ጨምሮ) በተፈጥሮ አደጋ (ድርቅ፣ ጎርፍ፣...) ለተጎዱ ወገኖቹ የዕለት ደራሽ መለገሰ እንዳይችሉ የሚከለክል መሆኑን አያውቅም፤ ቢያውቅም ግድ አይሰጠውም — የምቀኝነት ፖለቲካ ጥግ!!

በነገራችን ላይ HR6600 የአማራ ልዩ ሃይልና ፋኖ ሙሉ ለሙሉ እንዲፈርስ የሚጠይቅ መሆኑን እየመከርኩ እያወቁ በድፍረት ሳያውቁ በስህተት ይህንን ረቂቅ ሰነድ ለሚደግፉ የዋሆች ማሳሰብ እወዳለሁ!!

የአማራ ልዩ ሃይልና ፋኖ ይፍረሱ የሚል እሱ ከእኛ ወገን አይደለም!!

<>

ይኸው ነው
የሕወሓትን አርማ ምልክቶችን በይፋ መጠቀም የቀረው በአማራ ፖለቲካ ውስጥ በተቃዋሚ ስም የሚንቀሳቀስ ሃይል ተፈጥሯል። ይህ በተቃዋሚ ስም የሚንቀሳቀሰው ሃይል የኋላ ደጀን በመንግስታዊ መዋቅር ከአመራርነቱ በአቅመ ቢስነቱ በወንጀሉ የተባረረ ወይም የመባረር ስጋት ያደረበት አመራር እና በደህንነት መዋቅሩ ውስጥ ያለው ተመሳሳይ አካል ምርኩዝና አጀንዳ አቀባይ ሆኖ ጃስ የሚለው ነው።

በአማራ ፖለቲከኛ ራሱን እንደ አማራ ፅንፈኛ ብሔርተኛ የሚቆጥር አካል አለ። የመንግስት ተቃዋሚ ነኝ በሚል የሚንቀሳቀሰውና በመንግሥት መዋቅር ውስጥ በስልጣን ያኮረፈው በሕገ-ወጥ እንቅስቃሴና በሌሎች ወንጀሎች የተጠያቂነት ስጋት ያለበት ነው። የመንግስት ተቃዋሚ ነኝ በሚለው ረድፍ የሚንቀሳቀሰው ማንነቱን ደብቆ በብዕር ስም የሚጠቀመውና ወጥሮ የሚፅፈው ራሱ ወያኔ ሲሆን ሌላኛው ፅንፍ ብሔርን የፖለቲካ ማደራጃ ባደረገች ሐገር ወይም ትግል Balance of power ለመፍጠር በማሰብ እንቀሳቀሳለሁ የሚል ነው። ይህ ሃይል የጠራ ማንነቱ የማይታወቅ ግለሰቦች ጭምር አክተር የሆኑበት የጋራ የጠራ አላማና የጋራ ግብ አስቀምጦ የማይታገል ይልቅስ በጥላቻ ወለድ ስሜት የወያኔን አጀንጃ ብቻ ነክሶ ይዞ 24/7 ኦሮሙማ የሚል ወይም ከሁሉም ብሔር ከክልሉ መንግስት ከፌደራሉ መንግስት ጋር መናከስን፣ መሳደብን፣ መራገምን፣ የግለሰቦችን ስም ማጥፋትን ለአማራ የሕልውና የመዳኛ መንገድ እንደሆኑ አድርጎ መለፍለፍን እንደ እስትራቴጂ የሚቆጥር ነው።

ፅንፈኛ ነኝ ብሎ መንግስትን እንደሚቃወም የሚገልጸው ሃይል በመንግስታዊ መዋቅሩ ውስጥ ላኮረፈው የተጠያቂነት ስጋት ላለበት ለአፍቃሬ ወያኔው ሃይል የጎጥ ተቆርቋሪነትን ሽፋን በማድረግ ከፊት በመቅደም ቩቩዜላ ወይም ጡሩንባ ነፊ ሆኖ የሚያገለግልና የወያኔን አላማ የሚያስፈፅም ነው።

የአማራ ፖለቲካ የደፈረሰው እና ነገሮች የተወሳሰቡ የመሰሉት በመንግስታዊ መዋቅር ውስጥ ያለው አፍቃሬ ወያኔ አቅመ-ቢስ ወንጀለኛ አመራርና በደህንነት ክንፉ ውስጥም ያለው አቅመ ቢስ የሕገ-ወጥ እንቅስቃሴ ላይ የተሰማራው ወንጀለኛ አመራሮችና ባለሙያዎች የተቆርቋሪነት ስሜት ስም የሚለቁት ወይም በሚበትኑት መረጃ መረጃ ምክንያት ነው።

አገር ለማፍረስ በመንግስት መዋቅር ውስጥ ሆነው እንደ ምስጥ የሚሸረሽሩትን የወያኔ አጀንዳ አስፈፃሚዎችን ሳይረፍድበት ማፅዳት ወይም አደብ ማስያዝ ይገባዋል።

ከወያኔ በላይ ወያኔ ሆኖ የወያኔን አርማና ምልክቶችን መጠቀም የቀረው በአማራ ማልያ የሚንቀሳቀሰው አፍራሽ የጥፋት ሃይል መንጋውን በማደናገር ኢትዮጵያን በጢም ሳራዋ ለመድፋት እያሳየ ያለውን መቋመጥ፣እንቅልፍ አልባ የጥፋት እንቅስቃሴን ቸላ ማለት ተገቢ አይደለም። አላማው መቼም ቢሆን ሊሳካለት የማይችል ቢሆንም አላስፈላጊ መስዋዕትነት ላለመክፈል ግን ቅንጣት ታህል እድል ሊሰጠው አይገባም‼️

የሚሄዱበት መንገድ ልክ መስሏቸው በንፁህ ልቦናቸው የሚታገሉ የትግል ጉዟቸውን ያልመረመሩ ተደራቢ ሐቀኛ አማራዎችን አይመለከትም። የመንገዱን መዳረሻ ቆም ብሎ ማሰብ የግድ መሆኑን ግን እመክራለሁ‼️
ለእናት ኢትዮጵያ ዛሬም ድምፅ የሚሆኑ ቆራጥና የታመኑ ልጆች አሉ። ኤች አር 6600ን በመቃወም በአገረ አሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ድምፃቸውን እያሰሙ ነው!

ትናንትም ሆነ ዛሬ በኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና የሕዝብ ጥቅም የማትደራደሩ ኢትዮጵያዊያን በፀና ኢትዮጵያዊነታችሁ ባንዳነትን አሸንፋችሁታልና ምስጋና ይገባችኋል! ኩራቶችም ናችሁ‼️