አብን ከውስጥና ከውጭ በስመ አማራ ተቆርቋሪነት የተሰለፉ የአፍራሾቹን አላማ አክሽፎ ጉባኤውን በድልና በሰላም አጠናቋል። በጣም ደስም ይላል። በተሸናፊዎች ጩኸት መደንቆራችን ግን ይጠበቃል።
ኢትዮጵያን ሊያፈርሱ ክብሯን ሊያዋርዱ ቀን ተሌት እንቅልፍ አጥተው የሚደክሙ የእናት ጡት ነካሽ እንዳለ ሁሉ ስሟን በአለም አደባባይ የሚያነግሱ ብርቅዬ ልጆች አሏት።
የቤልግሬድ የ2022 የአለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ አንደኛ ሆና አጠናቃለች። እንኳን ደስ አለን!
የቤልግሬድ የ2022 የአለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ አንደኛ ሆና አጠናቃለች። እንኳን ደስ አለን!
ኢትዮ 360 እና ኢትዮ ፎረም በመቀሌ
የትግሬ ወራሪ ቡድን ስር ከሚገኙት ሚዲያዎች ውጭ መቀሌ ላይ ህዝብ እንዲሰማቸው የተከፈቱለት ሚዲያዎች አሉ። የሚሆነው እንዲህ ነው። ከዩቱዩብ አውርደው በስፒከር ለሕዝብ እንዲሰማ ያደርጉታል።
ያው ትህነግን ያህል ሚዲያ አፋኝ የለም። በአብዮታዊ ዲሞክራሲ አንደኛውና ትልቁ የተጠቀመበት ሚዲያን እንዴት ማፈንና ማሰራጨት እንዳለበት ነው። ስለሆነም ማን ለሕዝብ መድረስ ማን መታፈን እንዳለበት ያውቃል። ለጊዜው በአማራጭነት ሁለቱን ሚዲያዎች መርጦለታል። አንደኛው ኢትዮ ፎረም ነው። ይህ ሚዲያ ከትህነግ በቀጥታ የተከፈለው ነው። ከወራት በፊት አቻምየለህ ታምሩ ከአቃቤ ሕግ ያገኘውን መረጃ ዋቢ አድርጎ እነ ደብረፅዮን ለዚህ ሚዲያ እንዴት ሲከፍሉት እንደነበር ጠቅሷል።
ይህ ሚዲያ ላይ አሁን የሚሰራው ጋዜጠኛ በአንድ ወቅት በመተማ አሳፎ ቤንሻንጉል የሚደርሰውን የታላቋ ትግራይ የሚሏትን የሀሰብ አገር ካርታ ስህተት አስመስሎ በኢቲቪ የለቀቀው ጋዜጠኛ ነው። አሁን ደግሞ አማራን ሲሰድብ፣ ትህነግን ሰበብ ፈልጎ ሲደግፍ የሚውል ነው። ከዚህ ሚዲያ ባሻገር ሕዝብ እንዲሰማው በአደባባይ ማን ፈቃድ አገኘ! ኢትዮ 360! ለምን ይመስልሃል? ትግርኛ ሙዚቃ ስለሚለቅ ነው? በትግርኛ ፕሮግራም ስላለው ነው? ትህነግ የሀሰብ ነፃነትን ስለሚፈቅድ ነው? አይደለም!
ምንም እንኳን ከስር ባለው ፅሁፍ ሁለቱም ፀረ ትግሬ ናቸው ያለችው ሆን ብላ ነው። የውጭ ሰላም አስከባሪ ካልገባ የሚሉትን የሚያቀርበው 360 ነው፣ አዲስ አበባ ድረስ ሰተት ብለው ይግቡ ልቀቁላቸው የተባለው 360 ላይ ነው፣ ሲመቱም ምንም ሳይሆኑ ሰተት ብለው ይውጡ እባካችሁ ተብሎ የተለመነላቸው 360 ላይ ነው፣ በሁመራ በኩል ኮሪደር ይለቅላቸው የተባለው 360 ላይ ነው፣ ድርድር ይቀመጡ የተባለው 360 ላይ ነው፣ በቅርቤ የቤንሻልጉሉ ጉዳይ የመጀመርያ ፍንጭ ወጥቶ ደብረፅዮን ቃል በቃል የተናገረው አጀንዳ የተጀመረው 360 ላይ ነው። ኧረ ስንቱ?
ትህነግ አይደለም ትግራይ ላይ ኢትዮጵያ ውስጥ ስንት ሚዲያ አፍኗል። አሁን ከኢንተርኔት አውርዶ ሕዝብን ሊያስደምጣቸው የሚችለው ይጠቅሙኛል የሚላቸውን ሚዲያዎች ነው። ለማንኛው ትግራይ ላይ የተፈቀዱ ሚዲያዎች ዝርዝር
1) ድምፀ ወያነ
2) TMH
3)ትግራይ ቲቪ
4) ኢትዮ ፎረም
5) ኢትዮ 360
ማሳሰቢያ:_ ያለ ትህነግ ፈቃድና እቅድ ምንም አይነት ሚዲያ በነፃነት ይሰማል ብለው እንዳይሸወዱ። ትግራይ ነው።
ሌላ ማሳሰቢያ:_ ትህነግ ሁለቱን ሚዲያዎች መርጦ ሕዝብ እንዲሰማቸው ያደረገው ከፊታቸው "ኢትዮ" የሚል ስላላቸው እንዳይመስልዎት። አጀንዳቸውን ፈልጎት ነው። በምንም እሱን የሚጠቅሙ እንጅ የማይጎዱ እንደሆኑ ስለሚያውቅ ነው። አንደኛውን እንደከፈለው ዐቃቤ ሕግ አረጋግጧል። ሌላኛውን በአጀንዳው መገመት ነው።
****
ጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው እንደፃፈው
የትግሬ ወራሪ ቡድን ስር ከሚገኙት ሚዲያዎች ውጭ መቀሌ ላይ ህዝብ እንዲሰማቸው የተከፈቱለት ሚዲያዎች አሉ። የሚሆነው እንዲህ ነው። ከዩቱዩብ አውርደው በስፒከር ለሕዝብ እንዲሰማ ያደርጉታል።
ያው ትህነግን ያህል ሚዲያ አፋኝ የለም። በአብዮታዊ ዲሞክራሲ አንደኛውና ትልቁ የተጠቀመበት ሚዲያን እንዴት ማፈንና ማሰራጨት እንዳለበት ነው። ስለሆነም ማን ለሕዝብ መድረስ ማን መታፈን እንዳለበት ያውቃል። ለጊዜው በአማራጭነት ሁለቱን ሚዲያዎች መርጦለታል። አንደኛው ኢትዮ ፎረም ነው። ይህ ሚዲያ ከትህነግ በቀጥታ የተከፈለው ነው። ከወራት በፊት አቻምየለህ ታምሩ ከአቃቤ ሕግ ያገኘውን መረጃ ዋቢ አድርጎ እነ ደብረፅዮን ለዚህ ሚዲያ እንዴት ሲከፍሉት እንደነበር ጠቅሷል።
ይህ ሚዲያ ላይ አሁን የሚሰራው ጋዜጠኛ በአንድ ወቅት በመተማ አሳፎ ቤንሻንጉል የሚደርሰውን የታላቋ ትግራይ የሚሏትን የሀሰብ አገር ካርታ ስህተት አስመስሎ በኢቲቪ የለቀቀው ጋዜጠኛ ነው። አሁን ደግሞ አማራን ሲሰድብ፣ ትህነግን ሰበብ ፈልጎ ሲደግፍ የሚውል ነው። ከዚህ ሚዲያ ባሻገር ሕዝብ እንዲሰማው በአደባባይ ማን ፈቃድ አገኘ! ኢትዮ 360! ለምን ይመስልሃል? ትግርኛ ሙዚቃ ስለሚለቅ ነው? በትግርኛ ፕሮግራም ስላለው ነው? ትህነግ የሀሰብ ነፃነትን ስለሚፈቅድ ነው? አይደለም!
ምንም እንኳን ከስር ባለው ፅሁፍ ሁለቱም ፀረ ትግሬ ናቸው ያለችው ሆን ብላ ነው። የውጭ ሰላም አስከባሪ ካልገባ የሚሉትን የሚያቀርበው 360 ነው፣ አዲስ አበባ ድረስ ሰተት ብለው ይግቡ ልቀቁላቸው የተባለው 360 ላይ ነው፣ ሲመቱም ምንም ሳይሆኑ ሰተት ብለው ይውጡ እባካችሁ ተብሎ የተለመነላቸው 360 ላይ ነው፣ በሁመራ በኩል ኮሪደር ይለቅላቸው የተባለው 360 ላይ ነው፣ ድርድር ይቀመጡ የተባለው 360 ላይ ነው፣ በቅርቤ የቤንሻልጉሉ ጉዳይ የመጀመርያ ፍንጭ ወጥቶ ደብረፅዮን ቃል በቃል የተናገረው አጀንዳ የተጀመረው 360 ላይ ነው። ኧረ ስንቱ?
ትህነግ አይደለም ትግራይ ላይ ኢትዮጵያ ውስጥ ስንት ሚዲያ አፍኗል። አሁን ከኢንተርኔት አውርዶ ሕዝብን ሊያስደምጣቸው የሚችለው ይጠቅሙኛል የሚላቸውን ሚዲያዎች ነው። ለማንኛው ትግራይ ላይ የተፈቀዱ ሚዲያዎች ዝርዝር
1) ድምፀ ወያነ
2) TMH
3)ትግራይ ቲቪ
4) ኢትዮ ፎረም
5) ኢትዮ 360
ማሳሰቢያ:_ ያለ ትህነግ ፈቃድና እቅድ ምንም አይነት ሚዲያ በነፃነት ይሰማል ብለው እንዳይሸወዱ። ትግራይ ነው።
ሌላ ማሳሰቢያ:_ ትህነግ ሁለቱን ሚዲያዎች መርጦ ሕዝብ እንዲሰማቸው ያደረገው ከፊታቸው "ኢትዮ" የሚል ስላላቸው እንዳይመስልዎት። አጀንዳቸውን ፈልጎት ነው። በምንም እሱን የሚጠቅሙ እንጅ የማይጎዱ እንደሆኑ ስለሚያውቅ ነው። አንደኛውን እንደከፈለው ዐቃቤ ሕግ አረጋግጧል። ሌላኛውን በአጀንዳው መገመት ነው።
****
ጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው እንደፃፈው
አማራ የሕልውና አደጋ ተጋርጦበታል በሚል በአደባባይ በአማራ ተቆርቋሪነት ስም የተሰለፈው አካል ዋነኛ ስራው በኢትዮጵያዊነታቸው የማይደራደሩ ወያኔን አጥብቀው የሚቃወሙና የሚታገሉ ኢትዮጵያዊያንን፣ ለአማራ ሁለንተናዊ ጥቅም መከበር የሚሰሩ ጠንካራ የአማራ ልጆችን እና ለአማራው አጋር የሚሆኑ ብሄሮችን 24/7 መውቀስ፣ መተቸት፣ መስደብ እና ማሰደብ ነው። ለአማራ ሕልውና ቀዳሚ ስጋት ለሆነው ወያኔ በግልጽ እና በስውር ድጋፍ ማድረጋቸው እንዳለ ሆኖ ለአማራ ህዝብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚታገሉ ግለሰቦችን፣ ድርጅቶችን እና ተቋማትን ስም በማያቋርጥ ዘመቻ እያጠፉ የአማራን ሕልውናን ልናስከብር ነው የሚለው አካሄድ ፈፅሞ የሚያዛልቅ መንገድ ሊሆን አይችልም።
አማራ የሕልውና ስጋት እንዳለበት የሚያምን አማራ ነኝ የሚል ሰው ነጋ ጠባ አጀንዳው ወያኔን አምርረው የሚጠሉና የሚታገሉ ግለሰቦችና ቡድኖችን ማጥላላት ከሆነ ከዚህ በላይ ለአማራ አንድነት በመቆርቆር ስም ሊታለፍ አይችልም።
ወያኔ የሚጠላውን እየጠሉ ወያኔ የሚወደውን እየወደዱ አማራ የሕልውና አደጋ ላይ ነው ለማለት የሚያስችል እንደምንስ ያለ የአማራ ተቆርቋሪነት ነው?!
አማራ የሕልውና አደጋ እንዳለበት የሚምን የአማራ ተቆርቋሪ ነኝ ባይ ወያኔ የፈጠረለትን ጠላት ወዳጅ ፤ ወያኔን የሚጠላን ጠላት አድርጎ አድርጎ መቀጠል ከቶ አይችልም። ጠላት ስለመቀነስ አዲስ ጠላት እንዳይፈጠር እየሰሩ ወዳጅ ለማብዛት ሊሰራ እንጅ እንዴት ይባስ ብሎ ወያኔ ለአማራው ከፈጠረለት ጠላት በላይ ተጨማሪ ጠላት ለማብዛት ያለእረፍት የሚባዝን ኃይል አማራ ነኝ ሊል ይችላል?!
ለመሆኑ ለአማራ በዚህ መንገድ ማንነታቸውን ደብቀውም ሆነ ገልጠው ከሚፅፉ ከእነዚህ ከሀዲዎች በላይ ሌላ ጠላት ከወዴትስ ይገኛል ?‼️
ይሄን ጥያቄ እያንዳንዱ አማራ በማህጸን ያለ ጽንስ ወይም በመቃብር የተኛ ሙት ካልሆነ በቀር እንኳን ለአማራ ሕልውና እና ሁለንተናዊ ጥቅም እታገላለሁ የሚለው ቀርቶ በሕይወት ያለ አማራ የሆነ ሁሉ ሊጠይቀው የሚገባ ተገቢ ብቻ ሳይሆን የግድ የሚለው ጉዳይ ነው።
አማራ የሕልውና ስጋት እንዳለበት የሚያምን አማራ ነኝ የሚል ሰው ነጋ ጠባ አጀንዳው ወያኔን አምርረው የሚጠሉና የሚታገሉ ግለሰቦችና ቡድኖችን ማጥላላት ከሆነ ከዚህ በላይ ለአማራ አንድነት በመቆርቆር ስም ሊታለፍ አይችልም።
ወያኔ የሚጠላውን እየጠሉ ወያኔ የሚወደውን እየወደዱ አማራ የሕልውና አደጋ ላይ ነው ለማለት የሚያስችል እንደምንስ ያለ የአማራ ተቆርቋሪነት ነው?!
አማራ የሕልውና አደጋ እንዳለበት የሚምን የአማራ ተቆርቋሪ ነኝ ባይ ወያኔ የፈጠረለትን ጠላት ወዳጅ ፤ ወያኔን የሚጠላን ጠላት አድርጎ አድርጎ መቀጠል ከቶ አይችልም። ጠላት ስለመቀነስ አዲስ ጠላት እንዳይፈጠር እየሰሩ ወዳጅ ለማብዛት ሊሰራ እንጅ እንዴት ይባስ ብሎ ወያኔ ለአማራው ከፈጠረለት ጠላት በላይ ተጨማሪ ጠላት ለማብዛት ያለእረፍት የሚባዝን ኃይል አማራ ነኝ ሊል ይችላል?!
ለመሆኑ ለአማራ በዚህ መንገድ ማንነታቸውን ደብቀውም ሆነ ገልጠው ከሚፅፉ ከእነዚህ ከሀዲዎች በላይ ሌላ ጠላት ከወዴትስ ይገኛል ?‼️
ይሄን ጥያቄ እያንዳንዱ አማራ በማህጸን ያለ ጽንስ ወይም በመቃብር የተኛ ሙት ካልሆነ በቀር እንኳን ለአማራ ሕልውና እና ሁለንተናዊ ጥቅም እታገላለሁ የሚለው ቀርቶ በሕይወት ያለ አማራ የሆነ ሁሉ ሊጠይቀው የሚገባ ተገቢ ብቻ ሳይሆን የግድ የሚለው ጉዳይ ነው።
በ ረ/ፕ Damtew Tessema Deneke
ኢትዮ-360 የሚባል ሚዲያ አያለ የህዝብ እና የሀገር ሚስጥር የማይታሰብ ሆኗል-የአማራንም ህዝብ አንድነት የሚፈታተን ነው።
የአማራ ህዝብ Ethio 360ን የመሰሉ ሚዲያዎችን እየደገፈ በራሱ ላይ መከፋፈል፣ ተስፋ መቁረጥ እና የአሉባልታ ወሬ እንዲነዛበት እየፈቀደ ነው። የአማራ ህዝብ መሪዎች በጠባብ ጠረጴዛ መክረው ሊፈጽሙት የሚችሉት ሚስጥራዊ ስራዎችን በማጋለጥ፣ እርሰ በእርስ አቧድኖ ለማጓተት ሳይሰለች እየሰራ ያለ ሚዲያ ከመሆኑም በላይ የግለሰብ ቂም መወጫ ነው የሆነው። የዩቲዪብ ሽቀላውን ለማድራት የብሶት ዜና ይዞ ስለመጣ የአማራ ህዝብ ተቆርቋሪ ወይም ድምጽ ነው ማለት አይቻልም።
ከፖለቲካም ሆነ ከማህበራዊ ፋይዳ አንጻር ሲለካ ኢትዮ 360 ከአማራ ህዝብ ጥቅም በተቃራኒ የቆመ ነው። በግልጽም
ከአማራ ህዝብ ይልቅ ለትህነግ ጥሩ የፖለቲካ አጋር እና የመረጃ ምንጭ ነው። ከዚህ ሚዲያ መጠንቀቅ እና ድጋፍን ማቋረጥ እጅግ ጠቃሚ ነው። ለህዝባችንም ትልቅ ውለታ ነው።
ኢትዮ-360 የሚባል ሚዲያ አያለ የህዝብ እና የሀገር ሚስጥር የማይታሰብ ሆኗል-የአማራንም ህዝብ አንድነት የሚፈታተን ነው።
የአማራ ህዝብ Ethio 360ን የመሰሉ ሚዲያዎችን እየደገፈ በራሱ ላይ መከፋፈል፣ ተስፋ መቁረጥ እና የአሉባልታ ወሬ እንዲነዛበት እየፈቀደ ነው። የአማራ ህዝብ መሪዎች በጠባብ ጠረጴዛ መክረው ሊፈጽሙት የሚችሉት ሚስጥራዊ ስራዎችን በማጋለጥ፣ እርሰ በእርስ አቧድኖ ለማጓተት ሳይሰለች እየሰራ ያለ ሚዲያ ከመሆኑም በላይ የግለሰብ ቂም መወጫ ነው የሆነው። የዩቲዪብ ሽቀላውን ለማድራት የብሶት ዜና ይዞ ስለመጣ የአማራ ህዝብ ተቆርቋሪ ወይም ድምጽ ነው ማለት አይቻልም።
ከፖለቲካም ሆነ ከማህበራዊ ፋይዳ አንጻር ሲለካ ኢትዮ 360 ከአማራ ህዝብ ጥቅም በተቃራኒ የቆመ ነው። በግልጽም
ከአማራ ህዝብ ይልቅ ለትህነግ ጥሩ የፖለቲካ አጋር እና የመረጃ ምንጭ ነው። ከዚህ ሚዲያ መጠንቀቅ እና ድጋፍን ማቋረጥ እጅግ ጠቃሚ ነው። ለህዝባችንም ትልቅ ውለታ ነው።
ሁሉም እየተነሳ የአማራ አክቲቪስቶች እንዲህና... እንዲያ... ናቸው ወይም አሉ እየተባለ ድምዳሜ ላይ ተደርሶ የሚሰጠው ፍረጃ ፍፁም የተሳሳተ ነው።
በቅርቡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በብልፅግና ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የአማራ አክቲቪስቶች "እባካችሁ ለአማራ ሕዝብ ሰላም እረፍት ስጡት" ያሉትን ንግግር በተመለከተም ስለየትኞቹ የአማራ አክቲቪስቶች ነው የሚያወሩት የሚያስብል ስለሆነ አልስማማበትም ብቻ ሳይሆን የምቃወመው ፍረጃ ነው።
ለሚፅፉት ነገር ኋላፊነት ወስደው በኢትዮጵያዊ ጨዋነት የአማራን እሴቶችን ጠብቀው ለሕዝባቸው ሁለንተናዊ ጥቅም መከበር እኩልነትን አስቀድመው ለሐገራቸው ነፃነትና ክብር ለመጠበቅ እውቀታቸው፣ ገንዘባቸውን፣ ጉልበታቸውንና ጊዜያቸውን ሰጥተው የሚታገሉ የሚሞግቱ የሚከራከሩ የአማራ አክቲቪስቶችን ድካም ዋጋ የሚያሳጣና ሞራል የሚሰብር ጅምላ ጨራሽ ፍረጃ ነውና እቃወመዋለሁ።
ይህን መሰል የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድና የሌሎች ብሔሮች የፖለቲካ ልሂቃን የአማራ አክቲቪስቶች ተብሎ እየተደረገ ያለ ጥቅል ፍረጃ ከሕዝባቸውም ሆነ ከሐገራቸው ጥቅምና ክብር በተቃራኒው ከቆሙ የአፍራሽነትና የአደፍራሽነት ሚና ካላቸው ግጭት ጠማቂ ባንዳዎች ጋር እኩል ጥፋተኛ አድርጎ የሚደምር የተሳሳተ ግምገማና ድምዳሜ ስለሆነ ውጤቱን ያከፋዋል።
ለመሆኑ የአማራ አክቲቪስቶች እንዲህና ..እንዲያ አሉ ተብሎ ፍረጃ የሚሰጠው በእነማን ምክንያት ነው? ማንነታቸው መመርመር አለበት።
በሳይበሩ የአማራ አክቲቪዝም አማራ መሆናቸው በአካል ጭምር ማንነታቸው የሚታወቁና ለሚፅፉት ነገር ኋላፊነት የሚወስዱ የተለዩት ምን ያህል አክቲቪስቶች ናቸው? ማንነታቸው ከሚታወቁት በእጥፍ ማንነታቸውን ደብቀው በአማራ ስም የሚፅፉ አማርኛ ተናጋሪ ፀረ-አማራዎችን ሁሉ እንደ አማራ አክቲቪስት ልንቆጥር ነው?
ነገ ላይ በሚኖረው የአሰላለፍ ለውጥ ራሱን ሲገልጥ የሸኔ ወይም የሕወሓት አባል (በአስተሳሰቡ ሳይሆን በብሔሩ) ሊሆን የሚችለው አሁን ላይ አማራውን በአማራ ማልያ ከራሱና ከሌሎች ጋር ለማጋጨት ነጋ ጠባ ሁከትና ብጥብጥ የአመፅ ጥሪ የሚያደርገው በብዕር ስም ማንነቱን ደብቆ በአማርኛ የሚፅፈው ሁሉ እንደ አማራ አክቲቪስት እንቁጠረው ከተባለ በቀጣይ ለአማራው መከራና እዳ እናውርድበት እንደማለት ነው።
የይለፍ ቃልና ቀይ መስመር ስለሌለ ማንም ዘሎ አማረኛ የቻለ ሁሉ አማራው ተራራው ወይም ተነስ አማራ! እያለ አቧራው ጨሰ የሚያስጨፍረው ሁሉ እንደ አማራ አክቲቪስት ይቆጠር ማለት ፍፁም ጠላትነት ነው።
ከዚህ በኋላ ይህን በጭንብል የሚንቀሳቀስ ግለሰብ-ተኮር የጥላቻ አጀንዳ አራማጅ ብሔር የሚሳደብ የአፍራሽና የአደፍርስ ሚና የያዘውን ሁሉ እንደ አማራ አክቲቪስት ቆጥራችሁ ድምዳሜ ላይ በመድረስ ከሆነ አስተያየት እየሰጣችሁ ያላችሁት ፍፁም ከመሳሳታችሁ በላይ ሌላም ስም የመስጠት ተደርጎ የሚወሰድ ነው።
የአማራ አክቲቪስቶች ነገር ወይም እንዲህና እንዲያ አሉ ከማለታችሁ በፊት አማራ የሆኑ የአማራ አክቲቪስቶች እነማን እንደሆኑ መመርመር ያስፈልጋል። የአማራ አክቲቪስቶች እነማን እንደሆኑ ካወቃችሁ በኋላ የምትይዙት አቋምና ውሳኔ ፌር የመሆን እድል ይኖረዋል።
በአካል ሲገለጥ አድዋ ሊሆን በሚችል ማንነቱን ደብቆ የሚፅፈውን ፌስቡከር ሁሉ የአማራ አክቲቪስቶች ወይም ፅንፈኛ ብሔርተኞች ማለትም ፍፁም ስህተት ነው። አማራ ስለመሆኑ ምንም ማረጋገጫ በሌለበት ሁኔታ በስመ የአማራ ተቆርቋሪ መስሎ ስለቀረበ ብቻ የአማራ አክቲቪስት ወይም ብሔርተኛ ማለት ልክ አይደለም። እንዲህ አይነት የግምገማ ችግር ሁሉንም አካል ትልቅ ዋጋ ሊያስከፍለው ይችላልና ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል። እንኳን በድብቅ ማንነት የሚፅፈው በግልጽ የተገለጠው ፀሐፊ ሁሉ ማንነቱን በደንብ መመርመር ያስፈልጋል።
በቅርቡ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በብልፅግና ጠቅላላ ጉባኤ ላይ የአማራ አክቲቪስቶች "እባካችሁ ለአማራ ሕዝብ ሰላም እረፍት ስጡት" ያሉትን ንግግር በተመለከተም ስለየትኞቹ የአማራ አክቲቪስቶች ነው የሚያወሩት የሚያስብል ስለሆነ አልስማማበትም ብቻ ሳይሆን የምቃወመው ፍረጃ ነው።
ለሚፅፉት ነገር ኋላፊነት ወስደው በኢትዮጵያዊ ጨዋነት የአማራን እሴቶችን ጠብቀው ለሕዝባቸው ሁለንተናዊ ጥቅም መከበር እኩልነትን አስቀድመው ለሐገራቸው ነፃነትና ክብር ለመጠበቅ እውቀታቸው፣ ገንዘባቸውን፣ ጉልበታቸውንና ጊዜያቸውን ሰጥተው የሚታገሉ የሚሞግቱ የሚከራከሩ የአማራ አክቲቪስቶችን ድካም ዋጋ የሚያሳጣና ሞራል የሚሰብር ጅምላ ጨራሽ ፍረጃ ነውና እቃወመዋለሁ።
ይህን መሰል የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድና የሌሎች ብሔሮች የፖለቲካ ልሂቃን የአማራ አክቲቪስቶች ተብሎ እየተደረገ ያለ ጥቅል ፍረጃ ከሕዝባቸውም ሆነ ከሐገራቸው ጥቅምና ክብር በተቃራኒው ከቆሙ የአፍራሽነትና የአደፍራሽነት ሚና ካላቸው ግጭት ጠማቂ ባንዳዎች ጋር እኩል ጥፋተኛ አድርጎ የሚደምር የተሳሳተ ግምገማና ድምዳሜ ስለሆነ ውጤቱን ያከፋዋል።
ለመሆኑ የአማራ አክቲቪስቶች እንዲህና ..እንዲያ አሉ ተብሎ ፍረጃ የሚሰጠው በእነማን ምክንያት ነው? ማንነታቸው መመርመር አለበት።
በሳይበሩ የአማራ አክቲቪዝም አማራ መሆናቸው በአካል ጭምር ማንነታቸው የሚታወቁና ለሚፅፉት ነገር ኋላፊነት የሚወስዱ የተለዩት ምን ያህል አክቲቪስቶች ናቸው? ማንነታቸው ከሚታወቁት በእጥፍ ማንነታቸውን ደብቀው በአማራ ስም የሚፅፉ አማርኛ ተናጋሪ ፀረ-አማራዎችን ሁሉ እንደ አማራ አክቲቪስት ልንቆጥር ነው?
ነገ ላይ በሚኖረው የአሰላለፍ ለውጥ ራሱን ሲገልጥ የሸኔ ወይም የሕወሓት አባል (በአስተሳሰቡ ሳይሆን በብሔሩ) ሊሆን የሚችለው አሁን ላይ አማራውን በአማራ ማልያ ከራሱና ከሌሎች ጋር ለማጋጨት ነጋ ጠባ ሁከትና ብጥብጥ የአመፅ ጥሪ የሚያደርገው በብዕር ስም ማንነቱን ደብቆ በአማርኛ የሚፅፈው ሁሉ እንደ አማራ አክቲቪስት እንቁጠረው ከተባለ በቀጣይ ለአማራው መከራና እዳ እናውርድበት እንደማለት ነው።
የይለፍ ቃልና ቀይ መስመር ስለሌለ ማንም ዘሎ አማረኛ የቻለ ሁሉ አማራው ተራራው ወይም ተነስ አማራ! እያለ አቧራው ጨሰ የሚያስጨፍረው ሁሉ እንደ አማራ አክቲቪስት ይቆጠር ማለት ፍፁም ጠላትነት ነው።
ከዚህ በኋላ ይህን በጭንብል የሚንቀሳቀስ ግለሰብ-ተኮር የጥላቻ አጀንዳ አራማጅ ብሔር የሚሳደብ የአፍራሽና የአደፍርስ ሚና የያዘውን ሁሉ እንደ አማራ አክቲቪስት ቆጥራችሁ ድምዳሜ ላይ በመድረስ ከሆነ አስተያየት እየሰጣችሁ ያላችሁት ፍፁም ከመሳሳታችሁ በላይ ሌላም ስም የመስጠት ተደርጎ የሚወሰድ ነው።
የአማራ አክቲቪስቶች ነገር ወይም እንዲህና እንዲያ አሉ ከማለታችሁ በፊት አማራ የሆኑ የአማራ አክቲቪስቶች እነማን እንደሆኑ መመርመር ያስፈልጋል። የአማራ አክቲቪስቶች እነማን እንደሆኑ ካወቃችሁ በኋላ የምትይዙት አቋምና ውሳኔ ፌር የመሆን እድል ይኖረዋል።
በአካል ሲገለጥ አድዋ ሊሆን በሚችል ማንነቱን ደብቆ የሚፅፈውን ፌስቡከር ሁሉ የአማራ አክቲቪስቶች ወይም ፅንፈኛ ብሔርተኞች ማለትም ፍፁም ስህተት ነው። አማራ ስለመሆኑ ምንም ማረጋገጫ በሌለበት ሁኔታ በስመ የአማራ ተቆርቋሪ መስሎ ስለቀረበ ብቻ የአማራ አክቲቪስት ወይም ብሔርተኛ ማለት ልክ አይደለም። እንዲህ አይነት የግምገማ ችግር ሁሉንም አካል ትልቅ ዋጋ ሊያስከፍለው ይችላልና ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል። እንኳን በድብቅ ማንነት የሚፅፈው በግልጽ የተገለጠው ፀሐፊ ሁሉ ማንነቱን በደንብ መመርመር ያስፈልጋል።
በአሜሪካ ኮንግረስ እና ሴኔት በኩል በረቂቅ ደረጃ የሚገኙት ኤች አር 6600 እንዲሁም ኤስ 3199 በሚል የቀረቡ ረቂቅ ህጎችን ማርች 23 በሴኔቱ የውጭ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ለማየት የተያዘውን ቀጠሮ በሐገር ቤትና በባህር ማዶ የምንገኝ በተለይም በመላው አሜሪካ የምትገኙ ኢትዮጵያውያን ትውልደ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ በአንድነት ቆመን ረቂቅ ሕጉ እንዳይፀድቅ ተቃውሟችንን ልናሰማ ይገባል።
ረቂቅ ህጎቹ ከጸደቁ ኢትዮጵያ ከሌሎች አገራት ጋር የሚኖራት የጸጥታ፣ የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ ግንኙነት በሌሎች ኃይሎች በጎ ፈቃድ እንዲንጠለጠልና ኢትዮጵያ ራሷን እንዳትከላከል ጥገኛ የሚያደርግ በጥቅሉ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት የሚዳፈር ነው። ኢትዮጵያዊያን በተባበረ ክንዳቸው በከበረ ደማቸው በጦርነት ያስጠበቁትን ሉዓላዊነት የሚዳፈር ረቀቂ ሕግ ነው።
የውጭ ብድርና እርዳታ የውጭ ንግድና ኢንቨስትመንት ተከልክሎ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኘው ወገናችን ጨምሮ ዲያስፖራውን ከእናት አገሩ እና ዘመዱ ጋር የሚያቆራርጥ ጠርናፊ ሕግ ነው። በኮቪድ እና በኑሮ ውድነት የተጎዳውን ኢኮኖሚ በጦርነት ቤተሰቡን፣ ቤት ንብረቱን ያጣው ወገናችን ፈጥኖ እንዳይቋቋም፣ የወደሙ የትምህርት፣ የጤና እና ሌሎች የመሰረተ-ልማቶች ፈጥነው እንዳገነቡ እንቅፋት የሚሆን ነውና ሁሉም ኢትዮጵያዊ በአንድነት ቆሞ ረቂቅ ሕጉ እንዳይፀድቅ የተቃውሞ ድምፁን የማሰማት የትውልድ ኋላፊነት አለበት።
ከሁሉም በላይ ደግሞ ይህ ረቂቅ በህወሓት ተንኳሽነት የተጀመረውን ጦርነት ከግምት ውስጥ ያላስገባ፣ ህወሓት የፈጸማቸውን የዘር ማጥፋት ወንጀሎች የማያይ፣ በጥቆሉ ባለፉት 30 ዓመታት ሲጨፈጨፍና ሲመነዝር የነበረውን ህወሓትን ተጠያቂ የማያደርግ በመሆኑ ሴራው ግልጽ ነው። አገር ለማፍረስ የሚሰነዘር ሙከራ ነው።
የረቀቂ ሕጉ የሚፀድቅ ከሆነ የኢትዮጵያን ሕዝብ መስዕዋትነት ገደል የሚከት ከመሆኑም በላይ ኢኮኖሚካሊ ደሀ የሚያደርግ ህወሓትና መሰል የሽብር ቡድኖች ተመልሰው እንዲያንሰራሩ የሚያመቻች በመሆኑ አገር ወዳድ የሆነ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ያለ ልዩነት ጉዳዩን ሊያወግዘው ይገባል።
ረቂቅ ህጎቹ ከጸደቁ ኢትዮጵያ ከሌሎች አገራት ጋር የሚኖራት የጸጥታ፣ የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ ግንኙነት በሌሎች ኃይሎች በጎ ፈቃድ እንዲንጠለጠልና ኢትዮጵያ ራሷን እንዳትከላከል ጥገኛ የሚያደርግ በጥቅሉ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት የሚዳፈር ነው። ኢትዮጵያዊያን በተባበረ ክንዳቸው በከበረ ደማቸው በጦርነት ያስጠበቁትን ሉዓላዊነት የሚዳፈር ረቀቂ ሕግ ነው።
የውጭ ብድርና እርዳታ የውጭ ንግድና ኢንቨስትመንት ተከልክሎ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኘው ወገናችን ጨምሮ ዲያስፖራውን ከእናት አገሩ እና ዘመዱ ጋር የሚያቆራርጥ ጠርናፊ ሕግ ነው። በኮቪድ እና በኑሮ ውድነት የተጎዳውን ኢኮኖሚ በጦርነት ቤተሰቡን፣ ቤት ንብረቱን ያጣው ወገናችን ፈጥኖ እንዳይቋቋም፣ የወደሙ የትምህርት፣ የጤና እና ሌሎች የመሰረተ-ልማቶች ፈጥነው እንዳገነቡ እንቅፋት የሚሆን ነውና ሁሉም ኢትዮጵያዊ በአንድነት ቆሞ ረቂቅ ሕጉ እንዳይፀድቅ የተቃውሞ ድምፁን የማሰማት የትውልድ ኋላፊነት አለበት።
ከሁሉም በላይ ደግሞ ይህ ረቂቅ በህወሓት ተንኳሽነት የተጀመረውን ጦርነት ከግምት ውስጥ ያላስገባ፣ ህወሓት የፈጸማቸውን የዘር ማጥፋት ወንጀሎች የማያይ፣ በጥቆሉ ባለፉት 30 ዓመታት ሲጨፈጨፍና ሲመነዝር የነበረውን ህወሓትን ተጠያቂ የማያደርግ በመሆኑ ሴራው ግልጽ ነው። አገር ለማፍረስ የሚሰነዘር ሙከራ ነው።
የረቀቂ ሕጉ የሚፀድቅ ከሆነ የኢትዮጵያን ሕዝብ መስዕዋትነት ገደል የሚከት ከመሆኑም በላይ ኢኮኖሚካሊ ደሀ የሚያደርግ ህወሓትና መሰል የሽብር ቡድኖች ተመልሰው እንዲያንሰራሩ የሚያመቻች በመሆኑ አገር ወዳድ የሆነ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ያለ ልዩነት ጉዳዩን ሊያወግዘው ይገባል።
ወያኔ የሚጠላውን እየጠሉ ወያኔ የሚወደውን እየወደዱ አማራ የህልውና አደጋ ላይ ነው ለማለት የሚያስችል እንደምንስ ያለ የአማራ ተቆርቋረነት ነው?‼️
HR 6600 እንዲፀድቅ እየተንቀሳቀሱ ያሉ ሰዎች ወያኔ ከአማራ ጋር ሂሳብ ለማወራረድ ኢትዮጵያን ለማፍረስ አዋጅ እየነገረ ጦርነት ሲከፍት "ጦርነቱ እኛን አይመለከትም፤ እንዳትሳተፉ፤ጦርነቱ የአብይን ሕልውና ለማስጠበቅ ነው" ሲሉ የነበሩ በስመ የአማራ ተቆርቋሪነት የወያኔን አጀንዳ በመሸጥ መንገድ እየጠረጉ በሕዝባችን ላይ ግፍ እንዲፈፀምበት ሐገር እንዲፈርስ ያለ የሌለ አቅማቸው ተጠቅመው ያልተሳካላቸው ባንዳዎች ናቸው። እነ ነውር ጌጡ ሁሉም ሰው እንደነሱ ስለሚመስላቸው "ትናንት ዲያስፖራው ኢትዮጵያ አትፈርስም" ብሎ ሐሩና ቁሩ የተቀናጀው የተሳሳተው የፕሮፖጋንዳ ዘመቻ ሳይገድባቸውና ሳያደናግራቸው ድምፃቸውን በሚያሰሙበት ወቅት፣ ከዛም ወደእናት አገራቸው ገቡ ሲባሉ በዲያስፖራው ላይ የስድብ ሜኑ ያቀርቡ የነበሩ መሆናቸውን ረስተው፣ ዛሬ ተመልሰው ደግሞ ዲያስፖራውን ሆነው ዲያስፖራው በአብይ ላይ ስላኮረፈ ኤች አር 6600 ረቀቂ ሕግን በተመለከተ እንዲፀድቅ ካልሆነ በተቃውሞ ለኢትዮጵያ ድምፅ አይሆንም እያሉ ነው። እነዚህ የወያኔ አጀንዳ አሻሻጮች እየነገሩን ያሉት ስለ ዲያስፖራው ሳይሆን ስለእነሱ አላማ ነው። ቢሆን ብለው የሚመኙት ነው በዲያስፖራው በኩል ለማስፈጸም እየዳከሩ ያሉት። ኤች አር 6600 እንዲፀድቅ ብቻ ሳይሆን ሌሎች በወያኔ በኩል በጦርነት ያልተሳኩለትን ሐገርን በማዕቀብ አዳክሞ ለማፍረስ ሌሎች ተጨማሪ ማዕቀቦች ይረቀቁና ይፀድቁ ዘንድ የሚችለውን ግፊት የሚያደርግና ዱላ የሚያቀብል ነው።
እነዚህ የወያኔ አጀንዳ አሻሻጮች ወይም መንገድ ጠራጊ የእፍኝት ልጆች ዲያስፖራውን ያኮረፈ በማስመሰል ለኢትዮጵያ ድምፅ ለመሆን የተቃውሞ ድምፁን አያሰማም የሚሉትና ይህኑን በመደጋገም ለተቃውሞ ሰልፍ የተዘጋጀውን ለማስቀረትና ለማደናገር በማለም የሚሰራ እንጅ እውነታው እንደዛ ስለሆነ አይደለም። የኢትዮጵያን መፍረስ ለማየት የሚቋምጠው ሃይል ዲያስፖራው ትናንት ድምፁን ያስተጋባው ለአብይ አህመድ ስልጣን ስለመሰለው ነው። ዲያስፖራው ትናንት ድምፁን ያሰማው ግን ለአብይ አህመድ ስልጣን ሕልውና መከበር ሳይሆን ለእናት ሐገሩ ሉዓላዊነትና ጥቅም መከበር ሲል ነው።
እናት ኢትዮጵያ በሕዝብ ፍላጎት ወይም በተፈጥሮ ሞት ሊያልፉ በሚችሉት አብይ አህመድ ወይም ብልፅግና ፓርቲ የምትቀየር ወይም ለእነሱ ብቻ ልትተው የምትችል አገር አይደለችም። ኢትዮጵያ ትናንት በልጆቿ የተባበረ ክንድ ለዛሬ እንደበቃችው ዛሬም በቁርጥ ቀን የልጆቿ ትግል ሉዓላዊነቷን አስከብራ ወደነገ ትሻገራለች። እናት አስራበችኝ ወይም አስከፋችኝ ተብሎ እናትነቷ አይፋቅም ብቻ ሳይሆን ጠላት የምንለው አካል እጁን እንዲያነሳባት ይቅርና እንዲገላምጣት እድል እንደማንሰጠው ሁሉ አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ወያኔና የግብር ልጆቹ(በመንግስታዊ መዋቅሩ ውስጥ ባሉት ድጋፍ ጭምር) በሚያደርሱት ግፍ አኩርፈን እናት ኢትዮጵያን ለዘንዶው አሳልፈን ልንሰጣት አንችልም። አይገባምም።
ኤች አር 6600 ረቂቅ ሕጉ እንዳይፀድቅ ዲያስፖራው ድምፁን በተቃውሞ በሰልፍ የሚያሰማው የወያኔ አጀንዳ አሻሻጮች እንደሚሉት ለማንም ብሎ ሳይሆን ለእናት ሐገሩ ሕልውና ሉዓላዊነት እና ዘላቂ ጥቅም መረጋገጥ ብቻ ሲል ነው። የቱንም ያህል የፖለቲካ ልዩነት ቢፈጠር የሚያስኮርፍ ነገር ቢኖር በእናት አገር ኢትዮጵያ ሕልውና እና ሁለንተናዊ ዘላቂ ጥቅም መከበር የሚደራደር የለም። ካለም እሱ የእፍኝት ልጅ ነው።
የኢትዮጵያ ሕልውና እና ሁለንተናዊ ዘላቂ ጥቅም ግድ የሚለን ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ የእስስትና የአሳማንን ባህሪይ በተላበሱ በወያኔ ጉዳይ አስፈፃሚዎች የአፍራሽ ስራ ልንደነቅ አይገባም።
ነውርን ጌጥ ማድረግ ክብር፣ ባንዳነትን መላበስ አዋቂነትና የሕይወት መርህ እንዲሁም የባህሪይ ገንዘብ ካደረገ አካል በየትኛውም ጊዜ የምንሰማቸው ንግግሮች እና የምናያቸው ተግባሮች የኢትዮጵያን አንድነት የሚሸረሽርና ሕልውናዋን ወደባሰ አደጋ የሚያጋልጥ ነው። የማንንም አሳዳጊ የበደለውን አግድም አደግን የክህደት ጩኸት ሳንሰማ ሕዝብን ይጠቅማል ሐገርን ያለማል ብለን የምናስበውን እና የሚጠበቅብነን ታሪካዊ መልካም ነገሮችን መስራት ይገባናል። መተባበርና መከባበር ከቻልን እምቅ አቅም አለና ሊያቆመን የሚገባ ምንም አይነት ምድራዊ ሃይል የለም‼️
እነዚህ የወያኔ አጀንዳ አሻሻጮች ወይም መንገድ ጠራጊ የእፍኝት ልጆች ዲያስፖራውን ያኮረፈ በማስመሰል ለኢትዮጵያ ድምፅ ለመሆን የተቃውሞ ድምፁን አያሰማም የሚሉትና ይህኑን በመደጋገም ለተቃውሞ ሰልፍ የተዘጋጀውን ለማስቀረትና ለማደናገር በማለም የሚሰራ እንጅ እውነታው እንደዛ ስለሆነ አይደለም። የኢትዮጵያን መፍረስ ለማየት የሚቋምጠው ሃይል ዲያስፖራው ትናንት ድምፁን ያስተጋባው ለአብይ አህመድ ስልጣን ስለመሰለው ነው። ዲያስፖራው ትናንት ድምፁን ያሰማው ግን ለአብይ አህመድ ስልጣን ሕልውና መከበር ሳይሆን ለእናት ሐገሩ ሉዓላዊነትና ጥቅም መከበር ሲል ነው።
እናት ኢትዮጵያ በሕዝብ ፍላጎት ወይም በተፈጥሮ ሞት ሊያልፉ በሚችሉት አብይ አህመድ ወይም ብልፅግና ፓርቲ የምትቀየር ወይም ለእነሱ ብቻ ልትተው የምትችል አገር አይደለችም። ኢትዮጵያ ትናንት በልጆቿ የተባበረ ክንድ ለዛሬ እንደበቃችው ዛሬም በቁርጥ ቀን የልጆቿ ትግል ሉዓላዊነቷን አስከብራ ወደነገ ትሻገራለች። እናት አስራበችኝ ወይም አስከፋችኝ ተብሎ እናትነቷ አይፋቅም ብቻ ሳይሆን ጠላት የምንለው አካል እጁን እንዲያነሳባት ይቅርና እንዲገላምጣት እድል እንደማንሰጠው ሁሉ አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ወያኔና የግብር ልጆቹ(በመንግስታዊ መዋቅሩ ውስጥ ባሉት ድጋፍ ጭምር) በሚያደርሱት ግፍ አኩርፈን እናት ኢትዮጵያን ለዘንዶው አሳልፈን ልንሰጣት አንችልም። አይገባምም።
ኤች አር 6600 ረቂቅ ሕጉ እንዳይፀድቅ ዲያስፖራው ድምፁን በተቃውሞ በሰልፍ የሚያሰማው የወያኔ አጀንዳ አሻሻጮች እንደሚሉት ለማንም ብሎ ሳይሆን ለእናት ሐገሩ ሕልውና ሉዓላዊነት እና ዘላቂ ጥቅም መረጋገጥ ብቻ ሲል ነው። የቱንም ያህል የፖለቲካ ልዩነት ቢፈጠር የሚያስኮርፍ ነገር ቢኖር በእናት አገር ኢትዮጵያ ሕልውና እና ሁለንተናዊ ዘላቂ ጥቅም መከበር የሚደራደር የለም። ካለም እሱ የእፍኝት ልጅ ነው።
የኢትዮጵያ ሕልውና እና ሁለንተናዊ ዘላቂ ጥቅም ግድ የሚለን ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ የእስስትና የአሳማንን ባህሪይ በተላበሱ በወያኔ ጉዳይ አስፈፃሚዎች የአፍራሽ ስራ ልንደነቅ አይገባም።
ነውርን ጌጥ ማድረግ ክብር፣ ባንዳነትን መላበስ አዋቂነትና የሕይወት መርህ እንዲሁም የባህሪይ ገንዘብ ካደረገ አካል በየትኛውም ጊዜ የምንሰማቸው ንግግሮች እና የምናያቸው ተግባሮች የኢትዮጵያን አንድነት የሚሸረሽርና ሕልውናዋን ወደባሰ አደጋ የሚያጋልጥ ነው። የማንንም አሳዳጊ የበደለውን አግድም አደግን የክህደት ጩኸት ሳንሰማ ሕዝብን ይጠቅማል ሐገርን ያለማል ብለን የምናስበውን እና የሚጠበቅብነን ታሪካዊ መልካም ነገሮችን መስራት ይገባናል። መተባበርና መከባበር ከቻልን እምቅ አቅም አለና ሊያቆመን የሚገባ ምንም አይነት ምድራዊ ሃይል የለም‼️
HR-6600 ረቂቅ ሕግ ቢፀድቅ አማራን ሊጎዳው አይችልምና እንደግፈው እንደሚለው ወያኔ መሩ የፌስቡክ አማራ አይደለም ኤች አር 6600 ብቻ ሳይሆን ሪዞልሽኑን የብሔር መልክ ሰጥተን እንየው ከተባለ በኢትዮጵያ ውስጥ ከአማራ በላይ ሊጎዳ የሚችል ብሔር ፈፅሞ አይኖርም። ወያኔ መሩ የፌስቡክ አማራ ኤች አር 6600 ቢፀድቅ ይጠላል ወይም ይጎዳል ብሎ የሚያስበው አካል በተጠያቂነት ወይም በጉዳት ደረጃ ከአማራው ጥቅም ጋር ለድርድር ፈፅሞ የሚቀርብ አይደለም። ኤች አር 6600ን ጉዳቱን እንደብሔር ከተመለከትነው ሌሎች ብሔሮች ለተጠያቂነት ጥቂት ሰዎችን ከማዋጣታቸው ውጭ እንደ ሐገር በሚኖረው ተፅዕኖ ካልሆነ እዚህ ግባ የሚባል ጉዳት አያስተናግዱም። አማራ ግን በየትኛውም መመዘኛ እንደሕዝብ ተጠያቂ ወይም ተጎጅ የሚሆንበት ነው። በአጭሩ ረቂቅ ሕጉ የሚለው በጦርነቱ በየትኛውም አይነት መንገድ ጦርነቱን የደገፈና ተሳትፎ ያደረገ ሁሉ ተጠያቂ ነው ይላል።
ጦርነቱ የት አካባቢ ነው ነበር የተደረገው? ጦርነቱ እኛን አይመለከተንም ካሉ ሰዎች ውስጥ እነማንን ሊመለከት እንደማይችል መፈለግ ይቀላል😂
ጦርነቱ የት አካባቢ ነው ነበር የተደረገው? ጦርነቱ እኛን አይመለከተንም ካሉ ሰዎች ውስጥ እነማንን ሊመለከት እንደማይችል መፈለግ ይቀላል😂
HR-6600 ይፅደቅ አንቃወምም የሚሉት ሰዎች አብዛኞቹ ምን አይነት ሰዎች ቢሆኑ ጥሩ ነው። አማራው ተራራው! አማራ ተነስ! የሚሉ እንዲሁም በዋናነት የሚጠየቁትና የጉዳቱ ሰለባ የሚሆኑት የአማራ ልዩሃይል እና አማራ በፋኖ ጠንክሮ ይደራጅ ይታጠቅ የሚሉ ሰዎች መሆናቸው ነው😂
መታደል ነው እንዲህ እያሉ አዳማጭና ደጋፊ ማግኘት!
መታደል ነው እንዲህ እያሉ አዳማጭና ደጋፊ ማግኘት!
ወያኔ መሩ የፌስቡክ አማራ ምን ያህል ወደራሱ የሚተኩስ ሃይል እንደፈጠረ ለማወቅ የአማራ ልዩሃይል እና የፋኖ ደጋፊ ወይም ራሱ የአማራ ልዩሃይልና ፋኖ የነን ሰው የ HR-6600 ደጋፊ ሲያደርጉት ነው። ነገ ቢፀድቅ ይሄው ሃይል እኔማ ፋኖ ወይም የአማራ ልዩሃይል ነኝ ብሎ የአዛኝ መሳይ ቅቤ አንጓችነቱን ባሕሪይ ማሳየቱ አይቀርም። ነገሩ ለማስለቀስ ሲሞክር ቀድሞ ነጠላ የሚዘቀዝቅ ድንኳን የሚጥል ሐዘንተኛ ስላገኘ አይፈረድበትም።
የአማራ ብሔርተኝነት በማንም አልፎ ሂያጅ ማንነቱን ደብቆ በሚፅፍ የብዕር ስም ተጠቃሚ እንደፈለገ መነዳቱ ብቻ ሳይሆን እነሱ እየተደነቁ ማንነታቸውን ገልጠው በኋላፊነት ስም የሚፅፉ ሰዎች ስማቸው እንዲረክሱ መደረጉ ነው።
እስኪ ቸር ይንጋ‼️
የአማራ ብሔርተኝነት በማንም አልፎ ሂያጅ ማንነቱን ደብቆ በሚፅፍ የብዕር ስም ተጠቃሚ እንደፈለገ መነዳቱ ብቻ ሳይሆን እነሱ እየተደነቁ ማንነታቸውን ገልጠው በኋላፊነት ስም የሚፅፉ ሰዎች ስማቸው እንዲረክሱ መደረጉ ነው።
እስኪ ቸር ይንጋ‼️
በጌታቸው ሽፈራው
በHR 6600 ሰበብ ለትህነግ እጅ ስጡ ነው እያሉን ነው!
1) ወታደራዊ ጉዳይ ላይ ጠበቅ ብሎ የተሰራበት ነው። ትህነግ መንግስታዊ አይደለም። የመሳርያ እገዳ አልጣሉበትም። ቢችሉ እነሱ ይሰጡታል። በተለያየ መልኩ እንዳደረሱት እናውቃለን። ግብፅና ሱዳን በሱዳን ያለውን ሰራዊቱን እያስታጠቁት ነው። ነገር ግን ስለ ትህነግ በመሳርያ ክልከላ አልተነሳም። መሳርያ እንዳይገዛ የሚከለከለው የኢትዮጵያና የኤርትራ ሰራዊት፣የክልል ፀጥታ ኃይል ነው። የኢትዮጵያ ሰራዊት መሳርያ የሚገዛባቸው አገራት ተጠቅሰዋል። ትህነግ እንደ ሸማቂ በመቆጠሩ ከመደበኛ ሰራዊት ነው መሳርያ ቀምቶ ነው የሚታጠቀው። ከአሁን ቀደምም ከሰራዊቱ ቀምቷል። የቀማው በሌላ ተአምር አይደለም። የውጭ አካላት በመረጃ ወዘተ ደግፈውታል። ሀምሳ ሰው ከዚህ ጋር አለ፣ ከዚህ ደግሞ ይህን ያህል እያሉ በሳተላይት መረጃ ሲመግቡት፣ በኤምባሲ በኩል መረጃ ሲያደርሱት ከርመዋል። የውጭ የእርዳታ ድርጅቶች በብዙ ነገር አግዘውት ከጫካ አውጥተውታል። አሁንም እነዚህ አካላት ናቸው ይህን ሕግ እየደገፉ ያሉት።
የኢትዮጵያ ሰራዊት መሳርያ እንዳይገዛ ሲደረግ ነገ መሳርያም ተተኳሽም ሲያልቅበት የሚጎለብተው ትህነግ ነው። ባለፈው ትህነግን ያሽመደመደው ድሮን ተተኳሽ አይኖርም። ፋኖና ልዩ ኃይል የሚተኩሰው የመትረየስ ጥይት ቢያልቅ እንዳትገዛ ነው የተባልከው። የአፋርና የአማራ ፀጥታ ኃይል ከፊት ሆኖ ከኋላ የከባድ መሳርያ ድጋፍ እንዳያገኝ ነው የተባለው። እቀባው የኢትዮጵያ መንግስትን፣ የኤርትራ መንግስትን፣ የአማራ ክልልንና የአፋር ክልልን ፀጥታ ነው የሚያዳክመው። ትህነግን መሳርያ የሚያደርሰው ሞልቷል። ግን እቀባ ውስጥ እንዲገፋ አልተፈለገም። መሳርያ ኖረውም አልኖረውም አንድ ሚሊዮን ሰው አግተልትሎ ይመጣል። በሁሉም ተጠቃሚ ነው።
2) ማዕቀብ የትግሬ ወራሪ ማዳኛ ነው። ይህን ከአንዴም ሁለቴ አይተነዋል። ባለፈው መጋቢት ጥቃት ከማድረሱ በፊት የአሜሪካ መንግስት ማዕቀብን አጀንዳ አድርጎ ነበር። ይህን ማዕቀብ ፖለቲከኞቹና ወታደራዊ አመራሮቹ ፈርተው ወደፊት ወደኋላ ሲሉ ሰራዊቱን አስመቱት። ወደ ማዕቀብ ፊታቸውን እንዲያዞሩ ተደርገው ሰራዊቱ ማንንም አትንካ ተባለ። የትህነግ ታጣቂዎች ሲቪል መስለው ጭምር አጠቁት። የምዕራባውያኑ አላማ ተሳካ። ለትህነግ አትራፊ ነበር። አሁንም ለሌላ ጥቃት እያዘጋጁን ነው። ሰሞኑን በሱዳን በኩል በተደጋጋሚ ጥቃት ለመፈፀም ሞክሯል። ይህ ህግ ከገፋለት በደንብ ይቀጥላል። እያዘናጉን፣ወደ እነሱ እንድንዞር እያደረጉን ትህነግ ለጥቃት ይዘጋጃል።
3) ይህ አዋጅ የኢትዮጵያና የኤርትራ መንግስትን የአፋርና የአማራ ክልልን ቢጠቁ እንዳይመልሱ የሚያግድ ነው። ትህነግ እንደ ዋነኛ አካል ጠበቅ ያለ ትዕዛዝ አያርፍበትም። ቢተነኩስ እንደ ኢመደበኛ ቡድን ይታያል። ሌሎቹ ምላሽ ቢሰጡ ደግሞ ሕግ ጥሰት ነው። ስለሆነም ጎንደርም፣ ባሕርዳርም፣ ደሴም፣ ደብረብርሃንም፣ አስመራም፣ ሰመራም እንዲደርስ እድል ተመቻችቶለታል። የኢትዮጵያ መንግስት፣ የኤርትራ መንግስት፣ የአማራና አፋር ክልል ለመልሶ ማጥቃት ቢዘጋጁ ከአሁን ቀደም ምዕራባውያኑ ያቀዱትን ያሳካሉ። ሕገወጥ ስለሆነ ሰላም አስከባሪ ይግባ ይባለል።
4) ማዕቀቡ የአስር አመት እድሜ እንዳለው ተጠቅሷል። ይህ ማለት ኢትዮጵያና ኤርትራ ይዳከማሉ። ትህነግ የእርዳታ መንገዱ እንዲከፈትለት የመጀመርያው ቅድመ ሁኔታ ስለሆነ እርዳታውም ሌላውም ይደርሰዋል። ትህነግ አሁን ካለው ይጠናከራል። አገራቱና ክልሎቹ ሲዳከሙ ትህነግ በተራዘመ ጦርነትም ቢሆን የቻለውን ያደርጋል። የ17 አመት ጦርነት የሚጠቅሰው ትህነግ በቅርቡ ትንኮሳ ባያደርግ እንኳን ቀስ ብዬ አገኛቸዋለሁ ብሎ ያስባል። ተጠቃሚ ነው።
5) አበዳሪ ድርጅቶች እርዳታና ብድር እንዳይሰጡ ይከለከላሉ። ይህ ማለት በአማራና አፋር ክልል የወደሙባቸው አካባቢዎች ዩኒቨርሲቲዎችን ጨምሮ የመንግስት ተቋማት ከዓለም ባንክና ከሌሎች አበዳሪና እርዳታ ሰጭ ድርጅቶች እርዳታና ብድር አያገኙም። ፕሮጀክቶች አይኖሩም። የወደሙትን ለማካካስ ከባድ ነው። በአንፃሩ በሰብአዊ እርዳታው እንደ የአሜሪካ ተራድኦ ድርጅትን የመሳሰሉት ቅድሚያውን ወስደው እንዲሰሩ ይደረጋል። የእነ ሳማንታ ፓወር ድርጅት ደግሞ ምን ሲሰራ እንደከረመ የምናውቀው ነው። ለትህነግ የራዲዮ መገናኛም፣ መረጃም፣ ሌላም ሌላም የሚደርሰው በማን እንደነበር እናውቃለን።
6) ምዕራባውያኑ ንፁሃን ወለጋና መተከል ሲገደሉ ምንም አላሉም። በቀደም ኢሰመኮ ያወጣውን ዘግናኝ ወንጀል እንኳን አላወገዙም። በአንፃሩ ትህነግ በሀሰት ሲነግራቸው የከረመውን እውነት አስመስለው ሲዘግቡት ከርመዋል። በተለይ ወልቃይት ጠገዴን ምዕራብ ትግራይ እያሉ የሆነ ያልሆነውን ሲፅፉ ከርመዋል። ትህነግም ትግራይ ውስጥ ዘር ማጥፋት ተፈፅሞብኛል፣ በስሙ ይጠራ ሲል ነው የከረመው። የመጀመርያው "ዘር ማጥፋት" ተብሎ እንዲፈረጅ ይፈልጋል። ይህን ወለጋም መተከልም አያደርጉትም። የሚያደርጉት ትህነግ የሚፈልገው ላይ። ትህነግ ደግሞ ዘር ማጥፋት ተፈፀመ እንዲባል የሚፈልገው በዋነኛነት ወልቃይት ጠገዴ ነው። ከአሁን ቀደም አንቶኒዮ ብሊንከን ዘር ማፅዳት ተፈፅሟል ብሎ በሀሰት ከስሶናል። አሁን ይህን በሌላ ሕግ ማሰር ከዛም ትህነግን በተበዳይ ስም ወደ ወልቃይት ጠገዴ መመለስ ይፈልጋሉ። "ኮሪደር ይሰጣቸው" ሲሉ የከረሙት አላማቸው ይሄ ነው። ያኔ ሕዝባችን ከፍጅት የተከላከሉ ጀግኖቻችን ባንሸልማቸው እንኳን ይፈረጃሉ።
7) ይህን ሕግ እንዲፀድቅ በቀዳሚነት እየጮሁ ያሉት ትህነግና ኦነግ ናቸው። በእነሱ ፍላጎት ከፀደቀ የሚሆነው ግልፅ ነው። ድሮም ትህነግና ኦነግ አሜሪካ ተሰብስበው የሽግግር ወዘተ መንግስት ያቋቁሙ ተብሎ ነበር። አግዘዋቸዋል። ይህ ፍረጃ ፀደቀ ማለት ውጭ ያለ ሰው ለልዩ ኃይል፣ ለመከላከያ፣ ለፋኖ፣ ሚሊሻ ወዘተ እርዳታ ማድረስ አይችልም። የምንደግፋቸው ሳይቀሩ ይወነጀላሉ። ትህነግ ቢወረን፣ መከላከያን ደግፈን፣ ልዩ ኃይልን ደግፈን ወይንም የሚፈፅሙብንን ተቃውመን እንኳን ሰልፍ መውጣት አንችልም። የዘር ማጥፋት ብለው ወንጅለዋል። ለዚህ ውንጀላ ደጋፊ መሆን አይቻልም። ዲያስፖራው ሰልፍ እንኳን ማድረግ ይከለከላል።
አንድ የሚጠቀስ ነገር አለ። አሁን ያለው አገዛዝ አስጠቂ ነው። ዘራፊ ነው። ገዳይም ነው። ከሃዲም ነው። አዎ። ያኔም ትህነግ ላይ ስንሰለፍ ይህን እያወቅን ነው። እሱ ከእኛ ጋር ተሰለፈ ካልተባለ ትህነግ የራሱ አካል ነበር። ሲጨንቀው ነው ከሕዝብ ጋር አቋም ያዘ ሊባል የሚችለው። ለመደራደር እየጣረ ሕዝብን እየፈራ ዜና አያስደርጋትም። ለትህነግ ከሕዝብ አገዛዙ ቅርብ ነው። ስለሆነም ትህነግን የሚጠቅመውን በመቃወሙ ሕዝብ ከገዥዎቹ ጋር ሊጠጋጋ አይችልም። ሕዝብ ከትህነግ ሩቅ ነው።
ይህ ማዕቀብ ገዥዎችን ሊጎዳ ይችላል። ይሁንና መከላከያና ልዩ ኃይል እንጅ የመንግስት ባለስልጣን በአምስት ክላሽ የሚጠብቀው ሰራዊት አያጣም። ለአምስት መሳርያ ጥይት አያጣም። ጠባቂ የሚያጣው የወልቃይት፣ የአበርገሌ፣ የራያ፣ የአፋር ሕዝብ ነው። አማራና አፋር ነው። የኢትዮጵያና የኤርትራ ሕዝብ ነው።
በዚህ ሕግ ዙርያ የሚወሩ ጉዳዮች አሉ።
በHR 6600 ሰበብ ለትህነግ እጅ ስጡ ነው እያሉን ነው!
1) ወታደራዊ ጉዳይ ላይ ጠበቅ ብሎ የተሰራበት ነው። ትህነግ መንግስታዊ አይደለም። የመሳርያ እገዳ አልጣሉበትም። ቢችሉ እነሱ ይሰጡታል። በተለያየ መልኩ እንዳደረሱት እናውቃለን። ግብፅና ሱዳን በሱዳን ያለውን ሰራዊቱን እያስታጠቁት ነው። ነገር ግን ስለ ትህነግ በመሳርያ ክልከላ አልተነሳም። መሳርያ እንዳይገዛ የሚከለከለው የኢትዮጵያና የኤርትራ ሰራዊት፣የክልል ፀጥታ ኃይል ነው። የኢትዮጵያ ሰራዊት መሳርያ የሚገዛባቸው አገራት ተጠቅሰዋል። ትህነግ እንደ ሸማቂ በመቆጠሩ ከመደበኛ ሰራዊት ነው መሳርያ ቀምቶ ነው የሚታጠቀው። ከአሁን ቀደምም ከሰራዊቱ ቀምቷል። የቀማው በሌላ ተአምር አይደለም። የውጭ አካላት በመረጃ ወዘተ ደግፈውታል። ሀምሳ ሰው ከዚህ ጋር አለ፣ ከዚህ ደግሞ ይህን ያህል እያሉ በሳተላይት መረጃ ሲመግቡት፣ በኤምባሲ በኩል መረጃ ሲያደርሱት ከርመዋል። የውጭ የእርዳታ ድርጅቶች በብዙ ነገር አግዘውት ከጫካ አውጥተውታል። አሁንም እነዚህ አካላት ናቸው ይህን ሕግ እየደገፉ ያሉት።
የኢትዮጵያ ሰራዊት መሳርያ እንዳይገዛ ሲደረግ ነገ መሳርያም ተተኳሽም ሲያልቅበት የሚጎለብተው ትህነግ ነው። ባለፈው ትህነግን ያሽመደመደው ድሮን ተተኳሽ አይኖርም። ፋኖና ልዩ ኃይል የሚተኩሰው የመትረየስ ጥይት ቢያልቅ እንዳትገዛ ነው የተባልከው። የአፋርና የአማራ ፀጥታ ኃይል ከፊት ሆኖ ከኋላ የከባድ መሳርያ ድጋፍ እንዳያገኝ ነው የተባለው። እቀባው የኢትዮጵያ መንግስትን፣ የኤርትራ መንግስትን፣ የአማራ ክልልንና የአፋር ክልልን ፀጥታ ነው የሚያዳክመው። ትህነግን መሳርያ የሚያደርሰው ሞልቷል። ግን እቀባ ውስጥ እንዲገፋ አልተፈለገም። መሳርያ ኖረውም አልኖረውም አንድ ሚሊዮን ሰው አግተልትሎ ይመጣል። በሁሉም ተጠቃሚ ነው።
2) ማዕቀብ የትግሬ ወራሪ ማዳኛ ነው። ይህን ከአንዴም ሁለቴ አይተነዋል። ባለፈው መጋቢት ጥቃት ከማድረሱ በፊት የአሜሪካ መንግስት ማዕቀብን አጀንዳ አድርጎ ነበር። ይህን ማዕቀብ ፖለቲከኞቹና ወታደራዊ አመራሮቹ ፈርተው ወደፊት ወደኋላ ሲሉ ሰራዊቱን አስመቱት። ወደ ማዕቀብ ፊታቸውን እንዲያዞሩ ተደርገው ሰራዊቱ ማንንም አትንካ ተባለ። የትህነግ ታጣቂዎች ሲቪል መስለው ጭምር አጠቁት። የምዕራባውያኑ አላማ ተሳካ። ለትህነግ አትራፊ ነበር። አሁንም ለሌላ ጥቃት እያዘጋጁን ነው። ሰሞኑን በሱዳን በኩል በተደጋጋሚ ጥቃት ለመፈፀም ሞክሯል። ይህ ህግ ከገፋለት በደንብ ይቀጥላል። እያዘናጉን፣ወደ እነሱ እንድንዞር እያደረጉን ትህነግ ለጥቃት ይዘጋጃል።
3) ይህ አዋጅ የኢትዮጵያና የኤርትራ መንግስትን የአፋርና የአማራ ክልልን ቢጠቁ እንዳይመልሱ የሚያግድ ነው። ትህነግ እንደ ዋነኛ አካል ጠበቅ ያለ ትዕዛዝ አያርፍበትም። ቢተነኩስ እንደ ኢመደበኛ ቡድን ይታያል። ሌሎቹ ምላሽ ቢሰጡ ደግሞ ሕግ ጥሰት ነው። ስለሆነም ጎንደርም፣ ባሕርዳርም፣ ደሴም፣ ደብረብርሃንም፣ አስመራም፣ ሰመራም እንዲደርስ እድል ተመቻችቶለታል። የኢትዮጵያ መንግስት፣ የኤርትራ መንግስት፣ የአማራና አፋር ክልል ለመልሶ ማጥቃት ቢዘጋጁ ከአሁን ቀደም ምዕራባውያኑ ያቀዱትን ያሳካሉ። ሕገወጥ ስለሆነ ሰላም አስከባሪ ይግባ ይባለል።
4) ማዕቀቡ የአስር አመት እድሜ እንዳለው ተጠቅሷል። ይህ ማለት ኢትዮጵያና ኤርትራ ይዳከማሉ። ትህነግ የእርዳታ መንገዱ እንዲከፈትለት የመጀመርያው ቅድመ ሁኔታ ስለሆነ እርዳታውም ሌላውም ይደርሰዋል። ትህነግ አሁን ካለው ይጠናከራል። አገራቱና ክልሎቹ ሲዳከሙ ትህነግ በተራዘመ ጦርነትም ቢሆን የቻለውን ያደርጋል። የ17 አመት ጦርነት የሚጠቅሰው ትህነግ በቅርቡ ትንኮሳ ባያደርግ እንኳን ቀስ ብዬ አገኛቸዋለሁ ብሎ ያስባል። ተጠቃሚ ነው።
5) አበዳሪ ድርጅቶች እርዳታና ብድር እንዳይሰጡ ይከለከላሉ። ይህ ማለት በአማራና አፋር ክልል የወደሙባቸው አካባቢዎች ዩኒቨርሲቲዎችን ጨምሮ የመንግስት ተቋማት ከዓለም ባንክና ከሌሎች አበዳሪና እርዳታ ሰጭ ድርጅቶች እርዳታና ብድር አያገኙም። ፕሮጀክቶች አይኖሩም። የወደሙትን ለማካካስ ከባድ ነው። በአንፃሩ በሰብአዊ እርዳታው እንደ የአሜሪካ ተራድኦ ድርጅትን የመሳሰሉት ቅድሚያውን ወስደው እንዲሰሩ ይደረጋል። የእነ ሳማንታ ፓወር ድርጅት ደግሞ ምን ሲሰራ እንደከረመ የምናውቀው ነው። ለትህነግ የራዲዮ መገናኛም፣ መረጃም፣ ሌላም ሌላም የሚደርሰው በማን እንደነበር እናውቃለን።
6) ምዕራባውያኑ ንፁሃን ወለጋና መተከል ሲገደሉ ምንም አላሉም። በቀደም ኢሰመኮ ያወጣውን ዘግናኝ ወንጀል እንኳን አላወገዙም። በአንፃሩ ትህነግ በሀሰት ሲነግራቸው የከረመውን እውነት አስመስለው ሲዘግቡት ከርመዋል። በተለይ ወልቃይት ጠገዴን ምዕራብ ትግራይ እያሉ የሆነ ያልሆነውን ሲፅፉ ከርመዋል። ትህነግም ትግራይ ውስጥ ዘር ማጥፋት ተፈፅሞብኛል፣ በስሙ ይጠራ ሲል ነው የከረመው። የመጀመርያው "ዘር ማጥፋት" ተብሎ እንዲፈረጅ ይፈልጋል። ይህን ወለጋም መተከልም አያደርጉትም። የሚያደርጉት ትህነግ የሚፈልገው ላይ። ትህነግ ደግሞ ዘር ማጥፋት ተፈፀመ እንዲባል የሚፈልገው በዋነኛነት ወልቃይት ጠገዴ ነው። ከአሁን ቀደም አንቶኒዮ ብሊንከን ዘር ማፅዳት ተፈፅሟል ብሎ በሀሰት ከስሶናል። አሁን ይህን በሌላ ሕግ ማሰር ከዛም ትህነግን በተበዳይ ስም ወደ ወልቃይት ጠገዴ መመለስ ይፈልጋሉ። "ኮሪደር ይሰጣቸው" ሲሉ የከረሙት አላማቸው ይሄ ነው። ያኔ ሕዝባችን ከፍጅት የተከላከሉ ጀግኖቻችን ባንሸልማቸው እንኳን ይፈረጃሉ።
7) ይህን ሕግ እንዲፀድቅ በቀዳሚነት እየጮሁ ያሉት ትህነግና ኦነግ ናቸው። በእነሱ ፍላጎት ከፀደቀ የሚሆነው ግልፅ ነው። ድሮም ትህነግና ኦነግ አሜሪካ ተሰብስበው የሽግግር ወዘተ መንግስት ያቋቁሙ ተብሎ ነበር። አግዘዋቸዋል። ይህ ፍረጃ ፀደቀ ማለት ውጭ ያለ ሰው ለልዩ ኃይል፣ ለመከላከያ፣ ለፋኖ፣ ሚሊሻ ወዘተ እርዳታ ማድረስ አይችልም። የምንደግፋቸው ሳይቀሩ ይወነጀላሉ። ትህነግ ቢወረን፣ መከላከያን ደግፈን፣ ልዩ ኃይልን ደግፈን ወይንም የሚፈፅሙብንን ተቃውመን እንኳን ሰልፍ መውጣት አንችልም። የዘር ማጥፋት ብለው ወንጅለዋል። ለዚህ ውንጀላ ደጋፊ መሆን አይቻልም። ዲያስፖራው ሰልፍ እንኳን ማድረግ ይከለከላል።
አንድ የሚጠቀስ ነገር አለ። አሁን ያለው አገዛዝ አስጠቂ ነው። ዘራፊ ነው። ገዳይም ነው። ከሃዲም ነው። አዎ። ያኔም ትህነግ ላይ ስንሰለፍ ይህን እያወቅን ነው። እሱ ከእኛ ጋር ተሰለፈ ካልተባለ ትህነግ የራሱ አካል ነበር። ሲጨንቀው ነው ከሕዝብ ጋር አቋም ያዘ ሊባል የሚችለው። ለመደራደር እየጣረ ሕዝብን እየፈራ ዜና አያስደርጋትም። ለትህነግ ከሕዝብ አገዛዙ ቅርብ ነው። ስለሆነም ትህነግን የሚጠቅመውን በመቃወሙ ሕዝብ ከገዥዎቹ ጋር ሊጠጋጋ አይችልም። ሕዝብ ከትህነግ ሩቅ ነው።
ይህ ማዕቀብ ገዥዎችን ሊጎዳ ይችላል። ይሁንና መከላከያና ልዩ ኃይል እንጅ የመንግስት ባለስልጣን በአምስት ክላሽ የሚጠብቀው ሰራዊት አያጣም። ለአምስት መሳርያ ጥይት አያጣም። ጠባቂ የሚያጣው የወልቃይት፣ የአበርገሌ፣ የራያ፣ የአፋር ሕዝብ ነው። አማራና አፋር ነው። የኢትዮጵያና የኤርትራ ሕዝብ ነው።
በዚህ ሕግ ዙርያ የሚወሩ ጉዳዮች አሉ።
1) የኢትዮጵያ ሕዝብ ከዚህ በላይ አይጎዳ፣ምን ይመጣበታል የሚል ግድ የለሽ አስተያየት አለ። አሁን ከሚገዛው ላይ አምስት ብር ሲጨመርበት የሚያማርረው ሁሉ ነው ይሄን የሚለው። አንድ ሊትር ዘይት ላይ ውድነት ሲታይ ፌስቡክ ላይ ሲያለቅስ የሚውለው የማዕቀቡ ክብደት ባይታየው ነው። ምን አልባት ነገ ራሱም በበጀት እጥረት ስራ አጥ ይሆናል። አካባቢው ፕሮጀክቱን ያጣል። ያኔ "ወይኔ" ብሎ የሚያመጣው ለውጥ የለም። አስተያየቱ የእልህ ነው።
2) የአማራ ሕዝብን አሁንም እያለቀ ነው። ከእልቂይ ይዳርገዋል የሚሉ አሉ። ይህም ሌላ ስህተት ነው። ትህነግ ሲጠነክር አማራን በየፊናው የሚገድለው ይጠነክራል። ኦነግ ይጠነክራል። የጉሙዝ ታጣቂም ይጠነክራል። አሁን መንገድ ጠብቆ የሚገድለውን መከላከያን ሳይሆን ንፁሃንን ብቻ ነው የሚያገኘው። ትህነግ ተጠናክሮ በራያም፣ በአበርገሌም፣ በወልቃይትም ሲወርር፣ ከመሃልም አጋሮቹን ሲያጠናክር የአማራ ሕዝብ የበለጠ ይጠቃል እንጅ ጥቃቱ ሊቆም አይችልም።
3) ትናንት ሰራዊቱን የደገፉ መንግስት መሳርያ ቢያጣ ጥሩ ነው ይላሉ። ትናንትኮ ልዩ ሀይሉ፣ ሚሊሻው መሳርያ አጣ ሲሉ የነበሩ ናቸው። ትናንት መከላከያው ካልደረሰ፣ ለምን በድሮን አይመታም፣ አፋርና አማራ ላይ ሽፋን አልተሰጠም ሲባል ነበር። ብዙው እውነታ አለው። ትናንት ተጨማሪ መሳርያና ኃይል ሲጠይቁ የነበሩ ዛሬ መሳርያም እንዲታጣ ሰራዊቱም እንዲዳከም ከፈለጉ ችግራቸው የፖለቲካ ወስላታነት ነው። መወላወል ነው።
4) የመከላከያ አመራር፣ የልዩ ኃይል አመራር፣ የፋኖ አመራርን ሲያሞግስ የሚውል፣ ሲፈናቀል ለምን የሚል አክቲቪስት ወዘተ ሰራዊቱን መሳርያ አልባ፣ አቅም አልባ የሚያደርግ፣ እንዳይዋጋ የሚከለክለውን ይደግፋል። ትናንት ሰራዊቱ ለምን አይዋጋም ሲል ኖሮ አሁን ሰራዊቱ ምንም አይነት እርምጃ እንዳይወስድ የሚከለክልን ይደግፋል።
5) አንዳንዱ ይህን የሕልውና ጉዳይ የመንግስት ድጋፍ ያደርገዋል። መንግስትማ ከትህነግ የተሰነጠቀ ነው። ከትህነግ ጋር ለመደራደር እየፈለገ ሕዝብን የሚፈራ ነው። ግን ጳጳሱ ሳይቀር ከትህነግ ጎን ሲሰለፍ፣ የዓለም ጤና ድርጅት ኃላፊ ሳይቀር በየቀኑ ይህ አዋጅ እንዲወጣ ሲሰራ አንተ ግራ ከተጋባህ የረድፍ ችግር አለ። ጳጳሱ እንኳን ትግሬ ተነጥሎ እንዲያልቅ እየተደረገ ነው የሚሉት ዝም ብለው አይደለም። ወይ የራስን ወገን ረድፍ መያዝ አሊያም የትህነግ ምሽግ ሆኖ ወደ ሕዝብ መተኮስ ነው አማራጩ። ምዕራባውያኑ በዚህ ሕግ መሰረት እጃችሁን ለትህነግ ስጡ እያሉ ነው። እጅ መስጠት የሚፈልግ ይሰጣል። መንግስትንም ጨምሮ ለሕልውና ሲል የሚታገል ደግሞ መፅናት አለበት። የወገኑን እጅ ይዤ ካልሰጠሁ የሚለው ደግሞ አሰላለፉን በደንብ መለየት አለበት።
የያዝነው የሕልውና ጉዳይ ነው። ጳጳሱ ትግሬ ይጥፋ እየተባለ ነው ብለው ከትህነግ ጎን ሲሆኑ በአዋጅ ዓለም አቀፍ ጫና ሲመጣ ከሕዝቡ ጎን የማይሆን፣ ገና በገዥዎች ደጋፊነት እከሰሳለፉ ብሎ የሚፈራ የሕልውና ጉዳይን ከልብ ያልወሰደ ነው። ትናንት አብይ መጣ ሲባል ሙሴ መጣ ያለ ፌስቡከኛ አሁንም በአብይ ደጋፊነት በመፈረጅ የሚቀድመው የለም። ወይ ይቃወማል አሊያም ይደግፋል። ይህን ረድፍ መስያዝ የሚችሉ እየሰጉ ከተሸጎጡ አሊያም በስሜትና ግድየለሽነት ከቆሙ ታሪካዊ ኃላፊነት ዘንግተዋል። ዛሬ ተገንጣይ ያሽመደመደው ሕዝብ ነገ መንግስት ላይም ድምፅ ሊኖረው አይችልም።
2) የአማራ ሕዝብን አሁንም እያለቀ ነው። ከእልቂይ ይዳርገዋል የሚሉ አሉ። ይህም ሌላ ስህተት ነው። ትህነግ ሲጠነክር አማራን በየፊናው የሚገድለው ይጠነክራል። ኦነግ ይጠነክራል። የጉሙዝ ታጣቂም ይጠነክራል። አሁን መንገድ ጠብቆ የሚገድለውን መከላከያን ሳይሆን ንፁሃንን ብቻ ነው የሚያገኘው። ትህነግ ተጠናክሮ በራያም፣ በአበርገሌም፣ በወልቃይትም ሲወርር፣ ከመሃልም አጋሮቹን ሲያጠናክር የአማራ ሕዝብ የበለጠ ይጠቃል እንጅ ጥቃቱ ሊቆም አይችልም።
3) ትናንት ሰራዊቱን የደገፉ መንግስት መሳርያ ቢያጣ ጥሩ ነው ይላሉ። ትናንትኮ ልዩ ሀይሉ፣ ሚሊሻው መሳርያ አጣ ሲሉ የነበሩ ናቸው። ትናንት መከላከያው ካልደረሰ፣ ለምን በድሮን አይመታም፣ አፋርና አማራ ላይ ሽፋን አልተሰጠም ሲባል ነበር። ብዙው እውነታ አለው። ትናንት ተጨማሪ መሳርያና ኃይል ሲጠይቁ የነበሩ ዛሬ መሳርያም እንዲታጣ ሰራዊቱም እንዲዳከም ከፈለጉ ችግራቸው የፖለቲካ ወስላታነት ነው። መወላወል ነው።
4) የመከላከያ አመራር፣ የልዩ ኃይል አመራር፣ የፋኖ አመራርን ሲያሞግስ የሚውል፣ ሲፈናቀል ለምን የሚል አክቲቪስት ወዘተ ሰራዊቱን መሳርያ አልባ፣ አቅም አልባ የሚያደርግ፣ እንዳይዋጋ የሚከለክለውን ይደግፋል። ትናንት ሰራዊቱ ለምን አይዋጋም ሲል ኖሮ አሁን ሰራዊቱ ምንም አይነት እርምጃ እንዳይወስድ የሚከለክልን ይደግፋል።
5) አንዳንዱ ይህን የሕልውና ጉዳይ የመንግስት ድጋፍ ያደርገዋል። መንግስትማ ከትህነግ የተሰነጠቀ ነው። ከትህነግ ጋር ለመደራደር እየፈለገ ሕዝብን የሚፈራ ነው። ግን ጳጳሱ ሳይቀር ከትህነግ ጎን ሲሰለፍ፣ የዓለም ጤና ድርጅት ኃላፊ ሳይቀር በየቀኑ ይህ አዋጅ እንዲወጣ ሲሰራ አንተ ግራ ከተጋባህ የረድፍ ችግር አለ። ጳጳሱ እንኳን ትግሬ ተነጥሎ እንዲያልቅ እየተደረገ ነው የሚሉት ዝም ብለው አይደለም። ወይ የራስን ወገን ረድፍ መያዝ አሊያም የትህነግ ምሽግ ሆኖ ወደ ሕዝብ መተኮስ ነው አማራጩ። ምዕራባውያኑ በዚህ ሕግ መሰረት እጃችሁን ለትህነግ ስጡ እያሉ ነው። እጅ መስጠት የሚፈልግ ይሰጣል። መንግስትንም ጨምሮ ለሕልውና ሲል የሚታገል ደግሞ መፅናት አለበት። የወገኑን እጅ ይዤ ካልሰጠሁ የሚለው ደግሞ አሰላለፉን በደንብ መለየት አለበት።
የያዝነው የሕልውና ጉዳይ ነው። ጳጳሱ ትግሬ ይጥፋ እየተባለ ነው ብለው ከትህነግ ጎን ሲሆኑ በአዋጅ ዓለም አቀፍ ጫና ሲመጣ ከሕዝቡ ጎን የማይሆን፣ ገና በገዥዎች ደጋፊነት እከሰሳለፉ ብሎ የሚፈራ የሕልውና ጉዳይን ከልብ ያልወሰደ ነው። ትናንት አብይ መጣ ሲባል ሙሴ መጣ ያለ ፌስቡከኛ አሁንም በአብይ ደጋፊነት በመፈረጅ የሚቀድመው የለም። ወይ ይቃወማል አሊያም ይደግፋል። ይህን ረድፍ መስያዝ የሚችሉ እየሰጉ ከተሸጎጡ አሊያም በስሜትና ግድየለሽነት ከቆሙ ታሪካዊ ኃላፊነት ዘንግተዋል። ዛሬ ተገንጣይ ያሽመደመደው ሕዝብ ነገ መንግስት ላይም ድምፅ ሊኖረው አይችልም።
በሕግ ባለሙያው Andualem Buketo Geda ስለ HR-6600 ረቂቅ ሕግ አስመልክቶ የሚከተለውን ብሏል!
አሜሪካን እና አጋሮቿ የኢትዮጵያን እጅ ለመጠምዘዝ የሚሄዱበት ርቀት ከእለት ወደ እለት አስገራሚ እየሆነ ነው።
አሁን ላይ ደግሞ የኢትዮጵያን ሉኣላዊነት የሚገስ እስከዛሬ ከተሞከሩት በአይነቱም ሆነ በይዘቱ አስከፊ የሆነ HR6600 የሚባል ህግ ለማጽደቅ እየተንቀሳቀሱ ነው።
በዚህ ህግ የአሜሪካን የፋይናንስ ቢሮ እና የውጭ ጉዳይ ቢሮ ለኢትዮጵያ የሚደረጉ ማናቸውም ብድሮች እና እርዳታዎችን (ከአሜሪካ የምናገኘውን ብቻ ሳይሆን ከታላላቆቹ የገንዘብ ተቋማት (እነ ወርልድ ባንክን ማለት ነው) እንዳይሰጠን ቢሮዎቹ ተከታትለው ብሎክ እንዲያደርጉ አደራ ተጥሎባቸዋል!
ይህ እጅግ መረን የወጣ ብልግና ነው!
ረቂቅ ህጉ ከጸደቀ ምናልባት አሜሪካን ሃገር የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ለሃገር ቤት ድሃ ዘመዶቻቸው ድጋፍ ማድረግ መቻላቸው እራሱ አጠራጣሪ ነው!
ኢትዮጵያ የትኛውም አይነት ወረራ ቢያጋጥማት እንደ ረቂቅ ህጉ ከሆነ ከየትኛውም ሃገር የጦር መሳሪያ መግዛት አትችልም!
ይህን ህግ መቃወም ለሁሉም ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ(ባንዳን አይጨምርም) የተገባ ነው!!
በአንጻሩ ይህ ህግ እንዲጸድቅ ማናቸውም አይነት ድጋፍ መስጠት በሞራል ብቻ ሳይሆን በህግም ጭምር ተጠያቂ የሚያደርግ ይመስለኛል!
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የወንጀል ህግ ከአንቀጽ 248 እስከ 251 በጥቅሉ ሲታይ ይህንን በኢትዮጵያ ላይ የተቃጣን አደጋ መደገፍ 'በሃገር ክህደት' እና 'ከጠላት ጋር በመተባበር' የሚያስጠይቅ ከመሆኑም በላይ እንደ ነገሩ ሁኔታ ከ15 አመት ጽኑ እስራት እስከ ሞት ፍርድ ሊያስፈርድ ይችላል!
በዚህ ተግባር ላይ ባለማወቅ የሚሳተፉ ግለሰቦች (ከባንዳ በስተቀር) ምናልባት ይህ ድርጊታቸው በጠቅላይ አቃቤ ህግ አይን እኔ ከላይ ባስቀመጥሁት አግባብ የሚታይ ቢሆን ያላሰቡት መዘዝ የሚያስከትልባቸው መሆኑን ከግምት በማስገባት ሊታቀቡ ይገባል!
በሃገሬ ላይ የሚደረግ ማናቸውንም የእጅ አዙር ቅኝ አገዛዝ ሙከራ አምርሬ እቃወማለሁ!!
አሜሪካን እና አጋሮቿ የኢትዮጵያን እጅ ለመጠምዘዝ የሚሄዱበት ርቀት ከእለት ወደ እለት አስገራሚ እየሆነ ነው።
አሁን ላይ ደግሞ የኢትዮጵያን ሉኣላዊነት የሚገስ እስከዛሬ ከተሞከሩት በአይነቱም ሆነ በይዘቱ አስከፊ የሆነ HR6600 የሚባል ህግ ለማጽደቅ እየተንቀሳቀሱ ነው።
በዚህ ህግ የአሜሪካን የፋይናንስ ቢሮ እና የውጭ ጉዳይ ቢሮ ለኢትዮጵያ የሚደረጉ ማናቸውም ብድሮች እና እርዳታዎችን (ከአሜሪካ የምናገኘውን ብቻ ሳይሆን ከታላላቆቹ የገንዘብ ተቋማት (እነ ወርልድ ባንክን ማለት ነው) እንዳይሰጠን ቢሮዎቹ ተከታትለው ብሎክ እንዲያደርጉ አደራ ተጥሎባቸዋል!
ይህ እጅግ መረን የወጣ ብልግና ነው!
ረቂቅ ህጉ ከጸደቀ ምናልባት አሜሪካን ሃገር የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ለሃገር ቤት ድሃ ዘመዶቻቸው ድጋፍ ማድረግ መቻላቸው እራሱ አጠራጣሪ ነው!
ኢትዮጵያ የትኛውም አይነት ወረራ ቢያጋጥማት እንደ ረቂቅ ህጉ ከሆነ ከየትኛውም ሃገር የጦር መሳሪያ መግዛት አትችልም!
ይህን ህግ መቃወም ለሁሉም ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ(ባንዳን አይጨምርም) የተገባ ነው!!
በአንጻሩ ይህ ህግ እንዲጸድቅ ማናቸውም አይነት ድጋፍ መስጠት በሞራል ብቻ ሳይሆን በህግም ጭምር ተጠያቂ የሚያደርግ ይመስለኛል!
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የወንጀል ህግ ከአንቀጽ 248 እስከ 251 በጥቅሉ ሲታይ ይህንን በኢትዮጵያ ላይ የተቃጣን አደጋ መደገፍ 'በሃገር ክህደት' እና 'ከጠላት ጋር በመተባበር' የሚያስጠይቅ ከመሆኑም በላይ እንደ ነገሩ ሁኔታ ከ15 አመት ጽኑ እስራት እስከ ሞት ፍርድ ሊያስፈርድ ይችላል!
በዚህ ተግባር ላይ ባለማወቅ የሚሳተፉ ግለሰቦች (ከባንዳ በስተቀር) ምናልባት ይህ ድርጊታቸው በጠቅላይ አቃቤ ህግ አይን እኔ ከላይ ባስቀመጥሁት አግባብ የሚታይ ቢሆን ያላሰቡት መዘዝ የሚያስከትልባቸው መሆኑን ከግምት በማስገባት ሊታቀቡ ይገባል!
በሃገሬ ላይ የሚደረግ ማናቸውንም የእጅ አዙር ቅኝ አገዛዝ ሙከራ አምርሬ እቃወማለሁ!!