የዶ/ር አብይ አህመድ አስተዳደር ከወያኔ ጋር አንዴ በኬንያ ሌላ ጊዜ በናይጀሪያ ለምን ይደራደራል? ብለው እሪታ የሚያሰሙ ሰዎች ያስደንቁኛል። ያሳዝኑኛልም። በመንግስት እና በወያኔ መካከል ድርድር እየተደረገ ቢሆንም ባይሆንም ጦርነት መጨረሻው ወይም መቋጫው ድርድር መሆኑ የታወቀ ነው።
በሩሲያና በዩክሬን እየተካሄደ ባለው ጦርነት ስለድርድር በየጊዜው ይነሳል። ባይስማሙም ለመደራደር ተገናኝተዋል። ቅድመ ሁኔታዎች መደራደሪያዎች ሊለያዩ ይችላሉ እንጅ ድርድር የጦርነቱ መልክ መቀየሪያ ነው።
በኢትዮጵያ መንግስትና በአማፂው ወያኔ መካከል አሁን ላይ ድርድር እየተደረገ ሊሆንም ላይሆንም ይችላል። ስለድርድሩ በቂ መረጃ ያላቸው እየተደራደሩ ነው የተባሉት አካላት ናቸው።
መንግስት እንዴት ከወያኔ ጋር ይደራደራል ብለው ጩኸቱን የሚያቀልጡት አንዴ የሰላም ሰባኪ ሌላ ጊዜ ጦርነቱ አይመለከተንም ባይ ሰዎች ግን ስለድርድሩ ከፊት ቀድመው ወሳኝ ለመሆን የሚያደርጉት መፍጨርጨር አስገራሚ ነው።
ድርድር ሊኖር አይገባም የሚሉ ሰዎች ከዚህ በፊት "ጦርነቱ እኛን አይመለከተንም" ያሉ ናቸው። በቅርቡም ሕዝባችንን ለማዘናጋት #No More War ሲሉ የነበሩ ሰዎችም ናቸው። ታዲያ ጦርነት አያስፈልግም ሲሉ የነበሩት ጦርነቱን እንዴት እንዲቆም ፈልጎ እንደሆነ እነሱ ናቸው ሚስጢሩን የሚያውቁት።
ከፍየሏ በላይ የሆነው ጩኸት መንግስት ከወያኔ ጋር በሚያደርገው ድርድር ወልቃይት ለወያኔ ተላልፎ ሊሰጥ ነው የሚለው የአዛኝ መሳኝ ቅቤ አንጓችነት ጉዳይ ነው።
ዶ/ር አብይ አህመድ ስልጣኑ አይነካበት እንጅ የሕዝብ ጥያቄ ጉዳዩ ስላልሆነ ወልቃይትን ለወያኔ አሳልፎ ለመስጠትም ወስኗል ሲሉም ይደመጣሉ። የወልቃይት ጉዳይ ያሳስበኛል የሚሉ ሰዎች በበሬ ወለደ ወሬ ለምን በቀላሉ እንደሚደናገጡ እየገባኝ አይደለም። በድርድሩ ወልቃይት ለወያኔ ተላልፎ ሊሰጥ ስለመሆኑና በተክደሃል በለቅሶ ፖለቲካ ሕዝብን ለማደናገር የሚሞክሩ አካላት ወልቃይት በወያኔ እጅ እንዲገባ የሚፈልጉ ብቻ ሳይሆኑ እንዲሆን ሲሰሩ የቆዩ መሆናቸው ታውቆ ያደረ ነው።
ዶ/ር አብይ አህመድ በንግግር ደረጃ ወልቃይት የቤጌምድር መሆኑን በተለያዩ መድረኮች ባረጋገጠበት ሁኔታ(የጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግር ፊርማ ነው)፤በአማራ ክልል መንግስት ስር ወልቃይት እየተዳደረ ባለበት ሁኔታ አብይ ወልቃይትን ለወያኔ አሳልፎ ሊሰጥ ስለሆነ አማራ ከመካድህ በፊት ተነስ የሚሉ አዛኝ መሳይ ቅቤ አንጓቾች በዚህ ደረጃ አዳማጭ ማግኘታቸው የሚያስደንቅ የሚያሳስብም ነው።
ዶ/ር አብይ አህመድ ወልቃይትን በተመለከተ ከዚህ በላይ ምን እንዲያደርግ ወይም እንዲናገር ነው የተፈለገው? እጅግ በጣም የሚያሳፍረኝ የወያኔያዊ የአማራ ብሔርተኛ የፕሮፖጋንዳ ሰለባ የሆነው የወልቃይት ጉዳይ ያሳስበኛል የሚለው አካል ተደናብሮ ሌሎችን ለማደናበር የጠላትን አጀንዳ ተሸክሞ የሚያዘጠዝጠው ጉዳይም ነው።
ወያኔያዊው የአማራ ብሔርተኞች ወልቃይትን በተመለከተ ከአብይ አህመድ ይልቅ ኢሳያስን አምነን ወዳጅ ብናደርገው የተሻለ ስለመሆኑም በተለያየ መንገድ በአደባባይ በሶሻል ሚዲያው ሲናገሩ ይሰማሉ። አማራና ኤርትራ ወዳጅ ናቸው ወይም እንወዳጅ እየተባለ በሶሻል ሚዲያው በተለያየ መንገድ የሚራገበው አጀንዳ ከአማራ ለአማራ ሕዝብ ጥቅም ታሰቦ የሚሰራ ጉዳይ አይደለም። የኦሮሞ ወይም የሌሎች ብሔር ልሒቃንን መሬት ላይ በሌለ እንቅስቃሴ አማራው ከማዕከላዊ መንግስቱ የሚያፈነግጥ አስመስሎ ስጋት ለመፍጠር፣ በዋናነት በወልቃይት ጉዳይ የኦሮሞ ልሒቃንም ሆኑ የሌሎች ብሔር ልሒቃን ከአማራ ጎን በመቆም አቋም እንዳይዙ ለማድረግ ያለመም ነው።
በነገራችን ላይ በወልቃይት ጉዳይ ችግር ቢፈጠር የአማራ ክልል መንግስትና በብልፅግና ውስጥ ያሉ በስራቸው የተገፉና ያኮረፉ የተጠያቂነት ስጋት ያለባቸው አመራሮች ናቸው ተጠያቂ ሊሆኑ የሚችሉት። ሕዝቡን ለማታገያነት ለመጠቀም በማሰብ የወልቃይት ጉዳይን ከሚዲያ ዘመቻ እስከ መሬት የወረደ የማወሳሰብና አሳልፎ የመስጠት ስራ እየሰራ የሚገኘው አካል የማይታወቅ የተሰወረ አይደለም።
እራሳቸውን የወልቃይት ጉዳይ ዋና ተቆርቋሪ አድርገው የተደበቀ ፍላጎታቸውን ለማስፈጸም የሚዳክሩት ሰዎች ከሳምንት በፊት"ጦርነቱ የሰሊጥ ብሄረተኞች ጦርነት ነው፤ እኛን አይመለከተንም። " ሲሉን የነበሩ መሆናቸው ግልጽም ነው።
በሩሲያና በዩክሬን እየተካሄደ ባለው ጦርነት ስለድርድር በየጊዜው ይነሳል። ባይስማሙም ለመደራደር ተገናኝተዋል። ቅድመ ሁኔታዎች መደራደሪያዎች ሊለያዩ ይችላሉ እንጅ ድርድር የጦርነቱ መልክ መቀየሪያ ነው።
በኢትዮጵያ መንግስትና በአማፂው ወያኔ መካከል አሁን ላይ ድርድር እየተደረገ ሊሆንም ላይሆንም ይችላል። ስለድርድሩ በቂ መረጃ ያላቸው እየተደራደሩ ነው የተባሉት አካላት ናቸው።
መንግስት እንዴት ከወያኔ ጋር ይደራደራል ብለው ጩኸቱን የሚያቀልጡት አንዴ የሰላም ሰባኪ ሌላ ጊዜ ጦርነቱ አይመለከተንም ባይ ሰዎች ግን ስለድርድሩ ከፊት ቀድመው ወሳኝ ለመሆን የሚያደርጉት መፍጨርጨር አስገራሚ ነው።
ድርድር ሊኖር አይገባም የሚሉ ሰዎች ከዚህ በፊት "ጦርነቱ እኛን አይመለከተንም" ያሉ ናቸው። በቅርቡም ሕዝባችንን ለማዘናጋት #No More War ሲሉ የነበሩ ሰዎችም ናቸው። ታዲያ ጦርነት አያስፈልግም ሲሉ የነበሩት ጦርነቱን እንዴት እንዲቆም ፈልጎ እንደሆነ እነሱ ናቸው ሚስጢሩን የሚያውቁት።
ከፍየሏ በላይ የሆነው ጩኸት መንግስት ከወያኔ ጋር በሚያደርገው ድርድር ወልቃይት ለወያኔ ተላልፎ ሊሰጥ ነው የሚለው የአዛኝ መሳኝ ቅቤ አንጓችነት ጉዳይ ነው።
ዶ/ር አብይ አህመድ ስልጣኑ አይነካበት እንጅ የሕዝብ ጥያቄ ጉዳዩ ስላልሆነ ወልቃይትን ለወያኔ አሳልፎ ለመስጠትም ወስኗል ሲሉም ይደመጣሉ። የወልቃይት ጉዳይ ያሳስበኛል የሚሉ ሰዎች በበሬ ወለደ ወሬ ለምን በቀላሉ እንደሚደናገጡ እየገባኝ አይደለም። በድርድሩ ወልቃይት ለወያኔ ተላልፎ ሊሰጥ ስለመሆኑና በተክደሃል በለቅሶ ፖለቲካ ሕዝብን ለማደናገር የሚሞክሩ አካላት ወልቃይት በወያኔ እጅ እንዲገባ የሚፈልጉ ብቻ ሳይሆኑ እንዲሆን ሲሰሩ የቆዩ መሆናቸው ታውቆ ያደረ ነው።
ዶ/ር አብይ አህመድ በንግግር ደረጃ ወልቃይት የቤጌምድር መሆኑን በተለያዩ መድረኮች ባረጋገጠበት ሁኔታ(የጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግር ፊርማ ነው)፤በአማራ ክልል መንግስት ስር ወልቃይት እየተዳደረ ባለበት ሁኔታ አብይ ወልቃይትን ለወያኔ አሳልፎ ሊሰጥ ስለሆነ አማራ ከመካድህ በፊት ተነስ የሚሉ አዛኝ መሳይ ቅቤ አንጓቾች በዚህ ደረጃ አዳማጭ ማግኘታቸው የሚያስደንቅ የሚያሳስብም ነው።
ዶ/ር አብይ አህመድ ወልቃይትን በተመለከተ ከዚህ በላይ ምን እንዲያደርግ ወይም እንዲናገር ነው የተፈለገው? እጅግ በጣም የሚያሳፍረኝ የወያኔያዊ የአማራ ብሔርተኛ የፕሮፖጋንዳ ሰለባ የሆነው የወልቃይት ጉዳይ ያሳስበኛል የሚለው አካል ተደናብሮ ሌሎችን ለማደናበር የጠላትን አጀንዳ ተሸክሞ የሚያዘጠዝጠው ጉዳይም ነው።
ወያኔያዊው የአማራ ብሔርተኞች ወልቃይትን በተመለከተ ከአብይ አህመድ ይልቅ ኢሳያስን አምነን ወዳጅ ብናደርገው የተሻለ ስለመሆኑም በተለያየ መንገድ በአደባባይ በሶሻል ሚዲያው ሲናገሩ ይሰማሉ። አማራና ኤርትራ ወዳጅ ናቸው ወይም እንወዳጅ እየተባለ በሶሻል ሚዲያው በተለያየ መንገድ የሚራገበው አጀንዳ ከአማራ ለአማራ ሕዝብ ጥቅም ታሰቦ የሚሰራ ጉዳይ አይደለም። የኦሮሞ ወይም የሌሎች ብሔር ልሒቃንን መሬት ላይ በሌለ እንቅስቃሴ አማራው ከማዕከላዊ መንግስቱ የሚያፈነግጥ አስመስሎ ስጋት ለመፍጠር፣ በዋናነት በወልቃይት ጉዳይ የኦሮሞ ልሒቃንም ሆኑ የሌሎች ብሔር ልሒቃን ከአማራ ጎን በመቆም አቋም እንዳይዙ ለማድረግ ያለመም ነው።
በነገራችን ላይ በወልቃይት ጉዳይ ችግር ቢፈጠር የአማራ ክልል መንግስትና በብልፅግና ውስጥ ያሉ በስራቸው የተገፉና ያኮረፉ የተጠያቂነት ስጋት ያለባቸው አመራሮች ናቸው ተጠያቂ ሊሆኑ የሚችሉት። ሕዝቡን ለማታገያነት ለመጠቀም በማሰብ የወልቃይት ጉዳይን ከሚዲያ ዘመቻ እስከ መሬት የወረደ የማወሳሰብና አሳልፎ የመስጠት ስራ እየሰራ የሚገኘው አካል የማይታወቅ የተሰወረ አይደለም።
እራሳቸውን የወልቃይት ጉዳይ ዋና ተቆርቋሪ አድርገው የተደበቀ ፍላጎታቸውን ለማስፈጸም የሚዳክሩት ሰዎች ከሳምንት በፊት"ጦርነቱ የሰሊጥ ብሄረተኞች ጦርነት ነው፤ እኛን አይመለከተንም። " ሲሉን የነበሩ መሆናቸው ግልጽም ነው።
ወልቃይት መሬት ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያን ሕልውና ሊወስን የሚችልና በቀጠናው ላይ ትልቅ ተፅዕኖ መፍጠር የሚችል ስትራቴጂክ ኮሪደር ነው። የግብፅንና የሱዳንን ሁኔታ የውስጥ ባንዳዎችን አገር የማፍረስ የተላላኪነት ያልተቋረጠ እንቅስቃሴ የሚከታተል ሰው፣ መንግስት ወልቃይትን ለወያኔ አሳልፎ ሊሰጥ እንደሚችል በአደባባይ ቢናገር እንኳን መጠራጠር ይኖርበታል። ወልቃይት የጎንደር አማራ መሬትና ግዛት ስለሆነ ብቻ ሳይሆን ወልቃይት በወያኔ እጅ በገባ ማግስት ሊፈጠር የሚችለውን ነገር ማሰብ አይከብድም። ወያኔ በግጭት ተወልዶ በግጭት ያደገ ያለግጭት ሕልውና የሌለውና መቼም ቢሆን የሚታመን ሐይል አይደለም።
ወልቃይትን መንግስት በስሩ የሚያደርገው ለማንም ብሎ ሳይሆን ለራሱ ሕልውና ለአገረ-መንግስቱ መቀጠልና መፅናት ሲል ነው። የኢትዮጵያን መበልፀግ የሚሻ መንግስት የኢትዮጵያን ሕልውና አደጋ የሚጥል ስራ ፈፅሞ ሊሰራ አይችልም። ይህን አለመረዳት ችግሩ የማንም ሳይሆን የራስ ነው። በወያኔ ፕሮፖጋንዳ አዕምሮን የማጣት ምልክት ነው። ከዛ ካለፈ ደግሞ ከወያኔ እንደ አንዱ መሆንን የሚያረጋግጥ ነው።
በሌላ በኩል ወያኔያዊ የፌስቡክ የአማራ ብሔርተኛ በመንግሥት መከዳት ስለወልቃይት የሚናገረውና የሚፅፈው የቢሆን ፍላጎቱን ነው። በጓዳ እንዲሆን የሚመኘውንና ከውጭ ባዕዳን ጭምር ተቀናጅቶ መሬት ለማስነካት የሚሰራውን ጉዳይም ነው በፊት ለፊት በስመ አዛኝ ተቆርቋሪነት የጥርጣሬና ሐሰተኛ መረጃ በማሰራጨት ግርግርና ሁከት ለመፍጠር የሚሰራው።
ሕልማችሁ ከቀን ቅዥት የማያልፍና መቼም ሊሳካ የማይችል ነው‼️
ወልቃይትን መንግስት በስሩ የሚያደርገው ለማንም ብሎ ሳይሆን ለራሱ ሕልውና ለአገረ-መንግስቱ መቀጠልና መፅናት ሲል ነው። የኢትዮጵያን መበልፀግ የሚሻ መንግስት የኢትዮጵያን ሕልውና አደጋ የሚጥል ስራ ፈፅሞ ሊሰራ አይችልም። ይህን አለመረዳት ችግሩ የማንም ሳይሆን የራስ ነው። በወያኔ ፕሮፖጋንዳ አዕምሮን የማጣት ምልክት ነው። ከዛ ካለፈ ደግሞ ከወያኔ እንደ አንዱ መሆንን የሚያረጋግጥ ነው።
በሌላ በኩል ወያኔያዊ የፌስቡክ የአማራ ብሔርተኛ በመንግሥት መከዳት ስለወልቃይት የሚናገረውና የሚፅፈው የቢሆን ፍላጎቱን ነው። በጓዳ እንዲሆን የሚመኘውንና ከውጭ ባዕዳን ጭምር ተቀናጅቶ መሬት ለማስነካት የሚሰራውን ጉዳይም ነው በፊት ለፊት በስመ አዛኝ ተቆርቋሪነት የጥርጣሬና ሐሰተኛ መረጃ በማሰራጨት ግርግርና ሁከት ለመፍጠር የሚሰራው።
ሕልማችሁ ከቀን ቅዥት የማያልፍና መቼም ሊሳካ የማይችል ነው‼️
ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር‼️
ዶ/ር አብይ አህመድ በተለያዩ መድረኮች ወልቃይት የበጌምድር አማራ መሆኑን በማያሻማ መንገድ በጠራ አገላለፅ ባረጋገጠበት መንገድ(የጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግር ፊርማ ነው)፤ ወልቃይት በአማራ ክልል መንግስት ስር እየተዳደረ ባለበት ሁኔታ፤ ወልቃይትን አብይ አህመድ ለወያኔ አሳልፎ ሊሰጥ ስለሆነ አማራ ከመከዳትህ በፊት ተነስ የሚሉ የግጭት ነጋዴዎች ድምፅ ማሰማት ሳይሆን ለእነሱ ጆሮ የሚሰጠው ሰው ቁጥር በዚህ ደረጃ መጠኑ መጨመሩ የሚያስደንቅና የሚያሳስብም ነው። እርግጥ ነው ጉዳዩ የማንም ሳይሆን የራሱ የመንግስት የ PR ችግር የፈጠረው ነው።
ዶ/ር አብይ አህመድ ለአማራ እንቆረቆራለን ወይም እንታገላለን ከሚሉት በላይ በወልቃይት ጉዳይ የሕዝቡን የዓመታት ጥያቄና ትግል እውቅና ሰጥቶ ወልቃይት የበጌምድር አማራ መሆኑን የጠራ አቋሙን በአደባባይ አረጋግጦ ለሕዝቡ ጥያቄ የራቀ ሳይሆን መቅረቡን ያስመሰከረበትን ጉዳይ ጠላት ወያኔ ግን ወልቃይት እንዳይመለስ ወይም ለወያኔ ተላልፎ እንዲሰጥ አብይ እየሰራ እንደሆነ አድርጎ መንጋ የሚያደናግርበት ወይም በመንጋ እንዲከሰስ ዕድል የፈጠረበት ሁኔታ የጠላትን ጥንካሬ ሳይሆን የራሱ የመንግስት የመረጃ አሰጣጥ የሕዝብ ግንኙነት ድክመትን የሚያሳይ ነው።
የመላው አማራ ሕዝብ ከዳር እስከ ዳር በነቂስ ወጥቶ ወልቃይትን ብሎ ብዙ መከራና ግፍን የተቀበለበትን ጥያቄና ትግል ከሆነው አንዱ የወልቃይት ጉዳይ በዚህ ሰዓት በእጁ መዳፍ ይገኛል።
ስለወልቃይት በሕግ የቀሪውን ጉዳይ የማረጋገጥ ስራ በአማራ ክልል መንግስት እና የአማራ ኤሊት ነኝ በሚለው አካል ትክሻ ላይ የሚወድቅ ይሆናል። አብይ አህመድ እስካሁን ከተናገረው ወይም ካደረገው በላይ በዚህ ዙሪያ የሚጠበቅበት ግዴታ እንዳለበት በበኩሌ በፍፁም አይሰማኝም። ወልቃይት የበጌምድር አማራ ነው ከማለት በላይና በአማራ ክልል መንግስት ስር እንዲተዳደር ከማድረግ፣ ለቀጣይ ሂደቱን ነገሮችን ከማመቻቸት ያለፈ ከእሱ የሚጠበቅበት ነገር የለም። ከዛ ውጭ አብይ አህመድ መንደር ለመንደር ወይም ከክልል ክልል እየዞረ የወልቃይትን ጉዳይ ወረቀት ይዞ ሊያስፈፀም አይችልም። ፖስተኛም አይደለም።
ማንም እጅና እግሩን አጣጥፎ ተጎልቶ ጊዜውን የሚቆጥር አብይ አህመድ ሁሉንም ነገር ፈትፍቶ እንዲያጎርሰው የሚፈልግ የጠባቂነት መንፈስ የተጠናወተው ሁሉ እጁ ላይ የገባውን ወልቃይትን ሊነጥቁኝ ነው ወይም ተላልፎ ሊሰጥብኝ እያለ ሲነፋረቅ ቢታይ ድክመቱን ከማሳየት ነውሩን ከመግለጥ ያለፈ ትርጉም ያለው ነገር ማሳየት አይችልም።
እርግጥ ነው በሰሜን ሕብረት በስመ የአቢሲኒያ አሻራን የደቡቡ ሐይል ሊንደውና ሊያ*ጠፋው ነው በሚል የወያኔ አጀንዳን በማራገብ ከወያኔ ጋር አብረን ከቆምን ባርጌኒግ ፓወራችን ይጨምራል አብይ አህመድንም ከስልጣኑ ማስወ*ገድ ይቻላል እያለ የሚንቀሳቀስ አካል መልሶ በመሃል የወልቃይት ጉዳይን አስመልክቶ በተቆርቋሪነት ለመንቀሳቀስ ሲሞክር መታየቱ ተጠባቂ እንጅ አዲስ ነገር አይሆንም። በዚህ ማዕቀፍ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ጥላቻ የወለዳቸው በስሜት ፈረስ የሚጋልቡ የወያኔ የማደጎ ልጆች ለአላማቸው መሳካት እንደፈለጉ ሲገለባበጡ ሚግ 23 የሚያስንቁ ናቸው። በቀጣይ በየት በኩል ተገልብጠው ሊከሰቱ እንደሚችሉ መገመትም አይቻልም።
እነዚህ አካላት ዶ/ር አብይ አህመድን እንደ አንድ የሕወሓት ስራ አስፈፃሚ እኩል ነጥለው እያብጠለጠሉ ከስልጣኑ እናስ*ወግደዋለን ብለው እየተንቀሳቀሱ መልሰው የአማራ ጥያቄ እየተመለሰ አይደለም ሲሉ፤ወልቃይት በአብይ አህመድ ተላልፎ ሊሰጥ ነው የሚል ጩኸትም ሲያሰሙ መመልከት የሚያረጋግጥልን ጉዳይ የሞራል ቫልዩና መርህ አልባ መሆናቸውን ነው።
በመጨረሻም‼️
ለአማራ ሕዝብ እንቆረቆራለን የምንል ሰዎች ቅድሚያ እራሳችንን እንመልከት። ከዛም ከራሳችን ጋር ሆነን የራሳችንን አጀንዳ ቀርፀን ለአማራ ሕዝብ ሁለንተናዊ ጥቅም መረጋገጥ ደፋ ቀና ለማለት ሙከራ እናድርግ። አለበለዚያ በተመለደው በጠላት አጀንዳ በስማ በለው ስንወራጭ፣ አካኪ ዘራፍ እያልን ስንፏልል፣ ውለን ብናነጋ በውጤቱ ከአንዱም ሳንሆን እንደዳከርንና አረፋችንን እንደደፈቅን አወዳደቃችንን አበላሽተን ከመውደቅ ከፍ ያለ ድል ልንነሳው የምንችለው ጠላት አይኖረንም። ከጅምሩ የተከተልነው መስመር በእኛ የተነደፈ ወይም በእኛ የቀየሰ መንገድ አይደለምና። ስለሆነም የጠላት አጀንዳን ተሸክመን በጠላት መንገድ እየተመላለስን ጠላትን ለማሸነፍ ማሰብ የሞኝነታችንን ጥግና የአወዳደቃችንን ሁኔታ ከማሳየት ያለፈ አሸናፊነታችን አያረጋግጥም።
ዶ/ር አብይ አህመድ በተለያዩ መድረኮች ወልቃይት የበጌምድር አማራ መሆኑን በማያሻማ መንገድ በጠራ አገላለፅ ባረጋገጠበት መንገድ(የጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግር ፊርማ ነው)፤ ወልቃይት በአማራ ክልል መንግስት ስር እየተዳደረ ባለበት ሁኔታ፤ ወልቃይትን አብይ አህመድ ለወያኔ አሳልፎ ሊሰጥ ስለሆነ አማራ ከመከዳትህ በፊት ተነስ የሚሉ የግጭት ነጋዴዎች ድምፅ ማሰማት ሳይሆን ለእነሱ ጆሮ የሚሰጠው ሰው ቁጥር በዚህ ደረጃ መጠኑ መጨመሩ የሚያስደንቅና የሚያሳስብም ነው። እርግጥ ነው ጉዳዩ የማንም ሳይሆን የራሱ የመንግስት የ PR ችግር የፈጠረው ነው።
ዶ/ር አብይ አህመድ ለአማራ እንቆረቆራለን ወይም እንታገላለን ከሚሉት በላይ በወልቃይት ጉዳይ የሕዝቡን የዓመታት ጥያቄና ትግል እውቅና ሰጥቶ ወልቃይት የበጌምድር አማራ መሆኑን የጠራ አቋሙን በአደባባይ አረጋግጦ ለሕዝቡ ጥያቄ የራቀ ሳይሆን መቅረቡን ያስመሰከረበትን ጉዳይ ጠላት ወያኔ ግን ወልቃይት እንዳይመለስ ወይም ለወያኔ ተላልፎ እንዲሰጥ አብይ እየሰራ እንደሆነ አድርጎ መንጋ የሚያደናግርበት ወይም በመንጋ እንዲከሰስ ዕድል የፈጠረበት ሁኔታ የጠላትን ጥንካሬ ሳይሆን የራሱ የመንግስት የመረጃ አሰጣጥ የሕዝብ ግንኙነት ድክመትን የሚያሳይ ነው።
የመላው አማራ ሕዝብ ከዳር እስከ ዳር በነቂስ ወጥቶ ወልቃይትን ብሎ ብዙ መከራና ግፍን የተቀበለበትን ጥያቄና ትግል ከሆነው አንዱ የወልቃይት ጉዳይ በዚህ ሰዓት በእጁ መዳፍ ይገኛል።
ስለወልቃይት በሕግ የቀሪውን ጉዳይ የማረጋገጥ ስራ በአማራ ክልል መንግስት እና የአማራ ኤሊት ነኝ በሚለው አካል ትክሻ ላይ የሚወድቅ ይሆናል። አብይ አህመድ እስካሁን ከተናገረው ወይም ካደረገው በላይ በዚህ ዙሪያ የሚጠበቅበት ግዴታ እንዳለበት በበኩሌ በፍፁም አይሰማኝም። ወልቃይት የበጌምድር አማራ ነው ከማለት በላይና በአማራ ክልል መንግስት ስር እንዲተዳደር ከማድረግ፣ ለቀጣይ ሂደቱን ነገሮችን ከማመቻቸት ያለፈ ከእሱ የሚጠበቅበት ነገር የለም። ከዛ ውጭ አብይ አህመድ መንደር ለመንደር ወይም ከክልል ክልል እየዞረ የወልቃይትን ጉዳይ ወረቀት ይዞ ሊያስፈፀም አይችልም። ፖስተኛም አይደለም።
ማንም እጅና እግሩን አጣጥፎ ተጎልቶ ጊዜውን የሚቆጥር አብይ አህመድ ሁሉንም ነገር ፈትፍቶ እንዲያጎርሰው የሚፈልግ የጠባቂነት መንፈስ የተጠናወተው ሁሉ እጁ ላይ የገባውን ወልቃይትን ሊነጥቁኝ ነው ወይም ተላልፎ ሊሰጥብኝ እያለ ሲነፋረቅ ቢታይ ድክመቱን ከማሳየት ነውሩን ከመግለጥ ያለፈ ትርጉም ያለው ነገር ማሳየት አይችልም።
እርግጥ ነው በሰሜን ሕብረት በስመ የአቢሲኒያ አሻራን የደቡቡ ሐይል ሊንደውና ሊያ*ጠፋው ነው በሚል የወያኔ አጀንዳን በማራገብ ከወያኔ ጋር አብረን ከቆምን ባርጌኒግ ፓወራችን ይጨምራል አብይ አህመድንም ከስልጣኑ ማስወ*ገድ ይቻላል እያለ የሚንቀሳቀስ አካል መልሶ በመሃል የወልቃይት ጉዳይን አስመልክቶ በተቆርቋሪነት ለመንቀሳቀስ ሲሞክር መታየቱ ተጠባቂ እንጅ አዲስ ነገር አይሆንም። በዚህ ማዕቀፍ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ጥላቻ የወለዳቸው በስሜት ፈረስ የሚጋልቡ የወያኔ የማደጎ ልጆች ለአላማቸው መሳካት እንደፈለጉ ሲገለባበጡ ሚግ 23 የሚያስንቁ ናቸው። በቀጣይ በየት በኩል ተገልብጠው ሊከሰቱ እንደሚችሉ መገመትም አይቻልም።
እነዚህ አካላት ዶ/ር አብይ አህመድን እንደ አንድ የሕወሓት ስራ አስፈፃሚ እኩል ነጥለው እያብጠለጠሉ ከስልጣኑ እናስ*ወግደዋለን ብለው እየተንቀሳቀሱ መልሰው የአማራ ጥያቄ እየተመለሰ አይደለም ሲሉ፤ወልቃይት በአብይ አህመድ ተላልፎ ሊሰጥ ነው የሚል ጩኸትም ሲያሰሙ መመልከት የሚያረጋግጥልን ጉዳይ የሞራል ቫልዩና መርህ አልባ መሆናቸውን ነው።
በመጨረሻም‼️
ለአማራ ሕዝብ እንቆረቆራለን የምንል ሰዎች ቅድሚያ እራሳችንን እንመልከት። ከዛም ከራሳችን ጋር ሆነን የራሳችንን አጀንዳ ቀርፀን ለአማራ ሕዝብ ሁለንተናዊ ጥቅም መረጋገጥ ደፋ ቀና ለማለት ሙከራ እናድርግ። አለበለዚያ በተመለደው በጠላት አጀንዳ በስማ በለው ስንወራጭ፣ አካኪ ዘራፍ እያልን ስንፏልል፣ ውለን ብናነጋ በውጤቱ ከአንዱም ሳንሆን እንደዳከርንና አረፋችንን እንደደፈቅን አወዳደቃችንን አበላሽተን ከመውደቅ ከፍ ያለ ድል ልንነሳው የምንችለው ጠላት አይኖረንም። ከጅምሩ የተከተልነው መስመር በእኛ የተነደፈ ወይም በእኛ የቀየሰ መንገድ አይደለምና። ስለሆነም የጠላት አጀንዳን ተሸክመን በጠላት መንገድ እየተመላለስን ጠላትን ለማሸነፍ ማሰብ የሞኝነታችንን ጥግና የአወዳደቃችንን ሁኔታ ከማሳየት ያለፈ አሸናፊነታችን አያረጋግጥም።
ከጃዋር መሀመድ ምን እንማር?‼️
አገር፣ መንግስት፣ ፓርቲ ሶስቱ የተለያዩ ነገሮች መሆናቸውን ነጣጥሎ አለመመልከትና አለመታገል አላስፈላጊ መስዋዕትነትን ያስከፍላል።
የአንድን ፓርቲ ፕሮግራም መቃወም መንቀፍ መብት ነው። ተቃዋሚ ነኝ ከሚል አካልም የሚጠበቅ ነው። በመንግስት ላይ ተቃውሞ ማሰማት አልፎም ምን አይነት መንግስት ይኑረን? ወይም ይሁን በሚለው ዙሪያም ? የተለያዩ ሐሳቦችን ማንሸራሸር መከራከር ችግር አይደለም። ችግሩ አገረ-መንግስቱን ለማፍረስ ሽፋን አድርጎ መንቀሳቀስ ነው። በስመ ሐሳብን በነፃነት በመግለፅ መብት (Freedom of Expressions) አገር ለማፍረስ እስከመንቀሳቀስ የሚፈቅድ አይደለም። የማንንም ሰባዊ ክብር ስብዕናን እስከመንካት እንኳን የሚያደርስ መብት የለውም። መፃፍ ወይም መናገር ስለተቻለ ብቻ የሰዎችን ስብዕና ክብር መንካት አገር ለማፍረስ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መሳተፍ ወይም መተባበር እንደ ዲሞክራሲ ማሳያዎች የሚታዩ ስላልሆኑ ተጠያቂ ያደርጋሉ። ሐሳብን በነፃነት መግለፅ የሐሳብ አማራጮችን ሐእንጅ የስድብ አማራጮችን የሚያበረታታ አይደለም። አንድ ሰው በሐገር ክህደት ወንጀል ሊያስጠይቀው በሚችል ጉዳይ ጭምር እየተሳተፈ ወይም እየተባበረ ትጠየቃለህ ሲባል እንደመብት ለመቁጠር መሞከር ግሩም ያሰኛል። በዚህ አራት አመት በኢትዮጵያ በተለይ በአማራ ፖለቲካ በስመ ሐሳብን በነፃነት ስም አሳዳጊ የበደላቸው አግድም አደጎችን እንዲነግሱ አድርጓል። ከመዛዛት ያለፈ መገዳ*ደልም ፈጥሯል። በሂደት የሰዎችን ስብዕና መንካት አገር ለማፍረስ መንቀሳቀስ እንደመብት እንዲቆጠር አድርጓልም።
በኢትዮጵያ ሰማይ ስር በውሳጣዊና ውጫዊ ጫናዎችና ውጥረቶች ያልተዳከመ መንግስት ቢኖር ኖሮ በሐገር ክህደት ወንጀል ሊጠየቅ የሚችለው አካል ቁጥር እልፍ ነው።
መንግስት ሕግ የማስከበር የዜጎችን ሰላምና ደህንነት የመጠበቅ ተቀዳሚ ስራው ሆኖ ሳለ አለም ላይ የሌለ ለዲሞክራሲ ግንባ፣ ለፖለቲካው ምህዳር መስፋት በሚል ልጓም ሳይዘረጋ ወሰን-የለሽ መፈንጫ ሜዳ በማዘጋጀቱ ሕግና ስርዓት ይጣስና መንግስት የለም ይባል ዘንድም የራሱን ድርሻም ይወስዳል። በአገር ሕልውና እና ክብር የማይደራደር መንግስት፤ የዜጎችን ሰላምና ደህንነት የመጠበቅ ተቀዳሚ ስራው የሆነ መንግስት፤ በሕግ ወይም በሃይል ችግር የሚፈጥሩ አካላትን አደብ ማስገዛት የማይችል ከሆነ ለአገረ-መንግስቱ መፍረስ ራሱ መንንገስት የሆነው አካል ዱላ እያቀበለ ነው የሚል ክስ ቢቀርብበት ከማስተባበል ይልቅ የድርሻውን የጥፋት ተባባሪነት አምኖ ሊቀበል ይገባዋል።
በሕገ-ወጥ መንገድ ከተማ ላይ ተቀምጠው በትጥቅ ተደራጅተው በቡድንም ሆነ በግለሰብ ደረጃ መንግስትን እንደሌለ ቆጥረው ወይም መንግስትን እናፈርስሃለን ብለው በአደባባይ እስከመዛት በመድረሳቸው ሕዝቡም ፉከራቸውን አይቶ እውነት ስለመሰለው መንግስት የሌለ እንኳን ባይመስለው ከእነሱ አቅም በታች የሆነ ስለመሰው ግብሩን ለእነሱ ለመስጠትና እነሱን ተስፋ ለማድረግ ቢገደድ እንደጥፋት ሊወሰድበት አይገባም።
ሕዝቡ በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴው የሚመለከተውን ጉዳይ እንጅ መንግስት ለዲሞክራሲው ማሳያ እንደሚቆጥራቸውና ምንም አቅም የሌላቸው መሆኑን የሚያውቀው ነገር የለውም። የሚያየውና የሚሰማው ነገር መንግስት አለመኖሩን እንጅ መኖሩን የሚያረጋግጥለት አይደለምና።
ጃዋር መሀመድን በርካታ ሕዝብ እስከቀራኒዮ ድረስ ከአንተ ጋር ነን፤ የእኛ ጀግና እንከተልሃለን በርታልን ይለው የነበረው እኮ ጃዋር መሀመድ ከመንግስት በላይ አቅም ያለው ስለመሰለው ኑሮውን ለማቅለል መገበሩና ተስፋ ማድረጉ ነበር እንጅ የጃዋርን መንገድ ወዶና ፈቅዶለት እንደ ዘላለማዊ ጀግናም ቆጥሮት አልነበረም። በየቀኑ በሚታዩና በሚሰሙ ሽለላዎችና ቀረርቶዎች ከዛም ባለፈ የመንግስት ስራ ማስተጓጎሎች ጃዋር መሃመድ ሁለተኛው ሳይሆን አንተማ አንደኛው መንግስት ነህ ብሎ ሰገደለት። ጃዋርም ሕዝቡ ከልቡ የደገፈውና ከኦሮሚያ አልፎ ንጉሰ ነገስት ዘ ኢትዮጵያ ያለው መስሎት ተሸወደ። ጃዋር መሃመድ ራሱን አራት ኪሎ እየጠበቀ ድንገት ቃሊት የተገኘው ተሸውዶ እንጅ ቃሊት ምርጫው ስለነበረ አይደለም። በቃሊት እስር ቤት ከአንድ ዓመት በላይ ይቅርና አንድ ቀን እንኳን መቆየት እንደሚችል ግምገማ ቢኖረው ኖሮ ጃዋር መሃመድ እንቡር እንቡር ሳይል ክብሩን ጠብቆ በልኩ እያሰበ በጥንቃቄ ይራመድ ነበር።
ንጉሰ-ነገስታችን ጃዋር መሀመድ ሆይ! ይለው በነበረው ሕዝብ አራት ኪሎ መግባቱ ቢቀር የቃሊቲ በር ቢዘጋ እንኳ ቃሊት በአራቱም ማዕዘን ተከቦ ማረሚያ ቤቱ ተሰባብሮ እንደሚወጣ እንጅ ዛሬ ደግሞ እነማን መጥተው ይጠይቁኝ ብሎ ጠያቂ ቆጠራ ላይ የሚሰማራ የስው ረሃብ እንደሚያጋጥመው ግምገማ ቢኖረው የሚከተለው መንገድ ሌላ ነበር። መታሰሩን ተጠራጥረው ከሆነ በሚል የምግብ አድማ ላይ ነኝ ብሎ ቢያስነግርህም ከጥቂት ከንፈር መጣጮች ውጭ እንዳሰበው ሊሆን የሞከረ የለም።
ከታሰረማ ብሎ ሕዝቤ ምኑን መንግስት ሆነው በሚመስል መልኩ መንግስት የሆነውን ተከትሎ መደበኛ ኑሮውን ቀጠለ። ንጉሰ ነገስት ዘ ኦሮሚያ መሆኑ ተረጋግጦለታል የተባለው ጃዋር በቃሊቲ ማረሚያ ቤት ተወሰነ። እንደ ድንፋታዬና እንደስራዬ ፍርድ የሚሰጠኝ ከሆነማ በስብሼ ቀረው እያለ በከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ በነበረበት፣ ማንም ባልጠበቀውና በሕዝቡ በተረሳበት፣ ራሱም ተስፋ በቆረጠበት ፀሎት በሚያደርግበት ባልጠበቀው ወቅት በአብይ አህመድ መልካም ፈቃድ ከቃሊት ስለመውጣቱ ዜና ሲሆን ኦ ጃዋር ተብሎ ስለመኖሩ ወሬ ሆነ።
በሰሞኑ የጃዋር ቃለምልልስ ከቃሊት ለመውጣት በደረቁ ምን ያህል ዱዓ ላይ እንደከረመ፣ ይፀልዩለት የነበሩ ሰዎችን ከማመስገን ጀምሮ በመፈታቱ እሰይ ስለቴ ሰመረ ብሎ ምስጋና ለማቅረብ መካ ድረስ ስለመሄዱ የተናገረው ብዙ ነገሮችን ይናግረናል። ባልጠበቀው ሁኔታ ውስጥ ጃዋር እንዴት እንደተገኘ፣ ያሳለፈውንም ጊዜና የነበረበት ሁኔታም ፍንትው አድርጎ ይገልጣል፤በበኩሌ አንጀቴን እንዴት እንደበላኝ መደበቅም አልፈለኩም😂)።
ከእንግዲህም ጃዋር እንደመጀመሪያው አይሆንም ብቻ ሳይሆን በብዙ ነገሮች ከትናንቱ በተቃራኒ ሊቆም የሚችልባቸው ነገሮች ሊፈጠርም ይችላል። አሁን ላይ ብዙ ነገሮችም ገብተውታል። ያላየውን ነገር ሁሉም አይቷል። የጠበቃቸውና የሆኑ ነገሮችንም ለይቷል። ከዚህ በፊት መንግስት ማለት እንደሱ በሁለት እግር የሚራመደው በተወሰኑ ጠባቂዎች የሚንቀሳቀሰው በግለሰብ ደረጃ ያለው አብይ አህመድ ብቻ አለመሆኑን በገቢር ትርጓሜ ስላረጋገጥ በተለመደው መንገድ የትክሻ መለካካቱ ነገር ፈፅሞ ሊደግመው የማይችል ጉዳይም አይሆንም።
ምን ለማለት ነው? ሐሳብን በነፃነት መግለፅ ገደብ ስለመኖሩ በማንአለብኝነት በአደባባይ አመፅ መጥራትና መንግስትን እንደሌለ አድርጎ ራስን መንግስት ለማድረግ መቁጠርን ከጃዋር መሀመድ ብዙ ነገሮችን መማር ይቻላል። በመንግስት ቁጥጥር ስር ባለ ግዛት ውስጥ እየኖሩ መንግስትን አንዴ እንደሌለ ሌላ ጊዜ ደግሞ ቢኖርም በያዝኩት ጠብ-መንጃ በትጥቅ ትግል አፈርስሃለሁ እያሉ በነፃነት መንግስት ሆኖ እንዴት መኖር እንደሚቻልና እንደማይቻል ከበቂ በላይ የሚያስተምር ነው።ለዲሞክራሲ ማሳያ ተብለው እየታዩ እንዳልታዩ የታለፉና የሚታለፉ ሰዎች በራሳቸው አቅም እንደሚኖሩ ከማሰባቸው ባሻገር ለተጨማሪ ጥፋት የሚያደርጉት ሙከራ አላስፈላጊ ዋጋ የሚያስከፍል መሆኑን ማወቅ ያስፈልጋል። የመንግስትን ትርጉም በቅጡ ካለማወቅ የሚመነጭም ነው። ብዙ ማጣቀሻ አያስፈልገውም። በሕቡዕ ያልሆነ በአደባባይ በግላጭ መንግስት
አገር፣ መንግስት፣ ፓርቲ ሶስቱ የተለያዩ ነገሮች መሆናቸውን ነጣጥሎ አለመመልከትና አለመታገል አላስፈላጊ መስዋዕትነትን ያስከፍላል።
የአንድን ፓርቲ ፕሮግራም መቃወም መንቀፍ መብት ነው። ተቃዋሚ ነኝ ከሚል አካልም የሚጠበቅ ነው። በመንግስት ላይ ተቃውሞ ማሰማት አልፎም ምን አይነት መንግስት ይኑረን? ወይም ይሁን በሚለው ዙሪያም ? የተለያዩ ሐሳቦችን ማንሸራሸር መከራከር ችግር አይደለም። ችግሩ አገረ-መንግስቱን ለማፍረስ ሽፋን አድርጎ መንቀሳቀስ ነው። በስመ ሐሳብን በነፃነት በመግለፅ መብት (Freedom of Expressions) አገር ለማፍረስ እስከመንቀሳቀስ የሚፈቅድ አይደለም። የማንንም ሰባዊ ክብር ስብዕናን እስከመንካት እንኳን የሚያደርስ መብት የለውም። መፃፍ ወይም መናገር ስለተቻለ ብቻ የሰዎችን ስብዕና ክብር መንካት አገር ለማፍረስ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መሳተፍ ወይም መተባበር እንደ ዲሞክራሲ ማሳያዎች የሚታዩ ስላልሆኑ ተጠያቂ ያደርጋሉ። ሐሳብን በነፃነት መግለፅ የሐሳብ አማራጮችን ሐእንጅ የስድብ አማራጮችን የሚያበረታታ አይደለም። አንድ ሰው በሐገር ክህደት ወንጀል ሊያስጠይቀው በሚችል ጉዳይ ጭምር እየተሳተፈ ወይም እየተባበረ ትጠየቃለህ ሲባል እንደመብት ለመቁጠር መሞከር ግሩም ያሰኛል። በዚህ አራት አመት በኢትዮጵያ በተለይ በአማራ ፖለቲካ በስመ ሐሳብን በነፃነት ስም አሳዳጊ የበደላቸው አግድም አደጎችን እንዲነግሱ አድርጓል። ከመዛዛት ያለፈ መገዳ*ደልም ፈጥሯል። በሂደት የሰዎችን ስብዕና መንካት አገር ለማፍረስ መንቀሳቀስ እንደመብት እንዲቆጠር አድርጓልም።
በኢትዮጵያ ሰማይ ስር በውሳጣዊና ውጫዊ ጫናዎችና ውጥረቶች ያልተዳከመ መንግስት ቢኖር ኖሮ በሐገር ክህደት ወንጀል ሊጠየቅ የሚችለው አካል ቁጥር እልፍ ነው።
መንግስት ሕግ የማስከበር የዜጎችን ሰላምና ደህንነት የመጠበቅ ተቀዳሚ ስራው ሆኖ ሳለ አለም ላይ የሌለ ለዲሞክራሲ ግንባ፣ ለፖለቲካው ምህዳር መስፋት በሚል ልጓም ሳይዘረጋ ወሰን-የለሽ መፈንጫ ሜዳ በማዘጋጀቱ ሕግና ስርዓት ይጣስና መንግስት የለም ይባል ዘንድም የራሱን ድርሻም ይወስዳል። በአገር ሕልውና እና ክብር የማይደራደር መንግስት፤ የዜጎችን ሰላምና ደህንነት የመጠበቅ ተቀዳሚ ስራው የሆነ መንግስት፤ በሕግ ወይም በሃይል ችግር የሚፈጥሩ አካላትን አደብ ማስገዛት የማይችል ከሆነ ለአገረ-መንግስቱ መፍረስ ራሱ መንንገስት የሆነው አካል ዱላ እያቀበለ ነው የሚል ክስ ቢቀርብበት ከማስተባበል ይልቅ የድርሻውን የጥፋት ተባባሪነት አምኖ ሊቀበል ይገባዋል።
በሕገ-ወጥ መንገድ ከተማ ላይ ተቀምጠው በትጥቅ ተደራጅተው በቡድንም ሆነ በግለሰብ ደረጃ መንግስትን እንደሌለ ቆጥረው ወይም መንግስትን እናፈርስሃለን ብለው በአደባባይ እስከመዛት በመድረሳቸው ሕዝቡም ፉከራቸውን አይቶ እውነት ስለመሰለው መንግስት የሌለ እንኳን ባይመስለው ከእነሱ አቅም በታች የሆነ ስለመሰው ግብሩን ለእነሱ ለመስጠትና እነሱን ተስፋ ለማድረግ ቢገደድ እንደጥፋት ሊወሰድበት አይገባም።
ሕዝቡ በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴው የሚመለከተውን ጉዳይ እንጅ መንግስት ለዲሞክራሲው ማሳያ እንደሚቆጥራቸውና ምንም አቅም የሌላቸው መሆኑን የሚያውቀው ነገር የለውም። የሚያየውና የሚሰማው ነገር መንግስት አለመኖሩን እንጅ መኖሩን የሚያረጋግጥለት አይደለምና።
ጃዋር መሀመድን በርካታ ሕዝብ እስከቀራኒዮ ድረስ ከአንተ ጋር ነን፤ የእኛ ጀግና እንከተልሃለን በርታልን ይለው የነበረው እኮ ጃዋር መሀመድ ከመንግስት በላይ አቅም ያለው ስለመሰለው ኑሮውን ለማቅለል መገበሩና ተስፋ ማድረጉ ነበር እንጅ የጃዋርን መንገድ ወዶና ፈቅዶለት እንደ ዘላለማዊ ጀግናም ቆጥሮት አልነበረም። በየቀኑ በሚታዩና በሚሰሙ ሽለላዎችና ቀረርቶዎች ከዛም ባለፈ የመንግስት ስራ ማስተጓጎሎች ጃዋር መሃመድ ሁለተኛው ሳይሆን አንተማ አንደኛው መንግስት ነህ ብሎ ሰገደለት። ጃዋርም ሕዝቡ ከልቡ የደገፈውና ከኦሮሚያ አልፎ ንጉሰ ነገስት ዘ ኢትዮጵያ ያለው መስሎት ተሸወደ። ጃዋር መሃመድ ራሱን አራት ኪሎ እየጠበቀ ድንገት ቃሊት የተገኘው ተሸውዶ እንጅ ቃሊት ምርጫው ስለነበረ አይደለም። በቃሊት እስር ቤት ከአንድ ዓመት በላይ ይቅርና አንድ ቀን እንኳን መቆየት እንደሚችል ግምገማ ቢኖረው ኖሮ ጃዋር መሃመድ እንቡር እንቡር ሳይል ክብሩን ጠብቆ በልኩ እያሰበ በጥንቃቄ ይራመድ ነበር።
ንጉሰ-ነገስታችን ጃዋር መሀመድ ሆይ! ይለው በነበረው ሕዝብ አራት ኪሎ መግባቱ ቢቀር የቃሊቲ በር ቢዘጋ እንኳ ቃሊት በአራቱም ማዕዘን ተከቦ ማረሚያ ቤቱ ተሰባብሮ እንደሚወጣ እንጅ ዛሬ ደግሞ እነማን መጥተው ይጠይቁኝ ብሎ ጠያቂ ቆጠራ ላይ የሚሰማራ የስው ረሃብ እንደሚያጋጥመው ግምገማ ቢኖረው የሚከተለው መንገድ ሌላ ነበር። መታሰሩን ተጠራጥረው ከሆነ በሚል የምግብ አድማ ላይ ነኝ ብሎ ቢያስነግርህም ከጥቂት ከንፈር መጣጮች ውጭ እንዳሰበው ሊሆን የሞከረ የለም።
ከታሰረማ ብሎ ሕዝቤ ምኑን መንግስት ሆነው በሚመስል መልኩ መንግስት የሆነውን ተከትሎ መደበኛ ኑሮውን ቀጠለ። ንጉሰ ነገስት ዘ ኦሮሚያ መሆኑ ተረጋግጦለታል የተባለው ጃዋር በቃሊቲ ማረሚያ ቤት ተወሰነ። እንደ ድንፋታዬና እንደስራዬ ፍርድ የሚሰጠኝ ከሆነማ በስብሼ ቀረው እያለ በከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ በነበረበት፣ ማንም ባልጠበቀውና በሕዝቡ በተረሳበት፣ ራሱም ተስፋ በቆረጠበት ፀሎት በሚያደርግበት ባልጠበቀው ወቅት በአብይ አህመድ መልካም ፈቃድ ከቃሊት ስለመውጣቱ ዜና ሲሆን ኦ ጃዋር ተብሎ ስለመኖሩ ወሬ ሆነ።
በሰሞኑ የጃዋር ቃለምልልስ ከቃሊት ለመውጣት በደረቁ ምን ያህል ዱዓ ላይ እንደከረመ፣ ይፀልዩለት የነበሩ ሰዎችን ከማመስገን ጀምሮ በመፈታቱ እሰይ ስለቴ ሰመረ ብሎ ምስጋና ለማቅረብ መካ ድረስ ስለመሄዱ የተናገረው ብዙ ነገሮችን ይናግረናል። ባልጠበቀው ሁኔታ ውስጥ ጃዋር እንዴት እንደተገኘ፣ ያሳለፈውንም ጊዜና የነበረበት ሁኔታም ፍንትው አድርጎ ይገልጣል፤በበኩሌ አንጀቴን እንዴት እንደበላኝ መደበቅም አልፈለኩም😂)።
ከእንግዲህም ጃዋር እንደመጀመሪያው አይሆንም ብቻ ሳይሆን በብዙ ነገሮች ከትናንቱ በተቃራኒ ሊቆም የሚችልባቸው ነገሮች ሊፈጠርም ይችላል። አሁን ላይ ብዙ ነገሮችም ገብተውታል። ያላየውን ነገር ሁሉም አይቷል። የጠበቃቸውና የሆኑ ነገሮችንም ለይቷል። ከዚህ በፊት መንግስት ማለት እንደሱ በሁለት እግር የሚራመደው በተወሰኑ ጠባቂዎች የሚንቀሳቀሰው በግለሰብ ደረጃ ያለው አብይ አህመድ ብቻ አለመሆኑን በገቢር ትርጓሜ ስላረጋገጥ በተለመደው መንገድ የትክሻ መለካካቱ ነገር ፈፅሞ ሊደግመው የማይችል ጉዳይም አይሆንም።
ምን ለማለት ነው? ሐሳብን በነፃነት መግለፅ ገደብ ስለመኖሩ በማንአለብኝነት በአደባባይ አመፅ መጥራትና መንግስትን እንደሌለ አድርጎ ራስን መንግስት ለማድረግ መቁጠርን ከጃዋር መሀመድ ብዙ ነገሮችን መማር ይቻላል። በመንግስት ቁጥጥር ስር ባለ ግዛት ውስጥ እየኖሩ መንግስትን አንዴ እንደሌለ ሌላ ጊዜ ደግሞ ቢኖርም በያዝኩት ጠብ-መንጃ በትጥቅ ትግል አፈርስሃለሁ እያሉ በነፃነት መንግስት ሆኖ እንዴት መኖር እንደሚቻልና እንደማይቻል ከበቂ በላይ የሚያስተምር ነው።ለዲሞክራሲ ማሳያ ተብለው እየታዩ እንዳልታዩ የታለፉና የሚታለፉ ሰዎች በራሳቸው አቅም እንደሚኖሩ ከማሰባቸው ባሻገር ለተጨማሪ ጥፋት የሚያደርጉት ሙከራ አላስፈላጊ ዋጋ የሚያስከፍል መሆኑን ማወቅ ያስፈልጋል። የመንግስትን ትርጉም በቅጡ ካለማወቅ የሚመነጭም ነው። ብዙ ማጣቀሻ አያስፈልገውም። በሕቡዕ ያልሆነ በአደባባይ በግላጭ መንግስት
በሚያስተዳድረው ግዛት ለዛውም ከተማ ላይ ተሁኖ የትጥቅ ትግል ጥሪ የተደረገበትና ሕዝብና አገር እመራሃለሁ ተብሎ የታሰበበትም ሆነ የተሞከረበት በእኛ ዘመንና በእኛ አገር ብቻ ለመጀመሪያ ጊዜ እየተፈጠረ ካልሆነ ከዚህ በፊት በአገራችንም ሆነ በአለም ላይ የተፈጠረ አይመስለኝም። በአስቂነትና በቂልነት አዲስ ሙከራ ሆኖ በታሪክ የመመዝገብ እድል አይኖረውም ማለት ግን አይቻልም።
እንኳን ኦህዴድ ኦነግ አራት ኪሎ ገብቶ ሳለ በርካታ የኦሮሞ ልሒቃን ግን አሁንም ድረስ ኦሮሞ ስልጣን ስለመያዙ እርግጠኛ የሆኑ አይመስሉም። ቁጥሩ ቀላል የማይባል ሰው ተረኛው የኦሮሞ ሃይል ሊወጠን ነው በሚል በተሰለበ ስነልቦና ውስጥ ገብቶ እየተንበረከከላቸው ባለበት ሁኔታ ትናንት ለዓመታት ያቀነቀኑት የተጠቅተናል የለቅሶው ፖለቲካ ገና ስላለቀቃቸው፥ የአብይ አህመድ መንግስት የነፍጠኛው የአሃዳዊ ስርዓቱን ሊመልሰው ነው የሚለው የወያኔ ፕሮፖጋንዳ ሲያሸንፋቸው ይታያል። ኦነግ ሸኔም ሆኑ እሱን የሚደግፉ አካላት ምን ለማሳካት እንደሚታገሉ አይገባኝም።
ከእነ አብይ አህመድ ሽመልስ አብዲሳ ታከለ ኡማ አዳነች አበቤ... በላይ ምን አይነት የኦሮሞ ተቆርቋሪ ለማምጣትስ ተፈልጎ ነው? ጃል መሮ ወደስልጣን ቢወጣ ለኦሮሞ ሕዝብ ምን ያሳካለታል ተብሎ ታስቦ ነው?! የለቅሶ የተጠቅተናል ፖለቲካ ትልቁ ችግር ስልጣን ላይ ወጥተህም የእውነት ስልጣን የያዝክ ስለማይመስልህ እዬዬው አይለቅህም። የእዬዬው ሐይል ስልጣን ላይ ወጥቶ እንደነበረ የሚገባው ስልጣኑን ያጣ ቀን ነው። ከዛ በፊት እዬዬ ትግልም ነው የሚመስለው።
እናቱ የሞተችበትም እናቱ ገቢያ የሄደችበትም እኩል ያለቅሳሉ የሚለው ብሒል በኢትዮጵያ ፖለቲካ በግልጽ የሚታይ ነው። ለቅሶው በእዚህም በእዚያም አካባቢ እንደቀጠለም ነው። ሁሉም አልቃሽ አስለቃሾች የሕወሓት ፕሮፖጋንዳ ሰለባ የሆኑ ሕወሓት ከተጠያቂነት ውጭ ያደረጉ ወይም እንዲሆን የሚሰሩ መሆናቸው ሁሉንም አንድ ያደርጋቸዋል።
ከእነ አብይ አህመድ ሽመልስ አብዲሳ ታከለ ኡማ አዳነች አበቤ... በላይ ምን አይነት የኦሮሞ ተቆርቋሪ ለማምጣትስ ተፈልጎ ነው? ጃል መሮ ወደስልጣን ቢወጣ ለኦሮሞ ሕዝብ ምን ያሳካለታል ተብሎ ታስቦ ነው?! የለቅሶ የተጠቅተናል ፖለቲካ ትልቁ ችግር ስልጣን ላይ ወጥተህም የእውነት ስልጣን የያዝክ ስለማይመስልህ እዬዬው አይለቅህም። የእዬዬው ሐይል ስልጣን ላይ ወጥቶ እንደነበረ የሚገባው ስልጣኑን ያጣ ቀን ነው። ከዛ በፊት እዬዬ ትግልም ነው የሚመስለው።
እናቱ የሞተችበትም እናቱ ገቢያ የሄደችበትም እኩል ያለቅሳሉ የሚለው ብሒል በኢትዮጵያ ፖለቲካ በግልጽ የሚታይ ነው። ለቅሶው በእዚህም በእዚያም አካባቢ እንደቀጠለም ነው። ሁሉም አልቃሽ አስለቃሾች የሕወሓት ፕሮፖጋንዳ ሰለባ የሆኑ ሕወሓት ከተጠያቂነት ውጭ ያደረጉ ወይም እንዲሆን የሚሰሩ መሆናቸው ሁሉንም አንድ ያደርጋቸዋል።
ዋው!
እነዚህ የተመረጡ ሰዎች የሚዟዟሩት ምን አደረጉ ተብለው ነው?
ፌስቡክን የምወደው እኮ ያለምክንያት አይደለም። መሬት ላይ እንዳለው መዋቅር ቢሆን ከእነዚህ ሰዎች ጋር መቼ እኩል አልሰለፍም ነበር። የማርቆስን እድሜ ያርዝምልንና ይኼው ፌስቡክ ግን ሁሉንም እኩል ማድረግ አይሳነውምና እኔንም ከእነዚህ አካላት ጋር እኩል አሰለፈኝ። ግን ከእነሱ ጋር መሰለፌ ላልቀረ ወደውስጥ ከምትቀረቅሩኝ መሃል ላይ ትንሽ ጎላ አድርጋችሁ የሑሉም ጠቅላይ አዛዥ የሆንኩ ያህል እንዲሰማኝ ቢደረግ አሪፍ ነበር። ለማትከስሩበት ነገር ስልጣን ከሰጣችሁ አይቀር ንፉግ መሆን አልነበረባችሁም እኮ😂
በነገራችን ላይ እኔን ማስበለጥ እየተቻለ እኩል እንድሰለፍ የተደረገው እንዲሁ ሳይሆን በቀጣይ ጊዜዬን በስልጣን ሽኩቻ እንዳሳልፍ ለማድረግ ሆንተብሎ የታሰበ ሴራ ስለመሆኑ ቀልቤ እንደነገረኝ መደበቅ አልፈልግም😂
ፌስቡክ ለዘለዓለም ይኑር!
እነዚህ የተመረጡ ሰዎች የሚዟዟሩት ምን አደረጉ ተብለው ነው?
ፌስቡክን የምወደው እኮ ያለምክንያት አይደለም። መሬት ላይ እንዳለው መዋቅር ቢሆን ከእነዚህ ሰዎች ጋር መቼ እኩል አልሰለፍም ነበር። የማርቆስን እድሜ ያርዝምልንና ይኼው ፌስቡክ ግን ሁሉንም እኩል ማድረግ አይሳነውምና እኔንም ከእነዚህ አካላት ጋር እኩል አሰለፈኝ። ግን ከእነሱ ጋር መሰለፌ ላልቀረ ወደውስጥ ከምትቀረቅሩኝ መሃል ላይ ትንሽ ጎላ አድርጋችሁ የሑሉም ጠቅላይ አዛዥ የሆንኩ ያህል እንዲሰማኝ ቢደረግ አሪፍ ነበር። ለማትከስሩበት ነገር ስልጣን ከሰጣችሁ አይቀር ንፉግ መሆን አልነበረባችሁም እኮ😂
በነገራችን ላይ እኔን ማስበለጥ እየተቻለ እኩል እንድሰለፍ የተደረገው እንዲሁ ሳይሆን በቀጣይ ጊዜዬን በስልጣን ሽኩቻ እንዳሳልፍ ለማድረግ ሆንተብሎ የታሰበ ሴራ ስለመሆኑ ቀልቤ እንደነገረኝ መደበቅ አልፈልግም😂
ፌስቡክ ለዘለዓለም ይኑር!
ወያኔያዊ የአማራ ብሔርተኛን Demobilize እናደርገዋለን። እውነት ላይ ስለቆምን የተካኑበትን በውሸት ማደናገርን ለሰፊው ሕዝብ ገልጠን ነውራቸውን ጌጥ አድርገው ስድባቸውን ብቻ ታቅፈው እንዲቀሩ እናደርጋቸዋለን። የጊዜ ጉዳይ ነው‼️
ሰሞኑን ወያኔ እና ወያኒያዊነት ምንድን ነው? የሚል ክርክር እዚህም እዛ እየሰማን ነው።
'ወያኒያዊ' የሚለው ስም አሰጣጣችን ዝም ብሎ ጥቅም ላይ የዋለ ሳይሆን የሃይል አሰላለፍ መስመርን ለመለየት እና ቀጣይ የትግል አቅጣጫን ለመወሰን ጥቅም ላይ መዋሉን ሊታወቅ ይገባል።
ወያኔነት እና ወያኒያዊ አስተሰሰብ በትግ*ሬነት ብቻ የሚከሰት አይደለም። ወያኔ የፖለቲካ ፕሮግራሟን ጽፋ ደደቢት ከወረደችበት ዕለት አንስቶ ስፍር ቁጥር የሌላቸው ኢትዮጵያዊያንን በወያኔነት እና በወያኒያዊ አስተሳሰብ አጥምቃለች። ቁጥራቸው ቀላል የማይባሉ አማሮችን በወያኔነት እና በወያኒያዊ አስተሳሰብ አስጥማ እና የአማራ ህዝብ "ወኪል" አድርጋ በአማራ ህዝብ ላይ ወደር የሌለው ግፍ ፈጽማለች። በወያኒያዊ አስተሳሰብ የተጠመቁ/የተጠቁ "አማሮች" ዛሬም አሉ። አስተሳሰቡ በአንድ ጀንበር አልሰረጸም እና በአጭር ጊዜም ይጠፋል ተብሎ አይጠበቅም። ብዙ ስራ ይጠይቃል።
እንዲያው ግን "የወልቃይት-ራያን ህዝብ ዳግም ለዕልቂት እና ለባርነት ለትግሬ አሳልፈን ሰጥተን ከወያኔ ጋር ግንባር እንፍጠር ፤ ወያኔ የሚመራው የት*ግሬ ወ*ራሪ ጦር የከፈተው ጦርነት አማራን አይመለክትም ፤ አብይ/ብልጽግና የወልቃይት-ራያን ህዝብ ለትግ*ሬ ወ*ራሪ ጦር እንዳያስበላው ከአብይ/ብልጽግና ጋር ጦርነት እንግጠም፤ ወያኔን እንተወው እና ከአብይ/ብልጽግና ጋር ጦርነት እንግጠም" የሚል "አማራ"ን አፍቃሪ-ወያኔ /ወያኔያዊ/ ከማለት ውጭ ምን ልንለው እንችላለን?
በምን መመዘኛ ወያኔ የሚመራው የት*ግሬ ወራ*ሪ ሃይል የአማራ ህዝብ 2ኛ - ደረጃ ጠላት ሆኖ ፣ አለፍ ሲልም የአማራ አጋር ነው እያሉን ፤ አብይ/ብልጽግና 1ኛ - ደረጃ ጠላት ሊሆን የሚችለው?! ወያኔ የሚመራው የትግሬ ወራሪ ጦር በመቶ ሽህዎች የሚቆጠር ጦር አሰልፎ ለወረ*ራ ቀን እየቆጠረ ባለበት ወቅት ፣ አማራ በአራቱም አቅጣጫ ጦርነት ይክፈት የሚል ቅስቀሳ በየት አድርጎ ነው የአማራ ሕዝብ ፖለቲካ የሚሆነው?! በሰሜን በኩል ወያኔ የሚመራው የትግ*ሬ ወራ*ሪ ጦር ለሶስተኛ ወረራ ዝግጅቴን ጨርሻለሁ ብሎ ባወጀበት ወቅት : በደቡብ በኩል ከአብይ/ብልጽግና ጋር ጦርነት ካልገጠምን ማለት በምን ስሌት ነው የአማራ ትግል የሚሆነው?! በወያኒያዊ አስተሳሰብ እና በወያኔያዊ የሃይል አሰላለፍ ስሌት ካልሆነ በቀር?!
ወያኔነት የትግ*ሬዎች ስብስብ ብቻ አይደለም ፣ ለወያኔ ርዕዮተ ዓለም የሰገረ ፣ ከወያኔ ጋር የፖለቲካ ሽ**ጥና ውስጥ ገብቶ ለወያኔ የፖለቲካ ፕሮግራም ስኬት የሚሰራ ፤ ብርቱ ትዕግስት ፣ ከፍተኛ ንቃት እና የላቀ ጥንቃቄ የሚጠይቀውን እና ወያኔ ከገነባው ስርዓት እና መዋቅር ጋር የአማራ ህዝብ የሚያደርገውን ብርቱ ትግል ፣ ከግለሰቦች ጋር የሚደረግ ተራ ግብግብ አስመስሎ የሚያቀርብ/የሚቀሰቅስ ማንኛውም ግለሰብ/ቡድን ወያኔ እና ወያኒያዊ ካልሆነ በቀር ምን ሊሆን ይችላል?!
የጠላት የሆነውን ፖለቲካ የማይለይ እና ትልቁን ግብ ታሳቢ አድርጎ የማይመራ የፖለቲካ ትግል በጠላት መጠለፉ እና የጠላትን ዓላማ ከማሳካት ያለፈ ፋይዳ የለውም። በጠላት የሃይል አሰላለፍ ውስጥ ገብቶ የሚሳካ የወገን የፖለቲካ ግብ የለም። ሁነኛውን ጠላት በመለየት ፣ የጠላት ቁጥርን በመቀነስ እና አጋሮችን በማብዛት ስልት የሚመራ ፖለቲካ ብቻ አላማውን ያሳካል። ለብዙው ሰው ፍሬው አሁን ባይታየውም ፣ የአማራ ህዝብ ፖለቲካ በሀቀኛ ልጆቹ በዚህ አግባብ እየተመራ በመሆኑ ስትራቴጅካዊ ግቦቻችንን የምናሳካበት ፣ መዋቅራዊ እና ስልታዊ ፈተናዎቻችንን የምንቀለብስበትን የትግል መስመር ይዘናል። ድላችንም እርግጥ ነው!
Daniel Tilahun Tadesse
'ወያኒያዊ' የሚለው ስም አሰጣጣችን ዝም ብሎ ጥቅም ላይ የዋለ ሳይሆን የሃይል አሰላለፍ መስመርን ለመለየት እና ቀጣይ የትግል አቅጣጫን ለመወሰን ጥቅም ላይ መዋሉን ሊታወቅ ይገባል።
ወያኔነት እና ወያኒያዊ አስተሰሰብ በትግ*ሬነት ብቻ የሚከሰት አይደለም። ወያኔ የፖለቲካ ፕሮግራሟን ጽፋ ደደቢት ከወረደችበት ዕለት አንስቶ ስፍር ቁጥር የሌላቸው ኢትዮጵያዊያንን በወያኔነት እና በወያኒያዊ አስተሳሰብ አጥምቃለች። ቁጥራቸው ቀላል የማይባሉ አማሮችን በወያኔነት እና በወያኒያዊ አስተሳሰብ አስጥማ እና የአማራ ህዝብ "ወኪል" አድርጋ በአማራ ህዝብ ላይ ወደር የሌለው ግፍ ፈጽማለች። በወያኒያዊ አስተሳሰብ የተጠመቁ/የተጠቁ "አማሮች" ዛሬም አሉ። አስተሳሰቡ በአንድ ጀንበር አልሰረጸም እና በአጭር ጊዜም ይጠፋል ተብሎ አይጠበቅም። ብዙ ስራ ይጠይቃል።
እንዲያው ግን "የወልቃይት-ራያን ህዝብ ዳግም ለዕልቂት እና ለባርነት ለትግሬ አሳልፈን ሰጥተን ከወያኔ ጋር ግንባር እንፍጠር ፤ ወያኔ የሚመራው የት*ግሬ ወ*ራሪ ጦር የከፈተው ጦርነት አማራን አይመለክትም ፤ አብይ/ብልጽግና የወልቃይት-ራያን ህዝብ ለትግ*ሬ ወ*ራሪ ጦር እንዳያስበላው ከአብይ/ብልጽግና ጋር ጦርነት እንግጠም፤ ወያኔን እንተወው እና ከአብይ/ብልጽግና ጋር ጦርነት እንግጠም" የሚል "አማራ"ን አፍቃሪ-ወያኔ /ወያኔያዊ/ ከማለት ውጭ ምን ልንለው እንችላለን?
በምን መመዘኛ ወያኔ የሚመራው የት*ግሬ ወራ*ሪ ሃይል የአማራ ህዝብ 2ኛ - ደረጃ ጠላት ሆኖ ፣ አለፍ ሲልም የአማራ አጋር ነው እያሉን ፤ አብይ/ብልጽግና 1ኛ - ደረጃ ጠላት ሊሆን የሚችለው?! ወያኔ የሚመራው የትግሬ ወራሪ ጦር በመቶ ሽህዎች የሚቆጠር ጦር አሰልፎ ለወረ*ራ ቀን እየቆጠረ ባለበት ወቅት ፣ አማራ በአራቱም አቅጣጫ ጦርነት ይክፈት የሚል ቅስቀሳ በየት አድርጎ ነው የአማራ ሕዝብ ፖለቲካ የሚሆነው?! በሰሜን በኩል ወያኔ የሚመራው የትግ*ሬ ወራ*ሪ ጦር ለሶስተኛ ወረራ ዝግጅቴን ጨርሻለሁ ብሎ ባወጀበት ወቅት : በደቡብ በኩል ከአብይ/ብልጽግና ጋር ጦርነት ካልገጠምን ማለት በምን ስሌት ነው የአማራ ትግል የሚሆነው?! በወያኒያዊ አስተሳሰብ እና በወያኔያዊ የሃይል አሰላለፍ ስሌት ካልሆነ በቀር?!
ወያኔነት የትግ*ሬዎች ስብስብ ብቻ አይደለም ፣ ለወያኔ ርዕዮተ ዓለም የሰገረ ፣ ከወያኔ ጋር የፖለቲካ ሽ**ጥና ውስጥ ገብቶ ለወያኔ የፖለቲካ ፕሮግራም ስኬት የሚሰራ ፤ ብርቱ ትዕግስት ፣ ከፍተኛ ንቃት እና የላቀ ጥንቃቄ የሚጠይቀውን እና ወያኔ ከገነባው ስርዓት እና መዋቅር ጋር የአማራ ህዝብ የሚያደርገውን ብርቱ ትግል ፣ ከግለሰቦች ጋር የሚደረግ ተራ ግብግብ አስመስሎ የሚያቀርብ/የሚቀሰቅስ ማንኛውም ግለሰብ/ቡድን ወያኔ እና ወያኒያዊ ካልሆነ በቀር ምን ሊሆን ይችላል?!
የጠላት የሆነውን ፖለቲካ የማይለይ እና ትልቁን ግብ ታሳቢ አድርጎ የማይመራ የፖለቲካ ትግል በጠላት መጠለፉ እና የጠላትን ዓላማ ከማሳካት ያለፈ ፋይዳ የለውም። በጠላት የሃይል አሰላለፍ ውስጥ ገብቶ የሚሳካ የወገን የፖለቲካ ግብ የለም። ሁነኛውን ጠላት በመለየት ፣ የጠላት ቁጥርን በመቀነስ እና አጋሮችን በማብዛት ስልት የሚመራ ፖለቲካ ብቻ አላማውን ያሳካል። ለብዙው ሰው ፍሬው አሁን ባይታየውም ፣ የአማራ ህዝብ ፖለቲካ በሀቀኛ ልጆቹ በዚህ አግባብ እየተመራ በመሆኑ ስትራቴጅካዊ ግቦቻችንን የምናሳካበት ፣ መዋቅራዊ እና ስልታዊ ፈተናዎቻችንን የምንቀለብስበትን የትግል መስመር ይዘናል። ድላችንም እርግጥ ነው!
Daniel Tilahun Tadesse
በኤሊዳአር ከተማ ላይ የተነሳውን ድንገተኛ የእሳት ቃጠሎ ከደረሰው በላይ ከፍተኛ ውድመት እንዳይደርስ የጀግናው መከላከያ ሰራዊታችን አባላት ከሕዝባችን ጋር በመቀናጀት የእሳት ቋጠሮውን ለመቆጣጠር ተችሏል።
ክብር የኢትዮጵያን ሉዓላዊነትና ነፃነት ለመጠበቅ የሕዝቦቿን ዘላቂ ሰላምና ጥቅም ለማስከበር ያለ እረፍት በረመጥ መካከል ለሚያልፉ ጀግኖቻችን ይሁን‼️
ክብር የኢትዮጵያን ሉዓላዊነትና ነፃነት ለመጠበቅ የሕዝቦቿን ዘላቂ ሰላምና ጥቅም ለማስከበር ያለ እረፍት በረመጥ መካከል ለሚያልፉ ጀግኖቻችን ይሁን‼️
ኢትዮጵያን ለማፍረስ የባንዳ ባንዳ ሆነው በሐገር ውስጥና በባህርማዶ ለወያኔ መንገድ ለመጥረግ፣ መንገድ ለመምራት በተለያዬ መንገድ ተደራጅተው ከፊት ተሰልፈው ሲንቀሳቀሱ ለነበሩ የእፍኝት ልጆች ወደግንባር ከመዝመታችን በፊት ይልን መልዕክት አስተላልፈንላቸው ነበር። ምንም እንኳን ፊት ለፊት የሚያቆም አቅሞና ልብ ባይኖራውም በግንባር የግብር አባታቸውን ወያኔን አሰልፈው በጀርባ በኩል ደግሞ እነሱ ተሰልፈው ያለ የሌለ አቅማቸውን ተጠቅመው ሊወጉንና ሊያጠቁን ኢትዮጵያንም ሊያፈርሱ ቢሞክሩም አልተቻላቸውም። በተባበረው ክንዳችን ተንበርክከዋል። እኛ ኢትዮጵያዊያንን ሊቋቋሙን አልቻሉም። በሕልውና ዘመቻው ያንበረከክነውን ሃይል ነብስ ሊዘሩበት ከውስጥ በኩል የተለያዩ ግንባሮችን ሊከፍቱ ከጀርባ በኩል ጥቃት ሊከፍቱ ያሰፈሰፉትን በሐገር ቤት በአማራ ስም በተለያዬ የአደረጃጀት ቅርፅ በሕቡዕም በግላጭም የሚንቀሳቀሱትን የወያኔ መንገድ ጠራጊ መንገድ መሪዎችን በተጀመረው የሕግ ማስከበር ዘመቻ አላማቸው እየተንኮላሸ ይገኛል። ሕጋዊ እርምጃው የነገን የጀርባን ጥቃት ከመከላከል ባሻገር የሕዝቡን ዘላቂ ሰላምና ጥቅም ለማስከበር የሚያግዝ የተዋጣለት ኦፕሬሽንም ነው እየተካሄደ የሚገኘው። በዚህ አጋጣሚ በሕግ ማስከበር ኦፕሬሽን የተሰማሩ ዲስፕሊንድ የሆኑ የፀጥታ አካላት ምስጋና ይገባቸዋል።
ወደቀደመ ሐሳባችን ስንመለስ በአማራ ስም በተለያዩ የሲቪክ ማህበራትና የሚዲያ ተቋማት ሽፋን ኢትዮጵያን ለማፍረስ ለወያኔ መንገድ ሲጠርጉ የነበሩ የወያኔ የማደጎ ልጅነታቸውን በግብር የገለጡ በተለይም በዲያስፖራ በኩል ያሉ አካላትን ጭንብላቸውን የመግለጥ ስራዎች አሁንም ብዙ የሚቀር ቢሆንም የማድረግ አቅማቸውን ከተመለከተን ግን በራሳቸው የትም መድረስ የሚያስችል ከአቧራው ጨሰ ልፈፋ ያለፈ ሕዝባዊ መሰረት ያለው የፖለቲካ ተክለ ስብዕና የማድረግ አቅምም የሌላቸው መሆናቸውን በእርግጠኝነት መናገር ይቻላል።
በአማራ ስም በዲያስፖራው በኩልም ሆነ በሐገር ቤት ውስጥ የተለያዬ ቅርፅ ባለው በሕቡዕም ሆነ በግልፅ አደረጃጀት(ቤተክርስቲያንም ሆነ መስጊድን ጭምር ለመጠቀም )የሚንቀሳቀሰው የወያኔ መንገድ ጠራጊ ሃይል ትልቁ ጉልበቱ የሚነመጨው(አንዳንዶቹ አደረጃጀቶችም የተመሰረቱት) በመንግሥት መዋቅር እና በብልፅግና ውስጥ አገር ለማፍረስ መረጃ አሳልፎ የሚሰጠው፣ ከውጭ ሐይሎች ጋር በመቀናጀት ሲንቀሳቀስ የቆየው፣ በአማራ ላይ ሂሳብ እንዲወራረድበት (የግፍ ግፍ እንዲፈፀምበት) ለወያኔ መንገድ ሲጠርግና መንገድ ሲመራ የነበረው፣ አሁንም በዛው ግብር መልኩን እየቀያየረ የቀጠለው የወንጀል የተጠያቂነት ስጋት ያለበት፣ በብልፅግና ውስጥ ያለው ያልበለፀገው አፍቃሬ ወያኔ ነው። በአማራ ስም በሐገር ቤትና በባህርማዶ የሚንቀሳቀሰው የወያኔው የአማርኛ ክንፍ ከመንግስት መዋቅራዊ ድጋፍ እስካላገኘ ድረስ ብቻውን በራሱ መቆም የማይችል ነብስ የሌለው ሃይል ነው። የሕልውና መሰረቱ መንግስታዊ መዋቅሩ ነው።
ዶ/ር አብይ አህመድ በመንግስታዊ መዋቅሩና በብልፅግና ውስጥ ያሉ አፍቃሬ ወያኔ አገር አፍራሾችን እየለቀመ ወደሚገባቸው ቦታ ሊሸኛቸው እንጅ እንደተለመደው ሊንቃቸው አይገባም። አማራንም ሆነ ኢትዮጵያን አላስፈላጊ መስዋዕትነት ያስከፈላት ወደፊትም ሊያስከፍላት የሚችለው ከማንም በላይ በመንግስታዊ መዋቅሩ እና በብልፅግና ውስጥ ያሉ የወያኔ የግብር ልጆች ናቸው።
እነዚህ ልቡሳነ ስጋዎች ደግሞ መቼም ቢሆን ከመንግስታዊ መዋቅሩም ሆነ ከድርጅቱ በራሳቸው ፈቃድ ሊነጠሉ ስለማይችሉ(የጥፋት አላማቸውን የሚያሳኩበት ትክክለኛ ቦታ ላይ ስለሆኑ) ዶ/ር አብይ አህመድ ሁሉንም ጥፋት ደጋሾችን በመለቃቀም ወደሚገባቸው ቦታ ካልሆነም ሲፈልጉ አቅምና ልብ አለን ካሉ፣ ተከዜን እንዲሻገሩ ከግብር አባታቸው ከወያኔ ጋር ተሰልፈው ለጦርነትም ይሁን ለድርድር ኢትዮጵያን እንዲገጥሙ ማመቻቸት እንጅ በመንግሥት መዋቅር ውስጥና በብልፅግና ውስጥ ሆነው የውጭ ባዳንና ወያኔን መንገድ እየጠረጉ፣ መንገድ እየመሩ ኢትዮጵያን እንዲያደሟት ከቻሉ እንዲያፈርሷት ነገሮች ሊመቻቹላቸው ፈፅሞ አይገባም። ይህን አለማድረግ በራሱ በሌላ መንገድ አገር ለማፍረስ እንደመተባበር የሚቆጠርም ይሆናል‼️
ፅዳት መጀመር ያለበት ከራስም ነው ለማለት እንወዳለን‼️
ወደቀደመ ሐሳባችን ስንመለስ በአማራ ስም በተለያዩ የሲቪክ ማህበራትና የሚዲያ ተቋማት ሽፋን ኢትዮጵያን ለማፍረስ ለወያኔ መንገድ ሲጠርጉ የነበሩ የወያኔ የማደጎ ልጅነታቸውን በግብር የገለጡ በተለይም በዲያስፖራ በኩል ያሉ አካላትን ጭንብላቸውን የመግለጥ ስራዎች አሁንም ብዙ የሚቀር ቢሆንም የማድረግ አቅማቸውን ከተመለከተን ግን በራሳቸው የትም መድረስ የሚያስችል ከአቧራው ጨሰ ልፈፋ ያለፈ ሕዝባዊ መሰረት ያለው የፖለቲካ ተክለ ስብዕና የማድረግ አቅምም የሌላቸው መሆናቸውን በእርግጠኝነት መናገር ይቻላል።
በአማራ ስም በዲያስፖራው በኩልም ሆነ በሐገር ቤት ውስጥ የተለያዬ ቅርፅ ባለው በሕቡዕም ሆነ በግልፅ አደረጃጀት(ቤተክርስቲያንም ሆነ መስጊድን ጭምር ለመጠቀም )የሚንቀሳቀሰው የወያኔ መንገድ ጠራጊ ሃይል ትልቁ ጉልበቱ የሚነመጨው(አንዳንዶቹ አደረጃጀቶችም የተመሰረቱት) በመንግሥት መዋቅር እና በብልፅግና ውስጥ አገር ለማፍረስ መረጃ አሳልፎ የሚሰጠው፣ ከውጭ ሐይሎች ጋር በመቀናጀት ሲንቀሳቀስ የቆየው፣ በአማራ ላይ ሂሳብ እንዲወራረድበት (የግፍ ግፍ እንዲፈፀምበት) ለወያኔ መንገድ ሲጠርግና መንገድ ሲመራ የነበረው፣ አሁንም በዛው ግብር መልኩን እየቀያየረ የቀጠለው የወንጀል የተጠያቂነት ስጋት ያለበት፣ በብልፅግና ውስጥ ያለው ያልበለፀገው አፍቃሬ ወያኔ ነው። በአማራ ስም በሐገር ቤትና በባህርማዶ የሚንቀሳቀሰው የወያኔው የአማርኛ ክንፍ ከመንግስት መዋቅራዊ ድጋፍ እስካላገኘ ድረስ ብቻውን በራሱ መቆም የማይችል ነብስ የሌለው ሃይል ነው። የሕልውና መሰረቱ መንግስታዊ መዋቅሩ ነው።
ዶ/ር አብይ አህመድ በመንግስታዊ መዋቅሩና በብልፅግና ውስጥ ያሉ አፍቃሬ ወያኔ አገር አፍራሾችን እየለቀመ ወደሚገባቸው ቦታ ሊሸኛቸው እንጅ እንደተለመደው ሊንቃቸው አይገባም። አማራንም ሆነ ኢትዮጵያን አላስፈላጊ መስዋዕትነት ያስከፈላት ወደፊትም ሊያስከፍላት የሚችለው ከማንም በላይ በመንግስታዊ መዋቅሩ እና በብልፅግና ውስጥ ያሉ የወያኔ የግብር ልጆች ናቸው።
እነዚህ ልቡሳነ ስጋዎች ደግሞ መቼም ቢሆን ከመንግስታዊ መዋቅሩም ሆነ ከድርጅቱ በራሳቸው ፈቃድ ሊነጠሉ ስለማይችሉ(የጥፋት አላማቸውን የሚያሳኩበት ትክክለኛ ቦታ ላይ ስለሆኑ) ዶ/ር አብይ አህመድ ሁሉንም ጥፋት ደጋሾችን በመለቃቀም ወደሚገባቸው ቦታ ካልሆነም ሲፈልጉ አቅምና ልብ አለን ካሉ፣ ተከዜን እንዲሻገሩ ከግብር አባታቸው ከወያኔ ጋር ተሰልፈው ለጦርነትም ይሁን ለድርድር ኢትዮጵያን እንዲገጥሙ ማመቻቸት እንጅ በመንግሥት መዋቅር ውስጥና በብልፅግና ውስጥ ሆነው የውጭ ባዳንና ወያኔን መንገድ እየጠረጉ፣ መንገድ እየመሩ ኢትዮጵያን እንዲያደሟት ከቻሉ እንዲያፈርሷት ነገሮች ሊመቻቹላቸው ፈፅሞ አይገባም። ይህን አለማድረግ በራሱ በሌላ መንገድ አገር ለማፍረስ እንደመተባበር የሚቆጠርም ይሆናል‼️
ፅዳት መጀመር ያለበት ከራስም ነው ለማለት እንወዳለን‼️
ግልፅ ለማድረግ ያህል!
የእኔ የትኩረት ማዕከል ከትናንት እስከዛሬ ጥቅሜ ተነካብኝ ብሎ አገር ለማፍረስ በተለያዬ መንገድ በሚንቀሳቀሰው መዋቅራዊ ጉልበት ባለው አካል ላይ ብቻ ነው። መዋቅራዊ ጉልበት የሌለው የትኛውም ግለሰብም ሆነ ቡድን ፈፅሞ አጀንዳዬ ሆኖ አያውቅም። እስካሁን ከማንም ጋር የግል ፀብ ኖሮብኝ በስሜትና ሌላ ሽፋን በመስጠት የምፅፈው አንዳችም ጉዳይ የለም። ማንም ሰው የምፅፈውን የትኛውንም ፅሑፍ ወደራሱ ፍላጎትና ወደሚያስበው ጉዳይ ከአውድ ውጭ እንደፈለገ ሊተረጉመው ግን ይችላል። ለእኔ የሰዎች ትርጉም ጉዳዬ አይደለም። አይሆንምም።
እውነት ላይ እስከቆምን ድረስ የመንጋውን የስሜት ፈረስ ውሸትን አንበርክከን መንጋ አዝማቾችን እርቃናቸውን ማስቀረታችን የማይቀር ጉዳይ ነው። በሐቅ ለፍትህ ለነፃነትና ለእኩልነት እንጅ በጥላቻ ላይ የተመሰረተ ትግል አልጀመርንም። ለማንም ግለሰብም ሆነ ቡድን ጥላቻ የለንም። ጥላቻ ካንሰር ነውና ወደፊትም በውስጣችን ይኖር ዘንድ አንፈቅድለትም።
አገር ለማፍረስ መዋቅራዊ ድጋፍ ያለውን አካል በቻልነው ልክ እኩይ አስተሳሰቡን ለመዋጋት ግን መቼም ቢሆን አንቦዝንም‼️
የእኔ የትኩረት ማዕከል ከትናንት እስከዛሬ ጥቅሜ ተነካብኝ ብሎ አገር ለማፍረስ በተለያዬ መንገድ በሚንቀሳቀሰው መዋቅራዊ ጉልበት ባለው አካል ላይ ብቻ ነው። መዋቅራዊ ጉልበት የሌለው የትኛውም ግለሰብም ሆነ ቡድን ፈፅሞ አጀንዳዬ ሆኖ አያውቅም። እስካሁን ከማንም ጋር የግል ፀብ ኖሮብኝ በስሜትና ሌላ ሽፋን በመስጠት የምፅፈው አንዳችም ጉዳይ የለም። ማንም ሰው የምፅፈውን የትኛውንም ፅሑፍ ወደራሱ ፍላጎትና ወደሚያስበው ጉዳይ ከአውድ ውጭ እንደፈለገ ሊተረጉመው ግን ይችላል። ለእኔ የሰዎች ትርጉም ጉዳዬ አይደለም። አይሆንምም።
እውነት ላይ እስከቆምን ድረስ የመንጋውን የስሜት ፈረስ ውሸትን አንበርክከን መንጋ አዝማቾችን እርቃናቸውን ማስቀረታችን የማይቀር ጉዳይ ነው። በሐቅ ለፍትህ ለነፃነትና ለእኩልነት እንጅ በጥላቻ ላይ የተመሰረተ ትግል አልጀመርንም። ለማንም ግለሰብም ሆነ ቡድን ጥላቻ የለንም። ጥላቻ ካንሰር ነውና ወደፊትም በውስጣችን ይኖር ዘንድ አንፈቅድለትም።
አገር ለማፍረስ መዋቅራዊ ድጋፍ ያለውን አካል በቻልነው ልክ እኩይ አስተሳሰቡን ለመዋጋት ግን መቼም ቢሆን አንቦዝንም‼️
በአማራ ክልል በሁሉም አካባቢዎች በሕግ ማስከበር ዘመቻ መንግስት ለሐገራቸውና ለሕዝባቸው ሲሉ በጦርነቱ መስዋዕትነት በከፈሉ፣ ሕግና ስርዓትን አክብረው በሚንቀሳቀሱ ፋኖዎች ላይ እስካሁን እጁን አላነሳም። ለሐገር ሉዓላዊነትና ለሕብረተሰቡ ሰላም ዘብ የቆሙና የሚቆሙ ፋኖዎች በመንግሥት ካሉት የፀጥታ አካላት መካከል እንደ አንዱ የሚቆጥራቸው የሕዝብ ልጅ ናቸውና እንደ አይኑ ብሌን የሚጠብቃቸው እንጅ የሚያሳድዳቸው ወይም እርምጃ ሊወስድባቸው የሚችልባቸው አይደሉም። በሕግ ማስከበር ዘመቻው ከመንግሥትና ከሕዝብ ጎን ሆነው ሕገ-ወጦችን በሕግ ጥላ ስር ለማዋል አስፈላጊውን ትብብር እያደረጉ የሚገኙት ፋኖዎች ጭምር መሆናቸው መታወቅ አለበት።
መንግስት ሕግ ለማስከበር እጁን ያነሳው በፋኖ ሽፋን መንግስት በሚያስተዳድረው ለዛውም ከተማ ላይ መንደር ለመንደር ጠብ-መንጃ ስላወዛወዙና በመንግስት መዋቅር ውስጥ ጥቅማቸው የተነካባቸው ሰዎች እግረኛ ወታደር ስለሆኑ ብቻ አንዴ "መንግስት የለም፣ሌላ ጊዜ ደግሞ ቢኖርም የተዳከመ ነውና በትጥቅ እናፈርሰዋለን" እያሉ በመንግሥት ላይ ሕወሓትን በሚያስንቅ ሁኔታ ሲዝቱና ሲፎክሩ በነበሩ ስርዓት አልበኝነት እንዲነግስ፣ ወያኔ እንዲመለስ በወሎ በጎንደር በጎጃም በሸዋ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ኮንትሮባንዲስቶች አፈ-ጦረኞች ላይ ብቻ ነው።
በእነኚህ አፈ-ጦረኞች የወያኔ ፈረሶች ላይ ደግሞ መንግስት ገና "የሕግ የበላይነትን እናስከብራለን" ብሎ የፀጥታ ሐይሉን ለማንቀሳቀስ ትዕዛዝ በሰጠበት ቅፅበት አብዛኞቹ እምጥ ይግቡ ስምጥ ወይም እንደ ደመና ይትነኑ ወይም የሆነ ቦታ ረግተው ይደበቁ የሚያውቅ ቢያውቅም፤ መንጋው ግን ባትሪ ይዞ ፍለጋ ከወጣ ቀናቶች ተቆጥረዋል።
የመንግስትነትን ትርጉም በቅጡ የማያውቁ የመንደር አውደልዳዮች፣ ሳይዋጉ ጦርነት የሰለቻቸውና የተሰለበ አዕምሮና ማንነት ያላቸው ተንበርካኪዎች፣ ከዚህ በፊት በየአደባባዩ ' መንግስት ተብዮው ሆይ! አለቀልህ! አንለቅህም የትም ብትገባ! ' እያሉ ሲያቅራሩ የነበሩ ዘባተሎ ኮንትሮባንዲስቶች ያላቸው የመጨረሻ ምርጫ አገር የሕልውና አደጋ በገጣማት ወቅት የሕዝብን ሰላምና ደህንነት አደጋ ላይ ለመጣል ከያሉበት በፋኖ ስም ተሰባስበው አላስፈላጊ መስዋዕትነት ለማስከፈል የተወራጩ በሙሉ ከወዲሁ ይቅርታ በመጠየቅ ንስሓ ሊገቡ ይገባል። እነዚህ የወያኔ መንገድ ጠራጊ ባንዳዎች ሕዝብንና መንግስትን ይቅርታ ጠይቀው ምህረት እስካላገኙ ድረስ የትም ቢገቡ ወይም ቢጠለሉ ፈፅሞ ከተጠያቂነት ሊያመልጡ የሚያስችል አንዳችስ እንኳን እድል የላቸውም።
በሕግ ማስከበር ዘመቻው እስካሁን መንግስት ያሳደደው ወይም ያፈነው አንድም የሕዝብ ልጅ የሐገር አለኝታ ፋኖ የለም።
መንግስት ሕግ ለማስከበር እጁን ያነሳው በፋኖ ሽፋን መንግስት በሚያስተዳድረው ለዛውም ከተማ ላይ መንደር ለመንደር ጠብ-መንጃ ስላወዛወዙና በመንግስት መዋቅር ውስጥ ጥቅማቸው የተነካባቸው ሰዎች እግረኛ ወታደር ስለሆኑ ብቻ አንዴ "መንግስት የለም፣ሌላ ጊዜ ደግሞ ቢኖርም የተዳከመ ነውና በትጥቅ እናፈርሰዋለን" እያሉ በመንግሥት ላይ ሕወሓትን በሚያስንቅ ሁኔታ ሲዝቱና ሲፎክሩ በነበሩ ስርዓት አልበኝነት እንዲነግስ፣ ወያኔ እንዲመለስ በወሎ በጎንደር በጎጃም በሸዋ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ኮንትሮባንዲስቶች አፈ-ጦረኞች ላይ ብቻ ነው።
በእነኚህ አፈ-ጦረኞች የወያኔ ፈረሶች ላይ ደግሞ መንግስት ገና "የሕግ የበላይነትን እናስከብራለን" ብሎ የፀጥታ ሐይሉን ለማንቀሳቀስ ትዕዛዝ በሰጠበት ቅፅበት አብዛኞቹ እምጥ ይግቡ ስምጥ ወይም እንደ ደመና ይትነኑ ወይም የሆነ ቦታ ረግተው ይደበቁ የሚያውቅ ቢያውቅም፤ መንጋው ግን ባትሪ ይዞ ፍለጋ ከወጣ ቀናቶች ተቆጥረዋል።
የመንግስትነትን ትርጉም በቅጡ የማያውቁ የመንደር አውደልዳዮች፣ ሳይዋጉ ጦርነት የሰለቻቸውና የተሰለበ አዕምሮና ማንነት ያላቸው ተንበርካኪዎች፣ ከዚህ በፊት በየአደባባዩ ' መንግስት ተብዮው ሆይ! አለቀልህ! አንለቅህም የትም ብትገባ! ' እያሉ ሲያቅራሩ የነበሩ ዘባተሎ ኮንትሮባንዲስቶች ያላቸው የመጨረሻ ምርጫ አገር የሕልውና አደጋ በገጣማት ወቅት የሕዝብን ሰላምና ደህንነት አደጋ ላይ ለመጣል ከያሉበት በፋኖ ስም ተሰባስበው አላስፈላጊ መስዋዕትነት ለማስከፈል የተወራጩ በሙሉ ከወዲሁ ይቅርታ በመጠየቅ ንስሓ ሊገቡ ይገባል። እነዚህ የወያኔ መንገድ ጠራጊ ባንዳዎች ሕዝብንና መንግስትን ይቅርታ ጠይቀው ምህረት እስካላገኙ ድረስ የትም ቢገቡ ወይም ቢጠለሉ ፈፅሞ ከተጠያቂነት ሊያመልጡ የሚያስችል አንዳችስ እንኳን እድል የላቸውም።
በሕግ ማስከበር ዘመቻው እስካሁን መንግስት ያሳደደው ወይም ያፈነው አንድም የሕዝብ ልጅ የሐገር አለኝታ ፋኖ የለም።
"መከላከያ ባይኖር እንኳን ሕወሓትን ምስራቅ አፍሪካን በቀናነት እንቆጣጠራለን" እያለ ሲበጠረቅ የነበረ ፤ ጦርነት ምን እንደሆነ፣ ውጊያ ገብቶ የማያውቀው ብቻ ሳይሆን ክላሽ ይዞ ጥይት ወደሰማይ ተኩሶ የማያውቀው ሁሉ ነበር በተለይ ምስጊኑን የአማራን ዲያስፖራ ሜካናይዝድ ጦር እንዳደራጀ አማራ ሆኖ ሲሸልልና ሲያቅራራ የከረመው።
በነገራችን ላይ በየከተማው ለቦርጭ ቅነሳና ለአግላይነት "ቁጭ ብድግ!" ሲሰሩ የነበሩ ሰዎች (ወደበኋላ በወከባ ፋኖ የሆኑ ሰዎች ) መጀመሪያ አካባቢ የአማራ ክልል መንግስት እስከቀበሌ ድረስ ያለ ወጣት እንዲሰለጥን ባስተላለፈው መመሪያ መሰረት እንዲሰለጥኑ ከተሰጠው አቅጣጫ በዲጂታል ወያኔ ፕሮፖጋንዳ መስመር የሳቱ ሰዎች ናቸው ።
እነኚህ በየከተማው "ቁጭ ብድግ" ሲሉ የነበሩ ሰዎች እየቆዩ ሲሄዱ መንደራቸውን ሳይለቁ የትም ግንባር ላይም ሳይሳተፉ የሁሉንም አውደ ውጊያዎችን ድል ያለምንም ጦርነት መቀዳጀት የቻሉ በዓለም ታሪክ የመጀመሪያዎቹ ፈር ቀዳጆች የመሆን እድል ይኖራቸዋል። የሁሉም ጦርነት ድል አድራጊ ነን ባዮቹ አብዛኞቹ "ቁጭ ብድግ!" የሰሩት ራሱ ጦርነቱ ከተጠናቀቀ በኋላ መሆኑንስ ስንቶቻችን እናውቅ ይሆን?!
ስንት ጀግኖች እናት አገራቸውን ለመታደግ የሕዝባቸውን ዘላቂ ሰላምና ጥቅም ለማስከበር ከፍተኛ መስዋዕትነት የከፈሉበትን ጦርነት ማንም የቤት ሙሴ የመንደር አውደልዳይና የባንዳ ባንዳ ከድል ማግስት ነውሩን ጌጥ አድርጎ አርበኛ አርበኛ ሊጫወት ቢሞክርም ዝም ሊባል ግን አይገባውም።
በነገራችን ላይ በየከተማው ለቦርጭ ቅነሳና ለአግላይነት "ቁጭ ብድግ!" ሲሰሩ የነበሩ ሰዎች (ወደበኋላ በወከባ ፋኖ የሆኑ ሰዎች ) መጀመሪያ አካባቢ የአማራ ክልል መንግስት እስከቀበሌ ድረስ ያለ ወጣት እንዲሰለጥን ባስተላለፈው መመሪያ መሰረት እንዲሰለጥኑ ከተሰጠው አቅጣጫ በዲጂታል ወያኔ ፕሮፖጋንዳ መስመር የሳቱ ሰዎች ናቸው ።
እነኚህ በየከተማው "ቁጭ ብድግ" ሲሉ የነበሩ ሰዎች እየቆዩ ሲሄዱ መንደራቸውን ሳይለቁ የትም ግንባር ላይም ሳይሳተፉ የሁሉንም አውደ ውጊያዎችን ድል ያለምንም ጦርነት መቀዳጀት የቻሉ በዓለም ታሪክ የመጀመሪያዎቹ ፈር ቀዳጆች የመሆን እድል ይኖራቸዋል። የሁሉም ጦርነት ድል አድራጊ ነን ባዮቹ አብዛኞቹ "ቁጭ ብድግ!" የሰሩት ራሱ ጦርነቱ ከተጠናቀቀ በኋላ መሆኑንስ ስንቶቻችን እናውቅ ይሆን?!
ስንት ጀግኖች እናት አገራቸውን ለመታደግ የሕዝባቸውን ዘላቂ ሰላምና ጥቅም ለማስከበር ከፍተኛ መስዋዕትነት የከፈሉበትን ጦርነት ማንም የቤት ሙሴ የመንደር አውደልዳይና የባንዳ ባንዳ ከድል ማግስት ነውሩን ጌጥ አድርጎ አርበኛ አርበኛ ሊጫወት ቢሞክርም ዝም ሊባል ግን አይገባውም።
በኢትዮጵያ በተለይም በአማራ ፖለቲካ ለታላቁ የአማራ ሕዝብ ሁለንተናዊ ጥቅም መረጋገጥ፤ ለኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና ክብር መጠበቅ፣ እንደ ቡና በብረት ምጣድ በእሳት የተቆሉ አረፍን ሲሉ በሙቀጫ የተወቀጡ ተመልሰው በበራድ እሳት ላይ የተጣዱና የተንተከተኩ በፖለቲካ ውስጥ የሚሳተፉ ሰዎች ጥቂት ናቸው። ብዙሃኑ ምቾቱን ጠብቆ በተዋበ ሮኮቦት የድግሱ ሰዓት በኩራት እያብለጨለጨ እንደሚወጣ ስኒ (ፍንጃል) ነው።
አሁን ባለው በአማራ ፖለቲካ ውስጥ የሚሳተፈው አብዛኛው በሚባል መልኩ በችግር ወይም በእሳት ወቅት አይጥ እንደዋጠች ድመት ድምፁ የሚጠፋ ነው። በሚያምንበት የፖለቲካ አመለካከት በእሳት መሃል ተፈትኖ ማለፍ ይቅርና የእሳቱ ወላፈን እንዳያገኘው ራሱን የሚያርቅ ነው። አንዳንዱም ነገሮች ሲረጋጉ ወይም ድል ሲገኝ ከያለበት ጎሬ እየወጣ ይሉኝታ ቢስነትን መሳሪያ አድርጎ በነውሩ አጊጦ በሌሎች ድካምና ደም ቆምሮ ሊቆም የሚሞክረው ብልጥ ነን ባይ እዛም እዚህም ማየት የተለመደ ሆኗል።
ሌላው ቢቀር መስዋዕትነት የሚከፍሉ ሰዎች የሚገባቸውን ክብርና ቦታ ሊያገኙ ሲገባ ጭራሽ መስዋዕት የከፈሉለትን አላማ እንደስህተት እንዲቆጥሩ ሊያደርግ የሚችልን ባንዳ መር ግፊቶችን በፅናት ተቋቁሞ ነገሮችን መልክ ለማስያዝና ለአርበኞች የወደፊቱን ጊዜ ብሩህ ለማድረግ መስራት ከሁሉም የሚጠበቅ ነው።
አገሬ ኢትዮጵያ ሞኝ ነሽ ተላላ
የሞተልሽ ቀርቶ የገደለሽ በላ ።
ወይም
የጌሾው ወቀጣ ማንም ሰው አልመጣ
የመጠጡ ጊዜ ከየጎሬው ወጣ! እያልን ዛሬም ሆነ ነገን ዛሬ አድርገን እየቆዘምን ልንቀጥል ይገባል የሚል እምነት የለኝም።
በዘመቻ ሕልውና ወቅት በመንግስታዊ መዋቅሩ ውስጥ በኋላፊነት ያሉ ሰዎች የወያኔን ወረራ በመቃወም፣ ግፉን በማውገዝ፣ የአማራ ሕዝብ በአንድ ልብ ቆሞ አምርሮ እንዲታገል በሜንስትሪም ሚዲያው እየቀረቡ መልዕክት እንዲያስተላልፉ ሲጠየቁ ስልካቸውን እየዘጉ የጠፉ ሰዎች፣ ወያኔ ሊያሸንፍ ይችላል ብለው የጠራ አቋማቸውን ያላንፀባረቁ፣ ድምፃቸውን ያጠፉ አካላት፣ በድል ማግስት መልካቸውን ቀይረው በስመ የውስጥ አርበኛ መምጣታቸው የሚጠበቅ እንጅ የሚያስደንቅ አይሆንም።
ድንኳን ሰባሪነትን እንደክብር፣ የሌሊት ወፍነትን ወይም በአጥር ላይ መንጠልጠልን እንደ እውቀትና ጥበብ እንዲቆጠር የሚያደርግ ሁኔታ ተፈጥሯልና። የሃይል ሚዛኑ ሲታወቅ፣ ድሉ ሲበሰር፣ በስመ የወስጥ አርበኛ ወደፊት የመጡ ሰዎች በአርበኝነትና በአርበኞች መቃ*ብር ላይ ባንዳነትንና ባንዶችን እንዲነግሱ የሚያደርግ ነው።
ባንዳዎች ሲነግሱ በነገሮች ላይ የሚኖራቸው እይታ፣ የሚይዙት አቋምና የሚያደርጉት ትግል ከራሳቸው ሕልውና እና ጥቅም እንጅ ከአገር ሕልውና እና ከሕዝብ ጥቅም አንፃር አይደለም።
የባንዳዎች አስደናቂው ባሕርይ የአሳማነት፣ የአድርባይነትና የክህደት ጥግነታቸውን ለአርበኞች በመስጠት ራሳቸውን እንደአርበኛ እንዲቆጠሩ ለማድረግ መሽቀዳደማቸው ነው። ቀድመው እንዲያ ማድረግ ካልቻሉ ሊሞገሱና ሊነግሱ ቀርቶ በነፃነት በሕይወት ሊመላለሱ የሚችሉበት ዕድልም አነሳ ነውና!
በግልጽ በአማራ ላይ ሂሳብ እንዲወራረድ(የግፍ ግፍ እንዲፈፀም) ኢትዮጵያ እንድትፈርስ ከጠላት ጋር የተባበሩና ክህደታቸውን የገለፁ ሰዎች የጊዜ ጉዳይ እንጅ በመንጋው መወድስ ቢቀርብላቸውም ሆነ ቢነግሱ ያገኙት የስብዕና ግንባታ እንደ እንቧይ ካብ ነውና ማንም ሳይነካው መናዱ አያጠራጥርም።
ዛሬ በእሳት ለተፈተኑ ክብር ለሚገባቸው ሰዎች ክብር መስጠት ክብረ-ቢስ ነውረኞች ነገ ወደፊት መጥተው መንገድ እንዳይዘጉና እንቅፋት ሆነው አላስፈላጊ መስዋዕትነት እንዳይከፍል የሚያደርግ ነው።
አሁን ባለው በአማራ ፖለቲካ ውስጥ የሚሳተፈው አብዛኛው በሚባል መልኩ በችግር ወይም በእሳት ወቅት አይጥ እንደዋጠች ድመት ድምፁ የሚጠፋ ነው። በሚያምንበት የፖለቲካ አመለካከት በእሳት መሃል ተፈትኖ ማለፍ ይቅርና የእሳቱ ወላፈን እንዳያገኘው ራሱን የሚያርቅ ነው። አንዳንዱም ነገሮች ሲረጋጉ ወይም ድል ሲገኝ ከያለበት ጎሬ እየወጣ ይሉኝታ ቢስነትን መሳሪያ አድርጎ በነውሩ አጊጦ በሌሎች ድካምና ደም ቆምሮ ሊቆም የሚሞክረው ብልጥ ነን ባይ እዛም እዚህም ማየት የተለመደ ሆኗል።
ሌላው ቢቀር መስዋዕትነት የሚከፍሉ ሰዎች የሚገባቸውን ክብርና ቦታ ሊያገኙ ሲገባ ጭራሽ መስዋዕት የከፈሉለትን አላማ እንደስህተት እንዲቆጥሩ ሊያደርግ የሚችልን ባንዳ መር ግፊቶችን በፅናት ተቋቁሞ ነገሮችን መልክ ለማስያዝና ለአርበኞች የወደፊቱን ጊዜ ብሩህ ለማድረግ መስራት ከሁሉም የሚጠበቅ ነው።
አገሬ ኢትዮጵያ ሞኝ ነሽ ተላላ
የሞተልሽ ቀርቶ የገደለሽ በላ ።
ወይም
የጌሾው ወቀጣ ማንም ሰው አልመጣ
የመጠጡ ጊዜ ከየጎሬው ወጣ! እያልን ዛሬም ሆነ ነገን ዛሬ አድርገን እየቆዘምን ልንቀጥል ይገባል የሚል እምነት የለኝም።
በዘመቻ ሕልውና ወቅት በመንግስታዊ መዋቅሩ ውስጥ በኋላፊነት ያሉ ሰዎች የወያኔን ወረራ በመቃወም፣ ግፉን በማውገዝ፣ የአማራ ሕዝብ በአንድ ልብ ቆሞ አምርሮ እንዲታገል በሜንስትሪም ሚዲያው እየቀረቡ መልዕክት እንዲያስተላልፉ ሲጠየቁ ስልካቸውን እየዘጉ የጠፉ ሰዎች፣ ወያኔ ሊያሸንፍ ይችላል ብለው የጠራ አቋማቸውን ያላንፀባረቁ፣ ድምፃቸውን ያጠፉ አካላት፣ በድል ማግስት መልካቸውን ቀይረው በስመ የውስጥ አርበኛ መምጣታቸው የሚጠበቅ እንጅ የሚያስደንቅ አይሆንም።
ድንኳን ሰባሪነትን እንደክብር፣ የሌሊት ወፍነትን ወይም በአጥር ላይ መንጠልጠልን እንደ እውቀትና ጥበብ እንዲቆጠር የሚያደርግ ሁኔታ ተፈጥሯልና። የሃይል ሚዛኑ ሲታወቅ፣ ድሉ ሲበሰር፣ በስመ የወስጥ አርበኛ ወደፊት የመጡ ሰዎች በአርበኝነትና በአርበኞች መቃ*ብር ላይ ባንዳነትንና ባንዶችን እንዲነግሱ የሚያደርግ ነው።
ባንዳዎች ሲነግሱ በነገሮች ላይ የሚኖራቸው እይታ፣ የሚይዙት አቋምና የሚያደርጉት ትግል ከራሳቸው ሕልውና እና ጥቅም እንጅ ከአገር ሕልውና እና ከሕዝብ ጥቅም አንፃር አይደለም።
የባንዳዎች አስደናቂው ባሕርይ የአሳማነት፣ የአድርባይነትና የክህደት ጥግነታቸውን ለአርበኞች በመስጠት ራሳቸውን እንደአርበኛ እንዲቆጠሩ ለማድረግ መሽቀዳደማቸው ነው። ቀድመው እንዲያ ማድረግ ካልቻሉ ሊሞገሱና ሊነግሱ ቀርቶ በነፃነት በሕይወት ሊመላለሱ የሚችሉበት ዕድልም አነሳ ነውና!
በግልጽ በአማራ ላይ ሂሳብ እንዲወራረድ(የግፍ ግፍ እንዲፈፀም) ኢትዮጵያ እንድትፈርስ ከጠላት ጋር የተባበሩና ክህደታቸውን የገለፁ ሰዎች የጊዜ ጉዳይ እንጅ በመንጋው መወድስ ቢቀርብላቸውም ሆነ ቢነግሱ ያገኙት የስብዕና ግንባታ እንደ እንቧይ ካብ ነውና ማንም ሳይነካው መናዱ አያጠራጥርም።
ዛሬ በእሳት ለተፈተኑ ክብር ለሚገባቸው ሰዎች ክብር መስጠት ክብረ-ቢስ ነውረኞች ነገ ወደፊት መጥተው መንገድ እንዳይዘጉና እንቅፋት ሆነው አላስፈላጊ መስዋዕትነት እንዳይከፍል የሚያደርግ ነው።