Thomas Jejaw Molla - ቶማስ ጀጃው ሞላ
6.45K subscribers
2.98K photos
370 videos
1 file
31 links
No pain No gain
Download Telegram
በተለያዬ መንገድ የአማራ ፅንፈኛ መስለው ከሚንቀሳቀሱ ብሔርተኞች መካከል ቀዳሚዎቹ ከክልሉ ውጭ ተወለድን የሚሉ ነገር ግን የወያኔ ሰላይ የሆኑ ትግሬዎች(በሐይማኖት ጭምብል የሚንቀሳቀሱም አሉ) እና የማንነት ቀውስ ያለባቸው የወያኔ አላማ አስፈፃሚ ተልዕኮ ተቀባይ አማራ ነን ባይ በነጠላ ማንነት ስሌት አማራ የመሆን ችግር ያለባቸው ሰዎች ናቸው። አሁን በሶሻል ሚዲያ እየተቀነቀነ ያለው የአማራ ብሔርተኝነት አማርኛ ቋንቋ ከመሆኑ ውጭ ወያኔያዊ ነው‼️
አብን በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ በሰጠው መግለጫ ወደ ወያኔያዊ የአማራ ብሔርተኞች ሚሳኤል አስወንጭፏል። የተተኮሰው ሚሳኤል ከፍተኛ ጉዳት ስለማድረሱ ጫጫታውና ሁካታው ምስክር ነው። ተጨማሪውን ደግሞ ነገ ኢትዮ-360 (ግብፅ-360 ) በዛሬ ምናለ ፕሮግራሙ "በምስር ወጥ የተሸጠው አብን" በሚል ርዕሰ ጉዳይ የባጥ የቆጡን እየተነሳ ይተነተናል። እንጀራማ እየመጣላቸው ነው😂

የሐሳብ መስጫ ሳጥኑ ተዘጋብን የሚሉ ሰዎችን ሳስብ ደግሞ ምን ትዝ አለኝ፥ ከሰሞኑ የተደራጁ ጋጠ ወጦች ስድብን ለመግታት ስል፣ ሐሳብ መስጫ ሳጥኔን ስለዘጋሁ በውስጥ መስመር የስድብና የእርግማን ናዳውን በላይ በላይ ያጎርፉታል።

ታዲያ ከጋጠ ወጦቹ መካከል አንዱ ምን ቢለኝ ጥሩ ነው " አይ ቶማስ የሐሳብ መስጫውን የዘጋኸው ሐሳብ ስለምትፈራ ነው አይደል!?ካለኝ በኋላ፥ ቀጥሎ አንተ ሽን*ታም፣ የአብይ አህመድ ውታፍ ነቃይ፣ የኦሮሙማ ተላላኪ፣ ተጨማሪ ነውረኛ ስድቦችን" ያጎረፈልኝ ነገር ነው።

ቤትህ ገብቼ ካልሰደብኩህ የሚል ያፈጠጠ ነውረኛ የተፈጠረ ያለበት ሁኔታ ነው ያለው😂

የግርጌ ማስታወሻ በሐሳብ ልዕልና የምታምኑ ለራሳችሁ ክብር ያላችሁን ሰዎች ፈፅሞ አይመለከትም‼️
ወያኔያዊ የአማራ ብሔርተኛ ለራሱ ፍፁም ክብር የሌለው ምን ያህል ነውረኛ እንደሆነ ለማሳየት ነበር አብን የዘጋውን የሐሳብ መስጫ እኔ ከፍቼ የስድብ ሜኑው ተገልጦ እንዲታይ ያደረግኩት። እንደተለመደው ጋጠወጦቹ ፌስቡክ ስለሆነ ያሻቸውን ስድብ ነውረኝነት ለመግለፅ ችለዋል።

በነገራችን ላይ በፌስቡክ ከሚሳደበውና ከሚዝተው ውስጥ አንድም ሰው መሬት ላይ ፌስቡክ ላይ ያለው አቋም መድገም አይችልም። ከፌስቡክ ጀግኖችና ተሳዳቢዎች መካከል መሬት ላይ ፊት ለፊት ወይም መንገድ ላይ እንዳጋጣሚ ብታገኛቸው ቀድመው ራሳቸውን ለመደበቅ የሚጥሩ ናቸው። አንተ ሳታውቃቸው በፌስቡክ ስራቸው ። ፌስቡክ ላይ ከሚያሽላላው ውስጥ መሬት ላይ አንድም ደፋር ጀግና አታገኝም። ሲጀመር ጀግና አይዝትም። ባገኘው ሚዲያ ሁሉ አይለፈልፍም። ጀግና የማድረግ አቅም ያለው ስለሆነ ጀግንነቱን የሚገልጸው በተግባር ነው። ላደርግ ነው ብሎ ሳይሆን አድርጎ ነው ስራዬ ምስክር ይሁን የሚለው።

ወያኔያዊ የአማራ ብሔርተኛ ፌስቡክ ላይ እንዴት ቶማስ ላይ እርምጃ የሚወስድ አንድ ሰው ይጠፋል ይላል እንጅ ራሱ እርምጃ ለውሰድ አይሞከርም ቀርቶ ሊያስበው የማይችል የቦቅቧቃ ጥርቅም ነው።

የአየር ላይ ወከባውን ያዬ ሰው ግን አቤት በቀጣዩ ቀን በሕይወት ስለመኖሩ ብቻ ሳይሆን አስከ*ሬኑ ስለመገኘቱ ሁሉ እስከመጠራጠር ይደርሳል። ወያኔያዊ የአማራ ብሔርተኛ ምኞት እንጅ የማድረግ አቅም የለውም። የማድረግ አቅሙ በሌሎች ትክሻ ላይ የተንጠለጠለ ነው። ዘወትር ሌሎች ያደርጉለት ዘንድ የሚወተውት እንጅ በራሱ አንድ ኢንች የሚራመድ አይደለም። ይህ ባይሆን እንደምኞቱማ እስካሁን በስንት ሰው ላይ እርምጃ መውሰድ በቻለ ነበር። ጠጋ ብሎ ነገር ከመለኮስ ሐሜት ከማመላለስ ያለፈ ፈፅሞ አቅም የሌለውና መቼምም የማይኖረው የቡታ ሰዳጅነት ሚና ብቻ ያለው ስብስብ ነው።
#ማስታወቂያ

የሀገር መከታና አለኝታ ለሆነው መከላከያ ሰራዊት አባል ለመሆን መመዝገብ ለምትፈልጉና መስፈርቱን ለምታሟሉ ወጣቶች ምዝገባ ተጀምሯል። እንደሚታወቀው ሀገራችን ከገጠማት የህልውና ችግር ጎትቶ ያወጣት ጀግናው መከላከያ ሰራዊታችን ነው። ስለሆነም ተቋሙን ለማዘመን እና ለመገንባት ምዝገባ አስፈላጊ ሁኖ ተገኝቷ። መከላከያን መቀላቀል ክብር ነው፤ለአገር ዘብ መቆም ነው።

#የመመልመያ_መስፈርቶች
✔️ከዚህ በፊት በማንኛውም የውትድርና መስክ ያልተሳተፈ/ያልተሳተፈች/
✔️ አድሜው 18-24 የሆነ ወይም የሆነች
✔️ከ10ኛ ክፍል በላይ የሆነ የሆነች
✔️ ከማንኛውም ሱስና ወንጀል ነፃ የሆነ የሆነች
✔️ ትዳር የሌለውና በውትድርና ህግና ደንብ ለመሰልጠን ፍቃደኛ የሆነ የሆነች በሙሉ መመዝገብ ይችላሉ ።

➤ምዝገባው ከግንቦት 16/09/2014 ዓ.ም እሰከ 30/09/2014 ዓ.ም የሚቆይ ሲሆን በባህር ኃይል ፣ በአየር ኃይልና በእግረኛ ወታደር መመዝገብ የምትፈልጉ በአካባቢያችሁ በሚገኙ የቀበሌ ፅ/ቤት የወረዳ ሰላምና ደህንነት ፅ/ቤት ሂዶ መመዝገብ ይችላል ።
አዲሱ የብዓዴን ትርጉም ፦

፩) ብአዴን እየተባለ የሚብጠለጠለው ብአዴንን ተሻግሮ ብልጽግና የሆነውና ሐገርና ሕዝብን በታማኝነትና በሐቀኝነት እየመራ ያለው አካል ነው።

፪) ብአዴን የሚለው የብአዴን መፍረስ የእግር እሳት ሆኖበት ዛሬም የሚቆጨው ብልጽግና ውስጥ ያለ አፍቃሪ ትህነግ የሆነው ኃይል ነው። ይኼው ነው!
የዛሬ መሠረታዊ ወታደር የነገ ኮ/ል ጀኔራል አገር መሪ ይሆናል። የኢትዮጵያ አለኝታዎችን መቀላቀል ራስንም ሆነ ሐገርን ማስከበር ጀግንነትም ነው።

መከላከያ ከአራት በላይ ባሉት ዘመናዊ ክፍሎች
1. የምድርጦር (ከእግረኛ እስከ መካናይዝድ)
2.የባህር ሃይል
3. የአየር ሃይል
4. የምህንድስና ኢንተለጀንስ ዘርፎች

ከእነዚህ ውስጥ በመደበኛው የምድር ሃይልና በአየር ሃይልም ምልመላና ምዝገባ ተጀምሯልና ዕድሉን እንጠቀም!

#የመመልመያ_መስፈርቶች
✔️ከዚህ በፊት በማንኛውም የውትድርና መስክ ያልተሳተፈ/ያልተሳተፈች/
✔️ አድሜው 18-24 የሆነ ወይም የሆነች
✔️ከ10ኛ ክፍል በላይ የሆነ የሆነች
✔️ ከማንኛውም ሱስና ወንጀል ነፃ የሆነ የሆነች
✔️ ትዳር የሌለውና በውትድርና ህግና ደንብ ለመሰልጠን ፍቃደኛ የሆነ የሆነች በሙሉ መመዝገብ ይችላሉ ።

➤ምዝገባው ከግንቦት 16/09/2014 ዓ.ም እሰከ 30/09/2014 ዓ.ም የሚቆይ ሲሆን በባህር ኃይል ፣ በአየር ኃይልና በእግረኛ ወታደር መመዝገብ የምትፈልጉ በአካባቢያችሁ በሚገኙ የቀበሌ ፅ/ቤት የወረዳ ሰላምና ደህንነት ፅ/ቤት ሂዶ መመዝገብ ይችላል ።
የሕግ ማስከበር ዘመቻው እየተካሄደ ያለው በሐገር ደረጃ ነው። በደቡብ፣ በኦሮሚያ፣ በቤንሻንጉል፣ በአማራ ክልል...ሐገር ለማፍረስ የባንዳ ባንዳ ሆነው ከጠላት ወያኔና ከውጭ ባዳ ጠላቶች ጋር በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ግንኙነት በመፍጠር በትጥቅም ሆነ ያለትጥቅ በቡድንም ሆነ በተናጠል በሕገ-ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውር ላይ በተሰማሩ ኮንትሮባንዲስት ፀረ-ሰላም አካላት ላይ መንግስት እርምጃ መውሰድ ከጀመረ ቀናት መቆጠር ጀምረዋል።

የሕግ-ማስከበር እርምጃውን ተከትሎ በወንጀል የተጠረጠሩ ሰዎች በሕግ-ጥላ ስር በመዋል ላይም ይገኛሉ።

መንግስት ሕግ የማስከበር እርምጃ እየወሰደ ከሚገኘው አንዱ የአማራ ክልል ነው። በወንጀል በሚጠረጠሩ አካላት ላይ በክልሉ በሁሉም አካባቢዎች እርምጃ የመውሰድ እርምጃው ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ አሁንም ተጠናክሮ መቀጠሉን መረጃዎች ያመለክታሉ።በክልሉ ሕግ የማስከበር እርምጃ ያልተገባበት አንድም አካበቢ የለም።

ነገር ግን በአማራ ስም በፌስቡክ የሚንቀሳቀሰው የወያኔ ዲጂታል ሰራዊትና በወንጀል የሚጠረጠሩ አካላት በመቀናጀት የሕግ-ማስከበር ዘመቻው በጎጃም አካባቢ ብቻ እንደሚካሄድ አድርጎ ለማቅረብ የሚያሳየው መወራጨት የሚያስደንቅ ነው። እርግጥ ነው ችግሩ መረጃውን ወይም አጀንዳውን እንደወረደ የሚውጠው እንጅ እነሱማ አላማቸው በመሆኑ ለምሽግነት የሚያገለግላቸውን ሁሉ ይጠቀማሉ።
ማንም ሊያውቀው የሚገባው ነገር ቢኖር ግን በሌሎቹ አካባቢዎች በወንጀል ተጠርጥረው በሕግ-ጥላ ስር ለሚውሉ ሰዎች ድምፅ የሚሆናቸው ፌስቡከር ስለሌላቸው እንጅ መሬት ላይ ያለው ሐቅ ፌስቡክ ላይ እንደሚናፈሰው አይደለም ብቻ ሳይሆን ፍፁም የተገላቢጦሽ ነው። ስለሆነም ወያኔያዊ የአማራ ብሔርተኞችን የጩኸት አጀንዳዎችን አላማ ልናጤን ሁሉንም የጠላት ወያኔ አጀንዳዎችን እንደወረደ ከመዋጥ ተቆጥበን ነገሮችን በስክነት ግራ ቀኙን ልንመረምርና ከአላስፈላጊ መስዋዕትነት ራሳችንን ልንጠብቅ ይገባል። ይኼው ነው‼️
ለእናት ኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና ነፃነት መከበር፥ ለሕዝቦቿ ዘላቂ ሰላምና ጥቅም መረጋገጥ፥ ያለ እረፍት በሐሩርና በቁሩ ዳገት እየወጣ፣ ቆልቁለት እየወረደ፣ ጋራ ሸንተተር እያቆራረጠ፣ እንደ አንበሳና ነብር ሆኖ ለሚዋጋውና በቃላት ለማይገለፀው መስዋዕትነቱና ጀግንነቱ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊታችን ክብርና ምስጋና ይገባዋል‼️

እናንተ የኢትዮጵያ ሕልውና የመጨረሻው ምሽግና አለኝታ ናችሁና እንወዳችኋለን! እንኮራባችኋለንም‼️
በአማራ ክልል ከወያኔ ጋር ከነበረው ጦርነት ጋር ተያይዞ ሕገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴ ስለተስፋፋና ኮንትሮባንዲስቶቹ ለተጨማሪ የጥፋት አላማ ራሳቸውን እያደራጁ መምጣታቸውን ተከትሎ በሕዝቡ ተደጋጋሚ ጥያቄና ግፊት መንግስት በጀመረው ሕግ የማስከበር ዘመቻ በወንጀል የሚጠረጠሩ ግለሰቦች በሕግ-ጥላ ስር እየዋሉ ይገኛሉ።
ወያኔ አላማውን ለማስፈፀም በሳይበር በአማራ ማልያ እንዲጫወቱ ባሰማራቸው ጭፍሮቹና በወንጀል ተጠርጥረው ከሚፈለጉ የግብር ልጆቹ ጋር በመቀናጀት ነጋ ጠባ እንደሚለፈልፈው በጎጃም አካባቢ ብቻ ሳይሆን በሁሉም የአማራ አካባቢዎች ማለትም በጎንደር በወሎ በሸዋ ጭምር ነው የሕግ ማስከበር እርምጃ እየተወሰደ የሚገኘው።

በሕግ ማስከበሩ በወንጀል የሚጠረጠሩ ግለሰቦች ቁጥራቸው የት ቀበሌ ወይም አካባቢ ላይ በርከት አለ ወይም አነሰ የሚል የወንጀል ተጠርጣሪ የምጥጥን ስሌት ወይም ጥያቄ የሚያሳስብ አይደለም። አይሆንምም። በየትኛው ቀበሌ አካባቢ ብሔር አገር ወንጀለኛ ቦታ የለውም። ወንጀለኛን ጫካ ወይም ዱር ሊደብቀው ይችል ይሆናል እንጅ ሕዝብ ሊደብቀው አይችልም። የግለሰቦችን ወንጀል ሊረከብ ወይም ሊጋራ የሚችል ማህበረሰብ እስካሁን አልተፈጠረም፤ለወደፊትም አይፈጠርም።

የአማራ ሕዝብ ከመንግስት ቅን ፍርድን ይፈልጋል። ይጠብቃል። ለሕግና ስርዓት ተገዥ ሆኖ ለዘመናት የኖረ ስለ ስነ-መንግስት ብዙ ማለት የሚችል፣ በሕግ አምላክ ብሎ ሕግ የሚያስከብር ፍትህ አዋቂ ሕዝብ ነው። አማራ ያለ ሕግና ስርዓት የመኖር ልምምድ የሌለው ሕዝብ ነው። በፍርድ ከሄደች በቅሎዬ ይልቅ ያለፍርድ የሄደች ጭብጦዬ ያንገበግበኛል ብሎ የፍትህን መስፈን አጥብቆ የሚሻ መሆኑን ሁሉም የሚያውቀው ነው። ስለሆነም የአማራ ሕዝብ ወንጀለኞች ወደሕግ እንዳይቀርቡ የሚከራከር ሳይሆን ወንጀለኞችን አሳልፎ ለሕግ የሚሰጥና ራሱንም ከደሙ የሚያነፃ ነፃ የሆነ ሕዝብ ነው። እንደ አብራኩ ክፋይ ተመልክቶ ወንጀለኛን ለመደበቅ የመሞከር መሰል ልምምድ የለውም።

አንድ በማንነቱ አማራ ወይም ኦሮሞ የሆነ ማፍያ ከሲሲሊ ወይም ከየመን ከሐውቲ አማፂያን በሕገ-ወጥ የጦር መሳሪያ ወይም በእፅ ማዘዋወር አብረው ሊሰሩ ይችላሉ። ለማፍያዎች አገር ወይም ብሔር ለተጨማሪ ጥቅም ማራመጃ ወይም ለጥቅማቸው ማስከበሪያ ማለቃቀሻና ማስለቀሻ ከመፈለግ ያለፈ ጉዳያቸው አይደለም።
"አማራ የሕልውና አደጋ ውስጥ ነው፤ ኦሮሙማ እስካለ ድረስም አማራ እረፍት ሊኖረው አይችልምና ፋኖን አጠናክረን በማደራጀት ኦሮሙማን ልኩን ማሳየት ይኖርብናል" የሚል የዘወትር አጀንዳ የነበረው፣ ኑሮውን ከሐገር ውጭ ያደረገና ራሱን እንደ አማራ ወሳኝ ተቆርቋሪ አድርጎ የሚገልፀው ነገር ግን "እስኪ በቪዲዮ ኮል እናውራ" ስለው ዛሬ ነገ እናወራለን እያለ ከድምፅ ያለፈ ነገር ሳናወራ ከ3 ዓመት በላይ እሱም ለእኩይ ዓላማው ለመጠቀም እኔም ማን ይሆን አላማው ምን ቢሆን ነው በሚል ግንኙነቴን ሳላቋርጥ ቆየሁ።

  በጦርነቱ ወቅት "ይህ ጦርነት አማራን አይመለከተንም፤ የብአዴን ነው እናንተ ምን ቤት ናችሁ?" አለኝ። ሰውዬው ራሱን እንደ አማራ ወሳኝ ተቆርቋሪ ያደረገና የአማራ ጉዳይ concern እንደሚያደርገው አማራ ሆኖ የሚተውን ስለነበረ  "ወያኔ በአዋጅ "ከአማራ ጋር ሂሳብ አወራርዳለሁ" የሚለው ካልተመለከተህ አንተ ምኑን አማራ ሆንክ ከአንተስ ጋር ምን አለኝ ወደሚመስሉህ ተጠጋ" ስለው ምን ቢለኝ ጥሩ ነው? "የትግራይ እናቶች አልቅሰው አይቀሩም፤ ትግሬ ኮዝ አለው እንደአንተ ያለ እባብ ባንዳ ብልፅግናን ለማዳን የአብይን ስልጣን ለማስጠበቅ አማራ መስለህ ብአዴን በሚመራው ጦርነት ለመዝመትና ሌሎችን ለማዝመት የአገኘሁ ተሻገርን የክተት ጥሪ መቀበልህ ነገ ዋጋ ያስከፍልሃል፤TDF ን አዲስ አበባ ከመግባት ሊያስቆመው የሚችል ምድራዊ ሃይል የለም፤ ሽንታ*ሙንና የኦነግን መከላከያ ሰራዊት ተብዮውን የአማራ ሕዝብ ደጀን እንዲሆን የምታደርገው ስራም አይሳካም፤ አብይ አህመድም ይፈረጥጣል፤ አንተ ቅማንቴ ከመሰሎችህ ጋር የTDF ቁርስ ትሆናላችሁ" አለኝ። ተጨማሪ ቀፋፊ የተለመዱ ስድቦችን አላካተትኩም፤ቀንሻለሁ😂

በዚህ የማንነት መገለጥ የደም ፍላት ንግግር ያኔም ሆነ እስካሁን በፍጹም አልተገረምኩበትም።
እስከ ድምፅ ድረስ የሚያወሩ ሌሎች አማራ የሚመስሉ በተለያዩ አገራት የሚኖሩ የወያኔ ሰላዮችንና በግልጽ በሚታወቅ ማንነት በሐይማኖት ጭምብል ጭምር ከአማራ ክልልና ከክልሉ ውጭ ተወለድን የሚሉ የወያኔ ምልምሎች መኖራቸውን አውቅ ስለነበር ጨጓራው መላጡን በሚያሳየው የሰውየው የለየለት የንዴት ድንፋታ አልደነቀኝም። ደስታዬን መጨመሩን ግን መካድ አይቻልም።

የአማራን ፖለቲካ ዲጂታል ወያኔ በከፍተኛ ብቃት ለራሱ አላማ በራሱ መስመር በከፍተኛ ሁኔታ አቧራው ጨስ እያለ ሲያስጨፍረው የከረመ ሲሆን አሁንም ሳይበሩን በመቆጣጠር ለተጨማሪ ጥፋቶች ሊቀጥል ይችላል።

የወያኔ የሚዲያ hegemony አስተሳሰብን በመበረዝ በአማራም ሆነ በአገር ላይ ብዙ ጉዳቶችን ሊያደርስ ስለሚችል በተደራጀ አኳሃን መመከትና እኩይ አላማውን ማምከን ያስፈልጋል።
በስልክም ሆነ በአካል ወይም በሚዲያ ዘመቻ በመከላከያ ወይም በአማራ ልዩሃይል ውስጥ ያሉ አባላትን በተለያዬ መንገድ ለማስኮቦለል ጦሩን ለማዳከምና ለመበተን በተለይ መንግስት በሚያስተዳድረው ግዛት ውስጥ በሚኖር በየትኛውም አካል ላይ መንግስት የማያወላዳ እር*ምጃ መውሰድ ይገባዋል። በየትኛውም ዓለም ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ሰፍኖባቸዋል ተብሎ በሚለፈፍባቸው አገራትም ቢሆን መከላከያ ሰራዊትን መንካት ለማንም የተፈቀደ ጉዳይ አይደለም። የአገር መከላከያ ሰራዊት ቀይ መስመር ነው።

በውጭ ባዳና በውስጥ ባንዳ ተመልምለው አገር የማፍረስ እንቅስቃሴ ላይ የተሰማሩ ሰዎች ይቅርና አገር ለማዳን እንሰራለን የሚሉ ሰዎችም ቢሆኑ የአገር መከላከያ ሰራዊትን በተመለከተ በስመ ተገቢ ትችት አፍራሽ የጥፋት አጀንዳዎች ይሰራጩ ዘንድ ሊፈቀድለት አይገባም። መከላከያን ለማዳከም ለመበተን መንቀሳቀስ በራሱ ወያኔነትም ነው።

አንድ ወታደር ከመከላከያ ሰራዊቱ ከድቶ መንግስት ያስታጠቀውን መሳሪያ በመያዝ በሕገ-ወጥ መንገድ በቡድን ከተማ ላይ መንደር ለመንደር በነፃነት ሊንቀሳቀስ አይችልም። በማናቸውም ሁኔታ በየትኛውም አገር የመንግስትን መሳሪያ በመሸጥ ከሰራዊቱ መክዳት አይፈቀድም። በሐገር ክህደት የሚያስጠይቅ ወመኔ ወንጀልም ነው። ከዚህ ቀደም የወያኔ የጦር አመራሮችን ጨምሮ እነ ጌታቸው ረዳ እየደጋገሙ ሲናገሩት የነበረው "የኢትዮጵያን መከላከያ ሰራዊትን ማዳከም ተቀዳሚ ስራቸው መሆኑን ነው። አሁን ላይ ያለው ሁኔታ በደንብ የሚገለጥልን የወያኔ ሰዎች ንግግርን መልሰን ማስታወስ ከቻልን ነው።

መከላከያ ወይም ልዩሃይሉ በተለያዩ ምክንያቶች ተዳክሞ ካልተበተነ ወይም የመዋጋት ሞራሉ ካልፈዘዘ መከላከያ አሁን ላይ ባለው አቅም በግንባር ጦርነት ወያኔ ሊያንበረክከው ይቅርና ሊደፍረው የሚችል ሃይል አይደለም።

ስለሆነም መንግስት ከመከላከያና ከልዩ ኃይል የጠላት አጀንዳን በመስማት ከሰራዊቱ ከድቶ ወደከተማ በሚመጣና መንደር ለመንደር እየተዟዟርኩ የሕዝብን ሰላም እነሳለሁ በሚል በማንኛውም ወታደር ላይ ምንም ዓይነት ምህ*ረት የሌለው እርም*ጃ ሊወስድ ይገባዋል። ቀይ መስመሮች በመንግስት ሊከበሩና መንግስትም ሊያስከብራቸው የግድ ይለዋል‼️
የቆምንበት መሰረቱ እውነት ከሌለው፣ የምንታገለው ለነፃነት፣ ለእኩልነትና ለፍትህ ካልሆነ በስተቀር በተቃራኒው መንገድ የቆምን እንደሆነ ለጊዜው በመንጋ ጭብጨባ ልክ የሆንንና የተሳካልን እንምሰል እንጅ የተከተልነው የተሳሳተ መንገድ ስለሆነ ገደል ገብተን አወዳደቃችንን መክፋቱ የማይቀር ነው።

ከትዕቢት በመነጬ ንቀት፣ ጥላቻ በወለደውና በግብታዊነት በተመራ ትግል ማንም አወዳደቁን ሊያከፋው ካልሆነ በስተቀር ድልን ሊቀዳጅበትና መጨረሻውን ሊያሳምርበት የሚችልበት የስኬት ወይም የአሸናፊነት መንገድ ሆኖ ሊመረጥ የሚችል አይደለም። ሱሳይድም ነው።
የአማራ ክልል መንግስት ሕዝባዊ ቁጣውን ለማስቀየስ፣ አማራውን ለማዘናጋትና ለማታለል ሆንብሎ እስከዛሬ አድርጎት የማያውቀውን በመቶዎች የሚቆጠሩ ትራክተሮችን በመግዛት ለገበሬዎች መስጠት መጀመሩ እንደቀላል ሊታይ አይገባም።

አማራ ሆይ! በመቶዎች ለሚቆጠሩ ለኦሮሙማ ትራክተሮች ብለህ ትግልህን እንዳታቆም። ለአፍታም እንዳትዘናጋና እንዳትሸወድ። የአብይ አህመድ የኦሮሙማ መንግስት በዚህ ወቅት ትራክተር ለአማራ ገበሬዎች የሚሰጥበት ሴራ ካልገባህ አንተ ሆድ አደርነትህንና የብልጽግና ተላላኪነትህን አያረጋግጥም መሆንህም ሊታወቅ ይገባል። አማራዬ ንቃ!

ወያኔያዊ የአማራ ብሔርተኞች!
በሁሉም የአማራ አካባቢዎች የሕግ ማስከበር ዘመቻው በአማራ ክልል ልዩሃይል፣ሚሊሻና ፋኖ ቅንጅት በሕዝቡ የተደጋገመ "የሕግ ይከበርልን ጥያቄ" መሰረትና ከፍተኛ ትብብር እየተመራ ነው። በዚህ የሕግ ማስከበር ዘመቻ ከሕዝቡ ፍላጎት ወይም የአገራቸውን ሉዓላዊነት ለማስከበርና የሕዝባቸውን ዘላቂ ሰላምና ጥቅም ለማረጋገጥ በሚታገሉ፥ ነፍጣቸውን ለወያኔ ባነሱና በሚያነሱ፥ በባለፈው የሕልውና ጦርነትም ግንባር ገብተው በምሽግ ውለው አድረው በተዋደቁ በሕገ-ወጥ እንቅስቃሴ ላይ ባልተሰማሩ፣ ከተማ ተቀምጠው መንግስትን በትጥቅ ትግል አንዴ እናፈርሳለን ሌላ ጊዜ ላይ ደግሞ መንግስት የለም እያሉ ስርዓት አልበኝነትን ለማንገስ ጠመንጃ እያወዛወዙ ደፋ ቀና በማይሉ በተቧደኑም ሆነ በተናጠል በማይንቀሳቀሱ አካላት ላይ መንግስት እርምጃ እየወሰደ ስለመሆኑ የሚያመላክት የተረጋገጠ አንድም መረጃ በትም አካባቢ ስለመኖሩ እስካሁን አላገኘሁም። በሬ ወለደ ወሬውን ግን እነ ስማ በለውና ፍለጠው ቁረጠው የግጭት ጡረተኞች እንደፈለጉ አላጧጡፉትም ማለት አይቻልም።

የአማራ ልዩሃይልን መለዮ የለበሱ አንዴ ከኦሮሚያ ክልል መጣ የሚባል ልዩሃይል ሌላ ጊዜ ደግሞ ከፌደራል የተላከ ኦሮሞኛ ተናጋሪ አፋኝ ሃይል እየተባለ ተደጋግሞ በማህበራዊ ሚዲያው የሚነዛው ወሬም ፍፁም ነጭ ውሸት ነው።

የኦነግ ወታደር የአማራ ክልል ልዩሃይልን መለዮ ለብሶ እየተንቀሳቀሰ ነው የሚለው ለአማራ ክልል ልዩሃይል ትልቅ ንቀት ከመሆኑም ባሻገር ልዩሃይሉ ከሕዝብ ለመነጠልና እንደጠላት ተቆጥሮ ጥቃት እንዲደርስበት የታለመ ሴራ ነው።

ወያኔ ጦርነት ከመክፈቱ በፊት መንግስት በሚያስተዳድረው ክልል ቀድሞ የፀጥታ ሃይሉን ትኩረት ለመበታተንና ለማዳከም በሕገ-ወጥ መንገድ የሚንቀሳቀስን ኮንትሮባንዲስት ስርዓት ለማስያዝ የአማራ ልዩሃይል ፋኖና ሚሊሻ የሚያንስ ሆኖም የሌላ ክልልን እገዛ እስከመጠየቅ ወይም ማዕከላዊ መንግስቱ ተርበትብቶ ሃይል እስከመላክ የሚያደርሰው ደረጃ ላይ አይደለም። ፈፅሞም አይሆንም። የአማራ ልዩሃይል እንኳን በሕዝብ ፍላጎትና ትብብር እየተመራ ይቅርና ብቻውን ቢቆም እንኳን ሕገ-ወጦችን ስርዓት ለማስያዝ አቅም የሚያጥረው ወይም የሚቸገር ሃይል አይደለም። መቼምም አይሆንም!

ማንም ከሕግ በላይ አይደለም። ሁሉም በሕግ ፊት እኩል ነው። የሕግ የበላይነት መስፈን ለሁላችንም ነው። ሕግ አይከበርም የሚለው ደግሞ ሕገ-ወጥ የሆነው ብቻ ነው‼️
ክብር ከጥቅምት 24 የሰሜን ዕዝ መጠቃት ጀምሮ ከፍተኛ መስዋዕተነት ለእናት ኢትዮጵያ እየከፈለ ለሚገኘው ለጀግናው የአማራ ልዩሃይል ይሁን!
በአማራ ላይ ሂሳብ እንዲወራረድ (የግፍ ግፍ እንዲፈፀም) ኢትዮጵያ እንድትፈርስ ያሴሩና የሰሩ ሰዎች፥ እኛ በሕይወት ቆመን እየሄድን በኢትዮጵያ ሰማይ ስር ይነግሱ ዘንድ ፈፅሞ ልንፈቅድላቸው አንችልም። ምን አልባት ንስሓ ከገቡና የኢትዮጵያን ሕዝብ በአደባባይ ይቅርታ ከጠየቁ የማርያም መንገድ ሊያገኙ ይችላሉ። እንጅ ባንዳ ነግሶ አርበኛ እንዲንኳሰስ ሁኔታዎች ይመቻችላቸው ዘንድ ፈፅሞ በየትኛውም መንገድ ቆመን ልንመለከት ወይም ልንተባበራቸው አንችልም። ይኼው ነው‼️