Thomas Jejaw Molla - ቶማስ ጀጃው ሞላ
6.45K subscribers
2.98K photos
371 videos
1 file
31 links
No pain No gain
Download Telegram
በወሎ በደብረዘቢጥ በወሎ ግንባር በማይጠምሪ በጭና በጨው በር በማይጠብሪ ተከዜ ግንባር ጦር እየመራ ታላቅ ጀግንነት የፈፀመው ጀግናው ኮማንዶ ሀብቴ ወልዴ በጀግናው ጀኔራል አበባው ታደሰ እጅ የወርቅ ሜዳሊያ ተሸልሟል።

ሻለቃ ሀብቴ በደብረዘቢጥ በነበረው ውጊያ የጀግናው ቻላቸው እንየውን መሰዋት ተከትሎ ጦሩ የመፈታት ሁኔታ ውስጥ ሲገባ እስከመጨረሻው ያሳየው የመፋለም የጀግንነት ጥግ መቼም ሊረሳ የማይችልና ፍፁም ልበ ሙሉነቱን ያስመሰከረበት ነበር።

አርበኛ ሀብቴ ወልዴ ፍፁም ወታደራዊ ዲስፕሊን ያለው በጦርነቱ ወቅት በምሽግ በዱር በገደሉ በከፍተኛ ተጋድሎ ያሳለፈና የተሰጠውን ግዳጅ በጀግንነት የተወጣ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ ነው።

ለአንተና በስርህ ሆነው አማራ ሂሳብ አይወራረድበትም ኢትዮጵያም አትፈርስም ብለው ከፍተኛ መስዋዕትነት ለከፈሉ ጀግኖቻችን መቼም የማይቀየር ክብርና ምስጋና አለን‼️
እንኳን ደስ ያለን እንኳን ደስ ያላችሁ !!!
»»»»»»»»»»»»»»»»»»»»»»»»»
የባለሽርጦቹ የጦር መሪዎች
1/ ጀኔራል ሀሰን ከረሙ
2/ ሻለቃ ደምሌ አራጋው አህመድ
3/ የጋፍራው አርበኛ ንጋቱ

የአንደኛ ደረጃ የወርቅ ሽልማት ተበረከተላቸው።

ጀኔራል ሃሰን ከረሙ ሀዘን ላይ በመሆናቸው ግስላው ደምሌ አራጋው ሽልማቱን ተረክቧል።

ዘመን ተሻጋሪው
ወያኔ በአደባባይ በአዋጅ "ከአማራ ጋር ሂሳብ አወራርዳለሁ፤ ኢትዮጵያን አፈርሳለሁ!" ብሎ ጦርነት ሲከፍት "ጦርነቱ አይመለከተንም፣መንግስትም የለም፣ መከላከያም ፈርጣጭ ነው" እያሉ ለወያኔ አጀንዳ ሲያሻሽጡና የወያኔን አላማ ለማሳካት ሲተጉ የነበሩ ፤ ምሽግ ይዘው መዋጋት ይቅርና ምሽግ ባለበት ቀጠና አልፈው የማያውቁ፤ሕገ-ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውር ላይ ተሰማርተው የነበሩ ኮንትሮባንዲስቶች፤ ውሸታቸውን "አንድ ሻለቃ ብርጌድ ፋኖ እየመራን በዚህ ግንባር በዛኛው ግንባር ነን" እያሉ ከአንዱም ያልነበሩና ባሩድ ያላሸተቱ እምድጃ ዳር ተቀምጠው የምናብ ምሽግ ሰባሪዎች፤ ወታደራዊ ዲስፕሊን የሌላቸው እንደልቡ የውጊያ እንቅፋት መከላከያ ሰራዊትን ተሳዳቢዎች፤ በፕሮፖጋንዳ ለሰፊው ሕዝብ በተለይ መረጃ ለሌለው ዲያስፖራ ብአዴን በሚመራው ጦርነት አንሳተፍ ይሉ የነበሩ ነገር ግን መሬት ላይ ደግሞ እንዋጋለን ብለው ከመከላከያ የጦር መሳሪያ (ከቡድን መሳሪያ በ ሺ እስከሚቆጠር የጥይት ፍሬ እየተቀበሉ ከአንደኛው ግንባር ሾልከው ይጠፉ የነበሩ ይህ አልበቃ ብሏቸው ለተጨማሪ የሕገ-ወጥ ንግድ በሌላ ግንባር ደግሞ መልሰው የሚሰማሩ ከሃዲ አሳማዎች)፤ የግንባር ውሎዎችን ሁኔታ ልክ እንደሰፊው ሕዝብ በቤታቸው ሆነው ፌስቡክ ላይ ይከታተሉ የነበሩ ነገር ግን ለሰፊው ሕዝብ እራሳቸውን እንደጀግና የሚያስተዋውቁ የፌስቡክና የዩቱዩብ አፈ-ተዋጊዎች፤ ወያኔ ደሴ ሲደርስ በሚኒስቴር ደረጃ ባሉ ሰዎች ጭምር ታግዘው በኢትዮ 360(aka Egypt 360) ሚዲያ አየር ይዘው "ወያኔ ወደአዲስ አበባ ይግባ እንዳትዋጉት አሳልፉት" እያሉ በተለያየ መንገድ ጫና ሲፈጥሩ የነበሩ አካላት እውቅና እና ሽልማት መናፈቃቸው የነውረኝነታቸውን ጥግ ከማሳየታቸውም ባሻገር በግንባር በዱር በገደሉ ሲዋደቅ የነበረውን ሀገሩን ከአሸባሪው ጥቃት ለመከላከል የወጣውን ሕዝብ ምን ያህል እንደናቁት የሚያሳይ ነው።

አማራ ላይ ሂሳብ ይወራረድበት፤ ኢትዮጵያ ትፈርስ ዘንድ ሁሉንም አማራጮች ሁሉ ተጠቅመው የባንዳ ስራ ከሰሩ በኋላ መንግስት በሐገር ክህደት ወንጀል አለመክሰሱን እንደጥሩ አጋጣሚ ቆጥረው ነገሮችን ለማስተካከል የኢትዮጵያ ሕዝብንና መንግስት ይቅርታ ለመጠየቅ ከመስራት ይልቅ ጭራሽ የጦርነቱን ድል ሽልማቱንና ክብሩን እንውሰድ ማለት የጤና ሊሆን አይችልም።

በራያ፣ በማይፀብሪ ፣ በአበርገሌና ሰቆጣ ግንባሮች ከቀበሌ እስከ ፌደራል ድረስ ጠላት ወደመሃል ከተሞች ሲገሰገስ በወገን በኩል እነማን ምን አይነት መስዋዕትነት ከፈሉ? እነማንስ በባንዳነት ስራ ተሰማሩ የሚለው በመንግስታዊ መዋቅሩ፣ በፖለቲካው ክንፍ፣ በፀጥታ መዋቅሩና በደህንነቱ ክንፍ፣ በፋኖም ሆነ በሌላው ሕዝባዊ አደረጃጀት ከተሰማሩት ውስጥ የማይታወቅ የተደበቀ የማይገለጥ የተሰወረ ጉዳይ አይደለም። የእያንዳንዱ አኩሪ ተጋድሎና አሳፋሪ ክህደት ታውቆና ተሰንዶ  የሰነበት ጉዳይ ነው።

በሕግ ማስከበሩም ሆነ በሕልውና ተጋድሎው ወቅት በየትኛውም የውስጥ ባንዳና የውጭ ባደ የተቀናጀ ጦርነት "በአማራ ላይ ሂሳብ አይወራረድበትም፤ኢትዮጵያም አትፈርስም!" ብለው መስዋዕትነት ከፍለው በእውቅና እና ሽልማት ፕሮግራሙ ላይ በተለያየ ምክንያት ያልተገኙና የተዘለሉ ወይም የተረሱ ክብር የሚገባቸው ጀግኖች ሊኖሩ ስለሚችሉ መንግስት በቀጣይ የማስተካከል ስራ ይሰራል የሚል እምነት አለኝ። የዛሬው የእውቅና የሽልማት ፕሮግራም በግንባር ተገኝተው ከጀግናው የመከላከያ ሃይላችን ጋር ተቀናጅቶ የተሰጣቸውን ግዳጅ ለተወጡ የፀጥታ ሃይሎችና ለተዋጉ ፋኖዎች የተሰጠ ክብርና ሽልማት ይመስለኛል።

ኢትዮጵያ በልጆቿ የተባበረ ክንድ ነፃነቷን ጠብቃ ታፍራና ተከብራ ለዘለዓለም ትኖራለች‼️
በሕግ ማስከበር እና በሕልውና ዘመቻው (ሁለቱን በአንድነት ወይም በመነጣጠል እውቅና እና ሽልማት ይሰጥ አይሰጥ ባላውቅም) የሐገር ጥሪን ተቀብለው በግምባር የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ጀግኖች የእውቅና እና የሽልማት ፕሮግራም መደረጉ የሚያስመሰግን ነው። አርበኞች እንዲነግሱ ባንዳዎች እንዲኮስሱ የሚያደርግ ነው። ስለአገር ሉዓላዊነትና ነፃነት ስለሕዝብ ዘላቂ ጥቅም ራሳቸውን አሳልፈው የሰጡ ሰዎችን ማመስገንና መሸለም ፀረ-ወያኔነት ነው። ኢትዮጵያን ከፍ ማድረግ ነው። ነፃነቷንና ክብሯን ጠብቃ ትቀጥል ዘንድ የመፈለግ ምልክት ነው።

በታጋዮች መስዋዕትነት የሚሳለቀውን ሳይዋጋ ፊት አውራሪ ነኝ የሚለውን"የጌሾ ወቀጣ ማንም ሰው አልመጣ ለመጠጡ ጊዜ ከየጎሬው ወጣ" እንዲሉ የድል አጥቢያ ጀግኖችን ሁሉ መስመር የሚያሲዝ ነው። ማንም እውቅና እና ሽልማት የሚፈልግ በግዳጅ የላቀ ጀግንነቱን ማሳየት እንዳለበት የሚያደርግም ነው።

ከምንም በላይ ሊታወቅ የሚገባው እውቅና እና ሽልማት ለዘመተ ሁሉ ሳይሆን በጦርነቱ የላቀ አስተዋፅኦ ላበረከቱ ለተመረጡ የጀግኖች ጀግና ለሚባሉ ሰዎች የሚሰጥ መሆኑን ነው። ሁሉም ወታደሮች ጀግና ቢሆኑም እውቅና እና ሽልማቱን የሚቀበሉት ግን ጥቂት የተመረጡ ሰዎች ናቸው። ይህ በየትኛውም ዘመንና አለም ላይ የነበረ ያለና የሚቀጥል አሰራር ነው። የመከላከያ ሰራዊትም ሆነ የልዩሃይል አባላት በሙሉ በጦርነት ስለተሳተፉና ጀግና ስለሆኑ ለሁሉም እውቅና እና ሽልማት አይሰጥም። ከመካከላቸው የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ እንጅ። ስለሆነም በግንባር ጤዛ እየላሳችሁ፣ ድንጋይ እየተንተራሳችሁ፣ ያገኛችሁትን ቁራሽ ምግብ እየቀመሳችሁ፣ ውሎና አዳራችሁን በምሽግ ያሳለፋችሁ፣ ጋራ ሸንተረሩን ስታቋርጡ፣ ዳገት ቆልቁለቱን ስትወጡና ስትወርዱ የከረማችሁና ስለእናት ኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና ነፃነት መከበር ከፍተኛ መስዋዕትነት የከፈላችሁ የቁርጥ ቀን የኢትዮጵያ አለኝታዎች አኩሪ ተጋድሏችሁ ከትውልድ ወደትውልድ እየተላለፈ የሚዘክር ጀግነነት እንጅ በአንድ መድረክ ምስጋና ብቻ የማይቆም መሆኑን ማወቅ ይገባል። ነገሮችን በዚህ መልክ መረዳትም ተገቢ ይመስለኛል።

በተለያዩ ግንባሮች ስለ ማንነታችሁ ስለእናት አገራችሁ ሉዓላዊነትና ነፃነት የተዋደቃችሁ ነገር ግን በእውቅና እና በሽልማት ፕሮግራም ላይ ያልተገኛችሁ ጀግኖች ካላችሁ በአኩሪ ስራችሁ ቀጥላችሁ ለቀጣይ ለላቀ ሽልማትና ክብር ራሳችሁን ራስን ማዘጋጀት ይገባል። በዘመኑ አኩሪ ተጋድሎ የሰራ፣ ያደፈ ታሪክ የሌለው ሰው፣ በቀጣይ ትውልድ ዘንድም ስሙ ሕያውና በአርአያነት የሚጠቀስ ከአንድ መድረክ ያለፈ ዘመን ተሻጋሪም ነው‼️

በተለያዬ ምክንያት በትናንትናው የእውቅና እና የሽልማት ፕሮግራም ባልተካተቱ በኢትዮጵያ ሕልውና ባልተደራደሩ የግንባር ላይ ጀግኖች ታኮ ጀግና ለመሆንና ለጀግኖቹ የተሰጠውን ሽልማትና ክብርን ለማጣጣል መሞከር ወያኔያዊነት ነው‼️
ለአብራሪነት እና ለቴክኒሽያንነት ሙያ የወጣ የቅጠር ማስታወቂያ‼️

በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የኢ.ፌ.ዴ.ሪ አየር ኃይል ጠቅላይ መምሪያ በአውሮፕላን አብራሪነት እና በቴክኒሽያንነት ሙያ ፍላጎት ያላቸውንና የምልመላ መስፈርቱን የሚያሟሉ ወጣቶችን መልምሎ ማሰልጠን ይፈልጋል፡፡

በዚሁ መሠረት፡
1. አጠቃላይ መመዘኛ
- ዜግነት ኢትዮጵያ የሆነ/ነች፣
- ለህገ-መንግስቱ ተገዢ የሆነ/ነች፣
- መልካም ስነ-ምግባር ያለው/ላት፣
- ዕድሜ ከ18-24 የሆነ/ነች፣
- ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሚያወጣውን የጤንነት መመዘኛ መስፈርት የሚያሟላ/የምታሟላ፣
- የወንጀል ጥፋት ሪከርድ የሌለበት/ባት ስለመሆኑ ከአካባቢው ቀበሌ ወይም ፖሊስ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል/የምትችል፣
- ከአሁን በፊት የመከላከያ ወይም የፖሊስ ሰራዊት አባል ያልነበረ/ች፣

2. የትምህርትና ሌሎች መመዘኛዎች
2.1. ለአብራሪዎች መመልመያ መስፈርቶች
- የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪ ሆኖ/ሆና በ2012 እና በ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሃገር አቀፍ ፈተና ወስዶ/ወስዳ አጠቃላይ ውጤት 350 እና ከዚያ በላይ ያለው/ያላት እንዲሁም በእንግሊዘኛ፣ በሂሳብ እና በፊዚክስ የትምህርት አይነት አማካኝ ውጤት 70% እና ከዚያ በላይ ያለው/ያላት፣

- የ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የወሰደበትን/የወሰደችበትን የትምህርት ማስረጃ ኦርጅናል እና ፎቶ ኮፒ ማቅረብ የሚችል/የምትችል፣
- ቁመት 1.65ሜ እና ከዛ በላይ የሆነ/የሆነች፣
- ክብደት ከ50-60 ኪ.ግ የሆነ/የሆነች፣
- የአየር ኃይል አካዳሚን የመግቢያ ፈተና ወስዶ/ዳ ማለፍ የሚችል/የምትችል፣

2.2. የቴክኒሽያኖች መመልመያ መስፈርቶች
- የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪ ሆኖ/ና በ2012 እና በ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ወስዶ/ዳ አማካይ ውጤት 300 እና ከዚያ በላይ ያለው/ያላት እንዲሁም በእንግሊዘኛ፣ በሂሳብ እና በፊዚክስ ትምህርት አማካኝ ውጤት 60% እና ከዚያ በላይ ያለው/ያላት፣
- የ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የወሰደበትን/የወሰደችበትን የትምህርት ማስረጃ ኦርጅናል እና ኮፒ ማቅረብ የሚችል/የምትችል፣
- ቁመት 1.65ሜ እና ከዛ በላይ የሆነ/የሆነች፣
- ክብደት ከ50-60 ኪ.ግ የሆነ/የሆነች፣
- የአየር ኃይል አካዳሚን የመግቢያ ፈተና ወስዶ/ዳ ማለፍ የሚችል/፣የምትችል

3. የምዝገባ ቦታ
- ለአዲስ አበባ ተመዝጋቢዎች፡- አምባሳደር አካባቢ በሚገኘው የቀድሞ መከላከያ ሚኒስቴር ዋና መ/ቤት ብሄራዊ ተጠባባቂ ኃይል ማደራጃ እና ማስተባበሪያ ቢሮ፣
- ለድሬደዋ መስተዳድር ተመዝጋቢዎች፡- ድሬደዋ ከተማ በሚገኘው የፀጥታ ዘርፍ ቢሮ፣
- ለአማራ ክልል ተመዝጋቢዎች፡- ባህር ዳር፣ ጎንደር፣ ደብረ ማርቆስ፣ ደብረ ብርሃን፣ እና ደሴ ከተሞች በሚገኙ የፀጥታ ዘርፍ ቢሮዎች፣
- ለኦሮሚያ ክልል ተመዝጋቢዎች፡- ባሌ-ሮቤ፣ ጅማ፣ ነቀምት፣ ደምቢ ዶሎ፣ አምቦ፣ ቢሾፍቱ፣ አዳማ፣ ወሊሶ ከተሞች በሚገኙ የፀጥታ ዘርፍ ቢሮዎች፣
- ለደቡብ ክልል ተመዝጋቢዎች፡- አርባ ምንጭ፣ ወላይታ ሶዶ፣ ሆሳዕና(ዋቻሞ) በሚገኙ የፀጥታ ዘርፍ ቢሮዎች፣
- ለአፋር ክልል ተመዝጋቢዎች፡- ሰመራ ከተማ በሚገኘው የፀጥታ ዘርፍ ቢሮ፣
- ለሱማሌ ክልል ተመዝጋቢዎች፡- ጅግጅጋ ከተማ በሚገኘው የፀጥታ ዘርፍ ቢሮ፣
- ለሐረሪ ክልል ተመዝጋቢዎች፡- ሐረሪ ከተማ በሚገኘው የፀጥታ ዘርፍ ቢሮ፣
- ለቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ተመዝጋቢዎች፡- አሶሳ ከተማ በሚገኘው የፀጥታ ዘርፍ ቢሮ፣
- ለጋምቤላ ክልል ተመዝጋቢዎች፡- ጋምቤላ ከተማ በሚገኘው የፀጥታ ዘርፍ ቢሮ፣
- ለሲዳማ ክልል ተመዝጋቢዎች፡- ሐዋሳ ከተማ በሚገኘው የፀጥታ ዘርፍ ቢሮ፣
- ለደቡብ ምዕራብ ክልል ተመዝጋቢዎች፡- ቦንጋ ከተማ በሚገኘው የፀጥታ ዘርፍ ቢሮ ይሆናል፡፡

4. የምዝገባ ጊዜ
ከግንቦት 10 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ግንቦት 20 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ ባሉ ተከታታይ የስራ ቀናት መሆኑን እንገልፃለን፡፡

በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የኢ.ፌ.ዴ.ሪ አየር ኃይል ጠቅላይ መምሪያ
ወያኔያዊው የፌስቡክ የአማራ ብሔርተኛ መከላከያ ሰራዊትን መንግስት ከወልቃይት ሊያስወጣው ስለሆነ አማራ ውለታህ እንዲህ አልነበረም ልትካድ ነውና እባክህ በአንድነት ቆመህ ሆ ብለህ በመንግሥት ላይ ተነስና ተቃወም! እንደሚለው እንደባለፈው አይነት ጥሪና አጀንዳ ያለ ብዙ ነገሮችን የገለጠልኝ ነገር የለም።
የወያኔያዊው የፌስቡክ የአማራ ብሔርተኛ የፌስቡኩን አማራ ጭንቅላት ምን ያህል እንደተቆጣጠረውና እንዳደነዘዘው የተረዳሁበት እልፍ ጭንቅላቶች ለሌሎች መጠቀሚያ ተላልፈው የተከራዩበት፣ ያገኘውን አሰስ ገሰስ መረጃ ሁሉ እንደወረደ ሳያላምጥ ከአንዴም ሁለት ሶስቴ የሚውጠውን ሳይሆን ለማላመጥ የሚሞክረውን መቁጠር ይቀላል።

በሱዳን በኩል የማጥቃት የእንቅስቃሴ ምልክት ሲታይና የወያኔን የዳግም ወረራ ዝግጅትን ተከትሎ ለወልቃይት ሕዝብ የበጀት አለመኖርና የመሰረተ ልማት አለመሟላት የአገልግሎት ዘርፉ መጓደል ሁለቱን አመት ድምፁን አጥፍቶ የከረመው ወያኔያዊ የአማራ ብሔርተኛ በድንገት ደርሶ የወልቃይት ተቆርቋሪና ጠበቃ በመምሰል በማር የተለወሰ መርዝ መርጨቱን፣ የለመደውን የአስለቃሽነትና የምሬት የተስፋ ማስቆረጥ ጥሩንባውን እየነፋ ሆድ ሊያስብስ መሞከሩ ሳያንስ ለወልቃይት ጠበቃ የሆኑና በአማራ አስተዳደር ስር እንዲሆን ያደረገውን መንግስት ጭራሽ አሳልፎ ለወያኔ እንዲሰጥ አስቧል በማለት ሞኞቱን የሚገልፅበት መንገድ ነው። ያሉ ነገሮችን ከግራና ከቀኝ በኩል ተዟዙሮ ለማንሰላሰል የማይሞከር እንደጋሪ ፈረስ አይነት ሰዎችን ካልሆነ በስተቀር እኛ እንኳን ሆድ ሲያውቅ ደሮ ማታ ብለን የምናልፈው ጠላትነቱን ቀድመን የምናውቀውና ያረጋገጥነው አፈር የምናስልሰው ብቻ ሳይሆን ወደአፈርነት የምንቀይረው ሃይል መሆኑን ነው።

ወልቃይት የቀጠናው ወሳኝ ኮሪደር መሆኑን የግብፅንና የሱዳንን ሁኔታ የውስጥ ባንዳዎችን አገር የማፍረስ የተላላኪነት ቁርጠኝነት ለሚያውቅ ሰው መንግስት ራሱ መከላከያ ሰራዊት ከወልቃይት ላወጣ ነው ቢል እንኳን ሊታመን የሚችል ጉዳይ አይሆንም። ወልቃይት እንዲሁ ለም የሆነ የጎንደር አማራ መሬትና ግዛት ስለሆነ ብቻ ሳይሆን ወልቃይት በወያኔ እጅ በገባ በቀጣዩ ቀን በኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ድሮን ጭምር ላለመታጠቁ ምንም አይነት ዋስትናም ስለሌለም ነው።

የኢትዮጵያን መፍረስ የሚፈልግ መንግስት ከሆነ ብቻ ነው ወያኔያዊ የአማራ ብሔርተኛና ደመ-ነብሳዊው የስማ በለው አማራ እንደሚለው መንግስት ጦሩን ከወልቃይት ሊያስወጣ ወይም ቀጠናው ላይ ጦሩን እንዳይጠናከር ሊያደርግ የሚችለው። ከወያኔያዊ የአማራ ብሔርተኛ ሃይል የምንረዳው ነገር ቢኖር ወያኔ በሱዳን ጦር ከውጭ በኩል እየተመራ ከውስጥ በኩል ደግሞ ያለ የሌለ ሃይሉን ተጠቅሞ ወደጎንደር የማጥቃት ሙከራ የሚያደርግ መሆኑን ነው። እናም ማጥቃቱን ተከትሎ ድንገት ተሳክቶለት አንድ አካባቢ ቢቆጣጠር ለተክደሃል ጩኸት ቀድሞ የማመቻቸት አጀንዳ ነው።

ወልቃይትን መንግስት በስሩ የሚያደርገው ለማንም ብሎ ሳይሆን ለራሱ ሕልውና ለአገረ-መንግስቱ መቀጠልና መፅናት ሲል ነው። የኢትዮጵያን መበልፀግ የሚሻ መንግስት የኢትዮጵያን ሕልውና አደጋ የሚጥል ስራ ፈፅሞ ሊሰራ አይችልም። ይህን አለመረዳት ችግሩ የማንም ሳይሆን የራስ ነው። በወያኔ ፕሮፖጋንዳ አዕምሮን የማጣት ምልክት ነው። ከዛ ካለፈ ደግሞ ከወያኔ እንደ አንዱ መሆንን የሚያረጋግጥ ነው።

በሌላ በኩል ወያኔያዊ የፌስቡክ የአማራ ብሔርተኛ በመንግሥት መከዳት ስለወልቃይት የሚናገረውና የሚፅፈው የቢሆን ፍላጎቱን ነው። በጓዳ እንዲሆን የሚመኘውንና ከውጭ ባዕዳን ጭምር ተቀናጅቶ መሬት ለማስነካት የሚሰራውን ጉዳይም ነው በፊት ለፊት በስመ አዛኝ ተቆርቋሪነት ግርግርና ሁከት ለመፍጠር የሚሰራው። የጥርጣሬ አጀንዳዎችን በመንዛት በሕዝብና በመንግስት በልዩሃይልና በመከላከያ መካከል መተማመን እንዳይኖር ቢቻል እርስ በራሳቸው እንዲጋጩ ለማድረግና ጠላት ሰርጎ እንዲገባና ወልቃይትን እንዲቆጣጠር በተጠና መንገድ ጠላትነት አጀንዳን እያራገበ ያለው።

የአማራ ልዩሃይልም ሆነ መከላከያ የተደራጀውና የታጠቀው ወደየትም ስምሪት የሚሰጠው በመንግስት አቅጣጫ መሰረት ብቻ ነው። ከመንግሥት ውጭ ማንም አካል ተነስቶ እዚህ ተቀመጥ እዚያ ሂድ ወይም እንዲህና እንዲያ ሁን ሊለው አይችልም።

መከላከያ ወይም ልዩሃይል መቼ ማንን በየት በኩል ማጥቃትና መስፈር እንዳለበት ማንም ንጉሊያም ወይም ንቅል ወፈፌ ከመሬት እየተነሳ ለዛውም በስማ በለው ትዕዛዝ የሚሰጠው ወይም የሚደናገርም ተራ ሃይልም አይደለም።
#ኦነግ_ሸኔን ሲሆን "መንግስት እየቀለደ ነው, እየመታው አይደለም" ይሉህና ከህወሃት ጋ ሲሆን "#NO_More_war" ይሉሃል, የእናንተ ዶሮ ጭራ የምታገኘው ሴራ መቸ ጠፍቶን።

መንግስት አሁንም ህግ ያስከብር ወረራን ይከላከል!!!

Hamza Yasin Hussien
የወያኔ አጀንዳ አሻሻጭ የመንፈስ ልጆች ወያኔ በአደባባይ በአዋጅ "በአማራ ላይ ሂሳብ አወራርዳለሁ፤ኢትዮጵያን ለማፍረስ ሲኦልም ድረስ እወርዳለሁ" ሲል ተከትለው አትዝመቱ ከማለት ጀምሮ በዘመቱ ሰዎች ላይ አቃቂር ሲያወጣ የነበረው የባንዳው ባንዳ "ጦርነቱ እኛን አይመለከትም፤ጦርነቱ የኢትዮጵያን ሕልውና ሳይሆን የአብይን ስልጣን ለማስቀጠል ነው" ማለቱን የምናስታውሰው ጉዳይ ነው። አሁን ደግሞ ወያኔ ከውጭ ባዳ የኢትዮጵያ ጠላቶች ጋር በመቀናጀት ለዳግም ወረራ በተዘጋጀበት ከሰሞኑ እነ ጌታቸው ረዳና ደብረፅዮን አማራን እንደወዳጅና ስለሰላም የተናገሩትን ማዘናጊያን ተከትሎ የመንፈስ ልጆቹ #No More War ወደሚል ዘመቻ ከፍተዋል።

በእውነቱ የሰሞኑን የወያኔን የማዘናጊያ የሰላምና የወዳጅነት ፕሮፖጋንዳ የመንፈስ ልጆቹን የጦርነት አያስፈልግም ጎጅ ነው የባንዳነት የዘመነች ዘዴ አለማድነቅ አይቻልም። ወያኔያዊ ግብራቸውን መሸፈኛ ሊሆን የሚችል ከትናንቱ አንፃር ይህ ለነገ ክርክርም የሚጠቅማቸው ስልት ነው።

ማንም ሰው ማወቅ ያለበት ሰላም በአንድ ወገን ብቻ ፍላጎት የሚመጣ ወይም የሚረጋገጥ ጉዳይ አይደለም። ሰላምና ትዳር እንዲሁም የሚተላለፉ መኪናዎች በአንደኛው ወገን ጥንቃቄ ወይም ጥረት ብቻ አይረጋገጡም ወይም አይሰምሩም። የሁሉንም የነቃ መልካም ተሳትፎና ጥንቃቄን ይጠይቃል።
ሰላምም በስብከት ብቻ የሚረጋገጥ ነገር አይደለም። አለም ላይ ለሺ ዘመናት ስለጦርነት አስከፊነትና ስለሰላም አስፈላጊነት ያለማቋረጥ ተሰብኳል። ነገር ግን አለማችን በየጊዜው ሚሊዮን ሰዎችን የጨረሰ ቢሊዮን ዶላሮችን ያወደመ ጦርነትን ደጋግማ አካሂዳለች። አሁንም በዩክሬንና በሩሲያ መካከል እየተደረገ ያለው ጦርነትም ስለሰላም አስፈላጊነት ስለጦርነት አስከፊነት ግንዛቤ የሌላቸው ሆኖ ሳይሆን አንደኛው ወገን ጥቅሜን ማስከበር የምችለው በጦርነት ነው ብሎ ስለሚታመን ነው።
ጦርነት መግባት ሳትፈልግ ጦርነት እንድትገባ ከተገደድክ ምርጫህ ጦርነቱን ቀድሶ አሸናፊ ለመሆን መታገል ነው። ሰላምን ማንም ስለፈለገ በአንደኛው ወገን ብቻ የሚረጋገጠው ነገር አይደለም። ጦርነትን ማሸነፍ የሚቻለው በሰላሙ ቀን ለጦርነት ለመዘጋጀት ሲቻል ነው። የወያኔ የመንፈስ ልጆች እያደረጉት ያለው የአማራም ሆነ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲዘናጋ ብቻ ሳይሆን የጥፋት መንገድ እንዲመርጥ ለዳግም ወረራ ለጦርነት ለተዘጋጀውና ጦርነቱንም ሕዝባዊ ነው እያለ ላለው ወያኔ ደግሞ እንደተለመደው መንገድ መጥረግ ነው።

ማንም ያለውን ቢል የቱንም ያህል የጦርነት ዝግጅት ቢያደርግ አላስፈላጊ መስዋዕትነት ከማስከፈል ያለፈ የትም መድረስ አይችልም።
ያለመስዋዕትነት ደግሞ ድል የለምና ለእናት ኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና ነፃነት ለሕዝቧ ሰላምና ዘላቂ ጥቅም መከበር መከፈል ያለበትን መስዋዕትነት ለመክፈል ሁሌም የነቃንና የተዘጋጀን ነን!
ወያኔያዊ የአማራ ብሔርተኛ ተቃውሞውን የሚያሰማው ሆድ-ነክ ቃላቶችን በመጠቀም ነው። ተከፍሏል ወይም ሊከፈለው ነው፤ በላ ወይም ሊበላ ነው፤ ተሸጠ ወይም ሊሸጥ ነው፤ ስንት ቢከፈለው ነው ሕዝቡን የካደው(የትኛውን ሕዝብ ምን አይነት ውል ኖሮት ነው የካደው የሚል ጠያቂም ጠፋ)፣ ለነገሩ እኮ ለክፍያው ከኦህዴድ ይልቅ ሕወሓት ይሻላልም ይላል((የሁለቱን የክፍያ ዋጋ ከማወቅ አልፎ ማነፃፀር እድሉ እንዴትስ ተቻለ ብሎ የሚጠይቅ ባለመኖሩ ይደጋግመዋል)፤ አንተ ምኑ ሆዳም ነው(የሆዳምነት መስፈርቱ የተዘረዘረ ይመስል?)፤..." የመሳሰሉትን ከሆድ ጋር ብቻ የሚገናኙ ስድብና እርግማን ነክ ጉዳዮችን ብቻ በመዝገበ ቃላቱ ያሰፈረ ስለሐገርና የሕዝብ ጥቅም ሳይሆን ግለሰቦችን አጀንዳ የሚያደርግ ነውርን እንደጌጥ የሚቆጥር አግድም አደግ ነው። ፖለቲካውን ሲያመሰጥር ደግሞ የአማራ ጠላቱ ሆዳም አማራ ነው ብሏል አስራት የሚል ነው። ፕሮፌሰሩ አለ የሚባለው የሆዳምነት ትርጉም በእነዚህ እንደሚተረጎመውም አይደለም። ነው ከተባለም ፈፅሞ ስህተት የሆነ አረዳድ ነው!

ወያኔያዊ የአማራ ብሔርተኛ ትልቁ ድፍረቱና ነውረኝነቱ ደግሞ ስለክፍያ፣ ስለገንዘብ፣ ስለመብላትና መጠጣት የሚጨነቅና ያለምንም ክፍያ ለሐገርም ሆነ ለሕዝብ ጥቅም ካለመስራቱ ባሻገር ሌሎችን እንደራሱ አድርጎ የሚያስብና የደመደመ መሆኑ ነው። ያለ ክፍያ ጥቅም እንኳን ወደጦርነት ወደግንባር ወደ ሰላማዊ ቦታ አንድ ኢንች የሚራመድ አይደለም።

በጣም የሚደንቀው ደግሞ ከዚህ በፊት ምን ጎደለብህ? ምንስ ይሻልሃል? እያለ የወርና የዓመት ወጭህን የሚሸፍን፣ የአንተን የግል ሕይወት ውሎና አዳር የሚከታተልና የሚገባህን ሲያደርግ የቆየ ይመስል ጠላት በሚለው አካል ስንት ቢከፈለው ነው ይላል። ከሆድ-ነክ የወጣ አስተሳሰብ የሌለው የአሳማነት ባሕሪይ የተላበሰ ነው።

በክልል የቢሮ ኋላፊ፣ በሚኒስቴር ደረጃ የተሾሙ፣ በመንግስታዊ መዋቅሩ ውስጥ በደህንነቱ ክንፍ ያሉ፣ በቪ-8 የሚሽከረከሩ በቪላ ቤት የሚኖሩ፣ አብይ አህመድን እኩል እንደጌታቸው ረዳ እያብጠለጠሉና ጠላት ያደረጉ፣ ኢትዮጵያንም ለማፍረስ በነፃነት እዛም እዚህም የሚንቀሳቀሱ የተጠያቂነት ስጋት ያለባቸው ወንጀለኞችና አቅመቢስ አመራሮችን ነፃነት የሰጠ ስርዓት በሌላ በኩል እነሱን እንደጀግና የሕዝብ ልጅ በመንጋው ዘንድ እንዲታዩ ሲያደርግ በተቃዋሚ ወገን ያሉ ለኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና ነፃነት ለሕዝቦቿ ዘላቂ ሰላምና ጥቅም መከበር የሚሰሩ ሰዎች ደግሞ እንደ በብልፅግናነት ስማቸው ይነሳል። ተአምር ነው እኮ!

ሰው ለአላማው መሳካት ይረዳው ዘንድ ገንዘብ ሊፈልግ ሊከፈለው ሊበደር ሊዘርፍ ወይም ሌላ ሌላም ነገር ሊያደርግ ይችላል እንጅ እንዴት አንድ ሰው ለመብላት ብቻ ለመኖር የማይሆነውን ለመሆን ራሱን ያዘጋጃል። ያኖራልስ? አጃኢብ ነው!
በቁር በሐሩሩ መካከል እያለፉ ዳጋት እየወጡ ቁልቁለት እየወረዱ ጋራ ሸንተረሩን እያቆራረጡ ሌትና ቀን ሁሌም ስለኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና ነፃነት ስለሕዝቦቿ ዘላቂ ሰላምና ጥቅም መከበር የሚዋደቁ የኢትዮጽያዊያን የኩራት ምንጭ ጀግናው መከላከያ ሰራዊታችን አባላት እየከፈላችሁልን ስላለው በቃላት የማይገለፅ መስዋዕትነት እናመሰግናችኋለን‼️

ለኢትዮጵያ መታፈርና መከበር ቀዳሚ ባለድርሻዎች ናችሁ‼️
በክልል የቢሮ ኋላፊ፣ በሚኒስቴር ደረጃ የተሾሙ፣ በመንግስታዊ መዋቅሩ ውስጥ በደህንነቱ ክንፍም ያሉ፣ በቪ-8 የሚሽከረከሩ በቪላ ቤት የሚኖሩ፣ በብሔር ት*ግሬና የወያኔ ስራ አስፈፃሚ አለመሆናቸው ካልሆነ በስተቀር አብይ አህመድን እኩል እንደጌታቸው ረዳ የሚያብጠለጥሉና ጠላት ያደረጉ፣ ኢትዮጵያንም ለማፍረስ በነፃነት እዛም እዚህም የሚንቀሳቀሱ፣ የተጠያቂነት ስጋት ያለባቸው ወንጀለኞችና የአቅም ማነስ ያለባቸው አመራሮች በነፃነት እንደፈለጉ እንዲንቀሳቀሱ የፈቀደ ስርዓት በሌላ በኩል እነሱን እንደጀግና የሕዝብ ልጅ በመንጋው ዘንድ እንዲታዩ ሲያደርጋቸው በተቃዋሚ ወገን ያሉ ለኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና ነፃነት ለሕዝቦቿ ዘላቂ ሰላምና ጥቅም መከበር የሚሰሩ ሰዎችን ደግሞ ስማቸው በብልፅግናነት እንዲነሳ ማስደረግ ችሏል። መቼም በዚህ አለመገረም አይቻልም!

ብልፅግናንም ሆነ መንግስታዊ መዋቅሩን በመጠቀም እንጀራቸውን የሚጋግሩት፣ የሚፈልጉትን የግል ጥቅማቸውንና አላማቸውን እያሳኩ ያሉት እነሱ ሆነው ሳለ አንድ ቀን በብልፅግና በር ያለፈን ወይም አብዮታዊ ዲሞክራሲ ወይም ሞት! ከሚሉ ናፋቂ ወያኔዎች የተለየንና ብልፅግና ከሆኑ አመራሮች ጋር የሚታይን ተቃዋሚ በለፀገ ወይም የመንግስት ተቀላቢዎች እስከማለት የሚያደርስ የይሉኝታ ቢስ ጥግ ላይ ያሉ ነውረኞችን እስከማየት አድርሶናል። በእውነቱ ግን መበልፀግን ጠልቶ ድህነትን የሚመርጥ የመንግስትን ክፍያንስን የሚጠላ ሰው አለንስ? ተካፋዮች ተከፋይ የሚሉት ነገርስ😂

በየትኛው ዘመንና ታሪክ የፓርቲው ሊቀ-መንበርና የሐገሪቱ መሪ በራሱ በብልፅግና ውስጥ ባሉ ካቢኔዎቹ በጓዳ ያይደለ በአደባባይ፣ ከልብ በመነጬ የመረረ ጥላቻ ስሙ እየተጠራ የሚወነጀልበት፣በእሱ ላይ የጥላቻ ቅስቀሳ የሚያደርጉና እሱን ለማውረድ በነፃነት የሚደራጁና የሚያደራጁ፣ በብልፅግናም ሆነ በመንግስታዊ መዋቅሩ እዛው በጓዳው እንደምስጥ ያይደለ እንደ አንበጣ እየተንቀሳቀሱ፣ ሐገር ለማፍረስ እየተንቀሳቀሰ ከሚገኘው የፈረጠመ የተደራጀ የጥፋት ሃይል ባለበት ሁኔታና ከዚህ አገር አፍራሽ ሃይል ጋር አጀንዳ እየተመጋገቡ በጥፋት መንገድ እየተራመዱ ራሳቸውን እንደልክ እንዲቆጥሩ፣ እንደጀግና እንደየሕዝብ ልጅ እንዲታዩ የሚፈለግበትና የሚሆኑበት በጥቅሉ እንደፈለጉ እንዲፈነጩ የሚፈቅድ ስርዓት፣ ከዚህ ቀደም ተሰምቶና ታይቶ የሚታወቅ ለወደፊቱም የሚሆን አይመስለኝም። ለዲሞክራሲ ማሳያ ወይም ዲሞክራሲ ሲተረጎም እንዲህ ያለም አይደለም። ነው ከተባለ ይቅርብን እንዲህ ያለ ዲሞክራሲ አያስፈልገንም። ወያኔን የጠላነውና የምንታገለው አገር ለማፍረስ የሚንቀሳቀስ የጥፋት ሃይል ስለሆነ በግብሩ እንጅ ትግረኛ ተናጋሪ ስለሆነ አይደለም።

ብልፅግና ያልተመቸው ማንም አመራር ብልፅግናን ለቆ ባመነበት በራሱ መንገድ በድርጅት ወይም በግሉ መታገል እንጅ በብልፅግና ውስጥ ሆኖ ወያኔያዊ ብሔርተኝነትን እያራመደ መዋቅሩን በመጠቀም 24/7 ዶ/ር አብይ አህመድንና የተመረጡ ወያኔ ጠል አገር ወዳድ አመራሮችን የተቃዋሚ ፖለቲከኞችን አክቲቪስቶችን ጠላት ማድረግ ብቻ ሳይሆን ለማጥቃት ከወያኔ ጋር አጀንዳ በግልጽ እየተመጋገበ ኢትዮጵያን ለማፍረስ እንዲዋጋ ሊፈቀድለትና እድል ሊሰጠው አይገባም። እስከዛሬ የተፈፀመው የተከፈለው አላስፈላጊ መስዋዕትነት ከእንግዲህም እንዳይቀጥል በሩ ሊዘጋበት ይገባል። አገር የሰጠችውን ኋላፊነት ወደጎን በማለት መንግስታዊ መዋቅሩን በመጠቀም የግልንና የቡድን ጠባብ ፍላጎት ለሟሟላት ጭራሽ ከተቃዋሚው በላይ ተቃዋሚ ከአገር አፍራሾች በላይ አገር የማፍረስ እንቅስቃሴ እያደረገ መልሶ ደግሞ ከተቆርቋሪዎች በላይ ተቆርቋሪ ከሐቀኞቹ በላይ ሐቀኛ እንደሆነ በማሰብና በሚዲያ ጫጫታ የጀግንነት ካባ ይሰጠው ዘንድ የሚፈልገውና የሚሰራው ሃይል የተላበሰው ሞራል ያስደንቃል።

በብልፅግና ውስጥ ካሉት አመራሮች ውስጥ አብዮታዊ ዲሞክራሲ ወይም ሞት! ላይ እስካሁን ተቸንክረው የቀሩ እኛ ከሞትን ሰርዶ አይብቀል! የሚሉ መንግስታዊ መዋቅሩን ተቆጣጥረው በብልፅግና ውስጥ ብልፅግና ሳይሆኑ እንደፈለጉ እየሆኑ ያሉ ሁለመናቸው ወያኔን የሚናፍቅ ዓመቱን ሙሉ ይመጣል ብለው ከመጠበቅ ባሻገር ይመጣ ዘንድ በሁሉም መስክ ለመጎተት ሞክረው ያልተሳካላቸው፤ ከመጀመሪያውም ከወያኔ ጋር ቆላተንቤን ተገኝተው ኢትዮጵያን ለማፍረስ፤ ከአማራ ጋር ሂሳብ ለማወራረድ፤ ጠባችን ከአብይ ጋር ነው፤ እያሉ አሮጌ ከበሮ እየደለቁ በግልፅ መምጣት ሲኖርባቸው ባህርዳር አዲስ አበባ ተቀምጠው እንጀራቸውን በብልፅግና እንዲጋግሩ መደረጉ ትልቅ ስህተትና እንደሐገርም አላስፈላጊ ዋጋ ያስከፈለ ነው።

ታሪካዊ ጠላቶቻችን አገራችን ኢትዮጵያን ለማፍረስ የተቀናጀ የጥፋት ሁለንተናዊ ዘመቻ መግባት አንቆ ስለያዘንና የአባቶቻችን ልጆች ስለሆንን እንጅ ብልፅግናንም ሆነ የመንግስት መዋቅርን የተቆጣጠረው በደህንነት ክንፉ የተሰማራው ከሃዲና የባንዳ ባንዳ የሆነው አካል መስራት የሚገባውን ስራ እኛ ለመሸፈን ከብልፅግና በላይ ብልፅግና ከደህንነቱ በላይ ደህንነት ሆነን እንቅልፍ አጥተን ለመስራት የሚገባን አልነበረም ብቻ ሳይሆን ይህን ሃይል አብይ አህመድ እያየ እንዳላየ እየሰማ እንዳልሰማ የሚያልፈው መሆኑን እንዳረጋገጥን ፈልጎታል እሱም ያው ነው በሚል ድምዳሜ በነፍጥ ጭምር ተፋልመን ለማፅዳት ወደበረሃ ለመውረድ እንዳንገባ የማይገፋ አይደለም። ልባቸውና ቀልባቸው መቀሌ ላይ ባለ በብልጽግና በመንግስታዊ መዋቅሩ ውስጥ ባሉ አመራሮችና የደህንነት ሰዎች አገር እየተመራች የኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና ነፃነት የሕዝቦቿ ዘላቂ ሰላምና ጥቅም ፈፅሞ ሊከበር አይችልም‼️
Re-Post

ሳይቃጠል በቅጠል...‼️

የጦር መሃንዲሱና የሐገር መሪው ናፖሊዮ ቦናፓርት በተግባር ከተፈተነው ልምዱ ተነስቶ ጦርነት 90% መረጃ መሆኑን አስምሮ የተናገረው በጀኔራል ሰን ዙ "The Art of War" በሚለው ድንቅ መፅሐፍ ለሰፈረው ስትራቴጂ ቁልፍ ማስፈፀሚያ የሚሆን ነው። ጀኔራል ሰን ዙ ጠላትን ያለ ጦርነት ድል መቀዳጀት ወይም በሁኔታዎች ተገደህ ወደጦርነት የምትገባ ከሆነ ጦርነቱን በአነስተኛ መስዋዕትነትና ኪሳራ በአጠረ ጊዜ በድል ለመቀዳጀት ቀድመህ ራስህንና ጠላትህን ማወቅ ይገባሃል ይላል። ይህ መሆን የሚችለው በበቂ መረጃ ነው። በበቂ መረጃ ላይ ያልተመረኮዘ ትንተናና አቋም ሽንፈትና ውርደትን ሊያከናንብ ይችላል።

መቼ መዋጋት መቼ አለመዋጋት በየት በኩል ማጥቃት እንዳለብህ ማወቅ የምትችለው ስለጠላት በቂ መረጃ ሲኖርህ ነው።
"አሸናፊ ጦረኞች ወደጦርነቱ የሚገቡት ጦርነቱን አሸንፈው ሲሆን ተሸናፊዎች ግን ድልን በጦርነቱ መሃል ይፈልጓታል። ጦርነትን ለማሸነፍ ጠላትን በማጭበርበር ማሳሳት ሲቻል ነው "ይላል ጀኔራል ሰን ዙ። ይህን ያለመረጃ ልታደርገው አትችልም። በጦርነት ቃታ መሳብ ከ10% በታች የሚሰጠው ጉዳይ ነው። በአንድ ጉዳይ ላይ ቀድመህ የጠራ መረጃ ከሌለህ misinformation Disinformation ማሰራጨት አትችልምም።

የኢትዮጵያ አሁናዊ ትልቁ ፈተናዋ በእነ ጌታቸው አሰፋ የኢትዮጵያ የደህንነት ተቋሙ የመረጃ ቋቱና ጭንቅላቱ ተቆርጦ ወደመቀሌ ከመወሰዱ የቀረው የደህንነት ክንፍ ባዶ ቀፎ ከመሆኑ ባሻገር "እኔ እኮ ደህንነት ነኝ እያሉ ራሳቸውን ቀድመው በሚያስተዋውቁ የምድጃ ዳር ወሬ ቃራሚ ጀሮ ጠቢዎች" አቅመቢስነታቸውን አንዴ በብሔር ሌላ ጊዜ በጎጥ ተወሽቀው አጭበርብረውና ጥፋት አድርሰው መቀጠል በሚፈልጉ ሰዎች ቁጥጥር ስር መውደቁ ነው የሚል እምነት አለኝ። ከጠላት እንደ አንዱ በመምሰል በጠላት ጓዳ ሰፈር ቅኝት በማድረግ መረጃ እያፈነፈነና የጠላትን የመረጃ ቋትን በመፈተሽ ወደወገን ከስር ከስር መረጃ ማድረስ መረጃ መተንተንና ቀጣዩን ሁኔታ መገመት የሚችል ብቁ የሆነ የስለላ አቅም አለመኖርና መዳከም የአገሪቱን ፈተና ከድጡ ወደማጡ እየከተታት ይገኛል። በሐገሪቱ እየተፈጠሩ ካሉ ትርምሶች ጀርባ የቀደመው በእነ ጌታቸው አሰፋ የተበተነው የደህንነት ሐይል ብቻ ሳይሆን ከለውጡ ጋር የቀጠለው በመንግሥት እንጀራውን የሚጋግረው አቅመ ቢስ ጀሮ ጠቢዎች እኩል እንደሕወሓት ሰዎች መንግስትን ሲሳደቡና ሲያራክሱ ከተቀጠረበት መረጃ የሚወስዱ እንጅ መረጃ አፈንፍነው ማምጣት የማይችሉ መረጃ ሻጮች ጭምር ተሳታፊ ስለሆኑ ነው። ስለእናት ሐገራቸዉ እውቀታቸውንና ጊዜያቸውን ጉልበታቸውን አሳልፈው የሰጡ ቁርጠኛ የኢትዮጵያ ልጆችን ድካም ከንቱ እየሆነ ያለው በእነዚህ የሚበሉበትን ወጭት በሚሰብሩ ሰዎች የተነሳ ነው።

የሐገሪቱን ሕልውና አደጋ ላይ የጣለው የደህንነት ክንፉ ሽባ መሆን ነው። የክልል የቢሮ ኋላፊዎች በሚኒስተር ማዕረግ ያሉ እንጀራቸውን በብልፅግና የሚጋግሩ ደሞዝተኞች ባለ ቪ-8 አሽከርካሪዎች ስለአገር የሚቆረቆሩ ሰዎችን የመንግስት ተቀላቢ ወይም ተከፋ እያሉ የሚሳደቡ ገቨርመንትና ስቴትን ለይተው የማያውቁ የወያኔን አጀንዳ ሌት ተቀን የሚያሳልጡ ሰዎች እነሱ ሞራል ኖሯቸው ከመንግስት ቀለብተኝነት(እንዴት ስድብ እንደሆነ ሊገባኝ አይችልም) ልውጣና ልሳደብ እንኳን ባይሉ በመዋቅሩ ውስጥ እንዲቀጥሉና ሐገርን ከውስጥ በኩል እንዲያፈርሱ የሚመቻችበት እድል ተሰጥቶ ይህ እንደ ዲሞክራሲ ሲተረጎም የሚታይበት አግባብ የተፈጠረው ከመንግስት የማድረግ አቅም ማነስ ስለመነጨ እንደሆነ ነው የሚሰማኝ። Freedom of Expression ማለት መሳደብ ወይም የሰዎችን ስብዕና መንካት አገር አፍራሽ የሆነ ሐሳብ ማራመድ እንደማለትም አይደለም ሲተረጎም። የትም አለም ላይ በዚህ አግባብ አይሰራም ። የደህንነት ክንፉ ሽባ መሆንን ተከትሎ ማንም እየተነሳ አገር አፍራሽነቱን እንዲያውጅ እድል አልሰጠውም ማለት አይቻልም።

የመንግስት አፍ የሚባለው የመንግስት ኮሙኒኬሽንን ጨምሮ የመንግስት ሚዲያዎች አጀንዳ በመስጠት የአንድ ተቃዋሚ ግለሰብን ያህል ተፅዕኖ ያለመፍጠራቸው ምክንያት የተወሳሰበ አይደለም።

መረጃ ፖለቲካ ነው። መረጃ ደህንነት ነው። ጭራሽ የሴራ ፖለቲካ ያለ በቂ መረጃ የማይታሰብም ነው። ወያኔ የመንግስትንም ሆነ የአማራን ሕዝብ በተመለከተ ከበቂ በላይ መረጃ የነበረውና አሁንም የተሻለ መረጃ ያለው አሸባሪ ነው። ለዛም ነው የአማራን የፌስቡክ ብሔርተኝነትና ፖለቲካን በቀላሉ ተቆጣጥሮ ዋና ተቆርቋሪና አስጨፋሪ መሆን የቻለውም። የወያኔ እጅ የሌለበት ፖለቲካ በየትኛውም ብሔር አሁን ላይ እየተጋገረ አይደለም። በተቃራኒው በደሳለኝና በመሰለኝ ለመተንተን የሚሞክረው በአማራ ስም የሚንቀሳቀሰው አብዛኛው የፖለቲካ ኤሊት ቀርቶ መንግስት ነኝ የሚለው አካል በትግራይ ክልል መቀሌ አካባቢ ስላለው ሁኔታ አፉን ሞልቶ እንዲከራከር የሚያስችለው በቂ መረጃ ስለመኖሩ እጠራጠራለሁ። በወያኔ አማካኝነት ለራሱ የሚጠቅመውን መረጃ ከሚያደርሰው ውጭ የተለየ በራስ መንገድ የሚገኝ የተረጋገጠ መረጃ የማግኘት እድሎች ልክ እንደ አማራ ክልል ፖለቲካ ክፍት እንዳልሆነ ይሰማኛል። ነገሮች በዚህ የሚቀጥሉ ከሆነ ወደትክክለኛው መፍትሔ ለመድረስ እጅጉን አስቸጋሪ ነው።

ወያኔ አሁን ላይ ወረራ ከመጀመሩ በፊት ጦርነቱን መንግስት በሚመራው ክልል ላይ አስገብቶታል። ያለግጭት ሕልውና የሌለው ወያኔ በእጅ አዙር መስራት የሚገባውን ስራ ሰርቶ ለዳግም ወረራ አዘናግቶ ጦርነት መክፈቱ የማይቀር ነው።

እርግጥ ነው ወያኔ የኢትዮጵያን ሰራዊት በጦርነት ለማሸነፍ የሚያስችል በሰው ሃይልና በትጥቅ የደረጀ ቁመና የለውም። ነገር ግን ቀድሞ በዘረጋው መዋቅርና ባፀደቀው ሕግ እየታገዘ በሐገሪቱ አንዳንድ አካባቢዎች ቀድሞ ባደራጃቸውና ተልዕኮ ሰጥቶ ባሰማራቸው አካላት በኩል አላማውን ለማስፈፀም እየሰራ ሲሆን ሕዝቡን ደግሞ በተዛባ መረጃ በመንግስት ላይ እንዲነሳሳ የሚያደርገውን ሙከራ ተስፋ የሚያስቆርጠው ሳይሆን እንዲገፋበት የሚያደርገው ነው። የመረጃ ብልጫ ያለው አካል የሚዲያ hegemony የመውሰድ ዕድሉ ከፍተኛ ነው። ቀድሞ አጀንዳ ፍሬም በማድረግ አላማውን እንደጠላት በሚቆጥሩ አካላት ጭምር ሁሉ እንዲሸጥና ጉዳያቸው አድርገው እንዲሰሩበት የሚያደርግ ነው። ሕዝቡ በመንግስት ላይ እንዲማረርና ተስፋ እንዲቆርጥ ወያኔ በርትቶ እየሰራ ነው። የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ስም በሕዝቡ እንዲጠፋና ደጀን እንዳይኖረው ለማድረግ የኦነግ ጦር እንደሆነ ሲገልፅ ከውስጥ በኩል ደግሞ እርስ በራሱ ወታደሩ እንዳይተማመን በሴራ አለ ሴራ በቀላሉ ለመበታተን የሚያደርገው ሙከራ የሚናቅ አይደለም። የአንዲትን አገር የመጨረሻ የሕልውናዋ ምሽግ የሆነውን መከላከያን ለዛውም የራስን ጦርነት እየተዋጋለት በአደባባይ የሚሰደቦበትና ያለ ስሙ ስም እየተሰጠ ፕሮፖጋንዳ የሚሰራበትና መንግስት ተብዬው ጥሩ አደረጋችሁ በሚመስል መልኩ በዝምታ የሚያልፍበት አገር የትም አይገኝም። ሩሲያ ከዩክሬን ጋር ጦርነቱን ስትጀምር የመከላከያ ሰራዊቷ ላይ ስም የሚያጠፋ ማንም አካል እስከ 15 ዓመት እስር እንደሚጠብቀው እንዲያውቅ አዋጅ ያወጣችው።
አበው ጦር ከፈታው ወሬ የፈታው የሚሉት እንዲሁ አይደለም።
ጀኔራል ሰን ዙ የው ግዛትን 33 ሺ ጦር ይዞ ግዙፉን የቹ ግዛት የኗኗን በመቶ ሺ የሚቆጠርን ጦር ያሸነፈው እንደወያኔ የውሸት መረጃ በመርጬት በቹ ግዛቶች ገብቶ በተለያዩ አካባቢዎች ላይ ጥቃት በመክፈት በኗኗ ላይ እንኳን ሕዝቡ ጦሩ ራሱ እምነት እንዳይኖረውና ከኗኗ እየወጣ ለሰን ዙ ጦር እጅ እንዲሰጥ ገሚሱ ደግሞ ከጦሩ እየሾለከ እንዲጠፋና ጦሩ እንዲበተን ማድረግ ስለተቻለ ነበር።
ወያኔ አሁን እያደረገ ያለው የኢትዮጵያን ጦር በተለይ የአማራ ልዩሃይልን በወያኔ ናፋቂ በተተፉ አቅመ ቢሶች በኩል የጋራ ኮዝ እንዳይኖረው በማድረግ ልዩሃይሉን የዳቦ ስም በመስጠት ለመበተን ሲደከም ተከርሟል። ሕዝቡን ደግሞ በተለያየ መንገድ እንዲማረርና አልፎም በመንግሥት ላይ በአመፅ እንዲነሳ ለማድረግ ያልተቋረጠ ስራ እየተሰራ ነው። አንዴ የተመረጡ አካባቢዎች ላይ ጭፍጨፋ በመፈፀም ሌላ ጊዜ ደግሞ በሐይማኖት ስም እየተደረገ ያለው ስራ ለወያኔ መንገድ ጠረጋ ነው። ይህን አጀንዳ ወያኔን እንደጠላት የሚቆጥሩት ወይም እንታገለዋለን የሚሉ አካላት ሳይቀር አጀንዳውን ተቀብለው የማሻሻጥ ስራውን እያቀላጠፉትለም ነው። ዲስፕሊንድ ያልሆነ ኮዝ የሌለው በጠንካራ የወታደራዊ ስነ-ስርዓት የማይመራ ሰራዊት በየትኛውም ሁኔታ የሚሰጠውን ተልዕኮ ለማሳካት በበከፍተኛ ሞራል ተሞልቶ እስከመጨረሻው በፅናት ቆሞ ሊታገል አይችልም።

በናፒር በሚመራው የእንግሊዝ ጦር በአፄ ቴዎድሮስ ላይ ብልጫ የወሰደው በወታደራዊ ስርዓት የተሻለ ስለነበረ ነው። የናፒር ጦር ስለ አፄ ቴዎድሮስና ስለ ሕዝቡ ሁኔታም ከበቂ በላይ መረጃ ስለነበረው በክፍተቱ መጫወት ስለቻለም ነበር።

ጀኔራል ሰን ዙ ጥቂት ጦር እየመራ የኗኗን ግዙፍ ጦርን በራሱ በቹ ግዛት ጠልቆ ገብቶ ማሸነፍ የቻለው በበቂ መረጃ ተመርኩዞ በተዛባ በውሸት መረጃ በማጭበርበር ጦሩን አሳስቶ በሕዝቡ ቅሬታና ጥያቄ በኩል አልፎ ጦርነቱን መምራት ስለቻለ ነበር። የሰን ዙ ጦር ተቆራርጦ በቹ ግዛት የሽምቂ ውጊያ ማድረግ የቻለው የቹ ሕዝብ በኗኗ እና በጦሩ ላይ የተማረረ ስለነበረ ለሰን ዙ ምሽግ ሆኖ ስላገለገለው ነበር።

በናፔር የሚመራው የእንግሊዝ ጦር ስለ አፄ ቴዎድሮስ ጦርና ስለሚመራው ሕዝብ በቂ መረጃ ነበረው እንጅ የአፄ ቴዎድሮስ ጦር በናፔር ስለሚመራው የእንግሊዝ ጦር በቂ መረጃ ነበረው ለማለት የሚያስደፍር ነው ለማለት አያስደፍርም።
አፄ ቴዎድሮስ ስለኢትዮጵያ በክብር የወደቀው ቀድሞ በራሱ ኤሊትና ሕዝብ ስለተካደ ነበር። ሕዝቡንና ኤሊቱን ከአፄ ቴዎድሮስ ይልቅ የናፔር ጦር ተጠቅሞበታል።

ሰን ዙ እንዳለው "አሸናፊው ጦረኛ ወደጦርነት የሚሄደው ጦርነቱን አሸንፎ ነው። ተሸናፊው ደግሞ ድልን በጦርነት መሃል ይፈልጋል" ይላል።

ለዚህ ጥሩ ምሳሌ የሚሆነው የአፄ ሚኒሊክ የአድዋ ዘመቻ ነው። አፄ ሚኒሊክ በክተት አዋጃቸው ገና ሳይነሱ ጦርነቱን አሸንፈው ስለመጀመራቸው ማረጋገጫው ".ወስልተህ የቀረህ ግን ትጣላኛለህ አልተውህም። ማርያምን አማላጅ የለኝም" የሚለው አቋማቸው ስለ ድህረ-ጦርነት ሁኔታ ምን ያህል እርግጠኛ እንደነበሩ የሚያመላክት ነበር።

አፄ ሚኒሊክ ስለጣሊያንን ጦር ከበቂ በላይ መረጃ እንደነበራቸውና ይህን የጠላት ሃይል ለመመከትና ጦርነቱን በድል ለመወጣት የሚያስችል ከፍተኛ ዝግጅት ሲያደርጉ ስለመቆየታቸውም በክተት አዋጃቸው ላይ "...በፊት እግዚአብሔር የወሰነልንን ባህር አልፎ(የኢትዮጵያ ደንበር እስከየት እንደሆነ የሚናገርም ነው) መጥቷል፡፡ እኔም የአገሬን ከብት ማለቅ፤ የሰውን መድከም አይቼ እስካሁን
ዝም ብለው( የጠላትን እንቅስቃሴ በተመለከተ ያውቁና ለጠላት የሚመጥን የሰው ሃይልና የትጥቅ ዝግጅት ሲያደርጉ ስለመቆየታቸው የሚያሳይ ነው) ደግሞ እያለፈ እንደፍልፈል መሬት ይቆፍር ጀመር.." የሚለው አቋም ያረጋግጥልናል። በነገራችን ላይ በኢትዮጵያ ታሪክ በእኔ መረዳት ለውጊያ ጦርነቱ ከሚወስደው ጊዜ ይልቅ ለጦርነቱ የሚደረገው ዝግጅት ከፍተኛውን ጊዜ የሚወስድ ነው። ጦርነትን ለማሸነፍ በሰላም ጊዜ ለጦርነት መዘጋጀት የሚለው በተግባር ሲተረጎም ከዚህ የተለየም አይደለም‼️

ወያኔ አሁን እያደረገ የሚገኘው መንግስት በሚያስተዳድረው ክልል በሐይማኖት ስም ወይም ጥቃት እንዲፈፀም በማድረግ ጦርነቱን ራሱ ሕዝቡ እንዲመራለት ማድረግ ነው‼️

ለወያኔ አገር ለማፍረስ እየተሰጠ የሚገኘው እድል በጊዜ እልባት የማይሰጠው ከሆነ ማንም ወደማያተርፍበት አዘቅት ሁሉም ተያይዞ መግባቱ አይቀርም‼️
ታሪካዊ የኢትዮጵያ ጠላቶች ከውስጥ ባንዳዎች ጋር በመቀናጀት አገር አልባ ሊያደርጉን ሁለንተናዊ ዘመቻ መክፈታቸውን፣ በወያኔ በኩል በአዋጅ ግልፅ በሆነ መንገድ ኢትዮጵያን ለማፍረስ "ሲኦልም ድረስ ለመውረድ" ቆርጠው እየሰሩ መሆናቸውን ስለምናውቅ፥ አገር አልባዎች ላለመሆንና የአባቶቻችን ልጆች መሆናችንን ማረጋገጥ ስላለብን እንጅ፤ ብልፅግናንም ሆነ የመንግስት መዋቅርን የተቆጣጠረው በደህንነት ክንፉ ውስጥ ያለው የባንዳ ባንዳ የሆነው አካል ሁሉ እየሰራው ወይም እየሄደበት ያለው የጥፋት መንገድ የማያስቆጣ አይደለም።

መዋቅሩ ራሱ ወያኔ ሰራሽ ሆኖ አሁንም መዋቅሩን የተቆጣጠሩት የወያኔ ናፋቂዎች አቅም በፈጠሩበት ሁኔታ ወያኔን በግንባር ጦርነት ስለማሸነፈ ማሰቡ አድካሚ ነው። ዶ/ር አብይ አህመድ ወያኔ ሰራሹን መዋቅርን ለማስተካከል ጊዜ ያስፈልገዋል ቢባል እንኳን፣ አብዮታዊ ዲሞክራሲ ላይ የተቸነከሩ ናፋቂ ወያኔዎች ላይ ከዛሬ ነገ የማስተካከያ እርምጃ ይወሰዳል ብለን ስንጠብቅ ብንከርምም ይባስ ብሎ የእነሱ መንገድ ሕዝባዊ እውነተኛ እነሱ ደግሞ እንደጀግና እንዲቆጠር የሚያደርግና ሌሎችም መንገዱን እንደራመዱበት የሚያበረታታ ነው።

በሕልውና ጦርነቱ ኢትዮጵያን ለመታደግ ሁለንተናዊ ተሳትፎና መስዋዕትነት በመክፈል ሂደቱ ውስጥ በብልፅግና በመንግስታዊ መዋቅሩ በደህንነቱ ክንፍ ውስጥ ከተሰማራው ከብዙሃኑ ይልቅ በተቃዋሚው ጎራ የተሰለፈው ሃይል ሙሉ በሙሉ ያለምንም ክፍያ ወይም የቀን አበል ሕይወታቸውን ረክሰው ጭምር እስከመዋደቅ ደርሰዋል። በሕልውና ትግሉ እንደተቃዋሚው ወገን የብልፅግና ካቢኔ ኢትዮጵያ ለመታደግ ከመታገል ይልቅ የሚታገሉትን ለመታገል የሞከሩ ቁጥራቸውም ሆነ ተፅዕኗቸው የሚናቅ አይደለም። በተቃዋሚው ወገን የነበረው ሃይል በመንግሥት በኩል ከተሰለፈው ሃይል በተሻለ መስራት የሚገባውን ስርቷል ብቻ ሳይሆን በብልፅግና ውስጥ ያሉ የባንዳዎችን የጥፋትን እንቅስቃሴ በማክሸፍ ጭምር ስራቸውን በመሸፈን ታሪካዊ ግዴታውን ተወጥቷል ማለት ይቻላል።

ከብልፅግና በላይ ብልፅግና ከደህንነት ክንፉ በላይ ደህንነት መስለው ስለእናት አገራቸው ሉዓላዊነትና ነፃነት ስለዘላቂ ጥቅሟ ሲሉ እልፎች እንቅልፋቸውን አጥተው የስም ማጥፋት ዘመቻውን ሕይወታቸውን እያጡ በነበሩ ጀግኖች አንፃር አቅልለው አይተው በፅናትና በድል አልፈውታል። በብልፅግና አመራሮች ሳይቀር የስም ማጥፋት ተካሂዶባቸዋል። በተቃዋሚው በኩል ያለው ሃይል ከብልፅግና በላይ ብልፅግና እንደሆነ ያስመሰለው ሐገሩን በማስቀደሙና ብልፅግና ውስጥ ያለው የባንዳነት ስራ መጉላትም ነው።

ተቃዋሚው ስሙ እስኪጠፋ የሚያደርስ የሚያስገድደው የግል ጉዳይ ኖሮት ወይም በውለታ ታጥሮ ብልፅግና እስከመምሰል የደረሰው የአገር ጉዳይ ስለሆነበት፣ የወያኔ ጠላትነት ላይ ብዥታ የሌለውና በማንኛውም ነገር ወያኔ ሳይከስም ኢትዮጵያ ሰላም ልትሆን ጥቅሟ ሊከበር እንደማይችል የጠራ አቋም ያለው በመሆኑ ነው።

ልባቸውና ቀልባቸው መቀሌ ላይ የሆኑ በብልፅግና በመንግስታዊ መዋቅሩ በደህንነቱ ክንፍ ያሉ ሰዎችን አብይ አህመድ እያየ እንዳላየ እየሰማ እንዳልሰማ ሆኖ የሚያልፈውን ጉዳይ የእሱም ሐሳብና አቋም ያው ነው በሚል ድምዳሜ በነፍጥ ጭምር ብልፅግናን እንደወያኔ ለመዋጋት ወደበረሃ ለመውረድ አንቆ የያዘን አገር አልባዎች የመሆን ስጋትና የአባቶቻችን የመንፈስ ልጆች መሆናችን ነው።

በሐገር ክህደት መከሰስ እንኳን ባይቻል እንዴት አገር እንዲያፈርሱ በስራችሁ ቀጥሉ ግፉበት የሚያስብል ሁኔታዎች ይመቻችላቸዋል?

ልባቸውና ቀልባቸው መቀሌ ላይ ባለ አብዮታዊ ዲሞክራሲ ወይም ሞት! በሚሉ በብልጽግና በመንግስታዊ መዋቅሩ ውስጥ ባሉ አመራሮችና የደህንነት ሰዎች አገር እየተመራች የኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና ነፃነት የሕዝቦቿ ዘላቂ ሰላምና ጥቅም ፈፅሞ ሊከበር አይችልም‼️
FYI:

ማምሻውን ከአማራ ክልል መንግስት የፀጥታ ምክርቤት ከተሰጠ መግለጫ የተወሰዱ ቁልፍ መልዕክቶች👇

👉የወያኔን ዳግም ወረራ ለመቀልበስና ለመከላከል የውስጥ አንድነትን ማጠናከር፣ ሰላምና ደህንነትን መጠበቅ ቁልፍ ጉዳይ ነው ብሎ ያምናል። ህዝባችን ዳግሞ ለወያኔ ወረራ ለጥቃት እንዳይዳረግ እቅድሚያ ሰጥቶ እንደወትሮው ሁሉ የፀጥታ መዋቅሩ፣ ደጀኑ ህዝብ የራሱን ኃላፊነት ለመወጣት ዝግጁ መሆን እንዳለበት አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡

👉በመሆኑም በአንድ በኩል ከፌደራል የጸጥታ መዋቅር ጋር በመቀናጀት ከወያኔ የሚሰነዘርብንን ጥቃት ለመከላከል በተጠንቀቅና በዝግጁነት መቆም፤ በሌላ በኩል ደግሞ በውስጣችን ለወያኔ ሴራ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥሩትን ህገ-ወጦችንና ስርዓት አልበኞችን በመቆጣጠር የክልላችን ሰላምና ደህንነት ማስጠበቅ ግንባር ቀደም የትኩረት አቅጣጫ እንዲሆኑ ወስኗል፡፡

👉 ስለሆነም የክልሉ የጸጥታ ምክር ቤት በየደረጃው የጸጥታ ግብረ ሀይል አቋቁሞ ህገ-ወጥነትን ለመቆጣጠርና ህግን ለማስከበር ተገቢ ነው ያላቸውን ህጋዊ ርምጃ እንዲወስድ አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡