Sadat_Text_Posts
10.7K subscribers
291 photos
8 videos
12 files
378 links
Download Telegram
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
﴿إِنَّ لِلَّهِ مَلَائِكَةً سَيَّاحِينَ فِي الْأَرْضِ يُبَلِّغُونِي مِنْ أُمَّتِيَ السَّلَام﴾
“የህዝቦቼን ሰላምታ ለእኔ የሚያደርሱ በምድር ተንቀሳቃሽ የአላህ መላኢካዎች አሉ።”
📚 ሲልሲለቱ አሶሂሃ: 6853
*****

ከደጃል ፈተና ለመጠበቅ!

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ 
“ከምዕራፍ አልካህፍ የመጀመሪያ አስር አንቀፆችን በጭንቅላቱ የሸመደደ ከደጃል ፈተና ይጠበቃል።”
📚 ሙስሊም ዘግበውታል: 809
*****

  ማሰታወሻ
  ሱረቱል ካህፋ መቅራት አንረሳ
*****

እህቴ ተጠንቀቂ!

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
﴿أيما امرأةٍ استعطرتْ فمرتْ على قومٍ ليجدوا من ريحِها فهي زانيةٌ﴾
“ሽቶ ተቀብታና መዓዛው እንዲያውዳቸው አስባ በሰዎች አጠገብ የተላለለፈች ማንኛዋም ሴት ዝሙተኛ ነች።”
📚 ነሳዒ ሶሂህ ብለውታል: 5141
*****

  ጌታችን ይገረማል!
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
﴿إنّ ربَّك ليَعْجَبُ من عبدِه إذا قال: ربِّ اغفر لي ذنوبي، وهو يعلمُ أنّهُ لا يغفرُ الذنوبَ غيرِي.﴾
“ጌታችሁ እንዲህ ብሎ በሚናገረው ባሪያ ይገርማል። ‘ጌታዬ ሆይ ለወንጀሌ ምህረትን አድርግልኝ’ እሱም ያውቃል ከኔ ውጪ ወንጀልን የሚምር እንደሌለ።”
📚 ሶሂህ አልጃሚ: 2069
*****

አትቆጣ!

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
﴿ليسَ الشَّدِيدُ بالصُّرَعَةِ، إنَّما الشَّدِيدُ الذي يَمْلِكُ نَفْسَهُ عِنْدَ الغَضَبِ.﴾
“ጀግና ማለት ታግሎ የሚጥል ሳይሆን በንዴት ግዜ እራሱን የሚቆጣጠር ነው።”
📚 ቡኻሪ (6114) ሙስሊም (2609) ዘግበውታል
*****

ለልጆች የሚደረግ መለኮታዊ ጥበቃ!

ከኢብኑ አባስ (رضي ﷲ عنهما) ተይዞ:  እንዲህ ይላል፦
የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ) ለሀሰንና ለሁሰይን እንዲህ እያሉ ጥበቃ ያደርጉላቸው ነበር፦
﴿أُعِيذُكُمَا بِكَلِمَاتِ اللَّهِ التَّامَّةِ مِنْ كُلِّ شَيْطَانٍ  وَهَامَّةٍ ، وَمِنْ كُلِّ عَيْنٍ  لَامَّةٍ﴾
“ምሉዕና ፍፁም በሆኑት የአላህ ቃላት ከሰይጣናት ሁሉና ከእኩይ ሰው (ተንኮል) እንዲሁም ጎጅ ከሆነ ዓይን ሁሉ እጠብቃችኃለሁ፡፡”
📚 ቲርሚዚ ዘግበውታል: 2060
*****

«🔹በካፊሮች በዓል እንኳን አደረሳችሁ ማለት አይፈቀድም  ምክንያቱም ያሉበትን ክህደት ( ኩፈራችውን) መደገፈ ነው ።
(فَلَا تُطِعِ ٱلۡمُكَذِّبِینَ * وَدُّوا۟ لَوۡ تُدۡهِنُ فَیُدۡهِنُونَ * وَلَا تُطِعۡ كُلَّ حَلَّافࣲ مَّهِینٍ)
አስተባባዮችንም አትታዝዙ፡፡ ብትመሳሰላቸውና ቢመሳሰሉህ ተመኙ፡፡
*****

የጁሙአ ልዩ ሰጦታ                        
ከጃቢር  رضي الله عنهእንደተላለፋው ነብዩ صلى الله عليه وسلم   እንዲህ ብለዎል
የጁሙአ ቀን አንዲት ሰአት አለች በዛ ሰአት الله  ሚጠይቅ 
ሙስሊም  አይኖርም  የጠየቀውን
ቢሰጠው እንጂ   የመጨረሻዋ ሰአት ተጠባበቋት ከአስር በኋላ
  አብዳውድ ዘገበውታል
በዱአ በርቱ እኔንም እንዳትረሱኝ አደራ
*****

እህቴ ተጠንቀቂ!

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
﴿أيما امرأةٍ استعطرتْ فمرتْ على قومٍ ليجدوا من ريحِها فهي زانيةٌ﴾
“ሽቶ ተቀብታና መዓዛው እንዲያውዳቸው አስባ በሰዎች አጠገብ የተላለለፈች ማንኛዋም ሴት ዝሙተኛ ነች።”
📚 ነሳዒ ሶሂህ ብለውታል: 5141
*****

ማስታወሻ፡
ቀኑ ጅምአ ነው በግዜ ተገኝ እንዲሁም ስለዎት እንብዛ الله ይረዳን
*****

ይገረማል!

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
﴿إنّ ربَّك ليَعْجَبُ من عبدِه إذا قال: ربِّ اغفر لي ذنوبي، وهو يعلمُ أنّهُ لا يغفرُ الذنوبَ غيرِي.﴾
“ጌታችሁ እንዲህ ብሎ በሚናገረው ባሪያ ይገርማል። ‘ጌታዬ ሆይ ለወንጀሌ ምህረትን አድርግልኝ’ እሱም ያውቃል ከኔ ውጪ ወንጀልን የሚምር እንደሌለ።”
📚 ሶሂህ አልጃሚ: 2069
*****

📖አያተል ኩረስይን ም ማንበብ!!!

የالله መልክተኛ صلى الله عليه وسلم አያተል ኩረስይን ከግዴታ ከሰላት ቦሃላ የቀራ ጀነት ከመግባት ምንም አይከለከለውም ሞት እንጂ
📚ሲልሲለቱ አሰሂህ 972
*****

አላህ ለወንጀሉ ምህረት ያደርግለታል…

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
“ዑዱውን ለሰላት አሳምሮና በተሟላ መልኩ ያደረገ፤ ከዛ ለግዴታ ሰላት ጉዞ አድርጎ በመስጂድ ውስጥ ከሰዎች ጋር ወይም በጀምዓ  ( በመስጅድ) የሰገደ። አላህ ለወንጀሉ ምህረት ያደርግለታል።”
📚 ሙስሊም ዘግበውታል: 232
*****

መከራ የገጠመውን ሰው ሲያዩ የሚባል ዱዓ

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
“መከራ ያገኘውን ሰው የተመለከተ ከዛም ይህን ዱዓ  ‘አንተን ከሞከረህ ነገር ለጠበቀኝ ከፍጡራኖቹ ከብዙዎች ላላቀኝ አላህ ምስጋና ይገባው’ ያለ። መከራው አያገኘውም።”
📚 ሲልሲለቱ አሶሂሃ: 2737
*****

እሬቻ እንደ ኢስላም ?

1 የሸረክ ተግባረ የሚፈፀምበት
2 ከእስልምናችን ጋር በጣም የሚገጭ
ማንኛውም ሙስሊም የሆነ ሰው ወደዚህ ቦታ ከመሄድ ሊቆጠብ ይገባል።
ወላጆች ልጆቻችሁን ልታስተምሩና ልትከለክሉ ይገባል።
ዳዒዎች በተለይም  የኦሮምኛ ቋንቋ የምትችሉ ልታሰጠነቅቁ ይገባል ።            ፡الله ይጠበቅን
*****

🔰ከቀናቶች በላጬ የጁምአ ቀን ነው።

ረሱልም (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
﴿إنَّ مِن أفضَلِ أيّامِكم يومَ الجُمعةِ، فأكْثِروا عليَّ الصلاةَ فيه؛ فإنَّ صلاتَكم مَعروضةٌ عليَّ.﴾
“ከቀናችሁ ሁሉ በላጩ የጁምዓ ቀን ነው። በዚህ ቀን በኔ ላይ ሰለዋት ማውረድ አብዙ። ሰለዋታችሁ ለኔ ይቀርብልኛልና።”
📚 አቡ ዳውድ ሶሂህ ብለውታል: 1531
*****

#የሰደቃ ትሩፋት!
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
﴿داوُوا مَرضاكُمْ بِالصَّدقةِ﴾
“በሽተኞቻችሁን በሰደቃ አክሙ።”
📚 ሶሂህ አልጃሚዕ: 3358
*****

ሶላት!

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
“በትንሳኤ ቀን አንድ ባሪያ በቅድሚያ ከሚጠየቅባቸው ሥራዎች አንዱ ሰላቱ ነው። እሱ ከተስተካከለ ሌሎች ስራዎቹም የተስተካከሉ ይሆናሉ። እሱ ከተበላሻ ሌሎች ስራዎቹም የተበላሸ ይሆናሉ።”
📚 ቲርሚዚ ሶሂህ ብለውታል: 413
*****
ለቅሶዋችሁ በበዛ ነበር!
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
﴿وَاللَّهِ لَوْ تَعْلَمُونَ مَا أَعْلَمُ لَضَحِكْتُمْ قَلِيلًا وَلَبَكَيْتُمْ كَثِيرًا﴾
“ወላሂ! እኔ ማውቀውን ብታውቁ ኖሮ፣ ጥቂት ስቃችሁ ብዙ ባለቀሳችሁ ነበር።”

📚 ቡኻሪ ዘግበውታል: 1044
*****

🚨በተለይ ሁለት ወቅቶችን ጠብቀህ ስገድ🚧

ነቢዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
“ፀሀይ ከመውጣቷ እና ከመግባቷ በፊት የሰገደ አንድም ሰው እሳት አይገባም።”
ማለትም፦ የፈጅርና የአስር ሶላቶች።

📚 ሙስሊም ዘግበውታል: 634
*****

የባሰ የከፋ ነው!

💎ብስራት የረሱልንصلى الله عليه وسلم) ሀዲስ ለሚያሰራጭ!

ረሱል (صلى الله عليه سلم) እንዲህ ብለዋል፦
﴿نضَّرَ اللهُ امرأً سمِعَ مَقالتي فبلَّغَها﴾
“አላህ ፊቱን ያብራለት ንግግሬን ሰምቶ ላደረሰው (ላስተላለፈው) ሰው።”
📚 ኢብኑ ማጃህ ሶሂህ ብለውታል: 189
*****

🤎 ልብህን ጠይቅ!

ከነውዋስ ኢብኑ ሰምዓን (رضي الله عنه) ተይዞ፡ ነብዩ (صلى الله عليه وسلم) እንዲህ ብለዋል፦
“በጎ ነገር ማለት መልካም ስነ-ምግባር ነው። ወንጀል ማለት በደረትህ ውስጥ የተመላለሰ እና ሰዎች በሱ ላይ ሆነህ ቢያዩህ የምትጠላው ነው።”
📚 ሙስሊም ዘግበውታል፡ 2553
*****

⚠️⚠️ ከእሳት ውስጥ ነው…

ረሱል (صلى الله عليه وسلم) እንዲህ ብለዋል፦
﴿ما كان أسفَلَ مِنَ الكَعبَيْنِ مِنَ الإزارِ؛ فهو في النّارِ﴾
“ልብሱን (ኢዛሩን) ከቁርጭምጭሚት በታች አውርዶ የለበሰ ከእሳት ውስጥ ነው።”
📚 ቡኻሪ ዘግበውታል: 5787
⚠️🛑🛑ወንድም "ኢሳም ሐበሻ" 🛑🛑
🤲 አላህን ፍራ።

✔️ፊልም ትተህ በመምጣትህ በጣም ተደሰትናል አልሐምዱሊላህ።

🛑"ኢስላማዊ" ብለህ ግን ሰው ስታሳስት ጥፋትህ እጥፍ ድርብ ይሆናል። 

"ኡስታዞች" የሚባሉት ስታጠፋ ዝም ስላሉህ ሐቅ ላይ ነህ ማለት አይደለም። እነሱ ታላቁ ወንጀል ሺርክ (በአላህ ላይ ማጋራት) ቢፈፀምም ዝም ነው የሚሉት።

😀 ፕሮግራምህ ላይ ቶርታ ኬክ ካስቆረስካቸው ሰዎች ውስጥ በአላህ ላይ ማጋራት ያለባቸው የክህደት ጭፈራ ስብስቦች ላይ በደስታ አብሮ የሚጨፍር ሰው ይገኝበታል። እንዲህ አይነት ሰዎች ጋር አብርህ የምትሰራቸው ስራዎች ስህተትህን ይበልጥ ያገዝፉብሀል። ወደ አላህ ተመለስ።

💊 ለነፍስህ ፍራ። "25 አመት ፊልም ኢንዱስትሪ ላይ ነበርኩ።" ትላለህ። 25 አመት የሸሪአ እውቀት መሰብሰብ ላይ እኮ አልነበርክም። እንዴት በጥፋት ዘመን ላይ የኖርክበትን ዛሬ ለመስራት ላሰብከው የጥፋት "x ኢስላማዊ ፊልም" መንደርደሪያ ታደርገዋለህ?

🔑 ይልቁንም ለነፍስህ እዘንላት ሀይማኖትህን ተማር እና ወሎ፣ ሰሜኑ ኢትዮጵያ፣ መላው ኢትዮጵያ ላይ አላህ ንሰሃ ሳይገባ ለሞተ ሰው የማይምረው ወንጀል ሺርክ (በአላህ ላይ ማጋራት) ይሰራል። ሰውን በአላህ ፍቃድ ከዚህ ክህደት እንዲወጣ ተምረህ አስተምር ይህም የነብያት መንገድ ነው።

ወሎ ላይ
📱📱📱📱📱📱📱
1) የቦረናው ደግዬ እርዱኝ አባብዬ ይባላል። ይሄ ክህደት ነው።
2) ሙወከል እየተባለ ለሰይጣን ለነ ሰይፉ ጨንገሬ ይታረዳል። ይሄም ከኢስላም ያስወጣል።

📱📱📱📱📱📱📱

ታድያ ይሁ ሁሉ ክህደት እና በአላህ ላይ ማጋራት ያለበትን የኢትዮጵያ ህዝብ ጭራሽ ፊልማቸው ኦርቶጉል ውስጥ ኩፍር የጨመሩትን ቱርኮች አንት ልትሰራ ላሰብከው "ፊልም" ጭራሽ እርዳታ መጠየቅህ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ አይሆንምን?

🛑ወንድሜ መልካም ነገር ማለት አንተ መልካም ያልከው ሳይሆን ኢስላም መልካም ያለው ነው።

🎧 ኢስላምን ለማገዝ ከቁርአን ከሐዲስ ኡለማዎች ከሄዱበት መንገድ ውጭ ያለው ሁሉ የጥፋት መንገድ ነው።

😀 ገንዘብ እና ጊዜህን በጥፋት መንገድ ላይ አታባክን።

አላህ ፊት ብቻችንን ራቁታችንን የምንቆምበት ቀን አለ።

😀 ለአላህ ብለህ ተወው። አላህ በተሻለ እሱ በሚወደው፣ ወደሱ ለሚያቃርብህ አምልኮ አንተንም እኛንም ይለግሰን።
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
*️⃣*️⃣*️⃣ኢንሻ አላህ *️⃣*️⃣*️⃣

እሁድ ከጠዋቱ 3 ሰኣት ጀምሮ እስከ ዙሁር በሑዘይፋ መስጂድ የዳእዋ ፕሮግራም ይኖራል።

ፕሮግራም አቅራቢዎች

1️⃣🔁ኢብኑ ሙነወር፣

2️⃣🔁አቡ ኡስዋ፣

3️⃣🔁ሳዳት ከማል፣

4️⃣🔁አብዱ ሰኢድ፣

5️⃣🔁አማር በህረዲን።

ፕሮግራሙ ከሚያካትታቸው ትምህርቶች ውስጥ

1️⃣🔤ቁርኣንን በጥሞና ማዳመጥ፣

2️⃣🔤አቀራራችን ማስተካከል፣

3️⃣🔤የተመረጡ ምእራፎች የቁርአን ትርጉም፣

4️⃣🔤ዳእዋ እና ሌሎችም

ለሴቶች በቂ ቦታ አለ።
🚘🚘🚘🚘🚘🚘🚘🚘
አድራሻ ሸገር ሲቲ ከየሺ ደበሌ ከፍ ብሎ።
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Live stream started
Live stream finished (10 seconds)
🛑🛑🛑ኢንሻ አላህ 30 የነብዩ ﷺ ሐዲሶች በአንድ ቀን ይማሩ።

ይህ አጭር ኮርስ እሁድ

🕓ከ ጠዋቱ 3:00 እስከ ዙሁር።

📖📚ኪታቡ ቦታው ላይ በነፃ ይሰጣል። 4000 ኮፒ ኪታብ አለ አያስቡ።

ከእነ ቤተሰቦ ተጋብዘዋል።

ከእርሶ ምን ይጠበቃል?

✏️ማስታወሻ ለመያዝ እስክርቢቶ እና እርሳስ፣ ብሎም ጊዜዎን መስጠት።

ትምህርቱ ለሁሉም እድሜ ክልል የተዘጋጀ ነው።

ለሴቶች በቂ ቦታ አለ።

መልክቱን በማሰራጨት የአጅሩ ተካፋይ ይሁኑ።

🚘🚘🚘🚘🚘🚘🚘🚘
አድራሻ ሑዘይፋ መስጂድ ሸገር ሲቲ ከየሺ ደበሌ ከፍ ብሎ።
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
🆕🔴የመልካም ስራ ጥሪ
አሰላሙ ዐለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱ

بسم الله الرحمن الرحيم

⭐️እንደሚታወቀው መረከዝ አቡ ሙሳ አልአሽዐሪ ላለፉት 4 አመታት ገደማ የቁርአን ሂፍዝና ተያያዥ የተረቢያ ትምህርቶችን በተለያዩ መርሀግብሮች ማለትም በአዳሪ፣ በተመላላሽና በርቀት በርካታ ተማሪዎችን አስተምሮ ለውጤት በማብቃት ኡማውን በዲኑ የሚያገለግሉ ተተኪዎችን በማፍራት የበኩሉን አሰተዋፆ ሲያበረክት ቆይቷል ።

📸እነሆ አሁን ላይ መርከዙ ተደራሽነቱን በማስፋት በ3ቱም ቅርንጫፎች በበይነ መረብ የሚማሩትንም ጨምሮ ቁጥራቸው ወድ 400 ገደማ የሚደርሱ ተማሪዎችን እያስተማረ ይገኛል ።

አንዱ ቅርንጫፍ 30 አከባቢ የሚሆኑ ተማሪዎችን ያለ ምንም ክፍያ የምናስተምር ሲሆን በ2ቱ ቅርንጫፎች ላይ መክፈል ለማይችሉ የግድ መማር ያለባቸው 10ራ ምናምን ተማሪዎችን እና በ ኦንላይን በርከት ያሉ ተማሪዎች በነፃ ተቀብለን እያስተማርን እንገኛለን ።
አጠቃላይ በነፃ የምናስተምራቸው ተማሪዎች አሁን ላይ ቁጥራቸው ወድ 45 አከባቢ ደርሷል ።

☑️እኛ አቅማችን በሚችለው አላህ በረካ አድርጎልን  ይሄን ያክል ርቀት ተጉዘናልና እናንተስ ለቀጣዩ ፕሮጄክታችን ልታግዙን ዝግጁ አይደላችሁም ?  ዛሬ ስለሱ ይሆናል የምናወራው።

🥳ይሄንን ሁሉ ስናድርግ ሁሉም ነገር አልጋ በአልጋ ሆኖልን ሳይሆ በጣም ብዙ ቻሌንጆችን በመቋቋም መሆኑን እንድትረዱልን እንፈልጋለን ። በጣም ብዙ ውጣ ውረዶች ..
አሁን ላይ ግን አንዱንና ዋነኛውን ነው የምንነግራቹህ ። እሱም ቋሚ የሆነ ቦታ አለማግኘታችን እና በቤት ኪራይ መሰቃየታችን ትልቁ ተግዳሮታችን ነው ።

📣ስለሆነም እነሆ ዛሬ ላይ የሙስሊሙን ማህበረሰብ እገዛ ፈልገን የመጣነው በዚሁ ጉዳይ ላይ ነውና በአላህ ፍቃድ በህይውት እስካለን ድረስ ኢስላማዊ ሀለሰፊነታችንን የምንወጣበት እና ለልጆቻችንና ለቀጣዩ ትውልድ መልካምን ነገር ያስቀጥል ዘንድ ይሄንን መርከዝ ገንብተን ለማስረከብ ሁላችንም የበኩላችንን አሰተዋፆ እንድናበረክት በአለሰህ ስም እንጠይቃለን ።

ይሄንን በማስመልከት ታላቅ የዳዕዋና የኒያ ፕሮግራም አዘጋጀተናል። እርሶም እንዳይቀሩ በክብር ተገሰብዘዋል።

😬የእለቱ ተጋባዥ እንግዱች ▶️

ኡስታዝ  ሳዳት ከማል
ኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር
ኡስታዝ ሙሐመድ ሲራጅ
ሸይኽ   አወል ኬሚሴ
ኡስታዝ ኸድር ኬሚሴ
ኡስታዝ አቡ ሙሰሊም

😓እሁድ ማታ ከተረዊህ ሰላት በሇላ
4️⃣🔤1️⃣5️⃣


💎ፕሮግራሙ የሚካሄድበት የተሌግራም ግሩፕ⤵️
https://t.me/merkezabumussa1
https://t.me/merkezabumussa1

ውድና የተከበራቹህ ሙስሊም ወንድምና እህቶች፣ የቁርአንና ሱና ወዳጆች ይሄንን ፕሮግራም ሼር በማድረግ የአጅር ተካፋይ እንድትሆኑ ለማስታወስ እንወዳለን ።
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Forwarded from SadatKemal Abu Meryem
35 የነብዩ (ﷺ) ሐዲሶች.pdf
804.3 KB
⛔️35 የነብዩ (ﷺ) ሐዲሶች⛔️
የኪታቡ ፒዲኤፍ (pdf)
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
35 የነብዩ (ﷺ) ሐዲሶች
Sadat
🆕35 የነብዩ (ﷺ) ሐዲሶች🆕
የኪታቡን ፒዲኤፍ (pdf) ከሚከተለው ሊንክ ያግኙ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem/7256
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Forwarded from SadatKemal Abu Meryem
35 የነብዩ (ﷺ) ሐዲሶች
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem/7257
የኪታቡን ፒዲኤፍ (pdf) ከሚከተለው ሊንክ ያግኙ
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem/7256
ዘካተል ፊጥርና ኢድ
Sadat
ዘካተል ፊጥርና ኢድ
Forwarded from SadatKemal Abu Meryem
ዘካተል ፊጥርና ኢድ
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem/3057
🛑🛑🛑የፊታችን እሁድ

በአሸዋ ሜዳ ጉቱ አቡበክር መስጂድ
ኢንሻ አላህ 30 የነብዩ ﷺ ሐዲሶች
በአንድ ቀን ይማሩ።

ይህ አጭር ኮርስ እሁድ

🕓ከ ጠዋቱ 2⃣ : 3⃣0⃣እስከ ዙሁር።

📖📚ኪታቡ ቦታው ላይ በነፃ ይሰጣል።

ለሴትም በቂ ቦታ አለ።

ከእርሶ ምን ይጠበቃል?

✏️ማስታወሻ ለመያዝ እስክርቢቶ እና እርሳስ፣ ብሎም ጊዜዎን መስጠት።

ትምህርቱ ለሁሉም እድሜ ክልል የተዘጋጀ ነው።

መልክቱን በማሰራጨት የአጅሩ ተካፋይ ይሁኑ።

🚘🚘🚘🚘🚘🚘🚘🚘
አድራሻ አሸዋሜዳ ጉቱ ሪል እስቴት አቡበክር መስጂድ።

https://maps.app.goo.gl/B1rgP1vf2gr4G9VbA?g_st=atm

https://t.me/SadatKemalAbuMeryem
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Forwarded from عبدالكريم via @Qualitymovebot
🍃መውሊድን የተመለከተ🍂

{ በኡስታዝ ኢብኑ ሙነውር }
የተዘጋጁ ፅሁፎች ስብስብ ከስር ርዕሳቸውን
በመጫን ታገኛላችሁ👇