Forwarded from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
አሽሙር "የሚፀየፉ" አሽሙረኞች!!
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
እኔ እምለው አሽሙር አሽሙር የሚሉ በዙ ልበል?
ደግሞኮ ይህንኑ ሐሳባቸውን በአሽሙር ነው የሚገልፁት። በግልፅ "እነ እከሌን አትንኩብን" ብትሉ አይሻልም? ምነው ፍላጎታችሁን ለመግለፅ ዳር ዳሩን ትዞራላችሁ?!
።
እንጂ ኢንሷፍ ቢሸታችሁ እነዚህን እዚያ ሰፈር ደጋግመን የምንሰማቸውን ውንጀላዎች ዝም ባላላችሁ ነበር።
* "ጉላት (ወሰን አላፊዎች)"፣
* "ፅንፈኞች"፣
* "ሐዳዲያ"፣
* "ላይክና ሼር መቃረም የሚፈልጉ"፣
* "የደጋፊ ሽሚያ ውስጥ የገቡ"፣ "ደጋፊ ለማብዛት የሚሯሯጡ"
* "የሰለፍያ ጭምብል የለበሱ"፣
•
•
•
ይህ ሁሉ ሲባል ምን ብላችኋል? የትስ ነበራችሁ?!
•
ደግሞ ምነው ይህን በሰለፍዮች ላይ የሚያሳዩትን ጀግንነት ኢኽዋንም ላይ እያሳዩን ምንም ቢሉን በቻልናቸው!!
•
* ይሄው ከስር በሐዳዲይነት ሲፈርጁ። ከዚያ ደግሞ ሌላ ገፀ ባህሪ ተላብሰው ሪፍቅ፣ ሪፍቅ ይተውናሉ።
•
* አንድን ሙስሊም "ጣኦት አምላኪ"፣ "ጴንጤ" እያሉ ከመወረፍ የበለጠ ፀያፍ አለ?! ይሄ ነው እንግዲህ ስለ ፅንፈኝነት የሚያወራውና የሚያሰራጨው!!
•
ይህ ሁሉ ሲሆን ዝም ያለ ሰው እነሱ ሲነኩ እሪታ ማብዛት ምንድን ነው?! "ጴንጤ" "ጣኦት አምላኪ" እያለ የሚወርፈው ሳዳት ቢሆን ኖሮ ኡስታዞቻችሁም ዝም አይሉም ነበር። በራሳችሁ ጭንቅላት አስቡ። ይሄ በቡድን ማሰብ እራሳችሁን ነው የሚጎዳው።
እነዚህ ናቸውኮ ያለ ምንም ሃፍረት ስለ ሪፍቅ፣ ሊን፣ ሒክማ የሚደሰኩሩት። ሙስሊምን እያከፈረ "አሽሙር ጥሩ አይደለም" የሚል ሰው የተዋጣለት ኮሜዲያን ነው።
•
* "ሰዎችን ከሱንና ማስወጣት ከባድ ነው" የሚለውን ያራግብና ዞሮ በሐዳዲያነት ይወርፋል። ለመሆኑ እራሳቸውን በምን አይን ነው የሚያዩት?!
•
ከስር ያያያዝኳቸው የአወል ሸርሞሎ ንግግሮች ናቸው። መካሪ፣ ጓደኛ፣ ቤተሰብ ቢኖረው ይህን ሁሉ እያየ ዝም አይለውም ነበር።
።
① ቢድዐን የቀሰቀሰ ሳዳት ነው ይለናል።
إذا لم تستحي فاصنع ما شئت!
② "የኢኽዋንን ሬሳ ነፍስ ዘርቶ ለስልጣን ያበቃው ሳዳት ነው ይለናል። መዋሸት እንኳን የማይችል ቀላል ፍጡር። ኢኽዋን ሲሿሿም አብረው የተጣዱት ኡስታዞችህ እንጂ ሳዳት ነው እንዴ?! " እንኳን ደስ ያለን" መግለጫ ያወጣው ሳዳት ነውንዴ?! ኢኽዋን ጋር አይንና ናጫ የሆነውስ ሳዳት ነው ወይስ መርከዛችሁ? ምነው ሃይ የሚላችሁ ጠፋ?!
ቆይ "ኢኽዋን ሙቷል ስትል" ማነው የገደለው? "ገድለነዋል" ልትል ባልሆነ። እና ከሬሳው ጋር ነው ‘ለመስለሐ’ እየተቀማመጣችሁ ያላችሁት? ከሬሳ ጋር ነው ስብሰባ የምትቀማመጡት?!
•
③ "የተረሳውን መንዙማ በመፅሐፍ ፅፎ ለህዝብ ያስጠና " ይላል።
ሱብሓነላህ! ለወሬ የማይመች ፍጡር!! መንዙማ ተረስቷል? ሳዳት ነው ለህዝብ ያስተዋወቀው?
ሲጀመር በዚህ ጉዳይ ምን የሰራችሁት አለ?! ለካስ ለዚህ ነበር አንዳንዶቹ "መንዙማ" መፅሐፍን ሰ ቃወሙ የነበረው?
ጥላቻ ይህን ያክል ይጋርዳል። ወላሂ የሚናገረውን ባየሁ ቁጥር አእምሮውን በእጅጉ ነው የምጠረጥረው።
•
④ "የተረሱ የሙታን መቃብር ቦታዎችን ቦታቸውን ሁሌ እየጠቆመ እንዲጎበኙ ያስደረገው ሳዳት ነው ይላል።
ምናለብህ የፈለግከው ብትናገር፣ እንዳሰኘህ ብትዋሽ አንተን ማን ይነካሀል? የሙሪድነት መታወቂያ ይዘሀላ!
ለመሆኑ ጌታ አላህ እነ ላትን፣ እነ ዑዛን፣ እነ መናትን በስም እየጠቀሰ ሲኮንን እንዲመለኩ እያመለካተ ነበር?
•
⑤ ጠፍተው የነበሩ እርዶች በአልከሶ፣ በቃጥባሬ በአብሬት ከድሮው እንዲባባሱ ያደረገው ሳዳት ነው ከዚህ ወፈፌ ዘንድ።
ሱብሓነላህ!! ወላሂ ኢኽዋኖች እንዲህ ሲሉ ሰምቼ አላውቅም። እነዚህ ናቸው ስለ ሚዛናዊነት የሚደሰኩሩት እንግዲህ።
•
"አሽሙር ጥሩ አይደለም" ከማለታችሁ በፊት ይህን ተናካሽ ፍጡር አትይዙም?! "መርፉዐል ቀለም" ከሆነም እሰሩት።
•
* ምናልባት ለምን እስከዛሬ ዝም አላችሁ" የሚል ሊኖር ይችላል። በግምት ከ6 አመት አካባቢ እዚሁ ፌስቡክ ላይ በግልፅ ተናግረናል። ከ2 አመት በፊትም ለሚቀርበው አንድ ኡስታዝ "ለምን ስርአት አታስይዙትም?" ብየ ተናግሬ ነበር። "አናግረነዋል ይስተካከላል" ብሎኝ ነበር። ያናግሩት አያናግሩት የማውቀው ነገር የለም።
•
(وَإِنْ عُدْتُمْ عُدْنَا)
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
እኔ እምለው አሽሙር አሽሙር የሚሉ በዙ ልበል?
ደግሞኮ ይህንኑ ሐሳባቸውን በአሽሙር ነው የሚገልፁት። በግልፅ "እነ እከሌን አትንኩብን" ብትሉ አይሻልም? ምነው ፍላጎታችሁን ለመግለፅ ዳር ዳሩን ትዞራላችሁ?!
።
እንጂ ኢንሷፍ ቢሸታችሁ እነዚህን እዚያ ሰፈር ደጋግመን የምንሰማቸውን ውንጀላዎች ዝም ባላላችሁ ነበር።
* "ጉላት (ወሰን አላፊዎች)"፣
* "ፅንፈኞች"፣
* "ሐዳዲያ"፣
* "ላይክና ሼር መቃረም የሚፈልጉ"፣
* "የደጋፊ ሽሚያ ውስጥ የገቡ"፣ "ደጋፊ ለማብዛት የሚሯሯጡ"
* "የሰለፍያ ጭምብል የለበሱ"፣
•
•
•
ይህ ሁሉ ሲባል ምን ብላችኋል? የትስ ነበራችሁ?!
•
ደግሞ ምነው ይህን በሰለፍዮች ላይ የሚያሳዩትን ጀግንነት ኢኽዋንም ላይ እያሳዩን ምንም ቢሉን በቻልናቸው!!
•
* ይሄው ከስር በሐዳዲይነት ሲፈርጁ። ከዚያ ደግሞ ሌላ ገፀ ባህሪ ተላብሰው ሪፍቅ፣ ሪፍቅ ይተውናሉ።
•
* አንድን ሙስሊም "ጣኦት አምላኪ"፣ "ጴንጤ" እያሉ ከመወረፍ የበለጠ ፀያፍ አለ?! ይሄ ነው እንግዲህ ስለ ፅንፈኝነት የሚያወራውና የሚያሰራጨው!!
•
ይህ ሁሉ ሲሆን ዝም ያለ ሰው እነሱ ሲነኩ እሪታ ማብዛት ምንድን ነው?! "ጴንጤ" "ጣኦት አምላኪ" እያለ የሚወርፈው ሳዳት ቢሆን ኖሮ ኡስታዞቻችሁም ዝም አይሉም ነበር። በራሳችሁ ጭንቅላት አስቡ። ይሄ በቡድን ማሰብ እራሳችሁን ነው የሚጎዳው።
እነዚህ ናቸውኮ ያለ ምንም ሃፍረት ስለ ሪፍቅ፣ ሊን፣ ሒክማ የሚደሰኩሩት። ሙስሊምን እያከፈረ "አሽሙር ጥሩ አይደለም" የሚል ሰው የተዋጣለት ኮሜዲያን ነው።
•
* "ሰዎችን ከሱንና ማስወጣት ከባድ ነው" የሚለውን ያራግብና ዞሮ በሐዳዲያነት ይወርፋል። ለመሆኑ እራሳቸውን በምን አይን ነው የሚያዩት?!
•
ከስር ያያያዝኳቸው የአወል ሸርሞሎ ንግግሮች ናቸው። መካሪ፣ ጓደኛ፣ ቤተሰብ ቢኖረው ይህን ሁሉ እያየ ዝም አይለውም ነበር።
።
① ቢድዐን የቀሰቀሰ ሳዳት ነው ይለናል።
إذا لم تستحي فاصنع ما شئت!
② "የኢኽዋንን ሬሳ ነፍስ ዘርቶ ለስልጣን ያበቃው ሳዳት ነው ይለናል። መዋሸት እንኳን የማይችል ቀላል ፍጡር። ኢኽዋን ሲሿሿም አብረው የተጣዱት ኡስታዞችህ እንጂ ሳዳት ነው እንዴ?! " እንኳን ደስ ያለን" መግለጫ ያወጣው ሳዳት ነውንዴ?! ኢኽዋን ጋር አይንና ናጫ የሆነውስ ሳዳት ነው ወይስ መርከዛችሁ? ምነው ሃይ የሚላችሁ ጠፋ?!
ቆይ "ኢኽዋን ሙቷል ስትል" ማነው የገደለው? "ገድለነዋል" ልትል ባልሆነ። እና ከሬሳው ጋር ነው ‘ለመስለሐ’ እየተቀማመጣችሁ ያላችሁት? ከሬሳ ጋር ነው ስብሰባ የምትቀማመጡት?!
•
③ "የተረሳውን መንዙማ በመፅሐፍ ፅፎ ለህዝብ ያስጠና " ይላል።
ሱብሓነላህ! ለወሬ የማይመች ፍጡር!! መንዙማ ተረስቷል? ሳዳት ነው ለህዝብ ያስተዋወቀው?
ሲጀመር በዚህ ጉዳይ ምን የሰራችሁት አለ?! ለካስ ለዚህ ነበር አንዳንዶቹ "መንዙማ" መፅሐፍን ሰ ቃወሙ የነበረው?
ጥላቻ ይህን ያክል ይጋርዳል። ወላሂ የሚናገረውን ባየሁ ቁጥር አእምሮውን በእጅጉ ነው የምጠረጥረው።
•
④ "የተረሱ የሙታን መቃብር ቦታዎችን ቦታቸውን ሁሌ እየጠቆመ እንዲጎበኙ ያስደረገው ሳዳት ነው ይላል።
ምናለብህ የፈለግከው ብትናገር፣ እንዳሰኘህ ብትዋሽ አንተን ማን ይነካሀል? የሙሪድነት መታወቂያ ይዘሀላ!
ለመሆኑ ጌታ አላህ እነ ላትን፣ እነ ዑዛን፣ እነ መናትን በስም እየጠቀሰ ሲኮንን እንዲመለኩ እያመለካተ ነበር?
•
⑤ ጠፍተው የነበሩ እርዶች በአልከሶ፣ በቃጥባሬ በአብሬት ከድሮው እንዲባባሱ ያደረገው ሳዳት ነው ከዚህ ወፈፌ ዘንድ።
ሱብሓነላህ!! ወላሂ ኢኽዋኖች እንዲህ ሲሉ ሰምቼ አላውቅም። እነዚህ ናቸው ስለ ሚዛናዊነት የሚደሰኩሩት እንግዲህ።
•
"አሽሙር ጥሩ አይደለም" ከማለታችሁ በፊት ይህን ተናካሽ ፍጡር አትይዙም?! "መርፉዐል ቀለም" ከሆነም እሰሩት።
•
* ምናልባት ለምን እስከዛሬ ዝም አላችሁ" የሚል ሊኖር ይችላል። በግምት ከ6 አመት አካባቢ እዚሁ ፌስቡክ ላይ በግልፅ ተናግረናል። ከ2 አመት በፊትም ለሚቀርበው አንድ ኡስታዝ "ለምን ስርአት አታስይዙትም?" ብየ ተናግሬ ነበር። "አናግረነዋል ይስተካከላል" ብሎኝ ነበር። ያናግሩት አያናግሩት የማውቀው ነገር የለም።
•
(وَإِنْ عُدْتُمْ عُدْنَا)
Forwarded from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የሰልሰቢልን ፅሑፍ አየሁት
~~~~~~~~~~~~~~~~
ያየሁት ትላንት ነው። ብዙም ትኩረት ሳልሰጠው አልፌው ነበር። ዛሬ ግን አንድ ትኩረቴን የሳበኝ ነገር በማየቴ ትንሽ ልል ወደድኩኝ። አብዛኛው ረብ የለሽ ስለሆነብኝ ትቼዋለሁ። አንዳንድ ነጥቦችን እየመዘዝኩ ልይ:–
① "በርግጥ በአመለካከት ከሚራራቁ ሰዎች ጋር ግድ ሆኖብህ ስትቀማመጥ ከበባድ ነገሮችን ልትሰማና ልታይ ትችላለህ የሚጠበቅም ነው። ለዛም ነው ፕሮፌሰር አደም ካሚል የነቢያትን ክብር የሚነካ ንግግር ያሰማው" ይላል።
መልስ:–
~~~~~~
እንዲህ አይነት ነገር ሲያጋጥም ሸሪዐዊይ ብይኑ ወይ እርምት መስጠት ወይ ጥሎ መውጣት ነው ሰልሰቢል። አላህ እንዲህ ይላል:–
(وَقَدْ نَزَّلَ عَلَيْكُمْ فِي الْكِتَابِ أَنْ إِذَا سَمِعْتُمْ آيَاتِ اللَّهِ يُكْفَرُ بِهَا وَيُسْتَهْزَأُ بِهَا فَلَا تَقْعُدُوا مَعَهُمْ حَتَّىٰ يَخُوضُوا فِي حَدِيثٍ غَيْرِهِ ۚ إِنَّكُمْ إِذًا مِثْلُهُمْ)
"በእናንተም ላይ በመጽሐፉ ውስጥ የአላህን አንቀጾች በርሷ ሲካድባትና በርሷም ሲላገጥባት በሰማችሁ ጊዜ በሌላ ወሬ ውስጥ እስከሚገቡ ድረስ ከእነሱ ጋር አትቀመጡ ማለትን በእርግጥ አወረደ፡፡ እናንተ ያንጊዜ ብጤያቸው ናችሁና፡፡"
[አንኒሳእ: 140]
ነብዩም ﷺ እንዲህ ብለዋል:–
" مَنْ رَأَى مِنْكُمْ مُنْكَرًا فَلْيُغَيِّرْهُ بِيَدِهِ، فَإِنْ لَمْ يَسْتَطِعْ فَبِلِسَانِهِ، فَإِنْ لَمْ يَسْتَطِعْ فَبِقَلْبِهِ، وَذَلِكَ أَضْعَفُ الْإِيمَانِ "
"ከናንተ መጥፎን ነገር ያየ በእጁ ይቀይረው። ካልቻለ በምላሱ፤ ካልቻለ ደግሞ በልቡ። ይሄኛው የመጨረሻ ደካማው እምነት ነው።" [ሙስሊም]
ተሳታፊዎችህ ግን አንዱንም አላደረጉም። አድርገዋል ካልክ ማስረጃ አቅርብ።
•
② "ይሁንና ልክ ቦታው ላይ እንደነበሩ ሆነው "ይህ ሲሰማ ዝም አሉ" "ሌላው ቢያቅታቸው ጮኸው መውጣት ነበረባቸው" ወዘተ እያሉ መተቸታቸው ግን ተገቢ አይደለም። ምክንያቱም አንደኛ ተቃውመው ሊሆን ይችላል ወይም ያሉበት ሁኔታ ተቃውሟቸውን በምንም መልኩ ሊገልፁ ማይችሉበት ኡዝር የሚያሰጥ ሁኔታ ሊኖር ይችላል …።" ብለሃል ።
መልስ:–
~~~~
በቦታው ላይ ምላሽ እንዳልሰጡ ባደባባይ ሲመሰክር የነበረ ሰው ይህን ተልቢስ ሼር ሲያደርግ ሳየው ነው ምላሽ ልፅፍ የወሰንኩት።
ወንድሜ በቦታው ላይ ምላሽ አልሰጡም። በሌላም ጉዳይ ቢሆን አሕባሾች ናቸው ተሽለው የጮሁት።
"ተቃውመው ሊሆን ይችላል" ከማለት ጠይቀህ አትፅፍም? ይህን ያክል እሩቅ ናቸው ላንተ? ለማንኛውም አልተቃወሙም። በቦታው ከነበሩ ሰዎች መረጃ አለኝ። ከትግራይና ከአፋር የተካፈሉ ሰዎችን አግኝቼ አነጋግሬያለሁ። አንዱ "ንግግሩ ቢያስደነግጠኝም ሁሉም ፀጥ ሲል ጊዜ እኔ አማርኛየ ደካማ ስለሆነ በተሳሳተ መልኩ ተረድቼው ይሆናል ብየ ነው የገምትኩኝ" ሲለኝ ሌላኛው "ይሄ እጅግ አደገኛ ንግግር ነው። እኔ አማርኛ አልችልም። እንዴት ያ ሁሉ ታዳሚ (እነ እከሌ ብሎ ስም እየጠቀሰ) ዝም አለ?" ብሎኛል።
•
በተረፈ ከኢብኑ መስዑድ መርከዝ ሰዎች ውስጥ "አንድ ሰው በቦታው ስላልተመቸው ምላሽ ላይሰጥ ይችላል" እያለ የተናገረበት ድምፅ ሰምቻለሁ። ይህ ማለት በቦታው አልተናገርንም ማለቱ ነው። አሁን ያንተን ሾላ በድፍን መከላከያ ሼር ሲያደርግ እያየሁ ነው። እውነት እንዳልሆነ እያወቀ ያንተን ተልቢስ ያጣጥማል።
•
እሺ በቦታው መናገሩም ይቅር! ሲወጡ እርምት መስጠት አይችሉም ነበር? እንደሚታወቀው ጉባኤው ሰፊ ታዳሚ የተካፈለበት ነው። በዚያ ላይ ተቀርጿል። በዚያ ላይ በአሕባሽ ሲራገብ ነበር። እነዚህ ነገሮች ልክ የግል ውይይት ላይ እንዳለፈ ነገር አንዴ ሆኗል ተብሎ የሚታለፍ አይደለም። ለነገሩ የግልም ዝም ተብሎ አይታለፍም።
ወንድማችን ሰልሰቢል ግን እነዚህ እውነታዎች ባሉበት የተፈፀመውን ስህተት አስረግጦ እንደመነሳት በመከላከል ላይ ሲባክን ይታያል።
•
③ "ኢብን መስዑድ በዚህ እንቅስቃሴ … በመግባቱም ሳቢያ የተቋማዊ ለውጡ መሰረት በሚፈለገው ምሶሶ ላይ እንዲቆምና በተለይ ከነ ሀሰን ታጁ ጥራዝ ነጠቅ አቋም የፀዳ እንዲሆን የበኩሉን ጥረት አድርጓል ወሊላሂል ሀምድ።"
መልስ
-----
አነጋገሩ አሻሚነት አለው። "ሞክሯል" ሊል ከሆነ እሰየው። የነ ሀሰን ታጁ ተፅእኖ ግን ማንም በማይክደው መልኩ አግጥጦ የሚታይ ነው። ነገሩን ለማጥራት ያክል ነው።
•
④ "ይህ ሆኖ ሳለ ቀድሞውንም ከረዥም ጊዜ ጀምሮ የኢብን መስዑድ ሰዎች ላይ ሙላሀዛዎች አሉን የሚሉ ወንድሞች ይህን አጋጣሚ ተጠቅመው በዙልምና በተልቢስ ትችቶችን መሰንዘራቸውን አሟሙቀውታል።"
መልስ:–
~~~~~
ይሄ ንግግርህ በራሱ ዙልምና ተልቢስ ነው። የተናገርነው አንድም አካሄዳችሁ ስህተት ነው ብለን ስላመንን ነው። ችግሩ እራሳችሁን "አይነኬ" ማድረጋችሁ ነው። ቀጥታ አታወጡትም እንጂ "ምን ሲባል ተደፍረን?" ነው ነገራችሁ። እንጂ አመላለሳችን ልክ አይደለም ቢባል እንኳ ከሰፊው የኢኽዋን ዘመቻ ይልቅ የራሳችሁ ጉዳይ አስጨንቋችሁ አትንጨረጨሩም ነበር!!
ሁለተኛ ሀሳባችሁን የሚተችን እንደ ፅንፈኛ እየሳላችሁ ስለሆነ ነው ትችት የምንሰነዝረው።
•
ይልቅ ማስረጃዎችን ያለ ቦታቸው ማዋል፣ ለምሳሌ የሑደይቢያን ውል ያለ አግባብ መጠቀም ነው ተልቢስ። በሃሳብ ያልተጋራውን በፅንፈኝነት መወረፍ ነው ተልቢስ።
•
⑤ "በሀቅ መተቸት በትህትና ሀሳብ መስጠት ወይም ስህተቱን በመረጃ አጉልቶ ረድ መስጠት እየቻሉ እንዲህ አይነቱን ማድበስበስ መጠቀም ለምን እንደመረጡ ባይገባንም …"
መልስ
~~~~
ሱብሓነላህ! "ጅራፍ እራሱ ገርፎ እራሱ ይጮሃል!" በሐዳዲያ መወንጀል ነው በሐቅ መተቸት? ጉላት እያሉ መወረፍ ነው በትህትና መሀየስ? "ሺርክና ቢድዐ አሰራጫችሁ፣ ኢኽዋኖችን ለሥልጣን አበቃችሁ" እያሉ መቅጠፍ ነው በአደብ መሞገት? አንዳንዴ እንኳን እራሳችሁን ተመልከቱ እንጂ!
ግራ የሚገባኝ ኢኽዋን ከአመት እስካመት ሲፈነጭ ዝም ብሎ፣ "ተነካን" ብለው ሲያስቡ ነብር የሚሆኑበት ባህሪ ነው። እያድበሰበሱ "አታድበስብሱ!" እየሻከሩ "አትሻክሩ" ብሎ ጩኸት። ከተነኩ እስከ ተብዲዕ እስከ ተክፊር ለመሄድ የማያመነቱ ኡስታዞች ከውስጣቸው እንዳሉ አይተናል። የታል ሪፍቃችሁ? የታል ሒክማችሁ?!
•
⑥ "ይህን ክስተት ሲተቹ ከገረሙኝ ነገሮች "ስለ መረዳዳት የተናገረው የቁርዓን አንቀፅ ሙብተዲዖችን አይመለከትም። ከሰለፎች አንድም ሰው በዚህ አልፈሰረውም" ብለው ብዙ ሳይቆዩ "በሀቅ ከሆነ አይደለም ከሙብተዲዕ ከካፊር ጋርም መተባበር ይቻላል" እያሉ የሚናጋ መርሆ አንግበው አንድ ላይ መጮኸቸው ነው።"
መልስ:–
~~~~~~
"በሀቅ ከሆነ አይደለም ከሙብተዲዕ ከካፊር ጋርም መተባበር ይቻላል" ብየ የፃፍኩት እኔ ነኝ። የት ቦታ ከሙብተዲዕ ጋር መተባበር አይቻልም እንዳልኩ አቅርበው እስኪ። ያለበለዚያ እየዋሸህ ነው።
ስገምት "አንተ ባትልም ሌላ የሆነ ሰው ብሏል፣ ያው አንድ ናችሁ" ልትል ይመስለኛል። እንዲያ ካልክ የነ አወል ሸርሞሎን የነ ሙሐመድ ዐሊን ንግግር ወደናንተ ስናስጠጋ አይክፋችሁ።
•
⑦ "ኢብን መስዑድ ተሳትፎ ሲያደርግ ዓላማውም ሆነ ተግባሩ ከላይ የጠቀስኩት ሆኖ ሳለ ስኬት ግን በአላህ እጅ እንደሆነና ከኛ የሚጠበቀው ሰበብን በአግባቡ ማድረስ ብቻ እንደሆነ እናምናለን።"
መልስ:–
~~~~
"ኢብኑ መስዑድ (መርከዝ) የሄደበት መ
~~~~~~~~~~~~~~~~
ያየሁት ትላንት ነው። ብዙም ትኩረት ሳልሰጠው አልፌው ነበር። ዛሬ ግን አንድ ትኩረቴን የሳበኝ ነገር በማየቴ ትንሽ ልል ወደድኩኝ። አብዛኛው ረብ የለሽ ስለሆነብኝ ትቼዋለሁ። አንዳንድ ነጥቦችን እየመዘዝኩ ልይ:–
① "በርግጥ በአመለካከት ከሚራራቁ ሰዎች ጋር ግድ ሆኖብህ ስትቀማመጥ ከበባድ ነገሮችን ልትሰማና ልታይ ትችላለህ የሚጠበቅም ነው። ለዛም ነው ፕሮፌሰር አደም ካሚል የነቢያትን ክብር የሚነካ ንግግር ያሰማው" ይላል።
መልስ:–
~~~~~~
እንዲህ አይነት ነገር ሲያጋጥም ሸሪዐዊይ ብይኑ ወይ እርምት መስጠት ወይ ጥሎ መውጣት ነው ሰልሰቢል። አላህ እንዲህ ይላል:–
(وَقَدْ نَزَّلَ عَلَيْكُمْ فِي الْكِتَابِ أَنْ إِذَا سَمِعْتُمْ آيَاتِ اللَّهِ يُكْفَرُ بِهَا وَيُسْتَهْزَأُ بِهَا فَلَا تَقْعُدُوا مَعَهُمْ حَتَّىٰ يَخُوضُوا فِي حَدِيثٍ غَيْرِهِ ۚ إِنَّكُمْ إِذًا مِثْلُهُمْ)
"በእናንተም ላይ በመጽሐፉ ውስጥ የአላህን አንቀጾች በርሷ ሲካድባትና በርሷም ሲላገጥባት በሰማችሁ ጊዜ በሌላ ወሬ ውስጥ እስከሚገቡ ድረስ ከእነሱ ጋር አትቀመጡ ማለትን በእርግጥ አወረደ፡፡ እናንተ ያንጊዜ ብጤያቸው ናችሁና፡፡"
[አንኒሳእ: 140]
ነብዩም ﷺ እንዲህ ብለዋል:–
" مَنْ رَأَى مِنْكُمْ مُنْكَرًا فَلْيُغَيِّرْهُ بِيَدِهِ، فَإِنْ لَمْ يَسْتَطِعْ فَبِلِسَانِهِ، فَإِنْ لَمْ يَسْتَطِعْ فَبِقَلْبِهِ، وَذَلِكَ أَضْعَفُ الْإِيمَانِ "
"ከናንተ መጥፎን ነገር ያየ በእጁ ይቀይረው። ካልቻለ በምላሱ፤ ካልቻለ ደግሞ በልቡ። ይሄኛው የመጨረሻ ደካማው እምነት ነው።" [ሙስሊም]
ተሳታፊዎችህ ግን አንዱንም አላደረጉም። አድርገዋል ካልክ ማስረጃ አቅርብ።
•
② "ይሁንና ልክ ቦታው ላይ እንደነበሩ ሆነው "ይህ ሲሰማ ዝም አሉ" "ሌላው ቢያቅታቸው ጮኸው መውጣት ነበረባቸው" ወዘተ እያሉ መተቸታቸው ግን ተገቢ አይደለም። ምክንያቱም አንደኛ ተቃውመው ሊሆን ይችላል ወይም ያሉበት ሁኔታ ተቃውሟቸውን በምንም መልኩ ሊገልፁ ማይችሉበት ኡዝር የሚያሰጥ ሁኔታ ሊኖር ይችላል …።" ብለሃል ።
መልስ:–
~~~~
በቦታው ላይ ምላሽ እንዳልሰጡ ባደባባይ ሲመሰክር የነበረ ሰው ይህን ተልቢስ ሼር ሲያደርግ ሳየው ነው ምላሽ ልፅፍ የወሰንኩት።
ወንድሜ በቦታው ላይ ምላሽ አልሰጡም። በሌላም ጉዳይ ቢሆን አሕባሾች ናቸው ተሽለው የጮሁት።
"ተቃውመው ሊሆን ይችላል" ከማለት ጠይቀህ አትፅፍም? ይህን ያክል እሩቅ ናቸው ላንተ? ለማንኛውም አልተቃወሙም። በቦታው ከነበሩ ሰዎች መረጃ አለኝ። ከትግራይና ከአፋር የተካፈሉ ሰዎችን አግኝቼ አነጋግሬያለሁ። አንዱ "ንግግሩ ቢያስደነግጠኝም ሁሉም ፀጥ ሲል ጊዜ እኔ አማርኛየ ደካማ ስለሆነ በተሳሳተ መልኩ ተረድቼው ይሆናል ብየ ነው የገምትኩኝ" ሲለኝ ሌላኛው "ይሄ እጅግ አደገኛ ንግግር ነው። እኔ አማርኛ አልችልም። እንዴት ያ ሁሉ ታዳሚ (እነ እከሌ ብሎ ስም እየጠቀሰ) ዝም አለ?" ብሎኛል።
•
በተረፈ ከኢብኑ መስዑድ መርከዝ ሰዎች ውስጥ "አንድ ሰው በቦታው ስላልተመቸው ምላሽ ላይሰጥ ይችላል" እያለ የተናገረበት ድምፅ ሰምቻለሁ። ይህ ማለት በቦታው አልተናገርንም ማለቱ ነው። አሁን ያንተን ሾላ በድፍን መከላከያ ሼር ሲያደርግ እያየሁ ነው። እውነት እንዳልሆነ እያወቀ ያንተን ተልቢስ ያጣጥማል።
•
እሺ በቦታው መናገሩም ይቅር! ሲወጡ እርምት መስጠት አይችሉም ነበር? እንደሚታወቀው ጉባኤው ሰፊ ታዳሚ የተካፈለበት ነው። በዚያ ላይ ተቀርጿል። በዚያ ላይ በአሕባሽ ሲራገብ ነበር። እነዚህ ነገሮች ልክ የግል ውይይት ላይ እንዳለፈ ነገር አንዴ ሆኗል ተብሎ የሚታለፍ አይደለም። ለነገሩ የግልም ዝም ተብሎ አይታለፍም።
ወንድማችን ሰልሰቢል ግን እነዚህ እውነታዎች ባሉበት የተፈፀመውን ስህተት አስረግጦ እንደመነሳት በመከላከል ላይ ሲባክን ይታያል።
•
③ "ኢብን መስዑድ በዚህ እንቅስቃሴ … በመግባቱም ሳቢያ የተቋማዊ ለውጡ መሰረት በሚፈለገው ምሶሶ ላይ እንዲቆምና በተለይ ከነ ሀሰን ታጁ ጥራዝ ነጠቅ አቋም የፀዳ እንዲሆን የበኩሉን ጥረት አድርጓል ወሊላሂል ሀምድ።"
መልስ
-----
አነጋገሩ አሻሚነት አለው። "ሞክሯል" ሊል ከሆነ እሰየው። የነ ሀሰን ታጁ ተፅእኖ ግን ማንም በማይክደው መልኩ አግጥጦ የሚታይ ነው። ነገሩን ለማጥራት ያክል ነው።
•
④ "ይህ ሆኖ ሳለ ቀድሞውንም ከረዥም ጊዜ ጀምሮ የኢብን መስዑድ ሰዎች ላይ ሙላሀዛዎች አሉን የሚሉ ወንድሞች ይህን አጋጣሚ ተጠቅመው በዙልምና በተልቢስ ትችቶችን መሰንዘራቸውን አሟሙቀውታል።"
መልስ:–
~~~~~
ይሄ ንግግርህ በራሱ ዙልምና ተልቢስ ነው። የተናገርነው አንድም አካሄዳችሁ ስህተት ነው ብለን ስላመንን ነው። ችግሩ እራሳችሁን "አይነኬ" ማድረጋችሁ ነው። ቀጥታ አታወጡትም እንጂ "ምን ሲባል ተደፍረን?" ነው ነገራችሁ። እንጂ አመላለሳችን ልክ አይደለም ቢባል እንኳ ከሰፊው የኢኽዋን ዘመቻ ይልቅ የራሳችሁ ጉዳይ አስጨንቋችሁ አትንጨረጨሩም ነበር!!
ሁለተኛ ሀሳባችሁን የሚተችን እንደ ፅንፈኛ እየሳላችሁ ስለሆነ ነው ትችት የምንሰነዝረው።
•
ይልቅ ማስረጃዎችን ያለ ቦታቸው ማዋል፣ ለምሳሌ የሑደይቢያን ውል ያለ አግባብ መጠቀም ነው ተልቢስ። በሃሳብ ያልተጋራውን በፅንፈኝነት መወረፍ ነው ተልቢስ።
•
⑤ "በሀቅ መተቸት በትህትና ሀሳብ መስጠት ወይም ስህተቱን በመረጃ አጉልቶ ረድ መስጠት እየቻሉ እንዲህ አይነቱን ማድበስበስ መጠቀም ለምን እንደመረጡ ባይገባንም …"
መልስ
~~~~
ሱብሓነላህ! "ጅራፍ እራሱ ገርፎ እራሱ ይጮሃል!" በሐዳዲያ መወንጀል ነው በሐቅ መተቸት? ጉላት እያሉ መወረፍ ነው በትህትና መሀየስ? "ሺርክና ቢድዐ አሰራጫችሁ፣ ኢኽዋኖችን ለሥልጣን አበቃችሁ" እያሉ መቅጠፍ ነው በአደብ መሞገት? አንዳንዴ እንኳን እራሳችሁን ተመልከቱ እንጂ!
ግራ የሚገባኝ ኢኽዋን ከአመት እስካመት ሲፈነጭ ዝም ብሎ፣ "ተነካን" ብለው ሲያስቡ ነብር የሚሆኑበት ባህሪ ነው። እያድበሰበሱ "አታድበስብሱ!" እየሻከሩ "አትሻክሩ" ብሎ ጩኸት። ከተነኩ እስከ ተብዲዕ እስከ ተክፊር ለመሄድ የማያመነቱ ኡስታዞች ከውስጣቸው እንዳሉ አይተናል። የታል ሪፍቃችሁ? የታል ሒክማችሁ?!
•
⑥ "ይህን ክስተት ሲተቹ ከገረሙኝ ነገሮች "ስለ መረዳዳት የተናገረው የቁርዓን አንቀፅ ሙብተዲዖችን አይመለከትም። ከሰለፎች አንድም ሰው በዚህ አልፈሰረውም" ብለው ብዙ ሳይቆዩ "በሀቅ ከሆነ አይደለም ከሙብተዲዕ ከካፊር ጋርም መተባበር ይቻላል" እያሉ የሚናጋ መርሆ አንግበው አንድ ላይ መጮኸቸው ነው።"
መልስ:–
~~~~~~
"በሀቅ ከሆነ አይደለም ከሙብተዲዕ ከካፊር ጋርም መተባበር ይቻላል" ብየ የፃፍኩት እኔ ነኝ። የት ቦታ ከሙብተዲዕ ጋር መተባበር አይቻልም እንዳልኩ አቅርበው እስኪ። ያለበለዚያ እየዋሸህ ነው።
ስገምት "አንተ ባትልም ሌላ የሆነ ሰው ብሏል፣ ያው አንድ ናችሁ" ልትል ይመስለኛል። እንዲያ ካልክ የነ አወል ሸርሞሎን የነ ሙሐመድ ዐሊን ንግግር ወደናንተ ስናስጠጋ አይክፋችሁ።
•
⑦ "ኢብን መስዑድ ተሳትፎ ሲያደርግ ዓላማውም ሆነ ተግባሩ ከላይ የጠቀስኩት ሆኖ ሳለ ስኬት ግን በአላህ እጅ እንደሆነና ከኛ የሚጠበቀው ሰበብን በአግባቡ ማድረስ ብቻ እንደሆነ እናምናለን።"
መልስ:–
~~~~
"ኢብኑ መስዑድ (መርከዝ) የሄደበት መ
Forwarded from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ንገድ ውጤት ካመጣ ኋላ ታፍራላችሁ" ያልከው ልጅ ና እስኪ ይህንን እይ! የተሰጠህ ምላሽ ከዚህ የሰልሰቢል ንግግር ጋር አንድ አይደል?
ብቻ ጤነኛ ሰበብ ማድረስ ይጠበቃል። እንጂ "የትም ፍጪው…" እየዘመሩ "ዋናው ሰበብ ማድረስ ነው" አይባልም ።
•
⑧ የመጅሊሱን ስምምነት አስመልክቶ በራሱ መንገድ ከተበተበ በኋላ "እኔ በእውነቱ በዚ የማይደሰት ትክክለኛ የዓቂዳ ተቆርቋሪ ይኖራል ብዬ አላስብም ነበር" ይላል።
መልስ:–
~~~``
የሚደንቅ ነው። እኔ "ትክክለኛ የዓቂዳ ተቆርቋሪ አይደለህም" ትለኛለህ ብየ ሳልጨነቅ ስምምነቱ አያስደስተኝም እልሀለሁ። ይህን የምለው በሚከተሉት ምክንያቶች ነው።
አንደኛ:– ለሰለፍያ ደዕዋ ፈተና በመፍጠር በኩል ኢኽዋን የከፋ ነው ብየ ስለማምን ነው። እያወራሁ ያለሁት የሁለቱ ቡድኖች ዐቂዳ ሲነፃፀር አሕባሽ ይሻላል ለማለት አይደለም። ምንም እንኳን ኢኽዋን ውስጥ ከአሕባሽ ፈፅሞ የማይሻሉም እንዲያውም የሚከፉም ሰዎች ከመኖራቸውም ጋር እንደ ጥቅል ግን ኢኽዋን የተሻለ መሆኑ ይታወቃል። ይሁን እንጂ አሕባሽ የማይመስሉትን ሁሉ ጠላት ሲያደርግ ኢኽዋን ግን አሕባሽንም ሺዐንም በዐቂዳ ልዩነት ሳቢያ ጠላት አያደርግም። ይልቁንም በሙሉ ሃይሉ የሚዘምተው ሰለፍያ ላይ ነው። ይህንን ሐቅ ሌሌች ሊያምኑት ቢከብዳቸው እንኳ ሰለፍዮች ግን በተጨባጭ የሚያውቁት ነው። ይሄው እርቅ በሚዘምርበት ሰዓት እንኳ በአንዳንድ አካባቢዎች አሕባሾችን ማስተማርና መውሊድ መደገስ በፈቀዱበት ቦታ ሰለፍዮችን ሲያግዱ ተስተውለዋል። በአንዳንድ የአማራ፣ ኦሮሚያና አዲስ አበባ አካባቢዎች ላይ ያጋጠሙ ነገሮችን ማስተዋል ነው።
አብረን እየተንቀሳቀስን ነው ብለው አላፈሩም፣ አላረፉም።
ሁለተኛ:– በብዙ መልኩ ኢኽዋን ከአሕባሽ የተሻለ ጉልበት አለው። በአጃቢ ብዛት፣ በሚዲያ አቅም፣ በፋይናንስ… ። ይህም ፈተናቸውን ከአሕባሽ የከፋ ያደርገዋል።
ሶስተኛ:– የራስን አማራጭ መጠቀም ይቻላል። አማራጮች ባልተዘጉበት ዐቂዳን ለድርድር ካቀረበው ህብረት ውስጥ መግባት ማስተዋል ሳይሆን ሌሎች በቀደዱት መፍሰስ ነው።
•
⑨ "መንግስት አህባሽን ከሀገር ያባርልን የሚል የሚደንቅ ጥያቄ ካነሳን እንጂ አሁን ያለው ተጨባጭ ከመለስ ድፍረት በፊት የነበረው ተጨባጭ ነው።"
።
"መንግስት አህባሽን ከሀገር ያባርልን" የሚል ቂል የለም። እንዲህ አይነት አነጋገር ነገር ከማንዘላዘል ያለፈ ፋይዳ የለውም። ጥያቄው ከአሕባሽ… ጋር ሳይጋፉ መስራት ይቻላል ነው። የነገሩ ማሰሪያ እዚህ ላይ ነው። እራስህን ችለህ መስራት ከቻልክ ከአፈንጋጮች ጋር ምን አሰለፈህ?
•
(10) "ሚዛናዊ እንሁን እያልን የተለመደ ዲስኩር እያላችሁ የምታጣጥሏትንም «ሂክማ» የምንደጋግመውም ለዚህ ነው" ይላል።
መልስ:–
~~~~
ሒክማን ሳይሆን በሒክማ ስም መነገድን ነው ያጣጣልነው። በሒክማ ስም መዋሸትን ነው የተቃወምነው። በሒክማ ስም እየሰበኩ ፀያፍ የዱርየ ቃላት የሚተፉ "ኡስታዞቻችሁን" ያዙ ነው ያልነው። የተቀያየሟቸውን ሙስሊሞች ሲፈልጉ ከሱንና ሲፈልጉ ከኢስላም የሚያስወጡ ዋልጌዎቻችሁን ያዙ ነው ያልነው። እናንተ "ሒክማ የላቸውም" ከምትሏቸው ውስጥ ይህን ያደረገ አላውቅም። ኢኽዋኖችን ዝም ብሎ ሰለፍዮችን ማብጠልጠል ሒክማ አይደለም ነው የምንለው። ታላላቅ ዑለማዎች፣ ነብያትን ጨምሮ ባደባባይ ሲጠለሹ የተለጎመ አፍ ሰለፍዮች ላይ ለመዝመት መሞከሩ ሒክማ አይደለም ነው የምንለው። ይህንን የተገለበጠ አካሄድ "ሒክማ" ማለት ተልቢስ ነው።
•
(11) "ሂክማን ካልተረዳህ ግመል በመርፌ ቀዳዳ እስኪገባ ዳዒ ልትሆን አትችልም።"
መልስ
~~~~~
ሒክማ ያለው ሰው ይህን ቢል አይገርምም ነበር። ለመሆኑ እነ ሙሐመድ ዐሊ፣ አወል ሸርሞሎ እናንተ ዘንድ ዳዒዎች ኡስታዞች የሆኑት ባለ ሒክማ ሆነው ነው? ሲበዛ ፍርደ ገምድል ነህ?!
ስለ ሒክማ ከመስበካችሁ በፊት የስድብ ናዳ እያወረዱ ያሉ ዋልጌዎቻችሁን አደብ አታስይዙም?
ወንድሜ ያልመሰላቸውን "ሒክማ የለውም" እያሉ ማጣጣል የብዙዎች መታወቂያ ነው። ልዩነቱ አንተ እራስህን የምታይበት አይን ሌላ መሆኑ ነው።
ሲጀመር ሒክማን የምትዘምረው ብዙ ጊዜ ሌሎችን ለማሳጣት ነው። እንጂ በዐቂዳ ሂሳብ ሁሉን በሚያግበሰብሱት፣ ዑለማዎችን በሚያጠለሹት ኢኽዋኖች ላይ "ሒክማ የላችሁም" ብለህ አልዘመትክም። ይህም "ሒክማህ" የከንቱ አላማ ማስፈፀሚያ እንደሆነ ነው የሚያሳየው።
በተረፈ እነ ኢብኑ ተይሚያም፣ እነ አልባኒም፣ እነ ሙቅቢል፣ እነ ረቢዕም… ሙብተዲዖች ዘንድ ሒክማ የላቸውም። የሞጋቾች ሙግት መለኪያ አይሆንም ለማለት ያክል ነው። (ይህን ስል "እራሳችሁን ከነዚህ ዐሊሞች ጋር አመሳሰላችሁ" የሚል የዋህ እንዳይኖር እየሰጋሁ ነው።)
ብቻ ጤነኛ ሰበብ ማድረስ ይጠበቃል። እንጂ "የትም ፍጪው…" እየዘመሩ "ዋናው ሰበብ ማድረስ ነው" አይባልም ።
•
⑧ የመጅሊሱን ስምምነት አስመልክቶ በራሱ መንገድ ከተበተበ በኋላ "እኔ በእውነቱ በዚ የማይደሰት ትክክለኛ የዓቂዳ ተቆርቋሪ ይኖራል ብዬ አላስብም ነበር" ይላል።
መልስ:–
~~~``
የሚደንቅ ነው። እኔ "ትክክለኛ የዓቂዳ ተቆርቋሪ አይደለህም" ትለኛለህ ብየ ሳልጨነቅ ስምምነቱ አያስደስተኝም እልሀለሁ። ይህን የምለው በሚከተሉት ምክንያቶች ነው።
አንደኛ:– ለሰለፍያ ደዕዋ ፈተና በመፍጠር በኩል ኢኽዋን የከፋ ነው ብየ ስለማምን ነው። እያወራሁ ያለሁት የሁለቱ ቡድኖች ዐቂዳ ሲነፃፀር አሕባሽ ይሻላል ለማለት አይደለም። ምንም እንኳን ኢኽዋን ውስጥ ከአሕባሽ ፈፅሞ የማይሻሉም እንዲያውም የሚከፉም ሰዎች ከመኖራቸውም ጋር እንደ ጥቅል ግን ኢኽዋን የተሻለ መሆኑ ይታወቃል። ይሁን እንጂ አሕባሽ የማይመስሉትን ሁሉ ጠላት ሲያደርግ ኢኽዋን ግን አሕባሽንም ሺዐንም በዐቂዳ ልዩነት ሳቢያ ጠላት አያደርግም። ይልቁንም በሙሉ ሃይሉ የሚዘምተው ሰለፍያ ላይ ነው። ይህንን ሐቅ ሌሌች ሊያምኑት ቢከብዳቸው እንኳ ሰለፍዮች ግን በተጨባጭ የሚያውቁት ነው። ይሄው እርቅ በሚዘምርበት ሰዓት እንኳ በአንዳንድ አካባቢዎች አሕባሾችን ማስተማርና መውሊድ መደገስ በፈቀዱበት ቦታ ሰለፍዮችን ሲያግዱ ተስተውለዋል። በአንዳንድ የአማራ፣ ኦሮሚያና አዲስ አበባ አካባቢዎች ላይ ያጋጠሙ ነገሮችን ማስተዋል ነው።
አብረን እየተንቀሳቀስን ነው ብለው አላፈሩም፣ አላረፉም።
ሁለተኛ:– በብዙ መልኩ ኢኽዋን ከአሕባሽ የተሻለ ጉልበት አለው። በአጃቢ ብዛት፣ በሚዲያ አቅም፣ በፋይናንስ… ። ይህም ፈተናቸውን ከአሕባሽ የከፋ ያደርገዋል።
ሶስተኛ:– የራስን አማራጭ መጠቀም ይቻላል። አማራጮች ባልተዘጉበት ዐቂዳን ለድርድር ካቀረበው ህብረት ውስጥ መግባት ማስተዋል ሳይሆን ሌሎች በቀደዱት መፍሰስ ነው።
•
⑨ "መንግስት አህባሽን ከሀገር ያባርልን የሚል የሚደንቅ ጥያቄ ካነሳን እንጂ አሁን ያለው ተጨባጭ ከመለስ ድፍረት በፊት የነበረው ተጨባጭ ነው።"
።
"መንግስት አህባሽን ከሀገር ያባርልን" የሚል ቂል የለም። እንዲህ አይነት አነጋገር ነገር ከማንዘላዘል ያለፈ ፋይዳ የለውም። ጥያቄው ከአሕባሽ… ጋር ሳይጋፉ መስራት ይቻላል ነው። የነገሩ ማሰሪያ እዚህ ላይ ነው። እራስህን ችለህ መስራት ከቻልክ ከአፈንጋጮች ጋር ምን አሰለፈህ?
•
(10) "ሚዛናዊ እንሁን እያልን የተለመደ ዲስኩር እያላችሁ የምታጣጥሏትንም «ሂክማ» የምንደጋግመውም ለዚህ ነው" ይላል።
መልስ:–
~~~~
ሒክማን ሳይሆን በሒክማ ስም መነገድን ነው ያጣጣልነው። በሒክማ ስም መዋሸትን ነው የተቃወምነው። በሒክማ ስም እየሰበኩ ፀያፍ የዱርየ ቃላት የሚተፉ "ኡስታዞቻችሁን" ያዙ ነው ያልነው። የተቀያየሟቸውን ሙስሊሞች ሲፈልጉ ከሱንና ሲፈልጉ ከኢስላም የሚያስወጡ ዋልጌዎቻችሁን ያዙ ነው ያልነው። እናንተ "ሒክማ የላቸውም" ከምትሏቸው ውስጥ ይህን ያደረገ አላውቅም። ኢኽዋኖችን ዝም ብሎ ሰለፍዮችን ማብጠልጠል ሒክማ አይደለም ነው የምንለው። ታላላቅ ዑለማዎች፣ ነብያትን ጨምሮ ባደባባይ ሲጠለሹ የተለጎመ አፍ ሰለፍዮች ላይ ለመዝመት መሞከሩ ሒክማ አይደለም ነው የምንለው። ይህንን የተገለበጠ አካሄድ "ሒክማ" ማለት ተልቢስ ነው።
•
(11) "ሂክማን ካልተረዳህ ግመል በመርፌ ቀዳዳ እስኪገባ ዳዒ ልትሆን አትችልም።"
መልስ
~~~~~
ሒክማ ያለው ሰው ይህን ቢል አይገርምም ነበር። ለመሆኑ እነ ሙሐመድ ዐሊ፣ አወል ሸርሞሎ እናንተ ዘንድ ዳዒዎች ኡስታዞች የሆኑት ባለ ሒክማ ሆነው ነው? ሲበዛ ፍርደ ገምድል ነህ?!
ስለ ሒክማ ከመስበካችሁ በፊት የስድብ ናዳ እያወረዱ ያሉ ዋልጌዎቻችሁን አደብ አታስይዙም?
ወንድሜ ያልመሰላቸውን "ሒክማ የለውም" እያሉ ማጣጣል የብዙዎች መታወቂያ ነው። ልዩነቱ አንተ እራስህን የምታይበት አይን ሌላ መሆኑ ነው።
ሲጀመር ሒክማን የምትዘምረው ብዙ ጊዜ ሌሎችን ለማሳጣት ነው። እንጂ በዐቂዳ ሂሳብ ሁሉን በሚያግበሰብሱት፣ ዑለማዎችን በሚያጠለሹት ኢኽዋኖች ላይ "ሒክማ የላችሁም" ብለህ አልዘመትክም። ይህም "ሒክማህ" የከንቱ አላማ ማስፈፀሚያ እንደሆነ ነው የሚያሳየው።
በተረፈ እነ ኢብኑ ተይሚያም፣ እነ አልባኒም፣ እነ ሙቅቢል፣ እነ ረቢዕም… ሙብተዲዖች ዘንድ ሒክማ የላቸውም። የሞጋቾች ሙግት መለኪያ አይሆንም ለማለት ያክል ነው። (ይህን ስል "እራሳችሁን ከነዚህ ዐሊሞች ጋር አመሳሰላችሁ" የሚል የዋህ እንዳይኖር እየሰጋሁ ነው።)
Forwarded from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ጥቂት ስለ ኡስታዝ አቡ ሙስሊም
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
ወንድማችን ዑመር ሐሰን አቡ ሙስሊም ከ10 አመት በፊት የኡሙል ቁራ ዩኒቨርስቲ የትምህርት እድል (scholarship) በማግኘቱ በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ሲከታተለው የነበረውን አካዳሚ ትምህርት በመተው ወደ መካ አቀና። ከሄደበት ጊዜ አንስቶ እስካሁን ድረስ ለአስር አመታት ዒልም በመቅሰም ላይ ነው ያለው።
•
* የመጀመሪያ ዲግሪውን በመካ ከተማ ከሚገኘው የኡሙል ቁራ ዩኒቨርሲቲ በ
الكتاب والسنة مع الإعداد التربوي
አጠናቋል።
* የሁለተኛ ዲግሪውን በ الحديث وعلومه
(በሐዲሥ ጥናት ዘርፍ) መደበኛ ትምህርቱን እያጠናቀቀ በአሁኑ ሰዓት የሶስተኛ አመት ተማሪ ሲሆን የማሟያ ጥናት (ቴሲስ) በመስራት ላይ ነው።
* ከመደበኛው የኡሙል ቁራ ዩኒቨርስቲ ትምህርቱ ጎን ለጎን ከሄደበት ጊዜ አንስቶ ለ10 አመታት ታላላቅ ዑለማዎች ዘንድ በመሄድ በትጋት ይከታተላል። የተማረባቸውንና እየተማረባቸው ያሉ ዑለማዎችን ለምሳሌ ያክል ልጥቀስ:–
•
① ሸይኽ ረቢዕ ኢብኑ ሃዲ አልመድኸሊ፣
② ሸይኽ ዐብዱረሕማን አልዐጅላን፣
③ ሸይኽ ሙሐመድ ዐሊ ኣደም አልወሎዊ፣
④ ታዋቂው ሙሐዲሥ ሸይኽ ወሲዩላህ ኢብኑ ሙሐመድ አልዐባስ
⑤ ሸይኽ የሕያ ኢብኑ ዑሥማን (ከሸይኽ ሙቅቢል ሸይኾች ውስጥ ናቸው)፣
⑥ ሸይኽ ሙሐመድ ኢብኑ ዑመር ባዝሙል፣
⑦ ሸይኽ አሕመድ ኢብኑ ዑመር ባዝሙል (በአሁኑ ሰዓት ለማስትሬት ጥናቱ አማካሪው (አድቫይዘሩ) ናቸው።)
•
ከነዚህም በተጨማሪ ወደ መካ በሚመጡበት ጊዜ ባገኛቸው አጋጣሚ የተማረባቸው ዑለማዎች አሉ። ለምሳሌ:–
⑧ ሸይኽ ሷሊሕ ኢብኑ ፈውዛን አልፈውዛን
⑨ ሸይኽ ሷሊሕ አልሉሐይዳን፣
(10) ሙፍቲ ዐብዱል ዐዚዝ ኣሊ ሸይኽ፣
(11) ሸይኽ ፉኣድ ኢብኑ ሰዑድ አልዐምሪ፣
(12) ሸይኽ ዓዲል ኢብኑ መንሱር አልባሻ
(13) ሸይኽ አቡ ሁማም ሙሐመድ ኢብኑ ዐሊይ አልበይዷኒ እና ሌሎችም።
•
ከመካም ውጭ በተለያዩ ደውራዎች (አጫጭር ስልጠናዎች) ላይ በመካፈል ዒልም የቀሰመባቸው መሻይኾች ብዙ ናቸው። ለምሳሌ ያክል:–
•
* ሸይኽ ዘይድ ኢብኑ ሙሐመድ አልመድኸሊ (ረሒመሁላህ)፣
• ሸይኽ ሙሐመድ ኢብኑ ሃዲ አልመድኸሊ፣
• ሸይኽ ሱለይማን አርሩሐይሊ፣
• ሸይኽ ሙሐመድ ረምዛን አልሃጂሪ፣
• ሸይኽ ዐብዱረሕማን ኢብን ሙሕዪዲን፣
• ሸይኽ ዐልይ ኢብኑ የሕያ አልሐዳዲ፣
• ሸይኽ ዐብዱረዛቅ አልበድር፣
• ሸይኽ ሙሐመድ ኢብን ዐብዲል ወሃብ አልዐቂል፣
• ሸይኽ ኡሳማ አልዐምሪ እና ሌሎችም።
* ወንድም አቡ ሙስሊም ተባባሪና ፈጥኖ ሰው ጋር የሚግባባ ነው። ከሚማርባቸው መሻይኾች ዘንድ ያለው ቅርበት እና አመኔታ የሚያስቀና ነው።
* አቡ ሙስሊም የሳዑዲ ኢስላማዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር ከሚያሰማራቸው ዱዓት ጋር በመሆን በየዓመቱ ወደ መካ ለሚመጡ ኢትዮጵያውያን ሑጃጆች በማስተማር ይጠመዳል።
* ከሐጅ ውጪም የተለያዩ የማስተማር ስራዎች ላይ ይሳተፋል።
* በአንድ የመንግስት ትምህርት ቤት ውስጥም አስተምሯል።
* ወንድም አቡ ሙስሊም እኔ እስከማውቀው ድረስ ፌስቡክ ላይ የለም። በቴሌግራም ግን በአማርኛም በኦሮምኛም ያስተምራል። ትምህርቱን መከታተል ለሚሹ የቴሌግራም ቻናሉ ይሄውና
🌐 t.me/AbumuslimAlarsi
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
ወንድማችን ዑመር ሐሰን አቡ ሙስሊም ከ10 አመት በፊት የኡሙል ቁራ ዩኒቨርስቲ የትምህርት እድል (scholarship) በማግኘቱ በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ሲከታተለው የነበረውን አካዳሚ ትምህርት በመተው ወደ መካ አቀና። ከሄደበት ጊዜ አንስቶ እስካሁን ድረስ ለአስር አመታት ዒልም በመቅሰም ላይ ነው ያለው።
•
* የመጀመሪያ ዲግሪውን በመካ ከተማ ከሚገኘው የኡሙል ቁራ ዩኒቨርሲቲ በ
الكتاب والسنة مع الإعداد التربوي
አጠናቋል።
* የሁለተኛ ዲግሪውን በ الحديث وعلومه
(በሐዲሥ ጥናት ዘርፍ) መደበኛ ትምህርቱን እያጠናቀቀ በአሁኑ ሰዓት የሶስተኛ አመት ተማሪ ሲሆን የማሟያ ጥናት (ቴሲስ) በመስራት ላይ ነው።
* ከመደበኛው የኡሙል ቁራ ዩኒቨርስቲ ትምህርቱ ጎን ለጎን ከሄደበት ጊዜ አንስቶ ለ10 አመታት ታላላቅ ዑለማዎች ዘንድ በመሄድ በትጋት ይከታተላል። የተማረባቸውንና እየተማረባቸው ያሉ ዑለማዎችን ለምሳሌ ያክል ልጥቀስ:–
•
① ሸይኽ ረቢዕ ኢብኑ ሃዲ አልመድኸሊ፣
② ሸይኽ ዐብዱረሕማን አልዐጅላን፣
③ ሸይኽ ሙሐመድ ዐሊ ኣደም አልወሎዊ፣
④ ታዋቂው ሙሐዲሥ ሸይኽ ወሲዩላህ ኢብኑ ሙሐመድ አልዐባስ
⑤ ሸይኽ የሕያ ኢብኑ ዑሥማን (ከሸይኽ ሙቅቢል ሸይኾች ውስጥ ናቸው)፣
⑥ ሸይኽ ሙሐመድ ኢብኑ ዑመር ባዝሙል፣
⑦ ሸይኽ አሕመድ ኢብኑ ዑመር ባዝሙል (በአሁኑ ሰዓት ለማስትሬት ጥናቱ አማካሪው (አድቫይዘሩ) ናቸው።)
•
ከነዚህም በተጨማሪ ወደ መካ በሚመጡበት ጊዜ ባገኛቸው አጋጣሚ የተማረባቸው ዑለማዎች አሉ። ለምሳሌ:–
⑧ ሸይኽ ሷሊሕ ኢብኑ ፈውዛን አልፈውዛን
⑨ ሸይኽ ሷሊሕ አልሉሐይዳን፣
(10) ሙፍቲ ዐብዱል ዐዚዝ ኣሊ ሸይኽ፣
(11) ሸይኽ ፉኣድ ኢብኑ ሰዑድ አልዐምሪ፣
(12) ሸይኽ ዓዲል ኢብኑ መንሱር አልባሻ
(13) ሸይኽ አቡ ሁማም ሙሐመድ ኢብኑ ዐሊይ አልበይዷኒ እና ሌሎችም።
•
ከመካም ውጭ በተለያዩ ደውራዎች (አጫጭር ስልጠናዎች) ላይ በመካፈል ዒልም የቀሰመባቸው መሻይኾች ብዙ ናቸው። ለምሳሌ ያክል:–
•
* ሸይኽ ዘይድ ኢብኑ ሙሐመድ አልመድኸሊ (ረሒመሁላህ)፣
• ሸይኽ ሙሐመድ ኢብኑ ሃዲ አልመድኸሊ፣
• ሸይኽ ሱለይማን አርሩሐይሊ፣
• ሸይኽ ሙሐመድ ረምዛን አልሃጂሪ፣
• ሸይኽ ዐብዱረሕማን ኢብን ሙሕዪዲን፣
• ሸይኽ ዐልይ ኢብኑ የሕያ አልሐዳዲ፣
• ሸይኽ ዐብዱረዛቅ አልበድር፣
• ሸይኽ ሙሐመድ ኢብን ዐብዲል ወሃብ አልዐቂል፣
• ሸይኽ ኡሳማ አልዐምሪ እና ሌሎችም።
* ወንድም አቡ ሙስሊም ተባባሪና ፈጥኖ ሰው ጋር የሚግባባ ነው። ከሚማርባቸው መሻይኾች ዘንድ ያለው ቅርበት እና አመኔታ የሚያስቀና ነው።
* አቡ ሙስሊም የሳዑዲ ኢስላማዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር ከሚያሰማራቸው ዱዓት ጋር በመሆን በየዓመቱ ወደ መካ ለሚመጡ ኢትዮጵያውያን ሑጃጆች በማስተማር ይጠመዳል።
* ከሐጅ ውጪም የተለያዩ የማስተማር ስራዎች ላይ ይሳተፋል።
* በአንድ የመንግስት ትምህርት ቤት ውስጥም አስተምሯል።
* ወንድም አቡ ሙስሊም እኔ እስከማውቀው ድረስ ፌስቡክ ላይ የለም። በቴሌግራም ግን በአማርኛም በኦሮምኛም ያስተምራል። ትምህርቱን መከታተል ለሚሹ የቴሌግራም ቻናሉ ይሄውና
🌐 t.me/AbumuslimAlarsi
Telegram
ABU MUSLIM A-DUROOS
هذه قناة أبي مسلم العروسي ، ينشر فيها دروس العقيدة والفقه والحديث وغيرهم باللغة الأمهارية وأفان أرومو
እንደ ቀልድ ልምድ የሆኑ፣ ነገር ግን መስተካከል ካለባቸው ነገሮች ውስጥ
★ pleaae በእናትህ፣
★ በአባትህ፣
እና የመሳሰለውን እያሉ ሰዎች የሚደጋግሙት ሸሪአን የሚጋጭ አባባል ነው። ይህ አባባል ስህተት ነው።
ትክክለኛው
በአላህ ብቻ ብሎ መጠየቅ እና መለመን ነው ያለበተ።
https://t.me/SadatTextPosts
★ pleaae በእናትህ፣
★ በአባትህ፣
እና የመሳሰለውን እያሉ ሰዎች የሚደጋግሙት ሸሪአን የሚጋጭ አባባል ነው። ይህ አባባል ስህተት ነው።
ትክክለኛው
በአላህ ብቻ ብሎ መጠየቅ እና መለመን ነው ያለበተ።
https://t.me/SadatTextPosts
የዲን አስተማሪዎች ንግግራቸው በጣም ግልፅ ሊሆን ይገባል።
ይህን ማድረግ ከቻሉ ተማሪዎቻቸውን ከጭቅጭቅ ይቆጥባሉ።
ሸሪአም የመጣው ነገሮች ግልፅ በማድረግ ላይ ነው።
አላህ ቁርአንን አስመልክቶ እንዲህ ይላል
بِلِسَانٍ عَرَبِيّٖ مُّبِينٖ
ግልጽ በኾነ ዐረብኛ ቋንቋ (ቁርአን ወረደ)፡፡
يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ ٱتَّقُواْ ٱللَّهَ وَقُولُواْ قَوۡلٗا سَدِيدٗا
እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህን ፍሩ፡፡ ትክክለኛንም ንግግር ተናገሩ፡፡
አላህ ሐቁን ይምራን።
https://t.me/SadatTextPosts
ይህን ማድረግ ከቻሉ ተማሪዎቻቸውን ከጭቅጭቅ ይቆጥባሉ።
ሸሪአም የመጣው ነገሮች ግልፅ በማድረግ ላይ ነው።
አላህ ቁርአንን አስመልክቶ እንዲህ ይላል
بِلِسَانٍ عَرَبِيّٖ مُّبِينٖ
ግልጽ በኾነ ዐረብኛ ቋንቋ (ቁርአን ወረደ)፡፡
يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ ٱتَّقُواْ ٱللَّهَ وَقُولُواْ قَوۡلٗا سَدِيدٗا
እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህን ፍሩ፡፡ ትክክለኛንም ንግግር ተናገሩ፡፡
አላህ ሐቁን ይምራን።
https://t.me/SadatTextPosts
Forwarded from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ትብብር የጠየቀንን ሰው በምን አይን ነው የምናየው?!
~~~~~~~~
•
ኢብኑ ዐባስ ረዲየላሁ ዐንሁ እንዲህ ብለዋል: –
•
አራት ሰዎችን ውለታቸውን ልመልስ አልችልም።
1ኛ:– በሰላምታ የጀመረኝን ሰው
2ኛ:– ጉባኤ ላይ መቀመጫ ቦታ ያሰፋልኝ ሰው
3ኛ:– ጉዳዬን ሊፈፅምልኝ እግሮቹ አቧራ የለበሱ
4ኛው:– ግን አላህ – ዐዘ ወጀል – እንጂ ውለታውን የሚመልስልኝ የለም።"
•
"ማነው እሱ?!" ሲባሉ እንዲህ አሉ:–
•
"የሆነ ጉዳይ ገጥሞት ችግሩን የሚፈታለት ሰው እያሰበ ሌሊቱን ካነጋ በኋላ ከዚያም ችግሩን እንደምፈታለት አስቦኝ እኔ ላይ የጣለ ሰው ነው።"
•
[ወፈያቱል አዕያን፣ ኢብኑ ኸሊካን: 3/63]
~~~~~~~~
•
ኢብኑ ዐባስ ረዲየላሁ ዐንሁ እንዲህ ብለዋል: –
•
አራት ሰዎችን ውለታቸውን ልመልስ አልችልም።
1ኛ:– በሰላምታ የጀመረኝን ሰው
2ኛ:– ጉባኤ ላይ መቀመጫ ቦታ ያሰፋልኝ ሰው
3ኛ:– ጉዳዬን ሊፈፅምልኝ እግሮቹ አቧራ የለበሱ
4ኛው:– ግን አላህ – ዐዘ ወጀል – እንጂ ውለታውን የሚመልስልኝ የለም።"
•
"ማነው እሱ?!" ሲባሉ እንዲህ አሉ:–
•
"የሆነ ጉዳይ ገጥሞት ችግሩን የሚፈታለት ሰው እያሰበ ሌሊቱን ካነጋ በኋላ ከዚያም ችግሩን እንደምፈታለት አስቦኝ እኔ ላይ የጣለ ሰው ነው።"
•
[ወፈያቱል አዕያን፣ ኢብኑ ኸሊካን: 3/63]
Forwarded from MuhammedSirage M.Noor
ሰለፊና ኸለፊ አንድ አይደለም!!
ከነ አቡበክር ጋር የተደባለቀው አንዳንዱ "ተወካያችን" ወይም "መሪያችን" የአሽዐሪዮችን አቂዳ እምነቱ አድርጎ የያዘ ነው።
እነዚህ ሰዎች አላህ ከፍጡራን ፣ ከዐርሹ በላይ መሆኑን በማስተባበል የቁርአንንና የሐዲስን አስተምህሮ እንዲሁም የሰለፎችን ስምምነት ተፃረዋል ፣ ክደውበታል ።
አሽዐሪዮች ዘንድ "አላህ ለአማኞችና ለፍጡራን ያዝናል" ማለት ወይም የእዝነትን ባህሪ ለፈጣሪያችን ማፅደቅ ጥመትና ክህደት ነው— ቁርአንና ሐዲስ ላይ በሰፊው ግልፅ ሆኖ የምናገኘው አቋም ይሄው ሆኖ እያለ።
እነዚሁ ሰዎች ዘንድ አላህ በሙናፊቆችና በከሃዲያን ይቆጣል ብሎ ለሃያሉ ፈጣሪ የመቆጣትን ባህሪ ማስበት የሙስሊሞች እምነት አይደለም — ቅጥፈታቸው እዚህ የደረሰ ነው ። ባጠቃላይ፣ ቁርአንና ሐዲስ ላይ በምናገኛቸው በርካታ የአላህ ባህሪዎች የሚያምኑ አይደሉም ።
ታዲያ ከእንዲህ አይነት የአቂዳ ልዩነት ጋር ምን አይነት አንድነት ፣ ምን የሚሉት ጥምረት ነው የሚታለመው?!! እኛ ዘንድ እንዲህ አይነቱ መደባለቅ የሚሰራ ስሌት አይደለም!!
ከዚህም ሁሉ ጋር " ይህንን አንድነት የሚነካካን ሁሉ ተገቢውን ዋጋ እንሰጠዋለን! በዝምታ አናልፈውም በማለት ይዝታሉ !! አብሽሩ! የሻችሁትን ሁሉ በሉ! ዛቱም! አላህ ፊት የምንቆምበት ቀን የሚቀር አይደለምና ሁላችንም ተገቢያችንን ከአላህ ዘንድ እናገኛለን። የናንተን ዛቻ በመፍራት ሳንተኛና ሳንተነፍስ ማደር አንጀምርም— ኢን ሻ አላህ ። እኛ ትናንትም ዛሬም የጥቃት ዛቻን አናውቅም ። ስራችንን ግን አንፈታም! ልዩነታችንን ዛሬም በሰፊው እንተነፍሰዋለን !! በአላህ ፈቃድ እንቀጥላለን!! ሰለፊና ኸለፊን መደባለቅ ትልቅ ዙልም ነው !!
የሚገርመው ነገር ነጃሳው አህባሽ ከብልሹ የመንግስት አካላት ጋር ሙስሊሞችን ሲያሳስር በነሱም ላይ ሲዝት በወቅቱ "ሙናፊቅ " ብላችሁት ነበር። ዛሬ በተራችሁ መዛትን ያዛችሁ !! አየ እስስቱ ኢኽዋን! ! ብልሹው አሽዐሪ! !
ከነ አቡበክር ጋር የተደባለቀው አንዳንዱ "ተወካያችን" ወይም "መሪያችን" የአሽዐሪዮችን አቂዳ እምነቱ አድርጎ የያዘ ነው።
እነዚህ ሰዎች አላህ ከፍጡራን ፣ ከዐርሹ በላይ መሆኑን በማስተባበል የቁርአንንና የሐዲስን አስተምህሮ እንዲሁም የሰለፎችን ስምምነት ተፃረዋል ፣ ክደውበታል ።
አሽዐሪዮች ዘንድ "አላህ ለአማኞችና ለፍጡራን ያዝናል" ማለት ወይም የእዝነትን ባህሪ ለፈጣሪያችን ማፅደቅ ጥመትና ክህደት ነው— ቁርአንና ሐዲስ ላይ በሰፊው ግልፅ ሆኖ የምናገኘው አቋም ይሄው ሆኖ እያለ።
እነዚሁ ሰዎች ዘንድ አላህ በሙናፊቆችና በከሃዲያን ይቆጣል ብሎ ለሃያሉ ፈጣሪ የመቆጣትን ባህሪ ማስበት የሙስሊሞች እምነት አይደለም — ቅጥፈታቸው እዚህ የደረሰ ነው ። ባጠቃላይ፣ ቁርአንና ሐዲስ ላይ በምናገኛቸው በርካታ የአላህ ባህሪዎች የሚያምኑ አይደሉም ።
ታዲያ ከእንዲህ አይነት የአቂዳ ልዩነት ጋር ምን አይነት አንድነት ፣ ምን የሚሉት ጥምረት ነው የሚታለመው?!! እኛ ዘንድ እንዲህ አይነቱ መደባለቅ የሚሰራ ስሌት አይደለም!!
ከዚህም ሁሉ ጋር " ይህንን አንድነት የሚነካካን ሁሉ ተገቢውን ዋጋ እንሰጠዋለን! በዝምታ አናልፈውም በማለት ይዝታሉ !! አብሽሩ! የሻችሁትን ሁሉ በሉ! ዛቱም! አላህ ፊት የምንቆምበት ቀን የሚቀር አይደለምና ሁላችንም ተገቢያችንን ከአላህ ዘንድ እናገኛለን። የናንተን ዛቻ በመፍራት ሳንተኛና ሳንተነፍስ ማደር አንጀምርም— ኢን ሻ አላህ ። እኛ ትናንትም ዛሬም የጥቃት ዛቻን አናውቅም ። ስራችንን ግን አንፈታም! ልዩነታችንን ዛሬም በሰፊው እንተነፍሰዋለን !! በአላህ ፈቃድ እንቀጥላለን!! ሰለፊና ኸለፊን መደባለቅ ትልቅ ዙልም ነው !!
የሚገርመው ነገር ነጃሳው አህባሽ ከብልሹ የመንግስት አካላት ጋር ሙስሊሞችን ሲያሳስር በነሱም ላይ ሲዝት በወቅቱ "ሙናፊቅ " ብላችሁት ነበር። ዛሬ በተራችሁ መዛትን ያዛችሁ !! አየ እስስቱ ኢኽዋን! ! ብልሹው አሽዐሪ! !
Forwarded from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ቀዷ ያለበት ሰው የሸዋልን ስድስት ቀን መፆም ይችላል?
~~~~~`
የረመዳን ፆም ቀዷ ያለበት ሰው ቀዷውን ሳይፆም የሸዋልን ስድስት ቀን መፆም አይቻልም የሚሉ ፈትዋዎች በሰፊው ከመሰራጨታቸው የተነሳ ሌላ የተለየ (መፆም ይቻላል የሚል) ፈትዋ ያለ እስከማይመስል ደርሷል። እውነታው ግን ከዚህ የተለየ ነው።
① ለቀዷው ሰፊ ጊዜ ስላለና
② የሸዋል ጊዜ አጭር ስለሆነ
ከቀዷ በፊት ሸዋልን መፆም ይቻላል የሚለው የብዙሃን ዑለማዎች አቋም ነው። (ቀዷው ትንሽ ከሆነ ግን ግዴታውን አስቀድሞ ከዚያ የሸዋልን 6 ቀን ያስከትላል።)
ከስር ያያዝኩት የሸይኽ በድር ኢብኑ ዐልይ አልዑተይቢይ ፈትዋ ይህንኑ ሐሳብ የሚያጠናክር ነው።
youtu.be/P7hg2EzntxA
~~~~~`
የረመዳን ፆም ቀዷ ያለበት ሰው ቀዷውን ሳይፆም የሸዋልን ስድስት ቀን መፆም አይቻልም የሚሉ ፈትዋዎች በሰፊው ከመሰራጨታቸው የተነሳ ሌላ የተለየ (መፆም ይቻላል የሚል) ፈትዋ ያለ እስከማይመስል ደርሷል። እውነታው ግን ከዚህ የተለየ ነው።
① ለቀዷው ሰፊ ጊዜ ስላለና
② የሸዋል ጊዜ አጭር ስለሆነ
ከቀዷ በፊት ሸዋልን መፆም ይቻላል የሚለው የብዙሃን ዑለማዎች አቋም ነው። (ቀዷው ትንሽ ከሆነ ግን ግዴታውን አስቀድሞ ከዚያ የሸዋልን 6 ቀን ያስከትላል።)
ከስር ያያዝኩት የሸይኽ በድር ኢብኑ ዐልይ አልዑተይቢይ ፈትዋ ይህንኑ ሐሳብ የሚያጠናክር ነው።
youtu.be/P7hg2EzntxA
Forwarded from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ለኒካሕ ሃላፊ (ወልይ) የሚሆኑት እነማን ናቸው?
============================
ክፍል አንድ:– ያለ ሃላፊ (ወሊይ) ኒካሕ ዋጋ አለው?
~~~~~~~~~~~~~~~~
በመጀመሪያ ወሊይ ለኒካሕ ወሳኝ ቅድመ ሁኔታ ነው። ያለ ወሊይ እውቅና የተፈፀመ ጥምረት ፈፅሞ ከጋብቻ አይቆጠርም። ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል:–
(لا نكاح إلا بولي )
"በወሊይ ካልሆነ በስተቀር ኒካሕ የለም!!" [አልባኒ ሶሒሕ ብለውታል።]
•
* ስለዚህ ፈትም ሆነች ልጃገረድ አንዲት ሴት ያለ ወሊይ ፈፅሞ ልታገባ አይፈቅድላትም። ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል:–
أَيُّمَا امْرَأَةٍ نُكِحَتْ بِغَيْرِ إِذْنِ وَلِيِّهَا فَنِكَاحُهَا بَاطِلٌ، فَنِكَاحُهَا بَاطِلٌ، فَنِكَاحُهَا بَاطِلٌ
"ያለ ወሊዩዋ ይሁንታ የተገባች የትኛዋም ሴት ጋብቻዋ ውድቅ ነው! ጋብቻዋ ውድቅ ነው! ጋብቻዋ ውድቅ ነው!" [አቡ ዳውድና ቲርሚዚ ዘግበውታል።]
•
ክፍል ሁለት:– ወሊይ የሚሆኑት እነማን ናቸው?
~~~~~~~~~
ወሊይ የሚሆኑት በቅደም ተከተል የሚከተሉት ናቸው:–
1ኛ:– አባት፣
2ኛ:– የአባት አባት፣
3ኛ:– ወንዶች ልጆች፣
4ኛ:– ወንድም፣
5ኛ:– የወንድም ልጆች፣
8ኛ:– አጎቶች …እያለ ይቀጥላል።
•
* በአባትም በእናትም የሚገናኝ ወሊይ በአባት ብቻ ከሚገናኘው ይቀደማል።
* ተቀዳሚ የሆነው ወሊይ በቀላሉ የማይገኝ ከሆነ ተራውን ጠብቆ ሌሎች ወሊዮች ኃላፊነቱን ይወስዳሉ።
•
* አንድ ሰው ወሊይ ለመሆን
~~~~~~~~~~~~~~~~~
• ሙስሊም መሆን አለበት። ካፊር ወሊይ ሆኖ ሊድር አይችልም።
• አእምሮው ጤነኛ መሆን አለበት።
• ለአቅመ ኣደም የደረሰ መሆን አለበት።
• ወንድ መሆን አለበት።
•
* ወሊይ ከነ ጭራሹ ከሌለ ወይም ለአቅመ ኣደም የደረሱ ካልሆኑ ቃዲ ወሊይ ይሆናል።
َ (فالسلطان ولي من لا ولي له )
"አስተዳዳሪ ወሊይ ለሌለው ወሊይ ነው።" [አልባኒ ሶሒሕ ብለውታል]
•
* ወሊይ (ሃላፊ) በቅርብ ከሌለ ሌላ ሰው መወከል ይችላል። ውክልናው እንዲሁ "ይበጃል ላልከው ዳርልኝ" አይነት ክፍት ሊሆን ይችላል። ወይም "ለእከሌ ዳርልኝ" የሚል የተገደበ ሊሆን ይችላል።
* የሸሪዐ ቃዲዎች በሌሉበት ሃገር የኢስላማዊ መርከዝ ሃላፊ ወይም የመስጂድ ኢማም ወሊይ ሆኖ መዳር ይችላል።
* ወሊዩ ሺርክ ላይ የተዘፈቀ ወይም ሶላት የማይሰግድ ከሆነ ተራው ተጠብቆ ወደተሻሉት ኃላፊነቱ ይሻገራል።
* ወሊዩ #ያለ_ተጨባጭ_ምክንያት ለመዳር ፈቃደኛ ካልሆነ ተራው ተጠብቆ ወደተሻሉት ኃላፊነቱ ይሻገራል። ሌሎችም ፈቃደኛ ካልሆኑ ወደ ቃዲ ይሻገራል።
•
ጥንቃቄ ① ተራው ሳይጠበቅ (ሌሎች ወሊዮች እምቢ ሳይሉ) ዘሎ ወደ ቃዲ አይኬድም።
ጥንቃቄ ② ወላጅ ወይም የሚመለከተው ወሊይ በተጨባጭ ምክንያት ከከለከለ ሌሎች አማራጮችን መጠቀም አይፈቀድም። አርፎ መቀመጥ ነው።
ጥንቃቄ ③ የወሊዮች ምክንያት አሳማኝ ባይሆን እንኳ ያለ ወሊይ ይሁንታ የሚገባበት ጋብቻ አደጋዎች ሊኖሩት ስለሚችሉ ሴቶች ከመግባታቸው በፊት የሚችሉትን ያክል ጥንቃቄ ሊያደርጉ ይገባል። ዛሬ ብዙ ሰው ስነ ምግባሩ ወርዷል። ሴቷ ከቤተሰብ ተቀያይማ የገባችበት ጋብቻ ወይ ተመልካች አጥታ የሰቆቃ ህይወት ስትገፋ ወይ ደግሞ እንደ ዋዛ እየፈረሰ "ከሁለት ያጣች" ስትሆን ማየት እየተለመደ መጥቷል። ስለዚህ ከፍ ያለ ስጋት ካለ የቤተሰብ ተቃውሞ ተጨባጭ ባይሆን እንኳ መግባት አይገባም። ወላሁ አዕለም!!
============================
ክፍል አንድ:– ያለ ሃላፊ (ወሊይ) ኒካሕ ዋጋ አለው?
~~~~~~~~~~~~~~~~
በመጀመሪያ ወሊይ ለኒካሕ ወሳኝ ቅድመ ሁኔታ ነው። ያለ ወሊይ እውቅና የተፈፀመ ጥምረት ፈፅሞ ከጋብቻ አይቆጠርም። ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል:–
(لا نكاح إلا بولي )
"በወሊይ ካልሆነ በስተቀር ኒካሕ የለም!!" [አልባኒ ሶሒሕ ብለውታል።]
•
* ስለዚህ ፈትም ሆነች ልጃገረድ አንዲት ሴት ያለ ወሊይ ፈፅሞ ልታገባ አይፈቅድላትም። ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል:–
أَيُّمَا امْرَأَةٍ نُكِحَتْ بِغَيْرِ إِذْنِ وَلِيِّهَا فَنِكَاحُهَا بَاطِلٌ، فَنِكَاحُهَا بَاطِلٌ، فَنِكَاحُهَا بَاطِلٌ
"ያለ ወሊዩዋ ይሁንታ የተገባች የትኛዋም ሴት ጋብቻዋ ውድቅ ነው! ጋብቻዋ ውድቅ ነው! ጋብቻዋ ውድቅ ነው!" [አቡ ዳውድና ቲርሚዚ ዘግበውታል።]
•
ክፍል ሁለት:– ወሊይ የሚሆኑት እነማን ናቸው?
~~~~~~~~~
ወሊይ የሚሆኑት በቅደም ተከተል የሚከተሉት ናቸው:–
1ኛ:– አባት፣
2ኛ:– የአባት አባት፣
3ኛ:– ወንዶች ልጆች፣
4ኛ:– ወንድም፣
5ኛ:– የወንድም ልጆች፣
8ኛ:– አጎቶች …እያለ ይቀጥላል።
•
* በአባትም በእናትም የሚገናኝ ወሊይ በአባት ብቻ ከሚገናኘው ይቀደማል።
* ተቀዳሚ የሆነው ወሊይ በቀላሉ የማይገኝ ከሆነ ተራውን ጠብቆ ሌሎች ወሊዮች ኃላፊነቱን ይወስዳሉ።
•
* አንድ ሰው ወሊይ ለመሆን
~~~~~~~~~~~~~~~~~
• ሙስሊም መሆን አለበት። ካፊር ወሊይ ሆኖ ሊድር አይችልም።
• አእምሮው ጤነኛ መሆን አለበት።
• ለአቅመ ኣደም የደረሰ መሆን አለበት።
• ወንድ መሆን አለበት።
•
* ወሊይ ከነ ጭራሹ ከሌለ ወይም ለአቅመ ኣደም የደረሱ ካልሆኑ ቃዲ ወሊይ ይሆናል።
َ (فالسلطان ولي من لا ولي له )
"አስተዳዳሪ ወሊይ ለሌለው ወሊይ ነው።" [አልባኒ ሶሒሕ ብለውታል]
•
* ወሊይ (ሃላፊ) በቅርብ ከሌለ ሌላ ሰው መወከል ይችላል። ውክልናው እንዲሁ "ይበጃል ላልከው ዳርልኝ" አይነት ክፍት ሊሆን ይችላል። ወይም "ለእከሌ ዳርልኝ" የሚል የተገደበ ሊሆን ይችላል።
* የሸሪዐ ቃዲዎች በሌሉበት ሃገር የኢስላማዊ መርከዝ ሃላፊ ወይም የመስጂድ ኢማም ወሊይ ሆኖ መዳር ይችላል።
* ወሊዩ ሺርክ ላይ የተዘፈቀ ወይም ሶላት የማይሰግድ ከሆነ ተራው ተጠብቆ ወደተሻሉት ኃላፊነቱ ይሻገራል።
* ወሊዩ #ያለ_ተጨባጭ_ምክንያት ለመዳር ፈቃደኛ ካልሆነ ተራው ተጠብቆ ወደተሻሉት ኃላፊነቱ ይሻገራል። ሌሎችም ፈቃደኛ ካልሆኑ ወደ ቃዲ ይሻገራል።
•
ጥንቃቄ ① ተራው ሳይጠበቅ (ሌሎች ወሊዮች እምቢ ሳይሉ) ዘሎ ወደ ቃዲ አይኬድም።
ጥንቃቄ ② ወላጅ ወይም የሚመለከተው ወሊይ በተጨባጭ ምክንያት ከከለከለ ሌሎች አማራጮችን መጠቀም አይፈቀድም። አርፎ መቀመጥ ነው።
ጥንቃቄ ③ የወሊዮች ምክንያት አሳማኝ ባይሆን እንኳ ያለ ወሊይ ይሁንታ የሚገባበት ጋብቻ አደጋዎች ሊኖሩት ስለሚችሉ ሴቶች ከመግባታቸው በፊት የሚችሉትን ያክል ጥንቃቄ ሊያደርጉ ይገባል። ዛሬ ብዙ ሰው ስነ ምግባሩ ወርዷል። ሴቷ ከቤተሰብ ተቀያይማ የገባችበት ጋብቻ ወይ ተመልካች አጥታ የሰቆቃ ህይወት ስትገፋ ወይ ደግሞ እንደ ዋዛ እየፈረሰ "ከሁለት ያጣች" ስትሆን ማየት እየተለመደ መጥቷል። ስለዚህ ከፍ ያለ ስጋት ካለ የቤተሰብ ተቃውሞ ተጨባጭ ባይሆን እንኳ መግባት አይገባም። ወላሁ አዕለም!!
Forwarded from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ሙብተዲዕ ላይ አትማር!
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
ሸይኽ ኢብኑ ዑሠይሚን ረሒመሁላህ እንዲህ ብለዋል:–
•
"አንደበት ርቱእ የሆነ ማራኪ የአነጋገር ክህሎት ያለው ሙብተዲዕ ብናገኝ ከሱ ዘንድ ልንቀመጥ አይገባም። ምክንያቱም ሙብተዲዕ ነውና!! ለምንድን ነው የማይፈቀደው?
•
1⃣ አንደኛ:– ተንኮሉን ስለምንሰጋ ነው። ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም "ከአገላለፅም ድግምት አለ" ብለዋልና። ቢድዐው ላይ እንስማማው ዘንድ አእምሯችን ላይ ሊደግምብን ይችላል።
•
2⃣ ሁለተኛ: – ተቀምጠን መከታተላችን ይህን ሙብተዲዕ ያበረታታዋል። በዙሪያው የሚሆኑ ሰዎች እንዲበዙ እናደርጋለን። ታዋቂዎችና ክቡራን ሰዎች ሊቀመጡ ይችላሉ። ይሄ ደግሞ መኮፈስን እና በቢድዐው መጎረርን ይጨምረዋል።
•
3⃣ ሶስተኛ: – ከሙብተዲዑ ዘንድ የሚቀመጠው ሰው በክፉ ይጠረጠራል። ይህ የሚስተዋለው ግን ዘግይቶ ሊሆን ይችላል። ሰዎች የቢድዐ ባለቤት ዘንድ ስትሄድ ለጊዜው ባይገለጥም በክፉ ይጠረጥሩሀል። ስለዚህ እውቀት ፈላጊ የሆነ ሰው ከቢድዐ ሰዎች ሊርቅ ይገባል። ኧረ እንዲያውም ምራቁ ግዴታው ነው።"
•
📚 [ሸርሑል ሒልያ: 314]
⚠ "ነፃ ትርጉም"
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
ሸይኽ ኢብኑ ዑሠይሚን ረሒመሁላህ እንዲህ ብለዋል:–
•
"አንደበት ርቱእ የሆነ ማራኪ የአነጋገር ክህሎት ያለው ሙብተዲዕ ብናገኝ ከሱ ዘንድ ልንቀመጥ አይገባም። ምክንያቱም ሙብተዲዕ ነውና!! ለምንድን ነው የማይፈቀደው?
•
1⃣ አንደኛ:– ተንኮሉን ስለምንሰጋ ነው። ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም "ከአገላለፅም ድግምት አለ" ብለዋልና። ቢድዐው ላይ እንስማማው ዘንድ አእምሯችን ላይ ሊደግምብን ይችላል።
•
2⃣ ሁለተኛ: – ተቀምጠን መከታተላችን ይህን ሙብተዲዕ ያበረታታዋል። በዙሪያው የሚሆኑ ሰዎች እንዲበዙ እናደርጋለን። ታዋቂዎችና ክቡራን ሰዎች ሊቀመጡ ይችላሉ። ይሄ ደግሞ መኮፈስን እና በቢድዐው መጎረርን ይጨምረዋል።
•
3⃣ ሶስተኛ: – ከሙብተዲዑ ዘንድ የሚቀመጠው ሰው በክፉ ይጠረጠራል። ይህ የሚስተዋለው ግን ዘግይቶ ሊሆን ይችላል። ሰዎች የቢድዐ ባለቤት ዘንድ ስትሄድ ለጊዜው ባይገለጥም በክፉ ይጠረጥሩሀል። ስለዚህ እውቀት ፈላጊ የሆነ ሰው ከቢድዐ ሰዎች ሊርቅ ይገባል። ኧረ እንዲያውም ምራቁ ግዴታው ነው።"
•
📚 [ሸርሑል ሒልያ: 314]
⚠ "ነፃ ትርጉም"
ሪፍቅ (ልስላሴ)
አላህ ለፍጡራኖቹ አዛኝ ነው። ለዚህም ስለሆነ በተውሂድ ያዛቸዋል፣ ሽርክን እንዲርቁ ያስጠነቅቃቸዋል። በተውሂድ ላይ ኖረው፣ ሽርክን ከነባለቤቶቹ ርቀው፣ በተውሂድ ላይ ከሞቱ ጀነት የሚባል ልብ ጠርጥሮት፣ ጆሮ ሰምቶት፣ አይን አይቶት የማያውቅ አገር ተዘጋጅቶላቸዋል።
በተገላቢጦሹ አዛኙ አላህ፣ ፍትሃዊ፣ አያያዙ የበረታ፣ አሸናፊ ፈራጅ ነውና በሱ ላይ የሚያጋሩትን "አጋርያን እርኩሶች (ነጃሳዎች)" ናቸው ሁሉ ብሎ ጠርቷቸዋል። በዱንያ ውርደትን፣ በአኸይራ አሳማሚ ቅጣትን አዘጋጅቶላቸዋል። አላህ ይጠብቀን።
ልክ እንደዚሁ ለአማኞች ከነፍሳቸው በላይ የሆኑት ውዱ የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) አዛኝ ናቸው። በጣም አዛኝ ከመሆናቸውም የተነሳ ሰዎችን ዘላለም አለም እስታ ውስጥ የሚከታቸውን ሽርክ
1) እያዩ እንዳላዩ ዝም አላሉም፣
2) በሽርክና ቢድአ ጉዳይ ላይ አንድ ነን ብለው አልተስማሙም፣
3) ወደ ሽርክና ቢድአ የሚጣራን አይደለም ወደነዚህ መንገድ የሚወስዱን ነገሮች ዝም አላሉም።
በጣም አዛኙ ነብይ ስለ ቢድአ ሲያስጠነቅቁ ፊታቸው ደም ይለብስ ነበር፣ ይቆጡ ነበር ምክንያቱም ቢድአ ነውና የዚህ ኡማ ትልቁ ፀር።
ስለ ሪፍቅ ሲወራ ባይጠቀስም አብሮት ሺዳ በውስጡ አለ።
እዝነትም (ልስላሲ)፣ ጥንካሪም ቦታ ቦታ አላቸው። መቼም አንድ ዳኢ ሽርክን ስለሚያክል ታላቅ አደጋ እያስተማረ ለምን ይኮሳተራል? ተብሎ ሊጠየቅ አይገባውም። ምክንያቱም የነብያትም፣ በተለይ የነብዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምም አካሄድ ይሄ ነበረና።
ቢድአና ወንጀልንም ለያይተን ማስቀመጥ አለብን። የአላህ መልክተኛ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ዘንድ ወንጀለኞች (መጠጥ ጠጪዎች፣ ዝሙት የሰሩ) ሲመጡ የነበረውን አቀባበል አንርሳ። ልስላሲ ነበር ከመልክተኛው ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም የነበረው። እኚሁ የአላህ መልክተኛ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ጁምአ ኹጥባቸው ላይ "አዳዲስ በዲን ላይ ያሉ ፈጠራ ጭማሪዎችን ተጠንቀቁ፣ ሁሉም ፈጠራ ጥመት ነው፣ ሁሉም ጥመት የእሳት ነው" ሲሉ ምን ያህል ይቆጡ እንደነበር የሀዲስ መዛግብትን ማየት ይበጃል።
አንድ እናት ልጇን ብትገርፍ፣ አንድ አባት ልጁን ቢቆጣ እንዲስተካከልላቸው እንጂ ጠልተውት አይደለም። ስለሱ የማይጨነቁ ቢሆን ኖሮ ልጃቸውን ከነመጥፎ ባህሪው ይተውት ነበር።
ልክ እንደዚሁ ሁሉ መጥፎ ነገር ሽርክ፣ ቢድአ፣ መሀይምነት፣ ድራማ፣ ፊልምና የመሳሰሉት ተስፋፍተው ሲያዩ የአላህ ባርያዎች ስለሚያዝኑ ነው ለኡማው ያ ሁሉ ውርጅብኝ ከየአቅጣጫው እየወረደባቸው ሀቁን የሚናገሩት። አላህም ለባሮቹ ስለሚያዝን ነው አዛኝ ከመሆኑም ጋር ማስጠንቀቂያዎችንና ዛቻዎችን አብሮ ያስቀመጠው። ነብዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምም እንደዚሁ እዝነት በሚያስፈልገው ቦታ እዝነት፣ ጠንከር ማለት በሚያስፈልገው ቦታ ጠንከር ብለው ያሳዩን።
አሁን ያለንበት ወቅት ላይ በጣም እዝነት ያስፈልገዋል ይህ የማይካድ እውነታ ነው። ይህ ማለት ግን ቢድአና ሙብተዲ ላይ አለመናገር ማለት አይደለም። ቢድአና ሙብተዲ ላይ መናገር ለኡማው በጣም እጅግ በጣም ከማዘን ነው። ምክንያቱም ኢስላምንና ሙስሊሞችን ከውስጥ የሚንደውና የሚያዳክመው አዳዲስ መንገዶችና የቢድአ ሰዎች ናቸውና።
አላህ ሁሉንም በቦታው ላይ ከሚያስቀምጡት ባርያዎች ያድርገን። አላህ ሆይ! እውቀትን ጨምርልን፣ በምናውቀውም የምንሰራ አድርገን፣ በፈተና ወቅትም በሃቅ ላይ ከሚፀኑት አድርገን።
https://t.me/SadatTextPosts
አላህ ለፍጡራኖቹ አዛኝ ነው። ለዚህም ስለሆነ በተውሂድ ያዛቸዋል፣ ሽርክን እንዲርቁ ያስጠነቅቃቸዋል። በተውሂድ ላይ ኖረው፣ ሽርክን ከነባለቤቶቹ ርቀው፣ በተውሂድ ላይ ከሞቱ ጀነት የሚባል ልብ ጠርጥሮት፣ ጆሮ ሰምቶት፣ አይን አይቶት የማያውቅ አገር ተዘጋጅቶላቸዋል።
በተገላቢጦሹ አዛኙ አላህ፣ ፍትሃዊ፣ አያያዙ የበረታ፣ አሸናፊ ፈራጅ ነውና በሱ ላይ የሚያጋሩትን "አጋርያን እርኩሶች (ነጃሳዎች)" ናቸው ሁሉ ብሎ ጠርቷቸዋል። በዱንያ ውርደትን፣ በአኸይራ አሳማሚ ቅጣትን አዘጋጅቶላቸዋል። አላህ ይጠብቀን።
ልክ እንደዚሁ ለአማኞች ከነፍሳቸው በላይ የሆኑት ውዱ የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) አዛኝ ናቸው። በጣም አዛኝ ከመሆናቸውም የተነሳ ሰዎችን ዘላለም አለም እስታ ውስጥ የሚከታቸውን ሽርክ
1) እያዩ እንዳላዩ ዝም አላሉም፣
2) በሽርክና ቢድአ ጉዳይ ላይ አንድ ነን ብለው አልተስማሙም፣
3) ወደ ሽርክና ቢድአ የሚጣራን አይደለም ወደነዚህ መንገድ የሚወስዱን ነገሮች ዝም አላሉም።
በጣም አዛኙ ነብይ ስለ ቢድአ ሲያስጠነቅቁ ፊታቸው ደም ይለብስ ነበር፣ ይቆጡ ነበር ምክንያቱም ቢድአ ነውና የዚህ ኡማ ትልቁ ፀር።
ስለ ሪፍቅ ሲወራ ባይጠቀስም አብሮት ሺዳ በውስጡ አለ።
እዝነትም (ልስላሲ)፣ ጥንካሪም ቦታ ቦታ አላቸው። መቼም አንድ ዳኢ ሽርክን ስለሚያክል ታላቅ አደጋ እያስተማረ ለምን ይኮሳተራል? ተብሎ ሊጠየቅ አይገባውም። ምክንያቱም የነብያትም፣ በተለይ የነብዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምም አካሄድ ይሄ ነበረና።
ቢድአና ወንጀልንም ለያይተን ማስቀመጥ አለብን። የአላህ መልክተኛ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ዘንድ ወንጀለኞች (መጠጥ ጠጪዎች፣ ዝሙት የሰሩ) ሲመጡ የነበረውን አቀባበል አንርሳ። ልስላሲ ነበር ከመልክተኛው ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም የነበረው። እኚሁ የአላህ መልክተኛ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ጁምአ ኹጥባቸው ላይ "አዳዲስ በዲን ላይ ያሉ ፈጠራ ጭማሪዎችን ተጠንቀቁ፣ ሁሉም ፈጠራ ጥመት ነው፣ ሁሉም ጥመት የእሳት ነው" ሲሉ ምን ያህል ይቆጡ እንደነበር የሀዲስ መዛግብትን ማየት ይበጃል።
አንድ እናት ልጇን ብትገርፍ፣ አንድ አባት ልጁን ቢቆጣ እንዲስተካከልላቸው እንጂ ጠልተውት አይደለም። ስለሱ የማይጨነቁ ቢሆን ኖሮ ልጃቸውን ከነመጥፎ ባህሪው ይተውት ነበር።
ልክ እንደዚሁ ሁሉ መጥፎ ነገር ሽርክ፣ ቢድአ፣ መሀይምነት፣ ድራማ፣ ፊልምና የመሳሰሉት ተስፋፍተው ሲያዩ የአላህ ባርያዎች ስለሚያዝኑ ነው ለኡማው ያ ሁሉ ውርጅብኝ ከየአቅጣጫው እየወረደባቸው ሀቁን የሚናገሩት። አላህም ለባሮቹ ስለሚያዝን ነው አዛኝ ከመሆኑም ጋር ማስጠንቀቂያዎችንና ዛቻዎችን አብሮ ያስቀመጠው። ነብዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምም እንደዚሁ እዝነት በሚያስፈልገው ቦታ እዝነት፣ ጠንከር ማለት በሚያስፈልገው ቦታ ጠንከር ብለው ያሳዩን።
አሁን ያለንበት ወቅት ላይ በጣም እዝነት ያስፈልገዋል ይህ የማይካድ እውነታ ነው። ይህ ማለት ግን ቢድአና ሙብተዲ ላይ አለመናገር ማለት አይደለም። ቢድአና ሙብተዲ ላይ መናገር ለኡማው በጣም እጅግ በጣም ከማዘን ነው። ምክንያቱም ኢስላምንና ሙስሊሞችን ከውስጥ የሚንደውና የሚያዳክመው አዳዲስ መንገዶችና የቢድአ ሰዎች ናቸውና።
አላህ ሁሉንም በቦታው ላይ ከሚያስቀምጡት ባርያዎች ያድርገን። አላህ ሆይ! እውቀትን ጨምርልን፣ በምናውቀውም የምንሰራ አድርገን፣ በፈተና ወቅትም በሃቅ ላይ ከሚፀኑት አድርገን።
https://t.me/SadatTextPosts
ሐጅ እና ለይለቱል ቀድር
በለይለተል ቀርድ የዘንድሮ ሐጅ አድራጊዎች እንማን እንደሆኑ ይወሰናል፡፡
[Q 44:4] فِيهَا يُفْرَقُ كُلُّ أَمْرٍ حَكِيمٍ
በውስጧ (በለይለተል ቀድር) የተወሰነው ነገር ሁሉ ይልለያል፡፡
አብደላህ ኢብን አባስ (ረድየላሁ አንሁ) ይህንን ሲያብራሩ እንዲህ አሉ
“ከኡሙል ኪታብ (ከለውሀል መህፉዝ) በለይለተል ቀድር በአመት ውስጥ የሚከሰቱት ነገሮች ከሞት፣ ከህይወት፣ ከሲሳይ (ሪዝቅ)፣ ከዝናብ፣ ሐጅ አድራጊዎችም ጭምር እገሌ ሐጅ ያደርጋል፣ እገሌ ሐጅ ያደርጋል ሁሉ ይባላል ተብሎ ውሳኔው ይገለበጣል፡፡”
https://t.me/SadatTextPosts
በለይለተል ቀርድ የዘንድሮ ሐጅ አድራጊዎች እንማን እንደሆኑ ይወሰናል፡፡
[Q 44:4] فِيهَا يُفْرَقُ كُلُّ أَمْرٍ حَكِيمٍ
በውስጧ (በለይለተል ቀድር) የተወሰነው ነገር ሁሉ ይልለያል፡፡
አብደላህ ኢብን አባስ (ረድየላሁ አንሁ) ይህንን ሲያብራሩ እንዲህ አሉ
“ከኡሙል ኪታብ (ከለውሀል መህፉዝ) በለይለተል ቀድር በአመት ውስጥ የሚከሰቱት ነገሮች ከሞት፣ ከህይወት፣ ከሲሳይ (ሪዝቅ)፣ ከዝናብ፣ ሐጅ አድራጊዎችም ጭምር እገሌ ሐጅ ያደርጋል፣ እገሌ ሐጅ ያደርጋል ሁሉ ይባላል ተብሎ ውሳኔው ይገለበጣል፡፡”
https://t.me/SadatTextPosts
ሐጅ እና ለይለቱል ቀድር
በለይለተል ቀርድ የዘንድሮ ሐጅ አድራጊዎች እንማን እንደሆኑ ይወሰናል፡፡
[Q 44:4] فِيهَا يُفْرَقُ كُلُّ أَمْرٍ حَكِيمٍ
በውስጧ (በለይለተል ቀድር) የተወሰነው ነገር ሁሉ ይልለያል፡፡
አብደላህ ኢብን አባስ (ረድየላሁ አንሁማ) ይህንን ሲያብራሩ እንዲህ አሉ
“ከኡሙል ኪታብ (ከለውሀል መህፉዝ) በለይለተል ቀድር በአመት ውስጥ የሚከሰቱት ነገሮች ከሞት፣ ከህይወት፣ ከሲሳይ (ሪዝቅ)፣ ከዝናብ፣ ሐጅ አድራጊዎችም ጭምር እገሌ ሐጅ ያደርጋል፣ እገሌ ሐጅ ያደርጋል ሁሉ ይባላል ተብሎ ውሳኔው ይገለበጣል፡፡”
https://t.me/SadatTextPosts
በለይለተል ቀርድ የዘንድሮ ሐጅ አድራጊዎች እንማን እንደሆኑ ይወሰናል፡፡
[Q 44:4] فِيهَا يُفْرَقُ كُلُّ أَمْرٍ حَكِيمٍ
በውስጧ (በለይለተል ቀድር) የተወሰነው ነገር ሁሉ ይልለያል፡፡
አብደላህ ኢብን አባስ (ረድየላሁ አንሁማ) ይህንን ሲያብራሩ እንዲህ አሉ
“ከኡሙል ኪታብ (ከለውሀል መህፉዝ) በለይለተል ቀድር በአመት ውስጥ የሚከሰቱት ነገሮች ከሞት፣ ከህይወት፣ ከሲሳይ (ሪዝቅ)፣ ከዝናብ፣ ሐጅ አድራጊዎችም ጭምር እገሌ ሐጅ ያደርጋል፣ እገሌ ሐጅ ያደርጋል ሁሉ ይባላል ተብሎ ውሳኔው ይገለበጣል፡፡”
https://t.me/SadatTextPosts