Sadat_Text_Posts
10K subscribers
291 photos
8 videos
12 files
378 links
Download Telegram
የወር ደሞዝተኛ ዘካ
~~~~~~~~~~~~
የወር ደሞዝተኛ ገንዘብ ዘካ ግዴታ የሚሆንበት የሚከተሉትን መስፈርቶች ሲያሟላ ነው።

① ለዘካ መነሻ መጠን (ኒሷብ) ሲደርስ።
ይህም ከኒሷብ በታች የሆነና በየጊዜው ወጭ የሚደረግ ገንዘብ ዘካ አይመለከተውም።

② ኒሷብ ከደረሰ በኋላ አመት ሲቆይ። አመት ያልሞላው ከሆነ ዘካ አይመለከተውም።

ስለዚህ ለዘካ መጠን ደርሶ አመት ሲሞላው ዘካ ያወጣል። ለማውጪያ ጊዜ ይሆነው ዘንድ ከአመቱ ውስጥ አንድ ቀን ይወስናል። ከዚያም እስከ መጨረሻው ወር ከተጠራቀመው አጠቃላይ ገንዘብ ላይ 2•5% ያወጣል።

ውስብስብ አሰራር ውስጥ ከመግባት በዚህ መልኩ መጠቀም የተሻለ ነው። ወላሁ አዕለም።

@ibnumunewor
የዘንድሮው የወረቀት ብር ዘካ መነሻ መጠን ስንት ነው?
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
መግቢያ: –
የወረቀት ብር ኖት ዘካ አለበት ወይስ የለበትም በሚለው ላይ ቀደም ብሎ ሞቅ ያለ ውዝግብ ነበር። ነገር ግን "ዘካ የለበትም" የሚለው ሀሳብ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀዘቀዘ፣ እየደበዘዘ ነው ያለው። ምክንያቱም ዛሬ የሰው ንብረት እንዳለ የወረቀት ብር በመሆኑ በዚህ ላይ ዘካ የለም ማለት እንዳለ ዘካን ወደ ማራቆት ነው የሚወስደው። በዚህና በሌሎችም ምክንያቶች የብዙሃን ዑለማእ አቋም ከወረቀት ብር ኖት ዘካ ሊወጣ ይገባል የሚለው ሆኗል።


መነሻ ተመኑ (ኒሷቡ) ስንት ነው?
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
የወረቀት ብርን የዘካ መነሻ መጠን አስመልክቶ የዘመናችን ዑለማዎች ሶስት የተለያዩ ሐሳቦችን ሰንዝረዋል። (የልዩነታቸው መንስኤ የወረቀት ብር ድሮ ያልነበረ መሆኑ ነው።) እነሱም: –

ሐሳብ 1:– መነሻ ተመኑ የብር (ሲልቨር) መነሻ ተመን መድረስ ነው። ይህም 595 ግራም ብር የሚገዛ ማለት ነው።

ሐሳብ 2:– መነሻ ተመኑ የወርቅ መነሻ ተመን መድረስ ነው። ይህም 85 ግራም ወርቅ የሚገዛ ማለት ነው።

ሐሳብ 3:– ከሁለቱ መለኪያዎች ዝቅ ያለው ተመን ዋጋ ላይ መድረስ ነው።

★ በዚህ ርእስ ላይ ጥቂት ዳሰሳ ብናደርግ ሶስቱንም ሐሳቦች በየፊናቸው ያንፀባረቁ ዑለማዎች ሊገጥሙን ይችላሉ።

የቱ ሚዛን ይደፋል?
~~~~~~~~~~~~
ወርቅና ብር በነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ዘመን የነበሩ እራሳቸውን የቻሉ መገበያያዎች ናቸው። ሁለቱም የተረጋገጡ መለኪያዎች ናቸው። ስለዚህ ሁለቱም መለኪያ እንደሆኑ ከተማመንን ከሁለቱ መለኪያዎች የኒሷብ መጠኑ ያነሰውን እናስቀድማለን። (ከላይ 3ኛው ምርጫ ማለት ነው።) ዝቅ ያለውን አልፈን ወደ ከፍተኛው ለመዝለል አጥጋቢ ምክንያት ያስፈልገናል።

ይህንን እንደ ቀመር ከወሰድን በኋላ በአሁኑ ጊዜ ስላለው የወርቅና የብር ዋጋ ስንመለከት ሰፊ ልዩነት እናገኛለን። ቀድመን የምናገኘው የብሩን ኒሷብ ነው። ስለዚህ 595 ግራም ብር ለወረቀት ብር ኖት መነሻ የዘካ ተመን ይሆናል ማለት ነው።

ወቅታዊ ዋጋ
~~~~~~~~
ብር በግራም ስንት እንደሆነ ከተለያዩ ቦታዎች ለማጣራት ሞክሬያለሁ። የደረስኩበት ድምዳሜ በግራም 55 ብር ነው የሚል ነው። ይህም ማለት
55 ብር × 595 ግራም=32,725 ብር ይሆናል ማለት ነው።
ስለዚህ በአሁኑ ወቅት 32,725 ብርና ከዚህ በላይ ያለው ሰው ያጠቃላዩን 2•5% ያወጣል ማለት ነው። ለምሳሌ
32,725 ብር ያለው 818.10 ያወጣል።
40 ሺ ብር ያለው 1 ሺ ብር ያወጣል።
50 ሺ ብር ያለው 1,250 ብር ያወጣል።
በዚህ መሰረት ሌሎችንም መጠኖች ማስላት ነው።

* ልብ በሉ! ብሩ ለዘካ መጠን ከደረሰ በኋላ አመት ሲቆይ ነው ዘካ ግዴታ የሚሆንበት። አመት ካልሞላው ዘካ አይመለከተውም።

والله أعلم
ለምርመራ የሚሰጥ ደም ፆም ያበላሻል?
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
ለህክምና ምርመራ ደም መስጠት ፆም አያበላሽም። የሸይኽ ኢብኑ ባዝንና የኢብኑ ዑሠይሚንን ፈትዋ ይመልከቱ።

[መጅሙዑ ፈታዋ ኢብን ባዝ: 15/274] [ፈታዋ አርካኒል ኢስላም፣ ኢብኑ ዑሠይሚን : 478]
ብድርና ዘካ
~~~~~~
ገንዘቡን ለሰው ያበደረ ሰው
① ተበዳሪው ቸግሮት መመለስ ካልቻለ ወይም ደግሞ ባይቸግረውም ዛሬ ነገ እያለ የሚያጉላላ ከሆነ ባለ ገንዘቡ የዘካ ግዴታ የለበትም። ኋላ ገንዘቡ እጁ ከገባ ከገባበት ጊዜ ጀምሮ አመት ሲሞላው ዘካ ግዴታ ይሆንበታል።

② ተበዳሪው ቢጠየቅ በቀላሉ የሚመልሰው አይነት ብድር ግን ከተበዳሪው ተቀበለውም አልተቀበለውም ዘካው ሊወጣ ግድ ይላል።

ይህን የኢብኑ ባዝ ፈትዋ ያመሳክሩ።

https://binbaz.org.sa/fatwas/8946/%D9%84%D8%A7-%D8%B2%D9%83%D8%A7%D8%A9-%D9%81%D9%8A-%D8%A7%D9%84%D8%AF%D9%8A%D9%86-%D8%A7%D9%84%D8%B0%D9%8A-%D8%B9%D9%84%D9%89-%D9%85%D8%B9%D8%B3%D8%B1
በታክሲ ላይ ዘካ አለበት?
~~~~~~~~~~~~~~~
የህዝብ ማመላለሻና የጭነት መኪኖች በገቢያቸው እንጂ በራሳቸው ዘካ የለባቸውም። የሚያስገቡት ገቢ ለዘካ መጠን ከደረሰ በኋላ አመት ከሞላው የአጠቃላዩን 2•5% ዘካ ይወጣል።

[መጅሙዑል ፈታዋ፣ ኢብኑ ባዝ: 14/181]
[መጅሙዑል ፈታዋ፣ አልለጅነት አድዳኢማህ: 9/349]
ለሽያጭ ሳይሆን ለኪራይ የተዘጋጀ ቤት በራሱ ዘካ የለበትም። ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም "አንድ ሙስሊም በባሪያውና በፈረሱ ላይ ዘካ የለበትም" ማለታቸው ለዚህ መነሻ መሆን ይችላል። ባይሆን ከኪራዩ የሚሰበሰበው ገንዘብ ለአቅመ ዘካ ከደረሰና አመት ከሞላው 2•5% ዘካ ይወጣለታል።
የዘካ ፋይዳዎች እና ዘካን ያለመስጠት አደጋዎች!
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
ለሰጪው
① ዘካ ከአምስቱ የኢስላም ምሰሶዎች አንዱ እንደመሆኑ በትክክል የሚሰጥ ሰው ይህን የኢስላሙን ምሰሶ ነው ያፀናው። ባይሰጥ ደግሞ ይህን ምሰሶውን ነው ያናጋው።
② ዘካ በኢኽላስ እስከተወጣ ድረስ ኢማንን ይጨምራል፤ የአላህን ውዴታ ያጎናፅፋል።
③ ዘካ ወንጀልን ያብሳል። ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም "ውሃ እሳትን እንደሚያጠፋው ሶደቃ ሃጢአትን ያጠፋል" ብለዋል።
④ ዘካ ፈተናን መከራን ይመክታል ።
⑤ ዘካ ማውጣት የአዛኝነት፣ የርህሩህነት፣ የተቆርቋሪነት ባህሪን ያላብሳል። ዛሬ ራስ ወዳድነት በነገሰበት ዘመን ለሙስሊም ወገን ከምላስ ባለፈ ከልብ መቆርቆርና ማዘን ትልቅ መታደል ነው።
⑥ ዘካ የቀልብ መለዘብ፣ በሞራል መገራት፣ ከክፋት፣ ከስስት፣ ከድንበር ዘለል የዱንያ ፍቅር እንዲወጡ ሰዎችን ያግዛል።
⑦ ዘካ የህሊና እርካታን ፣ መንፈሳዊ ሰላምን፣ ስነ ልቦናዊ መረጋጋትን ያጎናፅፋል።
⑧ ዘካ ገንዘብን ያፋፋል፣ በረካ ይጨምርበታል።
⑨ ዘካ ለችግር ጊዜ ደራሽ ወገን እንዲኖረንም ይጠቅማል። መቼም ሁሌ ድሎት፣ ሁሌ ምቾት የለም። ዱንያ ተገለባባጭ ናት።

ለተቀባዩ ደግሞ
~~~~~~~~
① በዘካ ድሃዎች ይደጎማሉ ወይም ይቋቋማሉ።
② ሃብታሙን በቅናትና በክፋት ከማየት እንዲታቀቡ ያግዛቸዋል።
③ ይህን የሚደጎሙበትን ህግ ለዘረጋው ጌታ ውዴታ ለሃይማኖታቸውም ቀናኢነትን እንዲያሳድሩ ይጠቅማቸዋል። ይህ ሳይሆን ሲቀር ግን ከፊሉ ጌታውን ሊያማርር፣ ኢማኑ ሊሸረሸር ይችላል።
④ ለገንዘብ ሲሉ እምነታቸውን ከመሸጥ፣ በጥፋት ላይ ከመሰማራት ያቅባቸዋል።

የዘካ ማህበራዊ ፋይዳዎች
~~~~~~~~~~~
① በሰጭና በተቀባይ መካከል ትስስር እንዲጠነክር ያደርጋል። ዝምዳናን ይቀጥላል። የሰመረ ጉርብትና እንዲኖር ያግዛል። ምክንያቱም ነፍስ በጎ ለዋለላት አካል ተዘንባይ ነችና።
② ዘካ በአግባቡ ከተወጣ በሀብታሙና በደሃው መካከል ያለውን የሃብት ርቀት ስለሚያጠብ ለጤናማ ኢኮኖሚ የማይናቅ አስተዋጽኦ ያበረክታል።
③ ዘካ ከድህነት ወለል በታች ያሉ ወገኖች ተስፋ በመቁረጥ ወደ ስርቆትና ዝርፊያ በማምራት ማህበራዊ ቀውስ እንዳይፈጥሩ ይታደጋል።
④ ዘካ ሀብታሙን ሃላፊነት እንዲሰማው ስለሚያደርግ ከስግብግብ የካፒታሊዝም አስተሳሰብ በማቀብ የሃገር ሐብት በጥቂቶች እጅ ብቻ እንዳይሆን ያግዛል።

ዘካ አለመስጠት ያለው አደጋ
~~~~~~~~~~~~~~~~~
ባጭሩ እስካሁን የተዘረዘሩትን ፋይዳዎች ያሳጣል። የዱንያም የአኺራም ኪሳራን ያስከትላል። ሰጪንም፣ ተቀባይንም፣ ማህበረሰብንም አገርንም ይጎዳል።

ወገኔ ሆይ! ዘካ ወጅቦብሀል? እንግዲያውስ ውለታ ቢስ አትሁን። ላንተ የሰጠህ ጌታ ነው "ስጥ" ብሎ ያዘዘህ። በሰፊው ከሰጠህ ነው ጢኒጥየ ቆንጥረህ ስጥ ያለህ። ልብህ ፈታ ብሎ፣ ደስ ብሎህ ስጥ። ደስ እያለህ ጀነትን ትወርሳለህ።
ደግሞ አትሸወድ! ዘካ ገንዘብህን ያፋፋዋል እንጂ አይቀንሰውም። ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም "የአንድን ባሪያ ገንዘብ ሶደቃ አይቀንሰውም" ብለዋል።
በነገርህ ላይ የዘካው መጠን ያንተ ድርሻ፣ ያንተ ገንዘብ አይደለም። ዘካውን ባስቀረህ ጊዜ የሰው ሐቅ እየበላህ እንደሆነ ይታወቅህ። አይሰቀጥጥም? "ላቤን ጠፍ አድርጌ ያመጣሁት ነው" እያልክ የምትጎረር ከሆንክ ግን የነ ቃሩን ባቡር ላይ ተሳፍረሀል። ወዴት እንደሚወስድህ አልነግርህም።
ወንድሜ! ያገኘህ ባንተ ብልጠትም ብቃትም አይደለም። ስንት የበቁ የነቁ በድህነት እየማቀቁ መሰለህ?! ስንት መንቻካ ዶክተሮች ፕሮፌሰሮች ስንት ቁልቁል መደመር የማይችሉ ቱጃሮች አሉ።
ይልቅ ልንገርህ! ሌሎችን በድህነት የሚፈትነው ጌታ አንተን በሃብት እየፈተነህ ነው። እራስህ በምታዝበት ገንዘብ ፈተናውን ከወደቅክ አሳዛኝ ክሽፈት ነው። ገንዘብህ ተከትሎህ ቀብር አይገባም። ወራሽ ወገኖችህ የቀብር ጥያቄን፣ የአላህን ምርመራ አይታደጉህም። ዛሬ ነገ አትበል! ሞት አለቅጥ የበዛበት ዘመን ላይ ነን። እንደ ወጣ የሚቀረውን ብዛት እያየን ነው። ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ዘካ የማያወጣ ሰው ነገ በቂያማ ቀን የገዛ ገንዘቡ እባብ ሆኖ እንደሚያሰቃየው የተናገሩትን አስብ።
ደግሞም ዙሪያ ገባህን አስተውል። እድለኛ ማለት ሌላው ከደረሰው የተመከረ ነው። አላህ ሃብት ከሰጣቸው በኋላ ዘካ ሳያወጡ፣ሳያውቁ ሐጅ ሳይፈፅሙ አልፈው በቁጭት ወላፈን እየተለበለቡ ያሉ ስንት አግኝተው ያጡ ወገኖች አሉ?!
ባጭሩ ገንዘብህ ወይ ጀነትህ ወይ ጀሀነምህ ነው። ምርጫው ደግሞ በእጅህ ነው። ያሻህን ምረጥ።
የረመዳን ሌሊት!
~~~~~~~~~~
በጌታቸው የሚተማመኑ ሰዎች ስለሱ እንዴት እንደሚናገሩ ተመልከቱ!

① ሷሊሕ እንዲህ ብለዋል:–

﴿إن ربي قريب مجيب﴾

"ጌታዬ በእርግጥ ቅርብ (ፀሎትን) ተቀባይ ነው!" [ሁድ: 61]

② ሹዐይብ እንዲህ ብለዋል:–

﴿إن ربي رحيم ودود﴾

"ጌታዬ በእርግጥ አዛኝ ወዳድ ነው።" [ሁድ: 90]

③ ኑሕ እንዲህ ብለዋል:–

﴿إن ربي لغفور رحيم﴾

"ጌታ በእርግጥ መሃሪ አዛኝ ነው።" [ሁድ: 41]

④ ዩሱፍ እንዲህ ብለዋል:–

﴿إن ربي لطيف لما يشاء﴾

"ጌታዬ በእርግጥ ለሚሻው ነገር እዝነቱ ረቂቅ ነው።" [ዩሱፍ: 100]

⑤ ኢብራሂም እንዲህ ብለዋል:–

﴿إن ربي لسميع الدعاء﴾

"ጌታዬ በእርግጥ ፀሎትን ሰሚ ነው፡፡" [ኢብራሂም: 39]

⑥ ሱለይማን እንዲህ ብለዋል:–

﴿فإن ربي غني كريم﴾

"ጌታዬ በርግጥም ሃብታም ቸር ነው።" [አንነምል: 40]

ያ አላህ! ሁሌ ባንተ ከሚተማመኑት አድርገን።

[ከዐብዱለጢፍ ኣሊ ሸይኽ የትዊተር ገፅ ተወስዶ የተተረጎመ]
ለትርፍ ሳይሆን ለህዝባዊ ጉዳይ ወይም ለኸይር ስራ ታልሞ (ለምሳሌ ችግር፣ አደጋ፣ ሞት፣ ህመም ሲደርስ ለመረዳዳት፣…) በበጎ ፈቃኞች መዋጮ የሚሰበሰብ ገንዘብ ለዘካ መጠን ቢደርስም ዘካ የለበትም።
[ፈታወ ዘካ፣ ኢብኑ ባዝ: 48]
ዘካ የሚሰጠው ለምን አይነት ሰው ነው?
~~~~~~~~~~~~~~~
የዘካ ባለሐቆች 8 ናቸው። በቁርኣን እንዲህ ተዘርዝረዋል:–

(إِنَّمَا الصَّدَقَاتُ لِلْفُقَرَاءِ وَالْمَسَاكِينِ وَالْعَامِلِينَ عَلَيْهَا وَالْمُؤَلَّفَةِ قُلُوبُهُمْ وَفِي الرِّقَابِ وَالْغَارِمِينَ وَفِي سَبِيلِ اللَّهِ وَابْنِ السَّبِيلِ ۖ فَرِيضَةً مِنَ اللَّهِ ۗ وَاللَّهُ عَلِيمٌ حَكِيمٌ)

"ግዴታ ምጽዋቶች (የሚከፈሉት) ለድሆች፣ ለምስኪኖችም፣ በርሷም ላይ ለሚሰሩ ሰራተኞች፣ ልቦቻቸውም (በእስልምና) ለሚለማመዱት፣ ጫንቃዎችንም (በባርነት ተገዢዎችን) ነፃ በማውጣት፣ በባለ እዳዎችም፣ በአላህ መንገድም በሚሰሩ፣ በመንገደኛም ብቻ ነው፡፡ ከአላህ የተደነገገች ግዴታ ናት፡፡ አላህም አዋቂ ጥበበኛ ነው፡፡" [አትተውባ: 60]

መጠነኛ ማብራሪያ

① ድሃ ማለት:– ለመኖር (ልብሱ፣ ጉርሱ፣ ትዳር ለመመስረት፣ ለመማር፣) ምንም ነገር የሌለው ወይም ትንሽ ነገር ያለው ማለት ነው። እነዚህን ፍላጎቶች ለማሟላት ዘካ ሊሰጠው ይችላል።

② ምስኪን ማለት: – ለመኖር የሚሆን ነገር በተወሰነ መጠን ያለው ሲሆን የሚበቃው ግን አይደለም።

③ ዘካ ላይ የሚሰራ ሰራተኞች:– ዘካ እንዲሰበስቡ በመሪ የሚላኩ ሰዎች ናቸው። ዘካ ሶስት ነገሮችን ይፈልጋል። መሰብሰብ፣ መጠበቅና ማከፋፈል። በሶስቱም ዘርፍ ላይ የሚሰማሩ ሰራተኞች ሃብታም ቢሆኑም ዘካ ይሰጣቸዋል።
ልብ በሉ! ለዚሁ ስራ በመንግስት የሚሾሙትን እንጂ የግለሰቦች ወኪሎችን አይመለከትም። ደሞዝተኛ ሰራተኛም እዚህ ውስጥ አይገባም።

④ ልቦቻቸው (በእስልምና) የሚለማመዱ ማለት ሁለት አይነት ናቸው።

አንደኛ/ ካፊር (ሙስሊም ባይሆንም ለተሻጋሪ ፋይዳ ሲባል ነው ሊሰጠው የተፈቀደው): –
– ቢሰጠው ይሰልማል ወይም ሌላ ፋይዳ ይገኝበታል ተብሎ ተስፋ የሚጣልበት ከሆነ፣
– የሚያደርሰው ጉዳት ኖሮ በዚህ ማስቆም የሚቻል ከሆነ

ሁለተኛ/ ሙስሊም:–
– በዲኑ እንዲጠነክር ወይም ለሌላ ሰው መድከም/ መጠንከር ሰበብ ይሆናል ተብሎ ከተገመተ
– በሙስሊሞች ላይ ጉዳት የሚያደርስ ሆኖ በዚህ ማስቆም የሚቻል ከሆነ። [መጅሙዑል ፈታዋ፣ ኢብኑ ተይሚያ: 28/290]

⑤ እራሳቸውን ከአሳዳሪዎቻቸው በመግዛት ነፃ ለማውጣት የሚጣጣሩ ባሪያዎች ዘካ ከሚገባቸው ናቸው።

የተጠለፉ/ የተማረኩ ሙስሊሞችን ማስለቀቅም ከዚሁ ውስጥ ይካተታል።

⑥ ባለ እዳ:– የተጣሉ ሰዎችን ለማስታረቅ አልሞ እዳ የገባ ሰው ሃብታም እንኳን ቢሆን ዘካ ሊሰጠው ይችላል።
በራሱ ጉዳይ እዳ የተጫነው ከሆነ በቢሮው ባይቸገር እንኳ እዳውን ለመክፈል ሊሰጠው ይችላል።

⑦ በአላህ መንገድ የሚሰራ ማለት:– ለጂሃድ ዘማች ማለት ነው። ለትጥቅ፣ ለስንቅና አጠቃላይ ዝግጅት ዘካ ይሰጣል።

⑧ መንገደኛ:– አገሩ መግቢያ ከዘካ ገንዘብ ይሰጠዋል።
≈≈≈≈≈≈≈
አቡበክር ሲዲቅ በታመሙ ጊዜ ሰዎች ሊጠይቋቸው መጡ።

ሰዎቹ:– "ለምን ሃኪም አንጠራልህም?"
አቡበክር:– "ሃኪሙ አይቶኛል።"
ሰዎቹ:– "ምን አለህ ታዲያ?"
አቡበክር:– " 'እኔ የምፈልገውን ሰሪ ነኝ' አለኝ።"

[አዝዙህድ፣ ኢማሙ አሕመድ: 275] [አልሒልያ፣ አቡ ኑዐይም: 74]

@Ibnumunewor
ከቤተሰብ ርቃችሁ ለምትገኙ ተማሪዎች!
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
① ወላጆቻችሁ ዘካተል ፊጥር የማያወጡላችሁ ከሆነና
② የማውጣት አቅሙ ካላችሁ
ዘካተል ፊጥር ማውጣት እንዳትረሱ።

* ብዙዎች ስለማያስተውሉት መልእክቱን እናሰራጨው ባረከላሁ ፊኩም።
ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል: –

أيعجز أحدكم أن يقرأ في ليلة ثلث القرآن؟

"አንዳችሁ በአንድ ሌሊት የቁርኣንን ሲሶ መቅራት ያቅተዋልን?"

"እንዴት የቁርኣንን ሲሶ ይቀራል?" ሲሏቸውም

قل هو الله أحد تعدل ثلث القرآن

"ቁል ሁወልላሁ አሐድ የቁርኣንን ሲሶ ትስተካከላለች!!"

[ሙስሊም]
Forwarded from MuhammedSirage M.Noor (MuhammedSirage M.Nur G)
ድሮና ዘንድሮ
ስንቱ አለፈ! !
ከአመታት በፊት በርካታ አመታትን ባሳለፍንባቸው ሰፈሮች ውስጥ ባይተዋር ሆነን ኖረናል ። "መድኸሊዮች" የሙስሊሙ ጠላቶችና አንድነቱ ላይ የተጋረጡ እንቅፋቶች ናቸው ተብሎ በኢኽዋኖቹ ብዙ ተብሎና ተቀጥፎ ነበርና ብዙ ነገሮች ሲደርሱብን ቆይተዋል ። መስጂዶች ሶስት እና አራት ሆነን መቀመጣችንና ማውራታችን እንኳን ብቻውን እንደ ከባድ ሴራ ይቆጠር ነበር ።
በተልይ ደግሞ እነ " ኮሚቴዎች" እስር ቤት ውስጥ በነበሩ ግዜ የሙስሊሙን አንጀት መብላት ቀላል የሆነላቸው ኢኽዋኖች ጉዳዩን ብዙ አትርፈውበት ነበር ። "ኮሚቴውን የሚያከፍሩ ካድሬዎች" አሉን ። ከዚህም አልፈው " ሙናፊቆች " ብለው ፍርደ ገምድልን ብይን የበየኑብን ነበሩ ።
ለልጅ ለሽማግሌው " እነዚህ ተክፊሮች ናቸው!" በማለት ቀጠፉብን ።
መቼም ውሸት የኒህ ቀጣፊዎች ትልቅ እሴትና የማይነጠላቸው ደዌ ነውና የነሱ መዋሸት አያስደንቅም! !
የዛሬ አምስት አመት አካባቢ ይመስለኛል ። ወቅቱ የግዜው ክፉ ገዢዎች በሙስሊሙ ላይ አሰቃቂ ግፍን ሲፈፅሙበት የነበረ ነው ። ታዲያ አንድ ረመዳን ላይ ግፉ በጅጉ ድንበር እያለፈ ነበር ። በዚህ ወቅት ከወንድሞች ጋር አንድ መስጅድ ላይ ተቀምጠናል ። በእለቱ በበርካታ ወንድሞችና እህቶች ላይ ታጣቂዎች።ከበድ ግፍ መስራታቸው ሰማሁ ። በነገሩ አለቅጥ ተረበሽኩ ። የለመድኩትንና የምፈልገውን ያህል ቁርአን መቅራትም ሆነ ለጥናቴ ያዘጋጀሇቸውን ኪታቦች ማየት ተሳነኝ ። በጣሙን ተረበሽኩ ።
ከተቀመጥኩበት ተነስቼ ከመስጅዱ በር ወጣ ስል በረንዳ ላይ የተቀመጡ የኢኽዋንን መንሃጅ በማራመድ የሚታወቁ ሰዎች ተቀምጠዋል السلام عيكم
አልኳቸው ። አጉተመተሙ እንጂ አልመለሱለኝም ነበር ። ነገሩ አሰገርሞኝ ወደ ውስጥ ተመልሼ ገባሁ ። ጥቂት ከቆየሁ በሇሏ ሰላምታ መመለስን የነፈጉኝ ሰዎች እኛ ላይ እንዲህ ማለታቸውን ሰማሁ " በሙስሊሙ ላይ በሚደርሰው ድብደባ የሚደሰቱ ናቸውና ከደረሰብን ጉዳት ምንም ነገርን አትንገሯቸው ።
ቅጥፈታቸው፣ ነገራቸው ሁሉ ገረመኝ ።

በዛው ሰሞንም " ኮሚቴውን የሚያከፍሩ ተክፊሮች ብለውን አረፉ ። በእንዲህ አይነት መልኩ ሲወጉን ከረሙ ። ጥቂቶችንም በቅጥፈታቸው በመጥለፍ እኛን ጠላት አድርገው እንዲይዙ ማድረግ ችለው ነበር ። ቆይተው ግን ቅጥፈታቸው ደምቆ ታየ ፣ የቀድሞ ሰሚዎቻቸው እንኳን ጆሮ ነፈጓቸው ።
.......

ይሄ ሁሉ አለፈ! ! ብዙ ነገርን ሲጭኑብን ከነበሩት ውስጥ በርካቶች ሰለፊያን ተቀላቀሉ! አንዳንዶቹ ደግሞ ይህንን የፀዳ መንሃጅ ባይቀላቀሉም እንኳን የቀድሞ ጥላቻቸው ከስሞ ቢያንስ " ሙስሊም ወንድሞቻቸው" መሆናችንን በመቀበል በመልካም ያስተናግዱን ጀመር! ብዙ የተባልንበት መስጅድ ውስጥ ሰለፊያ ሲሰበክ ሰማን! በርካቶች ሰለፊይ ወዳጆቻችን ሆነው አነጉ! !
በርካታ ቤተሰብ የናንተን ዝቅጠት ተገነዘበና ሰለፊያን ተቀላቀለ! !!
ዛሬ ደግሞ የከፋው ውርደታችሁ ይበልጥ እየጎላ ሄደና በብዙ እይከሰራችሁ ትገኛላችሁ ።
وقل جاء الحق وزهق الباطل إن الباطل كان
زهوقا
ኢኽዋኖች ሆይ! ዛሬም አለን! በናንተ ላይ ዝምታን የመረጠ ማየታችሁ ልባችሁን አይሙላው ። እናንተን የሚያቆስል ዛሬም በብዙ ሞልቷል ።የሰበሰባችሁትም ይሁን ሰበሰብንው የምትሉት ሁሉ አያስፈራንም!
በመካከላችን ያለው ውጥረትና ጠላትነት ቀጣይ ነው— ወደሱና እስክትመለሱ ድረስ
t.me/Muhammedsirage
"የተረከብነው ባዶ ካዝና ነው። ድረሱልን" እያሉ ነው አዲሶቹ መጅሊሶች።

① የቀድሞዎቹ የዘረፉትን ቢመልሱ
② ያሁኖቹ ከመመረጣቸው ቀደም ብለው በቅርቡ በየክፍለ ሃገራቱ እየዞሩ የሰበሰቡትን ቢያስገቡ
ተደምሮ የመጅሊሱን ሰፋፊ ሽንቁሮች ይደፍን ነበር። ግን እነዚህ "የዘረፋችሁትን መልሱ" ሲሉ እነዚያ "የሰበሰባችሁትን አስገቡ" ይላሉ። "እባብ ለእባብ ይታያያል ካብ ለካብ!"
እዚህ መሐል የህዝብ ገንዘብ ተበላ። ለምን እንደሚውል አላህ ይወቅ። ተበልቶ ቢቀር እፎይታ ነበር። የባሰ አለኣ!! የሚያስፈራው ህዝብ ለሚያጠም አፍራሽ አላማ መዋሉ ነው።

ብቻ በሁለት አቅጣጫ የተሰበሰበ የህዝብ ንብረት መድረሻው ሳይታወቅ ህዝበ ሙስሊሙ ዳግም "እጅህ ከምን?" እየተባለ ነው። መጪውም ሐጅ አይደል? የመጅሊሱን ለውጥ ተከትሎ ቅናሽ እየጠበቀ ያለው ህዝብ ከወዲሁ ተስፋውን እንዲያሳሳ እየተሰራበት ሊሆን ይችላል። ምን ይታወቃል?!
የሑደይቢያ ውል ለከንቱ አላማ ሲውል
≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈≈
[ክፍል አንድ]:– በመልካም ነገር ላይ መተባበር በጥፋት ላይ ለመተባበር ሽፋን አይሆንም
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
የቢድዐ አጋፋሪዎችን ጮቤ ላስረገጠው ስምምነት ድጋፍ የሚሰጡ አካላት አካሄዳቸውን በመልካም ነገር ላይ እንደመተባበር አድርገው ሲያቀርቡ በተደጋጋሚ እያየን ነው። ይህን አካሄድ የሚነቅፉ ወንድሞችን ደግሞ "ከቢድዐ ሰዎች ጋር ፈፅሞ በመልካም ነገር ላይ መተባበር አይቻልም" እንደሚሉ አድርገው ይስሏቸዋል። የራስን ጥፋት በጥሩ መሰየም + ሌሎችን ባልዋሉበት መወንጀል= ድርርብ ጥፋት!!

የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል:–
﴿ ﻭَﺗَﻌﺎﻭَﻧﻮﺍ ﻋَﻠَﻰ ﺍﻟﺒِﺮِّ ﻭَﺍﻟﺘَّﻘﻮﻯ ﴾
"በመልካም ነገርና አላህን በመፍራት ላይ ተጋገዙ።" [አልማኢዳህ: 2]

በመልካም ነገር ላይ ማለት በቀጥታ በመልካም ነገር ላይ ነው። አለቀ።
የአሕባሽና የኢኽዋን እርቅ "መልካም ነገር" ለመሆኑ አንዳችም ማረጋገጫ የለውም። እንዲያውም ሰፊ ስጋት ነው ከፊት የተደቀነው። ጅምሩንም በተለያየ መልኩ እያየነው ነው። በዚህ ላይ በአንዳንዶች የሚጠቀሱት "ፋይዳዎች" ቀድመው አቋም ከያዙ በኋላ በባትሪ የሚፈልጓቸው ምናባዊ ስኬቶች ናቸው።

የሚደንቀው ከቢድዐ ጭፍሮች ደጅ መልከስከስን "ሚዛናዊ" ለማድረግ ሲባል ይህን የሚነቅፉ ወንድሞችን በፅንፈኝነት መሳላቸው ነው። ይህ የመጀመሪያ ውንጀላቸው አይደለም። ትላንትም ሰለፍያን ከሚያጠለሸው የነ ያሲን ኑሩ ዘመቻ ማግስት "ጉላት" /ወሰን አላፊዎች/ የሚል እሩምታ የተከፈተው ለኢኽዋኖች አልነበረም።

በነገራችን ላይ ከሙስሊም አንጃዎች ጋር "በመልካም ነገር መተባበርን" እንደምንቃወም በአንዳንዶች የሚስተጋባው ጩኸት ነጭ ውሸት ነው። እንኳን ከሙስሊም ጋር ከካፊርም ጋር በመልካም ነገር ላይ መተባበር እንደሚገባ እናምናለን። እደግመዋለሁ! እንኳን ከሙስሊሞች ጋር ከከሃዲዎች ጋርም በመልካም ነገር ላይ መተባበር እንደሚገባ እናምናለን።
ግና አንዳንዶች የነብያት ክብር በሚጎደፍበት፣ ሸሪዐ በሚጣስበት፣ …መድረክ ላይ መገኘታቸውን፣ ከቢድዐ አጫፋሪዎች ጋር እጅ ለእጅ እየተያያዙ ህብረታቸውን መግለፃቸውን፣… "በመልካም ነገር ላይ መተባበር" ብለው ሸላልመውታል። ይህን አካሄድ የሚነቅፉ ደግሞ ፅንፈኞች እየተባሉ ነው፣ ጉላት!! ይህ ነው አተያያቸው።

ከዚያስ? በኢኽዋን ላይ የዶለደመው ብእር እና የተለጎመው አንደበት ቀለሙን እየቀያየረ እንደተለመደው "ወደ ጎን" ለመውጋት አክቲቭ ሲሆን ይታያል።

* "ከስሜት ተከታዮች ጋር እጅ ለእጅ እየተያያዙ "አንድ ነን" ማለትን እና ከአሕባሽና ኢኽዋን የእርቅ ድግስ ላይ መገኘትን ከ'ወላእ ወልበራእ' ዐቂዳ ጋር ግንኙነት እንደሌለው ሊግቱን ይዳዳቸዋል።
– እጅ ለእጅ እየተያያዙ አንድ ነን ማለት ነው በመልካም ላይ መተባበር?
– የሙብተዲዖችን የእርቅ ድግስ ማድመቅ ነው በበጎ ነገር ላይ መተባበር?
– የነብያት ክብር ሲጎደፍ እርምት መስጠት የማይቻልበት መድረክ ላይ መገኘት ነው በጥሩ ነገር ላይ መተባበር?
– መቋጫው ላልታወቀውና መርዛማ ሐሳቦችን ላጨቀው እርቅ "እንኳን ደስ ያለን" ማለት ነው በመልካም ነገር ላይ መተባበር?

[ክፍል ሁለት]:– "ሀጅር" /ማኩረፍ፣ መራቅ/
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
ጭራሽ "በተሳሳቱ ሰዎች ላይ የሚተገበረውን 'ሐጅር' /ማኩረፍ/ ሙሉ በሙሉ ተፈፃሚ ለማድረግ በማሰብ እንዲህ አይነት ስህተት ላይ የሚወድቁም አሉ" ይባልልናል። እንዲህ ነው ሳይረዱ መወረፍ። ለማጠልሸት እንዲመቻቸው ያላልነውን ይለጥፉብናል። ክፉ በሽታ!
ብቻ የሚሳሳት ሰው ብዙ አይነት ነው። ትልልቅ እና ትንንሽ ወንጀሎች፣ ግልፅ ወንጀሎችና ቢድዐዎች፣ ሺርክና ኩፍር የሆኑና ያልሆኑ ወንጀሎች፣ ተሻጋሪና ራስ ላይ የተገደቡ፣… ።
ወንጀለኞችም እንዲሁ ብዙ አይነት ናቸው። ሙብተዲዕና "ፋሲቅ"፣ ወደ ጥፋቱ የሚጣራና የማይጣራ፣ ጧት ማታ ሱንናንና የሱንና ዑለማዎችን የሚያጠለሽና ፊትናው በንፅፅር የቀለለ፣ ቢድዐውን ለማሰራጨት አቅም ያለውና የሌለው፣ ወዘተ።
"በመልካም ነገር ላይ በመተባበር" ስም ከሚቀማመጧቸው ውስጥ ‘ሀጅር’ የማይገባው የትኛው ነው? "ይሻላሉ" የሚባሉት አይደሉ’ንዴ "መዳኺላ" እያሉ ሰፋፊ ዘመቻ የከፈቱት? የሱንና ዑለማዎችን ሌት ከቀን የሚያጠለሹት? በየመሳጂዱ ደርስ የሚከለክሉት? በግድያና በድብደባ የሚያስፈራሩት? በሐሰት እየከሰሱ፣ በሐሰት እየመሰከሩ የሚያሳስሩት? እነዚህን "ሀጅር" ማድረግ /መራቅ/ በምን መመዘኛ ነው እንደ ስህተት የሚቆጠረው?!

* በተረፈ " 'ሀጅር' ሰዎችን ለማረምና ለመገሰፅ ሲባል የሚፈፀም ነው" የሚለው የአንዳንዶች ሙግት ፈፅሞ ስህተት ነው። ‘ሀጅር’ የሚፈፀምባቸው ሌሎችም ምክንያቶች አሉና። በቅጡ ሳይረዱ ሌሎችን ለማሳጣት ከመቻኮል ቀድሞ በስርአት መረዳት ይቀድማል። ለማንኛውም ‘ሀጅር’ ከማረምና መገሰፅ ያለፉ ፋይዳዎች አሉት።
① ‘ሀጅር’ እራስን ለቢድዐና ለስሜቶች ለማጋለጥ ይጠብቃል፣
② ለአላህ ብሎ መውደድና ለአላህ ብሎ መጥላት /‘ወላእ ወልበራእ’/ ከኢማን ቋጠሮዎች ውስጥ ይበልጥ ጠንካራው ነው። ‘ሀጅር’ ይህ ቋጠሮ እንዳይጎዳ ይጠቅማል (ከሙብተዲዕ ጋር መቀማመጥ የለመደ ሰው በነሱ ላይ ጠንካራ አቋም አይኖረውም)፣
③ ‘ሀጅር’ ህዝብ ከሙብተዲዖች አንፃር ጥንቃቄ እንዲኖረው በማድረግ በቢድዐ ተውሳክ የመጠቃቱን እድል ይቀንሳል (በዚህ ላይ አንፀባራቂ የሆኑ በርካታ የሰለፎችን እርምጃዎች መዘርዘር ይቻላል)፣
④ ‘ሀጅር’ የሙብተዲዕን ቅስም በመስበር ቢድዐውን ለማሰራጨት ወኔ እንዳይኖረው ያሸማቅቃል። ለዚህም ፍቱን መድሃኒት እንደሆነ የሰለፎች አካሄድ ያሳያል።

★ ባጭሩ የ ‘ሀጅር’ ፋይዳዎች:–
① የሚራቀውን ወንጀለኛ፣
② ‘ሀጅር’ አድራጊውን አካል እና
③ ህዝበ ሙስሊሙን የሚመለከት ነውና ከአንድ አንግል ብቻ ማየት የራስን የአመለካከት ጥበት ነው የሚያሳየው።
እንደ ጥቅል ‘ሀጅር’ ለፋይዳ ነው የሚደረገው ቢባል ልክ ይሆናል። ዑለማዎች ስለ ‘ሀጅር’ እና ጥንቃቄዎቹ የሚናገሯቸውም በዚህ ዙሪያ የሚሽከረከሩ ናቸው። እንጂ ‘ሀጅር’ ኪታብ ላይ ብቻ የሚገኝ ወደ መሬት የማይወርድ ባዶ ሐሳብ አይደለም።

ምናባዊ ህልሞችን ለማሳካት በትንሽ በትልቁ ከቢድዐ ሰዎች ጋር መቀማመጥ ግን ከሸሪዐዊ ‘ሀጅር’ ጋር የሚጣረስ እንጂ አንዳች ስኬት የሚያመጣ አይደለም። ጭራሽ ደግሞ ስለ ‘ሀጅር’ ከአንድ ዛውያ እየተመለከቱ "የሀጅር ፅንሰ ሐሳብ አልገባችሁም" የሚሉ ሰዎች አስቂኝ ናቸው። ለነገሩ ከራስ መከላከል የወለደው አባዜ እንደሆነ ይገባናል።

[ክፍል ሶስት]:– የሑደይቢያ ውል ለከንቱ አላማ ሲውል
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
ከጥፋት ሃይሎች ጋር አላስፈላጊ መተሻሸት የሚፈጥሩ አካላት የሑደይቢያን ውል እንደ ሽፋን ሲጠቀሙ ማየት የጋራ ባህሪ ሆኗል።
በሑደይቢያ ውል ነብያችን -ﷺ- ከሙሽሪኮች ጋር ለ10 አመታት የሚቆይ ስምምነት ተፈራርመዋል። ምን አተረፉ?

① ሃይማኖታቸውን እንዲያስተምሩ፣ እንዲያስፋፉ እድል ሰጥቷል፣ ወደ ተለያዩ ሃገራት ወደ ኢስላም መልእክት ተልኳል፣
② ሌሎች ዘመቻዎችን ለማካሄድ አመቻችቷል (ለምሳሌ የሙእታህ እና የኸይበር ዘመቻዎች! ይህም ከባድ አደጋ የሚፈጥሩ ጠላቶችን ነው ያኮላሸው)፣
③ ለዋናው የመካ መከፈት መንገዱን ጠርጓል፣
④ አዲሱ ኢስላማዊ መንግስት ሌሎች ዘንድ ግርማ ሞገስ እንዲኖረውና እንዲከበር እንዲታፈር ሚና ተጫውቷል፣
⑤ በስምምነቱ መሰረት በቀጣይ አመት ዑምራ አድርገዋል።

ልብ በ
ሉ! በሑደይቢያ ስምምነት ወቅት ነብዩ -ﷺ- እንዲህ ብለው ነበር
" ﻭﺍﻟﺬﻱ ﻧﻔﺴﻲ ﺑﻴﺪﻩ، ﻻ ﻳﺴﺄﻟﻮﻧﻲ ﺧﻄﺔ ﻳﻌﻈﻤﻮﻥ ﻓﻴﻬﺎ ﺣﺮﻣﺎﺕ ﺍﻟﻠﻪ ﺇﻻ ﺃﻋﻄﻴﺘﻬﻢ ﺇﻳﺎﻫﺎ "
"ነፍሴ በእጁ በሆነችው እምላለሁ! ማንኛውንም የአላህን ድንጋጌዎች የሚያልቁበትን አንድ ጉዳይ ቢጠይቁኝ ሳላደርግላቸው አልቀርም።"

ይህ የነብዩ -ﷺ- ንግግር የአላህን ህግጋት ለመተግበር እስከሆነ ድረስ ከሙስሊም አንጃዎች ጋር ቀርቶ ከከሃድያን ጋርም መተባበር እንደሚገባ ያስገነዝባል። ኢብኑል ቀዪም እንዲህ ይላሉ:–
"(ከሑደይቢያ ውል ከሚወሰዱት ቁምነገሮች) ውስጥ፦ አጋሪዎች፣ የቢድዐ ሰዎች፣ ጋጠ-ወጦች፣ ወሰን አላፊ አማፅያንና በደለኞች ከተከበሩት የአላህ ድንጋጌዎች አንዱን ለሚያልቁበት ጉዳይ እርዳታ በጠየቁ ግዜ አዎንታዊ ምላሽ ይለገሳሉ። የጠየቁትም ይሰጣቸዋል። በዚህም ላይ እገዛ ይደረግላቸዋል። ምንም እንኳ ሌላውን ነገር ቢከለከሉም። #ክህደታቸውና_ድንበር_ማለፋቸው ላይ ሳይሆን የአላህን ህግጋት በሚያከብሩበት ላይ ይታገዛሉ። ከዚህ ውጪ ያለውን ይነፈጋሉ። አላህ ዘንድ ተወዳጅ የሆነና እርሱን የሚያስደስት ነገር ላይ እገዛን የፈለገ ማንም ይሁን ማን በዚህ ተወዳጅ ተግባር ላይ በሚደረግለት ትብብር ምክንያት ከዚህ #የከፋ_የተጠላ_ውጤት_እስካልተከተለ_ድረስ አዎንታዊ ምላሽ ይሰጠዋል። ይህ እጅግ ረቂቅ የሆነና ለነፍስ (መቀበል የሚያስቸግራት) ከባድና አስጨናቂ ርዕስ ነው።" [ዛዱል መዓድ 3/303]

ይስተዋል!

* በነዚህ ማስረጃዎች መሰረት ለተሻለ ጥቅም ሲባል መስዋዕትነት ሊከፈል እንደሚችል ነው።
* ትብብር ቢጠይቁ የሚታገዙት በመልካም እንጂ በሺርክና በቢድዐ ላይ አይደለም።
* የከፋ ውጤት በማያስከትል መልኩ እንጂ ለሺርኪያት፣ ለቢደዕና ለጥፋቶች እውቅና በሚሰጥ መልኩ አይደለም።
ታዲያ እነዚህን ማስረጃዎች ያለ አግባብ የሚመነዝሩ ሰዎች አሉ። የዛሬ 11 አመት በሱፍያና በኢኽዋን መካከል ውል ሲታሰር "እንዴት ተደርጎ…?" የሚል ተቃውሞ ሲነሳ ኢኽዋኖች ሑደይቢያን ነበር ያጣቀሱት። ትላንት "ሑደይቢያና እናንተ አራምባና ቆቦ ናችሁ" ሲል የነበረው አካል ዛሬ "ሑደይቢያ…" እያለ ነው። "የትላንቱ ውል ከዛሬ የከፋ ስለነበር ነው" እንዳይል ፈፅሞ ከእውነት የራቀ ነው። እንዲያውም የዛሬው የባሰ ነው። አቋራጩ ወይ "ትላንት ተሳስቼ ነበር" ነው። ወይ "ዛሬ ተሳስቻለሁ" ነው። ሁለቱም ግን የለም። "ትላንት ሲቃወሙን የነበሩት ዛሬ ተመልሰዋል" እየተባለ በኢኽዋን ፊታውራሪዎች መዘባበቻ መሆን ያሳቅቃል።
★ ብቻ የዛሬው ውል ከሑደይቢያ ውል በብዙ መልኩ ይለያል።
① የዛሬው ውል (አሽዐርያና ማቱሪዲያን፣ መውሊድን… በማካተት) ዐቂዳን ለድርድር ያቀረበ ነው። ሑደይቢያ ላይ እንዲህ የለም።
② የዛሬው ውል ተዋናዮች በግራም በቀኝም #በዋናነት ሁለት የጥፋት አንጃዎች ናቸው። ሑደይቢያስ ላይ?
③ የዛሬው ውል እጅግ ከባባድ ዐቂዳዊ ልዩነቶች ባልተፈቱበት "አንድነት" እየተዘመረበት ነው። ሑደይቢያ ላይ ፈፅሞ የመርህ መደባለቅ አልነበረም።
④ የዛሬው ውል ከሑደይቢያው በተለየ ሐቅን ለመጠበቅና ለማረጋገጥ ሳይሆን የተቋም ሽሚያ ላይ ያነጣጠረ ነው።
⑤ የዛሬው ውል በአንዳንዶች የሚታለሙ ስጋት ወለድ ምናባዊ ህልሞች እንጂ በቁርጥ የሚታወቁ ፋይዳዎች የሉትም። የሑደይቢያው ላይ በቀጣይ ዑምራ ሊያደርጉ፣ የአስር አመት የሰላም ውል በግልፅ የተቀመጡ ናቸው። እዚህስ ላይ? እንዲያውም አፍራሽ ነገሮች ናቸው በገሃድ የሚታዩት። "ጥሩ" የሚባሉት ነገሮች ውሉም ባይኖር የሚሰሩ ናቸው። ታዲያ የውሉ አስፈላጊነት ምኑ ላይ ነው?
⑥ የዛሬው ውል ‘ሙዳሀና’ እንጂ ‘ሙዳራ’ አይደለም። "የተጣላነው በጥቅም እንጂ ለእስልምና ብለን አልነበረም" ማለት፣ "ሁላችንም አንድ ነን" ማለት፣ የአሽዐርያ–ማቱሪዲያ፣ የመውሊድና መሰል ጉዳዮች፣… ባሉበት መስማማት በምን ስሌት ነው ‘ሙዳራ’ የሚባለው?!

* " 'ሙዳሀና' ለአንዳች ጥቅም ሲባል ሸሪዐዊ ገደቦችን በመጣስ የተከለከሉ ተግባራትን መፈፀም ወይም ከግዴታ ተግባራት መታቀብ" ነው አሉ። መልካም! ታዲያ በዚህ ውልና በሂደአጡ ላይ ስንት ሸሪዐዊ ጥሰቶች ናቸው የተፈፀሙት? ይሄኮ በገሃድ የሚታይ ሐቅ ነው።

* ኢብን ሐጀር -ረሒመሁላህ-
– "ዑለማዎች ‘ሙዳሀናን’ የሚተረጉሙት ፋሲቅ ከሆነ ሰው ጋር ምንም እንዳላጠፋ ሁሉ እርሱን መወዳጀትና የሚሰራው ስራ ትክክል እንደሆነ እውቅና እየሰጡ ከመጥፎ ከመከልከል መቆጠብ ነው" ሲሉት፤
– "ሙዳራት ግን በለስላሳ አገላለፅ የማያውቅን ሰው ማስተማር ፋሲቅን በተለይ ሐቅን አውቆ እንዲመለስ ማላመድ የሚያስፈልግ እስከሆነ በጥሩ ቃል ከጥፋቱ እንዲቆጠብ መምከር ነው" ብለዋል።

ይህን የዛሬውን ውል በዚህ የኢብኑ ሐጀር ንግግር የመዘነ ሰው ‘ሙዳራ’ ሳይሆን ‘ሙዳሀና’ እንደነገሰበት በቀላሉ ያገኘዋል።

* ኢማም ኢብኑል ቀዪምም የሁለቱን ልዩነት እንዲህ ሲሉ ገልፀውታል:–
– " 'ሙዳራ' የሚፈፅም ሰው ምሳሌው ልክ አንድ ህመምተኛን የሚያክም ሐኪም በሽተኛው ሳይሰቃይበት በሽታውን አግኝቶ ከስሩ የሚነቅል ህክምና እንደሚያደርግለት ነው።
– የ'ሙዳሀና' ምሳሌው ግን ሐኪም ሁኖ ለህመምተኛው ህክምና እንደማድረግ 'አይዞህ ቀላል ነው' እያለ በሽታውን አቃልሎ በማዘናጋት በሰውነቱ እንዲሰራጭ የሚያደርግ አይነት ነው።"
[አርሩሕ: 231]

ታዲያ የአሁኑ ውል በየትኛው ምድብ ላይ ነው የሚያርፈው?! ሰው መረጃ የሚሆንበትን ነገር እንዴት ያለ አግባብ ይጠቀማል?! በዚህ ውል እኮ ሁለት በሽተኞች "ጥቅም / መንግስት አጣልቶን እንጂ አንድ ነን" በማለት ዐቂዳዊ ልዩነቶችን ያንሳፈፉበት እርቅ ነው። ሶስተኛው ወገን በዚህ የተደበላለቀ አካሄድ ላይ አጃቢ ከመሆን ያለፈ ሚና የለውም! በፅሁፍም ሆነ በቃል ለመምከርማ ከውጭ ሆኖም ማድረግ ይቻላል። ምናልባት "ቀረብ ካላልን ሐሳባችንን በቀናነት አያዩትም" ከተባለ:–
① ስለቀረባችሁ ምን የተለየ ነገር ተገኘ? የትኛው የሰነዱ አንቀፅ ተለወጠ?
② ደግሞስ አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ለውይይትና ለምክክር ከመገናኘት ባለፈ እጅ ለእጅ እያጣመሩ አንድነትን ማሳየቱን፣ ከመጥፎ ነገር ለመከልከል እድል በጠበበበት ጉባኤ ላይ መገኘቱን፣ "እንኳን ደስ ያለን" ማለቱን፣ "በእንኳን ደስ ያላችሁ" ድግሳቸው ላይ መገኘቱን ምን አመጣው? አስገዳጅ ችግር ያልተፈቀደን ነገር ቢያስፈቅድም (ያውም ዶሩራው ከኖረ) የሚፈቀደው በልክ አይደለም እንዴ?!
* ቢያንስ በተገኘንበት ጉባኤ ላይ "ሙሳም ቢመጡ፣ ዒሳም ቢመጡ፣…" ተብሎ የነብያትን ክብር የሚያጎድፍ ዘግናኝ ጥፋት ሲፈፀም ጩኸንም ቢሆን እንደምንም ተሟሙተን በቦታው ማረም አልነበረብንም?
* እሱ ካልሆነ ቢያንስ ጥሎ መውጣት አይገባም? አላህ እንዲህ አላለም እንዴ?!
(وَقَدْ نَزَّلَ عَلَيْكُمْ فِي الْكِتَابِ أَنْ إِذَا سَمِعْتُمْ آيَاتِ اللَّهِ يُكْفَرُ بِهَا وَيُسْتَهْزَأُ بِهَا فَلَا تَقْعُدُوا مَعَهُمْ حَتَّىٰ يَخُوضُوا فِي حَدِيثٍ غَيْرِهِ ۚ إِنَّكُمْ إِذًا مِثْلُهُمْ)

"በእናንተም ላይ በመጽሐፉ ውስጥ የአላህን አንቀጾች በርሷ ሲካድባትና በርሷም ሲላገጥባት በሰማችሁ ጊዜ በሌላ ወሬ ውስጥ እስከሚገቡ ድረስ ከእነሱ ጋር አትቀመጡ ማለትን በእርግጥ አወረደ፡፡ እናንተ ያንጊዜ ብጤያቸው ናችሁና፡፡"
[አንኒሳእ: 140]

* ይህም ይቅር! ከወጡስ በኋላ ለእንዲህ አይነቱ በህዝብ ፊት ለተፈፀመ ዘግናኝ ጥፋት ግልፅ ምላሽ መስጠት አይ
ገባም?! ነብዩ ﷺ እንዲህ አላሉም?
" مَنْ رَأَى مِنْكُمْ مُنْكَرًا فَلْيُغَيِّرْهُ بِيَدِهِ، فَإِنْ لَمْ يَسْتَطِعْ فَبِلِسَانِهِ، فَإِنْ لَمْ يَسْتَطِعْ فَبِقَلْبِهِ، وَذَلِكَ أَضْعَفُ الْإِيمَانِ ".

"ከናንተ መጥፎን ነገር ያየ በእጁ ይቀይረው። ካልቻለ በምላሱ፤ ካልቻለ ደግሞ በልቡ። ይሄኛው የመጨረሻ ደካማው እምነት ነው።" [ሙስሊም]

በተረፈ በየጊዜው የማያባራውን የአህሉል ቢደዕ ዘመቻ እንዳላዩ እያለፉ ቦታና ጊዜ ሳይለዩ ላገኙት ሁሉ ዘወትር ስለ ሪፍቅ፣ ሒክማ፣ ሚዛናዊነት ማቀንቀን ሚዛናዊነት ሳይሆን ከግትር ፅንፈኝነት ማዶ ያለ እንዝህላል ፅንፈኝነት ነው።
ፅሁፌን የምቋጨው በሸይኽ ሱለይማን አርሩሐይሊ ንግግር ነው።

* ጠያቂ:– "የደዕዋው መንገድ ስለተጠበበብን አላህ እስከሚያብቃቃን ድረስ ከአንድ የኢኽዋን ማህበር ለደዕዋ አላማ የሚሆን ቅርንጫፍ ሆነን ፈቃድ ወስደናል…
* ሸይኽ ሱለይማን: – (አላስጨረሱትም) "ወላሂ እየውልህ ወንድሜ! ኢኽዋን ማለት ልክ እንደ እከክ ናቸው። ከነሱ አርቁ ። ወደነሱ አትቅረቡ።
ታያለህ? ወደ ኢኽዋን ህብረት ከምትጠጉ አንድ አንድ ሰው ብትጣሩ ለናንተ የተሻለ ነው። (በመጠጋታችሁ) ደዕዋ ቢኖራችሁ እንኳ!!
ወንድሜ ሆይ! ኢኽዋንዮች ሊደርሱበት የሚያስቡት ጥቅም ኖሯቸው ካልሆነ በስተቀር ሰለፊይ የሆነን ሰው ለደዕዋ አያመቻቹለትም። ከሚያልሙት ጥቅም ሁሉ እጅግ ቅርብ የሆነው የሰለፍዮችን ህብረት መሰንጠቅ ነው፤ በወንድሞች መካከል የቃላት መወራወር እንዲኖር!"
ሱብሓነላህ! አስተዋዮች አስተውሉ!!! ሸይኹ ይቀጥላሉ:–

"ወደ ኢኽዋን አንጃ መጠጋት አይፈቀድም። ከኢኽዋነል ሙስሊሚን ጋርም ወደነሱ በሚጠጋ ነገር ላይ መስራት አይፈቀድም።

እናም ወንድሞቼ ሆይ! አደራዬ: እኛ በማንቆጣጠረው ነገር ላይ እንድንሰማራ የምንገደድ አይደለንም። ወላህ! የደዕዋው መንገድ ከተጠበበብንና መንገድ ካጣን ደዕዋ እንድናደርግ ብለን ሐራም ነገር አንፈፅምም!! በጭራሽ! ‘ላ ሐውለ ወላ ቁውወተ ኢላ ቢልላህ’ / ብልሃትም ሃይልም በአላህ እንጂ የለም/ ብለን በምንችለው በዙሪያችን ያሉትን እንጣራለን። ማለፊያ! አላህን – ዐዘ ወጀል – የፈራ ሰው መልካምን እንጂ አያገኝም።"
https://youtu.be/udMx8Af6acQ

*ሰላም!*
(ኢብኑ ሙነወር፣ ግንቦት 23/2011)
ሸይኽ ሱለይማን አርሩሐይሊ "ከኢኽዋን ራቁ" ይሉናል።

* ጠያቂ:– "የደዕዋው መንገድ ስለተጠበበብን አላህ እስከሚያብቃቃን ድረስ ከአንድ የኢኽዋን ማህበር ለደዕዋ አላማ የሚሆን ቅርንጫፍ ሆነን ፈቃድ ወስደናል…

* ሸይኽ ሱለይማን: – (አላስጨረሱትም) "ወላሂ እየውልህ ወንድሜ! ኢኽዋን ማለት ልክ እንደ እከክ ናቸው። ከነሱ አርቁ ። ወደነሱ አትቅረቡ።

ታያለህ? ወደ ኢኽዋን ህብረት ከምትጠጉ አንድ አንድ ሰው ብትጣሩ ለናንተ የተሻለ ነው። (በመጠጋታችሁ) ደዕዋ ቢኖራችሁ እንኳ!!

ወንድሜ ሆይ! ኢኽዋንዮች ሊደርሱበት የሚያስቡት ጥቅም ኖሯቸው ካልሆነ በስተቀር ሰለፊይ የሆነን ሰው ለደዕዋ አያመቻቹለትም። ከሚያልሙት ጥቅም ሁሉ እጅግ ቅርብ የሆነው የሰለፍዮችን ህብረት መሰንጠቅ ነው፤ በወንድሞች መካከል የቃላት መወራወር እንዲኖር

"ወደ ኢኽዋን አንጃ መጠጋት አይፈቀድም። ከኢኽዋነል ሙስሊሚን ጋርም ወደነሱ በሚጠጋ ነገር ላይ መስራት አይፈቀድም።

እናም ወንድሞቼ ሆይ! አደራዬ: እኛ በማንቆጣጠረው ነገር ላይ እንድንሰማራ የምንገደድ አይደለንም (አላህ አንዲትን ነፍስ ከአቅሟ በላይ አላስገደዳትም)። ወላህ! የደዕዋው መንገድ ከተጠበበብንና መንገድ ካጣን ደዕዋ እንድናደርግ ብለን ሐራም ነገር አንፈፅምም!! በጭራሽ! ‘ላ ሐውለ ወላ ቁውወተ ኢላ ቢልላህ’ / ብልሃትም ሃይልም በአላህ እንጂ የለም/ ብለን በምንችለው በዙሪያችን ያሉት መልካም! አላህን – ዐዘ ወጀል – የፈራ ሰው መልካምን እንጂ አያገኝም።"
https://youtu.be/udMx8Af6acQ