እውነት ኢትዮጵያ የአህለ ሱና ሀገር ናትን?
★★★★★★★★★★★★
ኢትዮጵያ ሀገራችን የአህለ ሱና ሀገር ብትሆን ምንኛ ደስ ባለን ነበር። ነገር ግን ሺርክ፣ ቢድአ፣ መሀይምነት፣ ዘረኝነት፣ አመፀኝነት በሰፊው የተንሰራፋባት ሀገር ናት።
የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ባልደረባዎቻቸውን ወደ ሀበሻ ሁለት ጊዜ ስደት እንዲሄዱ ነበር ያዘዙት።
ተውሒድን ከማንም በላይ ይፋ ማድረግና ከሺርክ መራቅ ሲገባን፣ አላህ ካዘነላቸው ጥቂቶች ውጭ አብዛኛው ሺርክ እና ቢድአ በማጨማለቅ ላይ ነው።
"ሀገራችን የአህለ ሱና ሀገር ነው። ሁሉም አህለ ሱና ነው።" ብለው የሚዋሹ ሰዎች ስላሉ፣ ሀገራችን የአህለሱና ሀገር እንዳልሆነችና ሁሉም አህለ ሱና እንዳልሆነ በተጨባጭ ማስረጃ እንደሚከተለው አቀርበዋለሁ
ሺርክ ማለት ለብቸኛው ፈጣሪ አላህ የሚገባውን አምልኮ ለፍጡራን (መላኢካ፣ ነብይ፣ ጂን፣ ሷሊህ፣ ወልይ፣ ዛፍ፣ ዲንጋይ …) መስጠት ነው።
እውነት ሀገራችን የአህለ ሱና ሀገር ናት ወይንስ ሺርክ እና ቢድአ የተንሰራፋባት የሚለውን ለማየት የሚከተሉት ሀገራችን ላይ በየአቅጣጫው በሰፊው የሚሰሩ በአድ አምልኮዎችና፣ ኢስላም ላይ የተጨመሩ ቢድአዎች በከፊሉ እዘረዝራለሁ
1) በጎንደር "ጌታው ሸህ አሊ ግንደር፣ ሸህ አብድል ባሲጥ፣ ሸህ አባድር፣ ፈቂህ አሊ ሙዝ …" እየተባለ ለነዚህ ከአላህ ውጭ ላሉ ፍጡሮች ለአላህ ብቻ የሚገባው አምልኮ ይሰጣቸዋል፣
2) አሁንም በጎንደር "የእሽት ዶሮ" እየተባለ ዶሮ ለእርኩስ መንፈስ ይሰጣል፣
3) ጎጃም አዴት የሚባል ቦታ ለሞተ ውሻ እላዩ ላይ ቀብር ተሰርቶለት ይመለካል፣
4) ወሎ ደግዬ፣ ዳና ፣ እና እና ሌሎች ቦታዎችም ላይ ባአድ አምልኮ ይፈፀማል፣
5) አንበሶ፣ አዳል ሞቴ፣ ራሂሎ እና የመሳሰሉትን እየተባለ ለጂኖች "ሙወከል" እየተባለ ለሰይጣን ዶሮ ይታረድለታል፣
6) አዲስ አበባ የድሮ እስላም መቃብር የሸህ ሀሰን በቱል ቀብር ይመለካል፣ "ዱአ አድራጊ ናቸው" በሚል ስም ብዙ ጠንቋዮች ይመለካሉ፣
7) ጉራጊ አብሬት፣ ቃጥባሬ ከአላህ ውጭ ይመለካሉ፣
8) ስልጤ አልከሶ፣ ኑርሁሴን ከአላህ ውጭ ይመለካሉ፣
9) ካእባ ላይ ብቻ መደረግ ያለበትን ጠዋፍ ኦሮሚያ ባሌ ኑር ሁሴን ቀብር ላይ ጠዋፍ ይደረጋል፣
10) "የሸህ ሁሴን ትንቢት" እየተባለ በጥንቆላ ይታመናል፣
11) ምስራቅ ኢትዮጵያ ለጅብ ገንፎ በማገንፋት ባእድ አምልኮ ይፈፅማሉ፣
12) አላህ ያላዘዘው፣ ነብዩ ያልሰሩት ያላዘዙት "መውሊድ (የነብዩ ልደት)" ብለው በክህደት ስንኞች፣ በመጨፈር፣ በማፏጨት፣ ጫት በመቃም፣ ሴት እና ወንድ በመቀላቀል ያሳልፉታል፣
13) የአላህን ስም እና መገለጫዎች የሚያጣሙ ብሎም የማይቀበሉ አህባሽን ይመስል የጥመት ቡድኖች አሉ፣
14) ሀገራችን ላይ የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ባልደረባዎች የሚሰደቡበት ኪታብ ይሸጣል፣ ለዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ይከፋፈላል፣
15) አዲስ አበባ እና ሌሎች ከተማዎችም ላይ ሀሙስ ማታ ከመግሪብ እስከ ኢሻ ብለው በሰለዋት ስም ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ይመጣሉ ብለው ከተቀመጡበት "መርሃባ ነቢ" ብለው ይነሱላቸዋል፣
አረ ስንቱ……
ታድያ ይህችን ሀገራችንን ነው "ሀገራችን የአህለ ሱና ሀገር ነው። ሁሉም አህለ ሱና ነው።" እየተባለ የውሸት ምስክርነት የሚሰጣት?
አላህ ለምን አይፈራም።
የአላህ ባሪያዎች ሆይ! በአላህ ስም ምዮ የምናገረው ተውሒድን እና ሱናን የተፃረረ ብሎም ሺርክ እና ቢድአን የሚያጨማልቅ አህለ ሱና አይባልም።
አህለ ሱናዎች ማለት ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እና ሰሃባዎቻቸው የነበሩባትን መንገድ የሚከተሉ ናቸው።
ነብዩ እና ሰሀባዎቻቸው ደግሞ ከላይ ከተጠቀሱት እርጉም እና እርኩስ የጥፋት መንገዶች የራቁ ናቸው።
የአህለ ሱናዎችን መንገድ የተቃረኑ ሰዎች የጮሁትን ያህል ቢጮሁ፣ የዋሹትን ያህል ቢዋሹ አላህ አያሳካላቸውም።
ይሀው ሀገራችን ላይ በትክክለኛው እምነት መሰባሰብ አቅቷቸው አላህ ውርደት ያቀመሳቸውን የጥፋት ቡድኖች እና ግለሰቦች እያየን ነው።
አላህ ባዘዘው መንገድ ያልተሰባሰቡ ተበታተኑ እንጂ አንድ ሆኑ አይባልም።
መፍትሄው የውሸት መስካሪዎችን፣ አውቆ አጥፊዎችን በጭፍን መከተል ሳይሆን ቁርአን እና ሀዲስ በሰሀባዎች መንገድ መረዳት ነው።
ሙስሊም ወንድም እና እህቶቼ ሆይ! አላህ ከፊትና ይጠብቀን። ከሁሉም የጥመት ቡድኖች ይጠብቀን። ብቸኛዋን የሐቅ ጎዳና ይምራን።
https://t.me/SadatTextPosts
★★★★★★★★★★★★
ኢትዮጵያ ሀገራችን የአህለ ሱና ሀገር ብትሆን ምንኛ ደስ ባለን ነበር። ነገር ግን ሺርክ፣ ቢድአ፣ መሀይምነት፣ ዘረኝነት፣ አመፀኝነት በሰፊው የተንሰራፋባት ሀገር ናት።
የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ባልደረባዎቻቸውን ወደ ሀበሻ ሁለት ጊዜ ስደት እንዲሄዱ ነበር ያዘዙት።
ተውሒድን ከማንም በላይ ይፋ ማድረግና ከሺርክ መራቅ ሲገባን፣ አላህ ካዘነላቸው ጥቂቶች ውጭ አብዛኛው ሺርክ እና ቢድአ በማጨማለቅ ላይ ነው።
"ሀገራችን የአህለ ሱና ሀገር ነው። ሁሉም አህለ ሱና ነው።" ብለው የሚዋሹ ሰዎች ስላሉ፣ ሀገራችን የአህለሱና ሀገር እንዳልሆነችና ሁሉም አህለ ሱና እንዳልሆነ በተጨባጭ ማስረጃ እንደሚከተለው አቀርበዋለሁ
ሺርክ ማለት ለብቸኛው ፈጣሪ አላህ የሚገባውን አምልኮ ለፍጡራን (መላኢካ፣ ነብይ፣ ጂን፣ ሷሊህ፣ ወልይ፣ ዛፍ፣ ዲንጋይ …) መስጠት ነው።
እውነት ሀገራችን የአህለ ሱና ሀገር ናት ወይንስ ሺርክ እና ቢድአ የተንሰራፋባት የሚለውን ለማየት የሚከተሉት ሀገራችን ላይ በየአቅጣጫው በሰፊው የሚሰሩ በአድ አምልኮዎችና፣ ኢስላም ላይ የተጨመሩ ቢድአዎች በከፊሉ እዘረዝራለሁ
1) በጎንደር "ጌታው ሸህ አሊ ግንደር፣ ሸህ አብድል ባሲጥ፣ ሸህ አባድር፣ ፈቂህ አሊ ሙዝ …" እየተባለ ለነዚህ ከአላህ ውጭ ላሉ ፍጡሮች ለአላህ ብቻ የሚገባው አምልኮ ይሰጣቸዋል፣
2) አሁንም በጎንደር "የእሽት ዶሮ" እየተባለ ዶሮ ለእርኩስ መንፈስ ይሰጣል፣
3) ጎጃም አዴት የሚባል ቦታ ለሞተ ውሻ እላዩ ላይ ቀብር ተሰርቶለት ይመለካል፣
4) ወሎ ደግዬ፣ ዳና ፣ እና እና ሌሎች ቦታዎችም ላይ ባአድ አምልኮ ይፈፀማል፣
5) አንበሶ፣ አዳል ሞቴ፣ ራሂሎ እና የመሳሰሉትን እየተባለ ለጂኖች "ሙወከል" እየተባለ ለሰይጣን ዶሮ ይታረድለታል፣
6) አዲስ አበባ የድሮ እስላም መቃብር የሸህ ሀሰን በቱል ቀብር ይመለካል፣ "ዱአ አድራጊ ናቸው" በሚል ስም ብዙ ጠንቋዮች ይመለካሉ፣
7) ጉራጊ አብሬት፣ ቃጥባሬ ከአላህ ውጭ ይመለካሉ፣
8) ስልጤ አልከሶ፣ ኑርሁሴን ከአላህ ውጭ ይመለካሉ፣
9) ካእባ ላይ ብቻ መደረግ ያለበትን ጠዋፍ ኦሮሚያ ባሌ ኑር ሁሴን ቀብር ላይ ጠዋፍ ይደረጋል፣
10) "የሸህ ሁሴን ትንቢት" እየተባለ በጥንቆላ ይታመናል፣
11) ምስራቅ ኢትዮጵያ ለጅብ ገንፎ በማገንፋት ባእድ አምልኮ ይፈፅማሉ፣
12) አላህ ያላዘዘው፣ ነብዩ ያልሰሩት ያላዘዙት "መውሊድ (የነብዩ ልደት)" ብለው በክህደት ስንኞች፣ በመጨፈር፣ በማፏጨት፣ ጫት በመቃም፣ ሴት እና ወንድ በመቀላቀል ያሳልፉታል፣
13) የአላህን ስም እና መገለጫዎች የሚያጣሙ ብሎም የማይቀበሉ አህባሽን ይመስል የጥመት ቡድኖች አሉ፣
14) ሀገራችን ላይ የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ባልደረባዎች የሚሰደቡበት ኪታብ ይሸጣል፣ ለዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ይከፋፈላል፣
15) አዲስ አበባ እና ሌሎች ከተማዎችም ላይ ሀሙስ ማታ ከመግሪብ እስከ ኢሻ ብለው በሰለዋት ስም ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ይመጣሉ ብለው ከተቀመጡበት "መርሃባ ነቢ" ብለው ይነሱላቸዋል፣
አረ ስንቱ……
ታድያ ይህችን ሀገራችንን ነው "ሀገራችን የአህለ ሱና ሀገር ነው። ሁሉም አህለ ሱና ነው።" እየተባለ የውሸት ምስክርነት የሚሰጣት?
አላህ ለምን አይፈራም።
የአላህ ባሪያዎች ሆይ! በአላህ ስም ምዮ የምናገረው ተውሒድን እና ሱናን የተፃረረ ብሎም ሺርክ እና ቢድአን የሚያጨማልቅ አህለ ሱና አይባልም።
አህለ ሱናዎች ማለት ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እና ሰሃባዎቻቸው የነበሩባትን መንገድ የሚከተሉ ናቸው።
ነብዩ እና ሰሀባዎቻቸው ደግሞ ከላይ ከተጠቀሱት እርጉም እና እርኩስ የጥፋት መንገዶች የራቁ ናቸው።
የአህለ ሱናዎችን መንገድ የተቃረኑ ሰዎች የጮሁትን ያህል ቢጮሁ፣ የዋሹትን ያህል ቢዋሹ አላህ አያሳካላቸውም።
ይሀው ሀገራችን ላይ በትክክለኛው እምነት መሰባሰብ አቅቷቸው አላህ ውርደት ያቀመሳቸውን የጥፋት ቡድኖች እና ግለሰቦች እያየን ነው።
አላህ ባዘዘው መንገድ ያልተሰባሰቡ ተበታተኑ እንጂ አንድ ሆኑ አይባልም።
መፍትሄው የውሸት መስካሪዎችን፣ አውቆ አጥፊዎችን በጭፍን መከተል ሳይሆን ቁርአን እና ሀዲስ በሰሀባዎች መንገድ መረዳት ነው።
ሙስሊም ወንድም እና እህቶቼ ሆይ! አላህ ከፊትና ይጠብቀን። ከሁሉም የጥመት ቡድኖች ይጠብቀን። ብቸኛዋን የሐቅ ጎዳና ይምራን።
https://t.me/SadatTextPosts
አቂዳ አንድ ያላደረጋቸውን የበሬ አጥንት አንድ አያደርጋቸውም፡፡
★★★★★★★★★★★★
በአቂዳ ተለያይተው አንድነት እና ሰደቃ እያሉ በሬ አርደው በመብላት አንድ እንሆናለን ብለው ያሰቡትን ሰዎች መጨረሻ ተመለከታችሁን?
በኒ መስጂድ እና አየር ጤና ላይ ጥግ ጥጋቸውን ይዘው መደስኮራቸውን ይዘዋል፡፡
አቂዳ አንድ ያላደረጋቸውን በሬ አርዶ መብላት እና አብሮ ፎቶ መነሳት አንድ አያደርጋቸውም፡፡
በጥመት ላይ የተሰባሰቡ ሰዎች መጨረሻቸው ይህ ነው፡፡ አብዛኛውን ምስኪን ቢሸውዱትም አላህ ሁሉን ተመልካች ነውና አያሳካላቸውም፡፡ በኪታብ እና በሱና አንድ መሆን አቅቷቸው፣ በል እንዲያውም ወደ ተውሒድ እና ሱና የሚጣሩ ወንድሞችን “የኡማው ጠላቶች” እያሉ ከሺርክ እና ቢድኣ ሰዎች ጋር አብረው ሄደው ሲዶልቱ እና ሲተሻሹ የነበሩ ሰዎች ይሀው ውርደታቸውን ቀመሱ፡፡ ከተቋም በፊት በእምነት አንድ መሆን ይጠበቃል፡፡አላህም በእምነት ገመድ አንድ ሁሉ ሲል ነው ያዘዘው፡፡ ሱናን መፃረር ለውርደት ይዳርጋል፡፡ ሙስሊሞች ሆይ! በኪታብ እና በሱና አላህ አንድ ያድርገን፡፡ አሽአሪ፣ ማትሩዲ፣ አህባሽ፣ ሱፊ፣ ኢኽዋን….. ከሚባሉ የጥመት ቡድኖች ሁሉ አላህ ይጠብቀን፡፡ ብቸኛዋን የጥንት የጠዋቷን ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እና ሰሃባዎቻቸው የነበሩባትን የሰለፉነ ሷሊሂን መንገድ ይምራን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
★★★★★★★★★★★★
በአቂዳ ተለያይተው አንድነት እና ሰደቃ እያሉ በሬ አርደው በመብላት አንድ እንሆናለን ብለው ያሰቡትን ሰዎች መጨረሻ ተመለከታችሁን?
በኒ መስጂድ እና አየር ጤና ላይ ጥግ ጥጋቸውን ይዘው መደስኮራቸውን ይዘዋል፡፡
አቂዳ አንድ ያላደረጋቸውን በሬ አርዶ መብላት እና አብሮ ፎቶ መነሳት አንድ አያደርጋቸውም፡፡
በጥመት ላይ የተሰባሰቡ ሰዎች መጨረሻቸው ይህ ነው፡፡ አብዛኛውን ምስኪን ቢሸውዱትም አላህ ሁሉን ተመልካች ነውና አያሳካላቸውም፡፡ በኪታብ እና በሱና አንድ መሆን አቅቷቸው፣ በል እንዲያውም ወደ ተውሒድ እና ሱና የሚጣሩ ወንድሞችን “የኡማው ጠላቶች” እያሉ ከሺርክ እና ቢድኣ ሰዎች ጋር አብረው ሄደው ሲዶልቱ እና ሲተሻሹ የነበሩ ሰዎች ይሀው ውርደታቸውን ቀመሱ፡፡ ከተቋም በፊት በእምነት አንድ መሆን ይጠበቃል፡፡አላህም በእምነት ገመድ አንድ ሁሉ ሲል ነው ያዘዘው፡፡ ሱናን መፃረር ለውርደት ይዳርጋል፡፡ ሙስሊሞች ሆይ! በኪታብ እና በሱና አላህ አንድ ያድርገን፡፡ አሽአሪ፣ ማትሩዲ፣ አህባሽ፣ ሱፊ፣ ኢኽዋን….. ከሚባሉ የጥመት ቡድኖች ሁሉ አላህ ይጠብቀን፡፡ ብቸኛዋን የጥንት የጠዋቷን ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እና ሰሃባዎቻቸው የነበሩባትን የሰለፉነ ሷሊሂን መንገድ ይምራን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
ኢኽዋንንም ይሁን ሌሎች የቢድኣ ቡድኖችን ማጋለጥ ለሙስሊሞች ከማዘን እና ከማሰብ ነው፡፡
★★★★★★★★★★★★
ከሺርክ እና ከባለቤቶቹ፣ ከቢድ እና ከባለቤቶች ማስጠንቀቅ ለሙስሊሞች ከማዘን እና ለእነሱ ከመቆርቆር ነው፡፡
ለሙስሊሞች ማዘን ማለት እንደ ኢኽዋን፣ ኸዋሪጅ፣ እና ሌሎችም ሙስሊሞችን ለችግር የሚዳርጉ ቡድኖችን እና ሚድያዎቻቸውን ማጋለጥ ነው፡፡ ሙስሊሞችን ለተለያዩ ችግሮች የዳረጉት ኢኽዋኖች ናቸው፡፡ ይህንን ደግሞ አይደለም ኢልም አለኝ የሚል ሰው እራሳቸው ኢኽዋኖች ክስረት እንዳመጡ እራሳቸው ላይ እየመሰከሩ ነው፡፡ለምሳሌ አረብ ሀገራት (ቱኒስያ፣ ግብፅ፣ ሶሪያ፣ የመን፣ ሊብያ….) ሀገራችንም ላይ ተገለባባጭ እና ተለዋዋጭ የሆኑት ኢኽዋኖች ለፖለቲካ ጥቅማቸው ሲሉ በኢስላም ስም ሙስሊሞችን መከራ ላይ የዳረጉት፡፡
ሙስሊሙ በድጋሚ በነዚህ ሰዎች እንዳይሸወድ፣ እዚህ ከባድ መከራ ውስጥ ሙስሊሙን የከተቱት ኢኽዋኖች ናቸው ማለት ለሙስሊሙ አለማዘን አይደለም፡፡ እንዲያውም ከዚህ አደገኛ ቡድንም ይሁን ከሌሎች ቡድኖች ኡማውን ማስጠንቀቅ ለኡማው በጣም ከማዘን እና ከመጨነቅ ነው፡፡
በተገላቢጦሹ አንዳንድ የእውቀት ባለቤት ነን እያሉ ኡማው በነዚህ ተኩላዎች ሲሸወደ እያዩ ዝምታን የመረጡ ሰዎች አላህን አይፈሩትምን
አላህ እንዲህ ይላል
وَإِذْ أَخَذَ ٱللَّهُ مِيثَٰقَ ٱلَّذِينَ أُوتُوا۟ ٱلْكِتَٰبَ لَتُبَيِّنُنَّهُۥ لِلنَّاسِ وَلَا تَكْتُمُونَهُۥ فَنَبَذُوهُ وَرَآءَ ظُهُورِهِمْ وَٱشْتَرَوْا۟ بِهِۦ ثَمَنًا قَلِيلًا ۖ فَبِئْسَ مَا يَشْتَرُونَ
አላህ የነዚያን መጽሐፉን የተሰጡትን ቃል ኪዳን ለሰዎች በእርግጥ ታብራሩታላችሁ አትደብቁትምም በማለት የያዘባቸውን (አስታውሱ)፡፡ በጀርባዎቻቸውም ኋላ ጣሉት፡፡ በርሱም ጥቂትን ዋጋ ገዙ፡፡ የሚገዙትም ነገር ከፋ!
ይህ አንቀፅ አላህ እውቀት ሰጥቷቸው በእውቀታቸው የማይሰሩትን፣ እውነቱን ለሰዎች የማያብራሩትን እና የሚደብቁትን የሚወቅስበት ነው፡፡ እነዚህ ግለሰቦች ለቀላቢያቸው አልታመን ብለዋል፡፡ ሐቁን ደብቀዋል፡፡ ብሎም ለባጢል ጥብቅና ቆመዋል፡፡
ኢኽዋን የከሰረ የጥመት ቡድን ነው፡፡ ኢኽዋን ከእለት እለት ኪሳራው በግልፅ በወጣ ቁጥር ኢኽዋንን አናስነካም ብለው፣ ለኢኽዋን ጥብቅና የቆሙ፣ ማስረጃን ሲጠመዝዙ የነበሩ በጠቅላላ ከኢኽዋን በላይ የከሰሩ መሆናቸውን እያየን ነው፡፡
አላህ በሐቅ ላይ ይሰብስበን፡፡ ሐቅን በሐቅነቱ ያሳያን የምንቀበለውም ያድርገን፡፡ ባጢልን በባጢልነቱ ያሳየን የምንርቀውም ያድርገን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
★★★★★★★★★★★★
ከሺርክ እና ከባለቤቶቹ፣ ከቢድ እና ከባለቤቶች ማስጠንቀቅ ለሙስሊሞች ከማዘን እና ለእነሱ ከመቆርቆር ነው፡፡
ለሙስሊሞች ማዘን ማለት እንደ ኢኽዋን፣ ኸዋሪጅ፣ እና ሌሎችም ሙስሊሞችን ለችግር የሚዳርጉ ቡድኖችን እና ሚድያዎቻቸውን ማጋለጥ ነው፡፡ ሙስሊሞችን ለተለያዩ ችግሮች የዳረጉት ኢኽዋኖች ናቸው፡፡ ይህንን ደግሞ አይደለም ኢልም አለኝ የሚል ሰው እራሳቸው ኢኽዋኖች ክስረት እንዳመጡ እራሳቸው ላይ እየመሰከሩ ነው፡፡ለምሳሌ አረብ ሀገራት (ቱኒስያ፣ ግብፅ፣ ሶሪያ፣ የመን፣ ሊብያ….) ሀገራችንም ላይ ተገለባባጭ እና ተለዋዋጭ የሆኑት ኢኽዋኖች ለፖለቲካ ጥቅማቸው ሲሉ በኢስላም ስም ሙስሊሞችን መከራ ላይ የዳረጉት፡፡
ሙስሊሙ በድጋሚ በነዚህ ሰዎች እንዳይሸወድ፣ እዚህ ከባድ መከራ ውስጥ ሙስሊሙን የከተቱት ኢኽዋኖች ናቸው ማለት ለሙስሊሙ አለማዘን አይደለም፡፡ እንዲያውም ከዚህ አደገኛ ቡድንም ይሁን ከሌሎች ቡድኖች ኡማውን ማስጠንቀቅ ለኡማው በጣም ከማዘን እና ከመጨነቅ ነው፡፡
በተገላቢጦሹ አንዳንድ የእውቀት ባለቤት ነን እያሉ ኡማው በነዚህ ተኩላዎች ሲሸወደ እያዩ ዝምታን የመረጡ ሰዎች አላህን አይፈሩትምን
አላህ እንዲህ ይላል
وَإِذْ أَخَذَ ٱللَّهُ مِيثَٰقَ ٱلَّذِينَ أُوتُوا۟ ٱلْكِتَٰبَ لَتُبَيِّنُنَّهُۥ لِلنَّاسِ وَلَا تَكْتُمُونَهُۥ فَنَبَذُوهُ وَرَآءَ ظُهُورِهِمْ وَٱشْتَرَوْا۟ بِهِۦ ثَمَنًا قَلِيلًا ۖ فَبِئْسَ مَا يَشْتَرُونَ
አላህ የነዚያን መጽሐፉን የተሰጡትን ቃል ኪዳን ለሰዎች በእርግጥ ታብራሩታላችሁ አትደብቁትምም በማለት የያዘባቸውን (አስታውሱ)፡፡ በጀርባዎቻቸውም ኋላ ጣሉት፡፡ በርሱም ጥቂትን ዋጋ ገዙ፡፡ የሚገዙትም ነገር ከፋ!
ይህ አንቀፅ አላህ እውቀት ሰጥቷቸው በእውቀታቸው የማይሰሩትን፣ እውነቱን ለሰዎች የማያብራሩትን እና የሚደብቁትን የሚወቅስበት ነው፡፡ እነዚህ ግለሰቦች ለቀላቢያቸው አልታመን ብለዋል፡፡ ሐቁን ደብቀዋል፡፡ ብሎም ለባጢል ጥብቅና ቆመዋል፡፡
ኢኽዋን የከሰረ የጥመት ቡድን ነው፡፡ ኢኽዋን ከእለት እለት ኪሳራው በግልፅ በወጣ ቁጥር ኢኽዋንን አናስነካም ብለው፣ ለኢኽዋን ጥብቅና የቆሙ፣ ማስረጃን ሲጠመዝዙ የነበሩ በጠቅላላ ከኢኽዋን በላይ የከሰሩ መሆናቸውን እያየን ነው፡፡
አላህ በሐቅ ላይ ይሰብስበን፡፡ ሐቅን በሐቅነቱ ያሳያን የምንቀበለውም ያድርገን፡፡ ባጢልን በባጢልነቱ ያሳየን የምንርቀውም ያድርገን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
አንድ ሙስሊም በአደባባይ ቢድኣ ሲሰራ፣ ዲን ሲፈርስ፣ የባጢል ሰዎች ቢድአቸውን ሲረጩ ካየ ከቁርኣን፣ ከሀዲስ፣ ከሰለፎች ወይንም ከኡለማዎች ንግግር ጠቅሶ መልስ መስጠት ይችላል ብቻ ሳይሆን ተገቢም ነው፡፡ ቢድአ እና ጥፋትን ለማስጠንቀቅ ከየትኛውም ኢስላማዊ ዩኒቨርስቲ ዲግሪ፣ ማስተርስ፣ ዶክትሬት ብሎም የየትኛውም መርከዝም ይሁን ግለሰብ ፍቃድ አያስፈልገውም፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
https://t.me/SadatTextPosts
በእስልምና ወሮች 12 ናቸው እነሱም
1) ሙሐረም፣
2) ሰፈር፣
3) ረቢእ አል-አወል፣
4) ረቢእ አስ-ሳኒ፣
5) ጀማዳ አል-አወል፣
6) ጀማዳ አስ-ሳኒ፣
7) ረጀብ፣
8) ሻእባን፣
9) ረመዳን፣
10) ሸዋል፣
11) ዙል ቃኢዳ፣
12) ዙል ሂጃህ ናቸው፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
1) ሙሐረም፣
2) ሰፈር፣
3) ረቢእ አል-አወል፣
4) ረቢእ አስ-ሳኒ፣
5) ጀማዳ አል-አወል፣
6) ጀማዳ አስ-ሳኒ፣
7) ረጀብ፣
8) ሻእባን፣
9) ረመዳን፣
10) ሸዋል፣
11) ዙል ቃኢዳ፣
12) ዙል ሂጃህ ናቸው፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
የሀገራችን ጉዳይ ወሬ ሳይሆን ዱኣ ይፈልጋል፡፡ በየ ሶሻል ሚድያው፣ በየ ካፌው የማይጠቅም ወሬ ከማውራት፣ አንዱ የሌላውን ዘር ከማጥላላት አምርሮ ዱአ ማድረግ ወሳኝ ነው፡፡ ምክንያቱም አላህን ለማምለክ እንኳን ሰላም አስፈላጊ ነው፡፡
አላህ ሀገራችን ላይ ፍትህ እና ሰላም ያስፍን፡፡ እሱም ሁሉን በማድረግ ላይ ቻይ ነው፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
አላህ ሀገራችን ላይ ፍትህ እና ሰላም ያስፍን፡፡ እሱም ሁሉን በማድረግ ላይ ቻይ ነው፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
መፅሀፋ በገበያ ላይ ዋለ !!
አዲስ አበባ ባሉ ኪታብ ቤቶች ማግኘት ይችላሉ ክፍለ ሀገርም ያሉ ነጋዴዎች ጋር እየተዳረሰ በመሆኑ አቅራቢያችሁ በሚገኝ ኪታብ ቤት በመጠየቅ እንዲያስመጡላችሁ መጠየቅ ትችላላችሁ
ከሀገር ውጪ ያላችሁ ብዛት የምትፈልጉ በዚህ ቁጥር አናግሩት ይልክላችኋል
¶ 0925504315 ሙሀመድ ሰዒድ
አዲስ አበባ ባሉ ኪታብ ቤቶች ማግኘት ይችላሉ ክፍለ ሀገርም ያሉ ነጋዴዎች ጋር እየተዳረሰ በመሆኑ አቅራቢያችሁ በሚገኝ ኪታብ ቤት በመጠየቅ እንዲያስመጡላችሁ መጠየቅ ትችላላችሁ
ከሀገር ውጪ ያላችሁ ብዛት የምትፈልጉ በዚህ ቁጥር አናግሩት ይልክላችኋል
¶ 0925504315 ሙሀመድ ሰዒድ
አስደሳች ዜና
ማንኛውንም የተውሂድ ፣ የሱና ፣ ሴቶችን የተመለከቱ ህግጋቶችን እና የሰለፎችን ታሪክ የሚዳስሱ መፅሀፎችን ውጪ ሀገር ለምትኖሩ ወንድምና እህቶች በብዛት መላክ ጀምረናል።
ዱባይ፣ኩየት፣ሳኡድአረቢያ፣ኳታር፣
አሜሪካ፣እንግሊዝ እንዲሁም በሌሎች ሀገሮችም ጭምር እንልካለን።
ጀመአ ጀመአ በመሆን አንድን ሰው በመወከል ይዘዙን ባሉበት ቦታ እንልካለን።
በዚህ ስልክ ቁጥር ያናግሩን
በዋትስአፕም በቴሌግራምም
በኢሞም ያገኙናል
👇👇👇👇
+251925504315
+251925504315
ሙሐመድ ሰኢድ
ማንኛውንም የተውሂድ ፣ የሱና ፣ ሴቶችን የተመለከቱ ህግጋቶችን እና የሰለፎችን ታሪክ የሚዳስሱ መፅሀፎችን ውጪ ሀገር ለምትኖሩ ወንድምና እህቶች በብዛት መላክ ጀምረናል።
ዱባይ፣ኩየት፣ሳኡድአረቢያ፣ኳታር፣
አሜሪካ፣እንግሊዝ እንዲሁም በሌሎች ሀገሮችም ጭምር እንልካለን።
ጀመአ ጀመአ በመሆን አንድን ሰው በመወከል ይዘዙን ባሉበት ቦታ እንልካለን።
በዚህ ስልክ ቁጥር ያናግሩን
በዋትስአፕም በቴሌግራምም
በኢሞም ያገኙናል
👇👇👇👇
+251925504315
+251925504315
ሙሐመድ ሰኢድ
መውሊድን ስንቴ ነው የሚያከብሩት?
የአፊንጮ በሩ አል-አቅሳ መስጊድ?
እንደሚታወቀው በኢስላም ሁለት አመታዊ በዓል ተደንግገውልናል፡፡ እነሱም ኢድ አል-ፊጥር እና ኢድ አል-አድሃ ናቸው፡፡ በኢስላም ላይ አላህ እና ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ያላዘዙበት፡፡ ሰሃባዎች፣ አራቱ አኢማዎች፣ ቡኻሪ፣ ሙስሊም፣ ቲርሚዚ፣ ኢብን ማጃ እና ሌሎችም ሙሐዲሱች የማያውቁት እና ያልሰሩት፡፡ ከአራት መቶ አመት በኋላ ሺአዎች የጀመሩትን “መውሊድ (ነብዩ ሙሐመድ የተወለዱበትን ቀን ረቢአል አወል 12 ብለው ማክበር)” ተጀመረ፡፡ ይህ ፅሁፍ ኢስላም የማያውቀውን መውሊድን ስንቴ ነው የሚያከብሩት? የሚል ይሆናል፡፡ የሚገርመው ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) የተወለዱበት ቀን በኡለማዎች መሃል ልዩነት አለ፡፡ የሞቱበት ግን በቁርጥ ረቢአል አወል 12 ነው፡፡
እነዚህ ሰዎች የሚያከብሩት የሞቱበትን ወይንስ የተወለዱበትን?
ያሳለፍነው እሁድ አዲስ አበባ አፊንጮ በር አካባቢ የሚገኘው አል-አቅሳ መስጂድ መውሊድ ተከበረበት፡፡ 17 ረጀብ 1440 ሒጅራ አቆጣጠር ማለት ነው፡፡ ጥያቄው እነሱ ዘንድ “መውሊድ” የሚሉት በአል በወቅት የተገደበ አይደለምን? በአመት ስንት ጊዜ ነው የሚከበረው? ለምን ይሆን ከአምስት ወር በኋላ ደግመው ያከበሩት?
ሁለቱ በኢስላም የተደነገጉት ኢዶች (ኢድ እና አረፋ) በቀናቸው ነው የሚከበሩት፡፡ ይሀው ኢስላም የማያውቀው፣ የሺርክ መነሀሪያ፣ የጭፈራ እና የመደለቂያ ፈጠራ (ልደት ማክበር) ከመጣ በኋላ በተለይ በሀገራችን ይህን ሁሉ ውዥንብር እያየን ነው፡፡ ረቢአል አወል አስራ ሁለትን አልፈው ከአምስት ወር በኋላም ጭፈራ፣ መብላት መጠጣታቸውን ለመወጣት ያከብሩታል፡፡ መቼም የቢድኣ (ዲንን የማፍረስ) አባዚ የተጠናወተው በአንድ ቢድኣ ላይ አይቆምም፡፡ ይሀው አንዷ ቢድኣ ቀን አልበቃቸው ብላ ያችኑ ቢድኣ በተለያየ ቀን ያጨማልቋታል፡፡
በሀገራችን የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ልደት የሚሉትን ብቻ አይደለም የሚያከብሩት፡፡ ይልቁንም የአብሬት መውሊድ፣ የቃጥባሬ መውሊድ፣ የዳንግላው መውሊድ….. የመሳሰለውን እየተባለ በተለያየ ቀናት አመቱን ሙሉ የሺርክ እና ክህደት ስንኞች ይዜማሉ፣ ሴት እና ወንድ ተደብልቀው ይጨፈራል፣ ይህ መርዝ አደገኛ ቅጠል ጫት ይታኘካል፡፡
ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “የእኛ ትእዛዝ የሌለበትን ስራ የሰራ ሰው ስራው ተመላሽ ነው፡፡ (ተቀባይነት የለውም)” ብለዋል፡፡ መውሊድ አላህም መልክተኛውም አላዘዙበትም፡፡
ከሁሉ የሚገርመው እዚሁ መስጂድ ላይ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ቂርኣት መቅራት ጀምረው ነበር፡፡ ግን ተከለከሉ፡፡ አህባሽን መስጂድ ውስጥ የሚያስጨፍር፣ ተማሪዎችን ቂርኣት የሚከለክል ኡለማ፣ ባለሃብት እና ኮሚቴ ነገ አላህ ፊት ምን ይሆን መልሱ?
ያሳዝናል መስጂዱ በስንት መከራ እና መስዋትነት እንደተሰራ የሚያውቅ ያውቀዋል፡፡ ዛሬ ግን ቂርኣት ተከልክሎ መውሊድ የሚደለቁበት መስጂድ ሆኗል፡፡ አላህ ተውሒድ እና ሱና የበላይ የሚሆንበትን፣ ሺርክ እና ቢድኣ የሚዋረድበትን ወቅት ያቅርብልን፡፡
የአላህ ሰላት እና ሰላም በነብያት ሁሉ መደምደሚያ፣ በባለቤቶቻቸው፣ በባልደረባዎቻቸው እና ሐቅን በተከተለ ላይ ሁሉ ይሁን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
የአፊንጮ በሩ አል-አቅሳ መስጊድ?
እንደሚታወቀው በኢስላም ሁለት አመታዊ በዓል ተደንግገውልናል፡፡ እነሱም ኢድ አል-ፊጥር እና ኢድ አል-አድሃ ናቸው፡፡ በኢስላም ላይ አላህ እና ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ያላዘዙበት፡፡ ሰሃባዎች፣ አራቱ አኢማዎች፣ ቡኻሪ፣ ሙስሊም፣ ቲርሚዚ፣ ኢብን ማጃ እና ሌሎችም ሙሐዲሱች የማያውቁት እና ያልሰሩት፡፡ ከአራት መቶ አመት በኋላ ሺአዎች የጀመሩትን “መውሊድ (ነብዩ ሙሐመድ የተወለዱበትን ቀን ረቢአል አወል 12 ብለው ማክበር)” ተጀመረ፡፡ ይህ ፅሁፍ ኢስላም የማያውቀውን መውሊድን ስንቴ ነው የሚያከብሩት? የሚል ይሆናል፡፡ የሚገርመው ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) የተወለዱበት ቀን በኡለማዎች መሃል ልዩነት አለ፡፡ የሞቱበት ግን በቁርጥ ረቢአል አወል 12 ነው፡፡
እነዚህ ሰዎች የሚያከብሩት የሞቱበትን ወይንስ የተወለዱበትን?
ያሳለፍነው እሁድ አዲስ አበባ አፊንጮ በር አካባቢ የሚገኘው አል-አቅሳ መስጂድ መውሊድ ተከበረበት፡፡ 17 ረጀብ 1440 ሒጅራ አቆጣጠር ማለት ነው፡፡ ጥያቄው እነሱ ዘንድ “መውሊድ” የሚሉት በአል በወቅት የተገደበ አይደለምን? በአመት ስንት ጊዜ ነው የሚከበረው? ለምን ይሆን ከአምስት ወር በኋላ ደግመው ያከበሩት?
ሁለቱ በኢስላም የተደነገጉት ኢዶች (ኢድ እና አረፋ) በቀናቸው ነው የሚከበሩት፡፡ ይሀው ኢስላም የማያውቀው፣ የሺርክ መነሀሪያ፣ የጭፈራ እና የመደለቂያ ፈጠራ (ልደት ማክበር) ከመጣ በኋላ በተለይ በሀገራችን ይህን ሁሉ ውዥንብር እያየን ነው፡፡ ረቢአል አወል አስራ ሁለትን አልፈው ከአምስት ወር በኋላም ጭፈራ፣ መብላት መጠጣታቸውን ለመወጣት ያከብሩታል፡፡ መቼም የቢድኣ (ዲንን የማፍረስ) አባዚ የተጠናወተው በአንድ ቢድኣ ላይ አይቆምም፡፡ ይሀው አንዷ ቢድኣ ቀን አልበቃቸው ብላ ያችኑ ቢድኣ በተለያየ ቀን ያጨማልቋታል፡፡
በሀገራችን የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ልደት የሚሉትን ብቻ አይደለም የሚያከብሩት፡፡ ይልቁንም የአብሬት መውሊድ፣ የቃጥባሬ መውሊድ፣ የዳንግላው መውሊድ….. የመሳሰለውን እየተባለ በተለያየ ቀናት አመቱን ሙሉ የሺርክ እና ክህደት ስንኞች ይዜማሉ፣ ሴት እና ወንድ ተደብልቀው ይጨፈራል፣ ይህ መርዝ አደገኛ ቅጠል ጫት ይታኘካል፡፡
ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “የእኛ ትእዛዝ የሌለበትን ስራ የሰራ ሰው ስራው ተመላሽ ነው፡፡ (ተቀባይነት የለውም)” ብለዋል፡፡ መውሊድ አላህም መልክተኛውም አላዘዙበትም፡፡
ከሁሉ የሚገርመው እዚሁ መስጂድ ላይ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ቂርኣት መቅራት ጀምረው ነበር፡፡ ግን ተከለከሉ፡፡ አህባሽን መስጂድ ውስጥ የሚያስጨፍር፣ ተማሪዎችን ቂርኣት የሚከለክል ኡለማ፣ ባለሃብት እና ኮሚቴ ነገ አላህ ፊት ምን ይሆን መልሱ?
ያሳዝናል መስጂዱ በስንት መከራ እና መስዋትነት እንደተሰራ የሚያውቅ ያውቀዋል፡፡ ዛሬ ግን ቂርኣት ተከልክሎ መውሊድ የሚደለቁበት መስጂድ ሆኗል፡፡ አላህ ተውሒድ እና ሱና የበላይ የሚሆንበትን፣ ሺርክ እና ቢድኣ የሚዋረድበትን ወቅት ያቅርብልን፡፡
የአላህ ሰላት እና ሰላም በነብያት ሁሉ መደምደሚያ፣ በባለቤቶቻቸው፣ በባልደረባዎቻቸው እና ሐቅን በተከተለ ላይ ሁሉ ይሁን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
ዘረኝነት?
ማንም ከማንም አይበልጥም፣ ማንም ከማንም አያንስም አላህን በመፍራት ቢሆን እንጂ፡፡
ነብዩ (ﷺ) ከመሞታቸው በፊት ስለ ዘረኝነት አስከፊነት መክረውን ነበር፡፡
“አረብ እኮ አረብ ባልሆኑት ላይ ብልጫ የለውም፣
አረብ ያልሆነውም በአረብ ላይ ብልጫ የለውም፡፡
ነጭ (ፈረንጅ) በጥቁር ላይ ብልጫ የለውም፣
ጥቁርም በነጭ ላይ ብልጫ የለውም
አላህን በመፍራት ቢሆን እንጂ፡፡”
የአላህ ውድ፣ ነብዩ ሙሐመድ (ﷺ) እንዲህ በሽታችንን ሁሉ ግልፅልፅ አድርገው ነግረውናል፡፡ መድሃኒቱንም ነግረውናል፡፡
ለሚመከር ከነፍሱ በላይ የሆኑ መካሪ ናቸው፡፡ አላህ ጀነት ላይ የእኝህ ውድ መካሪያችን ጎረቤት ያድርገን፡፡
አላህ ሀገራችንን ከዘረኝነት የፀዳች፣ አላህን በመፍራት ላይ የተገነባች ያድርጋት፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
ማንም ከማንም አይበልጥም፣ ማንም ከማንም አያንስም አላህን በመፍራት ቢሆን እንጂ፡፡
ነብዩ (ﷺ) ከመሞታቸው በፊት ስለ ዘረኝነት አስከፊነት መክረውን ነበር፡፡
“አረብ እኮ አረብ ባልሆኑት ላይ ብልጫ የለውም፣
አረብ ያልሆነውም በአረብ ላይ ብልጫ የለውም፡፡
ነጭ (ፈረንጅ) በጥቁር ላይ ብልጫ የለውም፣
ጥቁርም በነጭ ላይ ብልጫ የለውም
አላህን በመፍራት ቢሆን እንጂ፡፡”
የአላህ ውድ፣ ነብዩ ሙሐመድ (ﷺ) እንዲህ በሽታችንን ሁሉ ግልፅልፅ አድርገው ነግረውናል፡፡ መድሃኒቱንም ነግረውናል፡፡
ለሚመከር ከነፍሱ በላይ የሆኑ መካሪ ናቸው፡፡ አላህ ጀነት ላይ የእኝህ ውድ መካሪያችን ጎረቤት ያድርገን፡፡
አላህ ሀገራችንን ከዘረኝነት የፀዳች፣ አላህን በመፍራት ላይ የተገነባች ያድርጋት፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
122 ሀዲሶች ለመሀፈዝ
رَوْضَةُ الْبَادِئِينَ
محمد بن على بن حزام البعداني
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ እጅግ በጣም አዛኝ፡፡ የአላህ ሰላት እና ሰላም በሙሐመድ፣ በባልደረባዎቻቸው፣ በባለቤቶቻቸው እና ሐቅን በተከተሉ ላይ ሁሉ ይሁን፡፡ ነብዩ (ﷺ) “አላህ መልካም የሻለት ሰው ዲኑን ያስገነዝበዋል” ብለዋል፡፡ ይህችን አጭር ኪታብ “የጀማሪዎች ጨፌ” በመባል ትታወቃለች፡፡ በአምስት ታላላቅ አርእስቶች የተከፋፈለች ናት፡፡ አርእስቶቹም በስራቸው ከያዟቸው ሀዲሶች ጋር እንደሚከተሉት ናቸው፡፡ ከአቂዳ ጋር የተያያዙ ሃያ አምስት ሀዲሶች፣ ከፊቅህ ጋር የተያያዙ ሃያ ሀዲሶች፣ ከከባባድ ወንጀሎች እና ከሀራም ጋር የተያያዙ ሃያ ስድስት ሀዲስች፣ ከስነ-ስርዓት ጋር የተያያዙ ሰላሳ አራት ሀዲሶች፣ ከዚክር እና ከዱኣ ጋር የተያያዙ አስራ ሰባት ሀዲሶች ናቸው፡፡ በአጠቃላይ አንድ መቶ ሃያ ሁለት የነብዩ (ﷺ) ሀዲሶች የያዘች መፀሀፍ ናት፡፡ ለመሸምደድም፣ ለመማር ማስተማርም በጣም ጠቃሚ ሆና አግኝቻታለሁ፡፡ ስለዚህም በአላህ ፍቃድ እና እገዛ ለህትመት በቅታለች፡፡ ውድ ኡስታዞች ሆይ! ተማሪዎቻችሁን እንዲሸመድዷት ገፋፉ፣ ትርጉሟንም በየቋንቋው ለማህበረሰባችን በደንብ አብራሩ፡፡ በየመርከዙ እና በየመድረሳው በትምህርትነት ብትሰጥ በአላህ ፍቃድ በጣም ጠቃሚ ትሆናለች፡፡ ይህ ህዝብ የዱንያውም ይሁን የአኸይራው ጉዳይ የሚስተካከለው ስለ ኢስላም ጠንቅቆ ሲማር ነው፡፡ አላህ እውቀትን ይጨምርልን፣ ዲኑን ያስገንዝበን፣ መሀይምነትን ያንሳልን፣ መጨረሻችንን ያሳምርልን፣ ሀገራችንን ሰላም ያድርግልን፡፡ አሚን፡፡
ኪታቡን ከሚከተሉት ሊንኮች ያውርዱ እና ለሌችም ሼር ያድርጉት
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem/1705
https://t.me/Kitaboch/198
رَوْضَةُ الْبَادِئِينَ
محمد بن على بن حزام البعداني
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ እጅግ በጣም አዛኝ፡፡ የአላህ ሰላት እና ሰላም በሙሐመድ፣ በባልደረባዎቻቸው፣ በባለቤቶቻቸው እና ሐቅን በተከተሉ ላይ ሁሉ ይሁን፡፡ ነብዩ (ﷺ) “አላህ መልካም የሻለት ሰው ዲኑን ያስገነዝበዋል” ብለዋል፡፡ ይህችን አጭር ኪታብ “የጀማሪዎች ጨፌ” በመባል ትታወቃለች፡፡ በአምስት ታላላቅ አርእስቶች የተከፋፈለች ናት፡፡ አርእስቶቹም በስራቸው ከያዟቸው ሀዲሶች ጋር እንደሚከተሉት ናቸው፡፡ ከአቂዳ ጋር የተያያዙ ሃያ አምስት ሀዲሶች፣ ከፊቅህ ጋር የተያያዙ ሃያ ሀዲሶች፣ ከከባባድ ወንጀሎች እና ከሀራም ጋር የተያያዙ ሃያ ስድስት ሀዲስች፣ ከስነ-ስርዓት ጋር የተያያዙ ሰላሳ አራት ሀዲሶች፣ ከዚክር እና ከዱኣ ጋር የተያያዙ አስራ ሰባት ሀዲሶች ናቸው፡፡ በአጠቃላይ አንድ መቶ ሃያ ሁለት የነብዩ (ﷺ) ሀዲሶች የያዘች መፀሀፍ ናት፡፡ ለመሸምደድም፣ ለመማር ማስተማርም በጣም ጠቃሚ ሆና አግኝቻታለሁ፡፡ ስለዚህም በአላህ ፍቃድ እና እገዛ ለህትመት በቅታለች፡፡ ውድ ኡስታዞች ሆይ! ተማሪዎቻችሁን እንዲሸመድዷት ገፋፉ፣ ትርጉሟንም በየቋንቋው ለማህበረሰባችን በደንብ አብራሩ፡፡ በየመርከዙ እና በየመድረሳው በትምህርትነት ብትሰጥ በአላህ ፍቃድ በጣም ጠቃሚ ትሆናለች፡፡ ይህ ህዝብ የዱንያውም ይሁን የአኸይራው ጉዳይ የሚስተካከለው ስለ ኢስላም ጠንቅቆ ሲማር ነው፡፡ አላህ እውቀትን ይጨምርልን፣ ዲኑን ያስገንዝበን፣ መሀይምነትን ያንሳልን፣ መጨረሻችንን ያሳምርልን፣ ሀገራችንን ሰላም ያድርግልን፡፡ አሚን፡፡
ኪታቡን ከሚከተሉት ሊንኮች ያውርዱ እና ለሌችም ሼር ያድርጉት
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem/1705
https://t.me/Kitaboch/198
Telegram
SadatKemal Abu Meryem
ሱዳን ላይ ከዳቦ መወደድ እና ከሺርኩ የቱ ይብሳል?
ሱዳኖቹ ዳቦ ተወደደ ብለው ህይወታችውን አደጋ ላይ ሲጥሉ፣ የአላህ መልክተኛ (ﷺ) ምን ብለው ነበር?
قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ مَنْ أَصْبَحَ مِنْكُمْ آمِنًا فِي سِرْبِهِ مُعَافًى فِي جَسَدِهِ عِنْدَهُ قُوتُ يَوْمِهِ فَكَأَنَّمَا حِيزَتْ لَهُ الدُّنْيَا
የአላህ መልክተኛ (ﷺ) እንዲህ አሉ “ከእናንተ ውስጥ በመኖሪያ ቤቱ (አካባቢው፣ ቤተሰቡ….) ሰላም ሆኖ፣ ሰውነቱ (አካሉ) ጤነኛ ሆኖ፣ የእለት ቀለቡ ያለው ሆኖ ያነጋ (ያደረ) ሰው፣ (ይህ ሰው) ለእርሱ ዱንያ እንደተሰበሰበችለት (የእሱ እንደሆነችለት) ነው፡፡” ቲርሚዚ ዘግበውታል አልባኒ ሀሰን ብለውታል 2346
ተመልከቱ በመላው አረብ ሀገራት ላይ “ኑሮ ተወደደ” እያሉ የተከበረውን ጁምዓ ቀን ለነሱ ከኢስላም ጋር ምንም ግንኙነት ለሌለው ፖለቲካዊ ሰልፍ ይጠቀሙበታል፡፡ እርጉሙ አልጀዚራ ያቀጣጥልላቸዋል፡፡ አስገራሚው ግን የአላህ መልክተኛ (ﷺ) ከላይ እንዳየነው አንድ ሰው ምን ሲሟላለት ዱንያ ለእሱ የተሰበሰበችለት እንደሆነ ጠቀሱ
- ሰላም ሆኖ በመኖሪያው ያነጋ፣
- ሰውነቱ ጤነኛ ሆኖ ያነጋ፣
- የእለት ቀለቡ ያነጋ ሰው
* ዱንያ ለእሱ እንደተሰበሰበችለት ነው ብለው ተናገረው ሲያበቁ ፖለቲከኞቹ ሰልፍ ወጪዎች አንሰማም “ዳቦ ተወደደብን” በሚል ህይወት ለመጥፋት ሰበብ የሆኑ ሰልፎች ተካሄዱ፡፡
አስገራሚው ሱዳን ላይ ከዳቦው ጉዳይ በላይ በአላህ ላይ የሚያጋሯቸው ስንት እና ስንት ቀብሮች አሉ፣ ስንት እና ስንት ጠንቋይ እና ድግምተኞች አሉ፡፡ ይህ ሁሉ “ዳቦ ተወደደ” ለሚሉት ፖለቲከኞች ደንታቸው አይደለም፡፡
አላህ ደግሞ እኛ እራሳችንን እስካልቀየርን ድረስ ምንም እንደማይቀይርልን ነገሮናል፡፡
አላህ በቁርዓን እና በነብዩ አስተምህሮት ከሚመከሩት ያድርገን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
ሱዳኖቹ ዳቦ ተወደደ ብለው ህይወታችውን አደጋ ላይ ሲጥሉ፣ የአላህ መልክተኛ (ﷺ) ምን ብለው ነበር?
قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ مَنْ أَصْبَحَ مِنْكُمْ آمِنًا فِي سِرْبِهِ مُعَافًى فِي جَسَدِهِ عِنْدَهُ قُوتُ يَوْمِهِ فَكَأَنَّمَا حِيزَتْ لَهُ الدُّنْيَا
የአላህ መልክተኛ (ﷺ) እንዲህ አሉ “ከእናንተ ውስጥ በመኖሪያ ቤቱ (አካባቢው፣ ቤተሰቡ….) ሰላም ሆኖ፣ ሰውነቱ (አካሉ) ጤነኛ ሆኖ፣ የእለት ቀለቡ ያለው ሆኖ ያነጋ (ያደረ) ሰው፣ (ይህ ሰው) ለእርሱ ዱንያ እንደተሰበሰበችለት (የእሱ እንደሆነችለት) ነው፡፡” ቲርሚዚ ዘግበውታል አልባኒ ሀሰን ብለውታል 2346
ተመልከቱ በመላው አረብ ሀገራት ላይ “ኑሮ ተወደደ” እያሉ የተከበረውን ጁምዓ ቀን ለነሱ ከኢስላም ጋር ምንም ግንኙነት ለሌለው ፖለቲካዊ ሰልፍ ይጠቀሙበታል፡፡ እርጉሙ አልጀዚራ ያቀጣጥልላቸዋል፡፡ አስገራሚው ግን የአላህ መልክተኛ (ﷺ) ከላይ እንዳየነው አንድ ሰው ምን ሲሟላለት ዱንያ ለእሱ የተሰበሰበችለት እንደሆነ ጠቀሱ
- ሰላም ሆኖ በመኖሪያው ያነጋ፣
- ሰውነቱ ጤነኛ ሆኖ ያነጋ፣
- የእለት ቀለቡ ያነጋ ሰው
* ዱንያ ለእሱ እንደተሰበሰበችለት ነው ብለው ተናገረው ሲያበቁ ፖለቲከኞቹ ሰልፍ ወጪዎች አንሰማም “ዳቦ ተወደደብን” በሚል ህይወት ለመጥፋት ሰበብ የሆኑ ሰልፎች ተካሄዱ፡፡
አስገራሚው ሱዳን ላይ ከዳቦው ጉዳይ በላይ በአላህ ላይ የሚያጋሯቸው ስንት እና ስንት ቀብሮች አሉ፣ ስንት እና ስንት ጠንቋይ እና ድግምተኞች አሉ፡፡ ይህ ሁሉ “ዳቦ ተወደደ” ለሚሉት ፖለቲከኞች ደንታቸው አይደለም፡፡
አላህ ደግሞ እኛ እራሳችንን እስካልቀየርን ድረስ ምንም እንደማይቀይርልን ነገሮናል፡፡
አላህ በቁርዓን እና በነብዩ አስተምህሮት ከሚመከሩት ያድርገን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
"አረብ ስፕሪንግ" ከእስልምና ሀይማኖት ጋር ምንም ግንኙነት የለውም።
በየ አረብ ሀገራቱ ከፍጡራን መብት በላይ የአላህ መብት ተገፎ
– ከአላህ ውጭ ለፍጡራን ይሰገዳል፣ ፍጡራን ይለመናሉ፣ ለፍጡራን እርድ አምልኮ ይፈፀማል፣ በፍጡራን ላይ ይመካሉ፣ የፍጡራንን ቀብር ይጠውፋሉ፣ የቀብር አፈር ይቅማሉ በጥብጠው ይጠጣሉ፣ በፍጡራን ይምላሉ …
– የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ሱና ትተው መውሊድ፣ ረጀብ፣ ሸእባን … እያሉ ዲኑን ከውስጥ ሆነው ይንዳሉ፣
– ሴቶች አላህ የተረገመበትን ቅንድብ ይቀነደባሉ። አለባበሳቸውም ከእለት እለት ከዲን ያፈነገጠ ሆኖዋል፣
– ወንዶች በተለያዩ ሱሶች ውስጥ ወድቀዋል፣
ይህ ሁሉ በደል እራሳቸው እየፈፀሙ "መሪ በደለን" ብለው ወንድ እና ሴት ተደባልቀው አደባባይ ወጡ። በዚህም ምክንያት
– ሀገራቸውን አወደሙ፣ አፈረሱ፣
– የሰው ህይወት ጠፋ፣
– ስደት ተስፋፋ፣
– ሴቶች ተደፈሩ፣
– ህፃናት ከአቅማቸው በላይ የሆነ ከባድ እንግልት ደረሰባቸው፣
ምንም እንኳን ጁምኣ ቀንን ለፖለቲካ አላማቸው ቢጠቀሙ፣ መፈክሮቻቸው ላይ "አላሁ አክበር፣ ላ ኢላሃ ኢለ አሏህ… …" ስላሉ፣ እዛው አደባባይ ላይ ሰላት ስለሰገዱ በፍፁም ሀይማኖታዊ ሊሆን አይችልም። እውነት ለኢስላም እና ለሙስሊሞች ቢሆን ኖሮ ትግላቸው ነብያት እንደለፉት ሰዎችን ዘላለም ጀሀነም እሳት ውስጥ የሚያከርመውን በአላህ ላይ ማጋራት ከምንም ነገር በፊት ቀድመው ይዋጉት ነበር።
ለዚህ ሁሉ ደም መፍሰስ፣ ስደት፣ ሀገር መፍረስ ይህንን የፖለቲካ አካሄድ ሀይማኖታዊ ቅብ እየቀቡ ወጣቱን ሲያነሳሱ የነበሩ የጠመጠሙ የሰው ሰይጣናት፣ አልጀዚራ የተባለው የቴሌቭዥን ጣቢያ ባለቤቶች፣ አሰራጮች አላህ ዘንድ ተጠያቂ ይሆናሉ። አላህም አያያዙ የበረታ ነው።
አብዛኛው ሰው በተለይ አላዋቂዎች "አላሁ አክበር" በተባለ ቁጥር ሁሉ ነገር ኢስላማዊ እና ለኢስላም የሚመስላቸው ስንት ምስኪኖች አሉ። አረብ ሀገራቱ ላይ "አ ሻእብ ዩሪድ… " ሲባል የነበረው ምንም የሀይማኖታዊ ሽፋን ሊሰጠው ቢሞክርም ከሀይማኖት ጋር ምንም ግንኙነት የሌለው ፖለቲካ ነው።
ለእኛ አዛኝ የሆኑት ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ሙስሊም መሪዎችን አስመልክቶ "ገንዘባችሁን ቢቀሟችሁ፣ ቢደበድቧችሁ… ሰላትን እስከሰገዱ ድረስ ስሟቸው ታዘዟቸው።" ብለው በጥብቅ አዘው ነበር። ምክንያቱም ሙስሊም መሪን አለመታዘዝ ምን ያህ አደጋ እንደሚያስከትል ወህይ (መለኮታዊ ራእይ) የማይለያቸው ታላቁ ነብይ በግልፅ ነግረው ነበር። ነገር ግን የሰው ሰይጣናት ይህን ግልፅ የሀዲስ መልክት በማዛባት የሙስሊሙን ኡማ ጌታውን አላህ እንዲያምፅ፣ የነብዩን ሱና እንዲቃረን በመልፋት አብዛኛው ሰው አጠመሙ።
የአላህ ባሪያዎች ሆይ! ሸሪአዊ እውቀትን ማካበት በሰው ሰይጣናት ወጥመድ ውስጥ ከመግባት ለመጠበቅ ትልቅ ሰበብ ነው። የነብዩን ሀዲስ እንማረው ለቢድአ ሰዎች ታላቁ እራስ ምታት የነብዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ሀዲስ ነው። እንማረው፣ እንስራበት፣ እናስተምረው።
አላህ ሁላችንንም ለሱና እጃቸውን ከሚሰጡት ያድርገን።
https://t.me/SadatTextPosts
በየ አረብ ሀገራቱ ከፍጡራን መብት በላይ የአላህ መብት ተገፎ
– ከአላህ ውጭ ለፍጡራን ይሰገዳል፣ ፍጡራን ይለመናሉ፣ ለፍጡራን እርድ አምልኮ ይፈፀማል፣ በፍጡራን ላይ ይመካሉ፣ የፍጡራንን ቀብር ይጠውፋሉ፣ የቀብር አፈር ይቅማሉ በጥብጠው ይጠጣሉ፣ በፍጡራን ይምላሉ …
– የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ሱና ትተው መውሊድ፣ ረጀብ፣ ሸእባን … እያሉ ዲኑን ከውስጥ ሆነው ይንዳሉ፣
– ሴቶች አላህ የተረገመበትን ቅንድብ ይቀነደባሉ። አለባበሳቸውም ከእለት እለት ከዲን ያፈነገጠ ሆኖዋል፣
– ወንዶች በተለያዩ ሱሶች ውስጥ ወድቀዋል፣
ይህ ሁሉ በደል እራሳቸው እየፈፀሙ "መሪ በደለን" ብለው ወንድ እና ሴት ተደባልቀው አደባባይ ወጡ። በዚህም ምክንያት
– ሀገራቸውን አወደሙ፣ አፈረሱ፣
– የሰው ህይወት ጠፋ፣
– ስደት ተስፋፋ፣
– ሴቶች ተደፈሩ፣
– ህፃናት ከአቅማቸው በላይ የሆነ ከባድ እንግልት ደረሰባቸው፣
ምንም እንኳን ጁምኣ ቀንን ለፖለቲካ አላማቸው ቢጠቀሙ፣ መፈክሮቻቸው ላይ "አላሁ አክበር፣ ላ ኢላሃ ኢለ አሏህ… …" ስላሉ፣ እዛው አደባባይ ላይ ሰላት ስለሰገዱ በፍፁም ሀይማኖታዊ ሊሆን አይችልም። እውነት ለኢስላም እና ለሙስሊሞች ቢሆን ኖሮ ትግላቸው ነብያት እንደለፉት ሰዎችን ዘላለም ጀሀነም እሳት ውስጥ የሚያከርመውን በአላህ ላይ ማጋራት ከምንም ነገር በፊት ቀድመው ይዋጉት ነበር።
ለዚህ ሁሉ ደም መፍሰስ፣ ስደት፣ ሀገር መፍረስ ይህንን የፖለቲካ አካሄድ ሀይማኖታዊ ቅብ እየቀቡ ወጣቱን ሲያነሳሱ የነበሩ የጠመጠሙ የሰው ሰይጣናት፣ አልጀዚራ የተባለው የቴሌቭዥን ጣቢያ ባለቤቶች፣ አሰራጮች አላህ ዘንድ ተጠያቂ ይሆናሉ። አላህም አያያዙ የበረታ ነው።
አብዛኛው ሰው በተለይ አላዋቂዎች "አላሁ አክበር" በተባለ ቁጥር ሁሉ ነገር ኢስላማዊ እና ለኢስላም የሚመስላቸው ስንት ምስኪኖች አሉ። አረብ ሀገራቱ ላይ "አ ሻእብ ዩሪድ… " ሲባል የነበረው ምንም የሀይማኖታዊ ሽፋን ሊሰጠው ቢሞክርም ከሀይማኖት ጋር ምንም ግንኙነት የሌለው ፖለቲካ ነው።
ለእኛ አዛኝ የሆኑት ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ሙስሊም መሪዎችን አስመልክቶ "ገንዘባችሁን ቢቀሟችሁ፣ ቢደበድቧችሁ… ሰላትን እስከሰገዱ ድረስ ስሟቸው ታዘዟቸው።" ብለው በጥብቅ አዘው ነበር። ምክንያቱም ሙስሊም መሪን አለመታዘዝ ምን ያህ አደጋ እንደሚያስከትል ወህይ (መለኮታዊ ራእይ) የማይለያቸው ታላቁ ነብይ በግልፅ ነግረው ነበር። ነገር ግን የሰው ሰይጣናት ይህን ግልፅ የሀዲስ መልክት በማዛባት የሙስሊሙን ኡማ ጌታውን አላህ እንዲያምፅ፣ የነብዩን ሱና እንዲቃረን በመልፋት አብዛኛው ሰው አጠመሙ።
የአላህ ባሪያዎች ሆይ! ሸሪአዊ እውቀትን ማካበት በሰው ሰይጣናት ወጥመድ ውስጥ ከመግባት ለመጠበቅ ትልቅ ሰበብ ነው። የነብዩን ሀዲስ እንማረው ለቢድአ ሰዎች ታላቁ እራስ ምታት የነብዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ሀዲስ ነው። እንማረው፣ እንስራበት፣ እናስተምረው።
አላህ ሁላችንንም ለሱና እጃቸውን ከሚሰጡት ያድርገን።
https://t.me/SadatTextPosts
ለፆመኛ የሚወደዱ ነገሮች፡-
1. ሰሑር መመገብ፡- ነብዩ ﷺ “በኛና በመፅሐፉ ሰዎች መካከል ያለው ጾም መበላለጫው የሱሑር ምግብ ነው” ብለዋል፡፡ [ሙስሊም፡ 1096]
2. ሰሑርን ተምር ማድረግ፡- ነብዩ ﷺ “ተምር ምን ያማረ የሙእሚን ሰሑር ነው” ብለዋል፡፡ [አስሶሒሐህ፡ 562]
3. ሰሑርን ማዘግየት፡- ነብዩ ﷺ “ሶስት ነገሮች ከነብያዊ ተግባራት ናቸው፡፡ ፊጥራን ማፋጠን፣ ሰሑርን ማዘግየት እና በሶላት ላይ ቀኝ እጅን ግራ ላይ ማድረግ ናቸው፡፡” [አልጃሚዑ አስሶጊር፡ 5349]
4. ፊጥራን ማፋጠን፡- ነብዩ ﷺ “ሰዎች ፊጥራን እስካቻኮሉ ድረስ ከኸይር አይወገዱም” ብለዋል፡፡ [ቡኻሪና ሙስሊም]
5. ሰሑርና ፊጥራን በልክ ማድረግ፣
6. በእሸት ተምሮች ማፍጠር፣ ካልተገኘ በበሰሉ ተምሮች፣ ከሌለ ውሃ መጎንጨት፡- “ነብዩ ﷺ ከመስገዳቸው በፊት በእሸት ተምሮች ያፈጥሩ ነበር፡፡ እሸቶች ከሌሉ በተምሮች፣ እነሱም ከሌሉ ውሃ ይጎነጩ ነበር፡፡” [አስሶሒሐህ፡ 2056]
7. ከፊጥራ በኋላ የሚከተለውን ዱዓእ ማድረግ፡- “ዘሀበ’ዝዞመኡ፣ ወብተልለቲል ዑሩቁ፣ ወሰበተል አጅሩ ኢንሻአላህ፡፡” አልባኒ “ሐሰን” ብለውታል፡፡ [ሶሒሑል ጃሚዕ፡ 4678] ትርጉሙም፡- “ጥሙ ተወገደ፤ ደም ስሮች ረጠቡ፤ በአላህ ፈቃድ ምንዳውም ተረጋገጠ፡፡”
8. ላስፈጠረህ ዱዓእ ማድረግ፣
9. ፆመኛ ማስፈጠርን ማብዛት፡- ነብዩ ﷺ “ፆመኛን ያሰፈጠረ ሰው ልክ የሱን (የፆመኛውን) አምሳያ ምንዳ አለው፡፡ ባይሆን የፆመኛው ምንዳ ምንም አይቀንስም” ብለዋል፡፡ [ሶሒሑል ጃሚዕ፡ 6415]
10. ተራዊሕን ኢማሙ እስከሚያጠናቅቅ አብሮ መስገድ፣
11. በመልካም ስራዎች ላይ ከወትሮው በተለየ መበርታት፡- ኢብኑ ዐባስ ረዲየላሁ ዐንሁ እንዲህ ይላሉ፡- “ነብዩ ﷺ ከማንም በላይ ቸር ነበሩ፡፡ ይበልጥ ቸር የሚሆኑት ደግሞ በረመዳን ነበር፡፡” [ቡኻሪና ሙስሊም] ስለዚህ ለቤተሰብ፣ ለዘመድ፣ ለጎረቤት፣ ለችግረኞች ከወትሮው በተለየ ማሰብና መደጎም፡፡ ዚክር፣ ዱዓእ፣ ቁርኣን መቅራት፣ ሱና ሶላቶችን መስገድ፣ በሽተኛን መጠየቅ፣ ቀብር መዘየር፣ ደዕዋ ማድረግ፣ መፋቂያ መጠቀም፣ ሰላምታ፣ ፈገግታ፣ መልካም ንግግር፣… ማብዛት፣
12. በመጨረሻው አስሩ የወሩ ቀናት በተለይም ሌሊቱ ላይ ይበልጥ ለዒባዳ መነሳሳት፡- “የአላህ መልእክተኛ ﷺ በመጨረሻዎቹ አስሮች ላይ - በሌሎቹ ከሚበራቱት በተለየ - ይበልጥ ይበራቱ ነበር፡፡” [ሙስሊም፡ 1175]
13. በሱሑር ሰዓት ኢስቲግፋር ማብዛት፣
14. ለሚሳደብ ሰው “እኔ ፆመኛ ነኝ” ብሎ መመለስ፡፡ [ቡኻሪና ሙስሊም]
15. ልጆችን ፆም ማለማመድ፣
16. ለቻለ ዑምራ ማድረግ፣
17. ኢዕቲካፍ ማድረግ፣…
1. ሰሑር መመገብ፡- ነብዩ ﷺ “በኛና በመፅሐፉ ሰዎች መካከል ያለው ጾም መበላለጫው የሱሑር ምግብ ነው” ብለዋል፡፡ [ሙስሊም፡ 1096]
2. ሰሑርን ተምር ማድረግ፡- ነብዩ ﷺ “ተምር ምን ያማረ የሙእሚን ሰሑር ነው” ብለዋል፡፡ [አስሶሒሐህ፡ 562]
3. ሰሑርን ማዘግየት፡- ነብዩ ﷺ “ሶስት ነገሮች ከነብያዊ ተግባራት ናቸው፡፡ ፊጥራን ማፋጠን፣ ሰሑርን ማዘግየት እና በሶላት ላይ ቀኝ እጅን ግራ ላይ ማድረግ ናቸው፡፡” [አልጃሚዑ አስሶጊር፡ 5349]
4. ፊጥራን ማፋጠን፡- ነብዩ ﷺ “ሰዎች ፊጥራን እስካቻኮሉ ድረስ ከኸይር አይወገዱም” ብለዋል፡፡ [ቡኻሪና ሙስሊም]
5. ሰሑርና ፊጥራን በልክ ማድረግ፣
6. በእሸት ተምሮች ማፍጠር፣ ካልተገኘ በበሰሉ ተምሮች፣ ከሌለ ውሃ መጎንጨት፡- “ነብዩ ﷺ ከመስገዳቸው በፊት በእሸት ተምሮች ያፈጥሩ ነበር፡፡ እሸቶች ከሌሉ በተምሮች፣ እነሱም ከሌሉ ውሃ ይጎነጩ ነበር፡፡” [አስሶሒሐህ፡ 2056]
7. ከፊጥራ በኋላ የሚከተለውን ዱዓእ ማድረግ፡- “ዘሀበ’ዝዞመኡ፣ ወብተልለቲል ዑሩቁ፣ ወሰበተል አጅሩ ኢንሻአላህ፡፡” አልባኒ “ሐሰን” ብለውታል፡፡ [ሶሒሑል ጃሚዕ፡ 4678] ትርጉሙም፡- “ጥሙ ተወገደ፤ ደም ስሮች ረጠቡ፤ በአላህ ፈቃድ ምንዳውም ተረጋገጠ፡፡”
8. ላስፈጠረህ ዱዓእ ማድረግ፣
9. ፆመኛ ማስፈጠርን ማብዛት፡- ነብዩ ﷺ “ፆመኛን ያሰፈጠረ ሰው ልክ የሱን (የፆመኛውን) አምሳያ ምንዳ አለው፡፡ ባይሆን የፆመኛው ምንዳ ምንም አይቀንስም” ብለዋል፡፡ [ሶሒሑል ጃሚዕ፡ 6415]
10. ተራዊሕን ኢማሙ እስከሚያጠናቅቅ አብሮ መስገድ፣
11. በመልካም ስራዎች ላይ ከወትሮው በተለየ መበርታት፡- ኢብኑ ዐባስ ረዲየላሁ ዐንሁ እንዲህ ይላሉ፡- “ነብዩ ﷺ ከማንም በላይ ቸር ነበሩ፡፡ ይበልጥ ቸር የሚሆኑት ደግሞ በረመዳን ነበር፡፡” [ቡኻሪና ሙስሊም] ስለዚህ ለቤተሰብ፣ ለዘመድ፣ ለጎረቤት፣ ለችግረኞች ከወትሮው በተለየ ማሰብና መደጎም፡፡ ዚክር፣ ዱዓእ፣ ቁርኣን መቅራት፣ ሱና ሶላቶችን መስገድ፣ በሽተኛን መጠየቅ፣ ቀብር መዘየር፣ ደዕዋ ማድረግ፣ መፋቂያ መጠቀም፣ ሰላምታ፣ ፈገግታ፣ መልካም ንግግር፣… ማብዛት፣
12. በመጨረሻው አስሩ የወሩ ቀናት በተለይም ሌሊቱ ላይ ይበልጥ ለዒባዳ መነሳሳት፡- “የአላህ መልእክተኛ ﷺ በመጨረሻዎቹ አስሮች ላይ - በሌሎቹ ከሚበራቱት በተለየ - ይበልጥ ይበራቱ ነበር፡፡” [ሙስሊም፡ 1175]
13. በሱሑር ሰዓት ኢስቲግፋር ማብዛት፣
14. ለሚሳደብ ሰው “እኔ ፆመኛ ነኝ” ብሎ መመለስ፡፡ [ቡኻሪና ሙስሊም]
15. ልጆችን ፆም ማለማመድ፣
16. ለቻለ ዑምራ ማድረግ፣
17. ኢዕቲካፍ ማድረግ፣…
ረመዳን አልደረሰምን….?
ጠለሃ ኢብን ኡበይዳህ (ረድየላሁ አንሁ) እንዳስተላለፉት
ሁለት ሰዎች ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ዘንድ መጥተው በእኩል ወቅት እስልምናን ተቀበሉ፡፡ አንደኛው ከሌላኛው በላይ ጂሀድ ላይ ይሳተፍ ነበር፡፡ በዚህም ምክንያት ጀሀድ ተሳትፎ ሰመኣት ሆነ፡፡ ሌላኛው ከዚህኛው አንድ አመት ያህል ቆይቶ ከዛም ሞተ፡፡
ጠለሀ እንዲህ አለ
“በህልሜ የጀነት በር ላይ ሆኜ አየሁ፡፡ ከሁለቱም ጋር ነበርኩ፡፡ አንድ ሰው ከጀነት ውስጥ መጥቶ ዘግይቶ የሞተውን ቀድሞ እንዲገባ አደረገው፡፡ ከዛም ድጋሚ መጥቶ ሰመኣቱን እንዲገባ አደረገው፡፡ ከዛም ተመልሶ መጣና አንተ ተመለስ ጊዜህ አልደረሰም አለኝ፡፡”
ጠለሀ (ከእንቅልፉ) ከነቃ በኋላ ለሰዎች ስለ ሁኔታው ተናገረ፡፡ ሁሉም ተገረሙ፡፡ ይህ ጉዳይ መልክተኛው ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ጋር ደረሰ፡፡ ለመልክተኛውም ጉዳዩ ሲነገራቸው
እሳቸውም (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ
من أي ذلك تعجبون؟ قالوا: يا رسول اللهّ هذا كان أشد الرجلين اجتهاداً ثم استشهد ودخل هذا الآخر الجنة قبله فقال رسول الله (صلى الله عليه وسلم) : أليس قد مكث هذا بعده سنة؟ قالوا: بلى. قال: أدرك رمضان فصام وصلى كذا وكذا من سجدة في السنة؟ قالوا: بلى. قال رسول الله (صلى الله عليه وسلم): فما بينهما أبعد مما بين السماء والأرض
“ምንድን ነው የሚገርማችሁ?”
እነሱም አሉ
“የ አላህ መልክተኛ ሆይ! ከሁለቱም ይህኛው በጣም ታግሏል (በጂሃድ) ሰመኣትም ሆነ፡፡ ነገር ግን ይህኛው ቀድሞት ጀነት ገባ፡፡”
የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ከሱ በኋላ አንድ አመት ወደ ኋላ አልቀረምን?” አሉ
እነሱም “አዎ ቀርቷል” አሉ
እሳቸውም (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ረመዳን አልደረሰምን፣ አልፆመምን፣ ይህን ይህን ያህል ሱጁዶች በዚህ አመት አልሰገደምን?” አሉ
እነሱም “አዎን (ደርሷል)” አሉ
የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “በሁለቱ መሃል ያለው ልዩነት በሰማይ እና ምድር ካለው ልዩነት ይበልጣል” አሉ
ኢብን ማጃህ የዘገቡት ትክክለኛ ዘገባ (2/345 346) እና አልባኒ አስ-ሲልሲላህ አስ-ሰሂሃ
የአላህ ባሪያዎች ሆይ! ረመዳንን በአግባቡ እንጠቀምበት፡፡ ይህን ያህል ታላቅ ምንዳ አለው፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
ጠለሃ ኢብን ኡበይዳህ (ረድየላሁ አንሁ) እንዳስተላለፉት
ሁለት ሰዎች ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ዘንድ መጥተው በእኩል ወቅት እስልምናን ተቀበሉ፡፡ አንደኛው ከሌላኛው በላይ ጂሀድ ላይ ይሳተፍ ነበር፡፡ በዚህም ምክንያት ጀሀድ ተሳትፎ ሰመኣት ሆነ፡፡ ሌላኛው ከዚህኛው አንድ አመት ያህል ቆይቶ ከዛም ሞተ፡፡
ጠለሀ እንዲህ አለ
“በህልሜ የጀነት በር ላይ ሆኜ አየሁ፡፡ ከሁለቱም ጋር ነበርኩ፡፡ አንድ ሰው ከጀነት ውስጥ መጥቶ ዘግይቶ የሞተውን ቀድሞ እንዲገባ አደረገው፡፡ ከዛም ድጋሚ መጥቶ ሰመኣቱን እንዲገባ አደረገው፡፡ ከዛም ተመልሶ መጣና አንተ ተመለስ ጊዜህ አልደረሰም አለኝ፡፡”
ጠለሀ (ከእንቅልፉ) ከነቃ በኋላ ለሰዎች ስለ ሁኔታው ተናገረ፡፡ ሁሉም ተገረሙ፡፡ ይህ ጉዳይ መልክተኛው ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ጋር ደረሰ፡፡ ለመልክተኛውም ጉዳዩ ሲነገራቸው
እሳቸውም (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ
من أي ذلك تعجبون؟ قالوا: يا رسول اللهّ هذا كان أشد الرجلين اجتهاداً ثم استشهد ودخل هذا الآخر الجنة قبله فقال رسول الله (صلى الله عليه وسلم) : أليس قد مكث هذا بعده سنة؟ قالوا: بلى. قال: أدرك رمضان فصام وصلى كذا وكذا من سجدة في السنة؟ قالوا: بلى. قال رسول الله (صلى الله عليه وسلم): فما بينهما أبعد مما بين السماء والأرض
“ምንድን ነው የሚገርማችሁ?”
እነሱም አሉ
“የ አላህ መልክተኛ ሆይ! ከሁለቱም ይህኛው በጣም ታግሏል (በጂሃድ) ሰመኣትም ሆነ፡፡ ነገር ግን ይህኛው ቀድሞት ጀነት ገባ፡፡”
የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ከሱ በኋላ አንድ አመት ወደ ኋላ አልቀረምን?” አሉ
እነሱም “አዎ ቀርቷል” አሉ
እሳቸውም (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ረመዳን አልደረሰምን፣ አልፆመምን፣ ይህን ይህን ያህል ሱጁዶች በዚህ አመት አልሰገደምን?” አሉ
እነሱም “አዎን (ደርሷል)” አሉ
የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “በሁለቱ መሃል ያለው ልዩነት በሰማይ እና ምድር ካለው ልዩነት ይበልጣል” አሉ
ኢብን ማጃህ የዘገቡት ትክክለኛ ዘገባ (2/345 346) እና አልባኒ አስ-ሲልሲላህ አስ-ሰሂሃ
የአላህ ባሪያዎች ሆይ! ረመዳንን በአግባቡ እንጠቀምበት፡፡ ይህን ያህል ታላቅ ምንዳ አለው፡፡
https://t.me/SadatTextPosts