Sadat_Text_Posts
10K subscribers
291 photos
8 videos
12 files
378 links
Download Telegram
Forwarded from SadatKemal Abu Meryem
👆🏻እነሱ ሳይፈልጉ ተኚታዬቻ቞ው ነው ፎቶዋ቞ውን ፖስት ዚሚያደርጉት ለሚሉ ወንድም እና እህቶቜ ማስሚጃ ይሆናቾው ዘንድ እና እነሱ እራሳ቞ው ፎቶዋ቞ውን ኡምራ ሲያደርጉ፣ ሰደቃ ሲሰጡ እና ሌላም ሲያደርጉ አምነውበት ለመሆኑ ይህቜን ማስሚጃ እንካቜሁ፡፡ አንድ ወንድሜ እንዲህ አለ
አላህ በሀዲሰል ቁድስ እንዲህ አለ፩
«ፆም ዚእኔ ነው በእርሱም ዚምመነዳው እኔው ነኝ!»
ይህን ገለፃ ይበልጥ ዚሚያጠናክሚው ነገር ቢኖር ሰዎቜ ዑምራ቞ውን እንደሚፖስቱት ሁሉ ፆማቾውን መፖሰት አለመቻላ቞ው ነው!
ዐጃኢብ!!!!!
Forwarded from SadatKemal Abu Meryem
ዚኢኜዋኖቜ ሚዛን?
አሁን ያለው ዚኳታር መሪ (አላህ ይጠብቀው) አባቱ እና አያቱ?
አሁን ያለው ዚኳታር መሪ (አላህ ይጠብቀው) አባትዚው ኚአያትዚው በመፈንቅለ መንግስት ስልጣን ሲቀማ ኢኜዋኖቜ ዝም አሉ፡፡ አሁን ያለው ዚግብፅ መሪ ሲሲ (አላህ ይጠብቀው) ኚሙሐመድ ሙርሲ ስልጣን በመፈንቅለ መንግስት ሲቀማ ኢኜዋኖቜ ሁሉ ተንጫጩ፡፡
ለምን?
አሁን ያለው ዚኳታር መሪ (አላህ ይጠብቀው) ኚአባቱ ስልጣንን ሲሚኚብ ኢኜዋኖቜ ዝም አሉ፣ ጭራሜ አደናነቁት፡፡
ታላቁ ሰሃባ ሙአዊያ ኢብን አቡ ሱፍያን (ሚድዚላሁ አንሁ) ለልጁ ስልጣን ሲያስተላልፍ ዹሚኹተለውን አሉ “ይሄ በኢስላም መሰሚት ዹለውም” ነው እና ዚመሳሰለውን አሉ፡፡
ሳውዲዎቹ መሪዎቜ (አላህ ይጠብቃ቞ውና) ወንድም ለወንድሙ ወይንም አባት ለልጁ ስልጣን ሲያስሚክብ ኢኜዋኖቜ “ስልጣን በዘር መወራሚስ በኢስላም ዹለም” አሉ፡፡
ለኳታር ሲሆን ዝምታ ለሳውዲ ሲሆን ተቃውሞ ዹሆነው በምን ምክንያት ነው?
አህሉሱና ወል ጀመኣ ሙስሊም መሪ በሰላምም ይያዝ በሃይል በመልካም እስካዘዘ ድሚስ ለሱ መስማት እና መታዘዝ አለ ይላሉ፡፡ ኢኜዋንን ዹመሰሉ ዚጥመት ቡድኖቜ እነሱ ዚሚፈልጉት ሲነግስ መስማት እና መታዘዝ አለብን እሱን መቃወም ክልክል ነው ይላሉ፡፡ እነሱ ዚማይፈልጉት ሲሆን ስሙን ያጠፉታል፡፡ በሰይጣናዊዉ አልጀዚራ ጣቢያ቞ው ህዝብ እንዲያምፅበት ይቀሰቅሳሉ፡፡
አላህ ሙስሊም መሪዎቜን በጠቅላላ ባሉበት ይጠብቃ቞ው፡፡ ህዝባ቞ውንም መሪዎቹንም አላህ ለመልካሙ ይለግሳ቞ው፡፡ አላህ በመሪዎቹ መካኚልም ይሁን በህዝባ቞ው መካኚል መስማማትን ይለግሳ቞ው፡፡
ኢኜዋኖቜ ተንቅቶባቜኋል፡፡
Forwarded from SadatKemal Abu Meryem
ነብዩ ï·º “ዹወር አበባ ላይ ያለቜን ሎት ወይም ደግሞ ሎትን በፊንጢጣዋ በኩል ዚተገናኘ፣ ወይም ኹጠንቋይ ዘንድ ሄዶ በሚናገሹው ያመነ ሰው በሙሐመድ ላይ በተወሹደው ክዷል” ብለዋል፡፡ አልባኒ ሶሒሕ ብለውታል፡፡ [ሶሒሑ አትተርጊብ ወትተርሂብ፡ 2433]
Forwarded from SadatKemal Abu Meryem
ጠያቂፊ ነሺዳን ኚዚት አመጣቜሁት?
እነርሱፊ ሚሱል(ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ሀሳን ኢብኑ ሳቢት ዚሚባል ገጣሚ ነበራ቞ው እኮ
ጠያቂፊ ሀሳን ኢብኑ ሳቢት እንደናንተ ድምፁን ለማሳመር እንደ ሎት ያምጥ ነበር? ቅላፄስ ነበሹው? ክሊፕስ ይሰራ ነበር? ሚመዳንን እዚጠበቀ በግጥሙ ሶሀቊቜን ኹቁርአን ያሰናክል ነበር? ሱሪውንስ ጎታቜ ነበር? ያጚበጭብስ ነበር? ሱና ላይ ዹሚገኙ ወንድሞቹን በነገር ይወጋ ነበር? ሶሀቊቜስ ልጆቻ቞ውን በሀሳን ግጥም ያንፁ ነበር? በዚትያትር ቀቱስ ያስመርቁ ነበር?
እነርሱፊ ኡመቱ አንድ እንዳይሆን ለምን እንቅፋት ትሆናላቹ?
ጠያቂፊ ዚሚሱል ሱንና ኚእናንተ ጋር ኚለያዚን አዎ አንድ አንሆንም።
By አብጀር አስሀማ ንጉስ አርማ
Forwarded from SadatKemal Abu Meryem
ጫት ዚዱኣ መሳሪያም ዚእስልምና አካል አይደለም፡፡
ያ ምርጡ ዚነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ዚመጡበት ውብ ሃይማኖት እስልምና በሰርጎ ገቊቜ ብዙ መጥፎ ነገሮቜን ዚኢስላም አካል አስመስለው ሰግስገውበታል፡፡ ዚኢስላም ምርጥ ሊቃውንትም በዹጊዜው እነዚህ ሰርጎ ገብ እምነቶቜ እና መጥፎ ተግባራት ኚኢስላም አካል አለመሆናቾውን ዹተቃወመ ቢቃወማ቞ውም አብራርተው አስሚድተዋል፡፡
ጫት እንደሚታወቀው ሙስሊሙን አሜመድምዶ ኚጌታው ጋር ያለንም ይሁን ኚፍጡራን ጋር ያለውን መብት አንድ ቃሚ እንዲያጓድል ሰበብ ዹሆነ አደገኛ መጥፎ ቅጠል ነው፡፡ አሳዛኙ እውቀት አላቾው ተብለው ሙስሊሙን ኡማ ዹሚቅመው በርትቶ እንዲቅም፣ ዹማይቅመው እንዲቅም ጫትን ዚኢስላም አካል እና ዚዱኣ መሳሪያ አድርገው ዚሚሰብኩ ሆድ አደሩዎቜ አሉ፡፡ አንዳንዶቹ በመንዙማ቞ው፣ ሌላኛዎቹ ባገኙት መድሚክ ላይ ጫትን እንደጥሩ ነገር ለሙስሊሙ ያስተዋውቃሉ፡፡ ሙስሊሞቜ ሊሚዱ ዚሚገባ቞ው ጫት በጣም አደገኛ ነው፡፡ ይህም በተግባር ዹምናዹው ዚት ይደርሳሉ ዚተባሉ ትዳሮቜ ሲበተኑ፣ ዚት ይደርሳሉ ዚተባሉ ወንድም እና እህቶቜ ተበለሻሜታ ማዚታቜን ኹበቂ በላይ ማስሚጃ ነው፡፡
በመንዙማዎቜ ላይ ስለ ጫት ኚተሰበኩ አደገኛ ስንኞቜ ውስጥ ዚሚኚተሉት ይገኙበታል፡፡
- “ጁሉሱ ሰኣቲን ጥቂት ቃቅምና (ጫት ቃምና ትንሜ ተቀመጥ)
ንገሹው ለመውላህ እበሩ ቁምና”
- “እነሱ ይበራሉ በመቶ ሃምሳ ጀት፣ እኛ ቀደም ናቾው በአንድ ዘርባ ጫት”
- “ፍዹል ቅጠል በልታ ትወልዳለቜ መንታ፣
መቌም እርባን ዹለው በጫት ዚተመታ”
- “ዝናቡ ዘነበ ጫቱ ለመለመ፣ ዹሚቅመው ቢያገኝ እያጉሚመሚመ”
- ኹ አስር ሺህ መትሚዚስ አጥምዶ ኚቆመ፣
ኚሺህ ፈሹሰኛ ተባብሮ ለቆመ፣
ይበልጣል ደግበል አጥብቆ ዚቃመ፣
ጠላቱንም ጎድቶ ወዳጁን ጠቀመ፡፡
ዹአላህ ባሪያዎቜ ሆይ! አላህ በዚህ ሱስ ዚተያዙትን በጠቅላላ እንዲያወጣ቞ው ዱኣ እና ምክር አይለያ቞ው፡፡ ጫት ዚምትቅሙ ወንድም እና እህቶቜ ሆይ! አላህ ዹውመል ቂያማ ጊዜያቜንን በምን እንዳሳለፍነው ይጠይቀናል፡፡ ኹዚህ ጊዜን እና ስብእናን ኚሚገድል እርኩስ ቅጠል አላህን ለምናቜሁ ለእሱ ስትሉ አቁሙ፡፡
Forwarded from SadatKemal Abu Meryem
April the fool?
ማንቂያ ደውል! እስኚመቌ ዲንን መቃሹን?
ዚነብዩን (ï·º) ቃል ኚነፍሶት፣ ኚጓደኞ቟ት እና ኹማንም በላይ ያስበልጣሉ ወይንስ አያስበልጡም?
ነብዩ (ï·º) “ለቀልድም ብሎ መዋሞት አይቻልም” ይሉናል፡፡
ዛሬ ዛሬ ፈሹንጅ ዚሰራውን ሁሉ መስራት ዹሚፈልግ አለ፡፡ ዹአላህ ባሪያዎቜ ሆይ! ሰውን ለማስደንገጥ፣ ያልሞተውን ሞተ፣ ያልተገጚውን ተገጚ፣ ያልደሚሰውን ደሹሰ ብሎ ሰዎቜን ማስደንገጥ ዚኢስላም አካል አይደለም፡፡ ኢስላም አይደለም ለማስደንገጥ ለቀልድ መዋሞትን ኚልክሏል፡፡ እባካቜሁ እጅ እንስጥ ሙሉ ለሙሉ ኚእዚህ እርኩስ ኩሚጃ እንራቅ፡፡ ኢስላም ሙሉ ነው፡፡ ኹፈሹንጅ መኮሚጅ አይፈልግም፡፡
ዹአላህ ሰላት እና ሰላም በነብዩ ሙሐመድ፣ በቀተሰቊቻ቞ው፣ በባልደሚባዎቻ቞ው እና ሀቅን በተኹተለ ላይ ሁሉ ይሁን፡፡
Forwarded from SadatKemal Abu Meryem
አምልኮ ለአላህ ብቻ ዚተገባ ነው።
ነብዩ (ï·º) ዹአላህ ባሪያው እና መልክተኛው ና቞ው። ኚአምልኮ ምንም አይገባ቞ውም።
ነብዩ (ﷺ) ማለት፡-
ይታመማሉ፡- ነብዩ ሙሐመድ (ï·º) ብዙ ጊዜ ታመው ዚነበሩባ቞ው ክስተቶቜ ነበሩ። ሞት አፋፍ ላይ ሆነውም ኚባድ ትኩሳት በሜታ አጋጥሟ቞ው ነበር። አምልኮ በብ቞ኝነት ዚሚገባው ጌታቜን ግን ዚታመመን ሁሉ ዚሚያድነው እሱ ብቻ ነው።

ይሚሳሉ፡-
ነብዩ (ï·º) እንዲህ ይላሉ “እናንተ እንደምትሚሱት እኔም እሚሳለሁ። ስሚሳ አስታወሱኝ።” አምልኮ በብ቞ኝነት ዚሚገባው ጌታቜን አላህ ግን ምንንም ነገር አይሚሳም።

ይራባሉ፡-
ነብዩ (ï·º) በአንድ አጋጣሚ እሳ቞ው፣ አቡበክር እና ኡመሚ (ሚድዚላሁ አንሁማ) ተርበው ነበር። አምልኮ በብ቞ኝነት ዚሚገባው ጌታቜን አላህ ግን ዚሚመግብ እና ዚማይመገብ ነው።

ይተኛሉ፡-
ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እንቅልፍ ወስዷ቞ው ፈጅር ሰላት አምልጧቾው ያውቃሉ። አምልኮ በብ቞ኝነት ዚሚገባው ጌታቜን አላህ ግን አያንጎላጅም አይተኛም።

ሞተዋል፡-
ነብዩ ሙሐመድ (ï·º) በሚቢአል አወል 12፣ ሰኞ ቀን ሞተዋል። በብ቞ኝነት አምልኮ ዚሚገባው ጌታቜን ግን ህያው እና ዚማይሞት ነው። ኚነብያት ቀጥሎ ምርጥ ሰው ዹሆነው አቡበክር ሲዲቅ (ሚድዚላሁ አንሁ) ዹአላህ መልክተኛ (ï·º) ዚሞቱ ጊዜ እንዲህ ብሏል “ሙሐመድን ዚሚያመልክ ኹነበሹ ሙሐመድ በእርግጥ ሞቷል። አላህን ዚሚያመልክ አላህ ህያው እና ዚማይሞት ነው።”

ሰው ና቞ው፡-
አንዳንድ አላዋቂዎቜ እንደሚሉት ብርሃን ወይንም ኚብርሀን ዚተፈጠሩ አይደሉም። ኚአባታ቞ው አብደላህ እና ኚእናታ቞ው አሚና ዚተወለዱ ሰው ና቞ው። አምልኮ በብ቞ኝነት ዚሚገባው ጌታቜን አላህ አልተወለደም።

አግብተዋል ወልደዋል፡-
ነብዩ ሙሐመድ (ï·º) አግብተው 7 ልጆቜ ወልደዋል። አምልኮ በብ቞ኝነት ዚሚገባው ጌታቜን አላህ ደግሞ ሚስት ዚለውም። አምልኮ በብ቞ኝነት ዚሚገባው ጌታቜን አላህ አልተወለደም።

ፍጡር ና቞ው፡-
ፈጣሪ ብ቞ኛው አንድ አምላክ አላህ ሲሆን ኚእርሱ ውጭ ያሉት በጠቅላላ ፍጡር ና቞ው። አምልኮም ዚሚገባው ለብ቞ኛው ፈጣሪያቜን አላህ ብቻ እና ብቻ ነው።

ይህን በግልፅ ማስቀመጥ ያስፈለገበት ምክንያት ብዙ ሰው ለአላህ ብቻ ዚሚገባውን አምልኮ ለነብዩ ሙሐመድ (ï·º) አሳልፎ ሲሰጥ ይታያል።

ለምሳሌ
- ኹአላህ ውጭ እሳ቞ውን “ነብዩ ልጅ ስጡን” በማለት ዹሚለምኑ አሉ፣
- ኹአላህ ውጭ “ነብዩ ያለፈውን እና መጪ ወንጀላቜንን ምሹውናል” ያለም አለ፣
- “መገን ነቢ ዹሁሉ ቀላቢ” ዹሚሉም አሉ፣
- “ኹዝ ቢዚዲ ያሚሱለላህ። አጊስና ያሚሱለላህ (እጄን ያዙኝ ያ አላህ መልክተኛ ሆይ! እርዱን ካለንበት ጭንቅ አውጡን አንቱ ዹአላህ መልክተኛ ሆይ!)” ዹሚሉም አሉ፣
- “ያቀመሚል መካ አሰላሙ አለይካ . ልቀ ባንቱ በእርሶ ተመካ” ዹሚልም አለ፣
- “አብሜር ወንድሜ ግባ በቶሎ፣ ምን ነው ያፈሚው ያ ነቢ ብሎ።” እና ዚመሳሰለውን እያሉ ዹአላህን ብ቞ኛ መብት ለነብዩ ሙሐመድ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ዚሚሰጡ አሉ።

ይህ በእርግጥ ሺርክ ነው። አምልኮ ዚሚገባው ለብ቞ኛው ፈጣሪ አላህ ብቻ እና ብቻ ነው። ነብዩ ሙሐመድ (ï·º) እንደ ሌሎቜ ነብያቶቜ ሁሉ ይዘውት ዚመጡት መልእክት “አላህን በብ቞ኝነት እንድናመልክ። ኚእርሱ ውጭ በሚመለኩት በጠቅላላ እንድንክድ ነው።”

ነብዚላህ ኢሳን (አለይሂ ሰላም) ነብይ እና ኹ5 ዚቁርጠኝነት ባለቀት መልክተኞቜ ውስጥ ኹመሆኑ ጋር ምንም አምልኮ አይገባውም ብለን አፋቜንን ሞልተን እንናገራለን። ምክንያቱም ውዱ ዹአላህ ባሪያና መልክተኛ ኢሳ (አለይሂ ሰላም) ኹአላህ ዹተላኹውን መልእክት ማድሚስ እንጂ ኹአላህ ኚጌትነትም ይሁን ኚአምላክነት ምንም ድርሻ ዚለውም፣ ሞሪካም አይደለም፣ ሚዳትም አይደለም፣ አላህ ኹፈቀደ በኋላ ቢሆን እንጂ አያማልድም።
ልክ እንደዚሁ ነብዩ (ï·º) ዹአላህ መልክተኛ እና ባሪያው ና቞ው። ኹአላህ ዚተላኩትን መልእክት ማድሚስ እንጂ ኹአላህ ኚጌትነትም ይሁን ኚአምላክነት ምንም ድርሻ ዚላ቞ውም፣ ሞሪካም አይደሉም፣ ሚዳትም አይደሉም፣ አላህ ኹፈቀደ በኋላ ቢሆን እንጂ አያማልዱም።
አላህ ሆይ! በነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ላይ ድንበር ኹማለፍ ጠብቀን። ሱና቞ውን እስኚለተሞታቜን ዹምንኹተል አድርገን።
Forwarded from SadatKemal Abu Meryem
By Ibnu Munewor
ለአስተዋዮቜ ብቻ!! [ቁጥር ①]
አቡ ዑሥማን አስሷቡኒ (373 ዓ.ሂ.) ሹሒመሁላህ ዚሰለፎቜን መዝሀብ ሲገልፁ እንዲህ ይላሉ፡-
“ዚቢድዐ ሰዎቜን በመጫን፣ በማዋሚድ፣ በማራቅ፣ ኚነሱም፣ እነሱን ኚመጎዳኘትም፣ እነሱ ጋር ኹመኗኗር በመራቅም #ተስማምተዋል፡፡ እነሱን በመራቅና በማኩሚፍ ወደ አላህ ዐዘ ወጀል በመቃሚብም እንዲሁ (ተስማምተዋል)፡፡” [ዐቂደቱ ሰለፍ ወአስሓቢል ሐዲሥ፡ 113]
በሙብተዲዖቜ ላይ ዚተንፀባሚቁ ዚሰለፎቜ ጠንካራ አቋሞቜን አልፎ አልፎ ዚተኚሰቱ ነጠላ ክስተቶቜ ብቻ እያስመሰሉ ለሚያቀርቡ አካላት!
አሁን ይሄ ሷቡኒ ያሰፈሩት መልእክት ዚአንድና ዚሁለት ሰው ነጠላ ክስተት ነው ወይስ ዚሰለፎቜን ኢጅማዕ ዹሚገልፅ ነው?! አላህ ማስተዋሉን ያድለን።
አንዳንዶቜ ሳይነቁ ዹነቁ እዚመሰላ቞ው ስለሆነ እንዲህ አይነት ማስሚጃዎቜን በሰፊው ልናዳርስ ይገባል።
Forwarded from SadatKemal Abu Meryem
ለአስተዋዮቜ ብቻ!! [ቁጥር ②]
ኢብኑ ቀይም አልጀውዚያ (751 ሂ) ሹሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ፡- “ቀደምቶቜና ታላላቅ ኢማሞቜ በቢድዐ ላይ ያላ቞ው ተቃውሞ ዹኹፋ ነበር፡፡ በዹአፅናፉ በቢድዐ ሰዎቜ ላይ ጩኞዋል፡፡ ፈተናቾውንም በኚባዱ አስጠንቅቀዋል፡፡ በዚህ ላይ አስቀያሚ ወንጀሎቜን፣ በደሎቜና ግፎቜን ኚሚቃወሙት በላይ ጫፍ ዹደሹሰ ተቃውሞ አሰምተዋል፡፡ ይህ ዚሆነበት ምክንያት ዚቢድዐ ጉዳት፣ ዚዲን አፍራሜነቷ እና ተፃራሪነቷ ዹኹፋ ስለሆነ ነው፡፡” [መዳሪጁ ሳሊኪን፡ 1/378]
በሙብተዲዖቜ ላይ ዚተንፀባሚቁ ዚሰለፎቜ ጠንካራ አቋሞቜን አልፎ አልፎ ዚተኚሰቱ ነጠላ ክስተቶቜ ብቻ እያስመሰሉ ለሚያቀርቡ አካላት:–
አሁን ይሄ ኢብኑል ቀይም ያቀሚቡት ሐሳብ ዚአንድና ዚሁለት ሰው ነጠላ ክስተት ነው ወይስ ባጠቃላይ ዚሰለፎቜና ቀደምት ምሁራን አቋም ነው?! ኚስሜት ነፃ ሆነን እናስተውል።
አንዳንዶቜ ሳይነቁ ዹነቁ እዚመሰላ቞ው ስለሆነ እንዲህ አይነት ማስሚጃዎቜን በሰፊው ልናዳርስ ይገባል።
By Ibnu Munewor
Forwarded from SadatKemal Abu Meryem
ኹሰላማዊ ሰልፍ በፊት እና በኋላ!
******************************
አላህ ሆይ! በሐቅ ላይ አጜናን፡፡

አለም ላይ ኹ 6 እና 7 አመት በፊት ስንት “ሰላማዊ ሰልፍ ሀራም ነውፀ ሰላማዊ ሰልፍ ዚሙስሊሞቜን ደም ያስፈስሳል፣ ሰላማዊ ሰልፍ ዚካፊር ሱና ነው፣ ሰላማዊ ሰልፍ ዚሱና ሰዎቜ አካሄድ አይደለም፣ ሰላማዊ ሰልፍ ጉዳት እንጂ ምንም ጥቅም ዹለውም” ሲሉ ዚነበሩ በጣም ብዙ ና቞ው፡፡

ኹዛም ዹፈተናው ጊዜ መጣና ቱኒስያ ላይ (ይህ ስሙ ብቻ) ሰላማዊ ሰልፉ በመባል ዚሚታወቀው ዚጥፋት ሰልፍ ሲጀመር በዹአለሙ ይህን ፈተና ትናንት ሲቃወሙ እንዳልነበር ዛሬ እጃ቞ውን ኹተው በንግግር በመደገፍ፣ እራሳ቞ው በመውጣት፣ ሰልፉን ዚወጡትን ሰዎቜ በመደገፍ፣ ሰልፉን ዚሚቃወሙትን ሰዎቜ በመቃወም እና በመተ቞ት ተምቊራጚቁበት፡፡

ይህ ሁሉ ሲሆን ዹሐቅ ሰዎቜ ድሮ ዚሚያውቁት ሐቅ ላይ በአላህ ፍቃድ እና እገዛ ጞኑ፡፡

እነዚህ በሐቅ ላይ መጜናት ያቃታ቞ው ስሜታ቞ውን ተኚታይ ዹሆኑ ዚፊትናው ተሳታፊዎቜ፣ ዚፊትናው ቀስቃሟቜ አለም ላይ ሙስሊሞቜ ላይ ዹሚኹተለው ሁሉ ጉዳት ሲደርስ ምን ይሰማቾው?
- አደለም ቜግሩ ሊወገድ ሙስሊሞቜ ላይ ጭራሜ ነገሮቜ ኚብደው፣
- ሙስሊሙ ክብሩ ተዋርዶ፣
- ሎቶቜ ሂጃባ቞ው ተገፎ እና ተደፍሚው፣
- ህፃናት እና ንጹሀን ተገድለው፣
- ስንቶቜ ዚአካል ጉዳተኛ ሆነው፣
- ልጆቜ ዚቲም ሆነው፣
- ሰላም ጠፍቶ፣
- ሙስሊሞቜ ለስደት ተዳርገው፣
- አገራ቞ው ዚጠላት መጫወቻ ሆና፣
- ገንዘባ቞ው ተዘርፎ

.
እና ዚመሳሰለው .
ታድያ እነዚህ በሐቅ ላይ ሳይፀኑ እንደ አዚሩ ፀባይ ዚሚቀያዚሩ ሰዎቜ አላህ ፊት እጃ቞ው ላሚፈበት ፈተና እንደማይጠዚቁ ምን አሳወቃ቞ው?
አያፍሩም መቃወም ባለባ቞ው ቊታ ዝም ብለው፣ ሰውን አፋቾውን ሞልተው ቀስቅሰው፣ ዹሰላማዊ ሰልፍ ተጣሪዎቜን አግዘው፣ በሰላማዊ ሰልፍ ቀስቃሟቜ ላይ መልስ ዚሚሰጡትን በመቃወም ዚሚያደርጉትን ዚጥፋት ጉዞ “ጥቅም እና ጉዳትን ማመዛዘን” ሲሉ ይጠሩታል፡፡ ጥቅም እና ጉዳት በቁርኣን እና በሀዲስ እንጂ በሌላ አይመዘንም፡፡ እውነታው ግን እስቲ ያመጡትን ጥቅም ያሳዩን? ኹላይ ዹዘሹዘርናቾው ሁሉ ጉዳቶቜ ና቞ው፡፡
ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂኡን፡፡
አላህ እንዲህ ይላል
قُلْ هَلْ نُنَؚِّ؊ُكُم ؚِٱلْأَخْسَرِينَ أَعْمَٰلًا
“በሥራዎቜ በጣም ኚሳሪዎቹን እንንገራቜሁን?” በላ቞ው፡፡
ٱلَّذِينَ ضَلَّ سَعْيُهُمْ فِى ٱلْحَيَوٰةِ ٱلدُّنْيَا وَهُمْ يَحْسَُؚونَ أَنَّهُمْ يُحْسِنُونَ صُنْعًا
እነዚያ እነሱ ሥራን ዚሚያሳምሩ ዚሚመስላ቞ው ሲሆኑ በቅርቢቱ ሕይወት ሥራ቞ው ዚጠፋባ቞ው ና቞ው፡፡

እውቀት ማለት ኹፈተና በፊት ያወቁትን በፈተና ወቅት ዚሚተገብሩት እንጂ እንደ አዚሩ ፀባይ ዚሚቀያዚሩበት አይደለም፡፡
ዹአላህ ባሪያዎቜ ሆይ! አብደላህ ኢብን መስኡድ (ሚድዚላሁ አንሁ) እንዲህ ይላል “መኹተል ዹፈለገ ዚሞቱትን (ዚሰሃባዎቜ) መንገድ ይኚተል፡፡ በህይወት ያለ ፈተና አይታመንለትምና”፡፡ እኛ ልንኹተል ዚሚገባው እነዛ በትክክለኛ እምነታ቞ው ጌታ቞ውን ዚተገናኙትን ዚሰሃባዎቜ እና ዹሰለፉነ ሷሊሂንን መንገድ እና እነሱን በበጎ ዹተኹተሏቾውን ብቻ እና ብቻ ነው፡፡ ሰላማዊ ሰልፍ በመምጣቱ ምንም ዹምንቀይሹው አቋም ዚለም፡፡ ሠዎቜ በሃቅ ይለካሉ ሃቅ በሠዎቜ አይለካም፡፡
አላህ ሆይ! በሐቅ ላይ አፅናን፣ በዛውም መንገድ ላይ ግደለን፡፡
ዹአላህ ሰላት እና ሰላም በነብዩ ሙሐመድ፣ በባለቀቶቻ቞ው፣ በባልደሚባዎቻ቞ው እና ሀቅን በተኹተለ ላይ ሁሉ ይሁን፡፡
Forwarded from SadatKemal Abu Meryem
ወፍ ኚአምሳያዎቿ ጋር ታርፋለቜ (ዘመድ ኚዘመዱ .....)

ያሲን ኑሩ ኹዚህ ጠሞ አጥማሚ ኢኜዋኒ ዩሱፍ አልቀርዳዊ ጋር ምን ፈልጎ ነው አብሮት ፎቶ ዚሚነሳው?
ዩሱፍ አልቀርዳዊን ለማታውቁት ዚሚኚተሉት ጥመቶቜን ዹተሾኹመ ሰው ነው፡፡

• ዚኩፍር ንግግሩ፡- ዹጁምዐ ሁለተኛ ኹጥባ ላይ ዹሚኹተለውን ተናግሯል ‹‹ኹጥባዬን ጚርሌ ኹመውሹዮ በፊት ትንሜ ስለ እስራኀል ምርጫ መናገር እፈልጋለሁ፡፡ አሚቡቹ በጠቅላላ ነዳህ ጲሪዝ ያሞንፋል ብለው ተስፋ቞ውን ጥለው ነበርፀ ነገር ግን ተሞነፈ፡፡ ኚእስራኀል ዚምንወድላትም ይህንን ነው፡፡ ዚእኛም ሀገር እነደዚህቜ አገር እንድትሆን እንመኛለን እንፈልጋለን፡፡ በጥቂት ሰዎቜ አማካኝነት ሲመራ ዹነበሹው ስልጣኑን አጥቷል፡፡ አገራቜን ላይ እንደለመድነው 94% ወይንም 95% (ድምፅ) አይደለም ነገር ግን 99% (አዎን 99%ፀ ምንድን ነው ይሄ?) አላህ ለሰው ልጆቜ እራሱን ተመራጭ አድርጎ ቢያቀርብ ይህንን ያህል ድምፅ አያገኝም ፡፡ይሄ (አሚብ አገር ላይ ዹምናዹው ምርጫ) ውሞት ማጭበርበር እና ዚመሳሰሉት እንጂ ሌላ አይደለም፡፡ እስራኀልን እሰዚው እንላታለን››፡፡ ምድር በዚህ ዚኩፍር ንግግር አትሰነጠቅምን? ለሞይኜ ኢሰይሚን (አላህ ይዘንላቾውና) ይህ ቃል በድምፅ ተኚፍቶላ቞ው ኹሰሙ በኋላ ዹሚኹተለውን ተናገሩ ‹‹በአላህ እጠበቃለሁ፡፡ ይህ ሰው መቶበት ግድ ይለዋልፀ እምቢ ካለ እንደ ሙርተድ (ሀይማኖቱን እንደኚዳ ሰው) ይገደል፡፡ ፍጡራንን ኚፋጣሪ ስላስበለጠ፡፡ ተውበት ካደሚገ አላህ ዚባሪያውን ወንጀል መሀሪ ነውፀ ካልሆነ ውላቱል አምር (ዚሙስሊም መንግስት) አንገቱን (በሰይፍ) ይቀንጥሰው፡፡››

• ‹‹ኚይሁዳዎቜን ጋር ዚእምነት ጊርነት ዹለንም ዚመሬት እንጂ፡፡ ካሃዲያንን ካሃዲያን ስለሆኑ አይደለም ዹምንዋጋቾው መሪታቜንና ቀቶቻቜንን ያላግባብ ስለቀሙን እንጂ›› (አራያህ መፅሄት ቁጥር 4696፣ 24 ሞዕባን 1995 ኢ.አ)፡፡ አላህ እና መልክተኛው ምን እንደሚሉ እንስማ፡፡ ይሁዳዎቜ ኚሰዎቜ ሁሉ ኚነሳራም ለአማኞቜ ጠላትነታ቞ው ዚበሚታ ነው አለህም እንዲህ ይላል ‹‹ለአማኞቜ ኚጠላትነት በኩል ዩሁዳንና ጣዖታዊያንን ታገኛለህ››ሱሚቱል ማኢዳ

• ዘፈንና ሙዚቃን መፍቀዱፀ እንዲያውም ጥሩ ነገር ነው ማለቱን ‹‹አል ሀራም ወል ሀላል›› ‹‹ፈትዋ ሙዐሲራ›› እና በመሳሰሉ መፀሃፎቹ መግለፁ፡፡ እራሱ እንደተናገሚው ‹‹ዚፋይዛ አህመድፀ ሻዲያፀ ኡሙ ኩልሱምፀ ፊሩዝ እና ዚመሳሰሉትን ሎቶቜ ዘፈን መኚታተል ይወድ እንደነበር ጠቅሷለል›› (አራያህ ዚሚባል ዚኳታር መፅሄት ቁጥር 5969 ቀን 19/ ጁማዱል ኡላ 1419 ሂጅሪ)፡፡ ዘፈን ሃራም ለመሆኑ ዚነብያቜን አንድ ሀዲስ ሀቅን ለሚፈልግ ትበቃዋኚቜ ‹‹ዚአላህ መልክተኛ (ሰላትና ሰላም በርሳ቞ው ላይ ይሁንና) ኹኔ ኡመት ሰዎቜ ይመጣሉ ለወንድ ልጅ ሀር ልብስን ዚሚፈቅዱፀ መጠጥን እና ዹሙዚቃ መሳሪያን ዚሚፈቅዱ›› ኢማሙ ቡኻሪ ዘግበውታል፡፡ ዹአላህ ባሪያዎቜ እንደው እናንተው ፍሚዱት፡፡

ኡለማዐል ኢስላም ኚሰሃባዎቜ ጀምሮፀ አቡ ሀኒፋፀ ኢማሙ ማሊክፀ ኢማሙ ሻፊዕፀ ኢማሙ አህመድፀ ሙሀዲስ ቡኻሪፀ ሙስሊም ሁሉም በአንድነት ዘፈንን ኚልክለዋል፡፡
ኢማሙ ማሊክ እንዲህ ይላሉ ‹‹እኛ ጋር ዘፈን ዚሚያዳምጥ ፋሲቅ ነው›› ታላቁ ሰሃባ አብደላህ ኢብን መስዑድ (አላህ መልካም ስራውን ይውደድለትና) እንዲህ ይላል ‹‹ዘፈን ማዳመጥ በቀልብ ኒፋቅን ያበቅላል ውሃ አዝርትን እንደሚያበቅል ሁሉ›› ፡፡ ቃዲ ኢያድ ዚተባሉ ዹማሊክ መዝሃብ ተኚታይ ታላቅ አሊም ዘፈን ሀራም ለመሆኑ ኢጅማዕ ጠቅሰዋል፡፡
ዹሙዚቃ መሳሪያን አስመልክቶ ኢማሙ አህመድና አቡዳውድ ዚዘገቡት ሰሂህ ሀዲስ እንጚምር፡፡ ዹአላህ መልክተኛ (ሰላትና ሰላም በርሳ቞ው ላይ ይሁን) ‹‹አላህ መጠጥንፀ ቁማርንፀ ኚበሮ መምታትን ሀራም አደሚገ›› ብለዋል፡፡

• ዚካቶሊኩ ፓፓስ በሞተ ጊዜ ‹‹አላህ ይማሹው ማለቱ››፡፡ አላህ ግን መልክተኛውንም ሆነ አማኞቜን ለነዛ በኩፍር ላይ ለሞቱ ሰዎቜ ምህሚትን እንዳይጠይቁ አዟል፡፡

• አሚቡ አለም ላይ ዚተነሳውን ዚስንት ሙስሊሞቜ ህይወት ዚጠፋበትን፣ አገር ጥለው ዚተሰደዱበትን፣ ዚጠላት መጫወቻ ዚሆኑበትን፣ ንብሚታ቞ው ዚተዘሚፈበትን ፈተና ቢንዚል በማርኹፍኹፍ ፊትና ሲቀሰቅስ ዹነበሹ ሰው ነው፡፡

ዩሱፍ አልቀርዳዊ ይህንን እና ብዙ መሰል ኚባባድ ስህተቶቜ አሉበት፡፡
ዚዩሱፍ አልቀርዳዊን አጥማሚነት ያላወቃቜሁ ወንድም እና እህቶቜ ተጠንቀቁት፣ ወደ ተውሂድ ሳይሆን ወደ ፖለቲካ እና ወደ ጥመት ዚሚጣራ ዚፊትና ሰው ነው፡፡ አላህ ኹጠሞ አጥማሚዎቜ ይጠብቀን፡፡

ያሲን ኑሩ ኹዚህ በፊትም እንደተናገርነው ወደ ትክክለኛው መንገድ ዚሚጣራ ሰው አይደለም፡፡ ሙስሊሞቜ ኚሱ ሊጠነቀቁ ይገባል፡፡ ‹‹ዚተውሂድ አድማስ›› በተሰኘው መፀሀፉም ላይ ዩሱፍ አል-ቀርዳዊ፣ ሰይድ ቁጡብና ሌሎቜም መንገድ ዚሳቱ ሰዎቜን እንደ ጥሩ አድርጎ ለኢትዬጵያ ሙስሊም ያስተዋወቀ ሰው ነው፡፡ ያሲን ኑሩና ጓደኞቹ ያሉበትን ዚተሳሳተ መንገድ ትተው ወደ አላህ ተመልሰው ዚጥንት ዚጠዋቷን መንገድ መኹተል ይኖርባ቞ዋል፡፡ ይህ እስኪሆን ድሚስ ግን ዚኢትዬጵያ ሙስሊም ኚነሱ እራሱን፣ ቀተሰቊቹን ያስጠነቅቅ ዘንድ እመክራለሁ፡፡ እንደሜታወቀው ሃቅ በሰዎቜ አይለካም፣ ሰዎቜ በሃቅ ይለካሉ እንጂ፡፡

እዚህ ጋር አንዳንድ ወንድሞቜ ዚዩሱፍ አል-ቀርዳዊን ስሀተት ተሚድተናል ግን ለያሲን ኑሩ ለምን በድብቅ አትመክሚውም ይሉ ይሆናል፡፡ መልሱም እሱ ይህን ፎቶ እንደትልቅ ነገር ሲነሳ ኹዚህ ጠሞ አጥማሚ ጋር ብሎም ለኢትዬጵያ ሙስሊም በገሃድ እያስተዋወቀው ይህን ግለሰብ እኔ ለምንድን ነው በድብቅ ዹምመክሹው?
እንዲህ በአደባባይ ዚወጣን ጥመት ማጋለጥ ላይ ሰውዹውን በድብቅ መምኹር ዚሚባል መስፈርት ዚለም፡፡
ያሲን ኑሩ ዚዩሱፍ አል-ቀርዳዊ ስህተቶቜ ተዘርዝሚውለት ሲያበቁ በአደባባይ ሚድያን ተጠቅሞ ዩሱፍ አል-ቀርዳዊ ጥመት ላይ እንደሆነ እና እሱም ቀርዳዊን ለኢትዬጵያ ሙስሊም በማስተዋወቁ ለአላህ ተውበት በማድሚግ ለህዝቡ ደግሞ ኚስህተቱ በመመለስ ሃቁን ግልፅ ሊያደርግ ግድ ይለዋል፡፡ ይህን ሳያደርግ ለቀርዳዊ ወግኖ ጥፋቱን ሞፍኖለት አስተዋውቀዋለሁ ቢል ኚራሱ ጀምሮ ባጠመማ቞ው ሰዎቜ ልክ ወንጀሉን ይሞኚማል፡፡

እኛ ደግሞ እውነት እራሳቜንንና ኡማውን ኚጥመት ለመጠበቅ ኹሆነ ወደ ጥመት ዚሚጣሩ ሰዎቜ መጋለጣ቞ው ሊያሳስበን አይገባም፡፡ እኛ ዘንድ ኹምንምና ኹማንም በላይ ተወዳጅ ሊሆን ዚሚገባው ሃቅ ነው፡፡

አላህ ሆይ ሃቅን በሃቅነቱ አሳዚን ዹምንኹተለውም አድርገን፣ ባጢልን በባጢልነቱ አሳዚን ዹምንርቀውም አድርገን፡፡ ዹአላህ ሰላትና ሰላም በነብዚት ሁሉ መደምደሚያ፣ በባለቀቶቻ቞ው፣ በባልደሚባዎቻ቞ውና ሃቅን በተኹተለ ላይ ሁሉ ይሁን፡፡
Forwarded from SadatKemal Abu Meryem
ስለ ሰሞኑን ኚባድ ብርድ እስልምና ምን ይላል፡፡
ዹአላህ ባርያዎቜ ሆይ! አሁንም አሹፈደም ንሰሃ እንግባ
ኢስላም ዚነብያት ሁሉ ሀይማኖት ነው፡፡ እንደሚታወቀው በሀይለኛ ሙቀት እና በሀይለኛ ብርድ ሰው ተ቞ግሯል፡፡ ይህም ኹመሆኑ ጋር ለአላህ ካጠፋነው ጥፋቶቜ ንሰሀ ኚመግባት ይልቅ በዹዜና አውታሩ “ዹአለም በሚዶ ስለቀለጠ ነው፣ ዛፎቜ በመቆሚጣ቞ው ነው፣ ኩዞን በመሳሳቱ ነው
..” እና ዚመሳሰሉትን ምክንያቶቜ ናቾው እዚተባለ ይለፈፋል፡፡
እስቲ ዚነብያት ሁሉ መደምደሚያ ነብዩ ሙሐመድ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ምን እንደሚሉ እንይ
አቡ ሁሚይራ (ሚድዚላሁ አንሁ) ባስተላለፉት፣ ኡማሙ አል-ቡኻሪ በዘገቡት ትክክለኛ ሀዲስ ላይ ዹአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ
“ጀሀነም (እሳት) ወደ ጌታዋ ስሞታ አቀሚበቜ፡፡ ኹፊሌ ኹፊሌን በላው አለቜ፡፡ አላህ ሁለት ጊዜ እስትንፋስን ፈቀደላት፡፡ አንደኛው በቀዝቃዜ ወራት ሌላኛው ጊዜ በሙቀት ወራት፡፡ በሙቀት ጊዜ ዚምታገኙት ኚባድ ሙቀት እና በቅዝቃዜ ጊዜ ዚምታገኙት ኚባድ ውርጭ (ቅዝቃዜ፣ ቀቅ) (ናቾው)፡፡”
حَدَّثَنَا أَُؚو الْيَمَانِ، أَخَؚْرَنَا ؎ُعَيٌؚْ، عَنِ الزُّهْرِيِّ، قَالَ حَدَّثَنِي أَُؚو سَلَمَةَ ؚْنُ عَؚْدِ الرَّحْمَنِ، أَنَّهُ سَمِعَ أََؚا هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ يَقُولُ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ ا؎ْتَكَتِ النَّارُ إِلَى رَؚِّهَا، فَقَالَتْ رَؚِّ أَكَلَ َؚعْضِي َؚعْضًا، فَأَذِنَ لَهَا ؚِنَفَسَيْنِ نَفَسٍ فِي ال؎ِّتَاءِ وَنَفَسٍ فِي الصَّيْفِ، فَأَ؎َدُّ مَا تَجِدُونَ فِي الْحَرِّ، وَأَ؎َدُّ مَا تَجِدُونَ مِنَ الزَّمْهَرِيرِ ‏"‌‏.‏
ልብ እንበል ኚባዱም ሙቀት እና ኚባዱም ብርድ ዚአዋቂዎቜ ሁሉ አዋቂ፣ ዹአላህን ፈሪዎቜ ሁሉ ፈሪ፣ ዚነብያት ሁሉ መደምደሚያ እንደነገሩን ዹጀሃነም እሳት ዚምትተነፍሰው ሁለት ትንፋሜ ምክንያት ነው፡፡
ሌላው መገንዘብ ያለብን ነገር እስልምና ሙሉ መሆኑን ለማንኛውም አለም ላይ ላለ ክስተት በል እንዲያውም ለሚቀጥለው አለም ጉዳዩቜ፣ ዚሚቀጥለው አለም ላይ ምን እንደሚኚሰት በዝርዝር እና በጥቅል ዹተናገር ዉድ፣ ልዩ፣ ዚማይበሚዝ፣ ዚማይሰሚዝ፣ ዚማይደለዝ፣ ዘመን ዚማያልፍበት ሀይማኖት ነውና አጥብቀን እንያዘው፡፡ ይሀው ተመልኚቱ አኹም “Econmic Crisese” ኢኮኖሚክ ክራይስስ ብለው ሲያወሩ አላህ ጥንትም ዚወለድ መጚሚሻው ይህ መሆኑን ነግሮን ነበር፡፡
ትዳር እንዲመሰሚት እና ኚዝሙት እንድንታቀብ ኚጥንትም ዚነብያት ሁሉ ሀይማኖት መክሮ ነበር፡፡ ግን ይህን አልሰማ ብለው አሁን አለም ላለቜበት ኚባባድ በሜታዎቜ ተዳርገዋል፡፡
በሁሉም ዚህይወት ዘርፍ ላይ ዚጥንት ዚጠዋቱ ኢስላም (ሰለፍያ) በሄደበት መንገድ መሄድ ብቻና ብቻ ነው ዋስትናው፡፡ ሁለት ሃቅ ዚለም፡፡ ሁሉም ሙስሊም ኚጥመት ቡድኖቜ እርቆ ወደ ብ቞ኛዋ አማራጭ እና ሁለተኛ ወደሌላት ሃቅ ጎዳና፣ ሰለፉነ ሷሊሂን ዚተጓዙባት ጎዳና መመለስ ግድ ይለዋል፡፡ አለበለዚያ በሙስሊሙ አለም ላይ እንዳዚነው አሁንም ኚባድ ኪሳራ ይኚሰታል፡፡
ታድያ ምን ይበጀን?
አማኞቜ ወደ ጌታ቞ው በንሰሃ ሊመለሱ፣ ያቜን “ጭማሪ አለን?” ብላ ዚምትጠይቀውን ጀሀነም ኚሷ ጌታቜን እንዲጠብቀን እሱን ዘውትር መለመን ግድ ይለናል፡፡ ዹአላህ ባርያዎቜ ሆይ! አሁንም አሹፈደም ንሰሃ እንግባ፡፡ አላህ እነዚህን ሁሉ ተዓምራት ዚሚያሳዚን በሰጠን አእምሮ ዚሱን ጌትነት፣ በቾኛ ተመላኪነት አውቀን ወደሱ እንድንመለስ ነው፡፡
አላህ ሆይ! ሁሌ ወዳንተ በጞጞት ኚሚመለሱት አድርገን፡፡
Forwarded from SadatKemal Abu Meryem
ትግሬ፣ አማራ፣ ኊሮሞ፣ ጉራጌ፣ ስልጀ፣ ሀደሬ፣ ወለኔ፣ 
 አሚብ፣ ነጭ፣ ጥቁር፣ እና ዚመሳሰለው ሁሉም
ዹዘር ሀሹጋቾውን ወደላይ ሄዶ ሄዶ ኹሰው ልጆቜ አባት ነብዩላህ አደም (አለይሂ ሰላም) ውጭ አይደለም፡፡ አደም ደግሞ ዹተፈጠሹው ኹአፈር ነው፡፡ ኹአፈር ዹተፈጠሹው ዹሰው ልጅ ደግሞ ሲሞት ወደ አፈር ይመለሳል፡፡
ታድያ ለምን ይሆን ዘሩን እንዲህ ዚሚመፃደቅበት እና አንዱ አንዱን ዚሚያንቋሜሜበት?
ዚፍጡራን ሁሉ ፈጣሪ፣ ብ቞ኛው አምላክ አላህ ዹሰው ልጆቜ ዚሚለያዩት ለእርሱ ባላ቞ው ፍራቻ ብቻና ብቻ እንደሆነ እንዲህ ሲል ይነግሚናል፡፡
يَٰٓأَيُّهَا ٱلنَّاسُ إِنَّا خَلَقْنَٰكُم مِّن ذَكَرٍ وَأُنثَىٰ وَجَعَلْنَٰكُمْ ؎ُعُوًؚا وَقََؚآ؊ِلَ لِتَعَارَفُوٓا۟ ۚ إِنَّ أَكْرَمَكُمْ عِندَ ٱللَّهِ أَتْقَىٰكُمْ ۚ إِنَّ ٱللَّهَ عَلِيمٌ خَؚِيرٌ
እናንተ ሰዎቜ ሆይ! እኛ ኚወንድና ኚሎት ፈጠርናቜሁ፡፡ እንድትተዋወቁም ጎሳዎቜና ነገዶቜ አደሚግናቜሁ፡፡ አላህ ዘንድ በላጫቜሁ በጣም አላህን ፈሪያቜሁ ነው፡፡ አላህ ግልጜን ዐዋቂ ውስጥንም ዐዋቂ ነው፡፡
አንድ አምላክ ዘንድ ዹሰው ልጆቜ ዚሚበላለጡት እሱን በመፍራታ቞ው ብቻና ብቻ ነው፡፡
ለአእምሮ ባለቀቶቜ ይህ ትልቅ ትምህርት አለበትና ዘሚኝነትን ሁላቜንም እንራቀው፡፡
ጠለኣል በድሩ አለይና ትክክለኛ ሀዲስ አይደለም፡፡
ሃይማኖታቜን በትክክለኛ ማስሚጃ ላይ ዚተገነባ ነው፡፡
ሞይኜ ሷሊህ አል-ፈውዛን እንዲህ ሲባል ጥያቄ ቀሚበላ቞ው፡፡
ጠያቂ፡- ዚተኚበሩ ሞይኜ አላህ ትክክለኛውን ነገር ይግጠሞትና ዚመዲና ሰዎቜ መልክተኛውን (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ጠለኣል በድሩ አለይና ዹሚለውን ነሺዳ እያሉ ተቀብለዋ቞ዋል ዚሚባለው እውነት ነውን?
(ይህንን ጥያቄ ዚጠዚቅኩት) ይህንን ታሪክ (ቂሳ) ለነሺዳ ማስሚጃ (መሹጃ) ዚሚያደርጉ ሰዎቜ ስላሉ ነው፡፡

ሞይኜ ፈውዛን መልስ፡- ይህቜ ቂሳ (ታሪክ) ትክክለኛ ሆና አልተገኘቜም (አልመጣቜም)፡፡ በውስጧ ትክክለኛ አለመሆኗን ዚሚያመላክት ነገር አለ፡፡ ምክንያቱም (ስንኙ) “ጠለኣል በድሩ አለይና ሚን ሰንዚቲል ወዳእ” ይላል፡፡ ሰንዹተል ወዳእ (ኚመዲና) በመካ አቅጣጫ አይደለም ያለው፡፡ ምክንያቱም መልክተኛው (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ወደ መዲና ዚመጡት በደቡብ አቅጣጫ ነው፡፡ መልክተኛው በሰሜን (አቅጣጫ) አልመጡም በሰንዹተል ወዳእ ሊያልፉ ዘንድ፡፡ ሰንዹተል ወዳእ ለመዲና በሰሜን አቅጣጫ ነው ያለው፡፡ ይሄ ዹማይገናኝ ነገር ነው፡፡

ዚሞይኜ ፈውዛን ንግግር እዚህ ላይ አበቃ፡፡
ሀይማኖታቜን በማስሚጃ ላይ ዚተገነባ ነው፡፡ በኢስላም ግጥም አለ፡፡ ግጥምን ለነሺዳ ማስሚጃ አድርጎ ለማቅሚብ መሞኹር ወይ አላዋቂነት ወይ አውቆ አጥፊነት ነው፡፡ ኡመተል ኢስላም ዹተጠማው ኢስላማዊ ብለው ዚሚጠሩትን ዜማ፣ አዝማቜ፣ ሙዚቃ መሳሪያ ያለው፣ በኮምፒውተር ዹተቀናበሹ ዘፈን ሳይሆን ዚጌታቜንን ቃል ቁርኣን፣ ዹአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ሀዲስ፣ ዚሰሃባዎቜና ፈለጋቾውን ዹተኹተሉ አስተምህሮትን ነው፡፡
እባካቜሁ ቻናል ኚፍታቜሁ ኡማውን በነሺዳ ቀልቡን ዚምታደርቁትና ኚቁርኣን ዚምታዘናጉት ሰዎቜ አላህን ፍሩ፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
በቁድስ ስም መነገድ ይቁም፡፡
ዹአላህን ትእዛዛት ብትፈፅሙ አላህ ይሚዳቜኋል፡፡
አል አቅሷን ማስለቀቅ ዚሚቻለው በአላህ ዲን ላይ በመፅናት ብቻ ነው፡፡
ዛሬ ዛሬ ወደ ዲናቜን እንመለስ ዹሚሉ ሰዎቜ ዹነ አል አቅሷና ዚሌሎቜ ሙስሊሞቜ ጉዳዬቜ ዚማያገቧ቞ው ተደርገው እንዲታዩ ዚጥፋት ተጣሪዎቜ ይፅፋሉ፡፡ ሺርክና ቢድኣ ኚነባለቀቶቹ ማስጠንቀቂያ በተሰጠባ቞ው ቁጥር “ዚቁድስ፣ ዚቊርማ፣ ዚሶሪያ ጉዳይ አያሳስባቜሁም ወይ?” እዚተባለ በነቁድስ ስም ይነገዳል፡፡ እነ ቁድስን ዚጥፋታ቞ው አለመታሚሚያ ሰበብ አድርገው ያቀርቧቿል፡፡ እውነታው ግን ወደ ትክክለኛው ዹአላህ ዲን ሳንመለስ አይደለም አላቅሷን ማስለቀቅ ይባስ መኚራ ውስጥ ነው ዚምንገባው፡፡
ብዙ በአል አቅሷ ስም ዚሚነግዱ ግን አላህ ያዘዘውን ለመፈፀም ዝግጁ ያልሆኑ አሉ፡፡
አላህ እኮ ዹአላህን ህግጋት ብትኚተሉ (ብትፈፅሙ) አላህ ይሚዳቜኋል ሲል ቃል ገብቶልናል፡፡ ኚነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) አስተምህሮት እንደተነገሚን ደጃል ሁሉን እያጠፋ መግደል ዚሚያቅተው ዚእምነት ባለቀት ዹሆነውን ግለሰብ ነው፡፡ ስለዚህ ደጃል ኚባዱ ፈተና ሆኖ ሳ፣ ዚሁዳዎቜ ተኚትለውት ሲያበቁ አብዛኛን ድል አድርጎ መጚሚሻው ሲደርስ ያንን አንድ አማኛ ግለሰብ መግደል ያቅተዋል፡፡ ድል አላህና መልክተኛውን በመታዘዝ ነው፡፡ ውርደት አላህና መልክተኛውን በማመፅ ነው፡፡ ዛሬ አላህን በማመፅ፣ ዹመልክተኛውን ትእዛዝ በመራቅ ድል ይገኛል ዚተባለ ይመስል አላህን እያመፁ ኢስላማዊ ስም ይሰጡታል፡፡
አላህ ካዘነላ቞ው ጥቂቶቜ ውጭ
- ሙስሊም ነኝ እያሉ በታላላቅ ሺርክ ተጥለቅልቀዋል፣
- ቢድኣ ሙስሊም አገራት ላይ ሳይቀር ነግሶ፣
- ዹወላጅ ሀቅ እዚተበደለና እዚተጣሰ፣
- ሰሃባዎቜ እዚተሰደቡና እዚተተቹ፣ ብሎም ሰሃባ ተሰዳቢና ለሰሃባ ተሳዳቢ ጥብቅና ዹሚቆም እንደ አዋቂ እዚተያ፣
- ዝሙት ተስፋፍቶ፣
- ወለድ እዚተበላ፣
- ጀመኣ ሰላት በተለይ ፈጅር አንድ ሰፍ ሁለት ሰፍ እዚተሰገደ (ዹሰላማዊ ሰልፍ ጊዜ አደባባይ ላይ ሚሊዬኖቜ ወጥተው)፣
- ሎቶቜ አላህ ዹሹገመውን ቅንድብ መቀንደብ ማስቀንደብ፣ ዊግ መቀጠል ማስቀጠል፣ ንቅሳት መንቀስ ማስነቀስ እዚፈፀሙ፣
- ኚቀቁርኣን ተርቆ፣
- መጠጥ እዚተጠጣ፣
- አደንዛዡን ጫት እዚተቃመ፣
- ሲጋራ፣ ሺሻ እዚተጚሰ፣
- ለኳስ ሲሉ ወንድ ልጆቜ ጀመኣ ሰላትን እዚተዉ፣
- ሎቶቜ ሙሰልሰል እያሉ ፊልም እያዩ፣
- ኚሀይማኖታዊ እውቀት ተርቆ እና ሌሎቜም 


. መጥፎ ተግባራት እዚተሰሩ 


ቁድስ ልባቜን ውስጥ ናት፣ ቊርማ፣ ዋ ሶሪያ እዚተባለ በስማ቞ው ሶሺያል ሚድያ ላይ ይነገዳል፡፡
አል አቅሷን ትላንት ኚዚሁዳዎቜ እጅ አስለቅቋት ዹነበሹው ኡመር ኢብኑ አል-ኞጣብ (ሚድዚላሁ አንሁ) ነው፡፡ ዛሬም ኡመርን ዚሚሳደቡ ራፊዳ ሺአዎቜ ወይንም ለነሱ ጥብቅና ዚሚቆሙት ኢኜዋኖቜ አያስለቅቋትም፡፡
እስቲ አላህን እንፍራና አላህ ግዎታ ያደሚገብንን ሁላቜንም በነፍስ ወኹፍ እንፈፅም፡፡ ኹኹለኹለን ሁሉ በቁርጥ እንራቅ፡፡ ሰላማዊ ሰልፍ ሲባል ኚሚወጣው ሰው በላይ መስጂዳቜንን ኹፈጅር ሰላት ጀምሮ እናስውበው  .. እና ሌላም ትእዛዛትን መፈፀም ክልኚላዎቜን እንኚልኚል፡፡ ኹዛም አላህ ይሚዳናል፡፡
አላህን እንፍራ ኡመተል ኢስላም በጠቅላላ ወደ አላህ ስንመለስ ሁለት አገር ለስኬት እንበቃለን፡፡ በመጚሚሻም ሙስሊሞቜ በነዚህ ዚሁዳዎቜ ላይ ድልን ይጎናፀፋሉ፡፡ አላህ እውነተኛ ሙስሊም ያድርገን፡፡ አል-ቁድስን፣ በርማን፣ ሶሪያም መላው አለም ላይ ያሉ ሙስሊሞቜን መኚራቜንን ያንሳልን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
አፍሪካ ቲቪ ላይ ማስታወቂያ቞ው ተለቀቀላቾው ስለተባሉት ሩቃ ቀቶቜ ..
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩሕሩሕ እጅግ በጣም አዛኝ፡፡
ይህቜ አጭር ፅሁፍ ዚምትሆነው ሰሞኑን ፌስቡክ ላይ በደንብ ስለ ተራገበው ቲቪ አፍሪካ ላይ ማስተወቂያ቞ው ስለ ተለቀቀላቾው ሩቃ ቀቶቜና ስለሚሰሩት አፀያፊ ተግባር ዚሚጠቅስ ነው፡፡

ወንድም ኢድሪስ ኢብን ኢልያስ በፃፈው ፅሁፍ ላይ አፍሪካ ቲቪ ላይ ማስታወቂያ ኚለቀቁት ሩቃ ቀቶቜ ውስጥ አብዛኛዎቹ እዚህ መጥፎ ተግባራት ላይ ዚተሰማሩ መሆናቾው ማስሚጃ እንዳለ ጥናት እንዳለም ነግሮኛል፡፡

ይህ ኹሆነ እውነታው አፍሪካ ቲቪ ማስታወቂያ ኚለቀቁት አጥፊዎቜ ውስጥ በማስሚጃ ዚተሚጋጋጡትን እዛው ቻናል ላይ እነዚህ ሩቃ ቀቶቜ በዚህ በዚህ ማስሚጃ ሙስሊሞቜን ዚሚጎዳ ይህን ይህን ጥፋት ፈፅመዋል ብሎ በግልፅ ማጋለጥ አለበት፡፡
በዚሁ በሶሺያል ሚድያ ላይም እነዚህ መጥፎ ሩቃ ቀቶቜ ኚትክክለኞቹ ይለዩ ዘንድ በስነስርኣት ሊጋለጡ እና ኡማው ሊጠነቀቃቾው ይገባል፡፡
አፍሪካ ቲቪ መጀመሪያ ላይ ዹነዚህን ሩቃ ቀቶቜ መጥፎ ስራ ሳይውቅ ቀርቶ ሊሆን ይቜላል፡፡ አሁን ግን ጥናት ዚሰሩ ወንጀሎቹን ዚተኚታተሉ ወንድሞቜ ስላሉ ያን ማስሚጃ ይዞ ሙስሊሙን ማህበሚሰብ ይቅርታ ሊጠይቅ፣ ለወደፊቱ እንዲህ አይነት ማስታወቂያዎቜን ኚመስራቱ በፊት ያ ማስታወቂያ እንዲለቀቅለት ዹሚፈልገውን ድርጅት አሰራር ኚሞሪኣ አኳያ ማጥናት አለበት፡፡ እዚህ ጋር “እኛ ማስታወቂ እናግኝ እንጂ ስለሌላው ምን አገባን” ዚሚባል አባባል ዚለም፡፡ ምክንያቱም አፍሪካ ቲቪ እራሱን ዚሀይማኖት ተቋም አድርጎ ስለሚንቀሳቀስ፡፡

እነዚህ ሙስሊሙ ላይ በእምነቱ፣ በክብሩ፣ በገንዘቡ በተለይ ሎት እህቶቻቜን ላይ ዚተጫወቱ ሩቃ ቀቶቜ አፍሪካ ቲቪን ተጠቅመው ማስታወቂያ቞ውን ሹጭተው ህዝብ ዘንድ እንደደሚሱ ሁሉ አፍሪካ ቲቪ አሁንም ስርጭቱን ተጠቅሞ፣ ለሙስሊሙ ማህበሚሰብ ወግኖ፣ ጥቅም ሳያታለው፣ ሀፍሚት ሳይዘው፣ እንዲህ አይነት አውሪዎቜን ማስጠንቀቅም ኚኢስላም ክፍሎቜ ስለሆነ ስማ቞ውን ጠቅሶ ተጠንቀቋቾው ማለት አለበት፡፡

በዚሁ ትክክለኛ ዚሩቃና ዚባህል ህክምና ቀቶቜ ዹምናውቅ ወንድም እና እህቶቜ ለሙስሊሙ ማህበሚሰብ እነዚህ ትክክለኞቹ ጋር እንዲሄዱ መጠቆም አለብን፡፡

ሙስሊሞቜ ሆይ! እራሳቜንን በቁርኣን፣ በሀዲስና ሞሪኣው ባስቀመጣ቞ው ማር ጥቁር አዝሙድ .. በመሳሰሉት ማኹም እንቜላለን፡፡
ኢንሻ አላህ በዚህ በኩል ተኚታታይ ፅሁፎቜ መዘጋጀት ይኖርባ቞ዋለው፡፡
አላህ ዚታመሙ ሙስሊም ወንድም እና እህቶቻቜንን ኚበሜታ቞ው ይፈውሳ቞ው፡፡