Sadat_Text_Posts
10K subscribers
291 photos
8 videos
12 files
378 links
Download Telegram
Forwarded from SadatKemal Abu Meryem
ጥፋታቸውን በዲን ሽፋን ቀብተው ይለቁና ሲጋለጡ እንዲህ ይሉናል
“የሰውን ነውር አትከታተሉ”
እኛም እንዲህ እንላቸዋለን
“ነውር ከሆነ ለምን ለቀቁት?”
ስለዚህ በዲን ስም የሚለቀቅ ጥፋታቸውን ህዝብ ይጠነቀቀው ዘንድ እኛም በአደባባይ እናጋልጠዋለን፡፡ የግል ጉዳይ ከዲን ጋር የማይገናኝ ከሆነ የሙስሊም ነውር ስለሚሸፈን እኛም እንሸፍነዋለን፡፡ የእኛንም አላህ ሸፍኖልናል፡፡ አላህም የሁላችንንም የግል ወንጀል ይሸፍንልን፡፡
Forwarded from SadatKemal Abu Meryem
👆🏻እነሱ ሳይፈልጉ ተከታዬቻቸው ነው ፎቶዋቸውን ፖስት የሚያደርጉት ለሚሉ ወንድም እና እህቶች ማስረጃ ይሆናቸው ዘንድ እና እነሱ እራሳቸው ፎቶዋቸውን ኡምራ ሲያደርጉ፣ ሰደቃ ሲሰጡ እና ሌላም ሲያደርጉ አምነውበት ለመሆኑ ይህችን ማስረጃ እንካችሁ፡፡ አንድ ወንድሜ እንዲህ አለ
አላህ በሀዲሰል ቁድስ እንዲህ አለ፦
«ፆም የእኔ ነው በእርሱም የምመነዳው እኔው ነኝ!»
ይህን ገለፃ ይበልጥ የሚያጠናክረው ነገር ቢኖር ሰዎች ዑምራቸውን እንደሚፖስቱት ሁሉ ፆማቸውን መፖሰት አለመቻላቸው ነው!
ዐጃኢብ!!!!!
Forwarded from SadatKemal Abu Meryem
የኢኽዋኖች ሚዛን?
አሁን ያለው የኳታር መሪ (አላህ ይጠብቀው) አባቱ እና አያቱ?
አሁን ያለው የኳታር መሪ (አላህ ይጠብቀው) አባትየው ከአያትየው በመፈንቅለ መንግስት ስልጣን ሲቀማ ኢኽዋኖች ዝም አሉ፡፡ አሁን ያለው የግብፅ መሪ ሲሲ (አላህ ይጠብቀው) ከሙሐመድ ሙርሲ ስልጣን በመፈንቅለ መንግስት ሲቀማ ኢኽዋኖች ሁሉ ተንጫጩ፡፡
ለምን?
አሁን ያለው የኳታር መሪ (አላህ ይጠብቀው) ከአባቱ ስልጣንን ሲረከብ ኢኽዋኖች ዝም አሉ፣ ጭራሽ አደናነቁት፡፡
ታላቁ ሰሃባ ሙአዊያ ኢብን አቡ ሱፍያን (ረድየላሁ አንሁ) ለልጁ ስልጣን ሲያስተላልፍ የሚከተለውን አሉ “ይሄ በኢስላም መሰረት የለውም” ነው እና የመሳሰለውን አሉ፡፡
ሳውዲዎቹ መሪዎች (አላህ ይጠብቃቸውና) ወንድም ለወንድሙ ወይንም አባት ለልጁ ስልጣን ሲያስረክብ ኢኽዋኖች “ስልጣን በዘር መወራረስ በኢስላም የለም” አሉ፡፡
ለኳታር ሲሆን ዝምታ ለሳውዲ ሲሆን ተቃውሞ የሆነው በምን ምክንያት ነው?
አህሉሱና ወል ጀመኣ ሙስሊም መሪ በሰላምም ይያዝ በሃይል በመልካም እስካዘዘ ድረስ ለሱ መስማት እና መታዘዝ አለ ይላሉ፡፡ ኢኽዋንን የመሰሉ የጥመት ቡድኖች እነሱ የሚፈልጉት ሲነግስ መስማት እና መታዘዝ አለብን እሱን መቃወም ክልክል ነው ይላሉ፡፡ እነሱ የማይፈልጉት ሲሆን ስሙን ያጠፉታል፡፡ በሰይጣናዊዉ አልጀዚራ ጣቢያቸው ህዝብ እንዲያምፅበት ይቀሰቅሳሉ፡፡
አላህ ሙስሊም መሪዎችን በጠቅላላ ባሉበት ይጠብቃቸው፡፡ ህዝባቸውንም መሪዎቹንም አላህ ለመልካሙ ይለግሳቸው፡፡ አላህ በመሪዎቹ መካከልም ይሁን በህዝባቸው መካከል መስማማትን ይለግሳቸው፡፡
ኢኽዋኖች ተንቅቶባችኋል፡፡
Forwarded from SadatKemal Abu Meryem
ነብዩ ﷺ “የወር አበባ ላይ ያለችን ሴት ወይም ደግሞ ሴትን በፊንጢጣዋ በኩል የተገናኘ፣ ወይም ከጠንቋይ ዘንድ ሄዶ በሚናገረው ያመነ ሰው በሙሐመድ ላይ በተወረደው ክዷል” ብለዋል፡፡ አልባኒ ሶሒሕ ብለውታል፡፡ [ሶሒሑ አትተርጊብ ወትተርሂብ፡ 2433]
Forwarded from SadatKemal Abu Meryem
ጠያቂ፦ ነሺዳን ከየት አመጣችሁት?
እነርሱ፦ ረሱል(ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ሀሳን ኢብኑ ሳቢት የሚባል ገጣሚ ነበራቸው እኮ
ጠያቂ፦ ሀሳን ኢብኑ ሳቢት እንደናንተ ድምፁን ለማሳመር እንደ ሴት ያምጥ ነበር? ቅላፄስ ነበረው? ክሊፕስ ይሰራ ነበር? ረመዳንን እየጠበቀ በግጥሙ ሶሀቦችን ከቁርአን ያሰናክል ነበር? ሱሪውንስ ጎታች ነበር? ያጨበጭብስ ነበር? ሱና ላይ የሚገኙ ወንድሞቹን በነገር ይወጋ ነበር? ሶሀቦችስ ልጆቻቸውን በሀሳን ግጥም ያንፁ ነበር? በየትያትር ቤቱስ ያስመርቁ ነበር?
እነርሱ፦ ኡመቱ አንድ እንዳይሆን ለምን እንቅፋት ትሆናላቹ?
ጠያቂ፦ የረሱል ሱንና ከእናንተ ጋር ከለያየን አዎ አንድ አንሆንም።
By አብጀር አስሀማ ንጉስ አርማ
Forwarded from SadatKemal Abu Meryem
ጫት የዱኣ መሳሪያም የእስልምና አካል አይደለም፡፡
ያ ምርጡ የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) የመጡበት ውብ ሃይማኖት እስልምና በሰርጎ ገቦች ብዙ መጥፎ ነገሮችን የኢስላም አካል አስመስለው ሰግስገውበታል፡፡ የኢስላም ምርጥ ሊቃውንትም በየጊዜው እነዚህ ሰርጎ ገብ እምነቶች እና መጥፎ ተግባራት ከኢስላም አካል አለመሆናቸውን የተቃወመ ቢቃወማቸውም አብራርተው አስረድተዋል፡፡
ጫት እንደሚታወቀው ሙስሊሙን አሽመድምዶ ከጌታው ጋር ያለንም ይሁን ከፍጡራን ጋር ያለውን መብት አንድ ቃሚ እንዲያጓድል ሰበብ የሆነ አደገኛ መጥፎ ቅጠል ነው፡፡ አሳዛኙ እውቀት አላቸው ተብለው ሙስሊሙን ኡማ የሚቅመው በርትቶ እንዲቅም፣ የማይቅመው እንዲቅም ጫትን የኢስላም አካል እና የዱኣ መሳሪያ አድርገው የሚሰብኩ ሆድ አደሩዎች አሉ፡፡ አንዳንዶቹ በመንዙማቸው፣ ሌላኛዎቹ ባገኙት መድረክ ላይ ጫትን እንደጥሩ ነገር ለሙስሊሙ ያስተዋውቃሉ፡፡ ሙስሊሞች ሊረዱ የሚገባቸው ጫት በጣም አደገኛ ነው፡፡ ይህም በተግባር የምናየው የት ይደርሳሉ የተባሉ ትዳሮች ሲበተኑ፣ የት ይደርሳሉ የተባሉ ወንድም እና እህቶች ተበለሻሽታ ማየታችን ከበቂ በላይ ማስረጃ ነው፡፡
በመንዙማዎች ላይ ስለ ጫት ከተሰበኩ አደገኛ ስንኞች ውስጥ የሚከተሉት ይገኙበታል፡፡
- “ጁሉሱ ሰኣቲን ጥቂት ቃቅምና (ጫት ቃምና ትንሽ ተቀመጥ)
ንገረው ለመውላህ እበሩ ቁምና”
- “እነሱ ይበራሉ በመቶ ሃምሳ ጀት፣ እኛ ቀደም ናቸው በአንድ ዘርባ ጫት”
- “ፍየል ቅጠል በልታ ትወልዳለች መንታ፣
መቼም እርባን የለው በጫት የተመታ”
- “ዝናቡ ዘነበ ጫቱ ለመለመ፣ የሚቅመው ቢያገኝ እያጉረመረመ”
- ከ አስር ሺህ መትረየስ አጥምዶ ከቆመ፣
ከሺህ ፈረሰኛ ተባብሮ ለቆመ፣
ይበልጣል ደግበል አጥብቆ የቃመ፣
ጠላቱንም ጎድቶ ወዳጁን ጠቀመ፡፡
የአላህ ባሪያዎች ሆይ! አላህ በዚህ ሱስ የተያዙትን በጠቅላላ እንዲያወጣቸው ዱኣ እና ምክር አይለያቸው፡፡ ጫት የምትቅሙ ወንድም እና እህቶች ሆይ! አላህ የውመል ቂያማ ጊዜያችንን በምን እንዳሳለፍነው ይጠይቀናል፡፡ ከዚህ ጊዜን እና ስብእናን ከሚገድል እርኩስ ቅጠል አላህን ለምናችሁ ለእሱ ስትሉ አቁሙ፡፡
Forwarded from SadatKemal Abu Meryem
April the fool?
ማንቂያ ደውል! እስከመቼ ዲንን መቃረን?
የነብዩን (ﷺ) ቃል ከነፍሶት፣ ከጓደኞቾት እና ከማንም በላይ ያስበልጣሉ ወይንስ አያስበልጡም?
ነብዩ (ﷺ) “ለቀልድም ብሎ መዋሸት አይቻልም” ይሉናል፡፡
ዛሬ ዛሬ ፈረንጅ የሰራውን ሁሉ መስራት የሚፈልግ አለ፡፡ የአላህ ባሪያዎች ሆይ! ሰውን ለማስደንገጥ፣ ያልሞተውን ሞተ፣ ያልተገጨውን ተገጨ፣ ያልደረሰውን ደረሰ ብሎ ሰዎችን ማስደንገጥ የኢስላም አካል አይደለም፡፡ ኢስላም አይደለም ለማስደንገጥ ለቀልድ መዋሸትን ከልክሏል፡፡ እባካችሁ እጅ እንስጥ ሙሉ ለሙሉ ከእዚህ እርኩስ ኩረጃ እንራቅ፡፡ ኢስላም ሙሉ ነው፡፡ ከፈረንጅ መኮረጅ አይፈልግም፡፡
የአላህ ሰላት እና ሰላም በነብዩ ሙሐመድ፣ በቤተሰቦቻቸው፣ በባልደረባዎቻቸው እና ሀቅን በተከተለ ላይ ሁሉ ይሁን፡፡
Forwarded from SadatKemal Abu Meryem
አምልኮ ለአላህ ብቻ የተገባ ነው።
ነብዩ (ﷺ) የአላህ ባሪያው እና መልክተኛው ናቸው። ከአምልኮ ምንም አይገባቸውም።
ነብዩ (ﷺ) ማለት፡-
ይታመማሉ፡- ነብዩ ሙሐመድ (ﷺ) ብዙ ጊዜ ታመው የነበሩባቸው ክስተቶች ነበሩ። ሞት አፋፍ ላይ ሆነውም ከባድ ትኩሳት በሽታ አጋጥሟቸው ነበር። አምልኮ በብቸኝነት የሚገባው ጌታችን ግን የታመመን ሁሉ የሚያድነው እሱ ብቻ ነው።

ይረሳሉ፡-
ነብዩ (ﷺ) እንዲህ ይላሉ “እናንተ እንደምትረሱት እኔም እረሳለሁ። ስረሳ አስታወሱኝ።” አምልኮ በብቸኝነት የሚገባው ጌታችን አላህ ግን ምንንም ነገር አይረሳም።

ይራባሉ፡-
ነብዩ (ﷺ) በአንድ አጋጣሚ እሳቸው፣ አቡበክር እና ኡመረ (ረድየላሁ አንሁማ) ተርበው ነበር። አምልኮ በብቸኝነት የሚገባው ጌታችን አላህ ግን የሚመግብ እና የማይመገብ ነው።

ይተኛሉ፡-
ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እንቅልፍ ወስዷቸው ፈጅር ሰላት አምልጧቸው ያውቃሉ። አምልኮ በብቸኝነት የሚገባው ጌታችን አላህ ግን አያንጎላጅም አይተኛም።

ሞተዋል፡-
ነብዩ ሙሐመድ (ﷺ) በረቢአል አወል 12፣ ሰኞ ቀን ሞተዋል። በብቸኝነት አምልኮ የሚገባው ጌታችን ግን ህያው እና የማይሞት ነው። ከነብያት ቀጥሎ ምርጥ ሰው የሆነው አቡበክር ሲዲቅ (ረድየላሁ አንሁ) የአላህ መልክተኛ (ﷺ) የሞቱ ጊዜ እንዲህ ብሏል “ሙሐመድን የሚያመልክ ከነበረ ሙሐመድ በእርግጥ ሞቷል። አላህን የሚያመልክ አላህ ህያው እና የማይሞት ነው።”

ሰው ናቸው፡-
አንዳንድ አላዋቂዎች እንደሚሉት ብርሃን ወይንም ከብርሀን የተፈጠሩ አይደሉም። ከአባታቸው አብደላህ እና ከእናታቸው አሚና የተወለዱ ሰው ናቸው። አምልኮ በብቸኝነት የሚገባው ጌታችን አላህ አልተወለደም።

አግብተዋል ወልደዋል፡-
ነብዩ ሙሐመድ (ﷺ) አግብተው 7 ልጆች ወልደዋል። አምልኮ በብቸኝነት የሚገባው ጌታችን አላህ ደግሞ ሚስት የለውም። አምልኮ በብቸኝነት የሚገባው ጌታችን አላህ አልተወለደም።

ፍጡር ናቸው፡-
ፈጣሪ ብቸኛው አንድ አምላክ አላህ ሲሆን ከእርሱ ውጭ ያሉት በጠቅላላ ፍጡር ናቸው። አምልኮም የሚገባው ለብቸኛው ፈጣሪያችን አላህ ብቻ እና ብቻ ነው።

ይህን በግልፅ ማስቀመጥ ያስፈለገበት ምክንያት ብዙ ሰው ለአላህ ብቻ የሚገባውን አምልኮ ለነብዩ ሙሐመድ (ﷺ) አሳልፎ ሲሰጥ ይታያል።

ለምሳሌ
- ከአላህ ውጭ እሳቸውን “ነብዩ ልጅ ስጡን” በማለት የሚለምኑ አሉ፣
- ከአላህ ውጭ “ነብዩ ያለፈውን እና መጪ ወንጀላችንን ምረውናል” ያለም አለ፣
- “መገን ነቢ የሁሉ ቀላቢ” የሚሉም አሉ፣
- “ኹዝ ቢየዲ ያረሱለላህ። አጊስና ያረሱለላህ (እጄን ያዙኝ ያ አላህ መልክተኛ ሆይ! እርዱን ካለንበት ጭንቅ አውጡን አንቱ የአላህ መልክተኛ ሆይ!)” የሚሉም አሉ፣
- “ያቀመረል መካ አሰላሙ አለይካ…. ልቤ ባንቱ በእርሶ ተመካ” የሚልም አለ፣
- “አብሽር ወንድሜ ግባ በቶሎ፣ ምን ነው ያፈረው ያ ነቢ ብሎ።” እና የመሳሰለውን እያሉ የአላህን ብቸኛ መብት ለነብዩ ሙሐመድ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) የሚሰጡ አሉ።

ይህ በእርግጥ ሺርክ ነው። አምልኮ የሚገባው ለብቸኛው ፈጣሪ አላህ ብቻ እና ብቻ ነው። ነብዩ ሙሐመድ (ﷺ) እንደ ሌሎች ነብያቶች ሁሉ ይዘውት የመጡት መልእክት “አላህን በብቸኝነት እንድናመልክ። ከእርሱ ውጭ በሚመለኩት በጠቅላላ እንድንክድ ነው።”

ነብየላህ ኢሳን (አለይሂ ሰላም) ነብይ እና ከ5 የቁርጠኝነት ባለቤት መልክተኞች ውስጥ ከመሆኑ ጋር ምንም አምልኮ አይገባውም ብለን አፋችንን ሞልተን እንናገራለን። ምክንያቱም ውዱ የአላህ ባሪያና መልክተኛ ኢሳ (አለይሂ ሰላም) ከአላህ የተላከውን መልእክት ማድረስ እንጂ ከአላህ ከጌትነትም ይሁን ከአምላክነት ምንም ድርሻ የለውም፣ ሸሪካም አይደለም፣ ረዳትም አይደለም፣ አላህ ከፈቀደ በኋላ ቢሆን እንጂ አያማልድም።
ልክ እንደዚሁ ነብዩ (ﷺ) የአላህ መልክተኛ እና ባሪያው ናቸው። ከአላህ የተላኩትን መልእክት ማድረስ እንጂ ከአላህ ከጌትነትም ይሁን ከአምላክነት ምንም ድርሻ የላቸውም፣ ሸሪካም አይደሉም፣ ረዳትም አይደሉም፣ አላህ ከፈቀደ በኋላ ቢሆን እንጂ አያማልዱም።
አላህ ሆይ! በነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ላይ ድንበር ከማለፍ ጠብቀን። ሱናቸውን እስከለተሞታችን የምንከተል አድርገን።
Forwarded from SadatKemal Abu Meryem
By Ibnu Munewor
ለአስተዋዮች ብቻ!! [ቁጥር ①]
አቡ ዑሥማን አስሷቡኒ (373 ዓ.ሂ.) ረሒመሁላህ የሰለፎችን መዝሀብ ሲገልፁ እንዲህ ይላሉ፡-
“የቢድዐ ሰዎችን በመጫን፣ በማዋረድ፣ በማራቅ፣ ከነሱም፣ እነሱን ከመጎዳኘትም፣ እነሱ ጋር ከመኗኗር በመራቅም #ተስማምተዋል፡፡ እነሱን በመራቅና በማኩረፍ ወደ አላህ ዐዘ ወጀል በመቃረብም እንዲሁ (ተስማምተዋል)፡፡” [ዐቂደቱ ሰለፍ ወአስሓቢል ሐዲሥ፡ 113]
በሙብተዲዖች ላይ የተንፀባረቁ የሰለፎች ጠንካራ አቋሞችን አልፎ አልፎ የተከሰቱ ነጠላ ክስተቶች ብቻ እያስመሰሉ ለሚያቀርቡ አካላት!
አሁን ይሄ ሷቡኒ ያሰፈሩት መልእክት የአንድና የሁለት ሰው ነጠላ ክስተት ነው ወይስ የሰለፎችን ኢጅማዕ የሚገልፅ ነው?! አላህ ማስተዋሉን ያድለን።
አንዳንዶች ሳይነቁ የነቁ እየመሰላቸው ስለሆነ እንዲህ አይነት ማስረጃዎችን በሰፊው ልናዳርስ ይገባል።
Forwarded from SadatKemal Abu Meryem
ለአስተዋዮች ብቻ!! [ቁጥር ②]
ኢብኑ ቀይም አልጀውዚያ (751 ሂ) ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ፡- “ቀደምቶችና ታላላቅ ኢማሞች በቢድዐ ላይ ያላቸው ተቃውሞ የከፋ ነበር፡፡ በየአፅናፉ በቢድዐ ሰዎች ላይ ጩኸዋል፡፡ ፈተናቸውንም በከባዱ አስጠንቅቀዋል፡፡ በዚህ ላይ አስቀያሚ ወንጀሎችን፣ በደሎችና ግፎችን ከሚቃወሙት በላይ ጫፍ የደረሰ ተቃውሞ አሰምተዋል፡፡ ይህ የሆነበት ምክንያት የቢድዐ ጉዳት፣ የዲን አፍራሽነቷ እና ተፃራሪነቷ የከፋ ስለሆነ ነው፡፡” [መዳሪጁ ሳሊኪን፡ 1/378]
በሙብተዲዖች ላይ የተንፀባረቁ የሰለፎች ጠንካራ አቋሞችን አልፎ አልፎ የተከሰቱ ነጠላ ክስተቶች ብቻ እያስመሰሉ ለሚያቀርቡ አካላት:–
አሁን ይሄ ኢብኑል ቀይም ያቀረቡት ሐሳብ የአንድና የሁለት ሰው ነጠላ ክስተት ነው ወይስ ባጠቃላይ የሰለፎችና ቀደምት ምሁራን አቋም ነው?! ከስሜት ነፃ ሆነን እናስተውል።
አንዳንዶች ሳይነቁ የነቁ እየመሰላቸው ስለሆነ እንዲህ አይነት ማስረጃዎችን በሰፊው ልናዳርስ ይገባል።
By Ibnu Munewor
Forwarded from SadatKemal Abu Meryem
ከሰላማዊ ሰልፍ በፊት እና በኋላ!
******************************
አላህ ሆይ! በሐቅ ላይ አጽናን፡፡

አለም ላይ ከ 6 እና 7 አመት በፊት ስንት “ሰላማዊ ሰልፍ ሀራም ነው፤ ሰላማዊ ሰልፍ የሙስሊሞችን ደም ያስፈስሳል፣ ሰላማዊ ሰልፍ የካፊር ሱና ነው፣ ሰላማዊ ሰልፍ የሱና ሰዎች አካሄድ አይደለም፣ ሰላማዊ ሰልፍ ጉዳት እንጂ ምንም ጥቅም የለውም” ሲሉ የነበሩ በጣም ብዙ ናቸው፡፡

ከዛም የፈተናው ጊዜ መጣና ቱኒስያ ላይ (ይህ ስሙ ብቻ) ሰላማዊ ሰልፉ በመባል የሚታወቀው የጥፋት ሰልፍ ሲጀመር በየአለሙ ይህን ፈተና ትናንት ሲቃወሙ እንዳልነበር ዛሬ እጃቸውን ከተው በንግግር በመደገፍ፣ እራሳቸው በመውጣት፣ ሰልፉን የወጡትን ሰዎች በመደገፍ፣ ሰልፉን የሚቃወሙትን ሰዎች በመቃወም እና በመተቸት ተምቦራጨቁበት፡፡

ይህ ሁሉ ሲሆን የሐቅ ሰዎች ድሮ የሚያውቁት ሐቅ ላይ በአላህ ፍቃድ እና እገዛ ጸኑ፡፡

እነዚህ በሐቅ ላይ መጽናት ያቃታቸው ስሜታቸውን ተከታይ የሆኑ የፊትናው ተሳታፊዎች፣ የፊትናው ቀስቃሾች አለም ላይ ሙስሊሞች ላይ የሚከተለው ሁሉ ጉዳት ሲደርስ ምን ይሰማቸው?
- አደለም ችግሩ ሊወገድ ሙስሊሞች ላይ ጭራሽ ነገሮች ከብደው፣
- ሙስሊሙ ክብሩ ተዋርዶ፣
- ሴቶች ሂጃባቸው ተገፎ እና ተደፍረው፣
- ህፃናት እና ንጹሀን ተገድለው፣
- ስንቶች የአካል ጉዳተኛ ሆነው፣
- ልጆች የቲም ሆነው፣
- ሰላም ጠፍቶ፣
- ሙስሊሞች ለስደት ተዳርገው፣
- አገራቸው የጠላት መጫወቻ ሆና፣
- ገንዘባቸው ተዘርፎ…….
እና የመሳሰለው….
ታድያ እነዚህ በሐቅ ላይ ሳይፀኑ እንደ አየሩ ፀባይ የሚቀያየሩ ሰዎች አላህ ፊት እጃቸው ላረፈበት ፈተና እንደማይጠየቁ ምን አሳወቃቸው?
አያፍሩም መቃወም ባለባቸው ቦታ ዝም ብለው፣ ሰውን አፋቸውን ሞልተው ቀስቅሰው፣ የሰላማዊ ሰልፍ ተጣሪዎችን አግዘው፣ በሰላማዊ ሰልፍ ቀስቃሾች ላይ መልስ የሚሰጡትን በመቃወም የሚያደርጉትን የጥፋት ጉዞ “ጥቅም እና ጉዳትን ማመዛዘን” ሲሉ ይጠሩታል፡፡ ጥቅም እና ጉዳት በቁርኣን እና በሀዲስ እንጂ በሌላ አይመዘንም፡፡ እውነታው ግን እስቲ ያመጡትን ጥቅም ያሳዩን? ከላይ የዘረዘርናቸው ሁሉ ጉዳቶች ናቸው፡፡
ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂኡን፡፡
አላህ እንዲህ ይላል
قُلْ هَلْ نُنَبِّئُكُم بِٱلْأَخْسَرِينَ أَعْمَٰلًا
“በሥራዎች በጣም ከሳሪዎቹን እንንገራችሁን?” በላቸው፡፡
ٱلَّذِينَ ضَلَّ سَعْيُهُمْ فِى ٱلْحَيَوٰةِ ٱلدُّنْيَا وَهُمْ يَحْسَبُونَ أَنَّهُمْ يُحْسِنُونَ صُنْعًا
እነዚያ እነሱ ሥራን የሚያሳምሩ የሚመስላቸው ሲሆኑ በቅርቢቱ ሕይወት ሥራቸው የጠፋባቸው ናቸው፡፡

እውቀት ማለት ከፈተና በፊት ያወቁትን በፈተና ወቅት የሚተገብሩት እንጂ እንደ አየሩ ፀባይ የሚቀያየሩበት አይደለም፡፡
የአላህ ባሪያዎች ሆይ! አብደላህ ኢብን መስኡድ (ረድየላሁ አንሁ) እንዲህ ይላል “መከተል የፈለገ የሞቱትን (የሰሃባዎች) መንገድ ይከተል፡፡ በህይወት ያለ ፈተና አይታመንለትምና”፡፡ እኛ ልንከተል የሚገባው እነዛ በትክክለኛ እምነታቸው ጌታቸውን የተገናኙትን የሰሃባዎች እና የሰለፉነ ሷሊሂንን መንገድ እና እነሱን በበጎ የተከተሏቸውን ብቻ እና ብቻ ነው፡፡ ሰላማዊ ሰልፍ በመምጣቱ ምንም የምንቀይረው አቋም የለም፡፡ ሠዎች በሃቅ ይለካሉ ሃቅ በሠዎች አይለካም፡፡
አላህ ሆይ! በሐቅ ላይ አፅናን፣ በዛውም መንገድ ላይ ግደለን፡፡
የአላህ ሰላት እና ሰላም በነብዩ ሙሐመድ፣ በባለቤቶቻቸው፣ በባልደረባዎቻቸው እና ሀቅን በተከተለ ላይ ሁሉ ይሁን፡፡
Forwarded from SadatKemal Abu Meryem
ወፍ ከአምሳያዎቿ ጋር ታርፋለች (ዘመድ ከዘመዱ .....)

ያሲን ኑሩ ከዚህ ጠሞ አጥማሚ ኢኽዋኒ ዩሱፍ አልቀርዳዊ ጋር ምን ፈልጎ ነው አብሮት ፎቶ የሚነሳው?
ዩሱፍ አልቀርዳዊን ለማታውቁት የሚከተሉት ጥመቶችን የተሸከመ ሰው ነው፡፡

• የኩፍር ንግግሩ፡- የጁምዐ ሁለተኛ ኹጥባ ላይ የሚከተለውን ተናግሯል ‹‹ኹጥባዬን ጨርሼ ከመውረዴ በፊት ትንሽ ስለ እስራኤል ምርጫ መናገር እፈልጋለሁ፡፡ አረቡቹ በጠቅላላ ነዳህ ጲሪዝ ያሸንፋል ብለው ተስፋቸውን ጥለው ነበር፤ ነገር ግን ተሸነፈ፡፡ ከእስራኤል የምንወድላትም ይህንን ነው፡፡ የእኛም ሀገር እነደዚህች አገር እንድትሆን እንመኛለን እንፈልጋለን፡፡ በጥቂት ሰዎች አማካኝነት ሲመራ የነበረው ስልጣኑን አጥቷል፡፡ አገራችን ላይ እንደለመድነው 94% ወይንም 95% (ድምፅ) አይደለም ነገር ግን 99% (አዎን 99%፤ ምንድን ነው ይሄ?) አላህ ለሰው ልጆች እራሱን ተመራጭ አድርጎ ቢያቀርብ ይህንን ያህል ድምፅ አያገኝም ፡፡ይሄ (አረብ አገር ላይ የምናየው ምርጫ) ውሸት ማጭበርበር እና የመሳሰሉት እንጂ ሌላ አይደለም፡፡ እስራኤልን እሰየው እንላታለን››፡፡ ምድር በዚህ የኩፍር ንግግር አትሰነጠቅምን? ለሸይኽ ኢሰይሚን (አላህ ይዘንላቸውና) ይህ ቃል በድምፅ ተከፍቶላቸው ከሰሙ በኋላ የሚከተለውን ተናገሩ ‹‹በአላህ እጠበቃለሁ፡፡ ይህ ሰው መቶበት ግድ ይለዋል፤ እምቢ ካለ እንደ ሙርተድ (ሀይማኖቱን እንደከዳ ሰው) ይገደል፡፡ ፍጡራንን ከፋጣሪ ስላስበለጠ፡፡ ተውበት ካደረገ አላህ የባሪያውን ወንጀል መሀሪ ነው፤ ካልሆነ ውላቱል አምር (የሙስሊም መንግስት) አንገቱን (በሰይፍ) ይቀንጥሰው፡፡››

• ‹‹ከይሁዳዎችን ጋር የእምነት ጦርነት የለንም የመሬት እንጂ፡፡ ካሃዲያንን ካሃዲያን ስለሆኑ አይደለም የምንዋጋቸው መሪታችንና ቤቶቻችንን ያላግባብ ስለቀሙን እንጂ›› (አራያህ መፅሄት ቁጥር 4696፣ 24 ሸዕባን 1995 ኢ.አ)፡፡ አላህ እና መልክተኛው ምን እንደሚሉ እንስማ፡፡ ይሁዳዎች ከሰዎች ሁሉ ከነሳራም ለአማኞች ጠላትነታቸው የበረታ ነው አለህም እንዲህ ይላል ‹‹ለአማኞች ከጠላትነት በኩል ዩሁዳንና ጣዖታዊያንን ታገኛለህ››ሱረቱል ማኢዳ

• ዘፈንና ሙዚቃን መፍቀዱ፤ እንዲያውም ጥሩ ነገር ነው ማለቱን ‹‹አል ሀራም ወል ሀላል›› ‹‹ፈትዋ ሙዐሲራ›› እና በመሳሰሉ መፀሃፎቹ መግለፁ፡፡ እራሱ እንደተናገረው ‹‹የፋይዛ አህመድ፤ ሻዲያ፤ ኡሙ ኩልሱም፤ ፊሩዝ እና የመሳሰሉትን ሴቶች ዘፈን መከታተል ይወድ እንደነበር ጠቅሷለል›› (አራያህ የሚባል የኳታር መፅሄት ቁጥር 5969 ቀን 19/ ጁማዱል ኡላ 1419 ሂጅሪ)፡፡ ዘፈን ሃራም ለመሆኑ የነብያችን አንድ ሀዲስ ሀቅን ለሚፈልግ ትበቃዋከች ‹‹የአላህ መልክተኛ (ሰላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይሁንና) ከኔ ኡመት ሰዎች ይመጣሉ ለወንድ ልጅ ሀር ልብስን የሚፈቅዱ፤ መጠጥን እና የሙዚቃ መሳሪያን የሚፈቅዱ›› ኢማሙ ቡኻሪ ዘግበውታል፡፡ የአላህ ባሪያዎች እንደው እናንተው ፍረዱት፡፡

ኡለማዐል ኢስላም ከሰሃባዎች ጀምሮ፤ አቡ ሀኒፋ፤ ኢማሙ ማሊክ፤ ኢማሙ ሻፊዕ፤ ኢማሙ አህመድ፤ ሙሀዲስ ቡኻሪ፤ ሙስሊም ሁሉም በአንድነት ዘፈንን ከልክለዋል፡፡
ኢማሙ ማሊክ እንዲህ ይላሉ ‹‹እኛ ጋር ዘፈን የሚያዳምጥ ፋሲቅ ነው›› ታላቁ ሰሃባ አብደላህ ኢብን መስዑድ (አላህ መልካም ስራውን ይውደድለትና) እንዲህ ይላል ‹‹ዘፈን ማዳመጥ በቀልብ ኒፋቅን ያበቅላል ውሃ አዝርትን እንደሚያበቅል ሁሉ›› ፡፡ ቃዲ ኢያድ የተባሉ የማሊክ መዝሃብ ተከታይ ታላቅ አሊም ዘፈን ሀራም ለመሆኑ ኢጅማዕ ጠቅሰዋል፡፡
የሙዚቃ መሳሪያን አስመልክቶ ኢማሙ አህመድና አቡዳውድ የዘገቡት ሰሂህ ሀዲስ እንጨምር፡፡ የአላህ መልክተኛ (ሰላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይሁን) ‹‹አላህ መጠጥን፤ ቁማርን፤ ከበሮ መምታትን ሀራም አደረገ›› ብለዋል፡፡

• የካቶሊኩ ፓፓስ በሞተ ጊዜ ‹‹አላህ ይማረው ማለቱ››፡፡ አላህ ግን መልክተኛውንም ሆነ አማኞችን ለነዛ በኩፍር ላይ ለሞቱ ሰዎች ምህረትን እንዳይጠይቁ አዟል፡፡

• አረቡ አለም ላይ የተነሳውን የስንት ሙስሊሞች ህይወት የጠፋበትን፣ አገር ጥለው የተሰደዱበትን፣ የጠላት መጫወቻ የሆኑበትን፣ ንብረታቸው የተዘረፈበትን ፈተና ቢንዚል በማርከፍከፍ ፊትና ሲቀሰቅስ የነበረ ሰው ነው፡፡

ዩሱፍ አልቀርዳዊ ይህንን እና ብዙ መሰል ከባባድ ስህተቶች አሉበት፡፡
የዩሱፍ አልቀርዳዊን አጥማሚነት ያላወቃችሁ ወንድም እና እህቶች ተጠንቀቁት፣ ወደ ተውሂድ ሳይሆን ወደ ፖለቲካ እና ወደ ጥመት የሚጣራ የፊትና ሰው ነው፡፡ አላህ ከጠሞ አጥማሚዎች ይጠብቀን፡፡

ያሲን ኑሩ ከዚህ በፊትም እንደተናገርነው ወደ ትክክለኛው መንገድ የሚጣራ ሰው አይደለም፡፡ ሙስሊሞች ከሱ ሊጠነቀቁ ይገባል፡፡ ‹‹የተውሂድ አድማስ›› በተሰኘው መፀሀፉም ላይ ዩሱፍ አል-ቀርዳዊ፣ ሰይድ ቁጡብና ሌሎችም መንገድ የሳቱ ሰዎችን እንደ ጥሩ አድርጎ ለኢትዬጵያ ሙስሊም ያስተዋወቀ ሰው ነው፡፡ ያሲን ኑሩና ጓደኞቹ ያሉበትን የተሳሳተ መንገድ ትተው ወደ አላህ ተመልሰው የጥንት የጠዋቷን መንገድ መከተል ይኖርባቸዋል፡፡ ይህ እስኪሆን ድረስ ግን የኢትዬጵያ ሙስሊም ከነሱ እራሱን፣ ቤተሰቦቹን ያስጠነቅቅ ዘንድ እመክራለሁ፡፡ እንደሜታወቀው ሃቅ በሰዎች አይለካም፣ ሰዎች በሃቅ ይለካሉ እንጂ፡፡

እዚህ ጋር አንዳንድ ወንድሞች የዩሱፍ አል-ቀርዳዊን ስሀተት ተረድተናል ግን ለያሲን ኑሩ ለምን በድብቅ አትመክረውም ይሉ ይሆናል፡፡ መልሱም እሱ ይህን ፎቶ እንደትልቅ ነገር ሲነሳ ከዚህ ጠሞ አጥማሚ ጋር ብሎም ለኢትዬጵያ ሙስሊም በገሃድ እያስተዋወቀው ይህን ግለሰብ እኔ ለምንድን ነው በድብቅ የምመክረው?
እንዲህ በአደባባይ የወጣን ጥመት ማጋለጥ ላይ ሰውየውን በድብቅ መምከር የሚባል መስፈርት የለም፡፡
ያሲን ኑሩ የዩሱፍ አል-ቀርዳዊ ስህተቶች ተዘርዝረውለት ሲያበቁ በአደባባይ ሚድያን ተጠቅሞ ዩሱፍ አል-ቀርዳዊ ጥመት ላይ እንደሆነ እና እሱም ቀርዳዊን ለኢትዬጵያ ሙስሊም በማስተዋወቁ ለአላህ ተውበት በማድረግ ለህዝቡ ደግሞ ከስህተቱ በመመለስ ሃቁን ግልፅ ሊያደርግ ግድ ይለዋል፡፡ ይህን ሳያደርግ ለቀርዳዊ ወግኖ ጥፋቱን ሸፍኖለት አስተዋውቀዋለሁ ቢል ከራሱ ጀምሮ ባጠመማቸው ሰዎች ልክ ወንጀሉን ይሸከማል፡፡

እኛ ደግሞ እውነት እራሳችንንና ኡማውን ከጥመት ለመጠበቅ ከሆነ ወደ ጥመት የሚጣሩ ሰዎች መጋለጣቸው ሊያሳስበን አይገባም፡፡ እኛ ዘንድ ከምንምና ከማንም በላይ ተወዳጅ ሊሆን የሚገባው ሃቅ ነው፡፡

አላህ ሆይ ሃቅን በሃቅነቱ አሳየን የምንከተለውም አድርገን፣ ባጢልን በባጢልነቱ አሳየን የምንርቀውም አድርገን፡፡ የአላህ ሰላትና ሰላም በነብየት ሁሉ መደምደሚያ፣ በባለቤቶቻቸው፣ በባልደረባዎቻቸውና ሃቅን በተከተለ ላይ ሁሉ ይሁን፡፡
Forwarded from SadatKemal Abu Meryem
ስለ ሰሞኑን ከባድ ብርድ እስልምና ምን ይላል፡፡
የአላህ ባርያዎች ሆይ! አሁንም አረፈደም ንሰሃ እንግባ
ኢስላም የነብያት ሁሉ ሀይማኖት ነው፡፡ እንደሚታወቀው በሀይለኛ ሙቀት እና በሀይለኛ ብርድ ሰው ተቸግሯል፡፡ ይህም ከመሆኑ ጋር ለአላህ ካጠፋነው ጥፋቶች ንሰሀ ከመግባት ይልቅ በየዜና አውታሩ “የአለም በረዶ ስለቀለጠ ነው፣ ዛፎች በመቆረጣቸው ነው፣ ኦዞን በመሳሳቱ ነው…..” እና የመሳሰሉትን ምክንያቶች ናቸው እየተባለ ይለፈፋል፡፡
እስቲ የነብያት ሁሉ መደምደሚያ ነብዩ ሙሐመድ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ምን እንደሚሉ እንይ
አቡ ሁረይራ (ረድየላሁ አንሁ) ባስተላለፉት፣ ኡማሙ አል-ቡኻሪ በዘገቡት ትክክለኛ ሀዲስ ላይ የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ
“ጀሀነም (እሳት) ወደ ጌታዋ ስሞታ አቀረበች፡፡ ከፊሌ ከፊሌን በላው አለች፡፡ አላህ ሁለት ጊዜ እስትንፋስን ፈቀደላት፡፡ አንደኛው በቀዝቃዜ ወራት ሌላኛው ጊዜ በሙቀት ወራት፡፡ በሙቀት ጊዜ የምታገኙት ከባድ ሙቀት እና በቅዝቃዜ ጊዜ የምታገኙት ከባድ ውርጭ (ቅዝቃዜ፣ ቀቅ) (ናቸው)፡፡”
حَدَّثَنَا أَبُو الْيَمَانِ، أَخْبَرَنَا شُعَيْبٌ، عَنِ الزُّهْرِيِّ، قَالَ حَدَّثَنِي أَبُو سَلَمَةَ بْنُ عَبْدِ الرَّحْمَنِ، أَنَّهُ سَمِعَ أَبَا هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ يَقُولُ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ اشْتَكَتِ النَّارُ إِلَى رَبِّهَا، فَقَالَتْ رَبِّ أَكَلَ بَعْضِي بَعْضًا، فَأَذِنَ لَهَا بِنَفَسَيْنِ نَفَسٍ فِي الشِّتَاءِ وَنَفَسٍ فِي الصَّيْفِ، فَأَشَدُّ مَا تَجِدُونَ فِي الْحَرِّ، وَأَشَدُّ مَا تَجِدُونَ مِنَ الزَّمْهَرِيرِ ‏"‌‏.‏
ልብ እንበል ከባዱም ሙቀት እና ከባዱም ብርድ የአዋቂዎች ሁሉ አዋቂ፣ የአላህን ፈሪዎች ሁሉ ፈሪ፣ የነብያት ሁሉ መደምደሚያ እንደነገሩን የጀሃነም እሳት የምትተነፍሰው ሁለት ትንፋሽ ምክንያት ነው፡፡
ሌላው መገንዘብ ያለብን ነገር እስልምና ሙሉ መሆኑን ለማንኛውም አለም ላይ ላለ ክስተት በል እንዲያውም ለሚቀጥለው አለም ጉዳዩች፣ የሚቀጥለው አለም ላይ ምን እንደሚከሰት በዝርዝር እና በጥቅል የተናገር ዉድ፣ ልዩ፣ የማይበረዝ፣ የማይሰረዝ፣ የማይደለዝ፣ ዘመን የማያልፍበት ሀይማኖት ነውና አጥብቀን እንያዘው፡፡ ይሀው ተመልከቱ አከም “Econmic Crisese” ኢኮኖሚክ ክራይስስ ብለው ሲያወሩ አላህ ጥንትም የወለድ መጨረሻው ይህ መሆኑን ነግሮን ነበር፡፡
ትዳር እንዲመሰረት እና ከዝሙት እንድንታቀብ ከጥንትም የነብያት ሁሉ ሀይማኖት መክሮ ነበር፡፡ ግን ይህን አልሰማ ብለው አሁን አለም ላለችበት ከባባድ በሽታዎች ተዳርገዋል፡፡
በሁሉም የህይወት ዘርፍ ላይ የጥንት የጠዋቱ ኢስላም (ሰለፍያ) በሄደበት መንገድ መሄድ ብቻና ብቻ ነው ዋስትናው፡፡ ሁለት ሃቅ የለም፡፡ ሁሉም ሙስሊም ከጥመት ቡድኖች እርቆ ወደ ብቸኛዋ አማራጭ እና ሁለተኛ ወደሌላት ሃቅ ጎዳና፣ ሰለፉነ ሷሊሂን የተጓዙባት ጎዳና መመለስ ግድ ይለዋል፡፡ አለበለዚያ በሙስሊሙ አለም ላይ እንዳየነው አሁንም ከባድ ኪሳራ ይከሰታል፡፡
ታድያ ምን ይበጀን?
አማኞች ወደ ጌታቸው በንሰሃ ሊመለሱ፣ ያችን “ጭማሪ አለን?” ብላ የምትጠይቀውን ጀሀነም ከሷ ጌታችን እንዲጠብቀን እሱን ዘውትር መለመን ግድ ይለናል፡፡ የአላህ ባርያዎች ሆይ! አሁንም አረፈደም ንሰሃ እንግባ፡፡ አላህ እነዚህን ሁሉ ተዓምራት የሚያሳየን በሰጠን አእምሮ የሱን ጌትነት፣ በቸኛ ተመላኪነት አውቀን ወደሱ እንድንመለስ ነው፡፡
አላህ ሆይ! ሁሌ ወዳንተ በጸጸት ከሚመለሱት አድርገን፡፡
Forwarded from SadatKemal Abu Meryem
ትግሬ፣ አማራ፣ ኦሮሞ፣ ጉራጌ፣ ስልጤ፣ ሀደሬ፣ ወለኔ፣ … አረብ፣ ነጭ፣ ጥቁር፣ እና የመሳሰለው ሁሉም
የዘር ሀረጋቸውን ወደላይ ሄዶ ሄዶ ከሰው ልጆች አባት ነብዩላህ አደም (አለይሂ ሰላም) ውጭ አይደለም፡፡ አደም ደግሞ የተፈጠረው ከአፈር ነው፡፡ ከአፈር የተፈጠረው የሰው ልጅ ደግሞ ሲሞት ወደ አፈር ይመለሳል፡፡
ታድያ ለምን ይሆን ዘሩን እንዲህ የሚመፃደቅበት እና አንዱ አንዱን የሚያንቋሽሽበት?
የፍጡራን ሁሉ ፈጣሪ፣ ብቸኛው አምላክ አላህ የሰው ልጆች የሚለያዩት ለእርሱ ባላቸው ፍራቻ ብቻና ብቻ እንደሆነ እንዲህ ሲል ይነግረናል፡፡
يَٰٓأَيُّهَا ٱلنَّاسُ إِنَّا خَلَقْنَٰكُم مِّن ذَكَرٍ وَأُنثَىٰ وَجَعَلْنَٰكُمْ شُعُوبًا وَقَبَآئِلَ لِتَعَارَفُوٓا۟ ۚ إِنَّ أَكْرَمَكُمْ عِندَ ٱللَّهِ أَتْقَىٰكُمْ ۚ إِنَّ ٱللَّهَ عَلِيمٌ خَبِيرٌ
እናንተ ሰዎች ሆይ! እኛ ከወንድና ከሴት ፈጠርናችሁ፡፡ እንድትተዋወቁም ጎሳዎችና ነገዶች አደረግናችሁ፡፡ አላህ ዘንድ በላጫችሁ በጣም አላህን ፈሪያችሁ ነው፡፡ አላህ ግልጽን ዐዋቂ ውስጥንም ዐዋቂ ነው፡፡
አንድ አምላክ ዘንድ የሰው ልጆች የሚበላለጡት እሱን በመፍራታቸው ብቻና ብቻ ነው፡፡
ለአእምሮ ባለቤቶች ይህ ትልቅ ትምህርት አለበትና ዘረኝነትን ሁላችንም እንራቀው፡፡