Sadat_Text_Posts
10K subscribers
291 photos
8 videos
12 files
378 links
Download Telegram
የመውሊድ ውድድር
ፈተና አንድ
1) ነብዩ ሙሐመድ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ስንት ጊዜ ነው መውሊድ በኣል ላይ የተሳተፉት?
___________________
2) የትኛው ከተማ ላይ ነበር መውሊድ ለመጀመሪያ ጊዜ በሰሃባዎች የተከበረው?
_____________________________________
3) ሰሃባዎች የትኛውን አይነት የመውሊድ አወጣጥ ነበር ለታቢኢኖች ያስተማሩት?
________________________________________________________
4) ምን አይነት ምግብ ነበር በመውሊድ ወቅት ሲመገቡት የነበረው?
________________________________________________________
5) መውሊድ ላይ በሰሃባዎች ሲዜሙ ከነበሩ ዘፈኖች ውስጥ ዋናዋናዎቹን ጥቀስ
___________________________________
___________________________________
• አስታውሱ ሁሉም መልሶች ከሚከተሉት መሰረታዊ ምንጮች ነው መሆን ያለባቸው፡
1. ከቁርኣን፣
2. ከሀዲስ፣
3. ከሰሃባዎች ንግግር
በደንብ አስባችሁ፣ ጊዜያችሁን ውሰዱና ቁርኣንን ፈትሹ፣ ቡኻሪ ሙስሊም እና ሌሎች የሀዲስ መዛግብትን መጠቀም ትችላላችሁ፡፡
የተተረጎመ
https://t.me/SadatTextPosts
ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ከሰሃባዎች ጋር አዲስ አበባ መዘጋጃ ቤት መጥተዋልን?
http://bit.ly/2DAlFv8
http://bit.ly/2ROcgCS
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem/1524

ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ከሰሃባዎች ጋር አዲስ አበባ መዘጋጃ ቤት መጥተዋልን?

ነብዩ ሙሐመድ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም)
- ሞተዋል፣
- የተቀበሩትም የምእመናን እናት አኢሻ (ረድየላሁ አንሃ) ቤት ውስጥ ሳውዲ አረቢያ ላይ መዲና ከተማ ውስጥ ነው፣
- ሞተው ከተቀበሩ በኋላ ሰሃባዎች ለማየት እንኳን ከቀብራቸው አልወጡም፡፡
- እሳቸው ወደ እኛ አይመጡም፡፡
- እኛ ካለንበት ሆነን እሳቸው ላይ የምናወርደው ሰለዋት ቀብራቸው ውስጥ ሆነው ይደርሳቸዋል፡፡
ሸሪአተል ኢስላም ላይ በመዋሸት ከሚታወቁት አንዱ ሙሐመድ አወል (የሺርክ መንዙማ አቀንቃኙ) አዲስ አበባ መዘጋጃ ቤት ላይ ለተሰበሰቡ ሰዎች እንዲህ ብሏቸዋል
“አይዟችሁ ተደሱ (ተደሰቱ)፣
መውሊድ የመጣችሁ፣
እስተ አስሀቦቹ (እስከነ ሰሃቦቹ)፣
ነቢ መጡላችሁ”
ሲል ይዋሻል፡፡
የትኛውን መውሊድ?
እንደሚታወቀው በኢስላም የታዘዙት ሁለት አመታዊ በኣላት፣ ኢድ አል-ፊጥር እና ኢድ አል-አድሃ ናቸው፡፡ ኢድ አል-ፊጥር አንድ ቀን ብቻ ሲሆን፣ ኢድ አል አድሃ ደግሞ 4 የበኣል ቀናቶች ናቸው፡፡ ታድያ በሀገራችን ተጨባጭ አላህ 4 ቀን እንዲከበር ያዘዘውን አንድ ቀን ብቻ እያከበርን ያልታዘዝነውን መውሊድ ግን ከአንድ ቀን በላይ በተለያዩ ሰዎች ስም ሲከበር ይታያል፡፡
ለምሳሌ ሀገራችን ላይ በተለያየ ቀናት ከሚከበሩ የመውሊድ አይነቶች ውስጥ
1) የነብዩ መውሊድ፣
2) የአሊ ጎንደር መውሊድ፣
3) የአባድር መውሊድ፣
4) የዳንግላው መውሊድ፣
5) የአብሬት መውሊድ፣
6) የቃጥባሬ መውሊድ፣
7) የአልከሶ መውሊድ፣
8) እና ስፍር ቁጥር የሌላቸው መውሊዶች……
ለምን ይሆን በኢስላም የታዘዝነውን ትተን ያልታዘዝነውን የምንሰራው?
እውነት ይህ ነው የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ውዴታ?
በፍፁም፡፡
ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “አደራችሁን አዳዲስ ነገሮችን (በዲን ላይ ከመጨመር) ተጠንቀቁ፡፡ ሁሉም አዲስ ነገር ጥመት ነው፡፡” ብለው ሲያበቁ
አሁንም ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “የእኛ ትእዛዝ የሌለበትን ስራ የሰራ ሰው ስራው ተመላሽ ነው (ተቀባይነት አያገኝም፣ ውድቅ ነው)” ብለው ሳለ

ዛሬ እሳቸው ያዘዙትን ትተው ያላዘዙትን የሳቸውንም ይሁን ሌሎች ጥሩ ሰዎች ናቸው ብለው የሚገምቷቸውን የአሊ ጎንደር መውሊድ፣ የአባድር መውሊድ፣ የዳንግላው መውሊድ፣ የአብሬት መውሊድ፣ የቃጥባሬ መውሊድ፣ የአልከሶ መውሊድ እና የመሳሰሉትን እያሉ በውዱ ሃይማኖታችን ላይ ቅጥፈትን ይቀጥፋሉ፣ የክህደት ንግግሮችን መውሊዶች ላይ ይናገራሉ፣ ይጨፍራሉ፣ ይህን አደንዛዥ ቅጠል ያላምጣሉ፡፡

ሱብሃነላህ ይህ በፍፁም ነብዩን መውደድ አይሆንም፡፡ ነብዩን ከማንም በላይ የሚወዱት ሰሃባዎች የነብዩን ፈለግ ህይወታቸው ላይ ተላበሱ እንጂ እንዲህ ልደት እናክብር አላሉም፡፡

ለሙስሊሙ ከታሰብ መውሊድ ብሎ በሺርክ፣ በቢድኣ፣ በጭፈራ እና አደንዛዥ ቅጠል ጫትን መቃም እና ማስቃም ሳይሆን፣ መስጂዶችን ማስፋፋት፣ መድረሳዎች መገንባት፣ እውነተኛውን የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) አስተምህሮት ማሰራጨት፣ ከሱስ የፀዳ ሃይማኖቱን እና ሀገሩን የሚጠቅም ትውልድ ማነፅ ይጠበቅብናል፡፡

ይሄ እውነተኛ የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ውዴታ የሚገለፀበት ተግባር ነው፡፡
አላህ ሱናቸውን ከሚከተሉት ከቢድኣ ከሚርቁት ትውልዶች ያድርገን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
መውሊድ ቢድኣን ማንገሻ ዲንን ማፍረሻ
መውሊድ ነብዩን (ﷺ) ማስታወሻ ሳይሆን የሳቸውን ሱና በማፍረስ፣ ቢድኣን የሚያነግሱበት በኢስላም ያልተደነገገ ተግባር ነው፡፡
መልክተኛውን (ﷺ) የወደደ ያዘዙትን ይሰራል፣ የሰሩትን ይሰራል፣ እሳቸው ሰሃባዎች ሲሰሩ አይተው ዝም ያሉትን (ማፅደቃቸው ነውና) ይሰራል፡፡
ከዛ ውጭ አዲስ ነገርን ማምጣት ዲንን ማፍረስ፣ የሙስሊሞችን አንድነት ማፍረስ፣ የጭቅጭቅ በርን መክፈት ነው፡፡
አላህ ከጥፋት መንገድ ይጠብቀን፡፡ ብሩሁን የነብዩ እና የሰሃባዎቻቸውን መንገድ ይምራን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
መውሊድ በበፊት አክባሪዎቹ ሲጋለጥ
ከዚህ በታች የምታነቡት መውሊድ የሚሄድ የነበረ ሰው ይፈፅም የነበረውን ሺርክ፣ አላህን ማመፅ፣ የሙስሊሞች ብር ዘረፋ እንዲህ ሲል ያስቀምጠየዋል
እኔ ገጠር ያደኩ ሥሆን በዛን ጊዜ ሥለድን ከቤተሠቦቼ እንኳን አንዳችንም አናቅ፡፡
ታዲያ መወልድ ደረሠና ሥንቃችንን ይዘን በጧት ተነሥተን ወደ ጀማ ንጉሥ መጎዝ ጀመረን፡፡
ይሄንን ቁልቁለት ሸቅበት በሥንት ጉድ ጨርሠን፡፡
ማታ ጀማ ንጉሥ ገባን፡፡
ከዛ ማታ ህዝቡ እደ ጉድ ተሠብሥቧል፡፡
ከዛ መንዙማ ተከፈተ ሤቱም ወንዱም እደ ዲልቂያ ተደበላልቆ እሥክታ ይመታ ጀመረ፡፡
ብቻ እኔ ሥለድኔም ምንም ባላቅ አልጣመኝምና ወደ ዳሡ ሄጂ ተኛሁኝ፡፡
ጧት ቀሠቀሡኝ እና እንሄድ አሉኝ፡፡
የት አልካቸው?
ወረፉ እንያዝ አሉኝ፡፡
ለምኑ?
ሸሆቹ እየመረቁ ነው እኮ አሉኝ፡፡
ሠልፉን ያዘን ከዛ እበራፉ ላይ ሁለት ጥምጣም የጠመጠሙ እየመረቁ የሄንን ብር ለጉድ ሠብሥበውታል፡፡
ከዛም አልፉ ወደ ቤቱ እየተገባ በመሥኮቱ ወደ ውሥጥ ብር ይወረወራል፡፡
እውሥጥ በድቦራ የተሸፈነ ትልቅ ጎራ የሚመሥል አለ፡፡
በዛ በመሥኮት ባለሀጃው መቶ ሥቅሥቅ ብሉ ያለቅሣል፣ ይለምናል፡፡
የሄንን ካደረጋችሁልኝ ኮርማ አቀርባለው፡፡
ብቻ አምልኮ በሙሉ ለፍጡር ይደረጋል፡፡
እኔ በአይኔ ያየሁት ጉዳይ ነው፡፡ ከዛ ለአንድ ጎደኛየ ይሄንን ነገር ነገርኩትና ያማ በድቦራ የተሸፈነው ቀብር ነው አለኝ፡፡
ጀማ ንጎሥ የሽርክ መነሀሪያ መሆኑን አወኩ፡፡
አሏህ ሽቶልኝ ወደ ሣወዲ አምጥቶ ዲኔን አሣወቀኝ፡፡ ጀህልና ወልቅ ብላ ሄደች አልሀምዱሊላህ እና ይሄንን ለመናገር የፈለኩት አንዳንድ ሠዎች መውሊድ እምናከብረው እና ሥናከብር ድሆችን ለማብላት ቁራአን ለመቅራት ወዘተ ይላሉ ወሸት ነው፡፡

የዚህ ወንድም ምስክርነት በዚህ አበቃ፡፡
ከዚህ የምንወስደው ትምህርት ሀገራችን ላይ
- ሱፊዬች የተውሒድ ሰዎች ናቸው እያሉ የሚያጭበረብሩት ውሸት ነው፡፡ ሱፍዬች ይሀው ሺርክ እና ቢድኣን አስፋፊ ናቸው፣
- መውሊድ ላይ ቀብር አምልኮ ይፈፀማል፣
- የድሆች ብር ይበዘበዛል፣
- ለሆዳቸው የደሩ አሊም ተብየዎች ይህንን ጥፋት በማስፋፋት ላይ የመጀመሪያውን ድርሻ ይይዛሉ፣
- መውሊድ ላይ ነብዩን እናወድስበታለን እያሉ የሚያጭበረብሩት ኪስ አውላቂዎች የነሱን ሀብት ለማዳለብ እንጂ ለነብዩ ውዴታ አይደለም፣
- መውሊድ በሃበሻ ዲን ለመስፋፋት አስተዋፅኦ አድርጓል የሚሉን ሰዎች ውሸታሞች ናቸው፡፡ መውሊድ ይሀው ዲንን አፍራሽ ለመሆኑ ሰሜን አካባቢ የሚሰራውን የአይን እማኞች የተናገሩት ከበቂ በላይ ማስረጃ ነው፡፡
አላህ ኡማውን ከማጭበርበር እና በአጭበርባሪዎች ከመጭበርበር ይጠብቀን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
ለአቂዳ ስንል ነው የታሰርነው ያሉት ሰዎች አቂዳቸው ከተበላሹ አህባሾች ጋር የሺርክ መነሀሪያ መውሊድ ላይ ምን ይሰራሉ?
የኢትዩጵያ ሙስሊሞች ሆይ! አሁንስ አትነቁም?
እንደሚታወቀው እነ አቡበክር አሕመድ፣ ካሚል ሸምሱ፣ አህመዲን ጀበል እና ሌሎችም ከዚህ በፊት ከመንግስት ጋር ተጋጭተው በታሰሩ ጊዜ “ለአቂዳ ነው የታሰርነው፡፡ ለዲን መሞት ክብር ነው፡፡” ሲሉ እና ሲባልላቸው ነበር፡፡ ዛሬ ግን በአንድ ጀንበር ተገልብጠው ከአህባሽ ጋር ምንም እንዳልተፈጠረ “የአንድነት እና የሰላም ኮንፍረንስ” ይላሉ፡፡ እኛን የሺርክ መናሀሪያ የሆነውን መውሊድ ስንቃወም “መውሊድ መውሊድ እያላችሁ ኡማውን አትበታትኑት፣ መውሊድ አቂዳ አይደለም” እንዳላሉ
መውሊድ አቂዳቸው ከሆኑት አህባሾች ጋር አቡበክር አህመድ፣ አህመዲን ጀበል እና ጓደኞቻቸው ይሀው “እንኳን ለመውሊድ አደረሰን” የሚል ዝግጅት ላይ ንግግር ሁሉ አደረጉ፡፡ ትላንት ከአህባሽ ጋር ያጣላቸው ስልጣን እንደሆነ በማስረጃ ስንናገር “የመንግስት ቅጥረኞች” ሲሉን ነበር…. ዛሬስ? ዛሬማ ህዝብ ነቃ ቅጥረኛ ምናምን ቡሊ ሰሚ የላቸውም፡፡ ሰውን ቢሸውዱ አላህን መሸወድ አይቻል፡፡ አልሐምዱሊላህ አላህም ህዝቡን አነቃው፡፡ ኢንሻአላህ ገና ያልነቃውም ይነቃል፡፡
ህዝቡ ከነቃ አይገደድም፡፡

https://t.me/SadatTextPosts
እሺ እዚህስ ምን ሊሰሩ ነበር የሄዱት?
በያዝነው ሳምንት ከሊፋ ህንፃ ላይ “መውሊድ በሀበሻ ያበረከተው አስተዋፆ” በሚል ጥናታዊ ፅሁፍ ቀርቦ ከራምሳ ጀምሮ መንዙማዎች በአማርኛና በኦሮምኛ ሁሉ ተዜሟል፡፡
ቦታው ላይ የተገኙት ሀሰን ታጁ (የፁሁፉ አቅራቢ)፣ ኢድሪስ ሙሐመድ፣ ካሚል ሰምሹ እና ሌሎችም ናቸው፡፡
እዚህ ፕሮግራም ላይ መቼም ካሚል ሸምሱ ምን ሊላቸው ነበር የተሳተፈው? “አላህን ፍሩ መውሊድ ቢድኣ ነው” በፍፁም አይላቸውም፡፡
የሺርክ መናሃሪያ የሆነውን፣ ነብዩ ይመጡበታል ብለው የሚዋሽበትን ኢስላም የማያውቀው መውሊድ እነሱ ሲያከብሩት “ዝም በሉ የሙስሊሞች አንድነት አትበትኑ” ይሉናል፡፡ እኛ ደግሞ እናንተ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ያላዘዙትን በመስራት የሙስሊሞችን አንድነት አትበትኑ እንላችኋለን፡፡ አንድነት ማለት በሐቅ ላይ መሰብሰብ እንጂ፣ ቢድኣን በማንገስ፣ አደንዛዥ ቅጠል በመቃም፣ የምስኪኖችን ብር በመዝረፍ ላይ አይደለም፡፡ የሚገርመው አህባሾች እንኳን አላመኗቸውም፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
ከሰሃባዎች በላይ ነብዩን የሚወድ አለን?
አላህ አማኞች፣ እውነተኞች ያላቸው ነብዩን ﷺ ከአላህ ቀጥሎ ከምንም በላይ የሚወዱት፣ በህይወታቸው፣ በገንዘባቸው የረዱት ሰሃባዎች መውሊድ አላከበሩም፡፡
ታድያ የእኛ ሀገሮቹ ይህንን የሺርክ መነሃሪያ፣ የቢድኣ ቁንጮ፣ አደንዛዥ ቅጠል ጫት የሚበላበት፣ መስጂድ ውስጥ የሚጨፈርበትን ሲያከብሩ ኢስላምን ከሰሃባዎች በላይ ተረድተውት ነውን?
መልክተኛውን ﷺ ከሰሃባዎች በላይ ወደዋቸው ነውን?
በፍፁም
የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “የእኛ ትእዛዝ የሌለበትን ስራ የሰራ ሰው ስራው ተመላሽ ነው፡፡”
ሰባሃዎች ያልታዘዙትን አይሰሩም ነበር፡፡ የዛሬዎቹ አታላዬች በነብዩ ﷺ ስም ይነግዳሉ፣ ሃይማኖት ያፈርሳሉ፡፡
አላህ ከጠሞ አጥማሚዎች ይጠብቀን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
ዛሬ አላህ ሲታመፅ የዋለበት ቀን ነው።
አምልኮ ምን እንደሆነ በዝርዝር የነገረን ውብ ኢስላም ውስጥ የሌለን መውሊድ በአል ነው ብለው በድፍረት መስጂዶች ውስጥ ሲጨፍሩ ዋሉ።
ደግነቱ የቢድአ ጠበቆች ተጋለጡበት።
አላህ ከሸራቸው ይጠብቀን።
https://t.me/SadatTextPosts
ሰኞ እና መውሊድ?

መውሊድ አክባሪዎች “ነብዩ ﷺ ሰኞን የተወለዱበት ቀን ስለሆነ ፆመዋል፡፡ ይህም መውሊድን (ልደታቸውን) ለማክበር ማስረጃ ነው፡፡” ይላሉ፡፡
በአላህ ፍቃድ እና እገዛ ማስረጃ ብለው ያቀረቡት፣ ማስረጃ መሆን እንደማይችል በሰፊው እንየው፡፡
ነብዩ (ﷺ) ሰኞን ቀን እንደሚፆሙ በትክክለኛ ሀዲሶች ተረጋግጧል፡፡ የሚከተሉትን ሀዲሶች እንይ

የአላህ መልክተኛ (ﷺ) ሰኞን ለምን እንደሚፆሙ ተጠየቁ፣ እሳቸውም “በዛ ቀን ተወለድኩ፣ እናም መለኮታዊ ራእይም በዛው ቀን መጣልኝ” ሰሂህ ሙስሊም 1162
በሌላ ዘገባ የአላህ መልክተኛ (ﷺ) እንዲህ አሉ “ስራዎች ሰኞ እና ሀሙስ (ወደ አላህ) ይወጣሉ፡፡ ስራዬ ፆመኛ ሆኜ እንዲቀርብልኝ እፈልጋለሁ” ቲርሚዚ 747

ከነዚህ ሁለት ሀዲሶች የምንማራቸው ትምህርቶች እንደሚከተለው ይቀርባሉ
1.) የአላህ መልክተኛ (ﷺ) ሰኞን የፆሙት ለሶስት ምክንያቶች ነው
a. የተወለዱበት ቀን ስለሆነ፣
b. ቁርኣን ለእሳቸው የወረደበት ቀን ነው፣
c. ስራዎችም ወደ አላህ የሚወጡበት ቀን ስለሆነ እና እሳቸው ስራቸው ፆመኛ ሆነው እንዲወጣላቸው ስለፈለጉ፡፡
የአላህ መልክተኛ (ﷺ) የፆሙት ከላይ በተጠቀሱት ሶስት ምክንያቶች እንጂ ሰኞን ስለተወለዱበት ብቻ አልነበረም፡፡

2.) ከዚህ ሀዲስ ሰሃባዎች አመት ጠብቀው በረቢአል አወል የነብዩን (ﷺ) ልደት ማክበርን አልተረዱም፡፡ ሰሃባዎች ደግሞ ለኢስላም በጣም ቅርብ፣ ኢስላምን ጠንቅቀው አዋቂዎች እና ኢስላምን ከማንም በላይ የተረዱ ከመሆናቸውም ጋር “መውሊድ” የሚባል በአል አያከብሩም ነበር፡፡

3.) ታቢኢን በመባል የሚታወቁት የሰሃባ ተማሪዎች ከዚህ ሀዲስ መውሊድ የሚባል በአል አለ ብለው አልተረዱም፡፡

4.) አራቱ ታላላቅ የፊቂህ ኢማሞች አቡ ሀኒፋ፣ ኢማሙ ማሊክ፣ ኢማሙ ሻፊኢ እና ኢማሙ አህመድ ይህን ሀዲስ እያወቁ፣ ሀዲሱን መውሊድ (የነብዩን ልደት) ማክበር ይቻላል ለሚል ማስረጃ አልተጠቀሙትም ፡፡

5.) በዚህ ሀዲስ የተገደበው አምልኮ ፆም ነው፡፡ ስለዚህ ፁሙ፡፡ ከዚህም አትለፉ፡፡ ዲኑ ገር ነው፡፡ ነብዩ (ﷺ) የሰሩትን እንስራ ያልሰሩትን አንስራ፡፡

አንዳንድ ሰዎች ይገርማሉ ሀዲስን ትርጉሙን ያዛባሉ፣ ይጠመዝዙታል ለምን ሲባል ቢድኣን ለማንገስ፡፡ እኛ ከሰሃባዎች በላይ አላህን አዋቂ፣ ፈሪም፣ አላህ ዘንድ እውነተኞችም አይደለንም፡፡ እኛ ከሰሃባዎች በላይ ነብዩ (ﷺ) አንወድም፣ አናከብርም፣ መስዋትም አልሆንም፡፡ ስለዚህ አደብ አድርገን እንቀመጥ፡፡
እንዲህ አይነት ጥፋቶችን ስናጋልጥ እናንተ በእድሜ ከጠገቡት ታላላቅ ኡለማዎች፣ ሙፍቲዎች፣ ዶክተሮች፣ ኡስታዞች ትበልጣላችሁን? ሲሉ ይጠይቃሉ
መልሱም ቀላል ነው
እነዚህ እናንተ ኡለማ ብላችሁ የምትከተሏቸው ሶዎች ከሰሃባዎች አላህን በመፍራት፣ አላህ እና መልክተኛውን በመውደድ፣ በእውቀት ይበልጣሉን?
አይበልጡም
ስለዚህ ሙፍቲም፣ ዶክተርም፣ ኡስታዝም፣ ሙነሺድም፣ ድቤ መቼም አርፈው ይቀመጡ፣ ዲን አይበጥብጡ፡፡
ኡማውን አይከፋፍሉ፡፡ ሺርክ እና ቢድኣን አያንግሱ፡፡
አላህ ከሺርክ፣ ከቢድኣ፣ ከዘረኝነት የፀዳ እውነተኛ አንድነት ይስጠን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
አቡበክር አሕመድ ህዝቡን ገላግለው ግራ አታጋባው
አህባሾች ያዘጋጁት መውሊድ ላይ ተገኝተህ “የሀሳብ ልዩነት የነበረ ነው” ብለሀል፡፡
የብዙዎች ጥያቄ የሚሆነው ከአህባሽ ጋር ያለን የሀሳብ ወይንስ የእምነት ልዩነት?
ይህንን መልስ በግልፅ ብትናገር አህባሾችንም ከአህባሽ ጋር የእምነት ልዩነት ያለውንም ትገላግለው ነበር፡፡
6 አመት ሙሉ ሰው የተገደለው፣ የታሰረው፣ ሀገር ለቆ የሄደው መስጂዶች የተደፈሩት ከአህባሽ ጋር የእምነት ልዩነት አለን ተብሎ እንደነበር አሁንም ድረስ ብዙዎች ያውቁታል፡፡
አላህ እውነተኞች ሁኑ ብሏል፡፡ እውነቱን ተናግሮ የመሸበት ማደር፡፡
https://t.me/SadatTextPosts