ለሙስሊሙ ብሎም ለሀገራችን ያሰበ “ጫት ሸርጡ ተጠብቆ ስላልተቃመ እንጂ መሻኢሆቻችን ጫት ቅመው ዝናብ ያዘንቡ ነበር” እያለ ባልዋሸና ባልሰበከ ነበር፡፡
የሚያሳዝነው እንዲህ አይነቱ ሀይማኖት እና ሀገር አፍራሽ ግለሰብ የሀይማኖት ሰው ተደርጎ መወሰዱ ነው፡፡
ጫት ሙስሊሙን ያሽመደመደ፣ ኢትዮጵያን ወደ ኋላ ያስቀረ አደገኘ መርዘኛ አደንዛዥ ቅጠል ነው፡፡
አላህ ለሙስሊሙም ለሀገርም የሚጨነቁ እውነተኛ የሀይማኖት አባቶች ይለግሰን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
የሚያሳዝነው እንዲህ አይነቱ ሀይማኖት እና ሀገር አፍራሽ ግለሰብ የሀይማኖት ሰው ተደርጎ መወሰዱ ነው፡፡
ጫት ሙስሊሙን ያሽመደመደ፣ ኢትዮጵያን ወደ ኋላ ያስቀረ አደገኘ መርዘኛ አደንዛዥ ቅጠል ነው፡፡
አላህ ለሙስሊሙም ለሀገርም የሚጨነቁ እውነተኛ የሀይማኖት አባቶች ይለግሰን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
ከ 7 ሰማይ በላይ…..
የአላህ ባርያዎች ሆይ! ማንኛውንም ስራ ስንሰራ ከ7 ሰማያት በላይ ያለውን ሁሉን አዋቂ፣ ተመልካች፣ ሰሚ አላህ አስበን፣ ፈርተን እንስራ፡፡
ምክንያቱም የሰራናት ስራ እሱ ዘንድ ተቀባይነት ካለት የእድለኞች ሁሉ እድለኞች እንሆናለን፡፡ እሱ ከተቆጣብንም የከሳሪዎች ሁሉ ከሳሪ እንሆናለን፡፡
ስለዚህ ለአላህ ብቻ አጥርተን እንስራ፡፡ ወንጀል ስንሰራ ወዲያውኑ በንሰሀ ወደ እሱ እንመለስ፡፡
የምንናገረው እና የምንሰራው መልካም መሆኑን እናረጋግጥ አላህ ዘንድ ይደርስልን ዘንድ፡፡ አላህ እንዲህ ይላል
إِلَيْهِ يَصْعَدُ ٱلْكَلِمُ ٱلطَّيِّبُ وَٱلْعَمَلُ ٱلصَّٰلِحُ يَرْفَعُهُۥ ۚ
መልካም ንግግር ወደርሱ (ወደ አላህ) ይወጣል፡፡ በጎ ሥራም ከፍ ያደርገዋል፡፡
[ 35:10]
አላህ ለእርሱ ብቻ ስራቸውን ከሚያጠሩት፣ እሱን ብቻ ከሚፈሩት፣ ሲሳሳቱ ወደ እሱ ከሚመለሱት ባሪያዎች ያድርገን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
የአላህ ባርያዎች ሆይ! ማንኛውንም ስራ ስንሰራ ከ7 ሰማያት በላይ ያለውን ሁሉን አዋቂ፣ ተመልካች፣ ሰሚ አላህ አስበን፣ ፈርተን እንስራ፡፡
ምክንያቱም የሰራናት ስራ እሱ ዘንድ ተቀባይነት ካለት የእድለኞች ሁሉ እድለኞች እንሆናለን፡፡ እሱ ከተቆጣብንም የከሳሪዎች ሁሉ ከሳሪ እንሆናለን፡፡
ስለዚህ ለአላህ ብቻ አጥርተን እንስራ፡፡ ወንጀል ስንሰራ ወዲያውኑ በንሰሀ ወደ እሱ እንመለስ፡፡
የምንናገረው እና የምንሰራው መልካም መሆኑን እናረጋግጥ አላህ ዘንድ ይደርስልን ዘንድ፡፡ አላህ እንዲህ ይላል
إِلَيْهِ يَصْعَدُ ٱلْكَلِمُ ٱلطَّيِّبُ وَٱلْعَمَلُ ٱلصَّٰلِحُ يَرْفَعُهُۥ ۚ
መልካም ንግግር ወደርሱ (ወደ አላህ) ይወጣል፡፡ በጎ ሥራም ከፍ ያደርገዋል፡፡
[ 35:10]
አላህ ለእርሱ ብቻ ስራቸውን ከሚያጠሩት፣ እሱን ብቻ ከሚፈሩት፣ ሲሳሳቱ ወደ እሱ ከሚመለሱት ባሪያዎች ያድርገን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
የሐጅ ጉዟችሁ በመጅሊስ በኩል ያልሆናችሁ ሰዎች አደራችሁን በሚናም ሆነ በዐረፋ የመጅሊሱን ድንኳን (ኸይማ) እንዳትጠቀሙ። በመጅሊስ በኩል ገንዘባቸውን ከስክሰው የሄዱ ወገኖች ድንኳን እየሞላባቸው በዚያ ከባድ ፀሐይ እየተለበለቡ፣ ለድንኳኑ ያልከፈላችሁ ሰዎች ድንኳኑን በማጨናነቅ የሌሎችን ሐቅ ልትጋፉ አይገባም። ይሄ ቀላል ጥፋት አይደለም። ሴቶችና አቅመ ደካሞች ድንኳኑ ዘንድ ለመድረስ ጊዜ ይፈጅባቸዋል። እንዳቅማቸው ተጉዘው እቦታው ሲደርሱ በወጣቶች፣ በተለይም ሳዑዲ ኗሪ በሆኑት ተስሪሕ የሌላቸው ኢትዮጵያውያን ወንድሞች ድንኳኑ ሞልቶ ይጠብቃቸዋል። በዚህም ሳቢያ ለዚያ ፈፅሞ ለማያውቁት ከባድ የፀሐይ ቃጠሎ (በተለይም ዐረፋ ላይ) ይጋለጣሉ። መቋቋም አቅቷቸው ነስር በነስር የሚሆኑ አሉ። በርግጠኝነት እነዚያ ያለ ሐቃቸው ቀድመው ኸይማውን የሚሞሉ ወጣቶች ይህን የደካሞችን እንግልት ከውጭ ሆነው ቢያዩ በጥፋታቸው ይሸማቀቃሉ። ይህ እንዳይሆን ዘንድ ያልከፈልንበትን አገልግሎት ለማግኘት ከመጋፋት ልንቆጠብ ይገባል። ደካሞችን ከተጨማሪ እንግልት፣ ሌሎቹን ደግሞ የሰው ሐቅ ከመጋፋት ለማትረፍ ሰበብ እንሆን ዘንድ መልእክቱን በማሰራጨት ተባበሩኝ። (ወንድማችሁ ኢብኑ ሙነወር፣ ሐምሌ 24/ 2010)
አቂዳ አንድ ያላደረገውን የበሬ አጥንት አንድ አያደርገውም፡፡
**********************************
በአቂዳ (በእምነት) እና በሱና አንድ ሳይሆኑ እጅ ለእጅ ተያይዞ ፎቶ በመነሳት፣ በሬ አርዶ ስጋ በመብላት አንድ መሆን አይቻልም፡፡
እምነት ያልሰበሰበውን አጥንት መጋጥ እና እጅ ለእጅ ተያይዞ ፎቶ መነሳት አንድ አያደርገውም፡፡
ፎቶ መነሳቱ፣ ሆቴል ተከራይቶ መደስኮሩ፣ እጅ ለእጅ ተያይዞ አንድ ነን ማለቱ አንድ ቢያደርግ ኖሮ ስንት የፖለቲካ ፓርቲዎችን አንድ ባደረገ ነበር፡፡
እባካችሁ የአላህና መልክተኛውን አማና አትብሉ፡፡ ነፍሳችሁን እንጂ ማንንም አታታሉም፡፡
አቂዳ አንድ ያላደረገውን የበሬ አጥንት አንድ አያደርገውም፡፡ ቅድሚያ ለእውነተኛ አንድነት፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
**********************************
በአቂዳ (በእምነት) እና በሱና አንድ ሳይሆኑ እጅ ለእጅ ተያይዞ ፎቶ በመነሳት፣ በሬ አርዶ ስጋ በመብላት አንድ መሆን አይቻልም፡፡
እምነት ያልሰበሰበውን አጥንት መጋጥ እና እጅ ለእጅ ተያይዞ ፎቶ መነሳት አንድ አያደርገውም፡፡
ፎቶ መነሳቱ፣ ሆቴል ተከራይቶ መደስኮሩ፣ እጅ ለእጅ ተያይዞ አንድ ነን ማለቱ አንድ ቢያደርግ ኖሮ ስንት የፖለቲካ ፓርቲዎችን አንድ ባደረገ ነበር፡፡
እባካችሁ የአላህና መልክተኛውን አማና አትብሉ፡፡ ነፍሳችሁን እንጂ ማንንም አታታሉም፡፡
አቂዳ አንድ ያላደረገውን የበሬ አጥንት አንድ አያደርገውም፡፡ ቅድሚያ ለእውነተኛ አንድነት፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
አላህ ሲያዝንልን እንወቅበት፡፡
ዙል-ሒጃ አስር ቀናትን ይመስል አዛኙ ለእኛ ሊያዝን ትንሹን ስራ ትልቅ አድርጎ ሊቀበለን፣ ወንጀላችንን ሊምረን በነዚህ እና በመሳሰሉት ቀናት ተጠቀሙባቸው ብሎ ቻንስ ሲሰጠን እንወቅባቸው፣ በአግባቡ እንጠቀምባቸው፡፡
መልካም ስራዎች ብዙ ናቸው፡፡ መፆም፣ ቁርኣን መቅራት፣ ሰደቃ መስጠት፣ አላህን ማውሳት እና ማወደስ፣ ዘመድ መጠየቅ……..
አላህ ወንጀላቸውን ከሚማሩ፣ ስራቸውን እጥፍ ድርብ አድርጎ ከሚቀበላቸው ያድርገን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
ዙል-ሒጃ አስር ቀናትን ይመስል አዛኙ ለእኛ ሊያዝን ትንሹን ስራ ትልቅ አድርጎ ሊቀበለን፣ ወንጀላችንን ሊምረን በነዚህ እና በመሳሰሉት ቀናት ተጠቀሙባቸው ብሎ ቻንስ ሲሰጠን እንወቅባቸው፣ በአግባቡ እንጠቀምባቸው፡፡
መልካም ስራዎች ብዙ ናቸው፡፡ መፆም፣ ቁርኣን መቅራት፣ ሰደቃ መስጠት፣ አላህን ማውሳት እና ማወደስ፣ ዘመድ መጠየቅ……..
አላህ ወንጀላቸውን ከሚማሩ፣ ስራቸውን እጥፍ ድርብ አድርጎ ከሚቀበላቸው ያድርገን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
አናሳ ብሄር፣ ትልቅ ብሄር አይባልም፡፡ ሰውን ትልቅ እና ትንሽ ያደረገው ከጌታው ጋር ያለው መልካም እና መጥፎ ግንኙነት ብቻ ነው፡፡ የትኛውም ዘር ከየትኛውም ዘር አይበልጥም አያንስምም፡፡ አናሳ እና ትልቅ ብሎ ብሄርን መከፋፈል አደለም ተምረናል ከሚሉና አልተማሩም ከሚባሉትም አይጠበቅም፡፡
የሁሉ ፈጣሪ አንድ አምላክ አላህ እንዲህ ይላል
يَٰٓأَيُّهَا ٱلنَّاسُ إِنَّا خَلَقْنَٰكُم مِّن ذَكَرٍ وَأُنثَىٰ وَجَعَلْنَٰكُمْ شُعُوبًا وَقَبَآئِلَ لِتَعَارَفُوٓا۟ ۚ إِنَّ أَكْرَمَكُمْ عِندَ ٱللَّهِ أَتْقَىٰكُمْ ۚ إِنَّ ٱللَّهَ عَلِيمٌ خَبِيرٌ
እናንተ ሰዎች ሆይ! እኛ ከወንድና ከሴት ፈጠርናችሁ፡፡ እንድትተዋወቁም ጎሳዎችና ነገዶች አደረግናችሁ፡፡ አላህ ዘንድ በላጫችሁ በጣም አላህን ፈሪያችሁ ነው፡፡ አላህ ግልጽን ዐዋቂ ውስጥንም ዐዋቂ ነው፡፡
አላህ እሱን ከሚፈሩት ያድርገን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
የሁሉ ፈጣሪ አንድ አምላክ አላህ እንዲህ ይላል
يَٰٓأَيُّهَا ٱلنَّاسُ إِنَّا خَلَقْنَٰكُم مِّن ذَكَرٍ وَأُنثَىٰ وَجَعَلْنَٰكُمْ شُعُوبًا وَقَبَآئِلَ لِتَعَارَفُوٓا۟ ۚ إِنَّ أَكْرَمَكُمْ عِندَ ٱللَّهِ أَتْقَىٰكُمْ ۚ إِنَّ ٱللَّهَ عَلِيمٌ خَبِيرٌ
እናንተ ሰዎች ሆይ! እኛ ከወንድና ከሴት ፈጠርናችሁ፡፡ እንድትተዋወቁም ጎሳዎችና ነገዶች አደረግናችሁ፡፡ አላህ ዘንድ በላጫችሁ በጣም አላህን ፈሪያችሁ ነው፡፡ አላህ ግልጽን ዐዋቂ ውስጥንም ዐዋቂ ነው፡፡
አላህ እሱን ከሚፈሩት ያድርገን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
ለአረፋ ቤተሰብ ዚያራ ለምትሄዱ
የሚከተሉትን ሶስት የተውሒድ ፓምፍሌቶች ከሚከተሉት ሊንኮች ብትወስዱ ወሳኝ መልክት አላቸው፡፡
1) አቂዳን ለሙስሊም ልጆች ማስተማር
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem/1463
2) ወሳኝና አንገብጋቢ ነጥቦች በጥያቄና መልስ
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem/1465
3) የእምነት መሰረቶችን ለአጠቃላይ ሙስሊም ማህበረሰብ ማስገንዘብ
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem/1467
ሌሎች ከ200 በላይ ሙሃደራ እና ደርሶችን በድምፅ ለማረድ የሚከተለውን ሊንክ ተጠቀሙ
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem
የሚከተሉትን ሶስት የተውሒድ ፓምፍሌቶች ከሚከተሉት ሊንኮች ብትወስዱ ወሳኝ መልክት አላቸው፡፡
1) አቂዳን ለሙስሊም ልጆች ማስተማር
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem/1463
2) ወሳኝና አንገብጋቢ ነጥቦች በጥያቄና መልስ
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem/1465
3) የእምነት መሰረቶችን ለአጠቃላይ ሙስሊም ማህበረሰብ ማስገንዘብ
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem/1467
ሌሎች ከ200 በላይ ሙሃደራ እና ደርሶችን በድምፅ ለማረድ የሚከተለውን ሊንክ ተጠቀሙ
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem
Telegram
SadatKemal Abu Meryem
ሐጅ ላይ ላልሆናችሁ የአላህ ባሪያዎች
ሰኞ ዙል-ሂጃ 9 መፆም እንዳንረሳ፡፡
የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ያለፈውን አመት እና የመጪውን አመት ወንጀል ያስምራል” ብለዋል፡፡ ኢማሙ ሙስሊም 1162 ዘግበውታል
የአላህ ባሪያዎች ሆይ! አላህ ለእኛ ለማዘን ብዙ ሰበቦችን አስቀምጦልናል፡፡ እኛም እንወቅበት፡፡ ሰኞ 9ኛው የዙል ሒጃ ቀንን በመፆም በአላህ ፍቃድ የሁለት አመት ወንጀላችንን እናስምር፡፡ ላልሰሙ ሙስሊሞች ሁሉ አድርሱት፡፡ የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ወደ መልካም ያመላከተ እራሱ እንደሰራው ነው” ብለዋል፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
ሰኞ ዙል-ሂጃ 9 መፆም እንዳንረሳ፡፡
የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ያለፈውን አመት እና የመጪውን አመት ወንጀል ያስምራል” ብለዋል፡፡ ኢማሙ ሙስሊም 1162 ዘግበውታል
የአላህ ባሪያዎች ሆይ! አላህ ለእኛ ለማዘን ብዙ ሰበቦችን አስቀምጦልናል፡፡ እኛም እንወቅበት፡፡ ሰኞ 9ኛው የዙል ሒጃ ቀንን በመፆም በአላህ ፍቃድ የሁለት አመት ወንጀላችንን እናስምር፡፡ ላልሰሙ ሙስሊሞች ሁሉ አድርሱት፡፡ የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ወደ መልካም ያመላከተ እራሱ እንደሰራው ነው” ብለዋል፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
ቢላዋን በደንብ መሳል
የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ስታርዱ አስተራረዳችሁን አሳምሩ፣ አንዳችሁ ቢላዋውን በድንብ ይሳል፣ የሚታረደውን ይገላግለው፡፡” ሙስሊም ዘግበውታል
https://t.me/SadatTextPosts
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem
የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ስታርዱ አስተራረዳችሁን አሳምሩ፣ አንዳችሁ ቢላዋውን በድንብ ይሳል፣ የሚታረደውን ይገላግለው፡፡” ሙስሊም ዘግበውታል
https://t.me/SadatTextPosts
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem
ተውሒድ
ተቀባይነት ያለው ዱኣ፣ ከዱኣ ሁሉ በላጭ ….
- የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ከዱኣ ሁሉ በላጭ የአረፋ ቀን ዱኣ ነው፡፡ ከምላቸው (ዱኣዎች ውስጥ) ምርጡ ዱኣ እኔና ከእኔ በፊት የነበሩ ነብዩች ያሉት [ላ ኢላሃ ኢለላህ ዋህደሁ ላሸሪከ ለሁ ለሁል ሙልክ ወለሁል ሀምድ ወሁወ ኣላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር] (ትርጉሙም ከአላህ በስተቀር በሐቅ የሚመለክ የለም፡፡ በብቸኝነት፣ ለእርሱም አጋር የለውም፣ ንግስና በጠቅላላ የእሱ ነው፣ ምስጋናም በጠቅላላ የእሱ ነው፣ እሱም ሁሉን ነገር በማድረግ ላይ ቻይ ነው፡፡”
የምንወስዳቸው ቁምነገሮች
- የዛሬው ቀን ወሳኝ የዱኣ ቀን እንደሆነ፡፡ ምክንያቱም የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ከዱኣ ሁሉ በላጭ የአረፋ ቀን ዱኣ ነው” ብለዋልና፡፡
- የተውሒድ ቃል “ላ ኢላሃ ኢለላህ ዋህደሁ ላሸሪከ ለሁ ለሁል ሙልክ ወለሁል ሀምድ ወሁወ ኣላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር” የነብዩ ሙሐመድም (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ሆነ የሌሎች ነብያት የሚጋሩት እና የተላኩበት መልክት እንደሆነ፡፡
- የሰው ልጅ ከእሳት ተጠብቆ ጀነት የሚገባው ይህችን ውድ የተውሒድ ቃል ሳያፈርሳት በውስጡ አምኖባት፣ በምላሱ እየተናገረ፣ በሰውነቱ ሲሰራባት ነው፡፡ ይህን ማድረግ ከቻለ አላህ በእዝነቱ ታላቁን ሽልማት ጀነት ይለግሰዋል፡፡ ከታላቁ ቅጣት ጀሀነም ይጠብቀዋል፡፡
- በዚህ ቀን ይህን ዱኣ ማብዛት፡፡ በነገራችን ላይ በሌላ ዘገባ በቀን 100“ላ ኢላሃ ኢለላህ ዋህደሁ ላሸሪከ ለሁ ለሁል ሙልክ ወለሁል ሀምድ ወሁወ ኣላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር” ያለ ሰው የቀኑ ኸይር ሰራተኛ ነው ከእሱ በላይ ያለ ሲቀር ብለው አዛኙ ነብይ ነግረውናል፡፡
- ዱኣ በሁለት ይከፈላል
o የጥየቃ ዱኣ፡- አላህ ሆይ! ጤና ስጠኝ፡፡ አላህ ሆይ! ልጅ ስጠኝ፡፡ አላህ ሆይ! ሚስት ስጠኝ፡፡
o የአምልኮ ዱኣ፡- አላህን ማምለክ በጠቅላላ እዚህ ውስጥ ይገባል፡፡ ለምሳሌ የአምልኮዎች ሁሉ ታላቁ አምልኮ የሆነውን ከላይ የተጠቀሰውን የተውሒድ ቃል አምኖበት ላለው ሰው ከዱኣ ሁሉ በላጭ የአረፋ ቀን የሚደረግ ነው፡፡ እኔም ከእኔ በፊት የነበሩ ነብያት ያሉት ሲሉ አዛኙ ነብይ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ነግረውናል፡፡ ከአላህ ጋር ያለን እውነተኛ የአምልኮ ትስስር ተውሒድ ሲያምር በተውሒድ ሰበብ ከጠፊዋ ዱንያ በላይ ያሉትን የእሱን ፊት ማየት፣ ጀነትን እና ፀጋዎቿን ይለግሰናል፡፡
አላህ በተውሒድ ኖረው በዛው መንገድ ላይ ከሚሞቱት ያድርገን፡፡ እኛንም ዝርያዎቻችንንም ከሺርክ ይጠብቀን፡፡
የአላህ ሰላትና ሰላም በሙሐመድ፣ በባለቤቶቻቸው፣ በባልደረባዎቻቸው እና ሐቅን በተከተሉ ላይ ሁሉ ይሁን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
ተቀባይነት ያለው ዱኣ፣ ከዱኣ ሁሉ በላጭ ….
- የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ከዱኣ ሁሉ በላጭ የአረፋ ቀን ዱኣ ነው፡፡ ከምላቸው (ዱኣዎች ውስጥ) ምርጡ ዱኣ እኔና ከእኔ በፊት የነበሩ ነብዩች ያሉት [ላ ኢላሃ ኢለላህ ዋህደሁ ላሸሪከ ለሁ ለሁል ሙልክ ወለሁል ሀምድ ወሁወ ኣላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር] (ትርጉሙም ከአላህ በስተቀር በሐቅ የሚመለክ የለም፡፡ በብቸኝነት፣ ለእርሱም አጋር የለውም፣ ንግስና በጠቅላላ የእሱ ነው፣ ምስጋናም በጠቅላላ የእሱ ነው፣ እሱም ሁሉን ነገር በማድረግ ላይ ቻይ ነው፡፡”
የምንወስዳቸው ቁምነገሮች
- የዛሬው ቀን ወሳኝ የዱኣ ቀን እንደሆነ፡፡ ምክንያቱም የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ከዱኣ ሁሉ በላጭ የአረፋ ቀን ዱኣ ነው” ብለዋልና፡፡
- የተውሒድ ቃል “ላ ኢላሃ ኢለላህ ዋህደሁ ላሸሪከ ለሁ ለሁል ሙልክ ወለሁል ሀምድ ወሁወ ኣላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር” የነብዩ ሙሐመድም (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ሆነ የሌሎች ነብያት የሚጋሩት እና የተላኩበት መልክት እንደሆነ፡፡
- የሰው ልጅ ከእሳት ተጠብቆ ጀነት የሚገባው ይህችን ውድ የተውሒድ ቃል ሳያፈርሳት በውስጡ አምኖባት፣ በምላሱ እየተናገረ፣ በሰውነቱ ሲሰራባት ነው፡፡ ይህን ማድረግ ከቻለ አላህ በእዝነቱ ታላቁን ሽልማት ጀነት ይለግሰዋል፡፡ ከታላቁ ቅጣት ጀሀነም ይጠብቀዋል፡፡
- በዚህ ቀን ይህን ዱኣ ማብዛት፡፡ በነገራችን ላይ በሌላ ዘገባ በቀን 100“ላ ኢላሃ ኢለላህ ዋህደሁ ላሸሪከ ለሁ ለሁል ሙልክ ወለሁል ሀምድ ወሁወ ኣላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር” ያለ ሰው የቀኑ ኸይር ሰራተኛ ነው ከእሱ በላይ ያለ ሲቀር ብለው አዛኙ ነብይ ነግረውናል፡፡
- ዱኣ በሁለት ይከፈላል
o የጥየቃ ዱኣ፡- አላህ ሆይ! ጤና ስጠኝ፡፡ አላህ ሆይ! ልጅ ስጠኝ፡፡ አላህ ሆይ! ሚስት ስጠኝ፡፡
o የአምልኮ ዱኣ፡- አላህን ማምለክ በጠቅላላ እዚህ ውስጥ ይገባል፡፡ ለምሳሌ የአምልኮዎች ሁሉ ታላቁ አምልኮ የሆነውን ከላይ የተጠቀሰውን የተውሒድ ቃል አምኖበት ላለው ሰው ከዱኣ ሁሉ በላጭ የአረፋ ቀን የሚደረግ ነው፡፡ እኔም ከእኔ በፊት የነበሩ ነብያት ያሉት ሲሉ አዛኙ ነብይ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ነግረውናል፡፡ ከአላህ ጋር ያለን እውነተኛ የአምልኮ ትስስር ተውሒድ ሲያምር በተውሒድ ሰበብ ከጠፊዋ ዱንያ በላይ ያሉትን የእሱን ፊት ማየት፣ ጀነትን እና ፀጋዎቿን ይለግሰናል፡፡
አላህ በተውሒድ ኖረው በዛው መንገድ ላይ ከሚሞቱት ያድርገን፡፡ እኛንም ዝርያዎቻችንንም ከሺርክ ይጠብቀን፡፡
የአላህ ሰላትና ሰላም በሙሐመድ፣ በባለቤቶቻቸው፣ በባልደረባዎቻቸው እና ሐቅን በተከተሉ ላይ ሁሉ ይሁን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
አላሁ (ሱብሃነሁ ወተአላ) እንዲህ ይላል።
وَمَا تَدْرِي نَفْسٌ مَاذَا تَكْسِبُ غَدًا ۖ وَمَا تَدْرِي نَفْسٌ بِأَيِّ أَرْضٍ تَمُوتُ ۚ إِنَّ اللَّهَ عَلِيمٌ خَبِير
ማንኛይቱ ነፍስም ነገ ምን እንደምትሰራ አታውቅም።
ማንኛይቱ ነፍስም የት እንደምትሞት አታውቅም።
አላህ አዋቂ ውስጥ አዋቂ ነው።
*************************
ሰው የት እንደሚሞት፣ መቼ እንደሚሞት ካላወቅ፣ በማንኛውም ቦታ እና ወቅት ለ ፍጡራን የማይቀረው ሞት ሳይቀድመው አላህን ሊፈራ ይገባዋል።
አላህ ሆይ! አንተን ከሚፈሩት ባሪያዎችህ አድርገን።
https://t.me/SadatTextPosts
وَمَا تَدْرِي نَفْسٌ مَاذَا تَكْسِبُ غَدًا ۖ وَمَا تَدْرِي نَفْسٌ بِأَيِّ أَرْضٍ تَمُوتُ ۚ إِنَّ اللَّهَ عَلِيمٌ خَبِير
ማንኛይቱ ነፍስም ነገ ምን እንደምትሰራ አታውቅም።
ማንኛይቱ ነፍስም የት እንደምትሞት አታውቅም።
አላህ አዋቂ ውስጥ አዋቂ ነው።
*************************
ሰው የት እንደሚሞት፣ መቼ እንደሚሞት ካላወቅ፣ በማንኛውም ቦታ እና ወቅት ለ ፍጡራን የማይቀረው ሞት ሳይቀድመው አላህን ሊፈራ ይገባዋል።
አላህ ሆይ! አንተን ከሚፈሩት ባሪያዎችህ አድርገን።
https://t.me/SadatTextPosts
በ Mohammed Ibrahim Ali
August 25 at 2:27 PM
#ዋቄፈና/Waaqeffannaa
.
.
ዋቄፈና በሀገራችን ከሚገኙ ዘልማዳዊ እምነቶች አንዱ ነው። በማእከላዊና ደቡባዊ ኢትዮጵያ ጥቂት የማይባሉ ተከታዮች የቀሩት እምነት ነው።
.
ከቅርብ አመታት ወዲህ ግን የብሄር ፓለቲካውን መነሳሳትን ተከትሎ ይህን ከጊዜ ጊዜ እየተመናመነ የሄደ ዘልማዳዊ እምነት መልሶ ለማንሳት የሚታትሩ ሰዎችን እያየን ነው።
.
.
#ዋቄፈና ምንድን ነው?
.
.
ስለዋቄፈና እምነት የሚገልፅ የእምነቱ መመሪያ መፅሀፍ የለም። እንዳውም ያለፈ ታሪኩን እንኳ የሚገልፅ ጥንታዊ ሰነድ አይገኝም። እንደ ተከታዮቹ ግንዛቤ በአንደበት ከሚተላለፈው እሳቤ በዘለለ የተጨበጠ እና አንድ አይነት ምልከታን የሚያስይዝ የጋራ ስምምነት የለውም። ለዛም ነው ዋቄፈና 'ዘልማዳዊ እምነት' የምንለው።
.
ዋቄፈና - ዋቃ/Waaqaa ከሚለው ቃል ተወስዶ ለእምነቱ መጠሪያነት እያገለገለ የሚገኝ ስያሜ ነው። ዋቃ በኦሮሚያ አካባቢ በሚገኙ አማኞቹ ዘንድ እንደ አምላክ የሚታሰብ አንዳንዶች ታላቅ ግኝ/Supreme being/ እንደሆነ ሌሎች ደግሞ ፈጣሪ እንደሆነ የሚያምኑበት ነው። 8
.
እምነቱ በከፊል ሰርጎ በገባባቸው እንደ አማራ ክልል ባሉ ቦታዎች 'ውቃቢ' እየተባለ ሲጠራ የሚሰጠው ባህሪ ግን ዋቄፈናዎች ዘንድ ካለው ፍፁም የተለየ ነው።
.
ወንድ የእምነቱ ተከታይ ዋቄፈታ/Waaqeffataa/ ሲባል ዋቄፈቱ/Waaqeffattuu/ ደግሞ ለሴት የእምነቱ ተከታይ የሚሰጥ መጠሪያ ነው፡፡
.
.
#የዋቄፈና እምነቶች
.
.
(እምነቱ የተፃፈ የወል መመሪያ ስለሌለው ከቦታ ቦታ ሊለያይ ይችላል)
.
.
* ዋቄፈናዎች 'ዋቃ' ድሮ ከሰዎች ጋር ይኖር ነበር ይላሉ፤ ሰዎች መጥፎ መስራት ሲጀምሩ ከነሱ ተለይቷል ብለው ያምናሉ።
.
* ዋቃ (አምላክ በነሱ እሳቤ) ጥቁር ነው ብለው ያምናሉ፤ በፀሎታቸውም ጥቁር አምላክ/Waaqaa gurracha ሲሉ ይጠሩታል።
.
* ዋቃን በሰማይ ይመስላሉ፤ መሬትም የዋቃ ሚስት ነች ብለው ያስባሉ። ይህንንም በምርቃትና እርግማኖቻቸው ይገልፁታል።
.
* ዋቃን ለመለማመን ወደ ተራሮች ይወጣሉ፤ እሱም በጥቁር ደመና ተመስሎ ይቀርበናል ብለው ያስባሉ።
.
* ለኦዳ/ዛፍ የተለየ ቦታ ይሰጣሉ። የተለያዩ እምነቶችንም በሱ ላይ ያሳድራሉ፤ ለመሬት መስዋእት ለማቅረብ በኦዳ/ዛፍ ስር ያርዳሉ። (አንዳንዶች የኦዳ ዛፍን እንደ እምነቱ ምልክት በመቁጠር ቅርፁን አንገታቸው ላይ ያስሩታል)
.
* ለምስጋና በሚል በዛፎች፣ በሀይቆችና ተራሮች ላይ የኢሬቻን በዓልን ያከብራሉ። ለዋቃ እርጥብ ሳርን በቁርባን መልክ ውሀ ላይ ይበትናሉ።
.
* 'ቃሉ' በመባል የሚጠሩ የዋቃን መልእክት ለህዝቡ የሚያደርሱ፣ የህዝቡንም ፀሎት ለዋቃ የሚያስተላልፉ ሰዎች አሉ ብለው ያምናሉ። (ቃሉዎች ልክ እንደ ጠንቋዮች ከጅኖች ጋር ቁርኝት እንዳላቸው ይገመታል)
.
[ እምነቱ በከፊል በሰረገባቸው ሌሎች ቦታዎች ጠንቋዮች 'ቃሉ/ቃልቻ' በመባል ይጠራሉ - ሆኖም 'ቃልቻ' የሚለውን ቃል ለሸሆች እንደተለዋጭ ስም የሚጠቀሙም እንዳሉ ልብ ይሏል]
.
* 'አያና' የሚባል የሞቱ ሰዎች መንፈስ አለ ብለው ያምናሉ። ያ መንፈስ በሰዎች ላይ እንደሚያድርም ያስባሉ። መንፈሱ አድሮባቸዋል የሚሏቸውንም ሰዎች አያና/አያንቱ ወይም ቃሉ/ቃሊቲ ብለው ይጠራሉ።
.
* አድባር እና አቴቴ የሚባሉ አማልክት በተለያየ በዓል እና ድግስ መልክ ምስጋናና ልመና ይቀርብላቸዋል።
[ይህ እምነቱ በከፊል በሰረገባቸው ማህበረሰቦችም ዘንድ ይታያል]
.
* የዋቄፈና እምነት ከአስተዳደራዊ የአባገዳ ስርአት ጋር ታሪካዊም መንፈሳዊም ቁርኝት አለው። (ይህንን መካድ የአፄዎቹ ስርዓት ከኦርቶዶክስ ክርስትና ጋር ቁርኝት አልነበረውም ብሎ እንደመሞገት ነው)
.
* ዋቄፈናዎች ከቀብር በኋላ ስላለው ህይወት ጥርት ያለ ምልከታ የላቸውም። በዚህና በሌሎችም አንዳንድ ነጥቦች ላይ ከሌሎች ሰማያዊ ሀይማኖቶች የተኮረጁ እምነቶችን ይቀላቅላሉ።
.
.
ይህ ከላይ የሰፈረው እንግዲህ ስለዋቄፈና እምነት በወፍ-በረር ጥቆማ ይሰጣል። እምነቱ ዘልማዳዊ እንደመሆኑ ያልደረጀ እና በተከታዮቹም ዘንድ ወጥ የሆነ ምልከታ የሌለው ነው።
.
ዋቄፈና ያልተብራሩ እምነቶችን ከመያዙም ጋር ከሌሎች ሃይማኖቶች በተኮረጁ ገለፃዎችም የተጠጋገነ ነው።
.
አንድ የሚያስማማን ነገር ግን እምነቱ በመሰረቱ ከአይሁድ፣ ከክርስትናም ሆነ እስልምና የተለየ መንገድን የሚከተል ግና ከዚህም ከዚያም እየኮረጀ በሁለት እግሩ ለመቆም የሚውተረተር መሆኑ ነው።
.
.
#ዋቄፈና ሌሎች ዘንድ...
.
.
ዋቄፈናን ሰዎች እንዴት እንደሚመለከቱት ስናስተውል ሶስት አይነት ሰዎችን እናገኛለን።
.
1. የመጀመሪያዎቹ ስለ እምነቱ የማያውቁ ሰዎች ሲሆኑ እይታቸው ከቃላቱ በመነሳት በተለይም 'ዋቃ' የሚለውን በመመልከት ብቻ ይህ ቃል የአምላክ የአፋን ኦሮሞ ስም እንደሆነ የሚገምቱና ከዚህ ያለፈ ግንዛቤ የሌላቸው ናቸው።
.
2. ሁለተኛዎቹ ስለእምነቱ ጥቂትም ቢሆን ግንዛቤ ያላቸው እና እምነቱን እንደባዕድ አምልኮ የሚቆጥሩ ናቸው።
.
3. ሶስተኛዎቹ ግን ስለእምነቱ ጥልቅ ግንዛቤ ያላቸው (ምናልባትም የሚያምኑበት) ሆኖም እምነቱን ከኦሮሞ ብሄርተኝነት ጋር በማቆራኘት ለማስፋፋት የሚጥሩና ይህም እንዳይታወቅባቸው በማድበስበስ የተጠመዱ ናቸው።
[እዚህ ጋር ግን ጥልቅ እውቀት ሳይኖራቸው በወገንተኝነት ብቻ ዋቄፈናን ከፍ ከፍ ለማድረግ የሚደክሙም እንዳሉ ልብ ይሏል]
.
የሶስተኛዎቹ ሰዎች ምልከታ ምናልባትም እምነቱን ከመክሰም በመታደግና ዘመናዊ ቁመና በማልበስ ወደ ገበያ ለመመለስ የሚፍጨረጨሩ እንዳሉ ያሳያል።
.
እነዚህ ሰዎች እምነቱ በሌሎች ሀይማኖቶች ዘንድ ጥርጣሬ እንዳያስነሳ ዋቄፈናን ከየሀይማኖቱ ለማመሳሰል ወይም የቃላት ትርጉም እንጂ ልዩነት እንደሌለ ለማሳመን ሲጥሩ ይስተዋላል።
.
በሌላ በኩል ደግሞ ዋቄፈና የኦሪት መሰረት ያለውና እስልምናንም ሆነ ክርስትናን የቀደመ እምነት እንደሆነ ሲደሰኩሩ ይሰማል። አያይዘውም የራሱ መርሆ እና ቀኖና እንዳለው ይሰብካሉ።
.
በግላጭ የሚታዩ የባዕድ አምልኮ ተግባራትን በመካድም ምንም አይነት ባዕድ አምልኮ እንደሌለ እንዳውም እምነቱ አሀዳዊ እንደሆነ ለመግለፅ ይሞክራሉ።
.
.
እኛስ ...
.
.
ከላይ በሶስተኝነት የተጠቀሱት አካላት ሰሞነኛ የፓለቲካ ትኩሳትን ተጠቅመው የተዘነጋውን ዘልማዳዊ እምነት ወደ ፊት ለማምጣት እየተሯሯጡ ነው። ይህን እያዩ ማለፍ ነገ ዋጋ ሊያስከፍል ስለሚችል እንደሙስሊም የምንችለውን ማድረግ ይኖርብናል።
.
እንደሚታወቀው እኛ ሙስሊሞች ሙሉ የሆነ እና ለየትኛውም ዘመን እና ህዝብ የሚመጥን ሀይማኖት ከጌታችን ተሰጥቶናል። ይህም በቁርአንና በነብያችን (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ሱና በበቂ ሁኔታ ተብራርቷል። በዓሊሞቻችን ትግልም ሳይበረዝ እኛ ዘንድ ደርሷል።
.
الْيَوْمَ أَكْمَلْتُ لَكمْ دِينَكُمْ وَأَتْمَمْتُ عَلَيْكُمْ نِعْمَتِي وَرَضِيتُ لَكُمُ الْإِسْلَامَ دِينًا
.
"ዛሬ ሐይማኖታችሁን ሞላሁላችሁ ፀጋዬንም በናንተ ላይ ፈፀምኩ፤ ከሐይማኖትም እስልምናን መረጥኩላችሁ" አል-ማኢዳ 3
.
ከዚህ ሀይማኖት ውጪ የሚሻ ወይም የሌላን አመለካከት ማስረግ የሚፈልግ ከቀጥተኛው ጎዳና እንደሚወጣና ራሱንም ለጥፋት እንደሚያጋልጥ በማስጠንቀቂያ ተናግሯል።
.
.
August 25 at 2:27 PM
#ዋቄፈና/Waaqeffannaa
.
.
ዋቄፈና በሀገራችን ከሚገኙ ዘልማዳዊ እምነቶች አንዱ ነው። በማእከላዊና ደቡባዊ ኢትዮጵያ ጥቂት የማይባሉ ተከታዮች የቀሩት እምነት ነው።
.
ከቅርብ አመታት ወዲህ ግን የብሄር ፓለቲካውን መነሳሳትን ተከትሎ ይህን ከጊዜ ጊዜ እየተመናመነ የሄደ ዘልማዳዊ እምነት መልሶ ለማንሳት የሚታትሩ ሰዎችን እያየን ነው።
.
.
#ዋቄፈና ምንድን ነው?
.
.
ስለዋቄፈና እምነት የሚገልፅ የእምነቱ መመሪያ መፅሀፍ የለም። እንዳውም ያለፈ ታሪኩን እንኳ የሚገልፅ ጥንታዊ ሰነድ አይገኝም። እንደ ተከታዮቹ ግንዛቤ በአንደበት ከሚተላለፈው እሳቤ በዘለለ የተጨበጠ እና አንድ አይነት ምልከታን የሚያስይዝ የጋራ ስምምነት የለውም። ለዛም ነው ዋቄፈና 'ዘልማዳዊ እምነት' የምንለው።
.
ዋቄፈና - ዋቃ/Waaqaa ከሚለው ቃል ተወስዶ ለእምነቱ መጠሪያነት እያገለገለ የሚገኝ ስያሜ ነው። ዋቃ በኦሮሚያ አካባቢ በሚገኙ አማኞቹ ዘንድ እንደ አምላክ የሚታሰብ አንዳንዶች ታላቅ ግኝ/Supreme being/ እንደሆነ ሌሎች ደግሞ ፈጣሪ እንደሆነ የሚያምኑበት ነው። 8
.
እምነቱ በከፊል ሰርጎ በገባባቸው እንደ አማራ ክልል ባሉ ቦታዎች 'ውቃቢ' እየተባለ ሲጠራ የሚሰጠው ባህሪ ግን ዋቄፈናዎች ዘንድ ካለው ፍፁም የተለየ ነው።
.
ወንድ የእምነቱ ተከታይ ዋቄፈታ/Waaqeffataa/ ሲባል ዋቄፈቱ/Waaqeffattuu/ ደግሞ ለሴት የእምነቱ ተከታይ የሚሰጥ መጠሪያ ነው፡፡
.
.
#የዋቄፈና እምነቶች
.
.
(እምነቱ የተፃፈ የወል መመሪያ ስለሌለው ከቦታ ቦታ ሊለያይ ይችላል)
.
.
* ዋቄፈናዎች 'ዋቃ' ድሮ ከሰዎች ጋር ይኖር ነበር ይላሉ፤ ሰዎች መጥፎ መስራት ሲጀምሩ ከነሱ ተለይቷል ብለው ያምናሉ።
.
* ዋቃ (አምላክ በነሱ እሳቤ) ጥቁር ነው ብለው ያምናሉ፤ በፀሎታቸውም ጥቁር አምላክ/Waaqaa gurracha ሲሉ ይጠሩታል።
.
* ዋቃን በሰማይ ይመስላሉ፤ መሬትም የዋቃ ሚስት ነች ብለው ያስባሉ። ይህንንም በምርቃትና እርግማኖቻቸው ይገልፁታል።
.
* ዋቃን ለመለማመን ወደ ተራሮች ይወጣሉ፤ እሱም በጥቁር ደመና ተመስሎ ይቀርበናል ብለው ያስባሉ።
.
* ለኦዳ/ዛፍ የተለየ ቦታ ይሰጣሉ። የተለያዩ እምነቶችንም በሱ ላይ ያሳድራሉ፤ ለመሬት መስዋእት ለማቅረብ በኦዳ/ዛፍ ስር ያርዳሉ። (አንዳንዶች የኦዳ ዛፍን እንደ እምነቱ ምልክት በመቁጠር ቅርፁን አንገታቸው ላይ ያስሩታል)
.
* ለምስጋና በሚል በዛፎች፣ በሀይቆችና ተራሮች ላይ የኢሬቻን በዓልን ያከብራሉ። ለዋቃ እርጥብ ሳርን በቁርባን መልክ ውሀ ላይ ይበትናሉ።
.
* 'ቃሉ' በመባል የሚጠሩ የዋቃን መልእክት ለህዝቡ የሚያደርሱ፣ የህዝቡንም ፀሎት ለዋቃ የሚያስተላልፉ ሰዎች አሉ ብለው ያምናሉ። (ቃሉዎች ልክ እንደ ጠንቋዮች ከጅኖች ጋር ቁርኝት እንዳላቸው ይገመታል)
.
[ እምነቱ በከፊል በሰረገባቸው ሌሎች ቦታዎች ጠንቋዮች 'ቃሉ/ቃልቻ' በመባል ይጠራሉ - ሆኖም 'ቃልቻ' የሚለውን ቃል ለሸሆች እንደተለዋጭ ስም የሚጠቀሙም እንዳሉ ልብ ይሏል]
.
* 'አያና' የሚባል የሞቱ ሰዎች መንፈስ አለ ብለው ያምናሉ። ያ መንፈስ በሰዎች ላይ እንደሚያድርም ያስባሉ። መንፈሱ አድሮባቸዋል የሚሏቸውንም ሰዎች አያና/አያንቱ ወይም ቃሉ/ቃሊቲ ብለው ይጠራሉ።
.
* አድባር እና አቴቴ የሚባሉ አማልክት በተለያየ በዓል እና ድግስ መልክ ምስጋናና ልመና ይቀርብላቸዋል።
[ይህ እምነቱ በከፊል በሰረገባቸው ማህበረሰቦችም ዘንድ ይታያል]
.
* የዋቄፈና እምነት ከአስተዳደራዊ የአባገዳ ስርአት ጋር ታሪካዊም መንፈሳዊም ቁርኝት አለው። (ይህንን መካድ የአፄዎቹ ስርዓት ከኦርቶዶክስ ክርስትና ጋር ቁርኝት አልነበረውም ብሎ እንደመሞገት ነው)
.
* ዋቄፈናዎች ከቀብር በኋላ ስላለው ህይወት ጥርት ያለ ምልከታ የላቸውም። በዚህና በሌሎችም አንዳንድ ነጥቦች ላይ ከሌሎች ሰማያዊ ሀይማኖቶች የተኮረጁ እምነቶችን ይቀላቅላሉ።
.
.
ይህ ከላይ የሰፈረው እንግዲህ ስለዋቄፈና እምነት በወፍ-በረር ጥቆማ ይሰጣል። እምነቱ ዘልማዳዊ እንደመሆኑ ያልደረጀ እና በተከታዮቹም ዘንድ ወጥ የሆነ ምልከታ የሌለው ነው።
.
ዋቄፈና ያልተብራሩ እምነቶችን ከመያዙም ጋር ከሌሎች ሃይማኖቶች በተኮረጁ ገለፃዎችም የተጠጋገነ ነው።
.
አንድ የሚያስማማን ነገር ግን እምነቱ በመሰረቱ ከአይሁድ፣ ከክርስትናም ሆነ እስልምና የተለየ መንገድን የሚከተል ግና ከዚህም ከዚያም እየኮረጀ በሁለት እግሩ ለመቆም የሚውተረተር መሆኑ ነው።
.
.
#ዋቄፈና ሌሎች ዘንድ...
.
.
ዋቄፈናን ሰዎች እንዴት እንደሚመለከቱት ስናስተውል ሶስት አይነት ሰዎችን እናገኛለን።
.
1. የመጀመሪያዎቹ ስለ እምነቱ የማያውቁ ሰዎች ሲሆኑ እይታቸው ከቃላቱ በመነሳት በተለይም 'ዋቃ' የሚለውን በመመልከት ብቻ ይህ ቃል የአምላክ የአፋን ኦሮሞ ስም እንደሆነ የሚገምቱና ከዚህ ያለፈ ግንዛቤ የሌላቸው ናቸው።
.
2. ሁለተኛዎቹ ስለእምነቱ ጥቂትም ቢሆን ግንዛቤ ያላቸው እና እምነቱን እንደባዕድ አምልኮ የሚቆጥሩ ናቸው።
.
3. ሶስተኛዎቹ ግን ስለእምነቱ ጥልቅ ግንዛቤ ያላቸው (ምናልባትም የሚያምኑበት) ሆኖም እምነቱን ከኦሮሞ ብሄርተኝነት ጋር በማቆራኘት ለማስፋፋት የሚጥሩና ይህም እንዳይታወቅባቸው በማድበስበስ የተጠመዱ ናቸው።
[እዚህ ጋር ግን ጥልቅ እውቀት ሳይኖራቸው በወገንተኝነት ብቻ ዋቄፈናን ከፍ ከፍ ለማድረግ የሚደክሙም እንዳሉ ልብ ይሏል]
.
የሶስተኛዎቹ ሰዎች ምልከታ ምናልባትም እምነቱን ከመክሰም በመታደግና ዘመናዊ ቁመና በማልበስ ወደ ገበያ ለመመለስ የሚፍጨረጨሩ እንዳሉ ያሳያል።
.
እነዚህ ሰዎች እምነቱ በሌሎች ሀይማኖቶች ዘንድ ጥርጣሬ እንዳያስነሳ ዋቄፈናን ከየሀይማኖቱ ለማመሳሰል ወይም የቃላት ትርጉም እንጂ ልዩነት እንደሌለ ለማሳመን ሲጥሩ ይስተዋላል።
.
በሌላ በኩል ደግሞ ዋቄፈና የኦሪት መሰረት ያለውና እስልምናንም ሆነ ክርስትናን የቀደመ እምነት እንደሆነ ሲደሰኩሩ ይሰማል። አያይዘውም የራሱ መርሆ እና ቀኖና እንዳለው ይሰብካሉ።
.
በግላጭ የሚታዩ የባዕድ አምልኮ ተግባራትን በመካድም ምንም አይነት ባዕድ አምልኮ እንደሌለ እንዳውም እምነቱ አሀዳዊ እንደሆነ ለመግለፅ ይሞክራሉ።
.
.
እኛስ ...
.
.
ከላይ በሶስተኝነት የተጠቀሱት አካላት ሰሞነኛ የፓለቲካ ትኩሳትን ተጠቅመው የተዘነጋውን ዘልማዳዊ እምነት ወደ ፊት ለማምጣት እየተሯሯጡ ነው። ይህን እያዩ ማለፍ ነገ ዋጋ ሊያስከፍል ስለሚችል እንደሙስሊም የምንችለውን ማድረግ ይኖርብናል።
.
እንደሚታወቀው እኛ ሙስሊሞች ሙሉ የሆነ እና ለየትኛውም ዘመን እና ህዝብ የሚመጥን ሀይማኖት ከጌታችን ተሰጥቶናል። ይህም በቁርአንና በነብያችን (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ሱና በበቂ ሁኔታ ተብራርቷል። በዓሊሞቻችን ትግልም ሳይበረዝ እኛ ዘንድ ደርሷል።
.
الْيَوْمَ أَكْمَلْتُ لَكمْ دِينَكُمْ وَأَتْمَمْتُ عَلَيْكُمْ نِعْمَتِي وَرَضِيتُ لَكُمُ الْإِسْلَامَ دِينًا
.
"ዛሬ ሐይማኖታችሁን ሞላሁላችሁ ፀጋዬንም በናንተ ላይ ፈፀምኩ፤ ከሐይማኖትም እስልምናን መረጥኩላችሁ" አል-ማኢዳ 3
.
ከዚህ ሀይማኖት ውጪ የሚሻ ወይም የሌላን አመለካከት ማስረግ የሚፈልግ ከቀጥተኛው ጎዳና እንደሚወጣና ራሱንም ለጥፋት እንደሚያጋልጥ በማስጠንቀቂያ ተናግሯል።
.
.
وَمَن يُشَاقِقِ الرَّسُولَ مِن بَعْدِ مَا تَبَيَّنَ لَهُ الْهُدَىٰ وَيَتَّبِعْ غَيْرَ سَبِيلِ الْمُؤْمِنِينَ نُوَلِّهِ مَا تَوَلَّىٰ وَنُصْلِهِ جَهَنَّمَ ۖ وَسَاءَتْ مَصِيرًا
.
"ቀናው መንገድ ከተገለጠለት በኋላ መልእክተኛውን የሚፃረር እና ከምእመናን መንገድ ሌላን የሚከተል በተሾመበት (ጥመት ላይ) እንሾመዋለን፣ ጀሀነምም እንዶለዋለን፣ መመለሻይቱም ከፋች" አ'ኒሳዕ 115
.
ስለሆነም የህይወት መመሪያችን የሆነውን እስልምና አጥብቀን በትክክለኛው ጎዳና እንዘልቅ ዘንድ ከእንዲህ አይነት የባህል ካባ የደረቡ እምነቶች ሙሉ በሙሉ ከመዘፈቅም ሆነ ጥቂቱን ከመቀበል ራሳችንን ልንጠብቅ ይገባል።.
.
ከዚህም ባሻገር አላዋቂ ወንድሞቻችን ተሳስተው ወደ ጥፋት እንዳይገቡ ልንታደጋቸው ይገባል። እንዲሁም እምነቱ እንደ ክርስትናና አይሁድ እምነት እንደማይቆጠር የነርሱንም ሑክም/ብያኔ እንደማያገኝ ልብ ማለት ያስፈልጋል።
.
ነገር ግን ስለዋቄፈና ስንናገር ጉዳዩን ከብሄር ጋር በማቆራኘት ከመቃወምም ሆነ ከመከላከል ልንቆጠብ ይገባል። ሁለቱም አካሄድ የማንፈልገውን ያመጣልና።
.
በመጨረሻም ጉዳዩ የተለየ ትኩረት ተሰጥቶት ዓሊሞችና ዱዓቶች ህዝቡ በሚረዳው ቋንቋ ትምህርት እንዲሰጡ ማስታወስ ያስፈልጋል።
.
.
አላህ በቀናው መንገድ ላይ ያፅናን!
.
"ቀናው መንገድ ከተገለጠለት በኋላ መልእክተኛውን የሚፃረር እና ከምእመናን መንገድ ሌላን የሚከተል በተሾመበት (ጥመት ላይ) እንሾመዋለን፣ ጀሀነምም እንዶለዋለን፣ መመለሻይቱም ከፋች" አ'ኒሳዕ 115
.
ስለሆነም የህይወት መመሪያችን የሆነውን እስልምና አጥብቀን በትክክለኛው ጎዳና እንዘልቅ ዘንድ ከእንዲህ አይነት የባህል ካባ የደረቡ እምነቶች ሙሉ በሙሉ ከመዘፈቅም ሆነ ጥቂቱን ከመቀበል ራሳችንን ልንጠብቅ ይገባል።.
.
ከዚህም ባሻገር አላዋቂ ወንድሞቻችን ተሳስተው ወደ ጥፋት እንዳይገቡ ልንታደጋቸው ይገባል። እንዲሁም እምነቱ እንደ ክርስትናና አይሁድ እምነት እንደማይቆጠር የነርሱንም ሑክም/ብያኔ እንደማያገኝ ልብ ማለት ያስፈልጋል።
.
ነገር ግን ስለዋቄፈና ስንናገር ጉዳዩን ከብሄር ጋር በማቆራኘት ከመቃወምም ሆነ ከመከላከል ልንቆጠብ ይገባል። ሁለቱም አካሄድ የማንፈልገውን ያመጣልና።
.
በመጨረሻም ጉዳዩ የተለየ ትኩረት ተሰጥቶት ዓሊሞችና ዱዓቶች ህዝቡ በሚረዳው ቋንቋ ትምህርት እንዲሰጡ ማስታወስ ያስፈልጋል።
.
.
አላህ በቀናው መንገድ ላይ ያፅናን!