Sadat_Text_Posts
10K subscribers
291 photos
8 videos
12 files
378 links
Download Telegram
ማን ነው ‹‹ሸሂድ (ሰመዓት)፣RIP (Rest in Peace)›› የሚባለው?
አንዳንድ ወንድምና እህቶች በአላህና በመልክተኛው መታመን ባለበት ሁሉ የማያምኑ ካፊሮችን ‹‹ሸሂድ (ሰመዓት)፣ RIP (Rest in Peace)›› ብለው ሲፅፉና ሲናገሩ ይሰማል፡፡ ይሄ ከባድ ስህተት ነው፣ እርምት ይሻል፡፡
አደለም በአላህ፣ በመልክተኛው መታመን ባለበት ሁሉ ያላመነን ካፊር፣ ሙስሊም የሆነን ሰው እንኳን አላህና መልክተኛው (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ከመሰከሩለት ሰው ውጭ እኛ ከመሬት ተነስተን ‹‹ሸሂድ (ሰመዓት)›› አንለውም፡፡
ኢማም አል-ቡኻሪ በሰሂሀል-ቡኻሪ ‹‹እገሌ (እንትና) ሸሂድ (ሰመዓት) አይባልም›› ብለው አርስት አዘጋጅተው የሚከተለውን ሀዲስ ዘግበውልናል
ሰህል ኢብን ሰዓድ አሳኢድይ (ረድየላሁ አንህ) ‹‹የአላህ መልክተኛ (ﷺ) እና ሙሽሪኮች ፊት ለፊት ጦር ተጋጥመው ነበር፡፡ የአላህ መልክተኛም (ﷺ) ሙሽሪኮችም ወደ ካምፓቸው ሲመለሱ፣ ስለ አንድ ብቻውን ያገኘውን ሙሽሪክ ሁሉ በሰይፉ ስለሚገድል ባልደረባቸው አንድ ሰው አወራ፡፡ እንዲህም አለ ‹‹ዛሬ እንደዛ ሰው በትክክል ስራውን (ውጊያውን) የሰራ የለም››
የአላህ መልክተኛ (ﷺ) ግን ‹‹ይህ ሰው ከእሳት ሰዎች ነው፡፡›› አሉ፡፡
ከሰዎች አንዱ ይህን ሰው መከታተል አለብኝ አለ (የአላህ መልክተኛ (ﷺ) የእሳት ነው ያሉትን ሰው ማለት ነው)
አብሮትም ሆነ ሲቆም ይቆማል፣ ሲሮጥ ይሮጣል፡፡ (ጀግና) የተባለው ሰውየም ቆሰለ ሞቱንም ማፍጠን ፈለገ፡፡ የሰይፉን መያዣ መሬት ላይ ቀበረውና ሁሉቱ ደረቶቹ መሃል ላይ አድርጎ ሰይፉ ላይ ተኛበት በዛውም ሞተ፡፡
ሌላኛው ሰውዬ የአላህ መልክተኛ (ﷺ) ዘንድ መጥቶ ‹‹የአላህ መልክተኛ መሆኖትን እመሰክራለሁ›› አላቸው፡፡ አል-ቡኻሪ 2898 ……………….
ከዚህ የምንረዳው የአላህ መልክተኛ (ﷺ) ከመሰከሩለት ሰው ውጭ እኛ አንድን ሰው ሸሂድ ነው፣ ለዲን ሲል ነው የሚታገለው ማለት አንችልም፡፡ ምክንያቱም ለአላህ ብሎ የሚታገለውን አላህ ብቻ እንደሚያውቀው አቡሁረይራ ባስተላለፉት
وَاللَّهُ أَعْلَمُ بِمَنْ يُجَاهِدُ فِي سَبِيلِهِ
‹‹አላህ የበለጠ ያውቃል ማን በእሱ መንገድ ላይ እንደሚታገል›› ሀዲስ የአላህ መልክተኛ (ﷺ) ነግረውናል ሰሂሀል አል-ቡኻሪ 2787፡፡

RIP (Rest in Peace) በሰላም እረፍ እንደማለት ነው፡፡ ይህን አባባል ከሙስሊም ውጭ ለሆነ ሰው መጠቀም በፍፁም አይገባም፡፡ ምክንያቱም የሚቀጥለው አለም ጌታ አላሁ ሱብሃነሁ ወተዓላን በትክክለኛ እምነት፣ በንፁህ ልብ፣ በነብዩ (ﷺ) ሱና፣ መታመን ባለበት ሁሉ አምኖ ለሄደ ብቻ ነው ሰላም ያለው፡፡ ከዛ ውጭ ግን ከባድ አደጋ ነው፡፡ አላህ የሚቀጥለው አለም ለነማን እንደሆነ ሰላም ያለው እንዲህ ሲል ይናገራል
ውዱ የአላህ ባርያ ነብየላህ ኢብራሂም (አለይሂ ሰላም) እንዲህ አለ
وَلَا تُخْزِنِى يَوْمَ يُبْعَثُونَ
በሚቀሰቀሱበት ቀንም አታዋርደኝ፡፡
يَوْمَ لَا يَنفَعُ مَالٌ وَلَا بَنُونَ
ገንዘብም ልጆችም በማይጠቅሙበት ቀን፡፡
إِلَّا مَنْ أَتَى ٱللَّهَ بِقَلْبٍ سَلِيمٍ
ወደ አላህ በንጹህ ልብ የመጣ ሰው ቢኾን እንጅ፡፡»
ይህ ነው እንግዲህ ተጨባጩ ሁኔታና እውነታ፡፡ ዛሬ ሙስሊም ያልሆነ ዘፋኝ፣ አርቲስትና የመሳሰለው ሲሞት RIP (Rest in Peace) እያሉ የሚፅፉ ስንቶች ናቸው፡፡ አላህ እውቀትን ይስጠንና፡፡
ማጠቃለያ፡-
1) ለካፊር ሰመዓት (ሸሂድ) አይባልም፣
2) ለሙስሊምም በጥቅሉ በአላህ መንገድ ላይ የሞተ ሸሂድ ነው እንላለን እንጂ እከሌ ብለን አንድን ሰው ነጥለን ሸሂድ ነው አንልም፡፡ ምክንያቱም መለኮታዊ ራእይ የማይለያቸው ነብዩ (ﷺ) ብቻ ናቸው እንዲህ ብለው ሊናገሩ የሚችሉት፡፡ እሳቸው ደግሞ ሞተዋል፡፡ በሳቸው ሞት ደግሞ መለኮታዊ ራእይ ተቋርጧል፡፡ ከሳቸው ባኋላ ማንም ይህን መናገር አይችልም፡፡ ኢንሻ አላህ ሸሂድ ይሆናል ብለን ግን መመኘትና ዱዐ ማድረግ ችግር የለውም፣
3) ለካፊር RIP (Rest in Peace) አይባልም፣
4) ሙስሊም የሆነ ሰው ሲሞት እንዲያውም ዱዓ እናደርግለታለን፡፡ አላህ ይዘንልህ/ሽ፣ ይማርህ/ሽ፣ ቀብርህን/ሽን ያስፋልህ/ልሽ እያልን፡፡

አላህ ሸሪዐችንን ጠንቅቀን የምናውቅ፣ የምንሰራበትም፣ የምንፀናበትም ያድርገን፡፡ ከአላህ ውጭ ሃይልም ጥበብም ብልሃትም የለም፡፡
የአላህ ሰላትና ሰላም በነብያት ሁሉ መደምደሚያ፣ በቤተሰቦቻቸው፣ በባልደረባዎቻቸው፣ ሃቅን በተከተለ ላይ ሁሉ ይሁን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
Channel photo updated
ጥያቄ፡- “ፌስ ቡክ ላይ ተውሒድ ተውሒድ ትላላችሁ፡፡ ለምን ክፍለ ሀገር አትሄዱም?”
መልስ፡- ክፍለ ሀገር ሄደን ዳእዋ ስናደርግ ፎቶ ተነስተን መልቀቅ የለብንም፡፡ እውነታው ደግሞ አብዛኛዎቹ በፌስቡክ የሚለቀቁ ዳእዋዎች ክፍለ ሀገር ተደርገው የተቀዱ ናቸው፡፡ በአላህ ፍቃድም በሜሞሪ መብራት የሌለባቸው፣ በሶላር የሚሰሩ፣ ከተማ ቻርጅ ተደርገው የሚመጡ ስልኮች ላይ ሁሉ ይህን የተውሒድ ጥሪ አላህ በፍቃዱ አሰራጭቶልናል፡፡ በጣም ገጠር የሚባለው ቦታ ላይ ሁሉ በአላህ እገዛ ገበሬዎች ሁሉ ጭምር እንደሚሰሙት ተረጋግጧል፡፡
ይልቁንስ አብዛኛው ህዝብ በሺርክ፣ በቢድኣ፣ በጫት ተዘፍቆ እያለ የማይመለከታቸው ፖለቲካ ውስጥ ገብተው፣ የተወለዱበት ክፍለ ሀገር ውስጥ ስንት ሺርክ እያለ ዩሮፕ እና አረብ ሀገራት ላይ የሚመላለሱትን ፖለቲከኞች “ለምን ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ቅድሚያ የሰጡትን ተውሒድ ቅድሚያ አትሰጡም” ብለው አይጠይቀዋቻም?”
በአላህ ፍቃድ እና እገዛ ሶሺያል ሚድያን ተጠቅመን ከአዲስ አበባ እስከ ክፍለ ሀገር ብሎም አለም ላይ ሐቅ ይሰራጫል፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
“ዝናቡ እኝኝ አለ፡፡ ዉይ አሰለቸን እኮ”
አንዳንድ ግለሰቦች ክረምት ላይ የሚዘንበው ዝናብ አመቱን ሙሉ የሚጠጣ ውሃ ብለን የምንጠጣው እንደሆነ አይገነዘቡም፡፡ አላህ በእዝነቱ ዝናብ አዝንቦልን ሲያበቃ እኛ “ኡፍ፣ ኤጭ“ ምናምን እያልን መበሳጨታችን፣ የእኛን አላዋቂነት፣ የአላህን እዝነት እና ጥበብ አለመረዳታችንን ነው የሚያስይዘው፡፡
ይልቁንስ ዱኣ ተቀባይነት ከሚያገኝባቸው ወቅቶች ውስጥ ዝናብ ሲዘንብ ነውና፣ ይህ የአላህ እዝነት በሚወርድበት ወቅት ከመበሳጨት ይልቅ አላህን እናመስግን ዱኣም እናድርግ፡፡
እኛ ሰዎች አብዛኛዎቻችን አስቸጋሪዎች ነው፡፡ ሲቸግረን እንነጫነጫለን፣ የአላህ ፀጋ ሲሰጠን እናስተባብላለን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
ሐጅ ዘንድሮም ግዴታ ነው፡፡
አላህ ግዴታ ያደረገውን ማንም ሊሽረው አይችልም፡፡ “መንገዱ ሰላም አይደለም” የሚል ውሸት እየሰማን ነው፡፡ የመን ጦርነት ቢኖር በጅቡቲ በኩል ነው አውሮፕላን እየበረረ ያለው፡፡ ሳውዲ ውስጥም ጦርነት የለም፡፡ ስለዚህ “መንገዱ ሰላም አይደለም” የሚለው ውሸት ከማንም ቢመጣ እንዳትቀበሉ፡፡
“ህገ ወጡ መጅሊስ ዘራፊ ነው፡፡ እነሱ ከስልጣን ካልወረዱ ዘንድሮ ሐጅ ግዴታ አይደለም” የሚላችሁን እንዲህ በሉት

- አምናም ይህ ህገወጥ መጅሊስ ይዘርፍ ነበር “ለምን ሐጅ አደረግን”፣
- ከአህባሹ በፊት የነበረው ሌላኛው ዘራፊ የሱፊያ መልጂስም ሙስሊሙን ከላይ እስከ ታች ሲዘርፈው ነበር፣ ሀጅ ላይም ሲያሰቃየው ነበር ታድያ ለምን ይህን ነገር መቀስቀስና ይህኛውን ዘራፊ ብቻ መናገር አስፈለገ?

ሙስሊሞች ሆይ! ንቁ፡፡ ሐጅን በህይወት አንድ ጊዜ፣ በቻለ ሰው ላይ አላህ ግዴታ አድርጎታል፡፡ አላህ ግዴታ ያደረገውን ማንም ሊሽረው አይችልም፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
ሙስሊሞች ከነዚህም ተጠንቀቁ፡፡
የፔንጤን ተንኮል ተጠንቀቁ፣ የአሕባሽን ተንኮል ተጠንቀቁ ተብሎ በማስረጃ ሲነገር የጀዛከላህ መኣት የምታዘንቡ ሙስሞች ሆይ! በሺርክ መንዙማቸው ወደ ክህደት የሚጣሩትን፣ በቢድኣቸው፣ ከኢስላም ባፈነገጡ ትምህርቶቻቸው ሙስሊሙን ጠመው የሚያጠሙ ሁሉ ስማቸውም በማስረጃ ተጠንቀቋቸው ሲባል ይህንንም ልንቀበል ይገባናል፡፡ አለበለዚያ ፔንጤውን እና አህባሹን ምን ይዘው ስለመጡ ነበር የተቃወምናቸው የሚለው ለነፍሳችን ከባድ ጥያቄ ይሆናል፡፡
ሙሐመድ አወል ሐምዛ እና ሌሎች ጓደኞቹ ኡመተል ኢስላምን ከተውሒድ ወደ ክህደት በአደባባይ ሲጣሩ መልስ ሲሰጥባቸው የከፋው ካለ መጀመሪያውንም ሰውን የሚወደውም የሚጠላውም ለአላህ ሲል አይደለምና እራሱን ይመርምር፡፡
እኛ ከብቸኛዋ፣ ከቀጥተኛዋ አንድ መንገድ ውጭ ያሉትን ማንኛውንም የጥመት መንገድ ይዞ የመጣን ቡድንም ይሁን ግለሰብ ልንቃወም ብሎም ሙስሊሞችን ልናስጠነቅቅ ይገባናል፡፡ አህባሽን ብቻ ተቃውሞ ሱፍያን፣ አሽአሪያ፣ ኢሕዋንን፣ ተብሊግን…. የተለያዩ የጥመት ቡድኖች ዝም ማለት፣ ብሎም አትንኳቸው ማለት የጥመት ምልክት ነው፡፡ ይህ ነው ኡማውን ከቀጥተኛው መንገድ ለያይቶ ሰዎችን በተለያየ የጥመት መንገድ ላይ ወደ እሳት እንዲጓዙ ማመቻቸት፡፡
በነገራችን ላይ ማንም የተደራጀውን ያህል ቢደራጅ፣ ያቀደውን ያክል ቢያቅድ፣ ያወጣውን ያህል ገንዘብ ቢያወጣ ሐቅ አንድ እና አንድ ብቻ ናት፡፡ እሷም የጥንት የጠዋቷ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እና ባልደረባዎቻቸው እነሱን በበጎ የተከተሉ ያሉባት መንገድ፡፡ ከዚህ ውጭ ያሉት የለፉትን ያህል ቢለፉ ሺርክን ተውሒድ አድርገው ለማቅረብ ቢሞክሩ፣ ቢድኣን ሱና አድርጎው ለማቅረብ ቢሞክሩ፣ ዘረኝነትን የተቀደሰ አድርገው ለማቅረብ ቢሞክሩ፣ ይህን አደንዛዥ ቅጠል ጫት የኢስላም አካል አድርገው ለማቅረብ ቢሞክሩም አላህ እያንዳንዷን ነገር ተመልካች ስለሆነ አያሳካላቸውም፡፡ ከዚህ በፊት እንደቀመሱት ውርደትን ቢቀምሱ እንጂ ሌላን አያመጡም፡፡
ከእኛ የሚጠበቀው ከማንም ይምጣ ከማን ጥመትን ማጋለጥ፡፡
አላህ ሆይ! ሐቅን በሐቅነቱ አሳየን የምንቀበለውም አድርገን፡፡ ባጢልን በባጢልነቱ አሳየን የምንርቀውም አድርገን፡፡
የአላህ ሰላት እና ሰላም በነብያችን፣ በሰሃባዎቻቸው፣ በባለቤቶቻቸው እና ሐቅን በተከተለ ላይ ሁሉ ይሁን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
ሰውን ማታለል ቢቻልም አላህን ግን በፍፁም ማታለል አይቻልም፡፡
“አህባሽ ብልሹ አቂዳ አለው፣ ተክፊር ነው፣ መጅሊሱን አህባሽ ሙሉ ለሙሉ ካለቀቅ ትግላችን አይቆምም፣ ተከትለናቸው አንሰግድም ካፊሮች ናቸው….” እና የመሳሰሉትን ሁሉ ያለ፣ ስለ አህባሾች የተናገረው እውነቱን ከነበር፣ ለአቂዳቸው ከተጣላቸው፣ ዛሬ በአንድ ጀንበር አህባሾች ከዚህ ሁሉ መጥፎ እምነታቸው ሳይመለሱ “አውፍ ተባብለናል… በጋራ አብረን እንሰራለን” ብለው ያውም ተቃቅፈው እና ተሳስቀው ስናያቸው ጌታችን አላህ ሐቁን ስላወጣልን ከልብ እናመሰግነዋለን፡፡
ሰው ከዲን ጋር ያልተያያዘ፣ ጠቡን አውፍ (ይቅር ይቅር) ይባባላል፡፡ ከዛ ውጭ የሀይማኖት ልዩነት ሲመጣ መንገድ የሳተው ወደ ሐቁ እስኪመለስ ድረስ በማስረጃ ትፋለመዋለህ፡፡ ከተመለሰ እሰየው፡፡ ካልተመለስ ከእሱ እና ይዞ ከመጣው ሃይማኖትን ከሚጋጨው ነገር እያስጠነቀቅክ ጠላትንት ይፋ ሆኖ ትቀጥላለህ፡፡ ይህም የሆነበት ምክንያት የአላህ ዲን ስለተነካ፣ ውዴታና ጥላቻ ደግሞ የሚመሰረተው ለአላህ ተብሎ ስለሆነ፡፡ ይህን የጥፋት ቡድን፣ መሪዎቹ፣ ተጣሪዎችን የግል ጠብ ኖሮህ ሳይሆን ለአላህ ስትል ትጣላቸዋለህ፡፡ ለአላህ ስትል የተጣላሀውን ሰው ደግሞ ለአላህ ስትል የምትታረቀው ያ ያጠፋውን የተሳሳተ እምነት ሲያስተካክል እና ማስተካከያ ሲሰጥ ብቻ እና ብቻ ነው፡፡ አለበለዚያ ዝም ብለህ ከተታረቅከው መጀመሪያውን በሃይማኖት ሽፋን ተጠቅመህ እንጅ ለአላህ ስትል አልነበረም የተጣላሀው፡፡
አላህ ደግሞ ውስጥ አዋቂ ነው፡፡ ማን ለዲኑ ማን ለግል ጥቅሙ እና ዱንያ ሲል እንደሚጣላ ጠንቅቆ ያውቃል፡፡ አላህ በራጅ፣ በሲቲ እስካን፣ በኤም አር አይ የማይገኘውን ሁሉ የተደበቀ ነገር በጠቅላላ ያውቃል፡፡ አላህ በልብ ውስጥ ያለውን፣ የቅርቡን የሩቁንም ያውቃል፡፡ ሰውን በተለይ ምስኪኖችን ማታለል ቢቻልም፣ አላህን ግን ማታለል አይቻልም፡፡ የፍርዱ ቀን አላህ ውስጥ የተደበቀውን ሁሉ አውጥቶ ፍርድ ስለሚሰጥ የጌታችንን ፍርድ በትግስት እንጠብቃለን፡፡
ከዚህ በላይ ምን ሐቁ ይውጣ፡፡ እራሳቸውን በራሳቸው ጊዜ አጋልጠዋል፡፡ ሐቅን ለሚቀበል ኢኽዋን እና አህባሽ የአቂዳ (የእምነት) ልዩነት (ጠብ) እንደሌላቸው በግልፅ ይመለከታል፡፡ ከዚህ በፊት በኢኽዋን ፍልስፍና የተመረዘ አንድ ወጣት “አህባሽን ለፖለቲካል አጀንዳው ብቻ ነው የምንቃወመው” ሲል ከፖለቲካ ውጭ ያለውን መርዝ የሆነ (የአህባሾችን) እምነታቸውን እንደማይቃወም “ብቻ” በሚለው ቃሉ ገልፆ ነበር፡፡ አስገራሚው ኡመተል ኢስላም እነዚህን አይነት ሰዎችን ስለሆነ የሚከተለው ቁም ሲሉት ይቆማል፣ ቁጭ በል ሲሉት ቁጭ ይላል፣ አህባሽን ተከትለህ እንዳትሰግድ ሲሉት አይሰግድም፣ ወድያው አቋማቸውን ቀይረው አህባሾች መሲጂድ ግቡ ሲሏቸው ይገባሉ፣ ኑር (በኒ) መስጂድ ሄደህ ከጁምኣ ሰላት በኋላ ፊኛ ነፍተህ ወደ ላይ ልቀቅ ሲሉት ይለቃል….. ሌላም ሌላም፡፡
ሙስሊሞች ሆይ! ንቁ፡፡ አላህ ያንቃን፡፡ እስከመቼ ጭፍን ተከታይ ሆናችሁ ህይወታችሁን፣ ንብረታችሁን፣ ጊዜያችሁን ለውሸት መስዋት ታደርጋላችሁ?
ከኢማን ስራ ሁሉ በላጭ ለአላህ ብሎ መውደድ ለአላህ ብሎ መጥላት ነው፡፡ ማንም ይናገር ማን በሸሪኣ ማስረጃ ያልተገኘለትን ነገር አሽቀንጥራችሁ ጣሉት፡፡ ከእንዲህ አይነት በየጊዜው ተለዋዋጭ ሰዎች እና ቡድኖች እራሳችሁንም ቤተሰባችሁንም ጠብቁ፡፡ ተጠንቀቁም አስጠንቅቁም፡፡
ጌታዬን አላህ አመሰግነዋለሁ፡፡ በዚህ ባለፉት አመታት በፈተናው ወቅት በነበርኩበት አቋም ላይ ላፀናኝ፡፡ ስለ ኢኽዋኖችም ተንኮል እና ተለዋዋጭነት በተግባር አሳይቶኝ ልቤን በኢማን ላፀናልኝ እና ላደላደለልኝ፡፡ አላህ ከዚህም በኋላ ከሚመጡ ፈተናዎች ይጠብቀን፡፡ በሐቅ ላይ ያፅናን፡፡
የአላህ ሰላትና ሰላም በነብያት ሁሉ መደምደሚያመ በባለቤቶቻቸው፣ በባልደረባዎቻቸው እና ሐቅን በተከተለ ላይ ሁሉ ይሁን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
Channel photo updated
መውሊድ?

ነብዩ ከሞቱ ከ1400 አመት በላይ ተቆጥሯል፡፡
ሰው ከሞተም በኋላ የልደት በአሉ ይከበርለታልን?
እንደ ውቡ፣ ሙሉው እስልምና ከሆነ፣ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) የተወለዱበትን ቀን አመት ጠብቀው በህይወት በነበሩበት ጊዜ እንኳን አንድም ጊዜ የራሳቸውንም ይሁን የሌሎች ነብያት ወይንም የሌላን ግለሰብ አላከበሩም፡፡ አይደለም ሰው ሞቶ ልደቱ ሊከበር ቀርቶ፡፡
ግን አሳዛኙ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) የተወለዱበት ቀን በቁርጥ ባይታወቅም፣ የሞቱበት ቀን ግን አሁን ሰዎች ረቢአል አወል 12 እያሉ የሚጨፍሩበት ቀን ነው፡፡ ሰይጣን ይህን ያህን የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምን) ዲን ነብዩን እንወዳለን በሚል ስም ሲንዱት ተግባራቸውን አሳምሮ አቀረበላቸው፡፡

አላህ በሱና ከሚብቃቁት ያድርገን፡፡ የነብዩን ሱና በቢድኣ ከመናድ ይጠብቀን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
አሰላሙአለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱሁ የአላህ ባሪያዎች ሆይ!
አል-ቀዋኢዱል አርበኣ ሙሉው ደርስ ከክፍል አንድ እስከ ክፍል አራት ከሚከተለው የቴሌግራም ቻናል ማውረድ ትችላላችሁ፡፡
https://t.me/Kitaboch
ከዚሁ የተመሳሳይ ቻናል
1) አቂደቱል ዋሲጥያ ሙሉ ደርስ፣
2) ኡሱሉ ሰላሳ ሙሉ ደርስ፣
3) ኹዝ አቂደተክ እምነትህም ከቁርኣን እና ከሀዲስ ያዝ ሙሉ ደርስ፣
4) አል-ዋጂባት ሙሉ ደርስ ማግኘት ትችላላችሁ
ላልደረሳቸውም አድርሱት
ከ200 መቶ በላይ ለሚሆኑ የድምፅ ፋይሎች ከሚከተሉት የቴሌግራም ቻናል ማውረድ ትችላላችሁ
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem
አላህ ይቀበለን፡፡
"የአላህን ህግጋቶች ብትከተሉ አላህ ይረዳችሇል"

አላህ እና መልክተኛውን (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እያመፁ ኢስላምን መርዳት ይቻላልን ወይንም ኢስላም እርዳታ ማግኘት ይችላልን???
======================

1) ሽርክ ፈጦ እየታየ፣
2) የሽርክ እና የጭፈራ መንዙማዎች በየመንገዱ በትልቅ ስፒከር እየተደመጡ፣
3) ቢድዓ በአይነታው ተንሰራፍቶ፣
4) የወላጆች ሃቅ ተጓድሎ
5) በስሜት እና መሃይምነት መመራት፣
6) ዲን ምን ይላል ሳይሆን ኢንተርኔት ላይ ያለን ማንነቱ የማይታወቅን ካፊር ይሁን ሙስሊም አለ ብሎ መከተል፣
7) ፊልም፣ ድራማ፣ አርት እያሉ ወንድ እና ሴት መጨባበጥ፣ የአጅነቢዮችን ምስል አላህ ቤት ላይ ለጥፎ መስጂዶችን ማቆሸሽ፣
8) ኢስላም ውሸትን ከልክሎ ሲያበቃ፣ በቻናል ላይ የሌለን የውሸት ታሪክ ድራማ ብሎ ከካፊር ተመሳስሎ ሰዎችን ከቁርዓን ማዘናጋት፣
9) ሴት ልጆች አላህ እና መልክተኛው የረገሙትን "ቅንድብ ማስቀንደብ እና መቀንደብ፣ ዊግ መቀጠል እና ማስቀጠል፣ ንቅሳት መንቀስ እና ማስነቀስ"፣ መጥፎ አለባበስ እየለበሱ፣
10) ወንዶች ኳስ፣ ጫት እያሉ ጀመዓ ሰላትን ትተው (በወንድ ላይ ግዴታ ነው ጀመአ ሰላት)፣ ጭራሽ የማይሰግድም ብዙ አለ፣
11) ነጋዴዎች ዘካን በስነስርአት ሳያወጡ፣
12) ዝሙት ተንሰራፍቶ፣ ኒካህ ላይ የጣጣ መዓት ተደርድሮበት፣
እና የመሳሰሉት ሁሉ ችግሮች እያሉ ከፈተና መውጣት ይቻላል???

በፍፁም፣ አይታሰብም ጭራሽ ፈተናው ቢብስ እንጂ።

የሀዲስ ሊቅ የሆኑት ሸይቭ አልባኒ (ረሂመሁላህ) "ኢንተንሱሩላህ የንሱርኩም" የሚለውን አንቀፅ ሲያብራሩ "የአላህን ህግጋቶች ብትከተሉ አላህ ይረዳችሇል" ብለዋል።

እስቲ ግዜ ሳንሰጥ ዛሬውን በጣም አሳሳቢ የሆነውን አገራችን ላይ የተስፋፋውን እና የተንሰራፋውን ሽርክ ከምንም ነገር በማስቀደም አስከፊነቱን እራሳችን አውቀን፣ ለማህበረሰቡ አዝነን ማስተማር እንጀምር።

አላህ በጣም አዛኝ ነው ባርያዎቹ እሱን ብቻ አምልከው 2 አገር ነጃ እንዲወጡ ነብያትን ላከ፣ መፀሃፍትን አወረደ፣ በዋነኝነት የእዝነት መገለጫ የሆነውን የሰው ልጆችን ከጨለማ የሚያወጣውን ተውሂድ አስቀደሙ መልክተኞች ሁሉ።

ታድያ መልክተኞች የሄዱበትን ተቃርኖ የሚሄድ እውነት ለማህበረሰቡ ያዝናል??? በፍፁም።

የተውሂድ እና ሱና ትልቅነት፣ የሽርክ እና ቢድአ አስከፊነት አውቀን እናሳውቅ። በነዚህ ጉዳዮች ላይ ቸልተኛ የሆነ ሰው፣ የለፋውን ቢለፋ ጠብም አይልለትን።

ከምንም በፊት ቅድሚያ ለተውሂድ እና ሱና።

አላህ ሆይ! ሃቅን በሃቅነቱ አሳየን የምንከተለውም አድርገን፣ ባጢልን በባጢልበቱ አሳየን የምንርቀውም አድርገን።
የአላህ ሰላት እና ሰላም በነብያት መደምደሚያ፣ በቤተሰቦቻቸው፣ በሰሃባዎቻቸው፣ ሀቅን በተከተለ ላይ ሁሉ ይሁን።
https://t.me/SadatTextPosts
ያለ ማስረጃ የሚነገረንን ሁሉ አሜን ብለን ብንቀበል ኖሮ ዲናችንን አፍርሰን ነበር፡፡
አንዳንድ ሰዎች “አሊም፣ ሙፍቲ” ናቸው እየተባለ የሚከተለውን አይነት ማስረጃ ሰንሰለት የሌለው ንግግር፣ ተሰምቶ የማያውቅ ወደ ኢስላም አስጠግተው ቢድኣ የሆነውን መውሊድ የዲን አካል አድርገው ሊያቀርቡልን አህባሾች ሬድዬ ላይ ቀርበው ነበር
“…እንዲሁም ከሰሃባዎች ውስጥ ከቶም አንዱ ሰሃባ ዝግጅት አዘጋጅቶ እንዲሁ ደግሶ ለነብያችን መላክ መወለድ ደስታ ዝግጅት አድርጎ ሰብስቦ አብልቷል….”

ታድያ ይህንን ከላይ ያለውን ንግግር የሚናገርን እና በኢስላም የሌለን ነገር ሊደነግግ የሚሞክርን ሰው “ሙፍቲ” ቢባል እንኳን ልንቀበለው ነው ወይ?
እነዛ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምን) ከነፍሳቸው በላይ ይወዱ የነበሩ ሰሃባዎች ይህንን ተግባር (መውሊድን) አያውቁትም፡፡ እነሱ ላይ መዋሸት ደግሞ በአደራ ያስተላላፉልንን ንፁህ ዲን እንደመናድ ነው የሚቆጠረው፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
ለሙስሊሙ ብሎም ለሀገራችን ያሰበ “ጫት ሸርጡ ተጠብቆ ስላልተቃመ እንጂ መሻኢሆቻችን ጫት ቅመው ዝናብ ያዘንቡ ነበር” እያለ ባልዋሸና ባልሰበከ ነበር፡፡
የሚያሳዝነው እንዲህ አይነቱ ሀይማኖት እና ሀገር አፍራሽ ግለሰብ የሀይማኖት ሰው ተደርጎ መወሰዱ ነው፡፡
ጫት ሙስሊሙን ያሽመደመደ፣ ኢትዮጵያን ወደ ኋላ ያስቀረ አደገኘ መርዘኛ አደንዛዥ ቅጠል ነው፡፡
አላህ ለሙስሊሙም ለሀገርም የሚጨነቁ እውነተኛ የሀይማኖት አባቶች ይለግሰን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
ከ 7 ሰማይ በላይ…..
የአላህ ባርያዎች ሆይ! ማንኛውንም ስራ ስንሰራ ከ7 ሰማያት በላይ ያለውን ሁሉን አዋቂ፣ ተመልካች፣ ሰሚ አላህ አስበን፣ ፈርተን እንስራ፡፡
ምክንያቱም የሰራናት ስራ እሱ ዘንድ ተቀባይነት ካለት የእድለኞች ሁሉ እድለኞች እንሆናለን፡፡ እሱ ከተቆጣብንም የከሳሪዎች ሁሉ ከሳሪ እንሆናለን፡፡
ስለዚህ ለአላህ ብቻ አጥርተን እንስራ፡፡ ወንጀል ስንሰራ ወዲያውኑ በንሰሀ ወደ እሱ እንመለስ፡፡
የምንናገረው እና የምንሰራው መልካም መሆኑን እናረጋግጥ አላህ ዘንድ ይደርስልን ዘንድ፡፡ አላህ እንዲህ ይላል

إِلَيْهِ يَصْعَدُ ٱلْكَلِمُ ٱلطَّيِّبُ وَٱلْعَمَلُ ٱلصَّٰلِحُ يَرْفَعُهُۥ ۚ
መልካም ንግግር ወደርሱ (ወደ አላህ) ይወጣል፡፡ በጎ ሥራም ከፍ ያደርገዋል፡፡
[ 35:10]
አላህ ለእርሱ ብቻ ስራቸውን ከሚያጠሩት፣ እሱን ብቻ ከሚፈሩት፣ ሲሳሳቱ ወደ እሱ ከሚመለሱት ባሪያዎች ያድርገን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
የሐጅ ጉዟችሁ በመጅሊስ በኩል ያልሆናችሁ ሰዎች አደራችሁን በሚናም ሆነ በዐረፋ የመጅሊሱን ድንኳን (ኸይማ) እንዳትጠቀሙ። በመጅሊስ በኩል ገንዘባቸውን ከስክሰው የሄዱ ወገኖች ድንኳን እየሞላባቸው በዚያ ከባድ ፀሐይ እየተለበለቡ፣ ለድንኳኑ ያልከፈላችሁ ሰዎች ድንኳኑን በማጨናነቅ የሌሎችን ሐቅ ልትጋፉ አይገባም። ይሄ ቀላል ጥፋት አይደለም። ሴቶችና አቅመ ደካሞች ድንኳኑ ዘንድ ለመድረስ ጊዜ ይፈጅባቸዋል። እንዳቅማቸው ተጉዘው እቦታው ሲደርሱ በወጣቶች፣ በተለይም ሳዑዲ ኗሪ በሆኑት ተስሪሕ የሌላቸው ኢትዮጵያውያን ወንድሞች ድንኳኑ ሞልቶ ይጠብቃቸዋል። በዚህም ሳቢያ ለዚያ ፈፅሞ ለማያውቁት ከባድ የፀሐይ ቃጠሎ (በተለይም ዐረፋ ላይ) ይጋለጣሉ። መቋቋም አቅቷቸው ነስር በነስር የሚሆኑ አሉ። በርግጠኝነት እነዚያ ያለ ሐቃቸው ቀድመው ኸይማውን የሚሞሉ ወጣቶች ይህን የደካሞችን እንግልት ከውጭ ሆነው ቢያዩ በጥፋታቸው ይሸማቀቃሉ። ይህ እንዳይሆን ዘንድ ያልከፈልንበትን አገልግሎት ለማግኘት ከመጋፋት ልንቆጠብ ይገባል። ደካሞችን ከተጨማሪ እንግልት፣ ሌሎቹን ደግሞ የሰው ሐቅ ከመጋፋት ለማትረፍ ሰበብ እንሆን ዘንድ መልእክቱን በማሰራጨት ተባበሩኝ። (ወንድማችሁ ኢብኑ ሙነወር፣ ሐምሌ 24/ 2010)