አልሐምዱሊላህ ሰው እንደዚህ ሲለወጥ ደስ ይላል፡፡
ከሺርክ እና ከቢድኣ በአላህ ፍቃድ ሰዎች እንደተለወጡት ሁሉ አሁን ደግሞ ስለ ነሺዳና መንዙማ ከቁርዓን አዘናጊነት ትምህርት ከተለቀቀ በኋላ አንድ የዩቲዩብ ተጠቃሚ እንዲህ ሲል ኮሜንት ፅፏል
"ውይ እኔ ነሺዳ ማዳመጥ አንድ ቁጥር ነኝ ቁርዓኑ ግን አንድ ሁለት ሱራ እደቀራሁ እንቅልፍ ይደፍኛል ……ከዛሬ ጀምሬ ስልኬ ላይ ነሺዳ ሚባል ሁላ አዎጣለሁ"
አልሐምዱሊላህ ገና ይቀጥላል ሙስሊሙ ኡማ ከጫትም ከሌሎችም መጥፎ ነገሮች በአላህ ፍቃድ እና እገዛ ይለወጣል፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
ከሺርክ እና ከቢድኣ በአላህ ፍቃድ ሰዎች እንደተለወጡት ሁሉ አሁን ደግሞ ስለ ነሺዳና መንዙማ ከቁርዓን አዘናጊነት ትምህርት ከተለቀቀ በኋላ አንድ የዩቲዩብ ተጠቃሚ እንዲህ ሲል ኮሜንት ፅፏል
"ውይ እኔ ነሺዳ ማዳመጥ አንድ ቁጥር ነኝ ቁርዓኑ ግን አንድ ሁለት ሱራ እደቀራሁ እንቅልፍ ይደፍኛል ……ከዛሬ ጀምሬ ስልኬ ላይ ነሺዳ ሚባል ሁላ አዎጣለሁ"
አልሐምዱሊላህ ገና ይቀጥላል ሙስሊሙ ኡማ ከጫትም ከሌሎችም መጥፎ ነገሮች በአላህ ፍቃድ እና እገዛ ይለወጣል፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
አላህ ሁሉን ሰሚ ነው፡፡
ዱኣ (ፀሎት) በአረብኛ ማድረግ በላጭ ነው፡፡ አረብኛውን ለማይችሉ በአማርኛ፣ በኦሮሚኛ፣በስልጢኛ፣ በጉራጊኛ፣ በትግሪኛ፣ በሀደሪኛ፣ በእንግሊዝኛ፣ በፈረንሳይኛ…. በማንኛውም ቋንቋ አላህን መለመን ይቻላል፡፡ ዱኣ ታላቅ አምልኮ ነው ትርጉሙን ተምረን አላህን እንለምነው፡፡ ዱኣን ትርጉሙን ካላወቅን ብዙም ጥፍጥናውን አናውቀውም፡፡ አላህ እውቀት ይጨምርልን፡፡ https://t.me/SadatTextPosts
ዱኣ (ፀሎት) በአረብኛ ማድረግ በላጭ ነው፡፡ አረብኛውን ለማይችሉ በአማርኛ፣ በኦሮሚኛ፣በስልጢኛ፣ በጉራጊኛ፣ በትግሪኛ፣ በሀደሪኛ፣ በእንግሊዝኛ፣ በፈረንሳይኛ…. በማንኛውም ቋንቋ አላህን መለመን ይቻላል፡፡ ዱኣ ታላቅ አምልኮ ነው ትርጉሙን ተምረን አላህን እንለምነው፡፡ ዱኣን ትርጉሙን ካላወቅን ብዙም ጥፍጥናውን አናውቀውም፡፡ አላህ እውቀት ይጨምርልን፡፡ https://t.me/SadatTextPosts
ረመዳን ገና አላለቀም፣ እኛም ገና አልሞትንም፡፡
የአላህ ባሪያዎች ሆይ! ረመዳን ሲገባ አልሐምዱሊላህ መስጂዶች ሰው በደንብ አስተናግደው ነበር፡፡ አሁን ገና ረመዳኑ ሳያልቅ ትንሽ መቀነስ ይታያል፡፡ ከዚህ በፊት የነበሩ አመታት ላይ እንደሚታየው ረመዳን ሲወጣ አብዛኛው ሰው ከመስጂድ ይርቃል፡፡ የአላህ ባሪያዎች ሆይ! ባረከላሁ ፊኩም ረመዳን ገና አላለቀም፡፡ ረመዳን አለቀ ቢባል እንኳን አንድ በበለጠ ሁኔታ ኸይር የሚሰራበት ወር አለቀ እንጂ ሌሎች አላህ የሚመለኩባቸው እና መልካሞች የሚሰሩበት እና ከመጥፎ የሚራቁባቸው ወራት እንደቀጠሉ ነው፡፡ ረመዳን ውስጥ በተለይ የተከበሩት የመጨረሻዎቹ ለይለቱል ቀድር ይገኝበታል ተብሎ የሚገመቱት አስር ቀናት አሉ፡፡ እባካችሁ ነቃ እንበል፡፡ እኛን አላህ የፈጠረን እስከለተ ሞታችን ድረስ እሱን በብቸኝነት እንድንገዛው ነው፡፡ አላህ ለሰው ልጆች ሁሉ ፈርጥ ነብዩ ሙሐመድ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እንዲህ አላቸው
[15:99] وَٱعْبُدْ رَبَّكَ حَتَّىٰ يَأْتِيَكَ ٱلْيَقِينُ
እውነቱም (ሞት) እስኪመጣህ ድረስ ጌታህን ተገዛ፡፡
እሳቸውም የጌታቸውን ትዕዛዝ በመፈፀም እስከለተ ሞታቸው ድረስ የማይሞተውን ህያው አምላክ አላህ አመለኩት፡፡ ከዚህ አለም ሲለዩም የመጨረሻ ንግግራቸው
“አላህ ሆይ! ከላይኛው የጀነት ጓዶች አድርገኝ” የሚል ነበር፡፡
ታድያ ያለፈውንም የሚመጣውን ሁሉ አላህ የማራቸው የሰው ልጆች ሁሉ ፈርጥ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ይህን ያህል ከለፉ እኛስ የሚል ጥያቄ ነፍሴንም እናንተም እየጥቃለሁ፡፡
ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ለሙኣዝ ኢብን ጀበል ሰላትን ከማጠናቀቁ በፊት “አላህ ሆይ! አንተን በማውሳት ላይ፣ በማመስገን ላይ እና ያማረን አምልኮ ላንተ በመፈፀም ላይ አግዘኝ” እንዲል ጠቁመውታል፡፡
እኛም አላህን እንለምነው፡፡
አላህ ፅናት ይስጠን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
የአላህ ባሪያዎች ሆይ! ረመዳን ሲገባ አልሐምዱሊላህ መስጂዶች ሰው በደንብ አስተናግደው ነበር፡፡ አሁን ገና ረመዳኑ ሳያልቅ ትንሽ መቀነስ ይታያል፡፡ ከዚህ በፊት የነበሩ አመታት ላይ እንደሚታየው ረመዳን ሲወጣ አብዛኛው ሰው ከመስጂድ ይርቃል፡፡ የአላህ ባሪያዎች ሆይ! ባረከላሁ ፊኩም ረመዳን ገና አላለቀም፡፡ ረመዳን አለቀ ቢባል እንኳን አንድ በበለጠ ሁኔታ ኸይር የሚሰራበት ወር አለቀ እንጂ ሌሎች አላህ የሚመለኩባቸው እና መልካሞች የሚሰሩበት እና ከመጥፎ የሚራቁባቸው ወራት እንደቀጠሉ ነው፡፡ ረመዳን ውስጥ በተለይ የተከበሩት የመጨረሻዎቹ ለይለቱል ቀድር ይገኝበታል ተብሎ የሚገመቱት አስር ቀናት አሉ፡፡ እባካችሁ ነቃ እንበል፡፡ እኛን አላህ የፈጠረን እስከለተ ሞታችን ድረስ እሱን በብቸኝነት እንድንገዛው ነው፡፡ አላህ ለሰው ልጆች ሁሉ ፈርጥ ነብዩ ሙሐመድ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እንዲህ አላቸው
[15:99] وَٱعْبُدْ رَبَّكَ حَتَّىٰ يَأْتِيَكَ ٱلْيَقِينُ
እውነቱም (ሞት) እስኪመጣህ ድረስ ጌታህን ተገዛ፡፡
እሳቸውም የጌታቸውን ትዕዛዝ በመፈፀም እስከለተ ሞታቸው ድረስ የማይሞተውን ህያው አምላክ አላህ አመለኩት፡፡ ከዚህ አለም ሲለዩም የመጨረሻ ንግግራቸው
“አላህ ሆይ! ከላይኛው የጀነት ጓዶች አድርገኝ” የሚል ነበር፡፡
ታድያ ያለፈውንም የሚመጣውን ሁሉ አላህ የማራቸው የሰው ልጆች ሁሉ ፈርጥ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ይህን ያህል ከለፉ እኛስ የሚል ጥያቄ ነፍሴንም እናንተም እየጥቃለሁ፡፡
ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ለሙኣዝ ኢብን ጀበል ሰላትን ከማጠናቀቁ በፊት “አላህ ሆይ! አንተን በማውሳት ላይ፣ በማመስገን ላይ እና ያማረን አምልኮ ላንተ በመፈፀም ላይ አግዘኝ” እንዲል ጠቁመውታል፡፡
እኛም አላህን እንለምነው፡፡
አላህ ፅናት ይስጠን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
በረመዳን ተውበት አድርገው በተመለሱ ወንድም እና እህቶች ላይ አታሹፍባቸው ምክንያቱም ይህ የመለወጫ ሰበባቸው ይሆናልና ኢንሻ አላህ ልክ አንተ/ቺ ከለታት በአንድ ቀን ውስጥ እንደተመለስከው/ሺው፡፡
የአላህ ባርያዎች ሆይ! ከማንኛውም ወንጀል ተውበት በማናችንም ላይ ግዴታ ነው፡፡ ከወንጀል የተመለሱ ወንድም እና እህቶችን በማበረታታት እና መጥፎ ጓደኛዎቻቸውን እንዲርቁ በመምከር በሀቅ ላይ ይፀኑ ዘንድ ማበረታታት ይገባል፡፡
አላህ ሁላችንንም ንፁህ ተውበት ይለግሰን፣ በሃቅ ላይም ያፅናን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
የአላህ ባርያዎች ሆይ! ከማንኛውም ወንጀል ተውበት በማናችንም ላይ ግዴታ ነው፡፡ ከወንጀል የተመለሱ ወንድም እና እህቶችን በማበረታታት እና መጥፎ ጓደኛዎቻቸውን እንዲርቁ በመምከር በሀቅ ላይ ይፀኑ ዘንድ ማበረታታት ይገባል፡፡
አላህ ሁላችንንም ንፁህ ተውበት ይለግሰን፣ በሃቅ ላይም ያፅናን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
Forwarded from MuhammedSirage M.Noor
ከሌሊቶች ሁሉ በላጭ የሆነችው ሌሊት በጀመርናቸዉ 10 የረመዳን መጨረሻ ሌሊቶች ውስጥ ትገኛለች — በርካታ ኡለሞቻችን እንደሚሉት ።
በርካታ ኸይሮች ያለባትን ይችን የተከበረች ሌሊት አትርፎባት ማለፍ የፈለገ አማኝ ከወዲሁ ጀምሮ ወገቡን ማጥበቅ ይጠበቅበታል — الله ለሚወዳቸው ስራዎች!!
ነብዩ እነዚህን ውድ ሌሊቶች ሽርጣቸውን ጠበቅ በማድረግ ( ከሚስቶቻቸው በመራቅና ኢባዳን በማብዛት) ፣ፈጣሪያቸውን በብርቱ በማምለክ ሳይተኙ ያሳልፏቸው ነበር!!
በተረፈ በነዚህ የተከበሩ ሌሊቶች ውስጥ የተጎዱ ወገኖቻችንን፣ ከአገርና ከቤቶቻቸው የተፈናቀሉ ወንድሞቻችንንና እህቶቻችንን እናስታውስ!! ዱዓ እናርግላቸው።
ወንድሞችና እህቶች አላህን እንፍራ!
በርካታ ኸይሮች ያለባትን ይችን የተከበረች ሌሊት አትርፎባት ማለፍ የፈለገ አማኝ ከወዲሁ ጀምሮ ወገቡን ማጥበቅ ይጠበቅበታል — الله ለሚወዳቸው ስራዎች!!
ነብዩ እነዚህን ውድ ሌሊቶች ሽርጣቸውን ጠበቅ በማድረግ ( ከሚስቶቻቸው በመራቅና ኢባዳን በማብዛት) ፣ፈጣሪያቸውን በብርቱ በማምለክ ሳይተኙ ያሳልፏቸው ነበር!!
በተረፈ በነዚህ የተከበሩ ሌሊቶች ውስጥ የተጎዱ ወገኖቻችንን፣ ከአገርና ከቤቶቻቸው የተፈናቀሉ ወንድሞቻችንንና እህቶቻችንን እናስታውስ!! ዱዓ እናርግላቸው።
ወንድሞችና እህቶች አላህን እንፍራ!
ዱባዬች ተጠንቀቁ
ማንን ?
ካላችሁ
በየአመቱ ኢድ እና አረፋ በመጣ ቁጥር ሴት እና ወንዶችን አዳራሽ ላይ በመደባለቅ ከአዲስ አበባ ከመጡት "ሙነሺዶች" ጋር በመሆን በአሉን እናክብር በማለት ብራችሁን ከሚበዘብዙት እና አላህ የጠላውን* "ኢኽቲላጥ" (ሴት እና ወንድን መደበላለቅ) ከሚፈፅሙት የዲን ደጋዴዎች።
አላህ በሚመሰገንበት ቀን አላህን ስታምፁ እንድትውሉ እነዚህ ተሳስተው አሳሳቾች ይጠሯችኀል፣ ይጎተጉቷችኀል አትስሟቸው ራቋቸው።
ተጠንቀቋቸው ከነሱም አስጠንቅቁ።
https://t.me/SadatTextPosts
ማንን ?
ካላችሁ
በየአመቱ ኢድ እና አረፋ በመጣ ቁጥር ሴት እና ወንዶችን አዳራሽ ላይ በመደባለቅ ከአዲስ አበባ ከመጡት "ሙነሺዶች" ጋር በመሆን በአሉን እናክብር በማለት ብራችሁን ከሚበዘብዙት እና አላህ የጠላውን* "ኢኽቲላጥ" (ሴት እና ወንድን መደበላለቅ) ከሚፈፅሙት የዲን ደጋዴዎች።
አላህ በሚመሰገንበት ቀን አላህን ስታምፁ እንድትውሉ እነዚህ ተሳስተው አሳሳቾች ይጠሯችኀል፣ ይጎተጉቷችኀል አትስሟቸው ራቋቸው።
ተጠንቀቋቸው ከነሱም አስጠንቅቁ።
https://t.me/SadatTextPosts
የእኛም ህይወት
የአላህ ባሪያዎች ሆይ! ረመዳኑ ቀኑ መፍጠኑ ብዙዎቻችንን አስደነገጠን፡፡ እንዲህ ሲፈጥን ሁሉም የአቅሙን መልካም በመስራት እንደው በዚህ የተከበረ ወቅት ልጠቀምበት በሚል መልካሞችን በአቅሙ ልክ እያበዛ ነው፡፡ ታድያ የአላህ ባሪያዎች የእኛንም ህይወት ከተመለከትነው እውነታው ይህ ነው፡፡ አንድ ቀን ባደርን ቁጥር አንድ ቀን ወደ ሞት እየተጠጋን ነው፡፡ ከሞት በኋላ ደግሞ ለሰራነው ስራ ውጤት ማግኘት እንጂ ስራ መስራት አይቻልም፡፡
የአላህ ባሪያዎች ሆይ! አንድ ቀን ባነጋን ቁጥር ወደ ማይቀረው የተቀጠርንለት ሞት እየቀረብን ነውና ለሚቀጥለው አለም ስንቃችንን እናዘጋጅ፡፡ አላህን ሁሌ እናምልከው፡፡ ከስንቆች ሁሉ በላጭ አላህን መፍራት ነውና አላህን እንፍራ፡፡
አላህ ሆይ! አንተን መፍራትን አላብሰን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
የአላህ ባሪያዎች ሆይ! ረመዳኑ ቀኑ መፍጠኑ ብዙዎቻችንን አስደነገጠን፡፡ እንዲህ ሲፈጥን ሁሉም የአቅሙን መልካም በመስራት እንደው በዚህ የተከበረ ወቅት ልጠቀምበት በሚል መልካሞችን በአቅሙ ልክ እያበዛ ነው፡፡ ታድያ የአላህ ባሪያዎች የእኛንም ህይወት ከተመለከትነው እውነታው ይህ ነው፡፡ አንድ ቀን ባደርን ቁጥር አንድ ቀን ወደ ሞት እየተጠጋን ነው፡፡ ከሞት በኋላ ደግሞ ለሰራነው ስራ ውጤት ማግኘት እንጂ ስራ መስራት አይቻልም፡፡
የአላህ ባሪያዎች ሆይ! አንድ ቀን ባነጋን ቁጥር ወደ ማይቀረው የተቀጠርንለት ሞት እየቀረብን ነውና ለሚቀጥለው አለም ስንቃችንን እናዘጋጅ፡፡ አላህን ሁሌ እናምልከው፡፡ ከስንቆች ሁሉ በላጭ አላህን መፍራት ነውና አላህን እንፍራ፡፡
አላህ ሆይ! አንተን መፍራትን አላብሰን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
የአላህ ባሪያዎች ሆይ! ትንሹ ኢድ የሚባል ነገር በሸሪዓ የለም፡፡
*************************************
ምስጋና ለአላህ ነው፤ ሁለት የመደሰቻ በአላትን የደነገገ፡፡ አሁንም ምስጋና ይገባው ይህንን ሸሪዓ ከመበረዝ እጠብቀዋለሁ ብሎ ቃል የገባው አላህ፤ የሃይማኖት ድንጋጊን ሁላ ለራሱ ብቻ ያደረገ፤ በዚህም ላይ ታላቅ ጥበቡን ያሳየ፡፡ እንደሌሎቸ ሀይማኖቶች፤ ቀሳውስት እንደበረዙት (እንደጨመሩበት እና እንደቀነሱበት) እንዳይሆን በግልፅ ሸሪዓዊ ድንጋጌን ለራሱ ብቸኛ አውጪ ያደረገ፡፡
ሱና ፆም ፆመን ዝም ብሎ ማለፍ እንጂ ከአላህ የተደነገገ በዓል የለም፡፡ ትንሹ ኢድ የሚባል ነገር ከነብያችንም (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም)፤ ከሰሃባዎቻቸው (ሪድዋኑላሂ አለይሂም)፤ ከ3 ምርጥ ትውልድ፤ ከ4 አኢማዎች አላገኘንም፡፡ ታድያ ለምንድን ነው እኛ ያልታዘዝነውን የምንሰራው???
ሰኞ እና ሀሙስ ፆመን ምንም በአል ከሌለ፤ 13፣14፣15 ፆመን ምንም በአል ከሌለ፤ የሸዋል 6 ከየት መጣ??? አላህን እንፍራ፡፡
አንዳንድ ቦታ ያውም ከዋናው ኢድ በላይ ይህን ቀን ያከብሩታል፡፡
እወቅ የአላህ ባሪያ ከሽርክ ቀጥሎ ሸይጧን ዘንድ የተወደደው ወንጀል ቢድዓ ነው፡፡ ሁሉም ቢድዓ ጥመት ነው፤ ጥመት ሁሉ ለእሳት ነው፡፡
አላህ በደነገገልን 2 ኢዶች፤ ከዛ በጁምዓ ብቻ እንብቃቃ፡፡ ሁሉ ነገር የሌለው ይቀላውጣል፡፡ አላህ ግን ይህን ዲን ሞልቶታል፤ ታድያ እንደ አህለል ኪታብ መጨማመሩ ምን አስፈለገ፤ የአላህን ቁጣ ለመውረስ ካልሆነ፡፡
የአላህ ባሪያዎች ሆይ! ትንሹ ኢድ የሚባል ነገር በሸሪዓ የለም፡፡ ተጠንቀቁ አስጠንቅቁ፡፡
የአላህ ሰላት እና ሰላም በነብያት እና ሩሱሎች ኢማም ላይ ይሁን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
*************************************
ምስጋና ለአላህ ነው፤ ሁለት የመደሰቻ በአላትን የደነገገ፡፡ አሁንም ምስጋና ይገባው ይህንን ሸሪዓ ከመበረዝ እጠብቀዋለሁ ብሎ ቃል የገባው አላህ፤ የሃይማኖት ድንጋጊን ሁላ ለራሱ ብቻ ያደረገ፤ በዚህም ላይ ታላቅ ጥበቡን ያሳየ፡፡ እንደሌሎቸ ሀይማኖቶች፤ ቀሳውስት እንደበረዙት (እንደጨመሩበት እና እንደቀነሱበት) እንዳይሆን በግልፅ ሸሪዓዊ ድንጋጌን ለራሱ ብቸኛ አውጪ ያደረገ፡፡
ሱና ፆም ፆመን ዝም ብሎ ማለፍ እንጂ ከአላህ የተደነገገ በዓል የለም፡፡ ትንሹ ኢድ የሚባል ነገር ከነብያችንም (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም)፤ ከሰሃባዎቻቸው (ሪድዋኑላሂ አለይሂም)፤ ከ3 ምርጥ ትውልድ፤ ከ4 አኢማዎች አላገኘንም፡፡ ታድያ ለምንድን ነው እኛ ያልታዘዝነውን የምንሰራው???
ሰኞ እና ሀሙስ ፆመን ምንም በአል ከሌለ፤ 13፣14፣15 ፆመን ምንም በአል ከሌለ፤ የሸዋል 6 ከየት መጣ??? አላህን እንፍራ፡፡
አንዳንድ ቦታ ያውም ከዋናው ኢድ በላይ ይህን ቀን ያከብሩታል፡፡
እወቅ የአላህ ባሪያ ከሽርክ ቀጥሎ ሸይጧን ዘንድ የተወደደው ወንጀል ቢድዓ ነው፡፡ ሁሉም ቢድዓ ጥመት ነው፤ ጥመት ሁሉ ለእሳት ነው፡፡
አላህ በደነገገልን 2 ኢዶች፤ ከዛ በጁምዓ ብቻ እንብቃቃ፡፡ ሁሉ ነገር የሌለው ይቀላውጣል፡፡ አላህ ግን ይህን ዲን ሞልቶታል፤ ታድያ እንደ አህለል ኪታብ መጨማመሩ ምን አስፈለገ፤ የአላህን ቁጣ ለመውረስ ካልሆነ፡፡
የአላህ ባሪያዎች ሆይ! ትንሹ ኢድ የሚባል ነገር በሸሪዓ የለም፡፡ ተጠንቀቁ አስጠንቅቁ፡፡
የአላህ ሰላት እና ሰላም በነብያት እና ሩሱሎች ኢማም ላይ ይሁን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
አመቱን ሙሉ እንደፆመ መሆኑ አይፈልጉምን?
ነብዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል
“ረመዳንን የፆመ ከዛም ከሸዋል (ወር) ስድስት ቀናትን (በመፆም) ያስከተለ፣ አመቱን ሙሉ እንደፆመ ነው::”
ይህን በፍላጎት የሚፆም ፆም እንፁም እና ከምንዳው እንካፈል፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
ነብዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል
“ረመዳንን የፆመ ከዛም ከሸዋል (ወር) ስድስት ቀናትን (በመፆም) ያስከተለ፣ አመቱን ሙሉ እንደፆመ ነው::”
ይህን በፍላጎት የሚፆም ፆም እንፁም እና ከምንዳው እንካፈል፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
የአላህ ችሮታ
በእስልምና አንድ አመት 12 ወራቶች አሉት፡፡
ረመዳን እንደ 10 ወር ሲቆጠር፣ ስድስቱ የሸዋል ቀኖች እንደ ሁለት ወር ይቆጠራሉ፡፡
ነብዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል
“ረመዳንን የፆመ ከዛም ከሸዋል (ወር) ስድስት ቀናትን (በመፆም) ያስከተለ፣ አመቱን ሙሉ እንደፆመ ነው::”
ምክንያቱም ቸሩ አላህ መልካም ስራን በአስር አባዝቶ ስለሚቀበል፡፡
የሚገርመው መሃሪው አላህ ረመዳንን በሁለት ረመዳኖች ውስጥ የተሰራውን ወንጀል ማስማሪያ ሰበብ አድርጎታል፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
በእስልምና አንድ አመት 12 ወራቶች አሉት፡፡
ረመዳን እንደ 10 ወር ሲቆጠር፣ ስድስቱ የሸዋል ቀኖች እንደ ሁለት ወር ይቆጠራሉ፡፡
ነብዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል
“ረመዳንን የፆመ ከዛም ከሸዋል (ወር) ስድስት ቀናትን (በመፆም) ያስከተለ፣ አመቱን ሙሉ እንደፆመ ነው::”
ምክንያቱም ቸሩ አላህ መልካም ስራን በአስር አባዝቶ ስለሚቀበል፡፡
የሚገርመው መሃሪው አላህ ረመዳንን በሁለት ረመዳኖች ውስጥ የተሰራውን ወንጀል ማስማሪያ ሰበብ አድርጎታል፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
ሸይኽ ፈውዛን (ሀፊዘሁላህ) እንዲህ ይላሉ
“(ረመዳን) ወሩ በማለቁ አንደሰትም፡፡ ነገር ግን የምንደሰተው ወሩን አላህን በመገዛት ስለጨረስን ነው፡፡”
አላህ የነብያት ወራሾች የሆኑትን አዋቂዎች ይጠብቅልን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
“(ረመዳን) ወሩ በማለቁ አንደሰትም፡፡ ነገር ግን የምንደሰተው ወሩን አላህን በመገዛት ስለጨረስን ነው፡፡”
አላህ የነብያት ወራሾች የሆኑትን አዋቂዎች ይጠብቅልን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
ሲሉ ሰምታ ዶሮ ታንቃ ሞተች!!
ኮሚቴ ተብየው የሆነ ሆቴል ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጡ ተብሎ ፎቶም ተለቋል፡፡ የሚገርመው ሀገራችን ብዙ ቦታዎች ላይ በአላህ ላይ ሲጋራ፣ የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ሱና ሲወድም እና ቢድኣ ሲስፋፋ፣ ዘረኝነት ኡመተል ኢስላምን ጎራ ይዞ ገዳይ “አላሁ አክበር” ተገዳይ “ላኢላሃ ኢለላህ” እያለ ሲጫረስ፣ ጫት ሙስሊሙን እና ትውልዱን ብሎም ሀገር ሲያወድም ዝም ያሉት ኮሚቴዎች ዛሬ የመጅሊስ ስልጣን እና ሌሎች ሀገሪቱ ላይ ያሉ የስልጣን ወንበሮች ላይ ጉብ ለማለት ደፋ ቀና እያሉ ነው፡፡
እኛ ፖለቲካ ውስጥ ለምን ገቡ አንልም። ኢስላምን መንጠላጠያ መሰላል ሲያደርጉት ግን ያመናል።
የእውነት የሙስሊሙ ጉዳይ የሚያስጨንቃቸው ከሆነ ግን
- ሀገራችን ላይ በሁሉም አቅጣጫ አዲስ አበባን ጨምሮ የሚሰራውን ከአላህ ውጭ አምልኮ ወገባቸውን ታጥቀው ሊዋጉት ይገባል፣
- መውሊድ እየተባለ የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ሱና የሚናድበትን፣ በነብዩ ውዴታ ስም የአላህ መብት ተቆርሶ ለነብዩ የሚሰጥበትን፣ ሸሆች የሚመለኩበትን፣ የሙስሊሙ ገንዘብ የሚበዘበዝበትን፣ ይህ አደንዛዥ ቅጠቅ የሚታኘክበትን በግልፅ እንዲህ መግለጫ እየሰጡ በአደባባይ በኢስላም የሌለ መሆኑን መናገርና ሲሰራም መቃወም አለባቸው፡፡ እነሱ እስከዛሬ ሲናገሩ የሰማናቸው “መውሊድ አይለያየንም፣ አይከፋፍለንም” ነው። ከዚህም አልፎ የነሱ አስተማሪ ሀሰን ታጁ “መውሊድ” የሚባል መፀሀፍ ፅፎ ኡማውን ወደ እሳት መርቷል፡፡ እነሱ ግን ከሱ ጋር እጅና ጓንት ናቸው።
- ሙስሊሙን ሲቀጥል ሀገራችንን እያወደመ ያለውን ጫት “ቀንሱ” እያል ማሽሞንሞን ሳይሆን ለሙስሊሙና ለሀገር ከታሰበ በግልፅ በየመስጂዱ ትምህርት ሊሰጥበት እናንተም በዚህ ጉዳይ ከመግለጫው በፊት ቢዚ ልትሆኑ ይገባ ነበር፡፡ አሳዛኙ ግን እናንተ አንድ ነን ከምትሏቸው ውስጥ ሙፍቲ የሚባለው “ጫት መስፈርቱ ተጠብቆ ስላማይቃም እንጂ ኡለማዎቻችን ጫት ቅመው ዝናብ ያዘንቡ ነበር” እያለ መስጂድ ውስጥ በማይክሮፎን መለፈፉ ነው፡፡ እስኪ ከናንየ ውስጥ ማነው ይህን ጥፋት መጋፈጥ የሚችል ጀግና?
ገርሞ ከሚገርመኝ “አኽላቃችሁ” ውስጥ የኢትዮጵያ ሙስሊሞችን ከትክክለኛው ተውሒድ ወደ ክህደት በመንዙማ ስንኛቸው የሚመሩትን የመንዙማ ጨፋሪዎች አይደለም ልትቆጧቸው፣ አይደለም ሙስሊሙ እንዲጠነቀቃቸው ልታደርጉ ቀርቶ “ቲቢ አፍሪካ” ላይ ማቅረባችሁ ነው፡፡ የኢድ እንግዳችን የሚል ስምም ትሰጧቸዋላችሁ፡፡ እንደው ያ አያያዙ የበረታውን አላህ አትፈሩትም፡፡ እስከመቼ ሸውዳችሁ ትኖራላችሁ?
እስቲ ሌሎች ፖለቲከኞችስ ስራቸው ሌላ ነው፡፡ እናንተ በየመስጂዱ የሙስሊሙ ጉዳይ ይመለከተናል የምትሉ ሰዎች ሙስሊሞችን የሚገድላቸው እና የሚያጋድላቸው ጉዳይ ከምንም በላይ እስቲ ስሩበት፡፡ እኛ ሙስሊሞች ከኢኮኖሚም፣ ከማህበራዊም ችግራችን በላይ አብዛኛው ህዝቡ በሺርክ፣ በቢድኣ፣ በዘረኝነት፣ በጫት በመጥፎ ህይወት ውስጥ እየዋዠቀ ነው፡፡
ይህን ችግር ለመቅረፍ ደግሞ የመጅሊስን ስልጣን መቆናጠጥም ይሁን፣ የፓርላማ ወንበርን መያዝ አይጠይቅም፡፡ ዳእዋን አርአያችን፣ አስተማሪያችን ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ቅድሚያ እምነትን የማስተካከል ተውሒድን የማስቀደም ስራ እንደሰሩት መስራት ነው፡፡ ያኔ ለውጥ ይመጣል፡፡
እስቲ ቃሉን የማያፈርሰው ጌታችን አላህ ምን እንዳለ ልብ እንበል
[Q 24:55] وَعَدَ ٱللَّهُ ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ مِنكُمْ وَعَمِلُوا۟ ٱلصَّٰلِحَٰتِ لَيَسْتَخْلِفَنَّهُمْ فِى ٱلْأَرْضِ كَمَا ٱسْتَخْلَفَ ٱلَّذِينَ مِن قَبْلِهِمْ وَلَيُمَكِّنَنَّ لَهُمْ دِينَهُمُ ٱلَّذِى ٱرْتَضَىٰ لَهُمْ وَلَيُبَدِّلَنَّهُم مِّنۢ بَعْدِ خَوْفِهِمْ أَمْنًا ۚ يَعْبُدُونَنِى لَا يُشْرِكُونَ بِى شَيْـًٔا ۚ وَمَن كَفَرَ بَعْدَ ذَٰلِكَ فَأُو۟لَٰٓئِكَ هُمُ ٱلْفَٰسِقُونَ
አላህ እነዚያን ከእናንተ ያመኑትንና መልካም ሥራዎችን የሠሩትን እነዚያን ከእነሱ በፊት የነበሩትን እንደተካ በምድር ለይ በእርግጥ ሊተካቸው፣ ለእነሱም ያንን የወደደላቸውን ሃይማኖታቸውን ሊያደላድልላቸው፣ ከፍርሃታቸውም በኋላ ጸጥታን ሊለውጥላቸው ተስፋን ቃል ሰጥቷቸዋል፡፡ በእኔ ምንንም የማያጋሩ ኾነው ይግገዙኛል፡፡ ከዚያም በኋላ የካደ ሰው እነዚያ እነርሱ አመጸኞች ናቸው፡፡
መልካም የተባሉ ነገሮችን ለማግኘት፣ የሙስሊሙን ችግር ለመቅረፍ፣ ይሄው አላህ እንዳለው “በእኔ ምንንም የማያጋሩ ሆነው ይግገዙኛል፡፡” እውነታው ግን የተገላቢጦሽ ነው፡፡
እናንተ አንድነት የመሰረታችሁት በአላህ ላይ ከሚያጋሩት፣ የነብዩን ሱና በቢድኣ ከሚያበላሹት ሰዎች ጋር ነው፡፡ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ሆይ! ጉዳያችሁ ይመለከተኛል ያለ ሁሉ የናንተ ጉዳይ የእውነት ያስጨንቀዋል ማለት አይደለም፡፡ ሁሉን ነገር በኢስላም ሚዛን እንመዝነው፡፡
አላህ ሆይ! ሐቅን በሃቅነቱ አሳየን የምንቀበለውም አድርገን፡፡ ባጢልን በባጢልነቱ አሳየን የምንርቀውም አድርገን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
ኮሚቴ ተብየው የሆነ ሆቴል ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጡ ተብሎ ፎቶም ተለቋል፡፡ የሚገርመው ሀገራችን ብዙ ቦታዎች ላይ በአላህ ላይ ሲጋራ፣ የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ሱና ሲወድም እና ቢድኣ ሲስፋፋ፣ ዘረኝነት ኡመተል ኢስላምን ጎራ ይዞ ገዳይ “አላሁ አክበር” ተገዳይ “ላኢላሃ ኢለላህ” እያለ ሲጫረስ፣ ጫት ሙስሊሙን እና ትውልዱን ብሎም ሀገር ሲያወድም ዝም ያሉት ኮሚቴዎች ዛሬ የመጅሊስ ስልጣን እና ሌሎች ሀገሪቱ ላይ ያሉ የስልጣን ወንበሮች ላይ ጉብ ለማለት ደፋ ቀና እያሉ ነው፡፡
እኛ ፖለቲካ ውስጥ ለምን ገቡ አንልም። ኢስላምን መንጠላጠያ መሰላል ሲያደርጉት ግን ያመናል።
የእውነት የሙስሊሙ ጉዳይ የሚያስጨንቃቸው ከሆነ ግን
- ሀገራችን ላይ በሁሉም አቅጣጫ አዲስ አበባን ጨምሮ የሚሰራውን ከአላህ ውጭ አምልኮ ወገባቸውን ታጥቀው ሊዋጉት ይገባል፣
- መውሊድ እየተባለ የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ሱና የሚናድበትን፣ በነብዩ ውዴታ ስም የአላህ መብት ተቆርሶ ለነብዩ የሚሰጥበትን፣ ሸሆች የሚመለኩበትን፣ የሙስሊሙ ገንዘብ የሚበዘበዝበትን፣ ይህ አደንዛዥ ቅጠቅ የሚታኘክበትን በግልፅ እንዲህ መግለጫ እየሰጡ በአደባባይ በኢስላም የሌለ መሆኑን መናገርና ሲሰራም መቃወም አለባቸው፡፡ እነሱ እስከዛሬ ሲናገሩ የሰማናቸው “መውሊድ አይለያየንም፣ አይከፋፍለንም” ነው። ከዚህም አልፎ የነሱ አስተማሪ ሀሰን ታጁ “መውሊድ” የሚባል መፀሀፍ ፅፎ ኡማውን ወደ እሳት መርቷል፡፡ እነሱ ግን ከሱ ጋር እጅና ጓንት ናቸው።
- ሙስሊሙን ሲቀጥል ሀገራችንን እያወደመ ያለውን ጫት “ቀንሱ” እያል ማሽሞንሞን ሳይሆን ለሙስሊሙና ለሀገር ከታሰበ በግልፅ በየመስጂዱ ትምህርት ሊሰጥበት እናንተም በዚህ ጉዳይ ከመግለጫው በፊት ቢዚ ልትሆኑ ይገባ ነበር፡፡ አሳዛኙ ግን እናንተ አንድ ነን ከምትሏቸው ውስጥ ሙፍቲ የሚባለው “ጫት መስፈርቱ ተጠብቆ ስላማይቃም እንጂ ኡለማዎቻችን ጫት ቅመው ዝናብ ያዘንቡ ነበር” እያለ መስጂድ ውስጥ በማይክሮፎን መለፈፉ ነው፡፡ እስኪ ከናንየ ውስጥ ማነው ይህን ጥፋት መጋፈጥ የሚችል ጀግና?
ገርሞ ከሚገርመኝ “አኽላቃችሁ” ውስጥ የኢትዮጵያ ሙስሊሞችን ከትክክለኛው ተውሒድ ወደ ክህደት በመንዙማ ስንኛቸው የሚመሩትን የመንዙማ ጨፋሪዎች አይደለም ልትቆጧቸው፣ አይደለም ሙስሊሙ እንዲጠነቀቃቸው ልታደርጉ ቀርቶ “ቲቢ አፍሪካ” ላይ ማቅረባችሁ ነው፡፡ የኢድ እንግዳችን የሚል ስምም ትሰጧቸዋላችሁ፡፡ እንደው ያ አያያዙ የበረታውን አላህ አትፈሩትም፡፡ እስከመቼ ሸውዳችሁ ትኖራላችሁ?
እስቲ ሌሎች ፖለቲከኞችስ ስራቸው ሌላ ነው፡፡ እናንተ በየመስጂዱ የሙስሊሙ ጉዳይ ይመለከተናል የምትሉ ሰዎች ሙስሊሞችን የሚገድላቸው እና የሚያጋድላቸው ጉዳይ ከምንም በላይ እስቲ ስሩበት፡፡ እኛ ሙስሊሞች ከኢኮኖሚም፣ ከማህበራዊም ችግራችን በላይ አብዛኛው ህዝቡ በሺርክ፣ በቢድኣ፣ በዘረኝነት፣ በጫት በመጥፎ ህይወት ውስጥ እየዋዠቀ ነው፡፡
ይህን ችግር ለመቅረፍ ደግሞ የመጅሊስን ስልጣን መቆናጠጥም ይሁን፣ የፓርላማ ወንበርን መያዝ አይጠይቅም፡፡ ዳእዋን አርአያችን፣ አስተማሪያችን ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ቅድሚያ እምነትን የማስተካከል ተውሒድን የማስቀደም ስራ እንደሰሩት መስራት ነው፡፡ ያኔ ለውጥ ይመጣል፡፡
እስቲ ቃሉን የማያፈርሰው ጌታችን አላህ ምን እንዳለ ልብ እንበል
[Q 24:55] وَعَدَ ٱللَّهُ ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ مِنكُمْ وَعَمِلُوا۟ ٱلصَّٰلِحَٰتِ لَيَسْتَخْلِفَنَّهُمْ فِى ٱلْأَرْضِ كَمَا ٱسْتَخْلَفَ ٱلَّذِينَ مِن قَبْلِهِمْ وَلَيُمَكِّنَنَّ لَهُمْ دِينَهُمُ ٱلَّذِى ٱرْتَضَىٰ لَهُمْ وَلَيُبَدِّلَنَّهُم مِّنۢ بَعْدِ خَوْفِهِمْ أَمْنًا ۚ يَعْبُدُونَنِى لَا يُشْرِكُونَ بِى شَيْـًٔا ۚ وَمَن كَفَرَ بَعْدَ ذَٰلِكَ فَأُو۟لَٰٓئِكَ هُمُ ٱلْفَٰسِقُونَ
አላህ እነዚያን ከእናንተ ያመኑትንና መልካም ሥራዎችን የሠሩትን እነዚያን ከእነሱ በፊት የነበሩትን እንደተካ በምድር ለይ በእርግጥ ሊተካቸው፣ ለእነሱም ያንን የወደደላቸውን ሃይማኖታቸውን ሊያደላድልላቸው፣ ከፍርሃታቸውም በኋላ ጸጥታን ሊለውጥላቸው ተስፋን ቃል ሰጥቷቸዋል፡፡ በእኔ ምንንም የማያጋሩ ኾነው ይግገዙኛል፡፡ ከዚያም በኋላ የካደ ሰው እነዚያ እነርሱ አመጸኞች ናቸው፡፡
መልካም የተባሉ ነገሮችን ለማግኘት፣ የሙስሊሙን ችግር ለመቅረፍ፣ ይሄው አላህ እንዳለው “በእኔ ምንንም የማያጋሩ ሆነው ይግገዙኛል፡፡” እውነታው ግን የተገላቢጦሽ ነው፡፡
እናንተ አንድነት የመሰረታችሁት በአላህ ላይ ከሚያጋሩት፣ የነብዩን ሱና በቢድኣ ከሚያበላሹት ሰዎች ጋር ነው፡፡ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ሆይ! ጉዳያችሁ ይመለከተኛል ያለ ሁሉ የናንተ ጉዳይ የእውነት ያስጨንቀዋል ማለት አይደለም፡፡ ሁሉን ነገር በኢስላም ሚዛን እንመዝነው፡፡
አላህ ሆይ! ሐቅን በሃቅነቱ አሳየን የምንቀበለውም አድርገን፡፡ ባጢልን በባጢልነቱ አሳየን የምንርቀውም አድርገን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
Forwarded from ABU MUSLIM A-DUROOS
*"የኔ ግጥም ጭንቅላት ነው የሚመታው!!"*
የሆነ ጊዜ አንድ ልጅ ግጥም እገጥማለሁ ብሎ ተነሳ። ግጥሞቹ ግን የመጀመሪያው ስንኝ ከሁለተኛው ጋር አይተዋወቁም። ይህን ያዩ ሰዎች "ያባትህ ግጥም ቤት ይመታል። ያንተ ግን አይመታምሳ?" ሲሉት ምን ቢላቸው ጥሩ ነው?
"የኔ ጭንቅላት ነው የሚመታው!!" አለ። አይ ቢጠግብ! ለካስ ቤት መምታት ምን እንደሆነ አልገባውም።
።።።።
አሁን ይህን ያስታወሰኝ የያሲን ኑሩ ግጥም ነው። ይሄውና እንዲህ ሲል ቅኔውን ዘርፎታል:–
――――
"ደመቀ " አሉኝ ሰማይ
"ለማ" አሉኝ ምድሩ
·
·
"ገዱ" እንዲቀናነ እነዲያምር ነገሩ
እንዲህ መደመር ነው "አብይ" ሚስጥሩ
____________
ከዚያም ከስር እንዲህ ተብሎበታል:–
"ገጣሚ ኡስታዝ ያሲን ኑሩ"
――――――――――
ቆማጣ ቤት አንድ ጣት ብርቅ ነው!! እነ እንቶኔ ቤት ሁለት ስንኝ የገጠመ ሰው – ያውም በዚህ መልኩ ― "ገጣሚ" የሚል ማእረግ ያሸልማል። ትንሽ ቢቀጥል ሎሬት ይሉት ይሆናል። ስለ ትራፕ ሲያወራ "የፖለቲካ ተንታኝ"፣ ትንሽ ታሪክ ሲደሰኮር የታሪክ ምሁር፣…። የስም ግንባታ ገበያው የጦፈ ነው።
ይህስ ይሁን። ግጥሙ ውስጥ ይህን ስንኝ አይታችሁታል?
―――
"ገዱ" እንዲቀናነ እነዲያምር ነገሩ
――――
ሰምና ወርቅ መሆኑ ነው። ወርቁ ገዱ አንዳርጋቸው መሆኑ ነው።
ሰሙስ?? ሰሙማ ግልፅ ነው!! "ገጣሚው" ገድ እንዲቀናቸው፣ ጥሩ እንዲገጥማቸው እየተመኘ ነው። "ገጣሚው" በኢስላም ይሄ የገድ እምነት (ጢየራ) ከሺርክ እንደሚመደብ አልተረዳም። ይሄ ነው እንግዲህ ስለተውሒድ መፅሀፍ የፃፈው። "የሌለው አይሰጥም" ይላሉ ዐረቦች። የራሱን የተውሒድ ግንዛቤ ሳያስተካክል የህዝብ ዐቂዳ ሊያርም ይነሳል።
✍ኢብኑ ሙነወር
📌 *ትምህርቱን ለመከታተል ይህን ቻናል ይቀላቀሉ*
🌐 t.me/AbumuslimAlarsi
የሆነ ጊዜ አንድ ልጅ ግጥም እገጥማለሁ ብሎ ተነሳ። ግጥሞቹ ግን የመጀመሪያው ስንኝ ከሁለተኛው ጋር አይተዋወቁም። ይህን ያዩ ሰዎች "ያባትህ ግጥም ቤት ይመታል። ያንተ ግን አይመታምሳ?" ሲሉት ምን ቢላቸው ጥሩ ነው?
"የኔ ጭንቅላት ነው የሚመታው!!" አለ። አይ ቢጠግብ! ለካስ ቤት መምታት ምን እንደሆነ አልገባውም።
።።።።
አሁን ይህን ያስታወሰኝ የያሲን ኑሩ ግጥም ነው። ይሄውና እንዲህ ሲል ቅኔውን ዘርፎታል:–
――――
"ደመቀ " አሉኝ ሰማይ
"ለማ" አሉኝ ምድሩ
·
·
"ገዱ" እንዲቀናነ እነዲያምር ነገሩ
እንዲህ መደመር ነው "አብይ" ሚስጥሩ
____________
ከዚያም ከስር እንዲህ ተብሎበታል:–
"ገጣሚ ኡስታዝ ያሲን ኑሩ"
――――――――――
ቆማጣ ቤት አንድ ጣት ብርቅ ነው!! እነ እንቶኔ ቤት ሁለት ስንኝ የገጠመ ሰው – ያውም በዚህ መልኩ ― "ገጣሚ" የሚል ማእረግ ያሸልማል። ትንሽ ቢቀጥል ሎሬት ይሉት ይሆናል። ስለ ትራፕ ሲያወራ "የፖለቲካ ተንታኝ"፣ ትንሽ ታሪክ ሲደሰኮር የታሪክ ምሁር፣…። የስም ግንባታ ገበያው የጦፈ ነው።
ይህስ ይሁን። ግጥሙ ውስጥ ይህን ስንኝ አይታችሁታል?
―――
"ገዱ" እንዲቀናነ እነዲያምር ነገሩ
――――
ሰምና ወርቅ መሆኑ ነው። ወርቁ ገዱ አንዳርጋቸው መሆኑ ነው።
ሰሙስ?? ሰሙማ ግልፅ ነው!! "ገጣሚው" ገድ እንዲቀናቸው፣ ጥሩ እንዲገጥማቸው እየተመኘ ነው። "ገጣሚው" በኢስላም ይሄ የገድ እምነት (ጢየራ) ከሺርክ እንደሚመደብ አልተረዳም። ይሄ ነው እንግዲህ ስለተውሒድ መፅሀፍ የፃፈው። "የሌለው አይሰጥም" ይላሉ ዐረቦች። የራሱን የተውሒድ ግንዛቤ ሳያስተካክል የህዝብ ዐቂዳ ሊያርም ይነሳል።
✍ኢብኑ ሙነወር
📌 *ትምህርቱን ለመከታተል ይህን ቻናል ይቀላቀሉ*
🌐 t.me/AbumuslimAlarsi
Telegram
ABU MUSLIM A-DUROOS
هذه قناة أبي مسلم العروسي ، ينشر فيها دروس العقيدة والفقه والحديث وغيرهم باللغة الأمهارية وأفان أرومو