ወንድሜ! አላህን ፍራ! እህቴ ሆይ! አላህን ፍሪ!! ህይወት ማለት የዱንያ ህይወት ማለት አይደለም፡፡ ይቺማ ጤዛ እኮ ናት፡፡ ይልቅ ነብዩ ﷺ ምን እንደሚሉ ተመልከት፡- “አንድ ሰው የሚያገኘው ገንዘብ ከሐላል ይሁን ከሐራም ደንታ የማይኖርበት ዘመን በሰዎች ላይ ይመጣል፡፡” [ቡኻሪ፡ 2059] ልብህ ካልሞተ ይሄ አስፈሪ መልእክት አለው፡፡ ሰው እንዴት እራሱን የቂያማ ምልክት ያደርጋል? ፍጥጥ ባለ መልኩ ሐራም ላይ መግባት ሲኖርስ? ያውም በአራጣ? አላህ ለሸሪዐዊ ትእዛዝ እጅ የምንሰጥ፣ ከዱንያ ይልቅ ኣኺራን የምናስቀድም ያድርገን፡፡ ኣሚን፡፡
(ኢብኑ ሙነወር፣ መጋቢት 23/2010)
(ኢብኑ ሙነወር፣ መጋቢት 23/2010)
የወለድ አደጋዎች
ዘመናችን በርካታ የቂያማ ምልክቶች የሚታዩበት አስፈሪ ዘመን ነው፡፡ ከነዚህ ምልክቶች ውስጥ አንዱ የወለድ መንሰራፋት ነው፡፡ ወለድ በቁርኣን፣ በሐዲሥና በምሁራን ኢጅማዕ የተወገዘ እጅግ አደገኛ ወንጀል ነው፡፡ ወንጀሉ ምንም እንኳን አደገኛ ቢሆንም ነገር ግን እንደ ሰደድ እሳት እየተስፋፋ ነው፡፡ ከጥፋቱ መስፋፋት በላይ ይበልጥ የሚደንቀው ግን በተለያዩ ስልቶች ኢስላማዊ ሽፋን ሊሰጡት አጉል የሚባዝኑ ስራዎች ብቅ ብቅ ማለታቸው ነው፡፡ ከነዚህ ውስጥም አንዱ “የወረቀት ገንዘብ እና ወለድ” በሚል ርእስ በቅርቡ የወጣው መፅሐፍ ነው፡፡ ፀሐፊው ጥራዝ ነጠቅ ብቻ ሳይሆን ሲበዛ ደፋር ነው፡፡ ስለ መፅሐፉ በሌላ ጊዜ እመለሳለሁ፣ ኢንሻአላህ፡፡ ላሁን የወለድን አስከፊነት የሚያሳዩ ማስረጃዎችን እንደሚከተለው አቅርቤያለሁ፡፡
1. ወለድ ከሰባት ከባባድ ወንጀሎች ውስጥ አንዱ ነው፡፡ ነብዩ ﷺ “ሰባት አጥፊዎችን ተጠንቀቁ” ይላሉ፡፡ “ምን ምን ናቸው እነሱ?” ሲባሉ፡-
((الشرك بالله، والسحر، وقتل النفس التي حرّم اللَّهُ إلا بالحق، وأكل الربا، وأكل مال اليتيم، والتّولّي يوم الزّحف، وقذف المحصنات الغافلات المؤمنات))
“በአላህ ማጋራት፣ ድግምት፣ አላህ ጥብቅ ያደረጋት ነፍስ መግደል - በሐቅ ካልሆነ በስተቀር፣ ወለድን መብላት፣ የየቲምን ገንዘብ መብላት፣ በጦርነት ጊዜ መሸሽ፣ ጥብቅና (ከጥፋት) የዘነጉ አማኝ ሴቶችን በዝሙት መወንጀል፡፡” [ቡኻሪና ሙስሊም]
ወለድ ከምን አይነት ወንጀሎች ጋር እንደተቆጠረ ተመልከት፡፡
2. ወለድ እንኳን ለአኺራ ለዱንያም አይጠቅምም፡፡ ይሄውና አላህ ምን እንደሚል፡-
{يَمْحَقُ اللَّهُ الرِّبا وَيُرْبِي الصَّدَقَاتِ }
“አላህ አራጣን ያጠፋል፡፡ ምፅዋቶችንም ያስፋፋል፡፡” [በቀራህ፡ 276]
በየገጠሩ ገበሬውን ባዶውን ያስቀሩት የቁጠባ ተቋማት ናቸው፡፡ ወለድ የገባው ሁሉ እንስሶቹ እያለቁ፣ ሰብሉ እየጠፋ፣ ንግዱ እየከሰረ መቀመቅ የገባው እጅግ በርካታ ህዝብ ነው፡፡ ወላሂ በአራቱም የሃገሪቱ አቅጣጫዎች የወጣ ከዚህ ጋር የተያያዘ ብዙ ለቅሶ ይሰማል፡፡ መሬት ላይ ያለው እውነት በኢቲቪ እንደሚደሰኮረው አይደለም፡፡ ነብዩ ﷺ “አንድ ሰው ከወለድ አያበዛም ፍፃሜው መመናመን ቢሆን እንጂ” ይላሉ፡፡ [ሶሒሑል ጃሚዕ፡ 5/120]
3. ያለ አስገዳጅ ሁኔታ ከወለድ ጋር የሚነካካ በሁሉም አቅጣጫ የተረገመ ነው፡፡ ሶሐባው ጃቢር ረዲየላሁ ዐንሁ እንዲህ ይላሉ፡-
((لعن رسول الله - صلى الله عليه وسلم -: آكل الربا، وموكله، وكاتبه، وشاهديه))، وقال: ((هم سواء))
“የአላህ መልእክተኛ ﷺ ወለድ የሚበላንም፣ የሚያበላውንም፣ ፀሐፊውንም፣ ምስክሮቹንም ተራግመዋል፡፡ ‘ሁሉም በወንጀሉ እኩል ናቸው!!’ ብለዋል፡፡” [ሙስሊም፡ 1598]
“እኔ ቢቸግረኝ ወሰድኩ እንጂ አራጣ አበዳሪ አይደለሁም” ብለህ እንዳትሸወድ፡፡ ያለፈውን ሐዲሥ ተመልከት፡፡ በተጨማሪም ነብዩ ﷺ “ወሳጅም ሰጪም እኩል ናቸው” ማለታቸውን ያዝ፡፡ [ሙስሊም፡ 1584] ስለዚህ ሙስሊም የሆነ ሰው ሌላው ቀርቶ በወለድ ተቋማት ውስጥ ጥበቃና ፅዳት እንኳን ሊሰራ አይገባውም፡፡
4. ወለድ ውስጥ የገባ ሰው ከአላህ ጋር ጦርነት ውስጥ ነው የገባው፡፡ አላህ እንዲህ ይላል፡-
{يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا اتَّقُوا اللَّهَ وَذَرُوا مَا بَقِيَ مِنَ الرِّبا إِنْ كُنْتُمْ مُؤْمِنِينَ * فَإِنْ لَمْ تَفْعَلُوا فَأْذَنُوا بِحَرْبٍ مِنَ اللَّهِ وَرَسُولِهِ}
“እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህን ፍሩ፡፡ ከአራጣም የቀረውን ተዉ፡፡ አማኞች እንደሆናችሁ (ተጠንቀቁ፡፡) (የታዘዛችሁትን) ባትሰሩም ከአላህና ከመልእክተኛው በሆነች ጦር (መወጋታችሁን) እወቁ፡፡” [አልበቀራ፡ 278-279]
ይቺ በነብዩ ﷺ ላይ መጨረሻ ላይ የወረደች አንቀፅ ነች ይላሉ ኢብኑ ዐባስ ረዲየላሁ ዐንሁ፡፡ [ቡኻሪ፡ 2086]
5. ወለድ የሚበላ ሰው ከቀብር የሚነሳው ልክ በጂን እንደተለከፈ ሰው እየተሳከረ ነው፡፡ አላህ እንዲህ ይላል፡-
{الَّذِينَ يَأْكُلُونَ الرِّبَا لا يَقُومُونَ إِلَّا كَمَا يَقُومُ الَّذِي يَتَخَبَّطُهُ الشَّيْطَانُ مِنَ الْمَسِّ}
“እነዚያ አራጣን የሚበሉ ያ ሰይጣን ከመንካቱ የተነሳ የሚጥለው ሰው (ከአውድቁ) እንደሚነሳ ብጤ እንጂ (ከመቃብራቸው) አይነሱም፡፡” [አልበቀራ፡ 275]
6. ወለድ ምህረት የለሸ ወንጀል ነው፡፡ ነብዩ ﷺ “ምህረት ከማያገኙ ወንጀሎች ተጠንቀቅ፡፡ … ወለድን መብላት፡፡ ወለድን የበላ ሰው በቂያማ ቀን ሸይጧን የሚጥለው እብድ ሆኖ ነው የሚነሳው” ካሉ በኋላ የላይኛውን አንቀፅ አነበቡ፡፡ ስለዚህ ትክክለኛ ተውበት ካልኖነ ጥፋቱ አደገኛ ነው፡፡
7. ወለድ የከሃዲዎቹ አይሁዳውያን ተግባር ነው፡፡ አላህ እንዲህ ይላል፡-
{وَأَخْذِهِمُ الرِّبا وَقَدْ نُهُوا عَنْهُ وَأَكْلِهِمْ أَمْوَالَ النَّاسِ بِالْبَاطِلِ وَأَعْتَدْنَا لِلْكَافِرِينَ مِنْهُمْ عَذَاباً أَلِيماً}
“ከርሱ በቁርጥ የተከለከሉ ሲሆኑ አራጣንም በመያዛቸውና የሰዎችን ገንዘቦች ያለ አግባብ በመብላታቸውም ሳቢያ (የተፈቀደላቸውን እርም አደረግንባቸው፡፡) ከነሱም ለከሃዲዎቹ አሳማሚን ቅጣት አዘጋጀን፡፡” [አንኒሳእ፡ 161]
8. የወለድ መብዛት የቂያማ ምልክት ነው፡፡ ነብዩ ﷺ “ቂያማ ሲቃረብ ወለድ፣ ዝሙት እና አስካሪ መጠጥ ይበዛል” ይላሉ፡፡ [ሶሒሑ አትተርጊብ ወትተርሂብ፡ 1861]
9. ወለድ የሚበላ ሰው አሰቃቂ ስቃይ አለበት፡፡ ነብዩ ﷺ እንዲህ ይላሉ፡-
“ዛሬ ሌሊት ሁለት ሰዎችን አየሁኝ፡፡ ወደተቀደሰች ምድርም ይዘውኝ ወጡ፡፡ ደም የሚጎርፍበት ወንዝ እስከምንደርስም ተጓዝን፡፡ በውስጡ አንድ የቆመ ሰው አለ፡፡ ከወንዙ ዳርቻ አንድ ሰው አለ፡፡ ከፊት ለፊቱ ድንጋዮች አሉ፡፡ ወንዙ ውስጥ ያለው ሰውየ ሊወጣ ሲያመራ ዳር ላይ ያለው ሰውየ አፍ አፉን በድንጋይ እየመታ ወደነበረበት ይመልሰዋል፡፡ ሊወጣ በሞከረ ቁጥር ድንጋይ እየወረወረ አፍ አፉን ይመታዋል፡፡ ከዚያም ወደነበረበት ይመለሳል፡፡ ‘ማነው ይሄ ወንዙ ውስጥ ያየሁት?’ ስል ‘ወለድ የሚበላ ነው’ ይለኛል፡፡” [ቡኻሪ፡ 2085]
10. ወለድ ከምናስበው በላይ እጅግ የገዘፈ ወንጀል ነው፡፡ ነብዩ ﷺ “ወለድ ሰባ ሶስት አይነት ነው፡፡ ከነዚህ ውስጥ ቀላሉ አንድ ሰው እናቱ ላይ ዝሙት እንደመስራት ነው” ይላሉ፡፡ [ሶሒሑ አትተርጊብ ወትተርሂብ፡ 1851]
11. የወለድ መብዛት በምድር ላይ የአላህን ቅጣት ያስከትላል፡፡ ነብዩ ﷺ “ዝሙትና ወለድ በአንድ ሃገር ላይ ከበዛ በራሳቸው ላይ የአላህን ቅጣት አስወስነዋል” ይላሉ፡፡ [ሶሒሑ አትተርጊብ ወትተርሂብ፡ 1859]
ዘመናችን በርካታ የቂያማ ምልክቶች የሚታዩበት አስፈሪ ዘመን ነው፡፡ ከነዚህ ምልክቶች ውስጥ አንዱ የወለድ መንሰራፋት ነው፡፡ ወለድ በቁርኣን፣ በሐዲሥና በምሁራን ኢጅማዕ የተወገዘ እጅግ አደገኛ ወንጀል ነው፡፡ ወንጀሉ ምንም እንኳን አደገኛ ቢሆንም ነገር ግን እንደ ሰደድ እሳት እየተስፋፋ ነው፡፡ ከጥፋቱ መስፋፋት በላይ ይበልጥ የሚደንቀው ግን በተለያዩ ስልቶች ኢስላማዊ ሽፋን ሊሰጡት አጉል የሚባዝኑ ስራዎች ብቅ ብቅ ማለታቸው ነው፡፡ ከነዚህ ውስጥም አንዱ “የወረቀት ገንዘብ እና ወለድ” በሚል ርእስ በቅርቡ የወጣው መፅሐፍ ነው፡፡ ፀሐፊው ጥራዝ ነጠቅ ብቻ ሳይሆን ሲበዛ ደፋር ነው፡፡ ስለ መፅሐፉ በሌላ ጊዜ እመለሳለሁ፣ ኢንሻአላህ፡፡ ላሁን የወለድን አስከፊነት የሚያሳዩ ማስረጃዎችን እንደሚከተለው አቅርቤያለሁ፡፡
1. ወለድ ከሰባት ከባባድ ወንጀሎች ውስጥ አንዱ ነው፡፡ ነብዩ ﷺ “ሰባት አጥፊዎችን ተጠንቀቁ” ይላሉ፡፡ “ምን ምን ናቸው እነሱ?” ሲባሉ፡-
((الشرك بالله، والسحر، وقتل النفس التي حرّم اللَّهُ إلا بالحق، وأكل الربا، وأكل مال اليتيم، والتّولّي يوم الزّحف، وقذف المحصنات الغافلات المؤمنات))
“በአላህ ማጋራት፣ ድግምት፣ አላህ ጥብቅ ያደረጋት ነፍስ መግደል - በሐቅ ካልሆነ በስተቀር፣ ወለድን መብላት፣ የየቲምን ገንዘብ መብላት፣ በጦርነት ጊዜ መሸሽ፣ ጥብቅና (ከጥፋት) የዘነጉ አማኝ ሴቶችን በዝሙት መወንጀል፡፡” [ቡኻሪና ሙስሊም]
ወለድ ከምን አይነት ወንጀሎች ጋር እንደተቆጠረ ተመልከት፡፡
2. ወለድ እንኳን ለአኺራ ለዱንያም አይጠቅምም፡፡ ይሄውና አላህ ምን እንደሚል፡-
{يَمْحَقُ اللَّهُ الرِّبا وَيُرْبِي الصَّدَقَاتِ }
“አላህ አራጣን ያጠፋል፡፡ ምፅዋቶችንም ያስፋፋል፡፡” [በቀራህ፡ 276]
በየገጠሩ ገበሬውን ባዶውን ያስቀሩት የቁጠባ ተቋማት ናቸው፡፡ ወለድ የገባው ሁሉ እንስሶቹ እያለቁ፣ ሰብሉ እየጠፋ፣ ንግዱ እየከሰረ መቀመቅ የገባው እጅግ በርካታ ህዝብ ነው፡፡ ወላሂ በአራቱም የሃገሪቱ አቅጣጫዎች የወጣ ከዚህ ጋር የተያያዘ ብዙ ለቅሶ ይሰማል፡፡ መሬት ላይ ያለው እውነት በኢቲቪ እንደሚደሰኮረው አይደለም፡፡ ነብዩ ﷺ “አንድ ሰው ከወለድ አያበዛም ፍፃሜው መመናመን ቢሆን እንጂ” ይላሉ፡፡ [ሶሒሑል ጃሚዕ፡ 5/120]
3. ያለ አስገዳጅ ሁኔታ ከወለድ ጋር የሚነካካ በሁሉም አቅጣጫ የተረገመ ነው፡፡ ሶሐባው ጃቢር ረዲየላሁ ዐንሁ እንዲህ ይላሉ፡-
((لعن رسول الله - صلى الله عليه وسلم -: آكل الربا، وموكله، وكاتبه، وشاهديه))، وقال: ((هم سواء))
“የአላህ መልእክተኛ ﷺ ወለድ የሚበላንም፣ የሚያበላውንም፣ ፀሐፊውንም፣ ምስክሮቹንም ተራግመዋል፡፡ ‘ሁሉም በወንጀሉ እኩል ናቸው!!’ ብለዋል፡፡” [ሙስሊም፡ 1598]
“እኔ ቢቸግረኝ ወሰድኩ እንጂ አራጣ አበዳሪ አይደለሁም” ብለህ እንዳትሸወድ፡፡ ያለፈውን ሐዲሥ ተመልከት፡፡ በተጨማሪም ነብዩ ﷺ “ወሳጅም ሰጪም እኩል ናቸው” ማለታቸውን ያዝ፡፡ [ሙስሊም፡ 1584] ስለዚህ ሙስሊም የሆነ ሰው ሌላው ቀርቶ በወለድ ተቋማት ውስጥ ጥበቃና ፅዳት እንኳን ሊሰራ አይገባውም፡፡
4. ወለድ ውስጥ የገባ ሰው ከአላህ ጋር ጦርነት ውስጥ ነው የገባው፡፡ አላህ እንዲህ ይላል፡-
{يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا اتَّقُوا اللَّهَ وَذَرُوا مَا بَقِيَ مِنَ الرِّبا إِنْ كُنْتُمْ مُؤْمِنِينَ * فَإِنْ لَمْ تَفْعَلُوا فَأْذَنُوا بِحَرْبٍ مِنَ اللَّهِ وَرَسُولِهِ}
“እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህን ፍሩ፡፡ ከአራጣም የቀረውን ተዉ፡፡ አማኞች እንደሆናችሁ (ተጠንቀቁ፡፡) (የታዘዛችሁትን) ባትሰሩም ከአላህና ከመልእክተኛው በሆነች ጦር (መወጋታችሁን) እወቁ፡፡” [አልበቀራ፡ 278-279]
ይቺ በነብዩ ﷺ ላይ መጨረሻ ላይ የወረደች አንቀፅ ነች ይላሉ ኢብኑ ዐባስ ረዲየላሁ ዐንሁ፡፡ [ቡኻሪ፡ 2086]
5. ወለድ የሚበላ ሰው ከቀብር የሚነሳው ልክ በጂን እንደተለከፈ ሰው እየተሳከረ ነው፡፡ አላህ እንዲህ ይላል፡-
{الَّذِينَ يَأْكُلُونَ الرِّبَا لا يَقُومُونَ إِلَّا كَمَا يَقُومُ الَّذِي يَتَخَبَّطُهُ الشَّيْطَانُ مِنَ الْمَسِّ}
“እነዚያ አራጣን የሚበሉ ያ ሰይጣን ከመንካቱ የተነሳ የሚጥለው ሰው (ከአውድቁ) እንደሚነሳ ብጤ እንጂ (ከመቃብራቸው) አይነሱም፡፡” [አልበቀራ፡ 275]
6. ወለድ ምህረት የለሸ ወንጀል ነው፡፡ ነብዩ ﷺ “ምህረት ከማያገኙ ወንጀሎች ተጠንቀቅ፡፡ … ወለድን መብላት፡፡ ወለድን የበላ ሰው በቂያማ ቀን ሸይጧን የሚጥለው እብድ ሆኖ ነው የሚነሳው” ካሉ በኋላ የላይኛውን አንቀፅ አነበቡ፡፡ ስለዚህ ትክክለኛ ተውበት ካልኖነ ጥፋቱ አደገኛ ነው፡፡
7. ወለድ የከሃዲዎቹ አይሁዳውያን ተግባር ነው፡፡ አላህ እንዲህ ይላል፡-
{وَأَخْذِهِمُ الرِّبا وَقَدْ نُهُوا عَنْهُ وَأَكْلِهِمْ أَمْوَالَ النَّاسِ بِالْبَاطِلِ وَأَعْتَدْنَا لِلْكَافِرِينَ مِنْهُمْ عَذَاباً أَلِيماً}
“ከርሱ በቁርጥ የተከለከሉ ሲሆኑ አራጣንም በመያዛቸውና የሰዎችን ገንዘቦች ያለ አግባብ በመብላታቸውም ሳቢያ (የተፈቀደላቸውን እርም አደረግንባቸው፡፡) ከነሱም ለከሃዲዎቹ አሳማሚን ቅጣት አዘጋጀን፡፡” [አንኒሳእ፡ 161]
8. የወለድ መብዛት የቂያማ ምልክት ነው፡፡ ነብዩ ﷺ “ቂያማ ሲቃረብ ወለድ፣ ዝሙት እና አስካሪ መጠጥ ይበዛል” ይላሉ፡፡ [ሶሒሑ አትተርጊብ ወትተርሂብ፡ 1861]
9. ወለድ የሚበላ ሰው አሰቃቂ ስቃይ አለበት፡፡ ነብዩ ﷺ እንዲህ ይላሉ፡-
“ዛሬ ሌሊት ሁለት ሰዎችን አየሁኝ፡፡ ወደተቀደሰች ምድርም ይዘውኝ ወጡ፡፡ ደም የሚጎርፍበት ወንዝ እስከምንደርስም ተጓዝን፡፡ በውስጡ አንድ የቆመ ሰው አለ፡፡ ከወንዙ ዳርቻ አንድ ሰው አለ፡፡ ከፊት ለፊቱ ድንጋዮች አሉ፡፡ ወንዙ ውስጥ ያለው ሰውየ ሊወጣ ሲያመራ ዳር ላይ ያለው ሰውየ አፍ አፉን በድንጋይ እየመታ ወደነበረበት ይመልሰዋል፡፡ ሊወጣ በሞከረ ቁጥር ድንጋይ እየወረወረ አፍ አፉን ይመታዋል፡፡ ከዚያም ወደነበረበት ይመለሳል፡፡ ‘ማነው ይሄ ወንዙ ውስጥ ያየሁት?’ ስል ‘ወለድ የሚበላ ነው’ ይለኛል፡፡” [ቡኻሪ፡ 2085]
10. ወለድ ከምናስበው በላይ እጅግ የገዘፈ ወንጀል ነው፡፡ ነብዩ ﷺ “ወለድ ሰባ ሶስት አይነት ነው፡፡ ከነዚህ ውስጥ ቀላሉ አንድ ሰው እናቱ ላይ ዝሙት እንደመስራት ነው” ይላሉ፡፡ [ሶሒሑ አትተርጊብ ወትተርሂብ፡ 1851]
11. የወለድ መብዛት በምድር ላይ የአላህን ቅጣት ያስከትላል፡፡ ነብዩ ﷺ “ዝሙትና ወለድ በአንድ ሃገር ላይ ከበዛ በራሳቸው ላይ የአላህን ቅጣት አስወስነዋል” ይላሉ፡፡ [ሶሒሑ አትተርጊብ ወትተርሂብ፡ 1859]
Forwarded from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የሽንት ቤት አጠቃቀም ስነ ስርኣት
ፅሑፉን ለማሳጠር ስል በእያንዳንዱ ነጥብ ስር ያሉትን ማስረጃዎች አልጠቀስኩም። ሆኖም ግን ማስረጃዎቹ የሚገኙበትን ምንጭ ስለጠቀስኩ ያስፈለገው በቁጥሩ ማግኘት ይችላል።
① እንዳይሰረቁ ወይም እንዳይጠፋ ካልሰጉ በስተቀር የአላህ ስም ያለበት ነገር ይዞ ሽንት ቤት ውስጥ አለመግባት።
② የሚፀዳዱት ሜዳ ላይ ከሆነ ከሰው እይታ ራቅ/ ሰወር ማለት። [ሶሒሕ ኢብኑ ማጃህ: 1/ 60]
③ በሰው መተላለፊያ መንገድ ላይ ወይ አጠገብ፣ ሰዎች ከሚጠለሉበት ዛፍ ስር፣ ፍሬው ከሚበላ ዛፍ ስር፣ የፍራፍሬ ዛፍና አትክልቶች አጠገብ፣ ወራጅ ባልሆነ ውሃ ላይ፣ የውሃ ምንጭ ላይ፣ በሙስሊሞች መቃብር ውስጥ አለመፀዳዳት። [ኢርዋኡል ገሊል: 1/100] [ሙስሊም: 269፣ 281] [ኢርዋእ: 1/102]
④ ንፋስ ወደሚነፍስበት አቅጣጫ ዙሮ አለመፀዳዳት፣ ይህን ትኩረት መስጠት ለጤናም፣ ለንፅህናም የተሻለ ነው።
⑤ የተሰነጠቀ መሬት ላይ ወይም ቀዳዳዎች ላይ አለመፀዳዳት። [አቡ ዳውድ: 29]
⑥ ውጭ ላይ የሚፀዳዱ ከሆነ ወደ መሬት ዝቅ እስከሚሉ ልብስን አለመሰብሰብ ወይም አለማውረድ። [ሶሒሑል ጃሚዕ: 4652]
⑦ ውጭ ላይ በሚፀዳዱ ጊዜ ወደ ቂብላ አለመዞር፣ ጀርባንም ለቂብላ አለመስጠት። ሽንት ቤት ውስጥ ከሆነ ወይም ከፊት የሚጋርድ (ግድግዳና መሰል) ነገር ከኖረ ችግር የለውም። ይህንንም ቢሆን ከተቻለ መጠንቀቅ። [ቡኻሪና ሙስሊም] [ኢርዋእ: ቁ· 61]
⑧ ሽንት ቤት ሲገቡ ግራ እግርን ማስቀደም፣
⑨ ሽንት ቤት ሲገቡ "ቢስሚላህ። አላሁመ ኢኒ አዑዙ ቢከ ሚነል ኹቡሢ ወልኸባኢሥ" ብሎ ከሸይጧን መጠበቂያ ዱዓ ማድረግ። [ሶሒሑል ጃሚዕ: 3611] [ቡኻሪና ሙስሊም]
(10) በሚፀዳዱ ጊዜ ብልትን በቀኝ እጅ አለመንካት፣ በቀኝ እጅ አለመፀዳዳት፣ [ቡኻሪና ሙስሊም]
(11) በሚፀዳዱበት ጊዜ በተቻለ መጠን ከማውራት መቆጠብ። [ሙስሊም: 370]
(12) ቢያንስ በሶስት ድንጋይ፣ ሶፍት፣ ወረቀትና መሰል ነገር መፀዳዳት። አንድም ቢሆን ሶስት የተለያዩ ጎኖች ወይም ገፆች ከኖሩትም በቂ ሊሆን ይችላል። ወይም በውሃ መጠቀም። አጥንት፣ ፋንዲያ፣ ምግብ ነክ ነገር እና ንፁህ ያልሆነ ነገር ለመፀዳጃነት አይውልም። [ሙስሊም: 262፣ 263፣ 271]
(12) ከሽንት ቤት ሲወጡ ቀኝ እግርን አስቀድሞ መውጣት።
(13) ከሽንት ቤት ሲወጡ "ጉፍራነክ" ማለት። [ሶሒሑል ጃሚዕ: 4707]
(ኢብኑ ሙነወር፣ መጋቢት 23/2010)
ፅሑፉን ለማሳጠር ስል በእያንዳንዱ ነጥብ ስር ያሉትን ማስረጃዎች አልጠቀስኩም። ሆኖም ግን ማስረጃዎቹ የሚገኙበትን ምንጭ ስለጠቀስኩ ያስፈለገው በቁጥሩ ማግኘት ይችላል።
① እንዳይሰረቁ ወይም እንዳይጠፋ ካልሰጉ በስተቀር የአላህ ስም ያለበት ነገር ይዞ ሽንት ቤት ውስጥ አለመግባት።
② የሚፀዳዱት ሜዳ ላይ ከሆነ ከሰው እይታ ራቅ/ ሰወር ማለት። [ሶሒሕ ኢብኑ ማጃህ: 1/ 60]
③ በሰው መተላለፊያ መንገድ ላይ ወይ አጠገብ፣ ሰዎች ከሚጠለሉበት ዛፍ ስር፣ ፍሬው ከሚበላ ዛፍ ስር፣ የፍራፍሬ ዛፍና አትክልቶች አጠገብ፣ ወራጅ ባልሆነ ውሃ ላይ፣ የውሃ ምንጭ ላይ፣ በሙስሊሞች መቃብር ውስጥ አለመፀዳዳት። [ኢርዋኡል ገሊል: 1/100] [ሙስሊም: 269፣ 281] [ኢርዋእ: 1/102]
④ ንፋስ ወደሚነፍስበት አቅጣጫ ዙሮ አለመፀዳዳት፣ ይህን ትኩረት መስጠት ለጤናም፣ ለንፅህናም የተሻለ ነው።
⑤ የተሰነጠቀ መሬት ላይ ወይም ቀዳዳዎች ላይ አለመፀዳዳት። [አቡ ዳውድ: 29]
⑥ ውጭ ላይ የሚፀዳዱ ከሆነ ወደ መሬት ዝቅ እስከሚሉ ልብስን አለመሰብሰብ ወይም አለማውረድ። [ሶሒሑል ጃሚዕ: 4652]
⑦ ውጭ ላይ በሚፀዳዱ ጊዜ ወደ ቂብላ አለመዞር፣ ጀርባንም ለቂብላ አለመስጠት። ሽንት ቤት ውስጥ ከሆነ ወይም ከፊት የሚጋርድ (ግድግዳና መሰል) ነገር ከኖረ ችግር የለውም። ይህንንም ቢሆን ከተቻለ መጠንቀቅ። [ቡኻሪና ሙስሊም] [ኢርዋእ: ቁ· 61]
⑧ ሽንት ቤት ሲገቡ ግራ እግርን ማስቀደም፣
⑨ ሽንት ቤት ሲገቡ "ቢስሚላህ። አላሁመ ኢኒ አዑዙ ቢከ ሚነል ኹቡሢ ወልኸባኢሥ" ብሎ ከሸይጧን መጠበቂያ ዱዓ ማድረግ። [ሶሒሑል ጃሚዕ: 3611] [ቡኻሪና ሙስሊም]
(10) በሚፀዳዱ ጊዜ ብልትን በቀኝ እጅ አለመንካት፣ በቀኝ እጅ አለመፀዳዳት፣ [ቡኻሪና ሙስሊም]
(11) በሚፀዳዱበት ጊዜ በተቻለ መጠን ከማውራት መቆጠብ። [ሙስሊም: 370]
(12) ቢያንስ በሶስት ድንጋይ፣ ሶፍት፣ ወረቀትና መሰል ነገር መፀዳዳት። አንድም ቢሆን ሶስት የተለያዩ ጎኖች ወይም ገፆች ከኖሩትም በቂ ሊሆን ይችላል። ወይም በውሃ መጠቀም። አጥንት፣ ፋንዲያ፣ ምግብ ነክ ነገር እና ንፁህ ያልሆነ ነገር ለመፀዳጃነት አይውልም። [ሙስሊም: 262፣ 263፣ 271]
(12) ከሽንት ቤት ሲወጡ ቀኝ እግርን አስቀድሞ መውጣት።
(13) ከሽንት ቤት ሲወጡ "ጉፍራነክ" ማለት። [ሶሒሑል ጃሚዕ: 4707]
(ኢብኑ ሙነወር፣ መጋቢት 23/2010)
የሴቶችን ድንግልና የሚወስደው ማን ነው?
ይህን ፅሁፍ ለማዘጋጀት ያነሳሳኝ አብዛኛውን ጊዜ አንዳንድ ወደ እስልምና እንጣራለን የሚሉ ሰዎች ህግጋቱን ሁሉ ሴቶች ላይ ጫን አድርገው ወንዶችን ብዙም ሲሉ አይሰማም፡፡
ሰሞኑን አላዋቂዎች ብዙ ሲሳለቁ እና እራሳቸውንም መግለጫ ሰጪ አድርገው ሲያዩ ተመልክተናል፡፡ የሴት ልጅ ድንግልና በብዙ መንገድ ይሄዳል፡፡ ለምሳሌ ሴት ልጆችን በገዛ የቅርብ ቤተሰቦቻቸው እና ዘመዶቻቸው በመደፈር ሁሉ ያጡታል፡፡ ሴት ልጆች ሲደፈሩ ያውም ደፋሪያቸው እየታወቀ “በቃ ዝም በይ” አይነት ማስጠንቀቂያዎች ይሰጧታል፡፡ ድንግልና ያለ ግንኙነትም ሊጠፋ የሚችልበት ሁኔታ እንዳለ ዑለማዎችም ሀኪሞችም ይገልፃሉ። ስለዚህ ድንግልና የሌላት ሁሉ ብልግና ፈፅማለች ማለት ዝቅ ሲል አላዋቂነት ከፍ ሲል ብልግና ነው። በሌሎችም መንገዶች ድንግልና ይሄዳል፡፡
አብዛኛዎቹ ሴቶች ልጅ በነበሩበት ሰኣት በጣም አይን አፋር እና ድንጉጥ ናቸው፡፡ ወንድን መቅረብ አይፈልጉም፡፡ ሴቶቹን ወደ መጥፎ ነገር የሚመሩዋቸው መጥፎ ሴት ጓደኞች እና ምላሳም ወንዶች ናቸው፡፡
መቼም ወንድ ከሌለ ሴቶች በራሳቸው ድንግልናቸውን አጠፉት አይባልም፡፡ አንድ ሴት ልጅ ድንግልናዋን ስታጣ እሷን ብቻ ከመውቀስ በምላሱ አታሎ፣ አጭበርብሮ ድንግልናዋን የወሰደባትን ለምን በደንብ አይኮንኑትም?
አስገራሚው ሴት ልጅ ስትሰራ ከነበረችው መጥፎ ነገር ቶብታለች ሲባል “እሷ እኮ…. ነበረች…. መጠንቀቅ ነው …. ምን ይታወቃል” እና የመሳሰለውን ትንኮሳዎች ይተበተባሉ፡፡
ወንድ ልጅ ግን ለምሳሌ አንዴ በድፍረት 21 ወይንም 22 አመት የሚጠጋው ወንድ ለጓደኞቹ “ከ180 እስከ 200 ሴቶች ጋር ግንኙነት ፈፅሚያለሁ” እንዳላቸው ሲናገሩ ሰምቻለሁ (የአላህ መልክተኛ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም የእኔ ኡመቶች ወንጀል ይማራል ግልፅ የሚያወጣው ሲቀር ብለዋል፡፡ ወንጀልን እንደቁም ነገር እና ጀብዱ የምታወሩ ሰዎች አላህን ፍሩ)፡፡ ለምሳሌ ይህን ሁሉ ሴት የነካካ ወንድ ቶብቷል ቢባል “አቤት እሱ እኮ ሷሊህ ነው፡፡ አቤት አኽላቁ፡፡ አቤት እሱን ያገኘች” ተብሎ ይለፈፋል፡፡
ለምን?
አላህ በተከበረው ቁርኣን ላይ
- ዝሙትን በተመለከት ተከልከሉ ሲል ለወንዱም ለሴቱም ነው፡፡
- ዝሙት ከፈፀሙ ያላገቡ ከሆኑ 100 ጅራፉ ይገረፉ ሲል ወንዱንም ሴቷንም ነው፡፡
- ዝሙትን የፈፀሙት ያገቡ ከሆነ በድንጋይ ተቀጥቅጠው ይገደሉ ሲል ወንድንም ሴትንም ነው፡፡
ታድያ ለምን ይሄን ያህል ሁለቱንም የሚመለከተውን ህግ ሴቶች ላይ ብቻ ጫን ማለት አስፈለገ፡፡ እንጨት ለምሳሌ በራሱ አይቀጣጠልም እሳት ሲቀላቀልበት ቢሆን እንጂ፡፡ ስለዚህ ወንድ እና ሴት በፈፀሙት ወንጀል አንዱን ብቻ ጠንከር አድርጎ መውቀሱ በተለይ ከኢስላም ውጭ ያሉ ሰዎች “ኢስላም ሴትን ይበድላል” እንዲሉ የሚያደርጋቸው ይህ ነው፡፡
ፍትሀዊ የሆነ ሀይማኖት ይዘን ፍትህ የሌለ አስመስለን አናቅርበው፡፡ ያለ እውቀት መናገር ሁሌም ጣጣው ከሚታሰበው በላይ ነው፡፡
የቶበቱ ሰዎችን አስመልክቶ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ወደ አላህ የተመለሰ ወንጀል እንደሌለበት ነው፡፡” ብለው ሲያበቁ ወደ አላህ የተመለሱ ሰዎችን እያጣጣሉ መናገር መሀይምነትን በይፋ የሚያሳይ ነው፡፡
አስገራሚው ግልፅ ቢድኣና ሺርክን የሚያሰራጩ ግለሰቦች ላይ የሌላቸውን ጥንካሪ እና ድፍረት ወንጀል ላይ የወደቁት ላይ ሲያደርጉት እንመለከታለን፡፡
ወንጀል በድብቅ የሰራ ሰው አይቡ ይደበቅለታል፡፡ ቢድኣን እና ሺርክን በአደባባይ የሚፈፅም ደግሞ በአደባባይ ሙስሊሞች እንዲጠነቀቁት መልስ ይሰጥበታል ይህ ነው ፍትህ እና ሚዛናዊነት፡፡
ዛሬ የቢድኣ ካዝና ለሆኖ ሰዎች ጥብቅና ቆመው እነሱን አናስነካም፡፡ እነሱን የነካ “አይባቸውን እንዳወጣ ነው” ሲሉ ይቆዩና ተደብቀው ወንጀል የሚሰሩ ሰዎችን “ተከታትለን በካሜራ እናጋልጣለን” ብለው ስሜት አምላኪነታቸውን ያሳዩናል፡፡
እንዲህ አይነት መሀይማን ጉዳታቸው እጅጉን የከፋ ነው፡፡
ፅሁፌን ስጨርስ ሴቶችን እንደነ መርየም ድንግልናችሁን ጠብቁ ስንል፣ ወንዶችንም ልክ እንደነ ኡስማን ኢብን አፋን ሁኑ ከዝሙት ራቁ፡፡ ወንድ እና ሴቶች ሆይ! አላህን ፈርታችሁ ቶሎ ተጋቡ፡፡ በኢስላም ትዳር ትልቅ ቦታ አለው፡፡ ከትዳር ያለ አስገዳጅ ሀጃ በመዘግየታችሁ ምንም የምትጨምሩት ነገር የለም፡፡ የምታጡት ነገር ቢብስ እንጂ፡፡
ስለ ትዳር የበሰሉ ሃያእ ያላቸውን ታላቆችን አማክሩ፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
ይህን ፅሁፍ ለማዘጋጀት ያነሳሳኝ አብዛኛውን ጊዜ አንዳንድ ወደ እስልምና እንጣራለን የሚሉ ሰዎች ህግጋቱን ሁሉ ሴቶች ላይ ጫን አድርገው ወንዶችን ብዙም ሲሉ አይሰማም፡፡
ሰሞኑን አላዋቂዎች ብዙ ሲሳለቁ እና እራሳቸውንም መግለጫ ሰጪ አድርገው ሲያዩ ተመልክተናል፡፡ የሴት ልጅ ድንግልና በብዙ መንገድ ይሄዳል፡፡ ለምሳሌ ሴት ልጆችን በገዛ የቅርብ ቤተሰቦቻቸው እና ዘመዶቻቸው በመደፈር ሁሉ ያጡታል፡፡ ሴት ልጆች ሲደፈሩ ያውም ደፋሪያቸው እየታወቀ “በቃ ዝም በይ” አይነት ማስጠንቀቂያዎች ይሰጧታል፡፡ ድንግልና ያለ ግንኙነትም ሊጠፋ የሚችልበት ሁኔታ እንዳለ ዑለማዎችም ሀኪሞችም ይገልፃሉ። ስለዚህ ድንግልና የሌላት ሁሉ ብልግና ፈፅማለች ማለት ዝቅ ሲል አላዋቂነት ከፍ ሲል ብልግና ነው። በሌሎችም መንገዶች ድንግልና ይሄዳል፡፡
አብዛኛዎቹ ሴቶች ልጅ በነበሩበት ሰኣት በጣም አይን አፋር እና ድንጉጥ ናቸው፡፡ ወንድን መቅረብ አይፈልጉም፡፡ ሴቶቹን ወደ መጥፎ ነገር የሚመሩዋቸው መጥፎ ሴት ጓደኞች እና ምላሳም ወንዶች ናቸው፡፡
መቼም ወንድ ከሌለ ሴቶች በራሳቸው ድንግልናቸውን አጠፉት አይባልም፡፡ አንድ ሴት ልጅ ድንግልናዋን ስታጣ እሷን ብቻ ከመውቀስ በምላሱ አታሎ፣ አጭበርብሮ ድንግልናዋን የወሰደባትን ለምን በደንብ አይኮንኑትም?
አስገራሚው ሴት ልጅ ስትሰራ ከነበረችው መጥፎ ነገር ቶብታለች ሲባል “እሷ እኮ…. ነበረች…. መጠንቀቅ ነው …. ምን ይታወቃል” እና የመሳሰለውን ትንኮሳዎች ይተበተባሉ፡፡
ወንድ ልጅ ግን ለምሳሌ አንዴ በድፍረት 21 ወይንም 22 አመት የሚጠጋው ወንድ ለጓደኞቹ “ከ180 እስከ 200 ሴቶች ጋር ግንኙነት ፈፅሚያለሁ” እንዳላቸው ሲናገሩ ሰምቻለሁ (የአላህ መልክተኛ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም የእኔ ኡመቶች ወንጀል ይማራል ግልፅ የሚያወጣው ሲቀር ብለዋል፡፡ ወንጀልን እንደቁም ነገር እና ጀብዱ የምታወሩ ሰዎች አላህን ፍሩ)፡፡ ለምሳሌ ይህን ሁሉ ሴት የነካካ ወንድ ቶብቷል ቢባል “አቤት እሱ እኮ ሷሊህ ነው፡፡ አቤት አኽላቁ፡፡ አቤት እሱን ያገኘች” ተብሎ ይለፈፋል፡፡
ለምን?
አላህ በተከበረው ቁርኣን ላይ
- ዝሙትን በተመለከት ተከልከሉ ሲል ለወንዱም ለሴቱም ነው፡፡
- ዝሙት ከፈፀሙ ያላገቡ ከሆኑ 100 ጅራፉ ይገረፉ ሲል ወንዱንም ሴቷንም ነው፡፡
- ዝሙትን የፈፀሙት ያገቡ ከሆነ በድንጋይ ተቀጥቅጠው ይገደሉ ሲል ወንድንም ሴትንም ነው፡፡
ታድያ ለምን ይሄን ያህል ሁለቱንም የሚመለከተውን ህግ ሴቶች ላይ ብቻ ጫን ማለት አስፈለገ፡፡ እንጨት ለምሳሌ በራሱ አይቀጣጠልም እሳት ሲቀላቀልበት ቢሆን እንጂ፡፡ ስለዚህ ወንድ እና ሴት በፈፀሙት ወንጀል አንዱን ብቻ ጠንከር አድርጎ መውቀሱ በተለይ ከኢስላም ውጭ ያሉ ሰዎች “ኢስላም ሴትን ይበድላል” እንዲሉ የሚያደርጋቸው ይህ ነው፡፡
ፍትሀዊ የሆነ ሀይማኖት ይዘን ፍትህ የሌለ አስመስለን አናቅርበው፡፡ ያለ እውቀት መናገር ሁሌም ጣጣው ከሚታሰበው በላይ ነው፡፡
የቶበቱ ሰዎችን አስመልክቶ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ወደ አላህ የተመለሰ ወንጀል እንደሌለበት ነው፡፡” ብለው ሲያበቁ ወደ አላህ የተመለሱ ሰዎችን እያጣጣሉ መናገር መሀይምነትን በይፋ የሚያሳይ ነው፡፡
አስገራሚው ግልፅ ቢድኣና ሺርክን የሚያሰራጩ ግለሰቦች ላይ የሌላቸውን ጥንካሪ እና ድፍረት ወንጀል ላይ የወደቁት ላይ ሲያደርጉት እንመለከታለን፡፡
ወንጀል በድብቅ የሰራ ሰው አይቡ ይደበቅለታል፡፡ ቢድኣን እና ሺርክን በአደባባይ የሚፈፅም ደግሞ በአደባባይ ሙስሊሞች እንዲጠነቀቁት መልስ ይሰጥበታል ይህ ነው ፍትህ እና ሚዛናዊነት፡፡
ዛሬ የቢድኣ ካዝና ለሆኖ ሰዎች ጥብቅና ቆመው እነሱን አናስነካም፡፡ እነሱን የነካ “አይባቸውን እንዳወጣ ነው” ሲሉ ይቆዩና ተደብቀው ወንጀል የሚሰሩ ሰዎችን “ተከታትለን በካሜራ እናጋልጣለን” ብለው ስሜት አምላኪነታቸውን ያሳዩናል፡፡
እንዲህ አይነት መሀይማን ጉዳታቸው እጅጉን የከፋ ነው፡፡
ፅሁፌን ስጨርስ ሴቶችን እንደነ መርየም ድንግልናችሁን ጠብቁ ስንል፣ ወንዶችንም ልክ እንደነ ኡስማን ኢብን አፋን ሁኑ ከዝሙት ራቁ፡፡ ወንድ እና ሴቶች ሆይ! አላህን ፈርታችሁ ቶሎ ተጋቡ፡፡ በኢስላም ትዳር ትልቅ ቦታ አለው፡፡ ከትዳር ያለ አስገዳጅ ሀጃ በመዘግየታችሁ ምንም የምትጨምሩት ነገር የለም፡፡ የምታጡት ነገር ቢብስ እንጂ፡፡
ስለ ትዳር የበሰሉ ሃያእ ያላቸውን ታላቆችን አማክሩ፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
አስተማሪና መሳጭ ታሪክ!
በስዑዲ የሚኖር አንድ የመኒ ነው፡፡ በአንድ ወቅት ያጋጠመውን ታሪክ እንዲህ ይተርከዋል፡፡
ከፊሌ የዘካ ገንዘብ ሊያከፋፍል ፈልጎ ከሱ ጋር ወጣሁ፡፡ የድሃ መንደሮች ወዳሉባቸው ጠረፍ አካባቢ ተጓዝን፡፡ የዘካው ገንዘቦች በፖስታ የታሸጉ ነበሩ፡፡ እያንዳንዱ ፖስታ በውስጡ 5 ሺ ሪያል ይዟል፡፡ ከአንዱ መንደር ወጥተን የጂዳ-ጂዛን መስመር ስንይዝ አንድ የ70 አመት አካባቢ ሽማግሌ አገኘን፡፡ ሽማግሌው ብርቱና ጤናማ ነው፡፡ ጎዳናውን ይዞ ይጓዛል፡፡
ወዳጄ “ይሄ ደግሞ በዚህ ሰዓት በዚህ በረሃ ምን ይሰራል?” አለኝ፡፡
ሹፌሩ “ህገ ወጥ የመኒ ነው” አለ፡፡
ካጠገቡ ደርሰን ቆምንና ሰላም አልነው፡፡
“ከየት ነው ወንድም?”
“ከየመን”
“የት ነው የምትሄደው?”
“የአላህን ቤት ናፍቄያለሁ”
“ህጋዊ ነህ?”
“አይደለሁም”
“ለምን ህጋዊ አልሆንክም?”
“ለዋስትና 2 ሺ ሪያል ማስያዝ ይጠበቅብኛል፡፡ እኔ ያለኝ 200 ብቻ ነው፡፡ በመቶዋ ተሳፈርኩባት፡፡ የቀረኝ መቶ ብቻ ነው” አለ፡፡
“እሺ አጎቴ! በጉዞ ላይ ምን ያክል ሆነህ?” አለው ጓደኛየ፡፡
“ስድስት ቀን!”
“እየፆምክ አይደለም?”
“አይ ፆመኛ ነኝ፡፡”
“ጥሩ፡፡ አንተ ከ 5 በላይ የፍተሸ ኬላዎችን አልፈሃል፡፡ እንዴት ነበር የምታልፋቸው?” ሲለው
“ከሱ በስተቀር እውነተኛ አምላክ በሌለው አላህ እምላለሁ! የማልፈው በነሱው ዘንድ ነው፡፡ ግን አንድም ያናገረኝ የለም!!” አለ፡፡
“ለስራ ነው አመጣጥህ?”
“በጭራሽ ወላሂ! እኔ የአላህን ቤት ናፍቄ ነው የመጣሁት፡፡ ዑምራ ማድረግ ነው የምፈልገው፡፡ ወደ መካ ነው የምጓዘው፡፡”
“በአስፋልት ላይ ስትጓዝ ተዘዋዋሪ ዘቦች /ፓትሮል/ አልያዙህም?”
“ከግማሽ ሰዓት በፊት በ 50 ኪ. ሜ. ርቀት ላይ ይዘውኝ ነበር፡፡ እዚህ ከመድረሴ አንድ ኪ. ሜ. ቀደም ብሎ ድረስ እነሱ ናቸው ያመጡኝ፡፡ የት እንደምሄድ ሲይቁኝ በአላህ ምየ የአላህን ቤት እንደምፈልግ ስነግራቸው ለቀቁኝ” አለ፡፡
“ሱብሓነላህ! ጭራሽ እስከዚህ ቦታ በፍጥነት እንዲያደርሱህ አላህ ፓትሮሎችን አመቻቸልህ” አልኩኝ በውስጤ፡፡
ወዳጄ ሁለት ፖስታዎችን እየሰጠው “እነዚህን ያዝ፡፡ ዘካ ነው” አለው፡፡
እየተቀበለ “ጀዛኩሙላህ ኸይር” አለ፡፡
በፖስታዎቹ ያለው ገንዘብ መጠኑ ምን ያክል እንደሆነ አያውቅም፡፡
“የሰዑዲን ብር ታውቃለህ?” አልኩት፡፡
“አዎ!” አለ፡፡
“ጥሩ፡፡ ፖስታውን ክፈትና እንዳይጠፋብህ ገንዘቡን በቀበቶህ (በሒዛምህ) ውስጥ ደብቅ” አልኩት፡፡
ሲከፍተው 10 ሺህ ሪያል!!
“ይህ ሁሉ ለኔ ነው?” አለ፡፡
“አዎ ላንተ ነው” አልነው፡፡
ከመኪናው ላይ ወደቀ፡፡ እራሱን ሳተ፡፡ ከመኪናው ወርደን በላዩ ላይ ውሃ መርጨት ያዝን፡፡
“ይህ ሁሉ ገንዘብ ለኔ ነው? ይህ ሁሉ ገንዘብ ለኔ ነው?” እያለ መጮህ ያዘ፡፡ ቁጭ ብሎ ማልቀስ ቀጠለ፡፡
ወዳጄ፡ “ከኛ ጋር ትንሽ ወደ ፊት እንውሰደው” አለ፡፡
ከኛ ጋር መኪና ላይ ወጣ፡፡ ትንሽ ሲረጋጋ ጠየቅኩት፡
“ምንድን ነው ይህ ሁሉ ለቅሶ?” አልኩት፡፡
“እኔ የመን ውስጥ ከቤቴ ጎን ቦታ አለችኝ፡፡ ለአላህ ሰጥቻታለሁ፡፡ እኔና ቤተሰቦቼ በሷ ላይ በጭቃና በድንጋይ አድርገን መስጅድ ገንብተንባታል፡፡ ግንባታው ቢጠናቀቅም ምንጣፍና ጥቂት ነገሮች ቀርተውት ነበር፡፡ ለዚህ መስጂድ እንዴት ምንጣፍ እንደማገኝ ተቀምጬ አስብ ነበር” አለ፡፡
ይህን ሲል የእውነት ሁላችንም አለቀስን፡፡ “አሳቡ ኣኺራ የሆነ ሰው ዱንያ እንዳለች ትመጣለታለች” የሚለውና “አሳቡ ኣኺራ የሆነ ሰው አላህ መብቃቃቱን ከልቡ ውስጥ ያደርግለታል፡፡ ነገሩንም ይሰበስብለታል፡፡ ዱንያ በግዷ ወደሱ ትመጣለች፡፡ አሳቡ ዱንያ የሆነ ደግሞ አላህ ድህነቱን በአይኖቹ መሀል ያደርግበታል፡፡ ነገሩንም ይበትንበታል፡፡ ከዱንያም የተወሰነለት ብቻ እንጂ አይመጣለትም” የሚለው የነብዩ ﷺ ንግግር ትዝ አለኝ፡፡
በዚህን ጊዜ ወዳጄን ለሰውየው እንዲጨምረው ጠየቅኩት፡፡ ተጨማሪ 2 እሽግ ፖስታ ሰጠው፡፡ በድምሩ 20 ሺ ሪያል አገኘ ሰውየው፡፡ ሰውየው ከመኪናው ከመውረዱ በፊት እያለቀሰ ያጉተመትምና ዱዓ ያደርግ ነበር፡፡
“በአላህ ላይ እውነተኛ የሆነውን መመካት ብትመኩ ኖሮ ልክ ወፍን እንደሚረዝቀው ይረዝቃችሁ ነበር፡፡ ተርባ ወጥታ ጠግባ ትመለሳለች” የሚለው የነብዩ ﷺ ሐዲሥ መጣብኝ፡፡
የተተረጎመ
(ኢብኑ ሙነወር፣ መጋቢት 25/2010)
በስዑዲ የሚኖር አንድ የመኒ ነው፡፡ በአንድ ወቅት ያጋጠመውን ታሪክ እንዲህ ይተርከዋል፡፡
ከፊሌ የዘካ ገንዘብ ሊያከፋፍል ፈልጎ ከሱ ጋር ወጣሁ፡፡ የድሃ መንደሮች ወዳሉባቸው ጠረፍ አካባቢ ተጓዝን፡፡ የዘካው ገንዘቦች በፖስታ የታሸጉ ነበሩ፡፡ እያንዳንዱ ፖስታ በውስጡ 5 ሺ ሪያል ይዟል፡፡ ከአንዱ መንደር ወጥተን የጂዳ-ጂዛን መስመር ስንይዝ አንድ የ70 አመት አካባቢ ሽማግሌ አገኘን፡፡ ሽማግሌው ብርቱና ጤናማ ነው፡፡ ጎዳናውን ይዞ ይጓዛል፡፡
ወዳጄ “ይሄ ደግሞ በዚህ ሰዓት በዚህ በረሃ ምን ይሰራል?” አለኝ፡፡
ሹፌሩ “ህገ ወጥ የመኒ ነው” አለ፡፡
ካጠገቡ ደርሰን ቆምንና ሰላም አልነው፡፡
“ከየት ነው ወንድም?”
“ከየመን”
“የት ነው የምትሄደው?”
“የአላህን ቤት ናፍቄያለሁ”
“ህጋዊ ነህ?”
“አይደለሁም”
“ለምን ህጋዊ አልሆንክም?”
“ለዋስትና 2 ሺ ሪያል ማስያዝ ይጠበቅብኛል፡፡ እኔ ያለኝ 200 ብቻ ነው፡፡ በመቶዋ ተሳፈርኩባት፡፡ የቀረኝ መቶ ብቻ ነው” አለ፡፡
“እሺ አጎቴ! በጉዞ ላይ ምን ያክል ሆነህ?” አለው ጓደኛየ፡፡
“ስድስት ቀን!”
“እየፆምክ አይደለም?”
“አይ ፆመኛ ነኝ፡፡”
“ጥሩ፡፡ አንተ ከ 5 በላይ የፍተሸ ኬላዎችን አልፈሃል፡፡ እንዴት ነበር የምታልፋቸው?” ሲለው
“ከሱ በስተቀር እውነተኛ አምላክ በሌለው አላህ እምላለሁ! የማልፈው በነሱው ዘንድ ነው፡፡ ግን አንድም ያናገረኝ የለም!!” አለ፡፡
“ለስራ ነው አመጣጥህ?”
“በጭራሽ ወላሂ! እኔ የአላህን ቤት ናፍቄ ነው የመጣሁት፡፡ ዑምራ ማድረግ ነው የምፈልገው፡፡ ወደ መካ ነው የምጓዘው፡፡”
“በአስፋልት ላይ ስትጓዝ ተዘዋዋሪ ዘቦች /ፓትሮል/ አልያዙህም?”
“ከግማሽ ሰዓት በፊት በ 50 ኪ. ሜ. ርቀት ላይ ይዘውኝ ነበር፡፡ እዚህ ከመድረሴ አንድ ኪ. ሜ. ቀደም ብሎ ድረስ እነሱ ናቸው ያመጡኝ፡፡ የት እንደምሄድ ሲይቁኝ በአላህ ምየ የአላህን ቤት እንደምፈልግ ስነግራቸው ለቀቁኝ” አለ፡፡
“ሱብሓነላህ! ጭራሽ እስከዚህ ቦታ በፍጥነት እንዲያደርሱህ አላህ ፓትሮሎችን አመቻቸልህ” አልኩኝ በውስጤ፡፡
ወዳጄ ሁለት ፖስታዎችን እየሰጠው “እነዚህን ያዝ፡፡ ዘካ ነው” አለው፡፡
እየተቀበለ “ጀዛኩሙላህ ኸይር” አለ፡፡
በፖስታዎቹ ያለው ገንዘብ መጠኑ ምን ያክል እንደሆነ አያውቅም፡፡
“የሰዑዲን ብር ታውቃለህ?” አልኩት፡፡
“አዎ!” አለ፡፡
“ጥሩ፡፡ ፖስታውን ክፈትና እንዳይጠፋብህ ገንዘቡን በቀበቶህ (በሒዛምህ) ውስጥ ደብቅ” አልኩት፡፡
ሲከፍተው 10 ሺህ ሪያል!!
“ይህ ሁሉ ለኔ ነው?” አለ፡፡
“አዎ ላንተ ነው” አልነው፡፡
ከመኪናው ላይ ወደቀ፡፡ እራሱን ሳተ፡፡ ከመኪናው ወርደን በላዩ ላይ ውሃ መርጨት ያዝን፡፡
“ይህ ሁሉ ገንዘብ ለኔ ነው? ይህ ሁሉ ገንዘብ ለኔ ነው?” እያለ መጮህ ያዘ፡፡ ቁጭ ብሎ ማልቀስ ቀጠለ፡፡
ወዳጄ፡ “ከኛ ጋር ትንሽ ወደ ፊት እንውሰደው” አለ፡፡
ከኛ ጋር መኪና ላይ ወጣ፡፡ ትንሽ ሲረጋጋ ጠየቅኩት፡
“ምንድን ነው ይህ ሁሉ ለቅሶ?” አልኩት፡፡
“እኔ የመን ውስጥ ከቤቴ ጎን ቦታ አለችኝ፡፡ ለአላህ ሰጥቻታለሁ፡፡ እኔና ቤተሰቦቼ በሷ ላይ በጭቃና በድንጋይ አድርገን መስጅድ ገንብተንባታል፡፡ ግንባታው ቢጠናቀቅም ምንጣፍና ጥቂት ነገሮች ቀርተውት ነበር፡፡ ለዚህ መስጂድ እንዴት ምንጣፍ እንደማገኝ ተቀምጬ አስብ ነበር” አለ፡፡
ይህን ሲል የእውነት ሁላችንም አለቀስን፡፡ “አሳቡ ኣኺራ የሆነ ሰው ዱንያ እንዳለች ትመጣለታለች” የሚለውና “አሳቡ ኣኺራ የሆነ ሰው አላህ መብቃቃቱን ከልቡ ውስጥ ያደርግለታል፡፡ ነገሩንም ይሰበስብለታል፡፡ ዱንያ በግዷ ወደሱ ትመጣለች፡፡ አሳቡ ዱንያ የሆነ ደግሞ አላህ ድህነቱን በአይኖቹ መሀል ያደርግበታል፡፡ ነገሩንም ይበትንበታል፡፡ ከዱንያም የተወሰነለት ብቻ እንጂ አይመጣለትም” የሚለው የነብዩ ﷺ ንግግር ትዝ አለኝ፡፡
በዚህን ጊዜ ወዳጄን ለሰውየው እንዲጨምረው ጠየቅኩት፡፡ ተጨማሪ 2 እሽግ ፖስታ ሰጠው፡፡ በድምሩ 20 ሺ ሪያል አገኘ ሰውየው፡፡ ሰውየው ከመኪናው ከመውረዱ በፊት እያለቀሰ ያጉተመትምና ዱዓ ያደርግ ነበር፡፡
“በአላህ ላይ እውነተኛ የሆነውን መመካት ብትመኩ ኖሮ ልክ ወፍን እንደሚረዝቀው ይረዝቃችሁ ነበር፡፡ ተርባ ወጥታ ጠግባ ትመለሳለች” የሚለው የነብዩ ﷺ ሐዲሥ መጣብኝ፡፡
የተተረጎመ
(ኢብኑ ሙነወር፣ መጋቢት 25/2010)
ለአቅመ አዳም ወይም ለአቅመ ሄዋን የሚደረሰው መቼ ነው?!
ብዙ ሰዎች ሸሪዐዊ ሃላፊነት ለመሸከም የሚደረስበትን እድሜ ሲያስቡ 15 አመት መድረስን ብቻ ነው ከግንዛቤ የሚያስገቡት፡፡ እውነታው ግን ሌሎች ተጨማሪ መለኪያዎች መኖራቸው ነው፡፡ በጥቅሉ አንድ ሰው እንደማንኛውም "አዋቂ" ሙስሊም ተቆጥሮ በሚሰራው መልካም ስራ የሚመነዳበት እና በሚሰራው ጥፋት የሚቀጣበት (ባጭሩ ስራዎቹ የሚመዘገቡበት) የእድሜ ክልል የሚደርሰው ከሚከተሉት አራት ምልክቶች ውስጥ ቀድሞ በተከሰተው ነው፡-
1. በህልምም ይሁን በውን የዘር ፈሳሽ መርጨት መጀመር
2. በብልት ዙሪያ ፀጉር መብቀል (መባለቅ)፡-
መጠኑም ፀጉሩ ለመላጨት የደረሰ ብዛት ሲኖረው ነው፡፡ እዚህ ላይ የፂም ወይም የብብት ፀጉር መለኪያ አይሆንም፡፡ የጡት መውጣት፣ የድምፅ መጎርነንና መቅጠን መለኪያ አይደሉም።
3. ለሴት የወር አበባ ማየት፡-
እነዚህ ሶስት ምልክቶች ከታዩ ልጅዎት ለሸሪዐዊ ሃላፊነት ደርሷል ወይም ደርሳለችና ያስገንዝቡ ይከታተሉ፡፡ 15 አመት መድረስን እየጠበቁ ተዘናግተው እንዳያዘናጉ፡፡ ደግሞም ከልጆችዎት ጋር ለጉዳዩ የሚያስፈልገውን ያክል ግልፅ ውይይትና መነጋገር ይኑር፡፡ ጉዳዩን ቀድሞው ካወቁ እራሳቸውን ለሃላፊነት ያዘጋጃሉና፡፡ ካላወቁ ግን እድሜያቸው ደርሶ ላይሰግዱ ላይፆሙ ይችላሉ፡፡ ልክ እንዲሁ ካላወቁ ወይም ደግሞ አጉል መተፋፈር የሚኖር ከሆነ ከነ ጀናባቸው ሊሰግዱ፣ የወር አበባ ላይ ሆነው ሊፆሙና ሊሰግዱ ይችላሉ፡፡ ይሄ ከባድ ጥፋት ነው። ስለዚህ ለልጆችዎት ወይም ደግሞ ለእህት ወንድሞችዎት በቂ ግንዛቤ ያድርሱ፡፡ መተፋፈሩ ሐቅ እንዳይሸፍንም ይጠንቀቁ፡፡
4. የመጨረሻው ምልክት 15 አመት መድረስ ነው።
ከላይ ከተራ ቁጥር አንድ እስከ ሶስት የተጠቀሱት ምልክቶች ባይታዩም 15 ከተደረሰ ቀጥታ የልጅነት የእድሜ ክልል ታልፏል ማለት ነው፡፡
ምልክቶቹ ከ 15 አመት ቀድሞ መታየት የጀመሩ ከሆነ ከዚያ ጊዜ ጀምሮ እንደማንኛውም አዋቂ ሰው ሸሪዐዊ ህግጋትን በጥብቅ መከታተል ይገባል፡፡ ምልክቶቹ ቀድመው ታይተው ሳለ ሳይፆም የታለፈ የረመዳን ፆም ካለ ቀዷ ማውጣት ግድ ይላል ይላሉ ሸይኽ ኢብኑል ዑሠይሚን ረሒመሁላህ፡፡ በማህበረሰቡ ዘንድ ስለጉዳዩ ጭራሽ ግንዛቤ ከሌለ ግን ቀዷ ማውጣቱ ግዴታ እንዳልሆነ ፍንጭ የሰጡበት ፈትዋ አለ፡፡ ወላሁ አዕለም፡፡ ዝርዝር መረጃ ወይም ግልፅ እና ቀጥተኛ ፈትዋ ያገኘ ሰው ከስር ቢያሰፍረው ሁላችንንም ይጠቅማል፡፡
በነገራችን ላይ 15 አመት መድረስ ሲባል የሚፈለገው በኢስላማዊው የሂጅራ አቆጣጠር እንጂ በፀሐይ አቆጣጠር አይደለም፡፡ (የሂጅራው አቆጣጠር የጨረቃ አቆጣጠር ሲሆን የኢትዮጵያውና የፈረንጆቹ ግን የፀሐይ አቆጣጠር እንደሚባል ያስተውሉ፡፡) በጨረቃ አቆጣጠር አንድ አመት 354 ቀን ከ 9 ሰዓት አካባቢ ሲሆን በፀሐይ አቆጣጠር ግን 365 ቀን ከ 6 አካባቢ ነው፡፡ እናም አንድ ልጅ በሂጅራው አቆጣጠር 15 አመት የሚደርሰው ከፀሐዩ አቆጣጠር ቢያንስ ከ 5 ወራት በፊት ቀድሞ ነው ማለት ነው፡፡
ስለዚህ አንድ ልጅ ከ 15 ዓመት በፊት ከላይ ከአንድ እስከ ሶስት ካሉት ምልክቶች አንዱ ከታየበት ወይም ደግሞ እነዚህ ሳይታዩ ቀርተው 15 አመት ከደረሰ ጊዜ ጀምሮ እንደማንኛውም አዋቂ ሰው ለሸሪዐዊ ህግጋት ተገዥ መሆን አለበት፡፡ ከዚህ በኋላ ሴቶችን መጨበጥ፣ መመልከት፣ ከአንዲት ሴት ጋር ለብቻ ተገልሎ መቀመጥ የለበትም፡፡ በቃ ከዚህ በኋላ በደረሱ ወንዶች ላይ የሚከለከሉ ነገሮች ሁሉ ለሱም ክልክል ናቸው፡፡ የደረሱ ወንዶችን የሚመለከቱ ግዴታዎች ሁሉ ይመለከቱታል፡፡ ሴቷንም እንዲሁ፡፡ አለባበስን ጨምሮ ነገሮችን በጥንቃቄ ልትከታተል ይገባታል፡፡
(ኢብኑ ሙነወር፣ ሚያዚያ 2/2009)
ብዙ ሰዎች ሸሪዐዊ ሃላፊነት ለመሸከም የሚደረስበትን እድሜ ሲያስቡ 15 አመት መድረስን ብቻ ነው ከግንዛቤ የሚያስገቡት፡፡ እውነታው ግን ሌሎች ተጨማሪ መለኪያዎች መኖራቸው ነው፡፡ በጥቅሉ አንድ ሰው እንደማንኛውም "አዋቂ" ሙስሊም ተቆጥሮ በሚሰራው መልካም ስራ የሚመነዳበት እና በሚሰራው ጥፋት የሚቀጣበት (ባጭሩ ስራዎቹ የሚመዘገቡበት) የእድሜ ክልል የሚደርሰው ከሚከተሉት አራት ምልክቶች ውስጥ ቀድሞ በተከሰተው ነው፡-
1. በህልምም ይሁን በውን የዘር ፈሳሽ መርጨት መጀመር
2. በብልት ዙሪያ ፀጉር መብቀል (መባለቅ)፡-
መጠኑም ፀጉሩ ለመላጨት የደረሰ ብዛት ሲኖረው ነው፡፡ እዚህ ላይ የፂም ወይም የብብት ፀጉር መለኪያ አይሆንም፡፡ የጡት መውጣት፣ የድምፅ መጎርነንና መቅጠን መለኪያ አይደሉም።
3. ለሴት የወር አበባ ማየት፡-
እነዚህ ሶስት ምልክቶች ከታዩ ልጅዎት ለሸሪዐዊ ሃላፊነት ደርሷል ወይም ደርሳለችና ያስገንዝቡ ይከታተሉ፡፡ 15 አመት መድረስን እየጠበቁ ተዘናግተው እንዳያዘናጉ፡፡ ደግሞም ከልጆችዎት ጋር ለጉዳዩ የሚያስፈልገውን ያክል ግልፅ ውይይትና መነጋገር ይኑር፡፡ ጉዳዩን ቀድሞው ካወቁ እራሳቸውን ለሃላፊነት ያዘጋጃሉና፡፡ ካላወቁ ግን እድሜያቸው ደርሶ ላይሰግዱ ላይፆሙ ይችላሉ፡፡ ልክ እንዲሁ ካላወቁ ወይም ደግሞ አጉል መተፋፈር የሚኖር ከሆነ ከነ ጀናባቸው ሊሰግዱ፣ የወር አበባ ላይ ሆነው ሊፆሙና ሊሰግዱ ይችላሉ፡፡ ይሄ ከባድ ጥፋት ነው። ስለዚህ ለልጆችዎት ወይም ደግሞ ለእህት ወንድሞችዎት በቂ ግንዛቤ ያድርሱ፡፡ መተፋፈሩ ሐቅ እንዳይሸፍንም ይጠንቀቁ፡፡
4. የመጨረሻው ምልክት 15 አመት መድረስ ነው።
ከላይ ከተራ ቁጥር አንድ እስከ ሶስት የተጠቀሱት ምልክቶች ባይታዩም 15 ከተደረሰ ቀጥታ የልጅነት የእድሜ ክልል ታልፏል ማለት ነው፡፡
ምልክቶቹ ከ 15 አመት ቀድሞ መታየት የጀመሩ ከሆነ ከዚያ ጊዜ ጀምሮ እንደማንኛውም አዋቂ ሰው ሸሪዐዊ ህግጋትን በጥብቅ መከታተል ይገባል፡፡ ምልክቶቹ ቀድመው ታይተው ሳለ ሳይፆም የታለፈ የረመዳን ፆም ካለ ቀዷ ማውጣት ግድ ይላል ይላሉ ሸይኽ ኢብኑል ዑሠይሚን ረሒመሁላህ፡፡ በማህበረሰቡ ዘንድ ስለጉዳዩ ጭራሽ ግንዛቤ ከሌለ ግን ቀዷ ማውጣቱ ግዴታ እንዳልሆነ ፍንጭ የሰጡበት ፈትዋ አለ፡፡ ወላሁ አዕለም፡፡ ዝርዝር መረጃ ወይም ግልፅ እና ቀጥተኛ ፈትዋ ያገኘ ሰው ከስር ቢያሰፍረው ሁላችንንም ይጠቅማል፡፡
በነገራችን ላይ 15 አመት መድረስ ሲባል የሚፈለገው በኢስላማዊው የሂጅራ አቆጣጠር እንጂ በፀሐይ አቆጣጠር አይደለም፡፡ (የሂጅራው አቆጣጠር የጨረቃ አቆጣጠር ሲሆን የኢትዮጵያውና የፈረንጆቹ ግን የፀሐይ አቆጣጠር እንደሚባል ያስተውሉ፡፡) በጨረቃ አቆጣጠር አንድ አመት 354 ቀን ከ 9 ሰዓት አካባቢ ሲሆን በፀሐይ አቆጣጠር ግን 365 ቀን ከ 6 አካባቢ ነው፡፡ እናም አንድ ልጅ በሂጅራው አቆጣጠር 15 አመት የሚደርሰው ከፀሐዩ አቆጣጠር ቢያንስ ከ 5 ወራት በፊት ቀድሞ ነው ማለት ነው፡፡
ስለዚህ አንድ ልጅ ከ 15 ዓመት በፊት ከላይ ከአንድ እስከ ሶስት ካሉት ምልክቶች አንዱ ከታየበት ወይም ደግሞ እነዚህ ሳይታዩ ቀርተው 15 አመት ከደረሰ ጊዜ ጀምሮ እንደማንኛውም አዋቂ ሰው ለሸሪዐዊ ህግጋት ተገዥ መሆን አለበት፡፡ ከዚህ በኋላ ሴቶችን መጨበጥ፣ መመልከት፣ ከአንዲት ሴት ጋር ለብቻ ተገልሎ መቀመጥ የለበትም፡፡ በቃ ከዚህ በኋላ በደረሱ ወንዶች ላይ የሚከለከሉ ነገሮች ሁሉ ለሱም ክልክል ናቸው፡፡ የደረሱ ወንዶችን የሚመለከቱ ግዴታዎች ሁሉ ይመለከቱታል፡፡ ሴቷንም እንዲሁ፡፡ አለባበስን ጨምሮ ነገሮችን በጥንቃቄ ልትከታተል ይገባታል፡፡
(ኢብኑ ሙነወር፣ ሚያዚያ 2/2009)
በ Ibnu Munewor
በኢኽዋን የተሸወዱ ወገኖችን ለማንቃት
በኢኽዋን ቡድን ከንቱ ማምታቻ ከተሸወዱ ወገኖች ውስጥ ከፊሎቹ የሱፍያን ብልሹ አቋም የሚያውቁና የሚፀየፉ ናቸው። እነዚህ ወገኖች ስለኢኽዋን እንዲነቁ ከፈለግን ቡድኑ ከሱፍዮች ጋር ያለው ጥብቅ ትስስር ማሳየት ይገባል። እንዲያውም ቡድኑ እራሱ ከምስረታው ጀምሮ ሱፊ እንደሆነ፣ መስራቹ ሐሰን አልበንናም የሻዚሊያ–ሐሷፊያ ጦሪቃ ተከታይ እንደነበር የራሱ ኪታብ እያጣቀሱ ማስረዳት ይገባል።
በኢኽዋን ቡድን ከንቱ ማምታቻ ከተሸወዱ ወገኖች ውስጥ ብዙዎቹ የሺዐዎችን መሰሪነት ጠማማነት ከሞላ ጎደል ያውቃል። ስለዚህ ኢኽዋን ከሺዐ ጋር ያለውን ጥብቅ ትስስር በማስረጃ በማጋለጥ ሰዎች የኢኽዋንን ትክክለኛ ማንነት እንዲያውቁ ማድረግ ይቻላል። ለዚህም የቡድኑ ቁንጮ የሆኑ ሰዎች ስራዎች ከበቂ በላይ ማስረጃ መሆን ይችላሉ።
በኢኽዋን ቡድን ከንቱ ማምታቻ ከተሸወዱ ወገኖች ውስጥ ብዙዎቹ የተክፊር አካሄድን ክፉኛ የሚፀየፉ ናቸው። ሆኖም ግን በኢኽዋን ደጋሚዎች ስለተደገመባቸው የቡድኑን ኸዋሪጃዊ አካሄድ አያውቁም። ስለዚህ ለዘመናዊ የኸዋሪጅ አስተሳሰብ የመሰረት ድንጋይ የጣለው ኢኽዋኒው ሰይድ ቁጥብ እንደሆነ በራሱ ኪታብ በማሳየት፣ የራሱን ደጋፊዎች ምስክር በማድረግ ውጤታማ ስራ መስራት ይቻላል።
በኢኽዋን የተሸወዱ ወገኖችን ለማንቃት
በኢኽዋን ቡድን ከንቱ ማምታቻ ከተሸወዱ ወገኖች ውስጥ ከፊሎቹ የሱፍያን ብልሹ አቋም የሚያውቁና የሚፀየፉ ናቸው። እነዚህ ወገኖች ስለኢኽዋን እንዲነቁ ከፈለግን ቡድኑ ከሱፍዮች ጋር ያለው ጥብቅ ትስስር ማሳየት ይገባል። እንዲያውም ቡድኑ እራሱ ከምስረታው ጀምሮ ሱፊ እንደሆነ፣ መስራቹ ሐሰን አልበንናም የሻዚሊያ–ሐሷፊያ ጦሪቃ ተከታይ እንደነበር የራሱ ኪታብ እያጣቀሱ ማስረዳት ይገባል።
በኢኽዋን ቡድን ከንቱ ማምታቻ ከተሸወዱ ወገኖች ውስጥ ብዙዎቹ የሺዐዎችን መሰሪነት ጠማማነት ከሞላ ጎደል ያውቃል። ስለዚህ ኢኽዋን ከሺዐ ጋር ያለውን ጥብቅ ትስስር በማስረጃ በማጋለጥ ሰዎች የኢኽዋንን ትክክለኛ ማንነት እንዲያውቁ ማድረግ ይቻላል። ለዚህም የቡድኑ ቁንጮ የሆኑ ሰዎች ስራዎች ከበቂ በላይ ማስረጃ መሆን ይችላሉ።
በኢኽዋን ቡድን ከንቱ ማምታቻ ከተሸወዱ ወገኖች ውስጥ ብዙዎቹ የተክፊር አካሄድን ክፉኛ የሚፀየፉ ናቸው። ሆኖም ግን በኢኽዋን ደጋሚዎች ስለተደገመባቸው የቡድኑን ኸዋሪጃዊ አካሄድ አያውቁም። ስለዚህ ለዘመናዊ የኸዋሪጅ አስተሳሰብ የመሰረት ድንጋይ የጣለው ኢኽዋኒው ሰይድ ቁጥብ እንደሆነ በራሱ ኪታብ በማሳየት፣ የራሱን ደጋፊዎች ምስክር በማድረግ ውጤታማ ስራ መስራት ይቻላል።
ሆኖም ግን ጉድንም ጉድ ይበልጠዋልና አንዱ ካንዱ ይበላለጣሉ፡፡
በ Ibnu Munewor
አሳዛኝ እውነታ!
በአሁኑ ሰዓት ህዝባችንን ይበልጥ የሚያስደነግጠው ወንጀል የቱ ነው? ለምሳሌ አንድ የመስጂድ ኢማም
ሀ/ ሺርክ ሲሰራ ቢታይ፣
ለ/ ሰው ሲገድል ቢታይ፣
ሐ/ የጎረቤቱን ሚስት ሲያባልግ ቢታይ
የትኛው ነው ይበልጥ የሚያሸማቅቀው? እነዚህ ጥፋቶች ሁሉም ከከባባድ ወንጀሎች ናቸው፡፡ ሆኖም ግን ጉድንም ጉድ ይበልጠዋልና አንዱ ካንዱ ይበላለጣሉ፡፡ የተጠቀሱት ሁለቱ ጥፋቶች ከሺርክ ጋር የሚስተካከሉ አይደሉም፡፡ ሶሐባው ኢብኑ መስዑድ ረዲየላሁ ዐንሁ እንዲህ ይላሉ፡-
سَأَلْتُ النَّبِيَّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ : أَيُّ الذَّنْبِ أَعْظَمُ عِنْدَ اللَّهِ ؟ قَالَ : أَنْ تَجْعَلَ لِلَّهِ نِدًّا وَهُوَ خَلَقَكَ ". قُلْتُ : إِنَّ ذَلِكَ لَعَظِيمٌ، قُلْتُ : ثُمَّ أَيُّ ؟ قَالَ : " وَأَنْ تَقْتُلَ وَلَدَكَ ؛ تَخَافُ أَنْ يَطْعَمَ مَعَكَ ". قُلْتُ : ثُمَّ أَيُّ ؟ قَالَ : " أَنْ تُزَانِيَ حَلِيلَةَ جَارِكَ ".
“ነብዩን ﷺ ‘ከወንጀል ሁሉ አላህ ዘንድ ከባዱ የትኛው ነው?’ ስል ጠየቅኳቸው። እሳቸውም {የፈጠረህ እሱ ሆኖ ሳለ ለአላህ ብጤን ማድረግህ ነው} አሉኝ። ‘ይሄ በርግጥም ከባድ ነው!’ አልኩኝ። ‘ከዚያ ቀጥሎስ የትኛው ነው?’ ስላቸው፡ {ካንተ ጋር መብላቱን ሰግተህ ልጅህን መግደልህ ነው} አሉኝ። ‘ከዚያ ቀጥሎስ የትኛው ነው?’ አልኩኝ። {ከጎረቤትህ ሚስት ጋር ዝሙት መፈፀምህ ነው} አሉኝ።” [ቡኻሪ፡ 4477፣ ሙስሊም፡ 267]
ይህንን እንያዝና የህዝባችንን ግንዛቤ እንታዘብ፡፡ ከሚከፋው ወንጀል ይልቅ የሚያስደነግጠው በንፅፅር ቀላሉ ነው፡፡ ለተውሒድ ከተገነባው የአላህ ቤት ከሚፈፀመው ሺርክ ይልቅ የሚሰቀጥጠን በስውር የሚፈፀሙት ብልግናዎች ናቸው፡፡ በርግጥ ሁሉም ያስደነግጣሉ፡፡ ግን ለከፋው ያለን እይታ ለምን ያነሰ ሆነ? ይበልጥ የሚያስደነግጠው ደግሞ ይሄ የተንሻፈፈ እይታ የተራው ህዝብ ችግር ብቻ አለመሆኑ ነው፡፡ ዱዓቶች፣ አስተማሪዎች ሳይቀሩ ይበልጥ የሚወተውቱት ስለየቱ እንደሆነ ተመልከቱ፡፡ ይበልጥ የሚያሳፍረው ደግሞ ከነ ጭራሹ የችግሩንም መኖር የሚክዱ አታላይ ሰባኪዎች መኖራቸው ነው፡፡
وإن كنت لا تدري فتلك مصيبة وإن كنت تدري فالمصيبة أعظم
በ Ibnu Munewor
አሳዛኝ እውነታ!
በአሁኑ ሰዓት ህዝባችንን ይበልጥ የሚያስደነግጠው ወንጀል የቱ ነው? ለምሳሌ አንድ የመስጂድ ኢማም
ሀ/ ሺርክ ሲሰራ ቢታይ፣
ለ/ ሰው ሲገድል ቢታይ፣
ሐ/ የጎረቤቱን ሚስት ሲያባልግ ቢታይ
የትኛው ነው ይበልጥ የሚያሸማቅቀው? እነዚህ ጥፋቶች ሁሉም ከከባባድ ወንጀሎች ናቸው፡፡ ሆኖም ግን ጉድንም ጉድ ይበልጠዋልና አንዱ ካንዱ ይበላለጣሉ፡፡ የተጠቀሱት ሁለቱ ጥፋቶች ከሺርክ ጋር የሚስተካከሉ አይደሉም፡፡ ሶሐባው ኢብኑ መስዑድ ረዲየላሁ ዐንሁ እንዲህ ይላሉ፡-
سَأَلْتُ النَّبِيَّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ : أَيُّ الذَّنْبِ أَعْظَمُ عِنْدَ اللَّهِ ؟ قَالَ : أَنْ تَجْعَلَ لِلَّهِ نِدًّا وَهُوَ خَلَقَكَ ". قُلْتُ : إِنَّ ذَلِكَ لَعَظِيمٌ، قُلْتُ : ثُمَّ أَيُّ ؟ قَالَ : " وَأَنْ تَقْتُلَ وَلَدَكَ ؛ تَخَافُ أَنْ يَطْعَمَ مَعَكَ ". قُلْتُ : ثُمَّ أَيُّ ؟ قَالَ : " أَنْ تُزَانِيَ حَلِيلَةَ جَارِكَ ".
“ነብዩን ﷺ ‘ከወንጀል ሁሉ አላህ ዘንድ ከባዱ የትኛው ነው?’ ስል ጠየቅኳቸው። እሳቸውም {የፈጠረህ እሱ ሆኖ ሳለ ለአላህ ብጤን ማድረግህ ነው} አሉኝ። ‘ይሄ በርግጥም ከባድ ነው!’ አልኩኝ። ‘ከዚያ ቀጥሎስ የትኛው ነው?’ ስላቸው፡ {ካንተ ጋር መብላቱን ሰግተህ ልጅህን መግደልህ ነው} አሉኝ። ‘ከዚያ ቀጥሎስ የትኛው ነው?’ አልኩኝ። {ከጎረቤትህ ሚስት ጋር ዝሙት መፈፀምህ ነው} አሉኝ።” [ቡኻሪ፡ 4477፣ ሙስሊም፡ 267]
ይህንን እንያዝና የህዝባችንን ግንዛቤ እንታዘብ፡፡ ከሚከፋው ወንጀል ይልቅ የሚያስደነግጠው በንፅፅር ቀላሉ ነው፡፡ ለተውሒድ ከተገነባው የአላህ ቤት ከሚፈፀመው ሺርክ ይልቅ የሚሰቀጥጠን በስውር የሚፈፀሙት ብልግናዎች ናቸው፡፡ በርግጥ ሁሉም ያስደነግጣሉ፡፡ ግን ለከፋው ያለን እይታ ለምን ያነሰ ሆነ? ይበልጥ የሚያስደነግጠው ደግሞ ይሄ የተንሻፈፈ እይታ የተራው ህዝብ ችግር ብቻ አለመሆኑ ነው፡፡ ዱዓቶች፣ አስተማሪዎች ሳይቀሩ ይበልጥ የሚወተውቱት ስለየቱ እንደሆነ ተመልከቱ፡፡ ይበልጥ የሚያሳፍረው ደግሞ ከነ ጭራሹ የችግሩንም መኖር የሚክዱ አታላይ ሰባኪዎች መኖራቸው ነው፡፡
وإن كنت لا تدري فتلك مصيبة وإن كنت تدري فالمصيبة أعظم
በ Ibnu Munewor
"አልጠጣም" በቂ መልስ አይደለም
ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል:–
"በአላህና በመጨረሻው የሚያምን የሆነ ሰው አስካሪ መጠጥ ከሚጠጣበት ማእድ ላይ እንዳይቀመጥ።"
አልባኒ ሶሒሕ ብለውታል።
"አልጠጣም" በቂ መልስ አይደለም
ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል:–
"በአላህና በመጨረሻው የሚያምን የሆነ ሰው አስካሪ መጠጥ ከሚጠጣበት ማእድ ላይ እንዳይቀመጥ።"
አልባኒ ሶሒሕ ብለውታል።
ማን ነው ‹‹ሸሂድ (ሰመዓት)፣RIP (Rest in Peace)›› የሚባለው?
አንዳንድ ወንድምና እህቶች በአላህና በመልክተኛው መታመን ባለበት ሁሉ የማያምኑ ካፊሮችን ‹‹ሸሂድ (ሰመዓት)፣ RIP (Rest in Peace)›› ብለው ሲፅፉና ሲናገሩ ይሰማል፡፡ ይሄ ከባድ ስህተት ነው፣ እርምት ይሻል፡፡
አደለም በአላህ፣ በመልክተኛው መታመን ባለበት ሁሉ ያላመነን ካፊር፣ ሙስሊም የሆነን ሰው እንኳን አላህና መልክተኛው (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ከመሰከሩለት ሰው ውጭ እኛ ከመሬት ተነስተን ‹‹ሸሂድ (ሰመዓት)›› አንለውም፡፡
ኢማም አል-ቡኻሪ በሰሂሀል-ቡኻሪ ‹‹እገሌ (እንትና) ሸሂድ (ሰመዓት) አይባልም›› ብለው አርስት አዘጋጅተው የሚከተለውን ሀዲስ ዘግበውልናል
ሰህል ኢብን ሰዓድ አሳኢድይ (ረድየላሁ አንህ) ‹‹የአላህ መልክተኛ (ﷺ) እና ሙሽሪኮች ፊት ለፊት ጦር ተጋጥመው ነበር፡፡ የአላህ መልክተኛም (ﷺ) ሙሽሪኮችም ወደ ካምፓቸው ሲመለሱ፣ ስለ አንድ ብቻውን ያገኘውን ሙሽሪክ ሁሉ በሰይፉ ስለሚገድል ባልደረባቸው አንድ ሰው አወራ፡፡ እንዲህም አለ ‹‹ዛሬ እንደዛ ሰው በትክክል ስራውን (ውጊያውን) የሰራ የለም››
የአላህ መልክተኛ (ﷺ) ግን ‹‹ይህ ሰው ከእሳት ሰዎች ነው፡፡›› አሉ፡፡
ከሰዎች አንዱ ይህን ሰው መከታተል አለብኝ አለ (የአላህ መልክተኛ (ﷺ) የእሳት ነው ያሉትን ሰው ማለት ነው)
አብሮትም ሆነ ሲቆም ይቆማል፣ ሲሮጥ ይሮጣል፡፡ (ጀግና) የተባለው ሰውየም ቆሰለ ሞቱንም ማፍጠን ፈለገ፡፡ የሰይፉን መያዣ መሬት ላይ ቀበረውና ሁሉቱ ደረቶቹ መሃል ላይ አድርጎ ሰይፉ ላይ ተኛበት በዛውም ሞተ፡፡
ሌላኛው ሰውዬ የአላህ መልክተኛ (ﷺ) ዘንድ መጥቶ ‹‹የአላህ መልክተኛ መሆኖትን እመሰክራለሁ›› አላቸው፡፡ አል-ቡኻሪ 2898 ……………….
ከዚህ የምንረዳው የአላህ መልክተኛ (ﷺ) ከመሰከሩለት ሰው ውጭ እኛ አንድን ሰው ሸሂድ ነው፣ ለዲን ሲል ነው የሚታገለው ማለት አንችልም፡፡ ምክንያቱም ለአላህ ብሎ የሚታገለውን አላህ ብቻ እንደሚያውቀው አቡሁረይራ ባስተላለፉት
وَاللَّهُ أَعْلَمُ بِمَنْ يُجَاهِدُ فِي سَبِيلِهِ
‹‹አላህ የበለጠ ያውቃል ማን በእሱ መንገድ ላይ እንደሚታገል›› ሀዲስ የአላህ መልክተኛ (ﷺ) ነግረውናል ሰሂሀል አል-ቡኻሪ 2787፡፡
RIP (Rest in Peace) በሰላም እረፍ እንደማለት ነው፡፡ ይህን አባባል ከሙስሊም ውጭ ለሆነ ሰው መጠቀም በፍፁም አይገባም፡፡ ምክንያቱም የሚቀጥለው አለም ጌታ አላሁ ሱብሃነሁ ወተዓላን በትክክለኛ እምነት፣ በንፁህ ልብ፣ በነብዩ (ﷺ) ሱና፣ መታመን ባለበት ሁሉ አምኖ ለሄደ ብቻ ነው ሰላም ያለው፡፡ ከዛ ውጭ ግን ከባድ አደጋ ነው፡፡ አላህ የሚቀጥለው አለም ለነማን እንደሆነ ሰላም ያለው እንዲህ ሲል ይናገራል
ውዱ የአላህ ባርያ ነብየላህ ኢብራሂም (አለይሂ ሰላም) እንዲህ አለ
وَلَا تُخْزِنِى يَوْمَ يُبْعَثُونَ
በሚቀሰቀሱበት ቀንም አታዋርደኝ፡፡
يَوْمَ لَا يَنفَعُ مَالٌ وَلَا بَنُونَ
ገንዘብም ልጆችም በማይጠቅሙበት ቀን፡፡
إِلَّا مَنْ أَتَى ٱللَّهَ بِقَلْبٍ سَلِيمٍ
ወደ አላህ በንጹህ ልብ የመጣ ሰው ቢኾን እንጅ፡፡»
ይህ ነው እንግዲህ ተጨባጩ ሁኔታና እውነታ፡፡ ዛሬ ሙስሊም ያልሆነ ዘፋኝ፣ አርቲስትና የመሳሰለው ሲሞት RIP (Rest in Peace) እያሉ የሚፅፉ ስንቶች ናቸው፡፡ አላህ እውቀትን ይስጠንና፡፡
ማጠቃለያ፡-
1) ለካፊር ሰመዓት (ሸሂድ) አይባልም፣
2) ለሙስሊምም በጥቅሉ በአላህ መንገድ ላይ የሞተ ሸሂድ ነው እንላለን እንጂ እከሌ ብለን አንድን ሰው ነጥለን ሸሂድ ነው አንልም፡፡ ምክንያቱም መለኮታዊ ራእይ የማይለያቸው ነብዩ (ﷺ) ብቻ ናቸው እንዲህ ብለው ሊናገሩ የሚችሉት፡፡ እሳቸው ደግሞ ሞተዋል፡፡ በሳቸው ሞት ደግሞ መለኮታዊ ራእይ ተቋርጧል፡፡ ከሳቸው ባኋላ ማንም ይህን መናገር አይችልም፡፡ ኢንሻ አላህ ሸሂድ ይሆናል ብለን ግን መመኘትና ዱዐ ማድረግ ችግር የለውም፣
3) ለካፊር RIP (Rest in Peace) አይባልም፣
4) ሙስሊም የሆነ ሰው ሲሞት እንዲያውም ዱዓ እናደርግለታለን፡፡ አላህ ይዘንልህ/ሽ፣ ይማርህ/ሽ፣ ቀብርህን/ሽን ያስፋልህ/ልሽ እያልን፡፡
አላህ ሸሪዐችንን ጠንቅቀን የምናውቅ፣ የምንሰራበትም፣ የምንፀናበትም ያድርገን፡፡ ከአላህ ውጭ ሃይልም ጥበብም ብልሃትም የለም፡፡
የአላህ ሰላትና ሰላም በነብያት ሁሉ መደምደሚያ፣ በቤተሰቦቻቸው፣ በባልደረባዎቻቸው፣ ሃቅን በተከተለ ላይ ሁሉ ይሁን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
አንዳንድ ወንድምና እህቶች በአላህና በመልክተኛው መታመን ባለበት ሁሉ የማያምኑ ካፊሮችን ‹‹ሸሂድ (ሰመዓት)፣ RIP (Rest in Peace)›› ብለው ሲፅፉና ሲናገሩ ይሰማል፡፡ ይሄ ከባድ ስህተት ነው፣ እርምት ይሻል፡፡
አደለም በአላህ፣ በመልክተኛው መታመን ባለበት ሁሉ ያላመነን ካፊር፣ ሙስሊም የሆነን ሰው እንኳን አላህና መልክተኛው (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ከመሰከሩለት ሰው ውጭ እኛ ከመሬት ተነስተን ‹‹ሸሂድ (ሰመዓት)›› አንለውም፡፡
ኢማም አል-ቡኻሪ በሰሂሀል-ቡኻሪ ‹‹እገሌ (እንትና) ሸሂድ (ሰመዓት) አይባልም›› ብለው አርስት አዘጋጅተው የሚከተለውን ሀዲስ ዘግበውልናል
ሰህል ኢብን ሰዓድ አሳኢድይ (ረድየላሁ አንህ) ‹‹የአላህ መልክተኛ (ﷺ) እና ሙሽሪኮች ፊት ለፊት ጦር ተጋጥመው ነበር፡፡ የአላህ መልክተኛም (ﷺ) ሙሽሪኮችም ወደ ካምፓቸው ሲመለሱ፣ ስለ አንድ ብቻውን ያገኘውን ሙሽሪክ ሁሉ በሰይፉ ስለሚገድል ባልደረባቸው አንድ ሰው አወራ፡፡ እንዲህም አለ ‹‹ዛሬ እንደዛ ሰው በትክክል ስራውን (ውጊያውን) የሰራ የለም››
የአላህ መልክተኛ (ﷺ) ግን ‹‹ይህ ሰው ከእሳት ሰዎች ነው፡፡›› አሉ፡፡
ከሰዎች አንዱ ይህን ሰው መከታተል አለብኝ አለ (የአላህ መልክተኛ (ﷺ) የእሳት ነው ያሉትን ሰው ማለት ነው)
አብሮትም ሆነ ሲቆም ይቆማል፣ ሲሮጥ ይሮጣል፡፡ (ጀግና) የተባለው ሰውየም ቆሰለ ሞቱንም ማፍጠን ፈለገ፡፡ የሰይፉን መያዣ መሬት ላይ ቀበረውና ሁሉቱ ደረቶቹ መሃል ላይ አድርጎ ሰይፉ ላይ ተኛበት በዛውም ሞተ፡፡
ሌላኛው ሰውዬ የአላህ መልክተኛ (ﷺ) ዘንድ መጥቶ ‹‹የአላህ መልክተኛ መሆኖትን እመሰክራለሁ›› አላቸው፡፡ አል-ቡኻሪ 2898 ……………….
ከዚህ የምንረዳው የአላህ መልክተኛ (ﷺ) ከመሰከሩለት ሰው ውጭ እኛ አንድን ሰው ሸሂድ ነው፣ ለዲን ሲል ነው የሚታገለው ማለት አንችልም፡፡ ምክንያቱም ለአላህ ብሎ የሚታገለውን አላህ ብቻ እንደሚያውቀው አቡሁረይራ ባስተላለፉት
وَاللَّهُ أَعْلَمُ بِمَنْ يُجَاهِدُ فِي سَبِيلِهِ
‹‹አላህ የበለጠ ያውቃል ማን በእሱ መንገድ ላይ እንደሚታገል›› ሀዲስ የአላህ መልክተኛ (ﷺ) ነግረውናል ሰሂሀል አል-ቡኻሪ 2787፡፡
RIP (Rest in Peace) በሰላም እረፍ እንደማለት ነው፡፡ ይህን አባባል ከሙስሊም ውጭ ለሆነ ሰው መጠቀም በፍፁም አይገባም፡፡ ምክንያቱም የሚቀጥለው አለም ጌታ አላሁ ሱብሃነሁ ወተዓላን በትክክለኛ እምነት፣ በንፁህ ልብ፣ በነብዩ (ﷺ) ሱና፣ መታመን ባለበት ሁሉ አምኖ ለሄደ ብቻ ነው ሰላም ያለው፡፡ ከዛ ውጭ ግን ከባድ አደጋ ነው፡፡ አላህ የሚቀጥለው አለም ለነማን እንደሆነ ሰላም ያለው እንዲህ ሲል ይናገራል
ውዱ የአላህ ባርያ ነብየላህ ኢብራሂም (አለይሂ ሰላም) እንዲህ አለ
وَلَا تُخْزِنِى يَوْمَ يُبْعَثُونَ
በሚቀሰቀሱበት ቀንም አታዋርደኝ፡፡
يَوْمَ لَا يَنفَعُ مَالٌ وَلَا بَنُونَ
ገንዘብም ልጆችም በማይጠቅሙበት ቀን፡፡
إِلَّا مَنْ أَتَى ٱللَّهَ بِقَلْبٍ سَلِيمٍ
ወደ አላህ በንጹህ ልብ የመጣ ሰው ቢኾን እንጅ፡፡»
ይህ ነው እንግዲህ ተጨባጩ ሁኔታና እውነታ፡፡ ዛሬ ሙስሊም ያልሆነ ዘፋኝ፣ አርቲስትና የመሳሰለው ሲሞት RIP (Rest in Peace) እያሉ የሚፅፉ ስንቶች ናቸው፡፡ አላህ እውቀትን ይስጠንና፡፡
ማጠቃለያ፡-
1) ለካፊር ሰመዓት (ሸሂድ) አይባልም፣
2) ለሙስሊምም በጥቅሉ በአላህ መንገድ ላይ የሞተ ሸሂድ ነው እንላለን እንጂ እከሌ ብለን አንድን ሰው ነጥለን ሸሂድ ነው አንልም፡፡ ምክንያቱም መለኮታዊ ራእይ የማይለያቸው ነብዩ (ﷺ) ብቻ ናቸው እንዲህ ብለው ሊናገሩ የሚችሉት፡፡ እሳቸው ደግሞ ሞተዋል፡፡ በሳቸው ሞት ደግሞ መለኮታዊ ራእይ ተቋርጧል፡፡ ከሳቸው ባኋላ ማንም ይህን መናገር አይችልም፡፡ ኢንሻ አላህ ሸሂድ ይሆናል ብለን ግን መመኘትና ዱዐ ማድረግ ችግር የለውም፣
3) ለካፊር RIP (Rest in Peace) አይባልም፣
4) ሙስሊም የሆነ ሰው ሲሞት እንዲያውም ዱዓ እናደርግለታለን፡፡ አላህ ይዘንልህ/ሽ፣ ይማርህ/ሽ፣ ቀብርህን/ሽን ያስፋልህ/ልሽ እያልን፡፡
አላህ ሸሪዐችንን ጠንቅቀን የምናውቅ፣ የምንሰራበትም፣ የምንፀናበትም ያድርገን፡፡ ከአላህ ውጭ ሃይልም ጥበብም ብልሃትም የለም፡፡
የአላህ ሰላትና ሰላም በነብያት ሁሉ መደምደሚያ፣ በቤተሰቦቻቸው፣ በባልደረባዎቻቸው፣ ሃቅን በተከተለ ላይ ሁሉ ይሁን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
እስኪ እንነጋገር!
በሙስሊም መሪ ላይ አምፆ ስለመውጣት ያሉ ብዥታዎችና መልሶቻቸው
▶️ካሉህ: በዳይ መሪ ላይ አምፆ መውጣት የአህሉ ሱንናን መርህ መቃረን ነው?
⏩በላቸው: አዎን!
▶️ካሉህ: የታለ መረጃችሁ?
⏩በላቸው:
"...إلا أن تروا كفرا بواحا"
"...ግልፅ የሆነ ክህደት (ኩፍር) እስክታዩ ድረስ (ከትዕዛዝ አትውጡ)" የሚለው የዑባዳህ ሐዲስ ነው።
▶️ካሉህ: ክህደት (ኩፍር) ማለት ወንጀል ማለት ነው።
⏩በላቸው: ተሳስታችኋል፣ ምክንያቱም በዓውፍ ኢብን ማሊክ ሐዲስ፣
"مَنْ وَلِيَ عَلَيْهِ وَالٍ فَرَآهُ يَأْتِي شَيْئًا مِنْ مَعْصِيَةِ اللَّهِ فَلْيَكْرَهْ مَا يَأْتِي مِنْ مَعْصِيَةِ اللَّهِ ، وَلا يَنْزِعَنَّ يَدًا مِنْ طَاعَةِ اللَّهِ."
"አንድ መሪ የተሾመበት ሰው አላህ የሚታመፅበትን ወንጀል (መሪው) ሲሰራ ካየ ወንጀሉን ይጥላ፣ (መሪውን በማመፅ) አላህን ከመታዘዝ ግን እጁን እንዳያነሳ" ተብሏልና።
"يا أيها الذين آمنوا أطيعوا الله وأطيعوا الرسول وأولوا الأمر منكم" (القرآن)
"እናንተ ያመናችሁ ሆይ፣ አላህን ታዘዙ፣ መልዕክተኛውንም ታዘዙ፣ ከናንተ የጉዳዩ ባለቤት የሆኑትንም (መሪዎች ታዘዙ)" (ቁርአን)
▶️ካሉህ: ነገር ግን እኮ ዑመር ረዲየሏሁ ዓንሁ " (ቀዊሙኒይ)(ካጠፋሁ) አቃኑኝ" ብሏል።
⏩በላቸው: ሲጀምር ይህ ዘገባ ሙስነድ ኪታብ ውስጥ ፈፅሞ አልሰፈረም። ሰሒሕ ነው እንኳን ብንል ማቃናት (ተቅዊም) ማለት ማስተካከል (ኢስላሕ) ማለት እንጂ መቀየር አይደለም።
▶️ካሉህ: እና እስከመቼ እንታገስ?
⏩በላቸው: በኡሰይድ ሐዲስ ነቢዩ ሶለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም
"...فاصبروا حتى تلقوني على الحوض"
"(ከመሪዎች አድሎና ግፍ ቢደርስባችሁ) ሐውድ ላይ እስክታገኙኝ ድረስ #ታገሱ" ብለዋል።
▶️ካሉህ: ሐቃችንን (መብታችንን) እንዴት እንወስዳለን?
⏩በላቸው: አሁንም መረጃችን ሐዲስ ነው። በኢብኑ መስዑድ ሐዲስ፣
"...أدوا الذي عليكم، وتسألون الله الذي لكم"
"እናንተ ላይ ያለባችሁን ሐቅ ተወጡ፣ የናንተን ደግሞ አሏህን ጠይቁ"
▶️ካሉህ: መታዘዝ የሚገባን መርጠን ለወደድነው መሪ እንጂ ስልጣን ላይ ላለ ወይም በሀይል ለያዘው አይደለም!
⏩በላቸው:
"... اسمعوا وأطيعوا وان تآمر عليكم عبد حبشي"
በዒርባድ ረዲየሏሁ ዓንሁ ሐዲስ፣
"(እናንተ ባትወዱትም) የሐበሻ ባሪያ መሪ ከሆነባችሁ ስሙት ታዘዙትም"
▶️ካሉህ: የምንታገሰው በሸሪዓው መሰረት ለሚመራ መሪ ነው። በስሜቱ እንጂ በሸሪዓው ለማይመራ መሪ ይህ ሐዲስ መረጃ አይሆንም።
⏩በላቸው: ዋሻችሁ! ምክንያቱም በሑዘይፋ ረዲየሏሁ ዓንሁ ሐዲስ፣
"يكون بعدي أئمة لا يهتدون بهداي ولا يستنون بسنتي فاسمع وأطع"
"ከእኔ በኋላ በኔ መንገድ የማይጓዙ፣ በሱንናዬም የማይመሩ መሪዎች ይመጣሉ። (እነኝህን መሪዎች) ስማ ታዘዝም"
(አቡ የሕያ ያሲን፣ ሚያዝያ 11,2010)
በሙስሊም መሪ ላይ አምፆ ስለመውጣት ያሉ ብዥታዎችና መልሶቻቸው
▶️ካሉህ: በዳይ መሪ ላይ አምፆ መውጣት የአህሉ ሱንናን መርህ መቃረን ነው?
⏩በላቸው: አዎን!
▶️ካሉህ: የታለ መረጃችሁ?
⏩በላቸው:
"...إلا أن تروا كفرا بواحا"
"...ግልፅ የሆነ ክህደት (ኩፍር) እስክታዩ ድረስ (ከትዕዛዝ አትውጡ)" የሚለው የዑባዳህ ሐዲስ ነው።
▶️ካሉህ: ክህደት (ኩፍር) ማለት ወንጀል ማለት ነው።
⏩በላቸው: ተሳስታችኋል፣ ምክንያቱም በዓውፍ ኢብን ማሊክ ሐዲስ፣
"مَنْ وَلِيَ عَلَيْهِ وَالٍ فَرَآهُ يَأْتِي شَيْئًا مِنْ مَعْصِيَةِ اللَّهِ فَلْيَكْرَهْ مَا يَأْتِي مِنْ مَعْصِيَةِ اللَّهِ ، وَلا يَنْزِعَنَّ يَدًا مِنْ طَاعَةِ اللَّهِ."
"አንድ መሪ የተሾመበት ሰው አላህ የሚታመፅበትን ወንጀል (መሪው) ሲሰራ ካየ ወንጀሉን ይጥላ፣ (መሪውን በማመፅ) አላህን ከመታዘዝ ግን እጁን እንዳያነሳ" ተብሏልና።
"يا أيها الذين آمنوا أطيعوا الله وأطيعوا الرسول وأولوا الأمر منكم" (القرآن)
"እናንተ ያመናችሁ ሆይ፣ አላህን ታዘዙ፣ መልዕክተኛውንም ታዘዙ፣ ከናንተ የጉዳዩ ባለቤት የሆኑትንም (መሪዎች ታዘዙ)" (ቁርአን)
▶️ካሉህ: ነገር ግን እኮ ዑመር ረዲየሏሁ ዓንሁ " (ቀዊሙኒይ)(ካጠፋሁ) አቃኑኝ" ብሏል።
⏩በላቸው: ሲጀምር ይህ ዘገባ ሙስነድ ኪታብ ውስጥ ፈፅሞ አልሰፈረም። ሰሒሕ ነው እንኳን ብንል ማቃናት (ተቅዊም) ማለት ማስተካከል (ኢስላሕ) ማለት እንጂ መቀየር አይደለም።
▶️ካሉህ: እና እስከመቼ እንታገስ?
⏩በላቸው: በኡሰይድ ሐዲስ ነቢዩ ሶለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም
"...فاصبروا حتى تلقوني على الحوض"
"(ከመሪዎች አድሎና ግፍ ቢደርስባችሁ) ሐውድ ላይ እስክታገኙኝ ድረስ #ታገሱ" ብለዋል።
▶️ካሉህ: ሐቃችንን (መብታችንን) እንዴት እንወስዳለን?
⏩በላቸው: አሁንም መረጃችን ሐዲስ ነው። በኢብኑ መስዑድ ሐዲስ፣
"...أدوا الذي عليكم، وتسألون الله الذي لكم"
"እናንተ ላይ ያለባችሁን ሐቅ ተወጡ፣ የናንተን ደግሞ አሏህን ጠይቁ"
▶️ካሉህ: መታዘዝ የሚገባን መርጠን ለወደድነው መሪ እንጂ ስልጣን ላይ ላለ ወይም በሀይል ለያዘው አይደለም!
⏩በላቸው:
"... اسمعوا وأطيعوا وان تآمر عليكم عبد حبشي"
በዒርባድ ረዲየሏሁ ዓንሁ ሐዲስ፣
"(እናንተ ባትወዱትም) የሐበሻ ባሪያ መሪ ከሆነባችሁ ስሙት ታዘዙትም"
▶️ካሉህ: የምንታገሰው በሸሪዓው መሰረት ለሚመራ መሪ ነው። በስሜቱ እንጂ በሸሪዓው ለማይመራ መሪ ይህ ሐዲስ መረጃ አይሆንም።
⏩በላቸው: ዋሻችሁ! ምክንያቱም በሑዘይፋ ረዲየሏሁ ዓንሁ ሐዲስ፣
"يكون بعدي أئمة لا يهتدون بهداي ولا يستنون بسنتي فاسمع وأطع"
"ከእኔ በኋላ በኔ መንገድ የማይጓዙ፣ በሱንናዬም የማይመሩ መሪዎች ይመጣሉ። (እነኝህን መሪዎች) ስማ ታዘዝም"
(አቡ የሕያ ያሲን፣ ሚያዝያ 11,2010)
በአላህ እና በመልክተኛው (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ሳያምን የሞተ ሰው “አላህ ይማርህ፣ አላህ ይዘንልህ አይባልም”፡፡ አላህን እንፍራ፡፡
ሙስሊም ወንድም እና እህቶቼ ሆይ! ኢስላም ማለት ሁሉን ነገር አቅፎ የያዘ የተሟላ ውብ ሃይማኖት ነው፡፡ ዛሬ ሃይማኖታዊ እውቀት ከመማር ተዘናግተን ይሀው አላህ የከለከለውን ሁሉ ስንጥስ ይታያል፡፡
አላህ እንዲህ ይላል
مَا كَانَ لِلنَّبِىِّ وَٱلَّذِينَ ءَامَنُوٓا۟ أَن يَسْتَغْفِرُوا۟ لِلْمُشْرِكِينَ وَلَوْ كَانُوٓا۟ أُو۟لِى قُرْبَىٰ مِنۢ بَعْدِ مَا تَبَيَّنَ لَهُمْ أَنَّهُمْ أَصْحَٰبُ ٱلْجَحِيمِ
ለነቢዩና ለነዚያ ላመኑት ለአጋሪዎቹ የዝምድና ባለቤቶች ቢኾኑም እንኳ እነሱ (ከሓዲዎቹ) የእሳት ጓዶች መኾናቸው ከተገለጸላቸው በኋላ ምሕረትን ሊለምኑ የሚገባ አልነበረም፡፡
ተመልከቱ የሞቱት ዘመዶቻችን ቢሆኑም እንኳን በአላህ ላይ እስካጋሩ ድረስ ምህረትን እንዳንጠይቅ ታዘናል፡፡ አይደለም የማናውቃቸው ግለሰቦች፡፡
ክርስትያኖችን ብትጠይቋቸው “ዘፋኝ የገሃነም ነው” ይሉሃል፡፡ ታድያ እኛ ምን ቤት ሆነን ነው በአላህ እና በመጨረሻው ቀን ሳያምን የሞተን ሰው “አላህ ይማርህ” የምንለው?
ነብዩ ሙሐመድ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “በአላህ ላይ እያጋራ የሞተ ሰው እሳት ገባ ብለዋል፡፡”
ከእስልምና ውጭ ያለ ሃይማኖት ተከታይ አንድ ሰው እስላም ሆኖ ቢሞት በተሳሳተ መንገድ ላይ እንደሞተ ነው የሚያምኑት፡፡ ፈጣሪ ብለው የሚያስቡትም ያንን ግለሰብ እነሱ የሚጓዙበትን መንገድ ስላልተከተለ እንደማይምረው ነው የሚያምኑት፡፡ እኛም ደግሞ የነብያትን ሁሉ ሃይማኖት እስልምናን ሳይቀበል ከሞተ በተሳሳተ መንገድ ላይ እንደሞተ ነው የምናምነው፡፡ እንዲያውም ነብዩ ሙሐመድ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እንዲህ ይላሉ “ከየሁዳና ከነሷራ ስለ እኔ መላክ አይሰማም፣ ከዛም ሳያምንብኝ አይሞትም የእሳት ቢሆን እንጂ፡፡”
አረ አላህን እንፍራ፡፡ መቻቻል ማለት ሃይማኖታችን የከለከለውን ተግባር እየፈፀምን አይደለም፡፡
አላህ ሆይ! እውቀት ለግሰን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
ሙስሊም ወንድም እና እህቶቼ ሆይ! ኢስላም ማለት ሁሉን ነገር አቅፎ የያዘ የተሟላ ውብ ሃይማኖት ነው፡፡ ዛሬ ሃይማኖታዊ እውቀት ከመማር ተዘናግተን ይሀው አላህ የከለከለውን ሁሉ ስንጥስ ይታያል፡፡
አላህ እንዲህ ይላል
مَا كَانَ لِلنَّبِىِّ وَٱلَّذِينَ ءَامَنُوٓا۟ أَن يَسْتَغْفِرُوا۟ لِلْمُشْرِكِينَ وَلَوْ كَانُوٓا۟ أُو۟لِى قُرْبَىٰ مِنۢ بَعْدِ مَا تَبَيَّنَ لَهُمْ أَنَّهُمْ أَصْحَٰبُ ٱلْجَحِيمِ
ለነቢዩና ለነዚያ ላመኑት ለአጋሪዎቹ የዝምድና ባለቤቶች ቢኾኑም እንኳ እነሱ (ከሓዲዎቹ) የእሳት ጓዶች መኾናቸው ከተገለጸላቸው በኋላ ምሕረትን ሊለምኑ የሚገባ አልነበረም፡፡
ተመልከቱ የሞቱት ዘመዶቻችን ቢሆኑም እንኳን በአላህ ላይ እስካጋሩ ድረስ ምህረትን እንዳንጠይቅ ታዘናል፡፡ አይደለም የማናውቃቸው ግለሰቦች፡፡
ክርስትያኖችን ብትጠይቋቸው “ዘፋኝ የገሃነም ነው” ይሉሃል፡፡ ታድያ እኛ ምን ቤት ሆነን ነው በአላህ እና በመጨረሻው ቀን ሳያምን የሞተን ሰው “አላህ ይማርህ” የምንለው?
ነብዩ ሙሐመድ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “በአላህ ላይ እያጋራ የሞተ ሰው እሳት ገባ ብለዋል፡፡”
ከእስልምና ውጭ ያለ ሃይማኖት ተከታይ አንድ ሰው እስላም ሆኖ ቢሞት በተሳሳተ መንገድ ላይ እንደሞተ ነው የሚያምኑት፡፡ ፈጣሪ ብለው የሚያስቡትም ያንን ግለሰብ እነሱ የሚጓዙበትን መንገድ ስላልተከተለ እንደማይምረው ነው የሚያምኑት፡፡ እኛም ደግሞ የነብያትን ሁሉ ሃይማኖት እስልምናን ሳይቀበል ከሞተ በተሳሳተ መንገድ ላይ እንደሞተ ነው የምናምነው፡፡ እንዲያውም ነብዩ ሙሐመድ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እንዲህ ይላሉ “ከየሁዳና ከነሷራ ስለ እኔ መላክ አይሰማም፣ ከዛም ሳያምንብኝ አይሞትም የእሳት ቢሆን እንጂ፡፡”
አረ አላህን እንፍራ፡፡ መቻቻል ማለት ሃይማኖታችን የከለከለውን ተግባር እየፈፀምን አይደለም፡፡
አላህ ሆይ! እውቀት ለግሰን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ምክር መሬትም ጠብ አይል
እንዲህ ሲሉ መክረውን ነበር ‹‹ሙስሊም መሪ በዳይም፣ ጨቋኝም፣ ገንዘብ የሚቀማም፣ የሚማታም ቢሆን፣ በመጥፎ እስካላዘዘ ድረስ ስሙት ታዘዙት፣ ግልፅ ክህደት እስካላያችሁበት ድረስ››
ሊብያ ላይ የነበረውን መሪ አምፀው ጣሉት ይሀው አገሪቱ ለዚህ ሁሉ መከራ ተዳረገች፣ ግብፅ፣ የመን እና ሌሎችም ቦታዎች ላይ የሰው ሰይጣናት ስልጣን ፈልገው በሃይማኖት ስም ፈተናውን ቀስቅሰው ኡማውን ለዚህ ሁሉ መከራ ዳረጉት፡፡
አላህ ሆይ! የነብዩን (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ትዕዛዝ ከሚያከብሩት አድርገን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
እንዲህ ሲሉ መክረውን ነበር ‹‹ሙስሊም መሪ በዳይም፣ ጨቋኝም፣ ገንዘብ የሚቀማም፣ የሚማታም ቢሆን፣ በመጥፎ እስካላዘዘ ድረስ ስሙት ታዘዙት፣ ግልፅ ክህደት እስካላያችሁበት ድረስ››
ሊብያ ላይ የነበረውን መሪ አምፀው ጣሉት ይሀው አገሪቱ ለዚህ ሁሉ መከራ ተዳረገች፣ ግብፅ፣ የመን እና ሌሎችም ቦታዎች ላይ የሰው ሰይጣናት ስልጣን ፈልገው በሃይማኖት ስም ፈተናውን ቀስቅሰው ኡማውን ለዚህ ሁሉ መከራ ዳረጉት፡፡
አላህ ሆይ! የነብዩን (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ትዕዛዝ ከሚያከብሩት አድርገን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
ግራጁዌሽን
አላህ ለዋለልን ውለታ ልናመሰግነው እንጂ ልናምፀው አይገባም፡፡ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በየአመቱ ግራጁዌሽን (ምርቃት) ሲደርስ ኢስላማዊ መፅሄት ማዘጋጀት አለብን፣ ፎቶ መነሳት አለብን …… እና የመሳሰለውን የሚሉ አልጠፉም፡፡ እንደው የማይሰልመውን ሁሉ ካላሰለምን ማለት ምናለ ቢቀርብን፡፡ የወንድም ይሁን የሴት ሙስሊሞች ፎቶ ተለጥፎ ስም ከነአባባሎች ተፅፈው በጎኑ ጥቄት ሀዲሶች ተደባልቀውበት ኢስላማዊ ሊባል አይችልም፡፡
ኢስላም የሚከለክለውን ሳይከለከሉ ኢስላማዊ ማለት ምንኛ ሞኝነት ነው፡፡ አስገራሚው አንዳንዶች ‹‹ዶሩራ (ለችግር ጊዜ የሚደረግ ነው)›› ይላሉ፡፡ እስቲ የሙስሊሞች መፅሄት ተብሎ የወጣት ሴቶችንና ወንዶችን ፎቶ አለመለጠፉ ምኑ ነው ችግር?
እንዲያውም ይሄ ፅድቅ፣ አላህን መታዘዝ እንጂ (ፎቶ አለመለጠፉ)፡፡
ያው ሳታማሃኝ ብላኝ እንዳለው ነው፡፡ ሴትና ወንድ ወጣቶችን መደባለቅ ማለት እሳትና ጭድን የመደባለቅ ያህል ነው፡፡ አስገራሚው ኢስላማዊ የሚል ስም ይሰጡታል፡፡ ተመራቂ ተማሪዎች ሆይ! እንዲህ አይነት አፀያፊ ተግባሮችን ራቋቸው፡፡ ‹‹የአሚር ትዕዛዝ ነው›› የሚባለውንም ቅጥፈት ወደ ጎን ተዉት፡፡ አላህ በሚታመፅበት ጉዳይ ፍጡራንን መታዘዝ የለም ይሉናል የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም)፡፡
ድሮ የዩኒቨርስቲ ተማሪ በነበርን ጊዜ ሸውደውን ነበር ‹‹ቁጥራችንን ማሳየት አለብን›› ፎቶ እንነሳ እያሉ፡፡ አላህ መርቶን ከሱና ኡስታዞች ጋር አስተዋውቆን ኢስላም ማለት በስሜት መነዳት እንዳልሆነ፣ ሱናን መከተልና ቢድዐን መራቅ እንደሆነ አስተማሩን፡፡
አልሃምዱሊላህ፡፡
ሙስሊም ተመራቂ ተማሪዎች ሆይ! አላህን ፍሩ ፎቶዋችሁ የሌለበት ከኢስላም አስተምህሮት ለናንተ የሚጠቅሙ ፅሁፎች እና ትምህርቶች ያሉበትን ትምህርት ብቻ አዘጋጁ፡፡ የሴትም ይሁን የወንድ ፎቶ እና አድራሻ መፅሄት ላይ ማስቀመጥ በፍፅም አያስፈልግም፡፡ ምክንያቱም ይሄ መልክቱ ሰዎችን ወዳልተፈለገ አቅጣጫ መምራት ነውና፡፡
አላህን እንፍራ በምርቃት ዙሪያ ከሚሰሩ ኢስላም የሚጠላቸውን ነገሮች ሁሉ እንራቅ፡፡
አላህን የፈራ አላህ መውጫ ቀዳዳ ያደርግለታል፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
አላህ ለዋለልን ውለታ ልናመሰግነው እንጂ ልናምፀው አይገባም፡፡ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በየአመቱ ግራጁዌሽን (ምርቃት) ሲደርስ ኢስላማዊ መፅሄት ማዘጋጀት አለብን፣ ፎቶ መነሳት አለብን …… እና የመሳሰለውን የሚሉ አልጠፉም፡፡ እንደው የማይሰልመውን ሁሉ ካላሰለምን ማለት ምናለ ቢቀርብን፡፡ የወንድም ይሁን የሴት ሙስሊሞች ፎቶ ተለጥፎ ስም ከነአባባሎች ተፅፈው በጎኑ ጥቄት ሀዲሶች ተደባልቀውበት ኢስላማዊ ሊባል አይችልም፡፡
ኢስላም የሚከለክለውን ሳይከለከሉ ኢስላማዊ ማለት ምንኛ ሞኝነት ነው፡፡ አስገራሚው አንዳንዶች ‹‹ዶሩራ (ለችግር ጊዜ የሚደረግ ነው)›› ይላሉ፡፡ እስቲ የሙስሊሞች መፅሄት ተብሎ የወጣት ሴቶችንና ወንዶችን ፎቶ አለመለጠፉ ምኑ ነው ችግር?
እንዲያውም ይሄ ፅድቅ፣ አላህን መታዘዝ እንጂ (ፎቶ አለመለጠፉ)፡፡
ያው ሳታማሃኝ ብላኝ እንዳለው ነው፡፡ ሴትና ወንድ ወጣቶችን መደባለቅ ማለት እሳትና ጭድን የመደባለቅ ያህል ነው፡፡ አስገራሚው ኢስላማዊ የሚል ስም ይሰጡታል፡፡ ተመራቂ ተማሪዎች ሆይ! እንዲህ አይነት አፀያፊ ተግባሮችን ራቋቸው፡፡ ‹‹የአሚር ትዕዛዝ ነው›› የሚባለውንም ቅጥፈት ወደ ጎን ተዉት፡፡ አላህ በሚታመፅበት ጉዳይ ፍጡራንን መታዘዝ የለም ይሉናል የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም)፡፡
ድሮ የዩኒቨርስቲ ተማሪ በነበርን ጊዜ ሸውደውን ነበር ‹‹ቁጥራችንን ማሳየት አለብን›› ፎቶ እንነሳ እያሉ፡፡ አላህ መርቶን ከሱና ኡስታዞች ጋር አስተዋውቆን ኢስላም ማለት በስሜት መነዳት እንዳልሆነ፣ ሱናን መከተልና ቢድዐን መራቅ እንደሆነ አስተማሩን፡፡
አልሃምዱሊላህ፡፡
ሙስሊም ተመራቂ ተማሪዎች ሆይ! አላህን ፍሩ ፎቶዋችሁ የሌለበት ከኢስላም አስተምህሮት ለናንተ የሚጠቅሙ ፅሁፎች እና ትምህርቶች ያሉበትን ትምህርት ብቻ አዘጋጁ፡፡ የሴትም ይሁን የወንድ ፎቶ እና አድራሻ መፅሄት ላይ ማስቀመጥ በፍፅም አያስፈልግም፡፡ ምክንያቱም ይሄ መልክቱ ሰዎችን ወዳልተፈለገ አቅጣጫ መምራት ነውና፡፡
አላህን እንፍራ በምርቃት ዙሪያ ከሚሰሩ ኢስላም የሚጠላቸውን ነገሮች ሁሉ እንራቅ፡፡
አላህን የፈራ አላህ መውጫ ቀዳዳ ያደርግለታል፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
ማን ነው የመንግስት ቅጥረኛ?
እዩልኝ እነዚህን ደፋሮች?
አንዴ ቱርክ ሄዶ ሃውልት በጀርባው አድርጎ ሱሪውን ከቁርጭምጭሚቱ በታች አድርጎ ፎቶ ተነስቶ ይለቃል፡፡ ዛሬ ደግሞ ሰላት ሲሰግድም ፎቶ ተነስቶ ያውም የሚከተለው ማሞካሻ እና የድፍረት ውዳሴ ታክሎበት ፎቶ ተለቀቀለት
“በዛሬው እለት ጀግናው ኡስታዝ ካሚል ሸምሱ በጠቅላይ ሚኒስተር ደ/ር አብይ አህመድ ቤተመንግስት ውስጥ ያለማንም ፍራቻ በሚገርም ሁኔታ ሰላቱን ሰገደ አላሁአኩበር! አላሁአኩበር….”
ጥያቄ አለኝ “ያለማንም ፍራቻ በሚገርም ሁኔታ ሰላቱን ሰገደ” የሚለው ያለ እውቀት ምስክርነት ነው፡፡ አንድ ሰው የሰራውን ቢሰራ ለማን እንደሰራው የሚያውቀው የሚመሰክረው አላህ እና መለኮታዊ ራእይ የማይለያቸው ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ብቻና ብቻ ናቸው፡፡ አሁን እንዲህ በድፍረት ሰው ማደናነቁን ምን አመጣው?
ኢኽዋኖች አንድ ሰው የነሱን ሀሳብ ስላልተቀበለ ብቻ ቀበሌ እናኳን ባያዩት አፋቸውን ሞልተው “የወያኔ ቅጥረኛ፣ የመንግስት ተላላኪ፣ ሙናፊቅ” ይሉታል፡፡ በተጨባጭ ከመንግስት እና ባለስልጣናት ጋር አንድ ወንበር ላይ ቁጭ ብሎ መግለጫ ሲደሰኩር የሚያዩትን ብሎም ቤተመንግስት እንዲህ ሲገባ የሚያዩትን ግለሰብ ግን “ዶ/ር አብይ አህመድ ቤተመንግስት ውስጥ ያለማንም ፍራቻ በሚገርም ሁኔታ ሰላቱን ሰገደ” እያሉ አላህ ብቻ ለማን እንደተሰራ የሚያውቀውን ሰላት እንኳን የሚያውቁትን ምስክር ይመሰክሩለታል፡፡
ካሚል ሸምሱ ቤተመንግስት ምን ሊሰራ ነው የገባው?
ካሚል ሸምሱ ሰላት እየሰገደ ለምን ፎቶ ይነሳል?
ካሚል ሸምሱ እና ጓደኞቹ ለምን ረመዳን ሲፆሙ ከንፈራቸው ደርቆ ፆመኛ ነን ብለው ለምን ፎቶ አይነሱም?
ለፎቶ አፍቃሪያን እስካሁን ያልተሰራው ካሜራ ፆመኝነታቸውን የሚያሳይ ነው፡፡
ሰዎችን ቅጥረኛ ቅጥረኛ እያላችሁ በውሸት ስትለፍፉ ዛሬ በራሳችሁን ስራ እራሳችሁ ፈራጅ ሁኑ፡፡
ቤተመንግስት እና የመንግስት ቤሮዎች እና ስብሰባዎች ላይ ከመዞር በሺርክ፣ በቢድኣ፣ በጫት እና በሌሎች ጎጂ ነገሮች እየተሸደ ያለውን ህዝብ መታጠቂያችሁን ጠበቅ አድርጋችሁ ነብያችን (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እንደለፉት ይህንን ህዝብ ከዚህ አደገኛ መርዝ ለማውጣት ብትለፉ ነው የሚሻላችሁ፡፡ አለበለዚያ ከዚህ በፊት እንደወደቃችሁት፣ አሁንም እንደወደቃችሁት፣ ለወደፊትም ትወድቃላችሁ፡፡
ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ውርደትና ክብረቢስነት ትእዛዜን በጣሰ ላይ ሁሉ ሆነ” ብለዋል፡፡
እዩልኝ እነዚህን ደፋሮች?
አንዴ ቱርክ ሄዶ ሃውልት በጀርባው አድርጎ ሱሪውን ከቁርጭምጭሚቱ በታች አድርጎ ፎቶ ተነስቶ ይለቃል፡፡ ዛሬ ደግሞ ሰላት ሲሰግድም ፎቶ ተነስቶ ያውም የሚከተለው ማሞካሻ እና የድፍረት ውዳሴ ታክሎበት ፎቶ ተለቀቀለት
“በዛሬው እለት ጀግናው ኡስታዝ ካሚል ሸምሱ በጠቅላይ ሚኒስተር ደ/ር አብይ አህመድ ቤተመንግስት ውስጥ ያለማንም ፍራቻ በሚገርም ሁኔታ ሰላቱን ሰገደ አላሁአኩበር! አላሁአኩበር….”
ጥያቄ አለኝ “ያለማንም ፍራቻ በሚገርም ሁኔታ ሰላቱን ሰገደ” የሚለው ያለ እውቀት ምስክርነት ነው፡፡ አንድ ሰው የሰራውን ቢሰራ ለማን እንደሰራው የሚያውቀው የሚመሰክረው አላህ እና መለኮታዊ ራእይ የማይለያቸው ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ብቻና ብቻ ናቸው፡፡ አሁን እንዲህ በድፍረት ሰው ማደናነቁን ምን አመጣው?
ኢኽዋኖች አንድ ሰው የነሱን ሀሳብ ስላልተቀበለ ብቻ ቀበሌ እናኳን ባያዩት አፋቸውን ሞልተው “የወያኔ ቅጥረኛ፣ የመንግስት ተላላኪ፣ ሙናፊቅ” ይሉታል፡፡ በተጨባጭ ከመንግስት እና ባለስልጣናት ጋር አንድ ወንበር ላይ ቁጭ ብሎ መግለጫ ሲደሰኩር የሚያዩትን ብሎም ቤተመንግስት እንዲህ ሲገባ የሚያዩትን ግለሰብ ግን “ዶ/ር አብይ አህመድ ቤተመንግስት ውስጥ ያለማንም ፍራቻ በሚገርም ሁኔታ ሰላቱን ሰገደ” እያሉ አላህ ብቻ ለማን እንደተሰራ የሚያውቀውን ሰላት እንኳን የሚያውቁትን ምስክር ይመሰክሩለታል፡፡
ካሚል ሸምሱ ቤተመንግስት ምን ሊሰራ ነው የገባው?
ካሚል ሸምሱ ሰላት እየሰገደ ለምን ፎቶ ይነሳል?
ካሚል ሸምሱ እና ጓደኞቹ ለምን ረመዳን ሲፆሙ ከንፈራቸው ደርቆ ፆመኛ ነን ብለው ለምን ፎቶ አይነሱም?
ለፎቶ አፍቃሪያን እስካሁን ያልተሰራው ካሜራ ፆመኝነታቸውን የሚያሳይ ነው፡፡
ሰዎችን ቅጥረኛ ቅጥረኛ እያላችሁ በውሸት ስትለፍፉ ዛሬ በራሳችሁን ስራ እራሳችሁ ፈራጅ ሁኑ፡፡
ቤተመንግስት እና የመንግስት ቤሮዎች እና ስብሰባዎች ላይ ከመዞር በሺርክ፣ በቢድኣ፣ በጫት እና በሌሎች ጎጂ ነገሮች እየተሸደ ያለውን ህዝብ መታጠቂያችሁን ጠበቅ አድርጋችሁ ነብያችን (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እንደለፉት ይህንን ህዝብ ከዚህ አደገኛ መርዝ ለማውጣት ብትለፉ ነው የሚሻላችሁ፡፡ አለበለዚያ ከዚህ በፊት እንደወደቃችሁት፣ አሁንም እንደወደቃችሁት፣ ለወደፊትም ትወድቃላችሁ፡፡
ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ውርደትና ክብረቢስነት ትእዛዜን በጣሰ ላይ ሁሉ ሆነ” ብለዋል፡፡