ቀብር ላይ ሱረቱል ፋቲሃ እና ሌላን ሱራ መቅራት?
የቱን ይከተላሉ አላህ ያወረደውን ወይንስ “የአባቶቻችን መንገድ” ብለው የሚጠሩትን?
.
.
.
.
.
.
.
.
.
.
.
.
.
.
.
.
መቼም እስልምናችን ውብ እና ሙሉ፣ ለየትኛውም ዘመን እና ቦታ ከበቂ በላይ የሆነ ነው፡፡ ታማኙ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ከአላህ የተላኩበትን ማንኛውም መልእክት አስተላልፈዋል፡፡ ቀብር ስንዘይር ምን ማለት እንዳለብንም አስተምረዋል፡፡ የሚከተለው ሀዲስ ላይ እንደተዘገበው
وعن بريدة رضي الله عنه قال: كان النبي صلى الله عليه وسلم يعلمهم إذا خرجوا إلى المقابر أن يقول قائلهم: “السلام عليكم أهل الديار من المؤمنين والمسلمين وإنا إن شاء الله بكم للاحقون، أسأل الله لنا ولكم العافية” ((رواه مسلم)).
የአላህ ሰላም በናንተ የዚህ መኖሪያ (ቀብር) ባለቤቶች ላይ ይሁን፡፡ ከአማኞች እና ከሙስሊሞች፡፡ እኛ በአላህ ፍቃድ ወደ እናንተ የምንከተል (ሟቾች) ነን፡፡ አላህን ለእኛም ለእናንተ አፊያን እንዲያደርግ እንጠይቀዋለን፡፡
ከዚህ ሀዲስ የምንወስደው ዋና ቁምነገር
- በህይወት ያለ ሰው ነው ለሙታን ዱዓ የሚያደርገው፣
- ሙታን ዱዓ ይደረግላቸዋል እንጂ እነሱ አይለመኑም፣
- ዛሬ ሺርክ ላይ የወደቁ ሰዎች ህያው የሆነውን፣ ሁሉን በማድረግ ላይ ቻይ የሆነውን፣ የማይሞት አላህ ትተው ስራቸው የተቋረጠባቸውን፣ ምንም ማድረግ የማይችሉ፣ ቢጠሩ የማይሰሙ፣ ቢሰሙም ኖሮ መልስ መስጠት የማይችሉ ሙታኖችን እርዳታ ይለምናሉ፣ ቀብራቸው ላይ ሄደው ያርዳሉ፣ ቀብራቸው ላይ ጠዋፍ ያደርጋሉ፡፡
በዚህ ሀዲስ መሰረት ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ያስተማሩን ወንድ ልጅ ቀብር ሲሄድ ይህንን ዱኣ እንዲል ነው፡፡ ከዚህ ውጭ ሱረቱል ፋቲሃንም ይሁን ሌሎች ሱራዎችን በተለይ አገራችን ላይ በጀመዓ ቁርኣንን እየጮሁ የሚቀሩት ቢድዓ (በዲን ላይ የተጨመረ ፈጠራ) ነው፡፡ ከአላህ ቀጥሎ ለማንም በላይ እንወዳቸዋለን እያልን የምንጠራቸው ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እንዲህ ይሉናል “የእኛ ትዕዛዝ የሌለበትን ስራ የሰራ ሰው ስራው ተመላሽ ነው፡፡” (ስራው ተቀባይነት የለውም)፡፡ ቀብር ላይ ሄዶ ሱረቱል ፋቲሃንም ይሁን ሌላን ሱና በጀመዓም ይሁን በነጠላ መቅራት የታለ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ያዘዙበት? መልሱም አላዘዙበትም፡፡ ስለዚህ ቀብር ላይ እሳቸው ያስተማሩትን ብቻ እንበል፡፡
እኛ የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ተከታዬች ነን ካልን በሁሉ ነገር ልንከተላቸው እና እሳቸው ያልሰሩትን ልንርቅ ይገባናል፡፡ ከዛ ውጭ የነብዩን (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ትእዛዝ ለሸሁም፣ ለኡስታዙም፣ ለአባቶቹም ሲል የተወ ሰው ከባድ አደጋ ውስጥ ገብቷል፡፡ ምክንያቱም ነብዩን (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ከማንም በላይ እኛ ዘንድ እስካልተወደዱ (እስካልተከተልናቸው እና በዲን ላይ ከሚደረግ ፈጠራ እስካልራቅን) ድረስ እውነተኛ አማኞች አልሆንም፡፡
የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) አስተምህሮት ሱና እንዲህ ሁሉን ነገር ገላልፆ ሲያበቃ የአባቶቻችን መንገድ ብሎ ሱናን መቃረን ለከባድ አደጋ ይዳርጋል፡፡
የአባቶቻችን መንገድ የተባለው ከነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ሱና ከገጠመ በደስታ እንቀበለዋለን፡፡ ከአባት ከእናታችን በላይ ውድና በላጭ የሆኑትን የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) መንገድ ከተቃረን አሽቀንጥረን እንወረውረዋለን፡፡ ምክንያቱም የሰይጣን መንገድ ነውና፡፡ አላህ እንዲህ ይላል
[2:170] وَإِذَا قِيلَ لَهُمُ ٱتَّبِعُوا۟ مَآ أَنزَلَ ٱللَّهُ قَالُوا۟ بَلْ نَتَّبِعُ مَآ أَلْفَيْنَا عَلَيْهِ ءَابَآءَنَآ ۗ أَوَلَوْ كَانَ ءَابَآؤُهُمْ لَا يَعْقِلُونَ شَيْـًٔا وَلَا يَهْتَدُونَ
ለእነርሱም “አላህ ያወረደውን ተከተሉ” በተባሉ ጊዜ “አይደለም አባቶቻችንን በርሱ ላይ ያገኘንበትን ነገር እንከተላለን” ይላሉ፡፡ አባቶቻቸው ምንም የማያውቁና (ወደ እውነት) የማይመሩም ቢኾኑ (ይከተሉዋቸዋልን?)
[31:21] وَإِذَا قِيلَ لَهُمُ ٱتَّبِعُوا۟ مَآ أَنزَلَ ٱللَّهُ قَالُوا۟ بَلْ نَتَّبِعُ مَا وَجَدْنَا عَلَيْهِ ءَابَآءَنَآ ۚ أَوَلَوْ كَانَ ٱلشَّيْطَٰنُ يَدْعُوهُمْ إِلَىٰ عَذَابِ ٱلسَّعِيرِ
ለእነርሱም አላህ ያወረደውን ተከተሉ በተባሉ ጊዜ አይደለም በእርሱ ላይ አባቶቻችንን ያገኘንበትን እንከተላለን ይላሉ፡፡ ሰይጣን ወደ እሳት ቅጣት የሚጠራቸው ቢሆንም (ይከተሉዋቸዋልን?)
ይሀው እነዚህ ሁለት አንቀፆች በግልፅ እንዳስቀመጡት “የአባቶቻችን መንገድ” እየተባለ አገራችን ላይ የሚነሳው የጥንቶቹም የሚያነሱት ብዥታ ነበር፡፡ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እና እሳቸውን በየዘመኑ የሚከተሉ ኡለማዎች እና ተጣሪዎች የሚያዙት “አላህ ያወረደውን ተከተሉ (እንከተል)” ሲሉ ነው፡፡ የነብያትን መንገድ የሚቃረኑ ሰዎች ደግሞ በየዘመኑ መልሳቸው “አይደለም አባቶቻችንን በርሱ ላይ ያገኘንበትን ነገር እንከተላለን” የሚል ነው፡፡
አላህ ግን እንዲህ ሲል ጠየቀ
- “አባቶቻቸው ምንም የማያውቁና (ወደ እውነት) የማይመሩም ቢኾኑ (ይከተሉዋቸዋልን?)”
- “ሰይጣን ወደ እሳት ቅጣት የሚጠራቸው ቢሆንም (ይከተሉዋቸዋልን?)”
ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂኡን፡፡ አንዳንዴ የአባቶቻችን መንገድ የሚሉትን ልክ አይደለም ሲባሉ እና በማስረጃ መልስ ሲሰጠው “እናንተ ከእነ ሸህ እከሌ በላይ ታውቃላችሁን?” ሲሉም ይደመጣል፡፡ ጥያቄው እነዚህ ሸህ ተብየዎች ከነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እና ከሰሃባዎቻቸው በላይ ያውቃሉን? በፍፁም፡፡ እኛ አላህ እና መልክተኛው በእውቀታቸው፣ በአማኝነታቸው፣ በእውነተኝነታቸው፣ በታጋሽነታቸው፣ በቁርጠኝነታቸው የመሰከሩላቸውን መልክተኛውን እና ሰሃባዎቻቸውን መንገድ ነው የምንከተለው፡፡
አላህ ያወረደውን የማይከተል ሰይጣን ወደ እሳት የሚጣራበትን መንገድ እየተከተለ ነው፡፡
አገራችን ላይ አብዛኛውን ጥፋት “የአባቶቻችን መንገድ” እየተባለ ይፈፀማል፡፡ አባቶቻችንን ሳይሆን አላህ ያወረደውን እንድንከተል ነው የታዘዝነው፡፡ መልካም ማለት እኛ መልካም ያለነው አይደለም፡፡ መልካም ማለት ዲን መልካም ያለው ነው፡፡
አምነው ለሞቱ አባቶቻችን በጠቅላላ አላህ ወንጀላቸውን እንዲምር ደረጃቸውን ከፍ እንዲያደርግ ቀብራቸውን እንዲያሰፋ እለምነዋለሁ፡፡ አላህ እኛንም ሙስሊም አድርጎ እንዲገድለን እለምነዋለሁ፡፡
አላህ እሱ ባወረደው፣ በነብዩ ሱና ከሚብቃቁት፣ ከሺርክና ከቢድኣ ከሚርቁት ያድርገን፡፡ በአላህ ቢሆን እንጂ ሀይልም ብልሀትም የለም፡፡
የአላህ ሰላት እና ሰላም በነብያት መደምደሚያ፣ በባለቤቶቻቸው፣ በቤተሰቦቻቸው፣ በባልደረባዎቻቸው እና ሀቅን በተከተለ ላይ ሁሉ ይሁን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
የቱን ይከተላሉ አላህ ያወረደውን ወይንስ “የአባቶቻችን መንገድ” ብለው የሚጠሩትን?
.
.
.
.
.
.
.
.
.
.
.
.
.
.
.
.
መቼም እስልምናችን ውብ እና ሙሉ፣ ለየትኛውም ዘመን እና ቦታ ከበቂ በላይ የሆነ ነው፡፡ ታማኙ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ከአላህ የተላኩበትን ማንኛውም መልእክት አስተላልፈዋል፡፡ ቀብር ስንዘይር ምን ማለት እንዳለብንም አስተምረዋል፡፡ የሚከተለው ሀዲስ ላይ እንደተዘገበው
وعن بريدة رضي الله عنه قال: كان النبي صلى الله عليه وسلم يعلمهم إذا خرجوا إلى المقابر أن يقول قائلهم: “السلام عليكم أهل الديار من المؤمنين والمسلمين وإنا إن شاء الله بكم للاحقون، أسأل الله لنا ولكم العافية” ((رواه مسلم)).
የአላህ ሰላም በናንተ የዚህ መኖሪያ (ቀብር) ባለቤቶች ላይ ይሁን፡፡ ከአማኞች እና ከሙስሊሞች፡፡ እኛ በአላህ ፍቃድ ወደ እናንተ የምንከተል (ሟቾች) ነን፡፡ አላህን ለእኛም ለእናንተ አፊያን እንዲያደርግ እንጠይቀዋለን፡፡
ከዚህ ሀዲስ የምንወስደው ዋና ቁምነገር
- በህይወት ያለ ሰው ነው ለሙታን ዱዓ የሚያደርገው፣
- ሙታን ዱዓ ይደረግላቸዋል እንጂ እነሱ አይለመኑም፣
- ዛሬ ሺርክ ላይ የወደቁ ሰዎች ህያው የሆነውን፣ ሁሉን በማድረግ ላይ ቻይ የሆነውን፣ የማይሞት አላህ ትተው ስራቸው የተቋረጠባቸውን፣ ምንም ማድረግ የማይችሉ፣ ቢጠሩ የማይሰሙ፣ ቢሰሙም ኖሮ መልስ መስጠት የማይችሉ ሙታኖችን እርዳታ ይለምናሉ፣ ቀብራቸው ላይ ሄደው ያርዳሉ፣ ቀብራቸው ላይ ጠዋፍ ያደርጋሉ፡፡
በዚህ ሀዲስ መሰረት ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ያስተማሩን ወንድ ልጅ ቀብር ሲሄድ ይህንን ዱኣ እንዲል ነው፡፡ ከዚህ ውጭ ሱረቱል ፋቲሃንም ይሁን ሌሎች ሱራዎችን በተለይ አገራችን ላይ በጀመዓ ቁርኣንን እየጮሁ የሚቀሩት ቢድዓ (በዲን ላይ የተጨመረ ፈጠራ) ነው፡፡ ከአላህ ቀጥሎ ለማንም በላይ እንወዳቸዋለን እያልን የምንጠራቸው ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እንዲህ ይሉናል “የእኛ ትዕዛዝ የሌለበትን ስራ የሰራ ሰው ስራው ተመላሽ ነው፡፡” (ስራው ተቀባይነት የለውም)፡፡ ቀብር ላይ ሄዶ ሱረቱል ፋቲሃንም ይሁን ሌላን ሱና በጀመዓም ይሁን በነጠላ መቅራት የታለ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ያዘዙበት? መልሱም አላዘዙበትም፡፡ ስለዚህ ቀብር ላይ እሳቸው ያስተማሩትን ብቻ እንበል፡፡
እኛ የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ተከታዬች ነን ካልን በሁሉ ነገር ልንከተላቸው እና እሳቸው ያልሰሩትን ልንርቅ ይገባናል፡፡ ከዛ ውጭ የነብዩን (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ትእዛዝ ለሸሁም፣ ለኡስታዙም፣ ለአባቶቹም ሲል የተወ ሰው ከባድ አደጋ ውስጥ ገብቷል፡፡ ምክንያቱም ነብዩን (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ከማንም በላይ እኛ ዘንድ እስካልተወደዱ (እስካልተከተልናቸው እና በዲን ላይ ከሚደረግ ፈጠራ እስካልራቅን) ድረስ እውነተኛ አማኞች አልሆንም፡፡
የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) አስተምህሮት ሱና እንዲህ ሁሉን ነገር ገላልፆ ሲያበቃ የአባቶቻችን መንገድ ብሎ ሱናን መቃረን ለከባድ አደጋ ይዳርጋል፡፡
የአባቶቻችን መንገድ የተባለው ከነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ሱና ከገጠመ በደስታ እንቀበለዋለን፡፡ ከአባት ከእናታችን በላይ ውድና በላጭ የሆኑትን የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) መንገድ ከተቃረን አሽቀንጥረን እንወረውረዋለን፡፡ ምክንያቱም የሰይጣን መንገድ ነውና፡፡ አላህ እንዲህ ይላል
[2:170] وَإِذَا قِيلَ لَهُمُ ٱتَّبِعُوا۟ مَآ أَنزَلَ ٱللَّهُ قَالُوا۟ بَلْ نَتَّبِعُ مَآ أَلْفَيْنَا عَلَيْهِ ءَابَآءَنَآ ۗ أَوَلَوْ كَانَ ءَابَآؤُهُمْ لَا يَعْقِلُونَ شَيْـًٔا وَلَا يَهْتَدُونَ
ለእነርሱም “አላህ ያወረደውን ተከተሉ” በተባሉ ጊዜ “አይደለም አባቶቻችንን በርሱ ላይ ያገኘንበትን ነገር እንከተላለን” ይላሉ፡፡ አባቶቻቸው ምንም የማያውቁና (ወደ እውነት) የማይመሩም ቢኾኑ (ይከተሉዋቸዋልን?)
[31:21] وَإِذَا قِيلَ لَهُمُ ٱتَّبِعُوا۟ مَآ أَنزَلَ ٱللَّهُ قَالُوا۟ بَلْ نَتَّبِعُ مَا وَجَدْنَا عَلَيْهِ ءَابَآءَنَآ ۚ أَوَلَوْ كَانَ ٱلشَّيْطَٰنُ يَدْعُوهُمْ إِلَىٰ عَذَابِ ٱلسَّعِيرِ
ለእነርሱም አላህ ያወረደውን ተከተሉ በተባሉ ጊዜ አይደለም በእርሱ ላይ አባቶቻችንን ያገኘንበትን እንከተላለን ይላሉ፡፡ ሰይጣን ወደ እሳት ቅጣት የሚጠራቸው ቢሆንም (ይከተሉዋቸዋልን?)
ይሀው እነዚህ ሁለት አንቀፆች በግልፅ እንዳስቀመጡት “የአባቶቻችን መንገድ” እየተባለ አገራችን ላይ የሚነሳው የጥንቶቹም የሚያነሱት ብዥታ ነበር፡፡ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እና እሳቸውን በየዘመኑ የሚከተሉ ኡለማዎች እና ተጣሪዎች የሚያዙት “አላህ ያወረደውን ተከተሉ (እንከተል)” ሲሉ ነው፡፡ የነብያትን መንገድ የሚቃረኑ ሰዎች ደግሞ በየዘመኑ መልሳቸው “አይደለም አባቶቻችንን በርሱ ላይ ያገኘንበትን ነገር እንከተላለን” የሚል ነው፡፡
አላህ ግን እንዲህ ሲል ጠየቀ
- “አባቶቻቸው ምንም የማያውቁና (ወደ እውነት) የማይመሩም ቢኾኑ (ይከተሉዋቸዋልን?)”
- “ሰይጣን ወደ እሳት ቅጣት የሚጠራቸው ቢሆንም (ይከተሉዋቸዋልን?)”
ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂኡን፡፡ አንዳንዴ የአባቶቻችን መንገድ የሚሉትን ልክ አይደለም ሲባሉ እና በማስረጃ መልስ ሲሰጠው “እናንተ ከእነ ሸህ እከሌ በላይ ታውቃላችሁን?” ሲሉም ይደመጣል፡፡ ጥያቄው እነዚህ ሸህ ተብየዎች ከነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እና ከሰሃባዎቻቸው በላይ ያውቃሉን? በፍፁም፡፡ እኛ አላህ እና መልክተኛው በእውቀታቸው፣ በአማኝነታቸው፣ በእውነተኝነታቸው፣ በታጋሽነታቸው፣ በቁርጠኝነታቸው የመሰከሩላቸውን መልክተኛውን እና ሰሃባዎቻቸውን መንገድ ነው የምንከተለው፡፡
አላህ ያወረደውን የማይከተል ሰይጣን ወደ እሳት የሚጣራበትን መንገድ እየተከተለ ነው፡፡
አገራችን ላይ አብዛኛውን ጥፋት “የአባቶቻችን መንገድ” እየተባለ ይፈፀማል፡፡ አባቶቻችንን ሳይሆን አላህ ያወረደውን እንድንከተል ነው የታዘዝነው፡፡ መልካም ማለት እኛ መልካም ያለነው አይደለም፡፡ መልካም ማለት ዲን መልካም ያለው ነው፡፡
አምነው ለሞቱ አባቶቻችን በጠቅላላ አላህ ወንጀላቸውን እንዲምር ደረጃቸውን ከፍ እንዲያደርግ ቀብራቸውን እንዲያሰፋ እለምነዋለሁ፡፡ አላህ እኛንም ሙስሊም አድርጎ እንዲገድለን እለምነዋለሁ፡፡
አላህ እሱ ባወረደው፣ በነብዩ ሱና ከሚብቃቁት፣ ከሺርክና ከቢድኣ ከሚርቁት ያድርገን፡፡ በአላህ ቢሆን እንጂ ሀይልም ብልሀትም የለም፡፡
የአላህ ሰላት እና ሰላም በነብያት መደምደሚያ፣ በባለቤቶቻቸው፣ በቤተሰቦቻቸው፣ በባልደረባዎቻቸው እና ሀቅን በተከተለ ላይ ሁሉ ይሁን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
የአብሬት ሸህ እና ደርግ?
Degami Yeteposete
አምልኮ በብቸኝነት የሚገባው የሁሉ ፈጣሪ፣ ህያው፣የማይሞተው፣ አሸናፊ ለሆነው አላህ ብቻ ነው፡፡ ሰሞኑን ጉዞ ወደ አብሬት ብለው ሰዎች የሚሄዱለት የአብሬት ሸይኽ በመባል ይታወቃሉ፡፡ አገራችን ላይ በጣም ድንበር ከሚታለፍባቸው ግለሰቦች ውስጥ ከቶፕ 5 ውስጥ ናቸው፡፡
እዚህ ትምህርት ላይ ማንሳት የፈለግኩት ምን አይነት ሰው ነበሩ? የሚለውን አይደለም፡፡ ነገር ግን መጥቀስ የምፈልገው ምን ያህል ድንበር እንደታለፈባቸው ነው፡፡
የአብሬት ሸይኽ አዲስ አበባ አውቶብስ ተራ ወረድ ብሎ ያለ አካባቢ “ጠቅላይ ቢሮ” የሚባል ቦታ ውስጥ እራሳቸውን አሟቸው በተኙበት ከሳቸው “ሙሪዶች” አንዱ ቤቱን 7 ጊዜ ዞሮ ፊዳ ልሁን እኔ ብሎ እራሱን በቢላዋ አርዶ ገድሏል፡፡
ሌላው የአብሬት ሸይኽን በጣም ብዙ ሰዎች ለአላህ ብቻ የሚገባውን አምልኮ ሲፈፅሙላቸው ይታያል፡፡ አሳዛኙ ግን የአብሬት ሸይኽም ይሁን ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ለራሳቸውም ይሁን ለጠየቃቸው ጥቅምን ማምጣት፣ መስጠት አይችሉም፡፡ ከጉዳትም እራሳቸውንም ሆነ ጠብቀኝ ያላቸውን መከላከል አይችሉም፡፡
የአብሬት ሸይኽ ደርግ ወስዷቸው እርምጃ እንደወሰደባቸው ቤተሰቦቻቸውም የእሳቸውን ሞት ሁሉ ተቀብለው ተቀምጠው ሳለ፣ ተከታዬቻቸው “አባባ ይመጣሉ”፣ “አባባ አልሞቱም” እያሉ ብዙ ችግር ውስጥ ገብተዋል፡፡
አምልኮ ከደርግ እራሳቸውን ማስጣል ለማይችሉት ለደካማው አብሬት አይገባም፡፡ ይሄ ሺርክ ነው፡፡
አምልኮ ሃያል፣ ህያው፣ የማይሞት፣ አሸናፊ ለሆነው አላህ ብቻ እና ብቻ ነው የሚገባው፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
Degami Yeteposete
አምልኮ በብቸኝነት የሚገባው የሁሉ ፈጣሪ፣ ህያው፣የማይሞተው፣ አሸናፊ ለሆነው አላህ ብቻ ነው፡፡ ሰሞኑን ጉዞ ወደ አብሬት ብለው ሰዎች የሚሄዱለት የአብሬት ሸይኽ በመባል ይታወቃሉ፡፡ አገራችን ላይ በጣም ድንበር ከሚታለፍባቸው ግለሰቦች ውስጥ ከቶፕ 5 ውስጥ ናቸው፡፡
እዚህ ትምህርት ላይ ማንሳት የፈለግኩት ምን አይነት ሰው ነበሩ? የሚለውን አይደለም፡፡ ነገር ግን መጥቀስ የምፈልገው ምን ያህል ድንበር እንደታለፈባቸው ነው፡፡
የአብሬት ሸይኽ አዲስ አበባ አውቶብስ ተራ ወረድ ብሎ ያለ አካባቢ “ጠቅላይ ቢሮ” የሚባል ቦታ ውስጥ እራሳቸውን አሟቸው በተኙበት ከሳቸው “ሙሪዶች” አንዱ ቤቱን 7 ጊዜ ዞሮ ፊዳ ልሁን እኔ ብሎ እራሱን በቢላዋ አርዶ ገድሏል፡፡
ሌላው የአብሬት ሸይኽን በጣም ብዙ ሰዎች ለአላህ ብቻ የሚገባውን አምልኮ ሲፈፅሙላቸው ይታያል፡፡ አሳዛኙ ግን የአብሬት ሸይኽም ይሁን ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ለራሳቸውም ይሁን ለጠየቃቸው ጥቅምን ማምጣት፣ መስጠት አይችሉም፡፡ ከጉዳትም እራሳቸውንም ሆነ ጠብቀኝ ያላቸውን መከላከል አይችሉም፡፡
የአብሬት ሸይኽ ደርግ ወስዷቸው እርምጃ እንደወሰደባቸው ቤተሰቦቻቸውም የእሳቸውን ሞት ሁሉ ተቀብለው ተቀምጠው ሳለ፣ ተከታዬቻቸው “አባባ ይመጣሉ”፣ “አባባ አልሞቱም” እያሉ ብዙ ችግር ውስጥ ገብተዋል፡፡
አምልኮ ከደርግ እራሳቸውን ማስጣል ለማይችሉት ለደካማው አብሬት አይገባም፡፡ ይሄ ሺርክ ነው፡፡
አምልኮ ሃያል፣ ህያው፣ የማይሞት፣ አሸናፊ ለሆነው አላህ ብቻ እና ብቻ ነው የሚገባው፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
የጥመት ተጣሪዎች እና አላህ የረገመው ዊግ ቀጣይ…
ተመልከቱ አፍሪካ ቲቪ ላይ ከሚቀርቡ በኢስላም ስም ከሚያላግጡ ደፋሮች ውስጥ አላህ የረገመውን ዊግ (አርቴፊሻል ፀጉር) ቀጥሎ ስለ ዲን ላወራ ነው ይላል፡፡
የጥመት ተጣሪዎች ይህን ያህል ደርሰዋል፡፡ ሀሺሽም ሳብ የሚያደርግ እያስመለ፣ አፉንም በጫት ይወጥር አይወጥር አላህ ነው የሚያውቀው በዚህ መንገድ ካላስተማርኩ ይላል፡፡
እስቲ በአላህ ይሁንባችሁ፡፡ ስለ ዝሙት አስከፊነት ለማስተማር ሴትና ወንድ ድራማ ካልሰሩ፣ ካልተሳሳሙ፣ ካልተጨባበጡ ይባላልን?
በፍፁም፡፡
አላህ “ዝሙትን አትቅረቡት ብሏል” ብቻ ብሎ የአላህን ቃል ለሙስሊሞች ማስተማር ከበቂ በላይ ነው፡፡
ዲንን ለማስተማር ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም)፣ ሰሃባዎችና የነሱን መንገድ የተከተሉ መልካም ሰዎች የሄዱበት መንገድ ብቻ ይበቃል፡፡
ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) የከለከሉትን ፓንክ ተቆርጦ ስለ ዲን ሊያወራ ብቅ ከሚል ደፋር የበለጠ ማን ጋጠወጥ አለ?
አፍሪካ ቲቪ እና አዘጋጆቹ ደጋፊዎቹ እንዲህ አይነት አጥፊዎችን እና ጥመትን እስካስተላለፋችሁ ድረስ ወደዳችሁም ጠላችሁም መልስ ይሰጥባችኋል፡፡
ለአጥፊዎች መልስ መስጠት ለኡማው ከማዘን ነው፡፡ ይሄም በፍፁም ሀሜት አይደለም፡፡ የአላህ ባሪያዎች ሆይ! እንዲህ አይነት ጠሞ አጥማሚዎችን አስጠንቅቁ፡፡ ለምን ለብቻው አትመክሩትም ብለው የእንቅልፍ ኪኒን ሊወጓችሁ የሚሞክሩትንም አትስሟቸው፡፡ እሱ በአደባባይ ጥፋቱን እየረጨ እኛ ዝም እንድንለው ወይንም በጓዳ ተው እንድንለው ማሰብ ለሀቅ መቆርቆር አይደለም፡፡ ለሐቅ መቆርቆር በነበር እሱ በአደባባይ ይህን ጥፋት ሲያጠፋ ከፍቷቸው በተቃወሙት ነበር፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
ተመልከቱ አፍሪካ ቲቪ ላይ ከሚቀርቡ በኢስላም ስም ከሚያላግጡ ደፋሮች ውስጥ አላህ የረገመውን ዊግ (አርቴፊሻል ፀጉር) ቀጥሎ ስለ ዲን ላወራ ነው ይላል፡፡
የጥመት ተጣሪዎች ይህን ያህል ደርሰዋል፡፡ ሀሺሽም ሳብ የሚያደርግ እያስመለ፣ አፉንም በጫት ይወጥር አይወጥር አላህ ነው የሚያውቀው በዚህ መንገድ ካላስተማርኩ ይላል፡፡
እስቲ በአላህ ይሁንባችሁ፡፡ ስለ ዝሙት አስከፊነት ለማስተማር ሴትና ወንድ ድራማ ካልሰሩ፣ ካልተሳሳሙ፣ ካልተጨባበጡ ይባላልን?
በፍፁም፡፡
አላህ “ዝሙትን አትቅረቡት ብሏል” ብቻ ብሎ የአላህን ቃል ለሙስሊሞች ማስተማር ከበቂ በላይ ነው፡፡
ዲንን ለማስተማር ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም)፣ ሰሃባዎችና የነሱን መንገድ የተከተሉ መልካም ሰዎች የሄዱበት መንገድ ብቻ ይበቃል፡፡
ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) የከለከሉትን ፓንክ ተቆርጦ ስለ ዲን ሊያወራ ብቅ ከሚል ደፋር የበለጠ ማን ጋጠወጥ አለ?
አፍሪካ ቲቪ እና አዘጋጆቹ ደጋፊዎቹ እንዲህ አይነት አጥፊዎችን እና ጥመትን እስካስተላለፋችሁ ድረስ ወደዳችሁም ጠላችሁም መልስ ይሰጥባችኋል፡፡
ለአጥፊዎች መልስ መስጠት ለኡማው ከማዘን ነው፡፡ ይሄም በፍፁም ሀሜት አይደለም፡፡ የአላህ ባሪያዎች ሆይ! እንዲህ አይነት ጠሞ አጥማሚዎችን አስጠንቅቁ፡፡ ለምን ለብቻው አትመክሩትም ብለው የእንቅልፍ ኪኒን ሊወጓችሁ የሚሞክሩትንም አትስሟቸው፡፡ እሱ በአደባባይ ጥፋቱን እየረጨ እኛ ዝም እንድንለው ወይንም በጓዳ ተው እንድንለው ማሰብ ለሀቅ መቆርቆር አይደለም፡፡ ለሐቅ መቆርቆር በነበር እሱ በአደባባይ ይህን ጥፋት ሲያጠፋ ከፍቷቸው በተቃወሙት ነበር፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
በየመስጂዱ ያሉ ኢማሞች ኹጥባቸው ስለ ዘረኝነት አደጋ መሆን አለበት፡፡ ኡለማዎች ዱዐቶች የሀገር ሽማግሌዎች ከምንም በላይ ይህንን የዘረኝነት ሰደድ እሳት ለማጥፋት ከባድ ጥረት ማድረግና አለ በሚባል በሚያገኙት አጋጣሚ ሁሉ ስለ ዘረኝነት አስከፊነት ማስተማር አለባቸው፡፡ አለበለዚያ የፍርዱ ቀን ባለቤት እራቁታችንን አድርጎ ሲጠይቀን ከባድ ቅጣትን ይከናነቧታል፡፡ ኡለማና ጃሂል እኩል አይጠየቅም፡፡ ኡለሞችና ዱአቶች ሀላፍትናችሁን ተወጡ፡፡ የአላህን አደራ አትብሉ፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
https://t.me/SadatTextPosts
የነብዩ ሀዲስ ለትግሬውም፣ ለአማራውም፣ ለኦሮሞውም፣ ለስልጤመውም፣ ለጉዳጌውም፣ ለወለኔውም፣ ለሀደሬውም በአጠቃላይ ለአጀሙም፣ ለአረቡም፣ ለጂኑም ለሰውም ነው፡፡
የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ምክር አንዱን ዘር የለየ አይደለም ለሁላችንም ነው፡፡
ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምን) መቃረን እና አለመቀበል ከባድ አደጋ አለው፡፡ ጀሀነም እሳት ውስጥ ያስገባል፡፡ አላህ እንዲህ ይላል
وَمَن يُشَاقِقِ ٱلرَّسُولَ مِنۢ بَعْدِ مَا تَبَيَّنَ لَهُ ٱلْهُدَىٰ وَيَتَّبِعْ غَيْرَ سَبِيلِ ٱلْمُؤْمِنِينَ نُوَلِّهِۦ مَا تَوَلَّىٰ وَنُصْلِهِۦ جَهَنَّمَ ۖ وَسَآءَتْ مَصِيرًا
ቅኑም መንገድ ለእርሱ ከተገለጸ በኋላ መልክተኛውን የሚጨቃጨቅና ከምእምኖቹ መንገድ ሌላ የኾነን የሚከተል ሰው (በዚህ ዓለም) በተሾመበት (ጥመት) ላይ እንሾመዋለን፤ ገሀነምንም እናገባዋለን፡፡ መመለሻይቱም ከፋች!
ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ዘረኝነት ጥምብ ናት ተዋት” ብለዋል ሲባል የነብዩን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ንግግር ላለመቀበል “ለእንትን ዘሮች ንገራቸው የሚሉ” ነፍሳቸውን አምላኪ ማየት ልብ ያደማል፡፡
የነብዩ ሀዲስ ለትግሬውም፣ ለአማራውም፣ ለኦሮሞውም፣ ለስልጤመውም፣ ለጉራጌውም፣ ለወለኔውም፣ ለሀደሬውም በአጠቃላይ ለአጀሙም፣ ለአረቡም፣ ለጂኑም ለሰውም ነው፡፡ እሳቸው የተናገሩትን የማይቀበል የሰይጣን ወንድም ነው፡፡ አላህ ይጠብቀን፡፡
በዚህ ዘረኝነት የተነሳ ይሀው ሙስሊም ናቸው የሚባሉ ሰዎች ላኢላሃ ኢለላህ ያሉ ሰዎች እና ንፁሀንን እርስ በእርስ እየተጋደሉ እያየን ነው፡፡ በየመስጂዱ ያሉ ኢማሞች ኹጥባቸው ስለ ዘረኝነት አደጋ መሆን አለበት፡፡ ኡለማዎች ዱዐቶች የሀገር ሽማግሌዎች ከምንም በላይ ይህንን የዘረኝነት ሰደድ እሳት ለማጥፋት ከባድ ጥረት ማድረግና አለ በሚባል በሚያገኙት አጋጣሚ ሁሉ ስለ ዘረኝነት አስከፊነት ማስተማር አለባቸው፡፡ አለበለዚያ የፍርዱ ቀን ባለቤት እራቁታችንን አድርጎ ሲጠይቀን ከባድ ቅጣትን ይከናነቧታል፡፡ ኡለማና ጃሂል እኩል አይጠየቅም፡፡ ኡለሞችና ዱአቶች ሀላፍትናችሁን ተወጡ፡፡ የአላህን አደራ አትብሉ፡፡
አሁንም እደግመዋለሁ ማንም ዘር ከማንም ዘር አይበልጥም፡፡ አደለም ሀበሻ ሀበሻን ሊበልጠው የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ዘሮች አረቦች እንኳን ሀበሻን አይበልጡም፡፡ የሰው ልጅ የሚበላለጠው እና የሚለያየው በእምነቱ ነው፡፡
አላህ በሚታመንበት ሁሉ አምነው እሱን ከሚገናኙት ያድርገን፡፡ አላህ ሆይ! ሀገራችን ላይ የመጣው የዘረኝነት ፈተና አንሳልን፡፡ ከዚህ እርኩስ ተግባር ጠብቀን፡፡ የንፁሃንን ደምና ክብር ታደግልን፡፡ አንተም ሁሉን በማድረግ ላይ ቻይ ነህ፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ምክር አንዱን ዘር የለየ አይደለም ለሁላችንም ነው፡፡
ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምን) መቃረን እና አለመቀበል ከባድ አደጋ አለው፡፡ ጀሀነም እሳት ውስጥ ያስገባል፡፡ አላህ እንዲህ ይላል
وَمَن يُشَاقِقِ ٱلرَّسُولَ مِنۢ بَعْدِ مَا تَبَيَّنَ لَهُ ٱلْهُدَىٰ وَيَتَّبِعْ غَيْرَ سَبِيلِ ٱلْمُؤْمِنِينَ نُوَلِّهِۦ مَا تَوَلَّىٰ وَنُصْلِهِۦ جَهَنَّمَ ۖ وَسَآءَتْ مَصِيرًا
ቅኑም መንገድ ለእርሱ ከተገለጸ በኋላ መልክተኛውን የሚጨቃጨቅና ከምእምኖቹ መንገድ ሌላ የኾነን የሚከተል ሰው (በዚህ ዓለም) በተሾመበት (ጥመት) ላይ እንሾመዋለን፤ ገሀነምንም እናገባዋለን፡፡ መመለሻይቱም ከፋች!
ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ዘረኝነት ጥምብ ናት ተዋት” ብለዋል ሲባል የነብዩን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ንግግር ላለመቀበል “ለእንትን ዘሮች ንገራቸው የሚሉ” ነፍሳቸውን አምላኪ ማየት ልብ ያደማል፡፡
የነብዩ ሀዲስ ለትግሬውም፣ ለአማራውም፣ ለኦሮሞውም፣ ለስልጤመውም፣ ለጉራጌውም፣ ለወለኔውም፣ ለሀደሬውም በአጠቃላይ ለአጀሙም፣ ለአረቡም፣ ለጂኑም ለሰውም ነው፡፡ እሳቸው የተናገሩትን የማይቀበል የሰይጣን ወንድም ነው፡፡ አላህ ይጠብቀን፡፡
በዚህ ዘረኝነት የተነሳ ይሀው ሙስሊም ናቸው የሚባሉ ሰዎች ላኢላሃ ኢለላህ ያሉ ሰዎች እና ንፁሀንን እርስ በእርስ እየተጋደሉ እያየን ነው፡፡ በየመስጂዱ ያሉ ኢማሞች ኹጥባቸው ስለ ዘረኝነት አደጋ መሆን አለበት፡፡ ኡለማዎች ዱዐቶች የሀገር ሽማግሌዎች ከምንም በላይ ይህንን የዘረኝነት ሰደድ እሳት ለማጥፋት ከባድ ጥረት ማድረግና አለ በሚባል በሚያገኙት አጋጣሚ ሁሉ ስለ ዘረኝነት አስከፊነት ማስተማር አለባቸው፡፡ አለበለዚያ የፍርዱ ቀን ባለቤት እራቁታችንን አድርጎ ሲጠይቀን ከባድ ቅጣትን ይከናነቧታል፡፡ ኡለማና ጃሂል እኩል አይጠየቅም፡፡ ኡለሞችና ዱአቶች ሀላፍትናችሁን ተወጡ፡፡ የአላህን አደራ አትብሉ፡፡
አሁንም እደግመዋለሁ ማንም ዘር ከማንም ዘር አይበልጥም፡፡ አደለም ሀበሻ ሀበሻን ሊበልጠው የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ዘሮች አረቦች እንኳን ሀበሻን አይበልጡም፡፡ የሰው ልጅ የሚበላለጠው እና የሚለያየው በእምነቱ ነው፡፡
አላህ በሚታመንበት ሁሉ አምነው እሱን ከሚገናኙት ያድርገን፡፡ አላህ ሆይ! ሀገራችን ላይ የመጣው የዘረኝነት ፈተና አንሳልን፡፡ ከዚህ እርኩስ ተግባር ጠብቀን፡፡ የንፁሃንን ደምና ክብር ታደግልን፡፡ አንተም ሁሉን በማድረግ ላይ ቻይ ነህ፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
“የአራዳ ልጅ” ለሚባሉት ዳእዋ ለማድረግ አዲስ አይነት ስልት አያስፈልግም፡፡ ቁርኣን እና ሀዲስን ጠቅሶ ማስተማር ብቻ ከበቂ በላይ ነው፡፡ በአላህ ፍቃድ የተመራ ይመራል፡፡ ሰሃባዎች ከሄዱበት መንገድ ውጭ ያለን መንገድ የሄደ የጥመት መንገድን በእርግጥ ተጉዟል፡፡ የጥፋት መንገድም ተከታዩ የፈለገውን ያህል ቢበዛ ኪሳራን እንጂ ሌላን አያመጣም፡፡ ቁርኣን እና ሀዲስ ያልቀየረውን ድራማ፣ ውሸት፣ ፊልም፣ ፓንክ፣ ቀልድ አይቀይረውም፡፡ ይህ መልክት በእርግጥ ለቁርኣን እና ለሀዲስ እጃቸውን ለሰጡ ህዝቦች መገሰጫ ነው፡፡
ከሰዎች ሁሉ መጥፎ ሰዎች ማለት በነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) አንደበት ዳእዋ ተደርጎላቸው ያስተባበሉት ናቸው፡፡ ለእኛ ህዝብ ወጣትም ይሁን ሽማግሌ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እና ሰሀባዎቻቸው ከዛም እነሱን የተከተሉ ያደረጉትን ጥሪ ብቻ ማድረግ ከበቂም በላይ ነው፡፡
ከሐቅ በኋላ ጥመት እንጂ ምን አለ?
የትኛው ኡለማ ነው የሀሺሽን አደገኝነት ለማስተማር “ዊግ ጭንቅላቱ ላይ ጣል አድርጎ፣ ሀሺሽ መሳይ ነገር እንደሚያጨስ አስመስሎ እየተንገዳገደ” ያስጠነቀቀው?
ኢኽዋነል ሙስሊሚን የተባለው የጥመት ቡድን የዘራቸው መርዞች ይሀው በቅለው አገራችን ላይ እንዲህ ጥመታቸውን ሙስሊሙን ኡማ ሊበርዙበት ደፋ ቀና እያሉ ነው፡፡ አስገራሚው አህባሽ የሆነ ሰው ይህን ቢሰራው ይሀው ኡመተል ኢስላምን ሊያወድሙት ነው ተብሎ ይጮሃል፡፡ ልክ አህባሽ የሚያጠፋውን ያህል ኢኽዋን ሲያጠፋ ለሀቅ ከለላ መሆን ሲገባቸው አብዛኞች ለኢኽዋን ጠበቃ ቆመው ይንጫጫሉ፡፡ እንዲህ አይነት አጥፊዎችን እዚህ ያደረሷቸው ሰዎችና ቻናሎች ካልቶበቱ የእጃቸውን ሳይቀምሱ አይቀራትም፡፡
እኛ ዘንድ ከማንም በላይ ተወዳጅ ሊሆን የሚገባው ሐቅ ብቻና ብቻ ነው፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
ከሰዎች ሁሉ መጥፎ ሰዎች ማለት በነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) አንደበት ዳእዋ ተደርጎላቸው ያስተባበሉት ናቸው፡፡ ለእኛ ህዝብ ወጣትም ይሁን ሽማግሌ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እና ሰሀባዎቻቸው ከዛም እነሱን የተከተሉ ያደረጉትን ጥሪ ብቻ ማድረግ ከበቂም በላይ ነው፡፡
ከሐቅ በኋላ ጥመት እንጂ ምን አለ?
የትኛው ኡለማ ነው የሀሺሽን አደገኝነት ለማስተማር “ዊግ ጭንቅላቱ ላይ ጣል አድርጎ፣ ሀሺሽ መሳይ ነገር እንደሚያጨስ አስመስሎ እየተንገዳገደ” ያስጠነቀቀው?
ኢኽዋነል ሙስሊሚን የተባለው የጥመት ቡድን የዘራቸው መርዞች ይሀው በቅለው አገራችን ላይ እንዲህ ጥመታቸውን ሙስሊሙን ኡማ ሊበርዙበት ደፋ ቀና እያሉ ነው፡፡ አስገራሚው አህባሽ የሆነ ሰው ይህን ቢሰራው ይሀው ኡመተል ኢስላምን ሊያወድሙት ነው ተብሎ ይጮሃል፡፡ ልክ አህባሽ የሚያጠፋውን ያህል ኢኽዋን ሲያጠፋ ለሀቅ ከለላ መሆን ሲገባቸው አብዛኞች ለኢኽዋን ጠበቃ ቆመው ይንጫጫሉ፡፡ እንዲህ አይነት አጥፊዎችን እዚህ ያደረሷቸው ሰዎችና ቻናሎች ካልቶበቱ የእጃቸውን ሳይቀምሱ አይቀራትም፡፡
እኛ ዘንድ ከማንም በላይ ተወዳጅ ሊሆን የሚገባው ሐቅ ብቻና ብቻ ነው፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
Forwarded from MuhammedSirage M.Noor
በሚናገረው ጉዳይ ላይ ትንሽየ እውቀት እንኳን ባይኖረው በድፍረት የሚናገር አቋሙ ብልሹ የሆነ ሰው መሆኑን ካወቅኩ ቆየሁ ። አቡበክር አህመድ።
سلامة الصدر
የተባለ ሙሃደራውን ባዳመጥኩ ግዜ ግን ሰውየው በእጅጉ የወረደ ደፋር መሆኑን ይበልጥ ተረዳሁ! እዚህ ሙሃደራ ላይ የኡለሞችን ስም ከነኪታቦቻቸው ስም ሰሲያዛባ ከዚህም አልፎ የነብዩን ሐዲስ ባልተዘገበ ለፍዝ እያዛባ ሲያወራ ሰምቼ በእጅጉ ደነገጥኩ— والله በጣም ነበር ያሰደነገጠኝ ( ያንን ያህል የወረደ መሆኑ)
ዛሬ ደሞ በነሺዳ ዙሪያ ላይ ያለውን።ሰምቼ ደመመኝ! ! الله ይምራው ። የሰውየው ሁኔታ አሳዛኝና አሰወደንጋጭ ነው። ደህና አቋም።ያለው አዋቂ አገኘን ብለው የሚጠይቁት ይበልጥ ያሳዝናሉ ።
የዘመናችንን ብልሹ ነሺዳዎች የፈቀደበት ድምፅ ላይ ስለ ታላላቅ ሶሐቦች ምን እንደሚል ተመልከቱ ፣
" ሙዐዝ ፈቂህ ነው ሌላ ቦታ ላይ አናገኘውም
... ኢብኑ መስዑድ ቁርአን ላይ ነው ሌላ ቦታ ለይ አናገኘውም
አብዱላህ ኢብኑ ኡመር ሐዲስ ላይ ነው ሌላ ቦታ ላይ አናገኘውም"።
ምናለ አቡበክር ስላልዳሰስከውና ስለማታወቀው ነገር ባታወራ?! ዝምታ በብዙ መልኩ የተሻለ ነበር ላንተ!! እንዲህ አይነቱን አደብ ያጣ ንግግር በነዚሀ ታላቅ ሶሓቦች ላይ ከምትሰነዝር በርህን ዘግተህ ብታርፍ ይሻልህ ነበር!!!
ቅጥ ያጣ የመሃይም ድፍረት ማለት ይሄ ነው!! እነዚህ ታላላቅ ሶሀቦች አቡበክር በጠቀሰላቸው መልካም ላይ እንጂ ሌሎች ስራዎች አይገኙም ነበር?!! አይታዩም ነበር?!
እኛ ግን የተጠቀሱትን ሶሀቦች በሙሉ ሐዲስ ላይ እናገኛቸዋለን ። ጂሀድ ላይ ፣ ዙህድ ላይ ፣ ፈትዋ ላይ ፣ ማስተማርና ዳዕዋላይ፣ ሌሎችም በርካታ ስራዎች ላይ እናገኛቸዋለን!! የነሱ መልካም ስራ ተቆጥሮ አይዘለቅም!!
አላህ ስራቸውን ይውደድላቸው!
سلامة الصدر
የተባለ ሙሃደራውን ባዳመጥኩ ግዜ ግን ሰውየው በእጅጉ የወረደ ደፋር መሆኑን ይበልጥ ተረዳሁ! እዚህ ሙሃደራ ላይ የኡለሞችን ስም ከነኪታቦቻቸው ስም ሰሲያዛባ ከዚህም አልፎ የነብዩን ሐዲስ ባልተዘገበ ለፍዝ እያዛባ ሲያወራ ሰምቼ በእጅጉ ደነገጥኩ— والله በጣም ነበር ያሰደነገጠኝ ( ያንን ያህል የወረደ መሆኑ)
ዛሬ ደሞ በነሺዳ ዙሪያ ላይ ያለውን።ሰምቼ ደመመኝ! ! الله ይምራው ። የሰውየው ሁኔታ አሳዛኝና አሰወደንጋጭ ነው። ደህና አቋም።ያለው አዋቂ አገኘን ብለው የሚጠይቁት ይበልጥ ያሳዝናሉ ።
የዘመናችንን ብልሹ ነሺዳዎች የፈቀደበት ድምፅ ላይ ስለ ታላላቅ ሶሐቦች ምን እንደሚል ተመልከቱ ፣
" ሙዐዝ ፈቂህ ነው ሌላ ቦታ ላይ አናገኘውም
... ኢብኑ መስዑድ ቁርአን ላይ ነው ሌላ ቦታ ለይ አናገኘውም
አብዱላህ ኢብኑ ኡመር ሐዲስ ላይ ነው ሌላ ቦታ ላይ አናገኘውም"።
ምናለ አቡበክር ስላልዳሰስከውና ስለማታወቀው ነገር ባታወራ?! ዝምታ በብዙ መልኩ የተሻለ ነበር ላንተ!! እንዲህ አይነቱን አደብ ያጣ ንግግር በነዚሀ ታላቅ ሶሓቦች ላይ ከምትሰነዝር በርህን ዘግተህ ብታርፍ ይሻልህ ነበር!!!
ቅጥ ያጣ የመሃይም ድፍረት ማለት ይሄ ነው!! እነዚህ ታላላቅ ሶሀቦች አቡበክር በጠቀሰላቸው መልካም ላይ እንጂ ሌሎች ስራዎች አይገኙም ነበር?!! አይታዩም ነበር?!
እኛ ግን የተጠቀሱትን ሶሀቦች በሙሉ ሐዲስ ላይ እናገኛቸዋለን ። ጂሀድ ላይ ፣ ዙህድ ላይ ፣ ፈትዋ ላይ ፣ ማስተማርና ዳዕዋላይ፣ ሌሎችም በርካታ ስራዎች ላይ እናገኛቸዋለን!! የነሱ መልካም ስራ ተቆጥሮ አይዘለቅም!!
አላህ ስራቸውን ይውደድላቸው!
#ቅድሚያ ለተውሒድ #
ልጅ ከአባቱ በሂወት እያለ መውረስ ያለበት ኢልምን ነበር አባቱ ሲሞት ሃብትን ነበር
ነገር ግን አሁን የምንሰማው በተቃራኒው ነው>አባት ሲሞት ልጅ አባቴ የሚያርደው በየአመቱ (ለጂን የቢገብረው )እሱ ሲሞት ወደኔ ዞረ በማለት ሺርክን ካባቱ ይወርሳል ወይ ደሞ አባቱ በሂወት እያለ ሰወችን ወደራሱ የሚጣራ ( ጣኦት )ከሆነ አባት ሲሞት ልጅ (የሺርክ አልጋ ወራሽ ) ይሆንና የአባቱን። አልጋ ከነ ሙሪዶቹ ይረከባል ይህ ነው ባገራች የምንሰማው ሰወች ከከተማ ወደገጠር (ሼይኽ ፉላንጋ ) በማለት እያመሩ ሺርክ የለም አትበሉ ።
Hayat bint Nure
https://t.me/SadatTextPosts
ልጅ ከአባቱ በሂወት እያለ መውረስ ያለበት ኢልምን ነበር አባቱ ሲሞት ሃብትን ነበር
ነገር ግን አሁን የምንሰማው በተቃራኒው ነው>አባት ሲሞት ልጅ አባቴ የሚያርደው በየአመቱ (ለጂን የቢገብረው )እሱ ሲሞት ወደኔ ዞረ በማለት ሺርክን ካባቱ ይወርሳል ወይ ደሞ አባቱ በሂወት እያለ ሰወችን ወደራሱ የሚጣራ ( ጣኦት )ከሆነ አባት ሲሞት ልጅ (የሺርክ አልጋ ወራሽ ) ይሆንና የአባቱን። አልጋ ከነ ሙሪዶቹ ይረከባል ይህ ነው ባገራች የምንሰማው ሰወች ከከተማ ወደገጠር (ሼይኽ ፉላንጋ ) በማለት እያመሩ ሺርክ የለም አትበሉ ።
Hayat bint Nure
https://t.me/SadatTextPosts
ጥቂት ስለሱፍያ ከዓሊሞች አንደበት
① ኢማሙ ማሊክ (179 ሂጅራ):–
"እኛ ዘንድ ሱፍያ የሚባሉ ሰዎች አሉ። በብዛት ይበሉና ከዚያ ያንጎራጉራሉ። ከዚያም ተነስተው ይጨፍራሉ" ሲሏቸው "ህፃናት ናቸው?" ብለው ጠየቁ። "አይደሉም" ሲሏቸው "እብዶች ናቸው?" ብለው ሲጠይቁ "አይደሉም ሸይኾች ናቸው" አሏቸው። "እኔ ከኢስላም ሰዎች ይህን የሚሰራ አንድም አልሰማሁም" አሉ። [ተርቲቡል መዳሪክ: 2/53]
② ኢማሙ አሽሻፍዒይ (204 ሂጅራ):–
"ተሶውፍ የተገነባው ስንፍና ላይ ነው" ይላሉ። [ተልቢሱ ኢብሊስ: 320] በተጨማሪም "አንድ ሰው ጧት ሱፊ ከሆነ ቀትር በሱ ላይ አይደርስም ሞኝ ሆኖ የምታገኘው ቢሆን አንጂ!!" ብለዋል። [መናቂቡ አሽሻፍዒይ: 2/207]
③ ኢብኑ በጥጧህ አልዑክበሪ (387 ሂጅራ):–
"ዘፈንን ማዳመጥ ዑለማዎች የሚጠሉት ግና ቂሎች የሚወዱት ነገር ነው። ይህንን የሚሰሩተደ ሱፍያ የሚባሉ ክፍሎች ናቸው። … የዘቀጡ አላማዎች እና የፈጠራ እምነት በሰለቤቶች ናቸው። … ልጆችን እና ሴቶችን በማሰማት ይዘፍናሉ። ይጮሃሉ፣ ራሳቸውን ስተው ይወድቃሉ፣ የሞቱ መስለው ለሰዎች ይታያሉ። ይህ ሁሉ የሚሆነው ለጌታቸው ካላቸው ብርቱ ወዴታ እና ናፍቆት የተነሳ እንደሆነ ይሞግታሉ። እነዚህ መሀይሞች ከሚሉት ነገር አላህ ከፍ ያለ መላቅን ላቀ።" [ተልቢሱ ኢብሊስ: 211]
④ አልቃዲ አቡ አጥጦይብ አጥጦበሪ (451 ሂጅራ):– "ይህቺ ቡድን (ሱፍያ) ለሙስሊሙ ጀማዐህ ተፃራሪ ነች። ምክንያቱም ዘፈንን ዲንና መቃረቢያ አድርገዋልና።" [አስሰማዕ ሊብኒል ቀይዪም: 262]
⑤ አቡበክር አጥጦርጡሺ (451 ሂጅራ):– "የሱፍያ አካሄድ ቦዘኔነት፣ መሀይምነት እና ጥመት ነው።" [ተፍሲሩል ቁርጡቢ: 11/238]
⑥ ኢብኑ ዐቂል (513 ሂጅራ):– "ሱፍዮች ስራን ያበላሻሉ። የእምነት መሰረቶችን ያናጋሉ። ቦዘኔነትንና ዜማ ማዳመጥን ይወዳሉ።" "በሸሪዐ ላይ እንደ ዒልመል ከላም ሰዎች እና እንደ ሱፍያ ያለ አደጋ የለም።" [ተልቢሱ ኢብሊስ: 375]
⑦ ቁርጡቢ (671 ሂጅራ):– "ሱፍዮች የፈጠሩትን (ዜማ) በተመለከተ በክልክልነቱ ላይ ውዝግብ ከማይነሳባቸው ነገሮች ነው። ነገር ግን ብዙ በጥሩ የሚታሰቡ ሰዎችን ስሜት አሸንፏቸዋል። ብዙዎቹ ላይ የእብዶችና የህፃናት ስራዎች እስከሚታዩባቸውና በተጠናመልኩ እስከሚደንሱ ደርሰዋል። ከዚያም ከፊል ሰዎች መቃረቢያና መልካም ስራ ስራ እስከማድረግ ደረሱ።" [ተፍሲሩል ቁርጡቢ: 14/54]
⑧ ከማሉዲን አልአድፈዊ (748 ሂጅራ):– "ማንቀላፋትና መሀይምነት ሱፍዮች መሀል የተንሰራፋ ነው። አንዳንዶቻቸው ድንቁርናቸው ልክ በማለፉ ግልፅ የሆኑ ህሊናዊ እውነታዎችን ይክዳሉ። ሁለት ተቃራኒ ነገሮችን ባንድ ላይ ሰብስበው ያምናሉ።" [አጥጧሊዑ አስሰዒድ: 133]
By Ibnu Munewor
① ኢማሙ ማሊክ (179 ሂጅራ):–
"እኛ ዘንድ ሱፍያ የሚባሉ ሰዎች አሉ። በብዛት ይበሉና ከዚያ ያንጎራጉራሉ። ከዚያም ተነስተው ይጨፍራሉ" ሲሏቸው "ህፃናት ናቸው?" ብለው ጠየቁ። "አይደሉም" ሲሏቸው "እብዶች ናቸው?" ብለው ሲጠይቁ "አይደሉም ሸይኾች ናቸው" አሏቸው። "እኔ ከኢስላም ሰዎች ይህን የሚሰራ አንድም አልሰማሁም" አሉ። [ተርቲቡል መዳሪክ: 2/53]
② ኢማሙ አሽሻፍዒይ (204 ሂጅራ):–
"ተሶውፍ የተገነባው ስንፍና ላይ ነው" ይላሉ። [ተልቢሱ ኢብሊስ: 320] በተጨማሪም "አንድ ሰው ጧት ሱፊ ከሆነ ቀትር በሱ ላይ አይደርስም ሞኝ ሆኖ የምታገኘው ቢሆን አንጂ!!" ብለዋል። [መናቂቡ አሽሻፍዒይ: 2/207]
③ ኢብኑ በጥጧህ አልዑክበሪ (387 ሂጅራ):–
"ዘፈንን ማዳመጥ ዑለማዎች የሚጠሉት ግና ቂሎች የሚወዱት ነገር ነው። ይህንን የሚሰሩተደ ሱፍያ የሚባሉ ክፍሎች ናቸው። … የዘቀጡ አላማዎች እና የፈጠራ እምነት በሰለቤቶች ናቸው። … ልጆችን እና ሴቶችን በማሰማት ይዘፍናሉ። ይጮሃሉ፣ ራሳቸውን ስተው ይወድቃሉ፣ የሞቱ መስለው ለሰዎች ይታያሉ። ይህ ሁሉ የሚሆነው ለጌታቸው ካላቸው ብርቱ ወዴታ እና ናፍቆት የተነሳ እንደሆነ ይሞግታሉ። እነዚህ መሀይሞች ከሚሉት ነገር አላህ ከፍ ያለ መላቅን ላቀ።" [ተልቢሱ ኢብሊስ: 211]
④ አልቃዲ አቡ አጥጦይብ አጥጦበሪ (451 ሂጅራ):– "ይህቺ ቡድን (ሱፍያ) ለሙስሊሙ ጀማዐህ ተፃራሪ ነች። ምክንያቱም ዘፈንን ዲንና መቃረቢያ አድርገዋልና።" [አስሰማዕ ሊብኒል ቀይዪም: 262]
⑤ አቡበክር አጥጦርጡሺ (451 ሂጅራ):– "የሱፍያ አካሄድ ቦዘኔነት፣ መሀይምነት እና ጥመት ነው።" [ተፍሲሩል ቁርጡቢ: 11/238]
⑥ ኢብኑ ዐቂል (513 ሂጅራ):– "ሱፍዮች ስራን ያበላሻሉ። የእምነት መሰረቶችን ያናጋሉ። ቦዘኔነትንና ዜማ ማዳመጥን ይወዳሉ።" "በሸሪዐ ላይ እንደ ዒልመል ከላም ሰዎች እና እንደ ሱፍያ ያለ አደጋ የለም።" [ተልቢሱ ኢብሊስ: 375]
⑦ ቁርጡቢ (671 ሂጅራ):– "ሱፍዮች የፈጠሩትን (ዜማ) በተመለከተ በክልክልነቱ ላይ ውዝግብ ከማይነሳባቸው ነገሮች ነው። ነገር ግን ብዙ በጥሩ የሚታሰቡ ሰዎችን ስሜት አሸንፏቸዋል። ብዙዎቹ ላይ የእብዶችና የህፃናት ስራዎች እስከሚታዩባቸውና በተጠናመልኩ እስከሚደንሱ ደርሰዋል። ከዚያም ከፊል ሰዎች መቃረቢያና መልካም ስራ ስራ እስከማድረግ ደረሱ።" [ተፍሲሩል ቁርጡቢ: 14/54]
⑧ ከማሉዲን አልአድፈዊ (748 ሂጅራ):– "ማንቀላፋትና መሀይምነት ሱፍዮች መሀል የተንሰራፋ ነው። አንዳንዶቻቸው ድንቁርናቸው ልክ በማለፉ ግልፅ የሆኑ ህሊናዊ እውነታዎችን ይክዳሉ። ሁለት ተቃራኒ ነገሮችን ባንድ ላይ ሰብስበው ያምናሉ።" [አጥጧሊዑ አስሰዒድ: 133]
By Ibnu Munewor
ዝናብ… ሰላም?
ዝናብ ሲጠፋ ከፍጡራኑ ሁሉ በላይ ከሰማያት በላይ ወዳለው አላህ አንጋጠን እንለምናልን፡፡ እሱም ያዘንብልናል፡፡ ከዝናብ በላይ የሆነው ሰላም ሲጠፋ አላህ ሁሉን በማድረግ ላይ ቻይ ነውና ሰላምን እና ፍትህን እንዲያመጣ አላህን እንለምን፡፡ ፈተናን ማንሳት የሚችለው አላህ ብቻ ነው፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
ዝናብ ሲጠፋ ከፍጡራኑ ሁሉ በላይ ከሰማያት በላይ ወዳለው አላህ አንጋጠን እንለምናልን፡፡ እሱም ያዘንብልናል፡፡ ከዝናብ በላይ የሆነው ሰላም ሲጠፋ አላህ ሁሉን በማድረግ ላይ ቻይ ነውና ሰላምን እና ፍትህን እንዲያመጣ አላህን እንለምን፡፡ ፈተናን ማንሳት የሚችለው አላህ ብቻ ነው፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
