መውሊድ ላይ የሚባሉ የሺርክ፣ ቢድኣና ኹራፋት ስንኞች፡፡ ከሚከተሉት ሊንኮች አውርዳችሁ አንብቡና እውነታው እናንተው ፍረዱ፡፡ 97 አደገኛ ስንኞች
https://goo.gl/x2eDmD
https://goo.gl/4CWQ6a
https://t.me/Menzuma
https://goo.gl/x2eDmD
https://goo.gl/4CWQ6a
https://t.me/Menzuma
መውሊድ ብለው የሚያከብሩት የሞቱበትን ወይንስ የተወለዱበትን?
ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂኡን፡፡ አዛኙ ነብይ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ቢድኣ (በዲን ላይ ያለ) ፈጠራ ሁሉ ጥመት ነው” ብለው ሲያበቃ፣ ያልታዘዙትን የሚሰሩት የቢድዓ ሰዎች መውሊድ (ነብዩ የተወለዱበትን ቀን) እናከብራለን ብለው ሞገቱ፡፡
ሰይጣን ለሰው ልጆች አደገኛ ጠላታቸው ነው፡፡ ጠላትነቱን በጣም የከፋ የሚያደርገው ደግሞ የሰው ልጆችን አላህ እና መልክተኛው የከለከላከሏቸውን ተግባር ሲያሰራቸው ለነሱ አዛኝ መስሎ ነው፡፡
ጥያቄው ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) የተወለዱበት ቀን ኺላፍ (ውዝግብ) እንዳለበት ይታወቃል፡፡ የሞቱበት ግን ያለ ምንም ውዝግብ ረቢአል አወል 12 መሆኑ ይታወቃል፡፡
ታድያ መውሊድን እናከብራለን የሚሉ ሰዎች የሺርክ ስንኞችን እያቀነቀኑ፣ እየጨፈሩ የሚያሳልፉት በተወለዱበት ወይንስ በሞቱበት ቀን?
ይሉ ይሆናል “የተወለዱበት ቀን ውዝግብ ቢኖረውም፣ የሞቱበት ቀን ረቢዓል አወል 12 መሆኑን ብናውቅም አላህ ንያችንን ይመለከታል፡፡ እኛ ልናከብር የፈለግነው የተወለዱበትን ቀን ነው፡፡” ነገር ግን ንያ ብቻውን ስራ ተቀባይነት እንዲኖረው መስፈርት አይሆንም፡፡ ከንያ በመቀጠል መሟላት ያለበት መስፈርት አለ፡፡ እሱም የሚሰራው ስራ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ያዘዙበት፣ የሰሩት፣ ወይንም ሰሃባዎቻቸው ሲሰሩ አይተው ዝም ያሉት መሆን አለበት፡፡ ለዚህም ማስረጃው የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “የእኛ ትዕዛዝ የሌለበትን ስራ የሰራ ሰው ስራው ተመላሽ (ውድቅ) ነው” ብለዋል፡፡
እሳቸው የተወለዱበትን ቀን አመት ጠብቆ ማክበር እሳቸው አላዘዙበትም፡፡ ሸይጧን እዚህ ድረስ እሱን የሚከተሉትን ሰዎች አግኝቷል፡፡ እንወዳቸዋለን የሚሉትን ነብይ የሞቱበትን ቀን የደስታ ቀን አድርገው የሚይዙ፡፡ ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂኡን፡፡
አላህ ሆይ! ሐቅን በሐቅነቱ አሳየን የምንቀበለውም አድርገን፡፡ ባጢልን በባጢልነቱ አሳየን የምንርቀውም አድርገን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem
https://www.facebook.com/sadat.kemal
https://www.youtube.com/user/TewhideFirst
ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂኡን፡፡ አዛኙ ነብይ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ቢድኣ (በዲን ላይ ያለ) ፈጠራ ሁሉ ጥመት ነው” ብለው ሲያበቃ፣ ያልታዘዙትን የሚሰሩት የቢድዓ ሰዎች መውሊድ (ነብዩ የተወለዱበትን ቀን) እናከብራለን ብለው ሞገቱ፡፡
ሰይጣን ለሰው ልጆች አደገኛ ጠላታቸው ነው፡፡ ጠላትነቱን በጣም የከፋ የሚያደርገው ደግሞ የሰው ልጆችን አላህ እና መልክተኛው የከለከላከሏቸውን ተግባር ሲያሰራቸው ለነሱ አዛኝ መስሎ ነው፡፡
ጥያቄው ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) የተወለዱበት ቀን ኺላፍ (ውዝግብ) እንዳለበት ይታወቃል፡፡ የሞቱበት ግን ያለ ምንም ውዝግብ ረቢአል አወል 12 መሆኑ ይታወቃል፡፡
ታድያ መውሊድን እናከብራለን የሚሉ ሰዎች የሺርክ ስንኞችን እያቀነቀኑ፣ እየጨፈሩ የሚያሳልፉት በተወለዱበት ወይንስ በሞቱበት ቀን?
ይሉ ይሆናል “የተወለዱበት ቀን ውዝግብ ቢኖረውም፣ የሞቱበት ቀን ረቢዓል አወል 12 መሆኑን ብናውቅም አላህ ንያችንን ይመለከታል፡፡ እኛ ልናከብር የፈለግነው የተወለዱበትን ቀን ነው፡፡” ነገር ግን ንያ ብቻውን ስራ ተቀባይነት እንዲኖረው መስፈርት አይሆንም፡፡ ከንያ በመቀጠል መሟላት ያለበት መስፈርት አለ፡፡ እሱም የሚሰራው ስራ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ያዘዙበት፣ የሰሩት፣ ወይንም ሰሃባዎቻቸው ሲሰሩ አይተው ዝም ያሉት መሆን አለበት፡፡ ለዚህም ማስረጃው የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “የእኛ ትዕዛዝ የሌለበትን ስራ የሰራ ሰው ስራው ተመላሽ (ውድቅ) ነው” ብለዋል፡፡
እሳቸው የተወለዱበትን ቀን አመት ጠብቆ ማክበር እሳቸው አላዘዙበትም፡፡ ሸይጧን እዚህ ድረስ እሱን የሚከተሉትን ሰዎች አግኝቷል፡፡ እንወዳቸዋለን የሚሉትን ነብይ የሞቱበትን ቀን የደስታ ቀን አድርገው የሚይዙ፡፡ ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂኡን፡፡
አላህ ሆይ! ሐቅን በሐቅነቱ አሳየን የምንቀበለውም አድርገን፡፡ ባጢልን በባጢልነቱ አሳየን የምንርቀውም አድርገን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem
https://www.facebook.com/sadat.kemal
https://www.youtube.com/user/TewhideFirst
👆🏻ማን የማን ቅጥረኛ ነው?
ኢኽዋኖች ከኢሀዲግ እስከ ግንቦት 7?
አቡበክር አሕመድ፣ ሀሰን ታጁ …..
የኢትዮጵያ ሙስሊም ሐቁን ለመገንዘብ ማዳመጥ ያለበት እውነታ፡፡
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem
ኢኽዋኖች ከኢሀዲግ እስከ ግንቦት 7?
አቡበክር አሕመድ፣ ሀሰን ታጁ …..
የኢትዮጵያ ሙስሊም ሐቁን ለመገንዘብ ማዳመጥ ያለበት እውነታ፡፡
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem
አልሐምዱሊላህ ወንድሜ ኢብኑ ሙነወር በአላህ ፈቃድ እና ምህረት ከደረሰበት አደጋጋ በማገገም ላይ ነው፡፡ በአላህ ፍቃድ ወደ አዲስ አበባ መኖሪያ ቤቱ በቀጣይ ቀናቶች ውስጥ ይመለሳል፡፡ አላህ ሆይ! በሁለት አገር አፊያ አድርገን፡፡ ወንድሜን ከከባድ አደጋ ስላተረፍከውም አመሰግንሃለሁ፡፡ ብቸኛው ተለማኝ ህያው ጌታችን ሆይ! መቼም ማናችንም ከሞት አናመልጥምና፣ ስንኖርም ስንሞትም በተውሒድ መንገድ ላይ አኑረህ ግደለን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
https://t.me/SadatTextPosts
አልሐምዱሊላህ አላህ ወንድማችን ኢብኑ ሙነወርን ከልጆቹ ጋር በሰላም አገናኝቶታል፣ ለቤቱም አብቅቶታል፡፡ የሱን ደህንነት ካላችሁበት ሆናችሁ ስትጠይቁና ዱዓ ላደረጋችሁለት ወንድም እና እህቶች በጠቅላላ አላህ አትርፎት ለቤቱ በመብቃቱ አላህ ምንዳችሁን እጥፍ ድርብ አድርጎ ይክፈላችሁ፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
https://t.me/SadatTextPosts
የሐበሻ ሙስሊሞች ሆይ! ማንም ከማንም ዘር አይበልጥም፡፡
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
የሐበሻ ሙስሊሞች ሆይ! አላህን እንፍራ ጥምቡን ዘረኝነት ከላያችን ላይ ጨርሰን አራግፈን እንጣል፡፡
ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ሰሃባዎቻቸው ላይ ከባድ በደል፣ ስቃይ እና እንግልት ሲደርስባቸው “ሂዱ ወደ ሀበሻ” ነበር ያሉት፡፡ እኛ ሙስሊሞች ነን፡፡ የሀበሻ ሙስሊሞች የሚለው ከበቂ በላይ መታወቂያችን ነው፡፡ ዘራችንን ከኢስላም አስቀድመን እርስ በርስ እየተናናቅን መከፋፈሉ ለከባድ አደጋ ነው የሚዳርገን፡፡
አንድ ሰው በእስልምናው እንጂ በዘሩ ጀነት አይገባም፡፡ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ስራው ወደ ኋላ ያስቀረውን ሰው ዘሩ (ወደፊት) አያስቀድመውም” ብለዋል፡፡
አንድ ሰው ጀነት ለመግባት ብቸኛው መንገዱ
- ተውሒድን አሳምሮ መያዙ ከሺርክ እና ከባለቤቶቹ ሙሉ ለሙሉ መፅዳቱ፣
- የነብዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምን ሱና አጥብቆ መያዙ ቢድኣ የተባለን በጠቅላላ መራቁ፣
- የሰሃባዎችን አረዳድ መከተሉ የጥመት መንገዶችን ሁሉ መራቁ፣
- የአላህንና የመልክተኛውን ትእዛዝ መፈፀሙ እነሱንም አለማመፁ ……
- …..
እንጂ ዘሩ አይደለም፡፡
ዘር ለመተዋወቅ ብቻ እንጅ ለሌላ አይደለም፡፡ እውነቱን ለፈለጉ ሰዎች አላህ እንዲህ ይላል
يَٰٓأَيُّهَا ٱلنَّاسُ إِنَّا خَلَقْنَٰكُم مِّن ذَكَرٍ وَأُنثَىٰ وَجَعَلْنَٰكُمْ شُعُوبًا وَقَبَآئِلَ لِتَعَارَفُوٓا۟ ۚ إِنَّ أَكْرَمَكُمْ عِندَ ٱللَّهِ أَتْقَىٰكُمْ ۚ إِنَّ ٱللَّهَ عَلِيمٌ خَبِيرٌ
እናንተ ሰዎች ሆይ! እኛ ከወንድና ከሴት ፈጠርናችሁ፡፡ እንድትተዋወቁም ጎሳዎችና ነገዶች አደረግናችሁ፡፡ አላህ ዘንድ በላጫችሁ በጣም አላህን ፈሪያችሁ ነው፡፡ አላህ ግልጽን ዐዋቂ ውስጥንም ዐዋቂ ነው፡፡
አላህ በግልፅ እውነታውን ነግሮናል፡፡
ዘረኞች፣ ዘራቸውን ከኢስላም የሚያስቀድሙ ጥምብ አንሳዎች ናቸው፡፡
ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ዘረኝነት ጥምብ ናት፡፡ ተዋት፡፡” እያሉን የነብዩን (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ትእዛዝ ትተው እሳቸው የከለከሉትን የሚያነሱ ጥምብ አንሳዎች ናቸው፡፡
የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “….ተዋት” ብለው ጥንቡን ዘረኝነት እንድንተው ሲነግሩን አይ አልተውም ብሎ ከእስልምና ዘሩን አስቀድሞ ሙስሊም የሆነ ከእሱ ዘር ያልሆነው ላይ አደጋ ሊያደርስ፣ ንብረቱን ሊቀማ የሚያስብ ሰው ምንኛ ከሰረ፡፡
የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ሁለት ሙስሊሞች ሰይፍ አይማዘዙም ገዳይም ተገዳይም የእሳት ናቸው” ሲሉ
ሰሃባዎች “ገዳይስ ገድሎ ነው” ተገዳይስ ሲሉ ጠየቁ
የአላህ መልክተኛም (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “እሱም ንያ ነበረው” ሲሉ እነዚህ ሰዎች የሚሰሩትን ስራ የእሳት መንገድ እንደሆነ ገለፁ፡፡
ኢስላም ለሁሉም ነገር ዝርዝር የሆነ መተዳደሪያ ያለው፣ ለሁሉም ዘመን፣ ለሁሉም ቦታ፣ ለሁሉም ትውልድ ሙሉና ከበቂ በላይ የሆነ አላህ የሚቀበለው ብቸኛ ሃይማኖት ነው፡፡
ውቡ ኢስላም እርስ በእርስ መጋደላችንን. መበዳደላችንን አጥብቆ ኮንኖታል፡፡
ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “አንድ ሙስሊም ለአንድ ሙስሊም ወንድሙ ነው፡፡ አይበድለው….” ብለዋል፡፡ ታድያ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “አይበድለው” እያሉ ዘሩ ስላልሆነ ብቻ ሌሎች ሙስሊሞችን ሊገድል የተነሳው ምን ሊባል ነው?
አላህ ይድረስልን፡፡ ከዚህ ቆሻሻ ተግባርም ይጠብቀን፡፡
የሀበሻ ሙስሊሞች ሆይ! ሙስሊም የሆነ ሰው እኛ ዘንድ እንደራሳችን አድርገን ልንወደው ይገባል፡፡ ሙስሊም ደሙም፣ ገንዘቡም፣ ክብሩም የተጠበቀ ነው፡፡ ልብ ያለው ልብ ይበል፡፡
የሀበሻ ሙስሊሞች ሆይ! አላህን እንፍራ ዘረኝነትን ከላያችን ላይ እናራግፍ፡፡ ማንም ማንንም በዘሩ አይበልጥም፡፡ የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ዘሮች የሆኑት አረቦች እንኳን አላህን በመፍራት ቢሆን እንጂ አጀሞችን (ከአረብ ውጭ) ያሉትን አይበልጡም፡፡ ለዚህም የሰው ልጆች ሁሉ ፈርጥ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “አረብ በአጀም (ከአረብ ውጭ ባሉ ሰዎች) ላይ ብልጫ የለውም” ብለዋል፡፡
አላህ እንደነገረን
إِنَّ أَكْرَمَكُمْ عِندَ ٱللَّهِ أَتْقَىٰكُمْ
አላህ ዘንድ በላጫችሁ በጣም አላህን ፈሪያችሁ ነው፡፡
የአላህ ባሪያዎች ሆይ! ዘረኝነት ከሺርክና ቢድኣ ቀጥሎ ነቀርሳ ሆኖ እየወጋን ይገኛል፡፡ ይህን መልእክት በየቋንቋችሁ እየተረጎማችሁ ለሁሉም በማድረስ ተባበሩኝ፡፡
አላህ ሆይ! ዘረኝነትን ከመካከላችን አስወግድልም፡፡ ኢስላምን ከዘራቸው የሚያስቀድሙ ምርጥ ትውልዶች አድርገን፡፡
የአላህ ሰላትና ሰላም ዘረኝነትን አጥፍተው እርስ በእርስ ሲጋደሉ የነበሩትን ሰሃባዎች በሱና አንድ ባደረጉት የአላህ ውድ፣ በቤተሰቦቻቸው፣ በባልደረባዎቻቸውና ሐቅን በተከተለ ላይ ሁሉ ይሁን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
የሐበሻ ሙስሊሞች ሆይ! አላህን እንፍራ ጥምቡን ዘረኝነት ከላያችን ላይ ጨርሰን አራግፈን እንጣል፡፡
ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ሰሃባዎቻቸው ላይ ከባድ በደል፣ ስቃይ እና እንግልት ሲደርስባቸው “ሂዱ ወደ ሀበሻ” ነበር ያሉት፡፡ እኛ ሙስሊሞች ነን፡፡ የሀበሻ ሙስሊሞች የሚለው ከበቂ በላይ መታወቂያችን ነው፡፡ ዘራችንን ከኢስላም አስቀድመን እርስ በርስ እየተናናቅን መከፋፈሉ ለከባድ አደጋ ነው የሚዳርገን፡፡
አንድ ሰው በእስልምናው እንጂ በዘሩ ጀነት አይገባም፡፡ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ስራው ወደ ኋላ ያስቀረውን ሰው ዘሩ (ወደፊት) አያስቀድመውም” ብለዋል፡፡
አንድ ሰው ጀነት ለመግባት ብቸኛው መንገዱ
- ተውሒድን አሳምሮ መያዙ ከሺርክ እና ከባለቤቶቹ ሙሉ ለሙሉ መፅዳቱ፣
- የነብዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምን ሱና አጥብቆ መያዙ ቢድኣ የተባለን በጠቅላላ መራቁ፣
- የሰሃባዎችን አረዳድ መከተሉ የጥመት መንገዶችን ሁሉ መራቁ፣
- የአላህንና የመልክተኛውን ትእዛዝ መፈፀሙ እነሱንም አለማመፁ ……
- …..
እንጂ ዘሩ አይደለም፡፡
ዘር ለመተዋወቅ ብቻ እንጅ ለሌላ አይደለም፡፡ እውነቱን ለፈለጉ ሰዎች አላህ እንዲህ ይላል
يَٰٓأَيُّهَا ٱلنَّاسُ إِنَّا خَلَقْنَٰكُم مِّن ذَكَرٍ وَأُنثَىٰ وَجَعَلْنَٰكُمْ شُعُوبًا وَقَبَآئِلَ لِتَعَارَفُوٓا۟ ۚ إِنَّ أَكْرَمَكُمْ عِندَ ٱللَّهِ أَتْقَىٰكُمْ ۚ إِنَّ ٱللَّهَ عَلِيمٌ خَبِيرٌ
እናንተ ሰዎች ሆይ! እኛ ከወንድና ከሴት ፈጠርናችሁ፡፡ እንድትተዋወቁም ጎሳዎችና ነገዶች አደረግናችሁ፡፡ አላህ ዘንድ በላጫችሁ በጣም አላህን ፈሪያችሁ ነው፡፡ አላህ ግልጽን ዐዋቂ ውስጥንም ዐዋቂ ነው፡፡
አላህ በግልፅ እውነታውን ነግሮናል፡፡
ዘረኞች፣ ዘራቸውን ከኢስላም የሚያስቀድሙ ጥምብ አንሳዎች ናቸው፡፡
ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ዘረኝነት ጥምብ ናት፡፡ ተዋት፡፡” እያሉን የነብዩን (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ትእዛዝ ትተው እሳቸው የከለከሉትን የሚያነሱ ጥምብ አንሳዎች ናቸው፡፡
የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “….ተዋት” ብለው ጥንቡን ዘረኝነት እንድንተው ሲነግሩን አይ አልተውም ብሎ ከእስልምና ዘሩን አስቀድሞ ሙስሊም የሆነ ከእሱ ዘር ያልሆነው ላይ አደጋ ሊያደርስ፣ ንብረቱን ሊቀማ የሚያስብ ሰው ምንኛ ከሰረ፡፡
የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ሁለት ሙስሊሞች ሰይፍ አይማዘዙም ገዳይም ተገዳይም የእሳት ናቸው” ሲሉ
ሰሃባዎች “ገዳይስ ገድሎ ነው” ተገዳይስ ሲሉ ጠየቁ
የአላህ መልክተኛም (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “እሱም ንያ ነበረው” ሲሉ እነዚህ ሰዎች የሚሰሩትን ስራ የእሳት መንገድ እንደሆነ ገለፁ፡፡
ኢስላም ለሁሉም ነገር ዝርዝር የሆነ መተዳደሪያ ያለው፣ ለሁሉም ዘመን፣ ለሁሉም ቦታ፣ ለሁሉም ትውልድ ሙሉና ከበቂ በላይ የሆነ አላህ የሚቀበለው ብቸኛ ሃይማኖት ነው፡፡
ውቡ ኢስላም እርስ በእርስ መጋደላችንን. መበዳደላችንን አጥብቆ ኮንኖታል፡፡
ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “አንድ ሙስሊም ለአንድ ሙስሊም ወንድሙ ነው፡፡ አይበድለው….” ብለዋል፡፡ ታድያ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “አይበድለው” እያሉ ዘሩ ስላልሆነ ብቻ ሌሎች ሙስሊሞችን ሊገድል የተነሳው ምን ሊባል ነው?
አላህ ይድረስልን፡፡ ከዚህ ቆሻሻ ተግባርም ይጠብቀን፡፡
የሀበሻ ሙስሊሞች ሆይ! ሙስሊም የሆነ ሰው እኛ ዘንድ እንደራሳችን አድርገን ልንወደው ይገባል፡፡ ሙስሊም ደሙም፣ ገንዘቡም፣ ክብሩም የተጠበቀ ነው፡፡ ልብ ያለው ልብ ይበል፡፡
የሀበሻ ሙስሊሞች ሆይ! አላህን እንፍራ ዘረኝነትን ከላያችን ላይ እናራግፍ፡፡ ማንም ማንንም በዘሩ አይበልጥም፡፡ የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ዘሮች የሆኑት አረቦች እንኳን አላህን በመፍራት ቢሆን እንጂ አጀሞችን (ከአረብ ውጭ) ያሉትን አይበልጡም፡፡ ለዚህም የሰው ልጆች ሁሉ ፈርጥ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “አረብ በአጀም (ከአረብ ውጭ ባሉ ሰዎች) ላይ ብልጫ የለውም” ብለዋል፡፡
አላህ እንደነገረን
إِنَّ أَكْرَمَكُمْ عِندَ ٱللَّهِ أَتْقَىٰكُمْ
አላህ ዘንድ በላጫችሁ በጣም አላህን ፈሪያችሁ ነው፡፡
የአላህ ባሪያዎች ሆይ! ዘረኝነት ከሺርክና ቢድኣ ቀጥሎ ነቀርሳ ሆኖ እየወጋን ይገኛል፡፡ ይህን መልእክት በየቋንቋችሁ እየተረጎማችሁ ለሁሉም በማድረስ ተባበሩኝ፡፡
አላህ ሆይ! ዘረኝነትን ከመካከላችን አስወግድልም፡፡ ኢስላምን ከዘራቸው የሚያስቀድሙ ምርጥ ትውልዶች አድርገን፡፡
የአላህ ሰላትና ሰላም ዘረኝነትን አጥፍተው እርስ በእርስ ሲጋደሉ የነበሩትን ሰሃባዎች በሱና አንድ ባደረጉት የአላህ ውድ፣ በቤተሰቦቻቸው፣ በባልደረባዎቻቸውና ሐቅን በተከተለ ላይ ሁሉ ይሁን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
በኢስላም ሸይኽም ይሁን ነብይ ሞተ ተብሎ የሙት አመት አይከበርለትም፡፡ ማንም ይስራው ማን፣ ለማንም ይሰራ ለማን
“የሙት አመት”
የሚባል ነገር የለም፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
“የሙት አመት”
የሚባል ነገር የለም፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
የኢስላም አስተማሪዎች፣ የመስጂድ ኸጢቦች፣ ሽማግሌዎች ሃላፍትናችሁን ተወጡ፡፡
“የኛሰው”፣ “ነመኬኛ”፣ “የባድ ወልድ” …. ብለን የምንጠራው ማንን ነው?
አንድን ሰው የእኛ ዘርም ባይሆን ሙስሊም እስከሆነ ድረስ አማራው “የኛሰው”፣ ኦሮሞው “ነመኬኛ”፣ ስልጤው “የባድ ወልድ” …… ብለን መጥራት እስካልቻልን ድረስ አደጋ ውስጥ ነን፡፡
የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ሙስሊም የሙስሊም ወንድሙ ነው፡፡” ብለዋል፡፡ ዛሬ ሰይጣን እና ሰራዊቶቹ ባጠመዱላቸው ወጥመድ ውስጥ ገብተው ለዘራቸው ሲሉ ላኢላሃኢለላህ ብለው ሲያበቁ እርስ በእርስ የሚጋደሉ፣ በመጥፎ የሚፈላለጉ፣ ሰው ሲሞት ሁሉ የእድር እቃ አንሰጥም የሚሉ አውሬዎች አሉ፡፡ አላህ ሁላችንንም ልብ ይስጠን፡፡ የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ሁለት ሙስሊሞች ሰይፍ አይማዘዙም ሁለትሙ የእሳት ናቸው” ብለው ነግረውን ሲያበቁ፡፡ የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ይህን ጥንብ ዘረኝነት “ተዉቱ” እያሉ፣ እሳቸው የከለከሉት ዘረኝነት አንተውም ብለው ታላቋን የምስክረት ቃል “ከአላህ በስተቀር በሐቅ የሚመለክ አምላክ እንደሌለ እመሰክራለሁ፡፡ ሙሐመድም የአላህ መልክተኛ መሆናቸውን እንዲሁ እመሰክራለሁ” ያሉ ሰዎች እርስ በእርስ ሲጋደሉ እንደማየት አስለቃሽና ልብ የሚያደማ ነገር የለም፡፡
ከማንም በላይ ሃላፍትና ያለባቸው የሃይማኖቱ አስተማሪዎች፣ ኢማሞች፣ ዱአቶች፣ ሽማግሌዎች፣ ኢስላማዊ ቻናሎችና ሬድዬኖች ናቸው፡፡ በጣም በሚያሳዝን ሁኔታ ኡመተል ኢስላም እርስ በእርስ እንዲህ እየተገዳደለ አላህ ካዘነላቸው በጣም ጥቂቶች ውጭ አብዛኛዎቹ አዋቂ ተብየዎች ዝምታን መርጠዋል፡፡ አላህን ብትፈሩ አይሻልም ወይ? አላህ አያያዙ የበረታ ነው፡፡ ኡለማዎች ሐቅን ማብራራትና አለመደበቅ ነው ያለባቸው፡፡ አላህ እንዲህ ይላል
وَإِذْ أَخَذَ ٱللَّهُ مِيثَٰقَ ٱلَّذِينَ أُوتُوا۟ ٱلْكِتَٰبَ لَتُبَيِّنُنَّهُۥ لِلنَّاسِ وَلَا تَكْتُمُونَهُۥ فَنَبَذُوهُ وَرَآءَ ظُهُورِهِمْ وَٱشْتَرَوْا۟ بِهِۦ ثَمَنًا قَلِيلًا ۖ فَبِئْسَ مَا يَشْتَرُونَ
አላህ የነዚያን መጽሐፉን የተሰጡትን ቃል ኪዳን ለሰዎች በእርግጥ ታብራሩታላችሁ አትደብቁትምም በማለት የያዘባቸውን (አስታውሱ)፡፡ በጀርባዎቻቸውም ኋላ ጣሉት፡፡ በርሱም ጥቂትን ዋጋ ገዙ፡፡ የሚገዙትም ነገር ከፋ!
ኡመቱ እርስ በእርስ ሲባላ እያዩ ተው አለማለት ምን የሚሉት ነው?
ዘረኝነት ውስጥ ገብታችሁ የተነሱ እሳቶች ላይ ቢንዚል የምታርከፈክፉ ሰዎች የጥፋታችሁን ልክ ላትገነዘቡት ትችላላችሁ፡፡ ግን ልብ በሉ የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “አንድ አማኝ ያለ አግባብ ከሚሞት ካእባ ቢወገድ ይሻላል” ሁሉ ብለዋል፡፡ መቼ ይሆን የምንመከረው? አላህና መልክተኛው (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል እየተባልን ልባችን ከድንጋይ በላይ ደርቆ የነሱን ቃል አልቀበልም ብለን ስሜታችንን ጋልበን መጨረሻን ምን ይሆናል ብለን እንገምታለን?
አረ አላህን እንፍራ፡፡ ከባድ የሆነ አዘቅት ውስጥ እንዳንገባ፡፡ ተወደደም ተጠላም ማንኛውም አይነት ችግር ይበልጥ ጎጂነቱ ለሙስሊሙ ነው፡፡ አእምሮ ያለው ልብ ይበል፡፡
አላህ ሆይ! ከሺርክ፣ ቢድኣ፣ ዘረኝነት የፀዳ እውነተኛ አንድነት ስጠን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
“የኛሰው”፣ “ነመኬኛ”፣ “የባድ ወልድ” …. ብለን የምንጠራው ማንን ነው?
አንድን ሰው የእኛ ዘርም ባይሆን ሙስሊም እስከሆነ ድረስ አማራው “የኛሰው”፣ ኦሮሞው “ነመኬኛ”፣ ስልጤው “የባድ ወልድ” …… ብለን መጥራት እስካልቻልን ድረስ አደጋ ውስጥ ነን፡፡
የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ሙስሊም የሙስሊም ወንድሙ ነው፡፡” ብለዋል፡፡ ዛሬ ሰይጣን እና ሰራዊቶቹ ባጠመዱላቸው ወጥመድ ውስጥ ገብተው ለዘራቸው ሲሉ ላኢላሃኢለላህ ብለው ሲያበቁ እርስ በእርስ የሚጋደሉ፣ በመጥፎ የሚፈላለጉ፣ ሰው ሲሞት ሁሉ የእድር እቃ አንሰጥም የሚሉ አውሬዎች አሉ፡፡ አላህ ሁላችንንም ልብ ይስጠን፡፡ የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ሁለት ሙስሊሞች ሰይፍ አይማዘዙም ሁለትሙ የእሳት ናቸው” ብለው ነግረውን ሲያበቁ፡፡ የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ይህን ጥንብ ዘረኝነት “ተዉቱ” እያሉ፣ እሳቸው የከለከሉት ዘረኝነት አንተውም ብለው ታላቋን የምስክረት ቃል “ከአላህ በስተቀር በሐቅ የሚመለክ አምላክ እንደሌለ እመሰክራለሁ፡፡ ሙሐመድም የአላህ መልክተኛ መሆናቸውን እንዲሁ እመሰክራለሁ” ያሉ ሰዎች እርስ በእርስ ሲጋደሉ እንደማየት አስለቃሽና ልብ የሚያደማ ነገር የለም፡፡
ከማንም በላይ ሃላፍትና ያለባቸው የሃይማኖቱ አስተማሪዎች፣ ኢማሞች፣ ዱአቶች፣ ሽማግሌዎች፣ ኢስላማዊ ቻናሎችና ሬድዬኖች ናቸው፡፡ በጣም በሚያሳዝን ሁኔታ ኡመተል ኢስላም እርስ በእርስ እንዲህ እየተገዳደለ አላህ ካዘነላቸው በጣም ጥቂቶች ውጭ አብዛኛዎቹ አዋቂ ተብየዎች ዝምታን መርጠዋል፡፡ አላህን ብትፈሩ አይሻልም ወይ? አላህ አያያዙ የበረታ ነው፡፡ ኡለማዎች ሐቅን ማብራራትና አለመደበቅ ነው ያለባቸው፡፡ አላህ እንዲህ ይላል
وَإِذْ أَخَذَ ٱللَّهُ مِيثَٰقَ ٱلَّذِينَ أُوتُوا۟ ٱلْكِتَٰبَ لَتُبَيِّنُنَّهُۥ لِلنَّاسِ وَلَا تَكْتُمُونَهُۥ فَنَبَذُوهُ وَرَآءَ ظُهُورِهِمْ وَٱشْتَرَوْا۟ بِهِۦ ثَمَنًا قَلِيلًا ۖ فَبِئْسَ مَا يَشْتَرُونَ
አላህ የነዚያን መጽሐፉን የተሰጡትን ቃል ኪዳን ለሰዎች በእርግጥ ታብራሩታላችሁ አትደብቁትምም በማለት የያዘባቸውን (አስታውሱ)፡፡ በጀርባዎቻቸውም ኋላ ጣሉት፡፡ በርሱም ጥቂትን ዋጋ ገዙ፡፡ የሚገዙትም ነገር ከፋ!
ኡመቱ እርስ በእርስ ሲባላ እያዩ ተው አለማለት ምን የሚሉት ነው?
ዘረኝነት ውስጥ ገብታችሁ የተነሱ እሳቶች ላይ ቢንዚል የምታርከፈክፉ ሰዎች የጥፋታችሁን ልክ ላትገነዘቡት ትችላላችሁ፡፡ ግን ልብ በሉ የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “አንድ አማኝ ያለ አግባብ ከሚሞት ካእባ ቢወገድ ይሻላል” ሁሉ ብለዋል፡፡ መቼ ይሆን የምንመከረው? አላህና መልክተኛው (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል እየተባልን ልባችን ከድንጋይ በላይ ደርቆ የነሱን ቃል አልቀበልም ብለን ስሜታችንን ጋልበን መጨረሻን ምን ይሆናል ብለን እንገምታለን?
አረ አላህን እንፍራ፡፡ ከባድ የሆነ አዘቅት ውስጥ እንዳንገባ፡፡ ተወደደም ተጠላም ማንኛውም አይነት ችግር ይበልጥ ጎጂነቱ ለሙስሊሙ ነው፡፡ አእምሮ ያለው ልብ ይበል፡፡
አላህ ሆይ! ከሺርክ፣ ቢድኣ፣ ዘረኝነት የፀዳ እውነተኛ አንድነት ስጠን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
ስለ ሰሞኑን ከባድ ብርድ እስልምና ምን ይላል፡፡
የአላህ ባርያዎች ሆይ! አሁንም አረፈደም ንሰሃ እንግባ
ኢስላም የነብያት ሁሉ ሀይማኖት ነው፡፡ እንደሚታወቀው በሀይለኛ ሙቀት እና በሀይለኛ ብርድ ሰው ተቸግሯል፡፡ ይህም ከመሆኑ ጋር ለአላህ ካጠፋነው ጥፋቶች ንሰሀ ከመግባት ይልቅ በየዜና አውታሩ “የአለም በረዶ ስለቀለጠ ነው፣ ዛፎች በመቆረጣቸው ነው፣ ኦዞን በመሳሳቱ ነው…..” እና የመሳሰሉትን ምክንያቶች ናቸው እየተባለ ይለፈፋል፡፡
እስቲ የነብያት ሁሉ መደምደሚያ ነብዩ ሙሐመድ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ምን እንደሚሉ እንይ
አቡ ሁረይራ (ረድየላሁ አንሁ) ባስተላለፉት፣ ኡማሙ አል-ቡኻሪ በዘገቡት ትክክለኛ ሀዲስ ላይ የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ
“ጀሀነም (እሳት) ወደ ጌታዋ ስሞታ አቀረበች፡፡ ከፊሌ ከፊሌን በላው አለች፡፡ አላህ ሁለት ጊዜ እስትንፋስን ፈቀደላት፡፡ አንደኛው በቀዝቃዜ ወራት ሌላኛው ጊዜ በሙቀት ወራት፡፡ በሙቀት ጊዜ የምታገኙት ከባድ ሙቀት እና በቅዝቃዜ ጊዜ የምታገኙት ከባድ ውርጭ (ቅዝቃዜ፣ ቀቅ) (ናቸው)፡፡”
حَدَّثَنَا أَبُو الْيَمَانِ، أَخْبَرَنَا شُعَيْبٌ، عَنِ الزُّهْرِيِّ، قَالَ حَدَّثَنِي أَبُو سَلَمَةَ بْنُ عَبْدِ الرَّحْمَنِ، أَنَّهُ سَمِعَ أَبَا هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ يَقُولُ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم " اشْتَكَتِ النَّارُ إِلَى رَبِّهَا، فَقَالَتْ رَبِّ أَكَلَ بَعْضِي بَعْضًا، فَأَذِنَ لَهَا بِنَفَسَيْنِ نَفَسٍ فِي الشِّتَاءِ وَنَفَسٍ فِي الصَّيْفِ، فَأَشَدُّ مَا تَجِدُونَ فِي الْحَرِّ، وَأَشَدُّ مَا تَجِدُونَ مِنَ الزَّمْهَرِيرِ ".
ልብ እንበል ከባዱም ሙቀት እና ከባዱም ብርድ የአዋቂዎች ሁሉ አዋቂ፣ የአላህን ፈሪዎች ሁሉ ፈሪ፣ የነብያት ሁሉ መደምደሚያ እንደነገሩን የጀሃነም እሳት የምትተነፍሰው ሁለት ትንፋሽ ምክንያት ነው፡፡
ሌላው መገንዘብ ያለብን ነገር እስልምና ሙሉ መሆኑን ለማንኛውም አለም ላይ ላለ ክስተት በል እንዲያውም ለሚቀጥለው አለም ጉዳዩች፣ የሚቀጥለው አለም ላይ ምን እንደሚከሰት በዝርዝር እና በጥቅል የተናገር ዉድ፣ ልዩ፣ የማይበረዝ፣ የማይሰረዝ፣ የማይደለዝ፣ ዘመን የማያልፍበት ሀይማኖት ነውና አጥብቀን እንያዘው፡፡ ይሀው ተመልከቱ አከም “Econmic Crisese” ኢኮኖሚክ ክራይስስ ብለው ሲያወሩ አላህ ጥንትም የወለድ መጨረሻው ይህ መሆኑን ነግሮን ነበር፡፡
ትዳር እንዲመሰረት እና ከዝሙት እንድንታቀብ ከጥንትም የነብያት ሁሉ ሀይማኖት መክሮ ነበር፡፡ ግን ይህን አልሰማ ብለው አሁን አለም ላለችበት ከባባድ በሽታዎች ተዳርገዋል፡፡
በሁሉም የህይወት ዘርፍ ላይ የጥንት የጠዋቱ ኢስላም (ሰለፍያ) በሄደበት መንገድ መሄድ ብቻና ብቻ ነው ዋስትናው፡፡ ሁለት ሃቅ የለም፡፡ ሁሉም ሙስሊም ከጥመት ቡድኖች እርቆ ወደ ብቸኛዋ አማራጭ እና ሁለተኛ ወደሌላት ሃቅ ጎዳና፣ ሰለፉነ ሷሊሂን የተጓዙባት ጎዳና መመለስ ግድ ይለዋል፡፡ አለበለዚያ በሙስሊሙ አለም ላይ እንዳየነው አሁንም ከባድ ኪሳራ ይከሰታል፡፡
ታድያ ምን ይበጀን?
አማኞች ወደ ጌታቸው በንሰሃ ሊመለሱ፣ ያችን “ጭማሪ አለን?” ብላ የምትጠይቀውን ጀሀነም ከሷ ጌታችን እንዲጠብቀን እሱን ዘውትር መለመን ግድ ይለናል፡፡ የአላህ ባርያዎች ሆይ! አሁንም አረፈደም ንሰሃ እንግባ፡፡ አላህ እነዚህን ሁሉ ተዓምራት የሚያሳየን በሰጠን አእምሮ የሱን ጌትነት፣ በቸኛ ተመላኪነት አውቀን ወደሱ እንድንመለስ ነው፡፡
አላህ ሆይ! ሁሌ ወዳንተ በጸጸት ከሚመለሱት አድርገን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
የአላህ ባርያዎች ሆይ! አሁንም አረፈደም ንሰሃ እንግባ
ኢስላም የነብያት ሁሉ ሀይማኖት ነው፡፡ እንደሚታወቀው በሀይለኛ ሙቀት እና በሀይለኛ ብርድ ሰው ተቸግሯል፡፡ ይህም ከመሆኑ ጋር ለአላህ ካጠፋነው ጥፋቶች ንሰሀ ከመግባት ይልቅ በየዜና አውታሩ “የአለም በረዶ ስለቀለጠ ነው፣ ዛፎች በመቆረጣቸው ነው፣ ኦዞን በመሳሳቱ ነው…..” እና የመሳሰሉትን ምክንያቶች ናቸው እየተባለ ይለፈፋል፡፡
እስቲ የነብያት ሁሉ መደምደሚያ ነብዩ ሙሐመድ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ምን እንደሚሉ እንይ
አቡ ሁረይራ (ረድየላሁ አንሁ) ባስተላለፉት፣ ኡማሙ አል-ቡኻሪ በዘገቡት ትክክለኛ ሀዲስ ላይ የአላህ መልክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እንዲህ አሉ
“ጀሀነም (እሳት) ወደ ጌታዋ ስሞታ አቀረበች፡፡ ከፊሌ ከፊሌን በላው አለች፡፡ አላህ ሁለት ጊዜ እስትንፋስን ፈቀደላት፡፡ አንደኛው በቀዝቃዜ ወራት ሌላኛው ጊዜ በሙቀት ወራት፡፡ በሙቀት ጊዜ የምታገኙት ከባድ ሙቀት እና በቅዝቃዜ ጊዜ የምታገኙት ከባድ ውርጭ (ቅዝቃዜ፣ ቀቅ) (ናቸው)፡፡”
حَدَّثَنَا أَبُو الْيَمَانِ، أَخْبَرَنَا شُعَيْبٌ، عَنِ الزُّهْرِيِّ، قَالَ حَدَّثَنِي أَبُو سَلَمَةَ بْنُ عَبْدِ الرَّحْمَنِ، أَنَّهُ سَمِعَ أَبَا هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ يَقُولُ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم " اشْتَكَتِ النَّارُ إِلَى رَبِّهَا، فَقَالَتْ رَبِّ أَكَلَ بَعْضِي بَعْضًا، فَأَذِنَ لَهَا بِنَفَسَيْنِ نَفَسٍ فِي الشِّتَاءِ وَنَفَسٍ فِي الصَّيْفِ، فَأَشَدُّ مَا تَجِدُونَ فِي الْحَرِّ، وَأَشَدُّ مَا تَجِدُونَ مِنَ الزَّمْهَرِيرِ ".
ልብ እንበል ከባዱም ሙቀት እና ከባዱም ብርድ የአዋቂዎች ሁሉ አዋቂ፣ የአላህን ፈሪዎች ሁሉ ፈሪ፣ የነብያት ሁሉ መደምደሚያ እንደነገሩን የጀሃነም እሳት የምትተነፍሰው ሁለት ትንፋሽ ምክንያት ነው፡፡
ሌላው መገንዘብ ያለብን ነገር እስልምና ሙሉ መሆኑን ለማንኛውም አለም ላይ ላለ ክስተት በል እንዲያውም ለሚቀጥለው አለም ጉዳዩች፣ የሚቀጥለው አለም ላይ ምን እንደሚከሰት በዝርዝር እና በጥቅል የተናገር ዉድ፣ ልዩ፣ የማይበረዝ፣ የማይሰረዝ፣ የማይደለዝ፣ ዘመን የማያልፍበት ሀይማኖት ነውና አጥብቀን እንያዘው፡፡ ይሀው ተመልከቱ አከም “Econmic Crisese” ኢኮኖሚክ ክራይስስ ብለው ሲያወሩ አላህ ጥንትም የወለድ መጨረሻው ይህ መሆኑን ነግሮን ነበር፡፡
ትዳር እንዲመሰረት እና ከዝሙት እንድንታቀብ ከጥንትም የነብያት ሁሉ ሀይማኖት መክሮ ነበር፡፡ ግን ይህን አልሰማ ብለው አሁን አለም ላለችበት ከባባድ በሽታዎች ተዳርገዋል፡፡
በሁሉም የህይወት ዘርፍ ላይ የጥንት የጠዋቱ ኢስላም (ሰለፍያ) በሄደበት መንገድ መሄድ ብቻና ብቻ ነው ዋስትናው፡፡ ሁለት ሃቅ የለም፡፡ ሁሉም ሙስሊም ከጥመት ቡድኖች እርቆ ወደ ብቸኛዋ አማራጭ እና ሁለተኛ ወደሌላት ሃቅ ጎዳና፣ ሰለፉነ ሷሊሂን የተጓዙባት ጎዳና መመለስ ግድ ይለዋል፡፡ አለበለዚያ በሙስሊሙ አለም ላይ እንዳየነው አሁንም ከባድ ኪሳራ ይከሰታል፡፡
ታድያ ምን ይበጀን?
አማኞች ወደ ጌታቸው በንሰሃ ሊመለሱ፣ ያችን “ጭማሪ አለን?” ብላ የምትጠይቀውን ጀሀነም ከሷ ጌታችን እንዲጠብቀን እሱን ዘውትር መለመን ግድ ይለናል፡፡ የአላህ ባርያዎች ሆይ! አሁንም አረፈደም ንሰሃ እንግባ፡፡ አላህ እነዚህን ሁሉ ተዓምራት የሚያሳየን በሰጠን አእምሮ የሱን ጌትነት፣ በቸኛ ተመላኪነት አውቀን ወደሱ እንድንመለስ ነው፡፡
አላህ ሆይ! ሁሌ ወዳንተ በጸጸት ከሚመለሱት አድርገን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
https://t.me/abdurrahmanorg
Authentic Islamic knowledge. Updates from AbdurRahman.Org related websites and beneficial reminders
Authentic Islamic knowledge. Updates from AbdurRahman.Org related websites and beneficial reminders
Telegram
AbdurRahmanOrg
Authentic Islamic knowledge. Updates from AbdurRahman.Org related websites and beneficial reminders
የት በደረሱ ነበር?
አላህ ካዘነላቸው ጥቂቶች ውጭ ስለ ግል ጉዳያቸው፣ ስለ ዘራቸው፣ ስለ መብታቸው ደም ስራቸው እስኪገተር ድረስ የሚቆጡ፣ የሚከራከሩ፣ የሚያብራሩ ሰዎችን ታያለህ፡፡ ነገር ግን ሺርክ (በአላህ ላይ ሲጋራ)፣ ቢድኣ (የነብዩ(ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ሱና ላይ ሲጨመር ሲቀነስ) እያ ዝም ሲሉ ትመለከታቸዋለህ፡፡ ለራሳቸው የተቆጡትን ቁጣ ሺርክና ቢድኣን ሲያዩ ያንን ቁጣ አታይባቸውም፡፡ ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂኡን፡፡ ከዚህ የበለጠ ዝቅጠት ምን አለ? የአላህ መብት ሲነካ ሌሎች ጉዳዬች ላይ እንደሚያንዘረዝረን ቢያንዘፈዝፈን፣ ቢዘገንነን፣ ብንቆጣ የት በደረስን ነበር?
አላህ ሆይ! ያንተን መብት ከሚያከብሩና ከሚያስከብሩ ትውልዶች አድርገን፡፡ ውስጥ እላያችንንም አሳምርልን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
አላህ ካዘነላቸው ጥቂቶች ውጭ ስለ ግል ጉዳያቸው፣ ስለ ዘራቸው፣ ስለ መብታቸው ደም ስራቸው እስኪገተር ድረስ የሚቆጡ፣ የሚከራከሩ፣ የሚያብራሩ ሰዎችን ታያለህ፡፡ ነገር ግን ሺርክ (በአላህ ላይ ሲጋራ)፣ ቢድኣ (የነብዩ(ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ሱና ላይ ሲጨመር ሲቀነስ) እያ ዝም ሲሉ ትመለከታቸዋለህ፡፡ ለራሳቸው የተቆጡትን ቁጣ ሺርክና ቢድኣን ሲያዩ ያንን ቁጣ አታይባቸውም፡፡ ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂኡን፡፡ ከዚህ የበለጠ ዝቅጠት ምን አለ? የአላህ መብት ሲነካ ሌሎች ጉዳዬች ላይ እንደሚያንዘረዝረን ቢያንዘፈዝፈን፣ ቢዘገንነን፣ ብንቆጣ የት በደረስን ነበር?
አላህ ሆይ! ያንተን መብት ከሚያከብሩና ከሚያስከብሩ ትውልዶች አድርገን፡፡ ውስጥ እላያችንንም አሳምርልን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
የአላህን መብቶች ያሟላን ጊዜ የእኛም መብቶች ይሟላሉ፡፡
የፈጣሪን መብት ሳናሟላ ፍጡራን መብቶቻችንን አያሟሉልንም፡፡
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem
https://t.me/SadatTextPosts
የፈጣሪን መብት ሳናሟላ ፍጡራን መብቶቻችንን አያሟሉልንም፡፡
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem
https://t.me/SadatTextPosts
ታላቁ በደል ለምን ያህል ዘመን?
በአላህ ስም እጅግ በጣም አዛኝ እጅግ በጣም ሩህሩህ፡፡ የአላህ ሰላትና ሰላም በመልክተኞች ሁሉ መደምደሚያ፣ በቤተሰቦቻቸውና ሀቅን በተከተለ ላይ ሁሉ ይሁን፡፡
የዛሬው አርእስት ልብ የሚያደማ ነው፡፡ አላህ መቼም ከናታችን ሆድ ስንወጣ ምንም የማናውቅ የነበርን ብንሆንም፣ መስሚያን፣ መመልከቻን ልቦናንን አድርጎልናል፡፡ የመልክተኞች ሁሉ ኢማም የሆኑትን ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምን) ላከልን፡፡ ቁርኣንን አወረደልን፡፡ ምስጋና ሁሉ ጥራት ለተገባው አላህ ይሁን፡፡ መቼም ይህን ሁሉ አድርጎልን ሀቁን ከባጢሉ ታላቁን በደል ከታላቁ በደል በታች ካሉት ለይተን ማወቂያ አእምሮን ሰጥቶናል፡፡
እኛ ሀበሾች ከማንም በፊት የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ጥርት ያለች ጥሪ እንደደረሰን ይታወቃል፡፡ ታድያ የበደሎች ሁሉ በደል ምን እንደሆነ ኢስላም ነግሮናል አልነገረንም? ነግሮናል እንጂ
አላህ እንዲህ ይላል
وَإِذْ قَالَ لُقْمَٰنُ لِٱبْنِهِۦ وَهُوَ يَعِظُهُۥ يَٰبُنَىَّ لَا تُشْرِكْ بِٱللَّهِ ۖ إِنَّ ٱلشِّرْكَ لَظُلْمٌ عَظِيمٌ
ሉቅማንም ለልጁ እርሱ የሚገሥጸው ሲኾን «ልጄ ሆይ! በአላህ (ጣዖትን) አታጋራ፡፡ ማጋራት ታላቅ በደል ነውና» ያለውን (አስታውስ)፡፡
አላህ ይሀው በግልፅ እንደነገረን ታላቁ በደል በእሱ ላይ ማንንም ይሁን ምንንም ማጋራት ነው፡፡ ሀገራችንንም ላይ ይሁን አለም ላይ በአላህ ላይ ሺርክን በመፈፀም ታላቁ በደል ይሰራል፡፡ ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂኡን፡፡
ታላቁ በደል (ሺርክ) ሁለት አገር ያጨልማል፡፡ የታላቁ በደል ተቃራኒ አላህን በብቸኝነት ማምለክ ነው፡፡ አላህን በብቸኝነት ማምለክ (ተውሒድ) የፍትሆች ሁሉ ፍትህ ነው፡፡ ሁለት ሀገር ለስኬት ያበቃል፡፡
የአላህን መብት እናሟላ የእኛም መብቶች እንዲሟሉልን፡፡ በሁለት ሀገር ስኬታማ እንድንሆን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
በአላህ ስም እጅግ በጣም አዛኝ እጅግ በጣም ሩህሩህ፡፡ የአላህ ሰላትና ሰላም በመልክተኞች ሁሉ መደምደሚያ፣ በቤተሰቦቻቸውና ሀቅን በተከተለ ላይ ሁሉ ይሁን፡፡
የዛሬው አርእስት ልብ የሚያደማ ነው፡፡ አላህ መቼም ከናታችን ሆድ ስንወጣ ምንም የማናውቅ የነበርን ብንሆንም፣ መስሚያን፣ መመልከቻን ልቦናንን አድርጎልናል፡፡ የመልክተኞች ሁሉ ኢማም የሆኑትን ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምን) ላከልን፡፡ ቁርኣንን አወረደልን፡፡ ምስጋና ሁሉ ጥራት ለተገባው አላህ ይሁን፡፡ መቼም ይህን ሁሉ አድርጎልን ሀቁን ከባጢሉ ታላቁን በደል ከታላቁ በደል በታች ካሉት ለይተን ማወቂያ አእምሮን ሰጥቶናል፡፡
እኛ ሀበሾች ከማንም በፊት የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ጥርት ያለች ጥሪ እንደደረሰን ይታወቃል፡፡ ታድያ የበደሎች ሁሉ በደል ምን እንደሆነ ኢስላም ነግሮናል አልነገረንም? ነግሮናል እንጂ
አላህ እንዲህ ይላል
وَإِذْ قَالَ لُقْمَٰنُ لِٱبْنِهِۦ وَهُوَ يَعِظُهُۥ يَٰبُنَىَّ لَا تُشْرِكْ بِٱللَّهِ ۖ إِنَّ ٱلشِّرْكَ لَظُلْمٌ عَظِيمٌ
ሉቅማንም ለልጁ እርሱ የሚገሥጸው ሲኾን «ልጄ ሆይ! በአላህ (ጣዖትን) አታጋራ፡፡ ማጋራት ታላቅ በደል ነውና» ያለውን (አስታውስ)፡፡
አላህ ይሀው በግልፅ እንደነገረን ታላቁ በደል በእሱ ላይ ማንንም ይሁን ምንንም ማጋራት ነው፡፡ ሀገራችንንም ላይ ይሁን አለም ላይ በአላህ ላይ ሺርክን በመፈፀም ታላቁ በደል ይሰራል፡፡ ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂኡን፡፡
ታላቁ በደል (ሺርክ) ሁለት አገር ያጨልማል፡፡ የታላቁ በደል ተቃራኒ አላህን በብቸኝነት ማምለክ ነው፡፡ አላህን በብቸኝነት ማምለክ (ተውሒድ) የፍትሆች ሁሉ ፍትህ ነው፡፡ ሁለት ሀገር ለስኬት ያበቃል፡፡
የአላህን መብት እናሟላ የእኛም መብቶች እንዲሟሉልን፡፡ በሁለት ሀገር ስኬታማ እንድንሆን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
ሐቅን መደበቅ ከባድ አደጋ ነው፡፡
አላህ እንዲህ ይላል
وَإِذْ أَخَذَ ٱللَّهُ مِيثَٰقَ ٱلَّذِينَ أُوتُوا۟ ٱلْكِتَٰبَ لَتُبَيِّنُنَّهُۥ لِلنَّاسِ وَلَا تَكْتُمُونَهُۥ فَنَبَذُوهُ وَرَآءَ ظُهُورِهِمْ وَٱشْتَرَوْا۟ بِهِۦ ثَمَنًا قَلِيلًا ۖ فَبِئْسَ مَا يَشْتَرُونَ
አላህ የነዚያን መጽሐፉን የተሰጡትን ቃል ኪዳን ለሰዎች በእርግጥ ታብራሩታላችሁ አትደብቁትምም በማለት የያዘባቸውን (አስታውሱ)፡፡ በጀርባዎቻቸውም ኋላ ጣሉት፡፡ በርሱም ጥቂትን ዋጋ ገዙ፡፡ የሚገዙትም ነገር ከፋ!
https://t.me/SadatTextPosts
አላህ እንዲህ ይላል
وَإِذْ أَخَذَ ٱللَّهُ مِيثَٰقَ ٱلَّذِينَ أُوتُوا۟ ٱلْكِتَٰبَ لَتُبَيِّنُنَّهُۥ لِلنَّاسِ وَلَا تَكْتُمُونَهُۥ فَنَبَذُوهُ وَرَآءَ ظُهُورِهِمْ وَٱشْتَرَوْا۟ بِهِۦ ثَمَنًا قَلِيلًا ۖ فَبِئْسَ مَا يَشْتَرُونَ
አላህ የነዚያን መጽሐፉን የተሰጡትን ቃል ኪዳን ለሰዎች በእርግጥ ታብራሩታላችሁ አትደብቁትምም በማለት የያዘባቸውን (አስታውሱ)፡፡ በጀርባዎቻቸውም ኋላ ጣሉት፡፡ በርሱም ጥቂትን ዋጋ ገዙ፡፡ የሚገዙትም ነገር ከፋ!
https://t.me/SadatTextPosts