ካነበብነው📖📜📰🗞
647 subscribers
20 photos
1 file
63 links
በዚህ መድረክ
#ቅምሻ
#ጥቆማ
#ከታሪክ_ማህደር
#ስነ_ግጥም
#ከዚም_ከዛም እና
#ለፈገግታ ይተላለፋሉ። እናንተም እዚህ ቻናል ላይ ካነበባቹት መፅሐፍ 📖 ፣ጋዜጣ 📰 ፣ መጽሔት 🗞፣ ከተለያዩ ቦታዎች ላይ ይጠቅማል ያስተምራል የምትሉትን ወቅታዊም ሆነ ዘመን ተሻጋሪ የድሮ ስራዎችን ማካፈል ለምትፈልጉ እንዲሁም ለማንኛውም አስተያየት
🌿 @Feed_it_bot ይጠቀሙ።
Download Telegram
📓🌓 ቅምሻ 🌗📓

✟✞✟
“መስቀሉ ወዴት ነው?”

ማለት ተጀመረ። “ተፈልጎ ተገኘ” የሚል ታሪክ ከወደ መካከለኛው ምሥራቅ ተገኝቶ ወደ ግዕዝ ተተርጉሟል። ታሪኩም በግዕዝ ድርሳን መልክ፥ በስንክሳር፥ በፍትሐ ነገሥት መቅድም ተጽፎ ይገኛል። እነዚህ ምንጮች የሚናገሩት ታሪክ አንዱ ከሌላው ሰፋ ይላል እንጂ አንዱ ከሌላው አይፋለስም። ሁሉም መስቀሉን ያገኘችው የኒቂያ ጉባኤን (325 AD) የሰበሰበው የታላቁ ቆስጠንጢኖስ (የሮማው ቄሳር) እናት ንግሥት እሌኒ መሆኗን ይናገራሉ። ታሪኩን ከፍትሐ ነገሥትና ከጸሎተ ሃይማኖት (EMML70) መቅድሞች እጠቅሰዋለሁ፤
✟✞✟
ቈስጠንጢኖስ (Constantine the Great) ተወለደ። በተወለደ በ፲፬ዓመት አባቱ ንጉሥ ቊንስጣ ሞተ። እሱ ነገሠ። ፍርድ አወቀ፤ ለሰው እጅግ አነጋገሡ በጀ።ከዚያ በኋላ ቈስጠንጢኖስ በዝ ትመውዕ ፀርከ
(=ቈስጠንጢኖስ ሆይ፥ በዚህ ጠላትህን ታሸንፋለህ) የሚል በአየር ነገር አየ
(በመስቀል ታሸንፋለህ ሲለው ነው)። እናቱ እሌኒም በሕልም አየች። ሑሪ
ሀበ ሀገረ ኢየሩሳሌም ወአርእዪ መስቀሎ ለኢየሱስ ክርስቶስ (=ኢየሩሳሌም
ከተማ ሂጂና የኢየሱስ ክርስቶስን መስቀል ግለጪ) አላት። ይህንን ነገር
ለቈስጠንጢኖስ ነገረችው። እርሱም የቀደመ ነገሩን ልብ አደረገና ሂጂ አላት።
እርሷም ሄደች። ምስለ ሠራዊተ ወልዳ (=በልጇ ሠራዊት ታጅባ) ሌሊት
በፋና ገሰገሰች። መስከረም ፲፮(16) ቀን ስትሻ ስትመረምር በየሀገሩ ስታድር እስከ
ጎልጎታ ደረሰች። ከዚያ ኋላ በተቀበረበት ሀገር ደርሳ ሹሙን ቄሰ ገበዙን
አስራ ብታስመረምር እኛ ቢሆን አናውቅም ከአዕሩግ የሰማነው ግን በጉድፍ መጣያ ሲሉ ብለው ተመረመሩ፥ አሮጊት ቢመረምሩ ከበር ሜዳ ጉድፍ ነው ስትል ተመረመረች። ኋላም ቄስ አስመጽታ ጫን ዕጣን አስወገረችና
(=አስጨሰችና) ቀኖና አስያዘች። እሷም ያዘች፤ ዕጣን ቢወግሩ አየር ወጽቶ
ተመልሶ በመስቀል እራስ ላይ እንደቀስተ ደመና ተተከለ። ጢስ ከተተከለበት
ብታስምስ በ፲ ክንድ የፀጋማይ መስቀል ተገኘ። የዕውር ሰው ዓይን ቢያብሱ
አላበራም አለ። የሐንካሳ ሰው እግር ቢያብሱ አላረታም አለ፤ ለለምጻም
ቢያብሱ አላነጻም አለ፤ ለድውይ ቢያብሱ አልፈውስም አለ፤ ሙት አላነሳም አለ። ደግማችሁ ማሱ የጌታዬ መስቀል አይደለውም አለችና ደግሞ ብታስምስ በ፲ ክንድ የየማናይ መስቀል ወጻ። እንዲያው (=እንደዚያው) አልፈውስም አለ። ደግሞ ብታስምስ ፲ ክንድ ታላቅ ደንጋይ ተገኘ፤ ደንገያን አውጽቶ ደግሞ ቢምሱ ፲ ክንድ የክርስቶስ መስቀል ተገኘ። ከዚያ ኋላ አውጽተው ለሙት ቢያስነኩት ሙት አነሳ፤ ድውይ ፈወሰ፥ ለምፅ አነጻ፤ ዕውር አበራ፥ ሐንካሳ አረታ። ያነግዜ ይህ የጌታዬ መስቀል ነው አለችና ያሬድ እንዳለ የበበት ዮም እሌኒ አጽሐሰት በእገሪሃ ወጠፍሐት በእደዊሃ መስቀል ኃይልነ፥ መስቀል መድኃኒተ ነፍስነ ብላ ስትል ረገፀች ይላል።መስቀሉን ስትፈልግ ወዲያ ወዲህ እያለ ይላላካት የነበረ ይሁዳ የሚባለውን የኢየሩሳሌም ሰው አስጠምቃ ጳጳስ አስሹማ ስሙን ኪራኮስ አሰኝታ ወደሀገሯ ተመለሰች።”መስከረም ፲፮ ደመራ የምናከብረው ይኸንኑ እሌኒ (St. Helena 255-330 A.D.) መስቀሉን ያገኘችበትን ቀን ለማስታወስ ነው።

~~~ ይቀጥላል ~~~

ምንጭ፦ “የጌታ መስቀል ወደ ኢትዮጵያ መምጣት” (ጌታቸው
ኃይሌ)

እናመሠግናለን
#Coททεcт WiтhUs 👣 @Feed_it_bot

┈┈┈••✦✦••┈┈┈
@Readers_To_Know
❀꧁✤┈┈┈••✦✦••┈┈┈✤꧂❀
​​📓🌓 ቅምሻ 🌗📓

"የጌታ መስቀል ወደ ኢትዮጵያ እንዴት መጣ"

የግማደ መስቀሉ ወደኢትዮጵያ መምጣት የዚህ የመስቀል ቁራጭ (ግማደ መስቀል) ወደኢትዮጵያ መምጣት ያፍ ታሪክ አይደለም። ብዙ የታሪክ
ምንጮች መዝግበውታል። ከነዚህም ውስጥ ታሪከ ነገሥታት፤ አምባ ግሼን
(ወሎ) የሚገኘው ወንጌልና ሲኖዶስ የተጻፈበት መጽሐፈ ጤፉት፣ ገድለ
መርቆሬዎስ፣ እግዚአብሄር ነግሠ ይገኙበታል። መስቀሉ ወደኢትዮጵያ
የመጣልን በአፄ ዳዊት ዘመን ነው። (1375-1403 ዓ.ም።) የመስቀሉ
ቁራጭና ሌሎችም ቅድሳት ቅርሳት ለዳዊት የተላከለት ከግብፅ የእስላም
መንግሥት ጋራ በክርስቲያኖች መጨቆን አለመግባባት ተፈጥሮ ስለነበረ
ለመታረቂያ ነው። ንጉሥ ዳዊት ከግብፁ ጳጳስ “ተገፋዕኩ ብዙኃ…ወአኮ አነ
ባሕቲትየ ዘተገፋዕኩ አላ ኲሎሙ ጳጳሳት ወኤጲስ ቆጶሳት ወአብያተ ክርስቲያናት መኲሎሙ ምእመናን ክርስቶሳውያን በእዴሁ ለሥልጣነ ምስር =ግብፅ…” የሚል ደብዳቤ ሲደርሰው ሠራዊቱን አስከትቶ በሱዳን በኩል ገሠገሠ። ስናር ሲደርስ የግብፁ ሡልጣን ከክርስቲያኖች ጋር ታረቀ። ሌላ ደብዳቤ መጣ። ገድለ መርቆርዮስ እንደሚነግረን፦ወበጽሐ ንጉሥነ ዳዊት እስከ ምድረ ስናር። ወሶበ ሰምዐ ዜና ምጸአቱ ሥልጣነ ምስር ፈርሀ ጥቀ ወጸበበቶ ምድር በምልኣ። ወገብረ ዕርቀ ምስለ ሊቀ ጳጳሳት በብዙኀ አስተብቊዖ ወፈነወ ሊቀ ጳጳሳት መጽሐፈ መልእክት ምሰለ መስቀለ ኢየሱስ
እንዘ ይብል፤ ግባእ ውስተ ሀገርከ በሰላም እስመ ገበርኩ ዕርቀ።…
“ንጉሣችን ዳዊት ምድረ ሲናር ድረስ መጣ። የመምጣቱን ዜና የግብፁ
ሡልጣን በሰማ ጊዜ በጣም ፈራ። ምድር በመላዋ ጠበበችው። በብዙ
አማላጅ ከሊቀ ጳጳሳቱ ጋር ታረቀ። ሊቀ ጳጳሳቱም ከኢየሱስ መስቀል ጋር
እንዲህ ሲል ደብዳቤ ላከ። ወደሀገርህ በሰላም ተመለስ፤ ታርቄያለሁና። …”ከግማደ መስቀሉ ጋር ቅዱስ ሉቃስ የሳላቸው ሰባት የማርያም ሥዕሎች፥ አንድ ቅዱስ ዮሐንስ የሳለው የጌታ ሥዕል (ኲርዐተ ርእሱ) እና መቶ ሀያ ሺህ የወርቅ ዲናር እንደተላከለት መጽሐፈ ጤፉት ይናገራል። ወርቁን ግን በኩራት አልተቀበለም። መስቀሉን ንግሥት እሌሊ
ካገኘችው ጀምሮ ጉራጁ ወደ ኢትዮጵያ እስከመጣ ድረስ ያለው ታሪክ ብዙ
አይታወቅም። ምናልባት ግብፆች ድርሻ አግኝተው ከዚያ ይሆናል የላኩልን።
መስቀሉ የመጣው በዳዊት ዘመን መሆኑን ማስረጃዎች ሁሉ ቢስማሙም
አለመግባባት የተፈጠረው በአጼ ሠይፈ አርዕድ ጊዜ ነው የሚሉ አሉ።እነዚህ
ቅዱሳን ቅርሶች በቤተ መንግሥት ሲኖሩ አፄ ዘርዓ ያዕቆብ (ከዳዊት ልጆች
አንዱ) ነገሠ። እሱም በሕልሙ አንብር መስቀልየ ዲበ መስቀል (=መስቀሌን
ከመስቀል ላይ አስቀምጥ፥) ሲለው ሰማ። ይኸ ሕልም የሚያመለክተው
የመስቀል ቅርጽ ያለውን አምባ ግሼንን (ወሎ) ነው ብሎ ከዚያ ልኮ አስቀመጠው። የግራኝ ወታደሮች እስኪመዘብሩት ድረስ ገዳሙ የነገሥታት
እቃ ማከማቻና ልዑላን እንዳይሸፍቱ መጠበቂያ ነበር። ስለዚህ አፄ ዘርዓ
ያዕቆብ እነዚህን እቃዎች ወደዚያ ለመላክ ሕልም ማየትም ባላስፈለገው
ነበረ።መጽሐፈ ጤፉት ውስጥ ተመዝግቦ የተገኘው የአፄ ዘርዓ ያዕቆብ
ደብዳቤ እንደሚመሰክረው በዚህ ንጉሥ ጊዜም ተጨማሪ የመስቀል ጉራጅና
ሌሎችም ቅዱሳን ቅርሶች ወደኢትዮጵያ መጥተዋል።

ምንጭ፦“የጌታ መስቀል ወደ ኢትዮጵያ መምጣት” (ጌታቸው
ኃይሌ)

እናመሠግናለን
#Coททεcт WiтhUs 👣 @Feed_it_bot

┈┈┈••✦✦••┈┈┈
@Readers_To_Know
❀꧁✤┈┈┈••✦✦••┈┈┈✤꧂❀
📓🌓 ቅምሻ 🌗📓

ያልተፈተሹ ባህሪያት

“ትዕግስት ስጠኝ ብለን ስንጠይቅ፤ የሚሰጠን እረጅም ሰልፍ ነው” ትላለች ጸሀፊ ትሬሲ ማክሚላን። ትዕግስትን ስንጠይቅ የሚሰጠን ትዕግስትን የምንለማመድበት መድረክና ትዕግስትን የምናዳብርባቸው ሁኔታዎች እንጂ ትዕግስት ልክ እንደተሰጥዎ ከላይ አይቸረንም። ለዛሬ ጽሁፌ መነሻ የሆነኝ ሀሳብ እንደሚከተለው ነው።

አንዳንዴ እራሳችንን ባላሰብነው ሁኔታ ውስጥ እናገኘውና ከራሳችን የማንጠብቀው ባህሪ ሲንጸባረቅብን እንደነግጣለን። ለወትሮ እኮ እንዲህ አልነበርኩም በማለት ግራ ይገባናል። ተሳድበን የማናውቅ ሰዎች በሆነ አጋጣሚ ሌላውን ሰው ስናጥረገርገው፤ ትዕግስተኛ ነን ብለን የምናስብ ሰዎች ቀጠሮዋችን እረፈደ ብለን የታክሲውን ሹፌር ስናመናጨቀው፤ ቂመኛ አይደለሁም ስንል የከረምን ሰዎች የወደድነው ሲከዳን ለበቀል ስናደባ፤ በደላችንን ይቅር በለን እያልን ጠዋት ማታ እየጸለይን የበደሉንን ሰዎች ይቅር ማለት ሲከብደን፤የሌሎች ሰዎች ማግኘት ያስደስተናል የምንል ሰዎች እኛ የተመኘነውን ሌላው ሰው ላይ ስናየውና ሲከፋን፤ ፈራጅ አይደለንም ስንል ከርመን የእኛ ህልውና ሲነካ የፍርድ ወንበር ላይ ቁጢጥ ስንል፤ ባህሪያችን ለገዛ እራሳችን እጅግ ግራ ያጋባል።

ማንነታችን የሚገለጸው እኛ ስለራሳችን ባለን አመለካከት ወይም ሌሎች ሰዎች ስለኛ ባላቸው አመለካከት ሳይሆን፤ እኛ ለሁኔታዎች በምንሰጠው ምላሽ ነው። ሰው እንቃለው የሚል ሰው ባያጋጥምም ፤ ሰው እጠላለሁ የሚል ሰው ስምተን ባናውቅም ሰው የሚንንቅና የምንጠላ ሰዎች ግን አንጠፋም። ከእኔ ከእራሴ ጭምር በውስጣችን መጥፎ ስሜት ያድራል ብለን ማሰቡ ይከብደናል፤ ይከብደናል ብቻም ሳይሆን ለማሰብም አንፈልግም። እውነታው ግን ከዚህ የተለየ ነው። “እኔ” ብለን የምንጠራው ማንነት በአብዛኛው የተገነባው ባልተፈተሹ ባህሪያቶቻችን ነው። ስለራሳችን ስናወራ በአብዛኛው የምናወራው በሀሳብ ስለገነባነው ማንነት እንጂ፤ በተግባር ስለምነተገብረው ባህሪዎቻችን አይደለም።

እኔ እንዲህ ነኝ ብሎ በድፍረት መናገሩ ከባድ የሚሆነውም ለዚህ ነው፤ ሁላችንም ያልተፈተኑ ባህሪያቶችን አጭቀን ስለምንቀሳቀስ። አብዛኛው ባህሪያቶቻችንና አስተሳሰቦቻችን በቲዎሪ ደረጃ እንጂ በሙከራ የተረጋገጡ አይደሉም። መልካምነታችን፤ ትዕግስተኛነታችን፤ ፍትሃዊነታችን፤ ሰው አክባሪነታችን፤ እውነተኛነታችን ተገቢውን ፈተና አላለፉም። ፈተና ስል እውነተኛ ባህሪዎቻችንን እንድናጸባርቅ የሚያስገድዱን ሁኔታዎችን ነው። ጊዜ ስለተረፈን ከኋላችን ያለውን ተሰላፊ ከፊታችን ስላስቀደምነው ትዕግስተኛ ልንባል እንችላለን? በፍጹም!!! የማንኛችንም መልካምነትና ጥንካሬ በመልካም አጋጣሚዎች ሊረጋገጥልን አይችልም። በፈተናዎችና በአስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ የምናሳያቸው ባህሪያቶች ይበልጥ እኛን ይገልጹናል።

ለዚህ ነው አንዳንዴ ውሳኔዎቻችንና ድርጊቶቻችን የሚያስደነግጡን። ተፈትነን ያገኘናቸው ባህሪዋቻችን ስላልሆኑ ልንጠቀምባቸው በሚገባን ቦታ ይጠፉብናል። ይህንን ማወቁ ምን ይጠቅምናል? ለሁለት ነገር ይጠቅመናል ብዬ አስባለው። አንደኛው ከውሸተኛ ማንነት ቀስ እያለ ያላቅቀናል፤ ሙሉ በሙሉ መላቀቅ ለሰው ልጅ ቢከብድም። የሚሰማንን ስሜት በካድን ቁጥርና “እኔ እኮ እንዲህ አይደለሁም” በማለት እራሳችንን በተከላከልን ቁጥር ባህሪያችንን ማሻሻል አስቸጋሪ ይሆንብናል። ከእራሳችን ጋር እየተቆራረጥን በቅዠት አለም ውስጥ መኖሩን እንለምደዋለን።በሌላ በኩል ማንነትና ባህሪያችንን ለሁኔታዎች ከምንሰጠው ምላሽ ተነስተን መዳኘት ከቻልን፤ ከእውነተኛ ምንነታችን ጋር እንቀራረባለን። የትኛው ባህሪያችን ላይ ይበልጥ ማሻሻል እንዳለብን ግልጽ ይሆንልናል። ስለራሳችን ባህሪ እርግጠኛ ሆኖ መናገሩ የሚያስከፍለው ዋጋ አለ፤ እሱም ወደ እውነት የሚወስደውን ጎዳና ያጠብብናል።እውንተኛ ማንነታችንን ለማወቅ ከፈለግን ስለራሳችን የምናስበውን ሳይሆን፤ ለሁኔታዎችና ለአጋጣሚዎች የምንሰጠውን ምላሽ ልናስተውል ግድ ይለናል። ሁለተኛው ጥቅም “እኔ ብሆን ኖሮ” በሚለው የፍርድ ዱላ እርስ በራሳችን ከመፈነካከት ያድነናል።

“ የሰው ባህሪያት በሁኔታዎችና በአጋጣሚዎች አይፈጠርም፤ በሁኔታዎችና በአጋጣሚዎች ይጋለጣል እንጂ”- ዚግ ዚግለር

ምንጭ፦ @EthioBini

እናመሠግናለን
#Coททεcт WiтhUs 👣 @Feed_it_bot

┈┈┈••✦✦••┈┈┈
@Readers_To_Know
❀꧁✤┈┈┈••✦✦••┈┈┈✤꧂❀
​​🎥📻 ከታሪክማህደር 🎙🎞

የዲያቆን ዶክተር ኢንጂነር ቅጣው እጅጉ አጭር የሕይወት ታሪክ
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~

ዲያቆን ዶክተር ኢንጂነር ቅጣው እጅጉ የካቲት 16 ቀን 1940 (እ.ኤ.አ) ከአባታቸው ከአቶ እጅጉ ሃይሌ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ አስካለ በላይነህ በከፋ ጠቅላይ ግዛት በቦንጋ ከተማ ተወለዱ። የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በቦንጋ፣ በዋከና በጅማ ከተማ ካጠናቀቁ በኃላ በባህር ዳር በሚገኘው ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅየከፍተኛ ትምህርታቸውን አጠናቀዋል።
ዶክተር ቅጣው ወደ ጃፓን አገር በመሄድ በኦሳካ ዪኒቨርስቲ በቋንቋና የጃፓን ኢኮኖሚ፣ በሄሮሺማ
ዩንቨርስቲ የኢንደስትሪ እና የአውቶሞቲቭ ኢንጂነሪንግ አጥንተው ትምህርታቸውን አጠናቀዋል። በኋላም አሜሪካን ሀገር ስኮላር ሺፕ አግኝተው በቢዝነስ አድሚንስትሬሽን ማስትሬታቸውን በመጨረሻም ለትምህርት ባላቸው ከፍተኛ ፍላጎት በኤሮ-ስፔስ ምህንድስና ዶክትሬታቸውን ተቀብለዋል።
ዶክተር ቅጣው በናሳ (NASA) በሲስተም መሃንዲስነትና በጠፈር ሳይንቲስትነት የሰሩ ሲሆን
ከሌሎች መሃንዲሶችና ሳይንትስቶች ጋር በመተባበር ለእኛ አለም (Planet Earth) እና ለተቀሩት ፕላኔቶች የምርምር ሳይንስ (Planetary Science
Research and Exploration) የሚረዱ የጠፈር መንኮራኩሮችና ሮኬቶች ፈጥረዋል። ዶክተር ቅጣው በዚህ ከፈጣሪ በተቸሩት ታላቅ ችሎታና እውቀት ለዚህች ለምንኖርባት ዓለምና ሕዝብ ታላቅ አስተዋፅዎ አበርክትዋል። ከነዚህም ጥቂቱን ለመጥቀስ ለናሳ (NASA) ሁለት የኤሮ-ስፔስ መወርወሪያ ሜካኒዝም ለቦይንግ ኩባንያ ሲሙሌተር
(Flight Dynamic Simulator) እና አድቫንስድ ወይንም ኔክስት ጀነሬሽን (Advance or Next Generation) በመባል የሚታወቁትን ግሎባል ፖዚሽን ሳተላይት ሲስተም (Global Positioning Satellite System) ከፈለሰፉት ውስጥ አንደኛው ሰው እሳቸው ነበሩ። ዶክተር ቅጣው Trans Tech International በመባል የሚታወቀውን ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ድርጅት መስራች ነበሩ።

ኢንጂነሩ በህግና በምጣኔ ሀብት አስተዳደር የማስትሬት ዲግሪ አላቸው። ስነ መለኮት(theology) ተምረዋል። የአብነት ትምህርትም ተከታትለው ሊቀ ዲያቆን ሆነዋል። መጽሐፍ ቅዱስን እስከ ምዕራፍ ቁጥሩ በጭንቅላታቸው አስቀምጠው፣ የፍልስፍናና የምርምር ስንቃቸው አድርገዋል። ፈሪሃ እግዚአብሔር የሌለው ትውልድ ያባቱን ርስት አይወርስም የሚል የዘወትር አባባል አላቸው።

ዶክተር ኢንጂነር ሳይንስቲስት ብቻ ሳይሆኑ አንደበተ ርቱዕ የፖለቲካ ሰውም ናቸው፡፡በምርጫ 97 የኢትዮጵያ ብሄራዊ
አንድነት ግንባር የሚል ብሄራዊ ፓርቲ በማቋቋም በኢትዮጵያ ፖለቲካ አሻራቸውን አስቀምጠዋል ፡፡
200 የሚደርሱ የፖለቲካ ስደተኛ ኢትየጵያዊ ተማሪዎችን በወር ከ 1 ሚሊየን ዶላር በላይ እየከፈሉ አስተምረው ለወግ ለማረግም አብቅተዋል፡፡

የዶክተር ኢንጂነር ቅጣው ባለቤት ፈረንጅ ናቸው፡፡ ወይዘሮ እስቴላ እጅጉ ይባላሉ፡፡ወይዘሮ እስቴላ ስራዓተ ጥምቀት ከመፈፀማቸው ባለፈ ፣የኢትዮጲያን ባህል ወርሰዋል፡፡ ዶክተር ቅጣው በህይወት ዘመናቸው ሶስት ልጆችን አፍርተዋል። ቢኒያም ፣ያሬድ፣አቢጋኤል የሚል ኢትዮጵያዊ ና መፅሀፍ ቅዱሳዊ ስም አላቸው፡፡

ዓለም እጇን ዘርግታ እየፈለገቻቸው ፣ሳይንሱም ድምፁን ከፍ አድርጎ እየጠራቸው፣የሀገር ፍቅር....እረፍት እየነሳቸው ብዙ እያለሙ ሳይታመሙ ጥር 5 /1998
ዓም(January 13/2006) ቅርጫት ኳስ እየተጫወቱ በ 58 ዓመታቸው አረፉ የሚል ዜና ተሰማ፡፡ በወቅቱ ዜናው አልታመነም፡፡የዶክተር ኢንጂነር ቅጣው ሞት እስካሁን በአወዛጋቢነቱ ቀጥሏል ፡፡
በጀግኖቻችን ታሪክ ወደ ኃላ እየተመለስን ወደ ፊት እንወጣለን!!! አናፈገፍግም፣ አናቅማማም ለለውጥ ነው ያለ ይስማዕከ በዴርቶጋዳ መፅሃፉ፡፡ ታሪክን የምንዘክረው ሙታንን ናፋቂ ሆነን ሳይሆን ታሪከኞች ህያው ስራቸውን መማርያ ለማድረግ ነው!!!ታሪክ የተግባር ትምህርት ቤት ነውና!! ደግሞም የትናንት ታሪከኞች የተማሩት ከትናንትና ወዲያ ባለታሪኮች ነው!!

በእውነትም ኢትዮጵያ ብቻ ሳትሆን ዓለም አንድ ትልቅ ሰው አጣች ቢባል ማጋነን አይሆንም።

እናመሠግናለን
#Coททεcт WiтhUs 👣 @Feed_it_bot

┈┈┈••✦✦••┈┈┈
@Readers_To_Know
❀꧁✤┈┈┈••✦✦••┈┈┈✤꧂❀
🧞‍♂👣 ከዚምከዛም 👣🧞‍♂

🤔. Quote:- weakness of attitude can become weakness of character
Albert Einstein

🧠. The average human body contains approximately 100 billion nerve cells.

👨‍🍳. uncooked food digests two times faster than cooked food.

. Bones are 4 times stronger than concrete.

እናመሠግናለን
#Coททεcт WiтhUs 👣 @Feed_it_bot

┈┈┈••✦✦••┈┈┈
@Readers_To_Know
❀꧁✤┈┈┈••✦✦••┈┈┈✤꧂❀
​​ዜና እረፍት
የክብር ዶክተር አርቲስት ለማ ጉያ በህክምና ሲረዱ ቆይተው በተወለዱ በ92 ዓመታቸው በዛሬው እለት ጥቅምት 16/2013 ዓ.ም ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል።

ለቤተሰቦቻቸው እንዲሁም ለጥበብ አድናቂዎቻቸው በጠቅላላ መጽናናትን እንመኛለን!😥
@Readers_To_Know
📓🌓 ቅምሻ 🌗📓

....."The Buddha says that pain or suffering arises through desire or craving and that to be free of pain we need to cut the bonds of desire.".....

The power of now : By Eckhart Tolle

እናመሠግናለን
#Coททεcт WiтhUs 👣 @Feed_it_bot

┈┈┈••✦✦••┈┈┈
@Readers_To_Know
❀꧁✤┈┈┈••✦✦••┈┈┈✤꧂❀
📓🌓 ቅምሻ 🌗📓

....."There are two levels to your pain: the pain that you create now, and the pain from the past that still lives on in your mind and body. Ceasing to create pain in the present and dissolving past pain this is what i want to talk about now.".....

....."The mind always seeks to deny the now and to escape from it. The more you are identified with your mind, the more you suffer. The more you are able to honor and accept the now, the more you are free of pain, of suffering and free of the egoic mind."......

The power of now : By Eckhart Tolle

እናመሠግናለን
#Coททεcт WiтhUs 👣 @Feed_it_bot

┈┈┈••✦✦••┈┈┈
@Readers_To_Know
❀꧁✤┈┈┈••✦✦••┈┈┈✤꧂❀
📓🌓 ቅምሻ 🌗📓

......"Just as you cannot fight the darkness, you cannot fight the pain body. Try to do so would create inner conflict and thus further pain. Watching it is enough. Watching it implies accepting it as part of what is at the moment.".....

The power of now : By Eckhart Tolle

እናመሠግናለን
#Coททεcт WiтhUs 👣 @Feed_it_bot

┈┈┈••✦✦••┈┈┈
@Readers_To_Know
❀꧁✤┈┈┈••✦✦••┈┈┈✤꧂❀
📓🌓 ቅምሻ 🌗📓

....."Certain things in the past didn't go the way you wanted them to go. You are still resisting what happened in the past, and now you are resisting what is. Hope is what keeps you going, but hope keeps you focused on the future, and this continued focus perpetuates your denial of the Now and therefore your unhappiness."........

The power of now : By Eckhart Tolle

እናመሠግናለን
#Coททεcт WiтhUs 👣 @Feed_it_bot

┈┈┈••✦✦••┈┈┈
@Readers_To_Know
❀꧁✤┈┈┈••✦✦••┈┈┈✤꧂❀
📓🌓 ቅምሻ 🌗📓

....."Nothing ever happened in the past; it happened in the Now.
Nothing will ever happen in the future; it will happen in the Now.
What u think of as the past is a memory trace, stored in the mind, of a former Now. When u remember the past, u reactivate a memory trace and u do so Now. The future is an imagined Now, a projection of the mind. When the future comes, it comes as the Now. When u think about the future, you do it Now. Past and Future obviously have no reality of their own. Just as the moon has no light of it's own, but can only reflect the light of the sun, so are past and future only pale reflections of the light, power and reality of the eternal present. Their reality is 'borrowed' from the Now.".....

The power of now : By Eckhart Tolle

እናመሠግናለን
#Coททεcт WiтhUs 👣 @Feed_it_bot

┈┈┈••✦✦••┈┈┈
@Readers_To_Know
❀꧁✤┈┈┈••✦✦••┈┈┈✤꧂❀
📓🌓 ቅምሻ 🌗📓

......" 'Time is what keeps the light from reaching us. There is no greater obstacle to God than time.' By Meister Eckhart ".......

......"Your life situation may be full of problems, Most life situations are, but find out if you have any problem at this moment. Not tomorrow or in ten minutes, but now. Do you have a problem now?"......

The power of now : By Eckhart Tolle

እናመሠግናለን
#Coททεcт WiтhUs 👣 @Feed_it_bot

┈┈┈••✦✦••┈┈┈
@Readers_To_Know
❀꧁✤┈┈┈••✦✦••┈┈┈✤꧂❀
📓🌓 ቅምሻ 🌗📓

......"Ask your self: is there joy, ease, and lightness in what i am doing? If there isn't, then time is covering up the present moment, and life is perceived as a burden or a struggle.
Of there is no joy, ease, or lightness in what you are doing, it does not necessarily mean that you need to change what you are doing. It may be sufficient to change the How. 'how' is always more important than 'what'. See if you can give much more attention to the doing than to the result that you want to achieve through it. Give your fullest attention to whatever the moment presents. This implies that you also completely accept what is, because you cannot give your full attention to something and at the same time resist it. As soon as you honor the present moment, all unhappiness and struggle dissolve, and life begins to flow with joy and ease. When you act out of present-moment awareness, whatever you do becomes imbued with a sense of quality, care, and love even the most simple action.".......

The power of now : By Eckhart Tolle

እናመሠግናለን
#Coททεcт WiтhUs 👣 @Feed_it_bot

┈┈┈••✦✦••┈┈┈
@Readers_To_Know
❀꧁✤┈┈┈••✦✦••┈┈┈✤꧂❀
😂🎩 ለፈገግታ 🎩🤣

አግአዚዎች ሰው ተሰብስቦ አንድ ቦታ ሲቆም ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ስለሚመስላቸው ደስ አይላቸውም።
ታድያ በምርጫው ሰሞን አዲስ አበባ ውስጥ ፌርማታ ላይ አውቶብስ በመጠበቅ ላይ ወደነበሩት ሰዎች አንድ የአግአዚ ጦር ባልደረባ እየተክለፈለፈ ይመጣና " ተበተኑ !! ምን ልታደርጉት ነው የተሰበሰባችሁት?! " ሲል ያፈጥባቸዋል። ሰዎቹም በፍርሀት እየተርበደበዱ "አረ ባስ እየጠበቅን ነው!" ብለው ሲመልሱለት አግአዚው የመሳሪያውን አፈሙዝ ወደነሱ አዙሮ " ተበተን!! ነው ያልኩህ! ለመጠበቅ አንድ ሰው ይበቃል! ሌሎቻችሁ ከዚህ ቦታ ዞር በሉ!? በማለት አንድ ሰው ብቻ ሲቀር ሌሎቹን አባረራቸው።😂😂
ምንጭ፦ እስኪ ዛሬ እንኳን እንሳቅ በቅዱስ-ሀብት በላቸው

እናመሠግናለን
#Coททεcт WiтhUs 👣 @Feed_it_bot

┈┈┈••✦✦••┈┈┈
@Readers_To_Know
❀꧁✤┈┈┈••✦✦••┈┈┈✤꧂❀
📓🌓 ቅምሻ 🌗📓

......" to be free of time is to be free of the psychological need of past for your identity and future for your fulfilment.".......

......"Stress is caused by being 'here' but wanting to be 'there', or being in the present but wanting to be in the future."......

The power of now : By Eckhart Tolle

እናመሠግናለን
#Coททεcт WiтhUs 👣 @Feed_it_bot

┈┈┈••✦✦••┈┈┈
@Readers_To_Know
❀꧁✤┈┈┈••✦✦••┈┈┈✤꧂❀
🎥📻 ከታሪክማህደር 🎙🎞

ከጥንት ጀምሮ የነበሩ የሀገራችን ነገስታትና ታዋቂ የጦር መሪዎች የሚጠሩበት የፈረስ ስም እንደነበራቸው ይታወቃል። እንደምሳሌ ለመጥቀስ ያህል፡
አፄ ቴዎድሮስ ፦ አባ ታጠቅ
አፄ ዮሐንስ ፦ አባ በዝብዝ
አፄ ምኒልክ ፦ አባ ዳኘው
ልጅ እያሱ ፦ አባ ጤና
አፄ ኃይለ ስላሴ ፦ አባ ጠቅል
ደጃች ባልቻ ፦ አባ ነፍሶ
ምንጭ፦ እስኪ ዛሬ እንኳን እንሳቅ በቅዱስ-ሀብት በላቸው

እናመሠግናለን
#Coททεcт WiтhUs 👣 @Feed\it_bot

┈┈┈••✦✦••┈┈┈
@Readers_To_Know
❀꧁✤┈┈┈••✦✦••┈┈┈✤꧂❀
📓🌓 ቅምሻ 🌗📓

....."Waiting is a state of mind. Basically it means that you want the future; you don't want the present. You don't want what you have got, and you want what you haven't got. With every kind of waiting, you unconsciously create inner conflict between your here and now, where you don't want to be, and the projected future, where you want to be. This greatly reduces the quality of your life by making you lose the present.".......

The power of now : By Eckhart Tolle

እናመሠግናለን
#Coททεcт WiтhUs 👣 @Feed_it_bot

┈┈┈••✦✦••┈┈┈
@Readers_To_Know
❀꧁✤┈┈┈••✦✦••┈┈┈✤꧂❀
📓🌓 ቅምሻ 🌗📓

......"something could happen at any moment, and if you are not absolutely awake, absolutely still, you will miss it.".......

The power of now : By Eckhart Tolle

እናመሠግናለን
#Coททεcт WiтhUs 👣 @Feed_it_bot

┈┈┈••✦✦••┈┈┈
@Readers_To_Know
❀꧁✤┈┈┈••✦✦••┈┈┈✤꧂❀
🧞‍♂👣 ከዚምከዛም 👣🧞‍♂

💯 Quote:- even though you know thousand things ask the man who knows one.

👅 Average life span of a taste bud is only 10 days.

👣🕺 You are born without knee caps and they don't appear until age of 2 to 6 years.

👼🤵 Children grow faster in spring time.

🤷‍♂ Eyes stay the same size throughout life but nose👃 and ears👂 never stop growing.

እናመሠግናለን
#Coททεcт WiтhUs 👣 @Feed\it_bot

┈┈┈••✦✦••┈┈┈
@Readers_To_Know
❀꧁✤┈┈┈••✦✦••┈┈┈✤꧂❀