ካነበብነው📖📜📰🗞 via @like
💫🌪 ጥቆማ 🌪💫
"ፍልስፍና ከምንም ተነስቶ ወደ
ምንም የሚያደርስ መንገድ ነው"
---------------------------------------
የፍልስፍና መምህሩ ወደ ክፍል ውስጥ ይገባና ለተማሪዎቹ የመጨረሻውን ፈተና ሊሰጥ ተዘጋጀ። አንድ ወንበር በማንሳት ከጠረጴዛ ላይ አስቀመጠና፦
"እስከዛሬ በዚህ ኮርስ የተማራችሁትን ቁም ነገር ከግምት ውስጥ በማስገባት ይኽ ወንበር አለመኖሩን አረጋግጡልኝ" አለ።
በዚህ ጊዜ ተማሪዎች የዚያን ወንበር አለመኖር ወይም መኖሩ እውነት አለመሆኑን ለማረጋገጥ መፃፍ ጀመሩ። ብዙዎቹ ለሰዓታት የፈጀ ጥናታቸውንና ማብራሪያቸውን ሲፅፉ አንድ ተማሪ ግን በሰላሳ ሴኮንድ ውስጥ መልሱን ፅፎ ለመምህሩ በማስረከብ ክፍሉን ለቅቆ ሄደ።
በነጋታው ፕሮፌሰሩ የተማሪዎቹን ውጤት ይዞ መጣ። ከሁሉም ተማሪ ከፍተኛውን ውጤት ያገኘው በሰላሳ ሴኮንድ ፈተናውን ጨርሶ የሄደው ተማሪ ነበር።
ፕሮፌሰሩም "ብዙዎቻችሁ የወንበሩን አለመኖር ለማሳየት ብዙ ደክማችኋል። ይኽ ተማሪ ግን ከሁላችሁም በላቀ መንገድ ወንበሩ አለመኖሩን አረጋግጦልኛል" አለ።
✅ ተማሪው ለጥያቄው የሰጠው ምላሽ እንዲህ የሚል ነበር።
"የቱ ወንበር?"።
----------------------------
"ጥ በ ብ" - ከጲላጦስ
(ኃይለጊዮርጊስ ማሞ)
📖 📖 📖 📖 📖 📖 ❣️ እናመሠግናለን ❣️
#share #participate #comment
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
"ፍልስፍና ከምንም ተነስቶ ወደ
ምንም የሚያደርስ መንገድ ነው"
---------------------------------------
የፍልስፍና መምህሩ ወደ ክፍል ውስጥ ይገባና ለተማሪዎቹ የመጨረሻውን ፈተና ሊሰጥ ተዘጋጀ። አንድ ወንበር በማንሳት ከጠረጴዛ ላይ አስቀመጠና፦
"እስከዛሬ በዚህ ኮርስ የተማራችሁትን ቁም ነገር ከግምት ውስጥ በማስገባት ይኽ ወንበር አለመኖሩን አረጋግጡልኝ" አለ።
በዚህ ጊዜ ተማሪዎች የዚያን ወንበር አለመኖር ወይም መኖሩ እውነት አለመሆኑን ለማረጋገጥ መፃፍ ጀመሩ። ብዙዎቹ ለሰዓታት የፈጀ ጥናታቸውንና ማብራሪያቸውን ሲፅፉ አንድ ተማሪ ግን በሰላሳ ሴኮንድ ውስጥ መልሱን ፅፎ ለመምህሩ በማስረከብ ክፍሉን ለቅቆ ሄደ።
በነጋታው ፕሮፌሰሩ የተማሪዎቹን ውጤት ይዞ መጣ። ከሁሉም ተማሪ ከፍተኛውን ውጤት ያገኘው በሰላሳ ሴኮንድ ፈተናውን ጨርሶ የሄደው ተማሪ ነበር።
ፕሮፌሰሩም "ብዙዎቻችሁ የወንበሩን አለመኖር ለማሳየት ብዙ ደክማችኋል። ይኽ ተማሪ ግን ከሁላችሁም በላቀ መንገድ ወንበሩ አለመኖሩን አረጋግጦልኛል" አለ።
✅ ተማሪው ለጥያቄው የሰጠው ምላሽ እንዲህ የሚል ነበር።
"የቱ ወንበር?"።
----------------------------
"ጥ በ ብ" - ከጲላጦስ
(ኃይለጊዮርጊስ ማሞ)
📖 📖 📖 📖 📖 📖 ❣️ እናመሠግናለን ❣️
#share #participate #comment
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ካነበብነው📖📜📰🗞 via @like
💫🌪 ጥቆማ 🌪💫
ፍልስምና ፩+፪+፫ የሚለው የደራሲ ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ መጽሐፍ ላይ ጋሽ ስብሃት ገ/እግዚአብሔር እና ቴዎድሮስ እንዲህ ሲሉ ያወጋሉ...
ከመጽሐፉ የተቀነጨበች ጽሑፍ...
፨፨፨
ቴዎድሮስ ፦ የወንድና የሴትን ትተን በተመሳሳይ ጾታዎች መሀል እኩል የሚባል ነገር ይኖራል? አንድ ወንድ ከሌላው ወንድ ጋር...?
#ስብሃት ፦ የውልህ..እኩል የሚለው እኮ ስታትስቲክስ ነው። #ሀሳብ ነው እንጂ እኩል የሚባል ነገር የለም። አንድ ሰው የማንም እኩል አይደለም። እያንዳንዳችን ራሳችንን የቻልን ዩኒቨርስ ነን። እኛ ብቻ ሳንሆን እያንዳንዷ የሰውነታችን ሴል ልዩ ናት። እኩል..ምናምን የምንለው ሃሳብ ነው እንጂ የለም።
፧
ቴዎድሮስ ፦ የሰው ልጅ መሞት የሚጀምረው መቼ ነው?
#ስብሃት ፦ የውልደቱ እለት ነው መሞት የሚጀምረውማ። ጥፍርህ ያበቅላል አይደለም? ግን ደግሞ እንደበቀለ ይሞታል። ተቆርጦ ሲሔድ አይሰማህም። ሞት እኮ ሁሌም አብሮህ ነው። ስትታጠብ ቆዳህ በመጠኑ እየተላጠ ይሄዳል። እየሞትክና እየተወለድክ ትኖራለህ ማለት ነው ።
ምንጭ ፦ / ፍልስምና ፩+፪+፫……ገጽ 77 /
ደራሲ ፦ ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ
ጋሽ ስብሃት ምን ለማለት ፈልጎ ይሆን...?
❣️ እናመሠግናለን ❣️
#share #participate #comment
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ፍልስምና ፩+፪+፫ የሚለው የደራሲ ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ መጽሐፍ ላይ ጋሽ ስብሃት ገ/እግዚአብሔር እና ቴዎድሮስ እንዲህ ሲሉ ያወጋሉ...
ከመጽሐፉ የተቀነጨበች ጽሑፍ...
፨፨፨
ቴዎድሮስ ፦ የወንድና የሴትን ትተን በተመሳሳይ ጾታዎች መሀል እኩል የሚባል ነገር ይኖራል? አንድ ወንድ ከሌላው ወንድ ጋር...?
#ስብሃት ፦ የውልህ..እኩል የሚለው እኮ ስታትስቲክስ ነው። #ሀሳብ ነው እንጂ እኩል የሚባል ነገር የለም። አንድ ሰው የማንም እኩል አይደለም። እያንዳንዳችን ራሳችንን የቻልን ዩኒቨርስ ነን። እኛ ብቻ ሳንሆን እያንዳንዷ የሰውነታችን ሴል ልዩ ናት። እኩል..ምናምን የምንለው ሃሳብ ነው እንጂ የለም።
፧
ቴዎድሮስ ፦ የሰው ልጅ መሞት የሚጀምረው መቼ ነው?
#ስብሃት ፦ የውልደቱ እለት ነው መሞት የሚጀምረውማ። ጥፍርህ ያበቅላል አይደለም? ግን ደግሞ እንደበቀለ ይሞታል። ተቆርጦ ሲሔድ አይሰማህም። ሞት እኮ ሁሌም አብሮህ ነው። ስትታጠብ ቆዳህ በመጠኑ እየተላጠ ይሄዳል። እየሞትክና እየተወለድክ ትኖራለህ ማለት ነው ።
ምንጭ ፦ / ፍልስምና ፩+፪+፫……ገጽ 77 /
ደራሲ ፦ ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ
ጋሽ ስብሃት ምን ለማለት ፈልጎ ይሆን...?
❣️ እናመሠግናለን ❣️
#share #participate #comment
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ካነበብነው📖📜📰🗞 via @like
🧞♂👣 ከዚም_ከዛም 👣🧞♂
🔴 ከሁለት ቢልዮን ሰዎች አንድ ሰው ብቻ 116 👩🦳👨🦳 ዓመትና ከዛ በላይ የመኖር እድል አለው። አይዞአችሁ የላቹበትም 😜😜😜
🔷 በ1926 ቴሌ ቪዥንን ( Television )📺 የፈጠረው ሰው እንግሊዛዊው Baird ነበር።
🎥 Quote :- What lies ahead will always be a mystery. Do not be afraid to explore.
🔶 ባሕረ ሀሳብ ማለት የግዕዝ ቃል ሲሆን በአረብኛ አቡሻከር በአማርኛ የዘመን አቆጣጠር 📆ይባላል። የቀመረው 12ኛው የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ ድሜጥሮስ 👳♂ነበሩ።
🔷 ይህን ይሞክሩ!
ባለ ሶስት አሐዝ ቁጥር ይምረጡ። ከዛም በ 7፣ በ 11 እና በ 13 ያባዙት። የሚያገኙት ውጤት የባለሶስት አሐዙን ሁለት ጊዜ የተደገመ ይሆናል።
ለምሳሌ :- 574 ብንወስድና በ 7፣ በ 11 እና በ 13 ቢያባዙት የመጨረሻው መልስ 574,574 ይሆናል።🎞🎞🎞
❣ እናመሠግናለን ❣
#share #participate
for any comment 👇
@R_e_a_d_e_rs
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
🔴 ከሁለት ቢልዮን ሰዎች አንድ ሰው ብቻ 116 👩🦳👨🦳 ዓመትና ከዛ በላይ የመኖር እድል አለው። አይዞአችሁ የላቹበትም 😜😜😜
🔷 በ1926 ቴሌ ቪዥንን ( Television )📺 የፈጠረው ሰው እንግሊዛዊው Baird ነበር።
🎥 Quote :- What lies ahead will always be a mystery. Do not be afraid to explore.
🔶 ባሕረ ሀሳብ ማለት የግዕዝ ቃል ሲሆን በአረብኛ አቡሻከር በአማርኛ የዘመን አቆጣጠር 📆ይባላል። የቀመረው 12ኛው የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ ድሜጥሮስ 👳♂ነበሩ።
🔷 ይህን ይሞክሩ!
ባለ ሶስት አሐዝ ቁጥር ይምረጡ። ከዛም በ 7፣ በ 11 እና በ 13 ያባዙት። የሚያገኙት ውጤት የባለሶስት አሐዙን ሁለት ጊዜ የተደገመ ይሆናል።
ለምሳሌ :- 574 ብንወስድና በ 7፣ በ 11 እና በ 13 ቢያባዙት የመጨረሻው መልስ 574,574 ይሆናል።🎞🎞🎞
❣ እናመሠግናለን ❣
#share #participate
for any comment 👇
@R_e_a_d_e_rs
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ካነበብነው📖📜📰🗞 via @like
💫🌪 ጥቆማ 🌪💫
"........ሺህ ምሁር ብትሆን መዋደድ ግድ ነው።
የተያያዝንበት ላስቲክ በመለጠጡ የተራራቅን ይመስለናል እንጂ የመያያዝ ባርነት ውስጥ ነን።
አዕምሮአቸው ብሩህ ባህላቸው ግን የባርያ የሆኑ ስንት አሉ በእግዜር። ባላምንበትም ልማልበት።
አይ አም ኢንተለጀንት ብሎ የሚናገር ግን ዘር ማንዘሩ በቁንጫ የሚበላበት፣ በጎጥ ብራንድ የነደደ ሰው አያበሽቅህም?
በ'ነኝ' ሰው የሚበላለጥ ቢሆን የአለም ጌታዋ ብዙ ነበር።
'ውበት ሃሰት ነው ደም ግባትም ከንቱ ነው' እንደሚባለው አዕምሮም ሃሰት ነው ብልጥነትም ከንቱ ነው።
ሁሉ ረጋፊ ነው። መደ'በር ደሞ የጋራችን ነው።......"
***
#ከ'አፍ መጽሐፍ የተወሰደ / አዳም ረታ/ ❣️ እናመሠግናለን ❣️
#share #participate #comment
@infho
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
"........ሺህ ምሁር ብትሆን መዋደድ ግድ ነው።
የተያያዝንበት ላስቲክ በመለጠጡ የተራራቅን ይመስለናል እንጂ የመያያዝ ባርነት ውስጥ ነን።
አዕምሮአቸው ብሩህ ባህላቸው ግን የባርያ የሆኑ ስንት አሉ በእግዜር። ባላምንበትም ልማልበት።
አይ አም ኢንተለጀንት ብሎ የሚናገር ግን ዘር ማንዘሩ በቁንጫ የሚበላበት፣ በጎጥ ብራንድ የነደደ ሰው አያበሽቅህም?
በ'ነኝ' ሰው የሚበላለጥ ቢሆን የአለም ጌታዋ ብዙ ነበር።
'ውበት ሃሰት ነው ደም ግባትም ከንቱ ነው' እንደሚባለው አዕምሮም ሃሰት ነው ብልጥነትም ከንቱ ነው።
ሁሉ ረጋፊ ነው። መደ'በር ደሞ የጋራችን ነው።......"
***
#ከ'አፍ መጽሐፍ የተወሰደ / አዳም ረታ/ ❣️ እናመሠግናለን ❣️
#share #participate #comment
@infho
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ካነበብነው📖📜📰🗞 via @like
📓🌓 ቅምሻ 🌗📓
💫በቀን፣ በሳምንት፣ በወር፣ በአመት ምን ያህል ሰው እንተዋወቃለን? ምን ያህሉንስ ጠብቀን አቆይተናል?
አንዳንዶች በህይወታቸው ውስጥ ሰው በየጊዜው ያስገባሉ። ነገር ግን ግንኙነታቸውን እንደነበረ ጠብቆ ማቆየት ላይ ደካማ ናቸው። እየቆየ የተበላሸ ግንኙነት ይሆናል። በግንኙነታቸው ውስጥ አንዱ ብቻ ጠንካራ ሆኖ አንዱን ላለማጣት ሲል ይበረታል በዚህም ምክንያት ወደ አንድ ጎን አድልቶ መሰለቻቸት ሊመጣ ይችላል ፤ ወይ ደግሞ ሁለቱም ደካማ ይሆኑና የነበራቸውን ደስ የሚል ነገር ረስተው ይለያያሉ። አንዳንዶች ደግሞ አጠገባቸው ስላለው ወዳጃቸው ግድ አይሰጣቸውም። እነሱ የሚጨነቁት ስለራሳቸው የግል ደስታና ስሜት ብቻ ነው። አንዳንዶች ከሰዎች ጋር ያላቸውን ግንኙነት በውሸት ማስቀጠል ይፈልጋሉ። ከዛ ሰው ጋር መለያየት፣ መቀያየም ወይም መጣላት አይፈልጉም። ነገር ግን ደግሞ ብዙ መቀራረብም አይመቻቸውም፤ ግንኙነታቸውን ያዝ ለቀቅ ያደርጋሉ። አንዳንድ ሰዎች ከዚህ በፊት በነበራቸው ያልሰመረ ግንኙነት ላይ በመናደድ ቀጣይ ጉዞአቸው ላይ ለነሱ የማይታወቃቸው ነገር ግን የበቀል በሚመስል ሁኔታ ኑሮአቸውን ይቀጥላሉ። በዚህ ሂደት ምንም የማያውቀው ተጎጂ ይሆናል። ያለፈውን ህይወታቸውን እንደ ትምህርት የሚጠቀሙትም ቁጥራቸው ትንሽ የሚባል አይደለም። አንዳንዶች መጀመሪያ ላይ ጥሩ ግንኙነት ይጀምሩና እየቆየ ሲሄድ ሆን ብለው ግንኙነታቸውን ማላላት ይፈልጋሉ። ምክንያታቸው ቢለያይም እነዚህም ሰዎች ስለራሳቸው እንጂ ስሌላው ስሜት ብዙም ግድ አይሰጣቸውም ማለት ነው፤ ወይ ደግሞ በቂ ምክንያት አላቸው፤ ሰው በማማረጥ ላይም ሊሆኑ ይችላል። አንዳንዶች ደግሞ ገና ትውውቃቸውን ሲጀምሩት የተበላሸና መስመር የሳተ በመሆኑ ዘላቂ ግንኙነት ለመጀመር ይከብዳቸዋል ። አንዳንዶች በዙሪያቸው ብዙ ሰው ካለ አጥብቆ የሚፈልጋቸውን ሰው ሳያውቁም ይሁን በቸልተኝነት ይጎዱታል። እዚጋ ለዛ ሰው እንዲከብድ የሚያረገው ግንኙነታቸው እንደ ዲምላይት በርቶ የሚጠፋ ስለሆነ ለመቁረጥና ለመተው ይከብደዋል። የአንዳንድ ሰዎች ወዳጅነት በእኩይ ተግባር በተጠመዱ ሰዎች ምክንያት እንዳልነበረ ሆኖ ሲበላሽ እናገኘዋለን።አንዳንዶች ደግም ከትውውቃቸው እስከ ፍፃሜያቸው የሚያስቀና ግንኙነት ይኖራቸዋል። እርስ በእርስ ካለፈው እየተማሩ፤ ዛሬን አብረው እየኖሩ፤ ነገን አብረው በተስፋ የሚጠባበቁ ወዳጆችም ጥቂት አይደሉም። ለዚህም ምስጢሩ መዋደዳቸው(መፋቀራቸው)፣ መተማመናቸው፣ ይቅር መባባላቸው፣ መተሳሰባቸው፣ መቻቻላቸው፣ በሀሳብ መደጋገፋቸው፣ አልፎ ተርፎም ግጭታቸውን አብረው የመፍታት ችሎታቸውና ሌሎችም ...... ወደ ህይወታችን ሰዎችን ስናስገባ ጥንቃቄ ማድረግ አንርሳ። ለምናረጋቸው ነገሮች ምክንያታዊ ለመሆን እንሞክር። ሰላም ከሁላችሁ ጋር ይሁን!!!!!
ፀሐፊ: - ©D.Ys
❣ እናመሠግናለን ❣
#share #participate #comment
@R_e_a_d_e_rs
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
💫በቀን፣ በሳምንት፣ በወር፣ በአመት ምን ያህል ሰው እንተዋወቃለን? ምን ያህሉንስ ጠብቀን አቆይተናል?
አንዳንዶች በህይወታቸው ውስጥ ሰው በየጊዜው ያስገባሉ። ነገር ግን ግንኙነታቸውን እንደነበረ ጠብቆ ማቆየት ላይ ደካማ ናቸው። እየቆየ የተበላሸ ግንኙነት ይሆናል። በግንኙነታቸው ውስጥ አንዱ ብቻ ጠንካራ ሆኖ አንዱን ላለማጣት ሲል ይበረታል በዚህም ምክንያት ወደ አንድ ጎን አድልቶ መሰለቻቸት ሊመጣ ይችላል ፤ ወይ ደግሞ ሁለቱም ደካማ ይሆኑና የነበራቸውን ደስ የሚል ነገር ረስተው ይለያያሉ። አንዳንዶች ደግሞ አጠገባቸው ስላለው ወዳጃቸው ግድ አይሰጣቸውም። እነሱ የሚጨነቁት ስለራሳቸው የግል ደስታና ስሜት ብቻ ነው። አንዳንዶች ከሰዎች ጋር ያላቸውን ግንኙነት በውሸት ማስቀጠል ይፈልጋሉ። ከዛ ሰው ጋር መለያየት፣ መቀያየም ወይም መጣላት አይፈልጉም። ነገር ግን ደግሞ ብዙ መቀራረብም አይመቻቸውም፤ ግንኙነታቸውን ያዝ ለቀቅ ያደርጋሉ። አንዳንድ ሰዎች ከዚህ በፊት በነበራቸው ያልሰመረ ግንኙነት ላይ በመናደድ ቀጣይ ጉዞአቸው ላይ ለነሱ የማይታወቃቸው ነገር ግን የበቀል በሚመስል ሁኔታ ኑሮአቸውን ይቀጥላሉ። በዚህ ሂደት ምንም የማያውቀው ተጎጂ ይሆናል። ያለፈውን ህይወታቸውን እንደ ትምህርት የሚጠቀሙትም ቁጥራቸው ትንሽ የሚባል አይደለም። አንዳንዶች መጀመሪያ ላይ ጥሩ ግንኙነት ይጀምሩና እየቆየ ሲሄድ ሆን ብለው ግንኙነታቸውን ማላላት ይፈልጋሉ። ምክንያታቸው ቢለያይም እነዚህም ሰዎች ስለራሳቸው እንጂ ስሌላው ስሜት ብዙም ግድ አይሰጣቸውም ማለት ነው፤ ወይ ደግሞ በቂ ምክንያት አላቸው፤ ሰው በማማረጥ ላይም ሊሆኑ ይችላል። አንዳንዶች ደግሞ ገና ትውውቃቸውን ሲጀምሩት የተበላሸና መስመር የሳተ በመሆኑ ዘላቂ ግንኙነት ለመጀመር ይከብዳቸዋል ። አንዳንዶች በዙሪያቸው ብዙ ሰው ካለ አጥብቆ የሚፈልጋቸውን ሰው ሳያውቁም ይሁን በቸልተኝነት ይጎዱታል። እዚጋ ለዛ ሰው እንዲከብድ የሚያረገው ግንኙነታቸው እንደ ዲምላይት በርቶ የሚጠፋ ስለሆነ ለመቁረጥና ለመተው ይከብደዋል። የአንዳንድ ሰዎች ወዳጅነት በእኩይ ተግባር በተጠመዱ ሰዎች ምክንያት እንዳልነበረ ሆኖ ሲበላሽ እናገኘዋለን።አንዳንዶች ደግም ከትውውቃቸው እስከ ፍፃሜያቸው የሚያስቀና ግንኙነት ይኖራቸዋል። እርስ በእርስ ካለፈው እየተማሩ፤ ዛሬን አብረው እየኖሩ፤ ነገን አብረው በተስፋ የሚጠባበቁ ወዳጆችም ጥቂት አይደሉም። ለዚህም ምስጢሩ መዋደዳቸው(መፋቀራቸው)፣ መተማመናቸው፣ ይቅር መባባላቸው፣ መተሳሰባቸው፣ መቻቻላቸው፣ በሀሳብ መደጋገፋቸው፣ አልፎ ተርፎም ግጭታቸውን አብረው የመፍታት ችሎታቸውና ሌሎችም ...... ወደ ህይወታችን ሰዎችን ስናስገባ ጥንቃቄ ማድረግ አንርሳ። ለምናረጋቸው ነገሮች ምክንያታዊ ለመሆን እንሞክር። ሰላም ከሁላችሁ ጋር ይሁን!!!!!
ፀሐፊ: - ©D.Ys
❣ እናመሠግናለን ❣
#share #participate #comment
@R_e_a_d_e_rs
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ካነበብነው📖📜📰🗞 via @like
🧞♂👣 ከዚም_ከዛም 👣🧞♂
🔶 Quote:- live as if you were to die tomorrow learn as if you were to live forever.
🔷 Diabetes is hereditary because our food habits are hereditary.
🔴 Smallest bone of body is in ears👂.
🔶 Human body needs natural sodium not sodium chloride salt.
⚪️ Largest muscle in your body is one on which you are sitting on. Don't see it pls 😂😂😂
❣ እናመሠግናለን ❣
#share #participate #comment
@R_e_a_d_e_rs
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
🔶 Quote:- live as if you were to die tomorrow learn as if you were to live forever.
🔷 Diabetes is hereditary because our food habits are hereditary.
🔴 Smallest bone of body is in ears👂.
🔶 Human body needs natural sodium not sodium chloride salt.
⚪️ Largest muscle in your body is one on which you are sitting on. Don't see it pls 😂😂😂
❣ እናመሠግናለን ❣
#share #participate #comment
@R_e_a_d_e_rs
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ካነበብነው📖📜📰🗞 via @like
📓🌓 ቅምሻ 🌗📓
ዓለማችን የሰለጠነች እንዳይመስላችሁ። የመጀመሪያው ዋሻ ቆፍሮ ይኖር የነበረው ሰው ከሥልጣኔ ቁንጮ ላይ እንደደረሰ ተሰምቶ ይሆናል። እሳትን የፈጠረውም እንደዛው። አሁን የተፈጠሩትን ውስብስብ መሣሪያዎች ስናይ ከሥልጣኔ ጫፍ የደረስን ሊመስላችሁ ይችላል። ነገርግን ዓለም ማብረቅረቅ ጀመረች እንጂ ገና አልሰለጠነችም። ... የሰው ልጅ የአዕምሮውን የመፍጠር እና የማሰብ ችሎታ ገና ምንም አልነካውም ማለት ይቻላል። የዛሬ መቶ ዓመት ከመቃብራችሁ ብትነቁ ይህን ታረጋግጣላችሁ። የሰው ልጅ የአእምሮ ህዋስ በብዙ ሚሊዮን እጥፍ ሊበለፀግ ይችላል።
ራማቶሓራ, ይስማዕከ ወርቁ፡ ገፅ 69
#share #participate #comment👇
@R_e_a_d_e_rs
@zhangidaa
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ዓለማችን የሰለጠነች እንዳይመስላችሁ። የመጀመሪያው ዋሻ ቆፍሮ ይኖር የነበረው ሰው ከሥልጣኔ ቁንጮ ላይ እንደደረሰ ተሰምቶ ይሆናል። እሳትን የፈጠረውም እንደዛው። አሁን የተፈጠሩትን ውስብስብ መሣሪያዎች ስናይ ከሥልጣኔ ጫፍ የደረስን ሊመስላችሁ ይችላል። ነገርግን ዓለም ማብረቅረቅ ጀመረች እንጂ ገና አልሰለጠነችም። ... የሰው ልጅ የአዕምሮውን የመፍጠር እና የማሰብ ችሎታ ገና ምንም አልነካውም ማለት ይቻላል። የዛሬ መቶ ዓመት ከመቃብራችሁ ብትነቁ ይህን ታረጋግጣላችሁ። የሰው ልጅ የአእምሮ ህዋስ በብዙ ሚሊዮን እጥፍ ሊበለፀግ ይችላል።
ራማቶሓራ, ይስማዕከ ወርቁ፡ ገፅ 69
#share #participate #comment👇
@R_e_a_d_e_rs
@zhangidaa
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ካነበብነው📖📜📰🗞 via @like
🧞♂👣 ከዚም_ከዛም 👣🧞♂
መቆም በቆምክበት ቦታ ብቻ ያለውን ዕድል እንድትጠቀም ያደርግሃል፤ መሄድ ግን የማታውቀውንም ዕድል እንድትሞክር ያረዳሃል። ስትቆም መጀመሪያ ታረጃለህ፣ ቆይቶም ትበሰብሳለህ። ስትሄድ ግን መጀመሪያ ትደክማለህ፣ ቀጥሎ ግን ትጠነክራለህ። ባለቀ ትናንት አትታሰር፣ በተበላ ዛሬ አትወሰን፣ ይልቅ ወደማይታየው ነገ ሂድ። ነገ ወዳንተ ሳይመጣብህ አንተ ወደ ነገ ሂድ። አንድ ቦታ ላይ የግድ እንድንቆም ቢፈለግ ኖሮ እግር ሳይሆን እንደ ዛፍ ሥር ይሰጠን ነበር። የመሄዳችን ዋናው ምክንያቱ የምንቆምበት ምክንያት አለመኖሩ ነው።
#share #participate #comment👇
@R_e_a_d_e_rs
@zhangidaa
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
መቆም በቆምክበት ቦታ ብቻ ያለውን ዕድል እንድትጠቀም ያደርግሃል፤ መሄድ ግን የማታውቀውንም ዕድል እንድትሞክር ያረዳሃል። ስትቆም መጀመሪያ ታረጃለህ፣ ቆይቶም ትበሰብሳለህ። ስትሄድ ግን መጀመሪያ ትደክማለህ፣ ቀጥሎ ግን ትጠነክራለህ። ባለቀ ትናንት አትታሰር፣ በተበላ ዛሬ አትወሰን፣ ይልቅ ወደማይታየው ነገ ሂድ። ነገ ወዳንተ ሳይመጣብህ አንተ ወደ ነገ ሂድ። አንድ ቦታ ላይ የግድ እንድንቆም ቢፈለግ ኖሮ እግር ሳይሆን እንደ ዛፍ ሥር ይሰጠን ነበር። የመሄዳችን ዋናው ምክንያቱ የምንቆምበት ምክንያት አለመኖሩ ነው።
#share #participate #comment👇
@R_e_a_d_e_rs
@zhangidaa
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ካነበብነው📖📜📰🗞 via @like
📓🌓 ቅምሻ 🌗📓 እኒህ የኢራቅ ኩርዶች የሚናገሯቸው ድንቅ አባባሎች ናቸው!
1 ችግሮችን ለመጋፈጥ ካልፈለግህ ችግሮችን እያነገሥካቸው ትሄዳለህ ይላሉ ኩርዶች፡፡ ችግርን ካታለልከው መልሶ ይይዝሃል፤ ከተጋፈጥከው ግን ጥሎህ ይሸሻል የሚል አባባልም አላቸው፡፡
2 የምትሠራው በር ምንጊዜም ልትሄድበት የምትችል መሆኑን አረጋግጥ፡፡ለአንድ ጊዜ መውጫ ብለህ በሩን ከሠራኸው ከበሩ በኋላ ወዴት እንደምትሄድ ግራ ይገባሃል፡፡በሩን ከነ መንገዱ አስበው፡፡መንገዱን ከነ መዳረሻው፤ መዳረሻውንም ከነመቆያው፤መቆያውን ከነ መክረሚያው፡፡
3 ችግርን በመፍትሔ መፍታትና ችግርን በሌላ ችግር ማለፍ ይለያያሉ፡፡ችግርን በችግር ካለፍከፈው ጊዜ እየገዛህ ነው፡፡ችግርን በመፍትሔ ካለፍከው ደግሞ ልብ እየገዛህ ነው፡፡❣️ እናመሠግናለን ❣️
#share #participate #comment
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
1 ችግሮችን ለመጋፈጥ ካልፈለግህ ችግሮችን እያነገሥካቸው ትሄዳለህ ይላሉ ኩርዶች፡፡ ችግርን ካታለልከው መልሶ ይይዝሃል፤ ከተጋፈጥከው ግን ጥሎህ ይሸሻል የሚል አባባልም አላቸው፡፡
2 የምትሠራው በር ምንጊዜም ልትሄድበት የምትችል መሆኑን አረጋግጥ፡፡ለአንድ ጊዜ መውጫ ብለህ በሩን ከሠራኸው ከበሩ በኋላ ወዴት እንደምትሄድ ግራ ይገባሃል፡፡በሩን ከነ መንገዱ አስበው፡፡መንገዱን ከነ መዳረሻው፤ መዳረሻውንም ከነመቆያው፤መቆያውን ከነ መክረሚያው፡፡
3 ችግርን በመፍትሔ መፍታትና ችግርን በሌላ ችግር ማለፍ ይለያያሉ፡፡ችግርን በችግር ካለፍከፈው ጊዜ እየገዛህ ነው፡፡ችግርን በመፍትሔ ካለፍከው ደግሞ ልብ እየገዛህ ነው፡፡❣️ እናመሠግናለን ❣️
#share #participate #comment
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ካነበብነው📖📜📰🗞 via @like
📓🌓 ቅምሻ 🌗📓
ሂንዲዎች ብርሃነ-ሕሊና ለመጎናፀፍ በሺዎች የሚቆጠሩ ሕይወቶችን መኖር ይጠይቃል ይላሉ፤ ቡድሂስቶች ደግሞ እንደ ጉተማ ቡድሃ ያለ ልዕለ-ሰብ ፍጡር እንኳን የሁሉ ነገር አናት ከሆነው የብርሃነ-ሕሊና ደረጃ ላይ ለመድረስ ከመቻሉ በፊት በሚሊዮኖች በሚቆጠሩ ሕይወቶች ውስጥ ኖሮ ማለፍ እንዳለበት ይናገራሉ። በአጠቃላይ ሁሉም ብርሃነ-ሕሊናን መጎናጸፍ በጣም አስቸጋሪ፣ የማይቻልና ረቂቅ፡ ልዕለ-ሀይል ሰብዓዊ ፍጡራን ብቻ የሚታደሉት፡ እጅግ ልፋትን የሚጠይቅ መሆኑን አጥብቀው ያምናሉ። እኔ ግን ብርሃነ-ሕሊና (Enlightenment) በጣም ቀላል፡ እጅግ ቀላል ከሆኑ የተፈጥሮ ክስተቶች አንዱ ነው እላችኋለሁ።
ምንጭ፡ ብርሃነ-ሕሊና, ኦሾ
❣️ እናመሠግናለን ❣️
#share #participate #comment👇
@R_e_a_d_e_rs
@zhangidaa
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ሂንዲዎች ብርሃነ-ሕሊና ለመጎናፀፍ በሺዎች የሚቆጠሩ ሕይወቶችን መኖር ይጠይቃል ይላሉ፤ ቡድሂስቶች ደግሞ እንደ ጉተማ ቡድሃ ያለ ልዕለ-ሰብ ፍጡር እንኳን የሁሉ ነገር አናት ከሆነው የብርሃነ-ሕሊና ደረጃ ላይ ለመድረስ ከመቻሉ በፊት በሚሊዮኖች በሚቆጠሩ ሕይወቶች ውስጥ ኖሮ ማለፍ እንዳለበት ይናገራሉ። በአጠቃላይ ሁሉም ብርሃነ-ሕሊናን መጎናጸፍ በጣም አስቸጋሪ፣ የማይቻልና ረቂቅ፡ ልዕለ-ሀይል ሰብዓዊ ፍጡራን ብቻ የሚታደሉት፡ እጅግ ልፋትን የሚጠይቅ መሆኑን አጥብቀው ያምናሉ። እኔ ግን ብርሃነ-ሕሊና (Enlightenment) በጣም ቀላል፡ እጅግ ቀላል ከሆኑ የተፈጥሮ ክስተቶች አንዱ ነው እላችኋለሁ።
ምንጭ፡ ብርሃነ-ሕሊና, ኦሾ
❣️ እናመሠግናለን ❣️
#share #participate #comment👇
@R_e_a_d_e_rs
@zhangidaa
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ካነበብነው📖📜📰🗞 via @like
😂🌍 ለፈገግታ 🌎😂
"እኔ በግሌ 'ኢትዮጵያ ልታድግ ነው' 😳 ሲባል ፍርሀት ይወረኛል። ምክንያቱም ኢትዮጵያ ባደገች ቁጥር መብላት እያቃተኝ እንደምሄድ አውቀዋለኋ!🤷♂ ኢትዮጵያ 11.5 በመቶ እድገት ባስመዘገበች ቁጥር አንድ ምግብ ላይ 11.5 ጨምሮ ያድራል። ገቢው ግን ከማደጓ በፊት የነበረው ገቢ ነው።"😂😂😂
ምንጭ፦ ይቅርባቹ 😜
❣ እናመሠግናለን ❣
#share #participate #comment
@R_e_a_d_e_rs
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
"እኔ በግሌ 'ኢትዮጵያ ልታድግ ነው' 😳 ሲባል ፍርሀት ይወረኛል። ምክንያቱም ኢትዮጵያ ባደገች ቁጥር መብላት እያቃተኝ እንደምሄድ አውቀዋለኋ!🤷♂ ኢትዮጵያ 11.5 በመቶ እድገት ባስመዘገበች ቁጥር አንድ ምግብ ላይ 11.5 ጨምሮ ያድራል። ገቢው ግን ከማደጓ በፊት የነበረው ገቢ ነው።"😂😂😂
ምንጭ፦ ይቅርባቹ 😜
❣ እናመሠግናለን ❣
#share #participate #comment
@R_e_a_d_e_rs
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ካነበብነው📖📜📰🗞 via @like
🦅🖊 ስነ_ግጥም 🖌🦅
አባት
""""¤¤¤''''""
አባትም ያረግዛል
አባትም ያምጣል
አባትም ይወልዳል
እናት የሞተች ቀን አባት ሴት ይሆናል።
ያውም ከሴት ሴት ማህፀኑ ሰፊ ሲያፈቅር ካንጀቱ
ማለቂያ የሌለው ውቅያኖስ ነው ጡቱ
የአባትነት ፍቅር ልኩንም ላወቀው
እናት የሞተች ቀን አባትም እናት ነው።
~~~~~~~"""""""""""~~~~~~~
❣ እናመሠግናለን ❣
ለአስተያየት፣ እናንተ የፃፋቹት ነገር እንዲሁም እንዲፖሰትሎት የሚፈልጉት ነገር ካለ👉 @R_e_a_d_e_rs ምንጭ የተጠበቀ ነው።
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
አባት
""""¤¤¤''''""
አባትም ያረግዛል
አባትም ያምጣል
አባትም ይወልዳል
እናት የሞተች ቀን አባት ሴት ይሆናል።
ያውም ከሴት ሴት ማህፀኑ ሰፊ ሲያፈቅር ካንጀቱ
ማለቂያ የሌለው ውቅያኖስ ነው ጡቱ
የአባትነት ፍቅር ልኩንም ላወቀው
እናት የሞተች ቀን አባትም እናት ነው።
~~~~~~~"""""""""""~~~~~~~
❣ እናመሠግናለን ❣
ለአስተያየት፣ እናንተ የፃፋቹት ነገር እንዲሁም እንዲፖሰትሎት የሚፈልጉት ነገር ካለ👉 @R_e_a_d_e_rs ምንጭ የተጠበቀ ነው።
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
Forwarded from Quality Button [SCAM]
"ማንበብ አስተውሎትን፣ ጥበብን እና ትዕግስትን ታጎናፅፋለች"
Quality Button
"ማንበብ አስተውሎትን፣ ጥበብን እና ትዕግስትን ታጎናፅፋለች"
ይሄን ለወዳጅ ዘመዶችዎ share በማድረግ የቻናላችን ቤተሰብ አድርጓቸው
❣ እናመሠግናለን ❣
❣ እናመሠግናለን ❣
ካነበብነው📖📜📰🗞 via @like
📓🌓 ቅምሻ 🌗📓
ኃይማኖት ያለ ዕውቀት አሸባሪ ያደርግሃል። ሥልጣን ያለ ዕውቀት አምባገነን ያደርግሃል። ነፃነት ያለ ዕውቀት ሥርዓት አልበኛ እና ሀኬተኛ ያደርጋል። ዕውቀት አልባነት የስህተቶች ሁሉ ስር ናት። ማርከሻው መድሀኒት ትምህርት ነው። በብራዚል እስር ቤት ውስጥ አንድ እስረኛ አንድ መፅሐፍ አንብቦ መጨረሱን ሪፖርት ባደረገ ቁጥር ከእስር ጊዜው ውስጥ አንድ ሳምንት ይቀነስለታል። የትምህርት ምንጩም መጽሐፍ ነው። ዓላማውም ዕውቀት እና ጥበብን መጎንጨት ነው።
ምንጭ፦ ዶ/ር ኬኬ
❣ እናመሠግናለን ❣
ለአስተያየት፣ እናንተ የፃፋቹት ነገር እንዲሁም እንዲፖሰትሎት የሚፈልጉት ነገር ካለ👉 @R_e_a_d_e_rs 👉 @zhangidaa ምንጭ የተጠበቀ ነው።
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ኃይማኖት ያለ ዕውቀት አሸባሪ ያደርግሃል። ሥልጣን ያለ ዕውቀት አምባገነን ያደርግሃል። ነፃነት ያለ ዕውቀት ሥርዓት አልበኛ እና ሀኬተኛ ያደርጋል። ዕውቀት አልባነት የስህተቶች ሁሉ ስር ናት። ማርከሻው መድሀኒት ትምህርት ነው። በብራዚል እስር ቤት ውስጥ አንድ እስረኛ አንድ መፅሐፍ አንብቦ መጨረሱን ሪፖርት ባደረገ ቁጥር ከእስር ጊዜው ውስጥ አንድ ሳምንት ይቀነስለታል። የትምህርት ምንጩም መጽሐፍ ነው። ዓላማውም ዕውቀት እና ጥበብን መጎንጨት ነው።
ምንጭ፦ ዶ/ር ኬኬ
❣ እናመሠግናለን ❣
ለአስተያየት፣ እናንተ የፃፋቹት ነገር እንዲሁም እንዲፖሰትሎት የሚፈልጉት ነገር ካለ👉 @R_e_a_d_e_rs 👉 @zhangidaa ምንጭ የተጠበቀ ነው።
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ካነበብነው📖📜📰🗞 via @like
📓🌓 ቅምሻ 🌗📓
🐎🐎📽 ክፍል አንድ 🎞🐎🐎
የአውሮፓ ሀገራት አፍሪካን በተቀራመቱበት ዘመን ኢጣሊያም ኢትዮጲያን በቅኝ ግዛቷ ለማድረግ መንገድ የሚከፍትላትን የውጫሌ ውል ከአፄ ምኒልክ ጋር ውጫሌ ከተማ ላይ በተወካይዋ አንቶሌኒ መሰረት ተዋዋለች፡፡ ከተደረገው ውል አንቀፅ 17 ግን የአማርኛ እና የኢጣልያንኛ ትርጓሜው የተለያየ ነው፡፡ በአማርኛ የተፃፈው ‹‹ ግርማዊ የኢትዮጲያ ንጉሠ ነገሥት ከአውሮፓ መንግስታት ጋር ግንኙነት ለማድረግ ወይም
ለመነጋገር ሲፈልጉ በግርማዊ የኢጣሊያ ንጉሥ አማካይነት ሊያደርጉ ይችላሉ፡፡›› የሚል ሲሆን የኢጣሊያንኛው ትርጉም ግን እንዲህ የሚል ነበር….‹‹ ግርማዊ የኢትዮጲያ ንጉሠ ነገሥት ከአውሮፓ መንግስታት ጋር ግንኙነት ለማድረግ ወይም ለመነጋር ሲፈልጉ በግርማዊ የኢጣሊያ ንጉሥ አማካይነት ያደርጋሉ፡፡›› የዚህ ፍቺው ኢትዮጲያ በኢጣሊያ ሞግዚት አስተዳደር ስር መሆኗን የሚገልፅ ነው፡፡ ይህንንም
የኢጣሊያ መንግስት ለአውሮፓ መንግስታት በደብዳቤ አሳውቋል፡፡ ይህም በታወቀ ግዜ አንቀፅ 17 ይቅር በሚል አፄ ምኒልክ ከባለሟሎቻቸው ጋር ወሰኑ
በዚህም ሌላ ውል ተፈረመ፡፡ ኮንት አንቶሌኒ ‹ይቅር› የሚለውን ቃል የተረዳው እንዳለ ይቀመጥ አይለወጥ በሚል ነበርና አለመሆኑን ሲረዳ ምኒልክ እልፍኝ ገብቶ ደነፋ፡፡
የኢጣሊያ መንግስት ይህን እንደውርደት ይቆጥራል፡፡ ክብሩን ለማስጠበቅ ጦርነት ያደርጋል፡፡ ክብሩን በጉልበት ያስጠብቃል ብሎ ፎከረ፡፡
~~~ ክፍል ሁለት ይቀጥላል ~~~
❣ እናመሠግናለን ❣
#share #participate #comment
@R_e_a_d_e_rs
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
🐎🐎📽 ክፍል አንድ 🎞🐎🐎
የአውሮፓ ሀገራት አፍሪካን በተቀራመቱበት ዘመን ኢጣሊያም ኢትዮጲያን በቅኝ ግዛቷ ለማድረግ መንገድ የሚከፍትላትን የውጫሌ ውል ከአፄ ምኒልክ ጋር ውጫሌ ከተማ ላይ በተወካይዋ አንቶሌኒ መሰረት ተዋዋለች፡፡ ከተደረገው ውል አንቀፅ 17 ግን የአማርኛ እና የኢጣልያንኛ ትርጓሜው የተለያየ ነው፡፡ በአማርኛ የተፃፈው ‹‹ ግርማዊ የኢትዮጲያ ንጉሠ ነገሥት ከአውሮፓ መንግስታት ጋር ግንኙነት ለማድረግ ወይም
ለመነጋገር ሲፈልጉ በግርማዊ የኢጣሊያ ንጉሥ አማካይነት ሊያደርጉ ይችላሉ፡፡›› የሚል ሲሆን የኢጣሊያንኛው ትርጉም ግን እንዲህ የሚል ነበር….‹‹ ግርማዊ የኢትዮጲያ ንጉሠ ነገሥት ከአውሮፓ መንግስታት ጋር ግንኙነት ለማድረግ ወይም ለመነጋር ሲፈልጉ በግርማዊ የኢጣሊያ ንጉሥ አማካይነት ያደርጋሉ፡፡›› የዚህ ፍቺው ኢትዮጲያ በኢጣሊያ ሞግዚት አስተዳደር ስር መሆኗን የሚገልፅ ነው፡፡ ይህንንም
የኢጣሊያ መንግስት ለአውሮፓ መንግስታት በደብዳቤ አሳውቋል፡፡ ይህም በታወቀ ግዜ አንቀፅ 17 ይቅር በሚል አፄ ምኒልክ ከባለሟሎቻቸው ጋር ወሰኑ
በዚህም ሌላ ውል ተፈረመ፡፡ ኮንት አንቶሌኒ ‹ይቅር› የሚለውን ቃል የተረዳው እንዳለ ይቀመጥ አይለወጥ በሚል ነበርና አለመሆኑን ሲረዳ ምኒልክ እልፍኝ ገብቶ ደነፋ፡፡
የኢጣሊያ መንግስት ይህን እንደውርደት ይቆጥራል፡፡ ክብሩን ለማስጠበቅ ጦርነት ያደርጋል፡፡ ክብሩን በጉልበት ያስጠብቃል ብሎ ፎከረ፡፡
~~~ ክፍል ሁለት ይቀጥላል ~~~
❣ እናመሠግናለን ❣
#share #participate #comment
@R_e_a_d_e_rs
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ካነበብነው📖📜📰🗞 via @like
📓🌓 ቅምሻ 🌗📓
🐎🐎📽 ክፍል ሁለት 🎞🐎🐎
እቴጌ ጣይቱ እንዲህ አሉት… ‹‹የዛሬ ሳምንት አድርገው፡፡ እኔ ሴት ነኝ፡፡ ጦርነት አልወድም፤ ነገር ግን ሀገሬን እንደዚህ ያለ ክብር የሚነካ ዘለፋ ከምትሸከም ጦርነትን እመርጣለሁ፡፡ ሂድ መንገዱን ጨርቅ ያድርግልህ! እግሩን ለጠጠር ደረቱን ለጦር
አስጥቶ ደሙን ለሀገሩ ፍቅር አፍስሶ ለአፈሩ ክብር ለብሶ እሱ ወድቆ ሀገሩን የማያቆም እዚህ ያለ እንዳይመስልህ! ሂድ! የኢትዮጲያን ሰው ባታውቀው ነው፡፡ ለሀገሩ መሞት ማለት ለሀበሻ ጌጡ ነው፡፡ ሂድ ባሻህ ግዜ ተመለስ ተሰናድተን እንጠብቅሃለን፡፡ ያንተን
ወንድነትና የጣይቱን ሴትነትም ያን ግዜ እናየዋለን ሂድ መንገዱን ጨርቅ ያድርግልህ፡፡››
በዚህም የኢትዮጲያና የኢጣሊያ ወዳጅነት ጥያቄው፡ የጦርነቱ አይቀሬነትም ተረጋገጠ።
የኢጣሊያ መንግስት በተወካዩ አማካይነት ኢትዮጲያ ላይ ጦርነት ሲያውጁ አፄ ምኒልክ የኢጣሊያ በጦር መሳሪያም ሆነ በስልጣኔ ከፍ ማለቱ ሳያሸብራቸው ‹‹ቴዎድሮስ በመቅደላ ዮሐንስ በመተማ የሞቱላትን ሀገር እኔም ደሜን አፍስሼ ነፃነቷን አስጠብቃለሁ፡፡ እሞትላታለሁ›› ብለው አዋጅ አወጁ…
‹‹….የሀገሬ ሰው ከአሁን ቀደም የበደልኩህ አይመስለኝም፤ አንተም አላስቀየምሀኝም፡፡ ጉልበት ያለህ በጉልበትህ ዕርዳኝ፤ ጉልበት የሌለህ ለልጅህ ለሚስትህ ለሃይማኖትህ ስትል በሐዘን ዕርዳኝ፡፡ ወስልተህ የቀረህ ግን ኋላ ትጣላኛለህ፤ አልተውህም፡፡
ማርያምን ለዚህ አማላጅ የለኝም..ዘመቻዬ በጥቅምት ነው እና የሸዋ ሰው እስከ ጥቅምት እኩሌታ ድረስ ወረይሉ ከተህ ላግኝህ፡፡››
አዋጁን ተከትሎ ህዝብ ከዳር አስከ ዳር ተመመ፡፡ እቴጌይቱ እንዳሉት ደረቱን ለጥይት እግሩን ለጠጠር ሰጥቶ ሀገሩን ከጠላት ሊታደግ የኢትዮጲያ ህዝብ ከዳር እስከ ዳር ነቅሎ ተነሳ፡፡
~~~ ክፍል ሶስት ይቀጥላል ~~~
❣ እናመሠግናለን ❣
#share #participate #comment
@R_e_a_d_e_rs
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
🐎🐎📽 ክፍል ሁለት 🎞🐎🐎
እቴጌ ጣይቱ እንዲህ አሉት… ‹‹የዛሬ ሳምንት አድርገው፡፡ እኔ ሴት ነኝ፡፡ ጦርነት አልወድም፤ ነገር ግን ሀገሬን እንደዚህ ያለ ክብር የሚነካ ዘለፋ ከምትሸከም ጦርነትን እመርጣለሁ፡፡ ሂድ መንገዱን ጨርቅ ያድርግልህ! እግሩን ለጠጠር ደረቱን ለጦር
አስጥቶ ደሙን ለሀገሩ ፍቅር አፍስሶ ለአፈሩ ክብር ለብሶ እሱ ወድቆ ሀገሩን የማያቆም እዚህ ያለ እንዳይመስልህ! ሂድ! የኢትዮጲያን ሰው ባታውቀው ነው፡፡ ለሀገሩ መሞት ማለት ለሀበሻ ጌጡ ነው፡፡ ሂድ ባሻህ ግዜ ተመለስ ተሰናድተን እንጠብቅሃለን፡፡ ያንተን
ወንድነትና የጣይቱን ሴትነትም ያን ግዜ እናየዋለን ሂድ መንገዱን ጨርቅ ያድርግልህ፡፡››
በዚህም የኢትዮጲያና የኢጣሊያ ወዳጅነት ጥያቄው፡ የጦርነቱ አይቀሬነትም ተረጋገጠ።
የኢጣሊያ መንግስት በተወካዩ አማካይነት ኢትዮጲያ ላይ ጦርነት ሲያውጁ አፄ ምኒልክ የኢጣሊያ በጦር መሳሪያም ሆነ በስልጣኔ ከፍ ማለቱ ሳያሸብራቸው ‹‹ቴዎድሮስ በመቅደላ ዮሐንስ በመተማ የሞቱላትን ሀገር እኔም ደሜን አፍስሼ ነፃነቷን አስጠብቃለሁ፡፡ እሞትላታለሁ›› ብለው አዋጅ አወጁ…
‹‹….የሀገሬ ሰው ከአሁን ቀደም የበደልኩህ አይመስለኝም፤ አንተም አላስቀየምሀኝም፡፡ ጉልበት ያለህ በጉልበትህ ዕርዳኝ፤ ጉልበት የሌለህ ለልጅህ ለሚስትህ ለሃይማኖትህ ስትል በሐዘን ዕርዳኝ፡፡ ወስልተህ የቀረህ ግን ኋላ ትጣላኛለህ፤ አልተውህም፡፡
ማርያምን ለዚህ አማላጅ የለኝም..ዘመቻዬ በጥቅምት ነው እና የሸዋ ሰው እስከ ጥቅምት እኩሌታ ድረስ ወረይሉ ከተህ ላግኝህ፡፡››
አዋጁን ተከትሎ ህዝብ ከዳር አስከ ዳር ተመመ፡፡ እቴጌይቱ እንዳሉት ደረቱን ለጥይት እግሩን ለጠጠር ሰጥቶ ሀገሩን ከጠላት ሊታደግ የኢትዮጲያ ህዝብ ከዳር እስከ ዳር ነቅሎ ተነሳ፡፡
~~~ ክፍል ሶስት ይቀጥላል ~~~
❣ እናመሠግናለን ❣
#share #participate #comment
@R_e_a_d_e_rs
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ካነበብነው📖📜📰🗞 via @like
📓🌓 ቅምሻ 🌗📓
🐎🐎📽 ክፍል ሶስት 🎞🐎🐎
የሩቁንም ሀገር የጎጃሙንም፣ የደንቢያውንም፣ የቋራውንም፣ የበጌምድሩንም ከጨጨሆ በላይ ያለውን አገር ሁሉ አሸንጌ ድረስ ክተት ብለው አዘዙ፡፡ የሰሜንና የወልቃይት ጠገዴንም ሰው መቀሌ ድረስ ክተት ብለው አዘዙ፡፡ ከዚህ በኋላ ራስ መኮንን የሐረርጌን ጦር ይዘው በመስከረም እኩሌታ አዲስ አበባ ገቡ፡፡ ከጊቤ በታች ያለው አገር ጦር የወለጋው ሹም ፊታውራሪ ተክሌ ጦራቸውን ይዘው ገቡ፡፡ አፄ ምኒልክ አዋጃቸውን በመስከረም ወር ካስነገሩ በኋላ ለአገር ጥበቃ አጎታቸውን ራስ ዳርጌ ሣህለ ሥላሴን ሾመው እርሳቸው በጥቅምት 2 ቀን 1888 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ተነስተው በጊዳ በኩል አድርገው ጥቅምት 18 ቀን ወረይሉ ከተማ ገቡ፡፡ ከዚያም ራስ ሚካኤልን፣ ራስ ወሌን፣ ራስ መኮንንን፣ ራስ መንገሻ አቲከምን፣ ራስ አሉላን፣ ዋግሹም ጓንጉልን፣ ደጃች ወልዴን፣ ፊታውራሪ ገበየሁን፣ ፊታውራሪ ተክሌን፣ ሊቀ መኳስ አድነውን፣ ቀኛዝማች ታፈሰን ‹‹ቀድማችሁ ወደ አላጌ ዝመቱ የሚቀላችሁ ከሆነ ወጉት፡፡ የሚከብዳችሁ ከሆነ ላኩብኝ ›› ብለው አስቀድመው መላካቸውን ይነገራል፡፡
ምን አልባትም ይህ አዋጅ ታውጆ የኢትዮጲያ ህዝብ ከዳር እስከ ዳር ተሞ አድዋ ላይ ጣሊያንን ድባቅ ባይመታ ኖሮ የኛ ዕጣ እንደሌሎቹ የአፍሪካ ሀገራት በባርነት ቀንበር ወድቀን በኛ ማንነት ላይ የኢጣሊያ ማንነት ተለጥፎብን እንቀር ነበር፡፡ ለዛም አይደል
‹‹ምኒልክ ተወልዶ ባያነሳ ጋሻ፡ ግብሩ እንቁላል ነበር ይሄን ግዜ ሐበሻ›› የተባለው፡፡
~~~ ክፍል አራት ይቀጥላል ~~~
❣ እናመሠግናለን ❣
#share #participate #comment
@R_e_a_d_e_rs
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
🐎🐎📽 ክፍል ሶስት 🎞🐎🐎
የሩቁንም ሀገር የጎጃሙንም፣ የደንቢያውንም፣ የቋራውንም፣ የበጌምድሩንም ከጨጨሆ በላይ ያለውን አገር ሁሉ አሸንጌ ድረስ ክተት ብለው አዘዙ፡፡ የሰሜንና የወልቃይት ጠገዴንም ሰው መቀሌ ድረስ ክተት ብለው አዘዙ፡፡ ከዚህ በኋላ ራስ መኮንን የሐረርጌን ጦር ይዘው በመስከረም እኩሌታ አዲስ አበባ ገቡ፡፡ ከጊቤ በታች ያለው አገር ጦር የወለጋው ሹም ፊታውራሪ ተክሌ ጦራቸውን ይዘው ገቡ፡፡ አፄ ምኒልክ አዋጃቸውን በመስከረም ወር ካስነገሩ በኋላ ለአገር ጥበቃ አጎታቸውን ራስ ዳርጌ ሣህለ ሥላሴን ሾመው እርሳቸው በጥቅምት 2 ቀን 1888 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ተነስተው በጊዳ በኩል አድርገው ጥቅምት 18 ቀን ወረይሉ ከተማ ገቡ፡፡ ከዚያም ራስ ሚካኤልን፣ ራስ ወሌን፣ ራስ መኮንንን፣ ራስ መንገሻ አቲከምን፣ ራስ አሉላን፣ ዋግሹም ጓንጉልን፣ ደጃች ወልዴን፣ ፊታውራሪ ገበየሁን፣ ፊታውራሪ ተክሌን፣ ሊቀ መኳስ አድነውን፣ ቀኛዝማች ታፈሰን ‹‹ቀድማችሁ ወደ አላጌ ዝመቱ የሚቀላችሁ ከሆነ ወጉት፡፡ የሚከብዳችሁ ከሆነ ላኩብኝ ›› ብለው አስቀድመው መላካቸውን ይነገራል፡፡
ምን አልባትም ይህ አዋጅ ታውጆ የኢትዮጲያ ህዝብ ከዳር እስከ ዳር ተሞ አድዋ ላይ ጣሊያንን ድባቅ ባይመታ ኖሮ የኛ ዕጣ እንደሌሎቹ የአፍሪካ ሀገራት በባርነት ቀንበር ወድቀን በኛ ማንነት ላይ የኢጣሊያ ማንነት ተለጥፎብን እንቀር ነበር፡፡ ለዛም አይደል
‹‹ምኒልክ ተወልዶ ባያነሳ ጋሻ፡ ግብሩ እንቁላል ነበር ይሄን ግዜ ሐበሻ›› የተባለው፡፡
~~~ ክፍል አራት ይቀጥላል ~~~
❣ እናመሠግናለን ❣
#share #participate #comment
@R_e_a_d_e_rs
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ካነበብነው📖📜📰🗞 via @like
📓🌓 ቅምሻ 🌗📓
🐎🐎📽 ክፍል አራት 🎞🐎🐎
የአድዋ ጦርነት የተጀመረው የካቲት 23 ቀን 1988 ዓ.ም ከማለዳው 11 ሰዓት ከ 32 ደቂቃ ላይ ነበር፡፡ የጄኔራል አልቤርቶኔ ክፍለ ጦር በፊታውራሪ ገበየሁ፣ በዋግሹም ጓንጉል፣ በራስ ሚካኤል እና በራስ መንገሻ ጦር ላይ በሰነዘረው ጥቃት ተከፈተ፡፡ የንጉሰ ነገስቱ ሠራዊት የመሐል ጦር አዛዥ ፊታውራሪ ገበየሁ በዚህ ከጣሊያኖች ጋር በተደረገው ጦርነት የተመሰከረለት ጀግና ነበር፡፡ ጎራዴውን መዞ በዋናው የትግል አውድማ ላይ ተወርውሮ ገባ፡፡ በዚህም ጊዜ በጠመንጃ ጥይት ተመትቶ ህይወቱ አለፈ፡፡ በገበየሁ መሞት ተሸብሮ የነበረው የኢትዮጵያ ወታደር ወድያው መልሶ ተረጋጋ፡፡ በታላቅ ቆራራጥነት አልቤርቶኔን እንደገና ገጠመው፡፡ በ4 ሰዓት አከባቢ ላይ አልቤርቶኔ ከመኮንኖቹ አብዛኞቹን አጥቷል፡፡ በጦርነቱ እንደተሸነፈ ግልፅ ነበር፡፡ የኢጣሊያ ወታደሮች በድንጋጤ ተውጠው ፈረጠጡ፡፡ ከፊሉ ተማረከ፡ የቀረውም ወደ ሌሎቹ
ክፍላተ ጦር በመሸሽ ራሱን አተረፈ፡፡ በዚህ ጊዜ ያልተነካው ክፍል የሚይዘውን አጥቶ ይተራመስ ገባ፡፡ በዚህ ሰዓት ቀጥታ በአጼ ምኒሊክ የሚታዘዘው ጦር ከውጊያው ገባ፡፡ በጦርነቱ ወቅት አጼ ምንሊክ በትክክል ወዴት እንደሚገኙ ጣልያኖች አያውቁም ነበር፡፡ ሁልጊዜ ሳይለዩት አብረውት ከሚገኙት ሁለት ሊቀመኳሶች አንዱ በአለባበሱ ንጉሱን መስሎ በስፍራው ይገኛል፡፡ ከሊቀመኳስ ተግባሮች ውስጥ አንዱ የጠላትን ትኩረት ወደ እሱ በመሳብ ንጉሰ ነገስቱን መጠበቅ ነው፡፡ በጦርነቱ ስፍራ አጼምኒሊክ እንደ አንድ ተራ ወታደር ለብሶ በጦርነቱ መሃከል ተገኝቶ ያዋጋም ይዋጋም ነበር፡፡
ቀኑን ሙሉ ውጊያ ሆኖ ከምሽቱ ዐስራ ሁለት ሰዓት ላይ ድሉ 🇪🇹🇪🇹🇪🇹የኢትዮጲያ🇪🇹🇪🇹🇪🇹 መሆኑ ታወቀ፡፡
~~~ ክፍል አምስት ይቀጥላል ~~~
❣ እናመሠግናለን ❣
#share #participate #comment
@R_e_a_d_e_rs
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
🐎🐎📽 ክፍል አራት 🎞🐎🐎
የአድዋ ጦርነት የተጀመረው የካቲት 23 ቀን 1988 ዓ.ም ከማለዳው 11 ሰዓት ከ 32 ደቂቃ ላይ ነበር፡፡ የጄኔራል አልቤርቶኔ ክፍለ ጦር በፊታውራሪ ገበየሁ፣ በዋግሹም ጓንጉል፣ በራስ ሚካኤል እና በራስ መንገሻ ጦር ላይ በሰነዘረው ጥቃት ተከፈተ፡፡ የንጉሰ ነገስቱ ሠራዊት የመሐል ጦር አዛዥ ፊታውራሪ ገበየሁ በዚህ ከጣሊያኖች ጋር በተደረገው ጦርነት የተመሰከረለት ጀግና ነበር፡፡ ጎራዴውን መዞ በዋናው የትግል አውድማ ላይ ተወርውሮ ገባ፡፡ በዚህም ጊዜ በጠመንጃ ጥይት ተመትቶ ህይወቱ አለፈ፡፡ በገበየሁ መሞት ተሸብሮ የነበረው የኢትዮጵያ ወታደር ወድያው መልሶ ተረጋጋ፡፡ በታላቅ ቆራራጥነት አልቤርቶኔን እንደገና ገጠመው፡፡ በ4 ሰዓት አከባቢ ላይ አልቤርቶኔ ከመኮንኖቹ አብዛኞቹን አጥቷል፡፡ በጦርነቱ እንደተሸነፈ ግልፅ ነበር፡፡ የኢጣሊያ ወታደሮች በድንጋጤ ተውጠው ፈረጠጡ፡፡ ከፊሉ ተማረከ፡ የቀረውም ወደ ሌሎቹ
ክፍላተ ጦር በመሸሽ ራሱን አተረፈ፡፡ በዚህ ጊዜ ያልተነካው ክፍል የሚይዘውን አጥቶ ይተራመስ ገባ፡፡ በዚህ ሰዓት ቀጥታ በአጼ ምኒሊክ የሚታዘዘው ጦር ከውጊያው ገባ፡፡ በጦርነቱ ወቅት አጼ ምንሊክ በትክክል ወዴት እንደሚገኙ ጣልያኖች አያውቁም ነበር፡፡ ሁልጊዜ ሳይለዩት አብረውት ከሚገኙት ሁለት ሊቀመኳሶች አንዱ በአለባበሱ ንጉሱን መስሎ በስፍራው ይገኛል፡፡ ከሊቀመኳስ ተግባሮች ውስጥ አንዱ የጠላትን ትኩረት ወደ እሱ በመሳብ ንጉሰ ነገስቱን መጠበቅ ነው፡፡ በጦርነቱ ስፍራ አጼምኒሊክ እንደ አንድ ተራ ወታደር ለብሶ በጦርነቱ መሃከል ተገኝቶ ያዋጋም ይዋጋም ነበር፡፡
ቀኑን ሙሉ ውጊያ ሆኖ ከምሽቱ ዐስራ ሁለት ሰዓት ላይ ድሉ 🇪🇹🇪🇹🇪🇹የኢትዮጲያ🇪🇹🇪🇹🇪🇹 መሆኑ ታወቀ፡፡
~~~ ክፍል አምስት ይቀጥላል ~~~
❣ እናመሠግናለን ❣
#share #participate #comment
@R_e_a_d_e_rs
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
📓🌓 ቅምሻ 🌗📓
🐎🐎📽 ክፍል አምስት 🎞🐎🐎
በአድዋው ጦርነት እቴጌ ጣይቱ ብጡል የኢትዮጵያን ጦር በሞራል በማነቃቃትና በማበረታት እንዲሁም ሠራዊቱን እግር በእግር እየተከተሉ በፉከራ ያበረታቱ ነበር፡፡
እቴጌ ጣይቱ ጥቁር ጥላ አስይዘው ዓይነ ርግባቸውን ገልጠው በእግር እየተራመዱ በንጉሠ ነገሥቱ ልጅ ወ/ሮ ዘውዲቱና በደንገጡሮቻቸው ታጅበው ከወታደሩ ጎን
ተሰልፈው ነበር፡፡ የኋላው ወታደር ሲያመነታ ‹ በርታ ምን ሆነሃል ድሉ የእኛ ነውና በለው› ብለው ይናገራሉ፡፡ ወንድ ሴት ሲያበረታው መሸሽ አይሆንለትምና ሁሉም በወኔና በጀግንነት ወደፊት ገፋ፡፡ እቴጌይቱም በዚህ ቀን የሴትነት ባሕሪያቸውን ትተው እንደ ወንድ ወታደሮቻቸውን በቀኝና በግራ አሰልፈው ወደ ጦርነቱ ገቡ፡፡ መድፈኞቻቸውንም በቀኛቸው በኩል ጠምደው እየተኮሱ በመካከል የሚዋጋውን የጠላት ጦር ይቆሉት ጀመር፡፡
በየካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም መላው የኢትዮጲያ ህዝብ በአፄ ምኒልክ እና እቴጌ ጣይቱ አጋፋሪነት በባዶ እግሩ አድዋ ዘምቶ ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ድል አደረገ፡፡ይህም ኢትዮጲያን አንድ የማድረጉን ዘመቻ ቋጨው፡፡ ወደ ማዕከላዊ መንግስት ለመጠቃለል እምቢተኛ የነበሩት ገዦች ለሀገራቸው ክብር ከሚቃወሟቸው አፄ ምኒልክ ጎን ተሰልፈው ጠላትን ድባቅ መቱት፡፡ ይህም ያ ትውልድ በተሻለ መልኩ በጎሳና በሃይማኖት ሳይለያይ ስለ ሀገር ፍቅር ስለ ክብርና ስለ ነፃነት ስለ መብት ያወቀና የተረዳ መሆኑን አስረግጦ ያስረዳናል፡፡
❣ እናመሠግናለን ❣
#share #participate #comment
@R_e_a_d_e_rs
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
🐎🐎📽 ክፍል አምስት 🎞🐎🐎
በአድዋው ጦርነት እቴጌ ጣይቱ ብጡል የኢትዮጵያን ጦር በሞራል በማነቃቃትና በማበረታት እንዲሁም ሠራዊቱን እግር በእግር እየተከተሉ በፉከራ ያበረታቱ ነበር፡፡
እቴጌ ጣይቱ ጥቁር ጥላ አስይዘው ዓይነ ርግባቸውን ገልጠው በእግር እየተራመዱ በንጉሠ ነገሥቱ ልጅ ወ/ሮ ዘውዲቱና በደንገጡሮቻቸው ታጅበው ከወታደሩ ጎን
ተሰልፈው ነበር፡፡ የኋላው ወታደር ሲያመነታ ‹ በርታ ምን ሆነሃል ድሉ የእኛ ነውና በለው› ብለው ይናገራሉ፡፡ ወንድ ሴት ሲያበረታው መሸሽ አይሆንለትምና ሁሉም በወኔና በጀግንነት ወደፊት ገፋ፡፡ እቴጌይቱም በዚህ ቀን የሴትነት ባሕሪያቸውን ትተው እንደ ወንድ ወታደሮቻቸውን በቀኝና በግራ አሰልፈው ወደ ጦርነቱ ገቡ፡፡ መድፈኞቻቸውንም በቀኛቸው በኩል ጠምደው እየተኮሱ በመካከል የሚዋጋውን የጠላት ጦር ይቆሉት ጀመር፡፡
በየካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም መላው የኢትዮጲያ ህዝብ በአፄ ምኒልክ እና እቴጌ ጣይቱ አጋፋሪነት በባዶ እግሩ አድዋ ዘምቶ ዘመናዊ የጦር መሳሪያ የታጠቀውን የኢጣሊያ ጦር ድል አደረገ፡፡ይህም ኢትዮጲያን አንድ የማድረጉን ዘመቻ ቋጨው፡፡ ወደ ማዕከላዊ መንግስት ለመጠቃለል እምቢተኛ የነበሩት ገዦች ለሀገራቸው ክብር ከሚቃወሟቸው አፄ ምኒልክ ጎን ተሰልፈው ጠላትን ድባቅ መቱት፡፡ ይህም ያ ትውልድ በተሻለ መልኩ በጎሳና በሃይማኖት ሳይለያይ ስለ ሀገር ፍቅር ስለ ክብርና ስለ ነፃነት ስለ መብት ያወቀና የተረዳ መሆኑን አስረግጦ ያስረዳናል፡፡
❣ እናመሠግናለን ❣
#share #participate #comment
@R_e_a_d_e_rs
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚