📓🌓 ቅምሻ 🌗📓
"መግባትና መውጣት" ከተሰኘው የ 'በዕውቀቱ ሥዩም' መጽሐፍ የተቆነጠረ...
📖📖📖
ቀኑ ደመናማ በመሆኑ፣ ፀሐይዋ ያለውትሮዋ በመራቋ አውሮፕላን ጀርባ ላይ ካልተሰጣ በቀር የረጠበው ልብሴ እንደማይደርቅ ገባኝ ይሁን እንጂ ወዲያው ብልሃት መጣልኝ ። መንገዱ ዳር ወደሚገኝ ካፌ ገብቼ ትኩስ ነገር ለመውሰድ ለመውሰድ አሰብሁ። ሆዴ በጣም ከሞቀ ቢያንስ ካናቴራዬ ይደርቃል። ገባሁና አስተናጋጇን ጠርቼ ጦመኛ ስለ ሆንኩ ሻይ እና ችብስ እንዲያመጣልኝ ነገርሁት። አሻግሬ ወደ ውጭ መመልከት ጀመርሁ ። ማዶ ካለው አሮጌ አጥር ሥር አንድ መጽሐፍ አዟሪ ጎረምሳ ብልቱን በጳውሎስ ኞኞ መጽሐፍ ጋርዶ ሽንቱን ይሸናል ። እየሸና ሰው አየኝ አላየኝ ብሎ ሲገላመጥ ከእኔ ጋራ ተገጣጠምንና በእጄ ምልክት ጠራሁት ። ሽንቱን ሳይቋጭ ተንደርድሮ ገባ ። አንዱን መጽሐፍ እየመዘዝሁ ፣ "በቢንላደን ላይ መጽሐፍ ጽፈውበት ነው?" ብዬ ጠየቅሁት ።
፧
"ቢንላደን አይደለም፤ ኦሾ ነው!" አለኝ አዟሪው እየሳቀ ። ከኦሾ መጽሐፍ ለናሙና ሁለት አንቀጽ አንብቤ የእግዜርን ህልውና ስለ ተጠራጠርሁ፣ አስተናጋጁ ችብሱን ትቶ ጥብስ እንዲያመጣልኝ ነገርሁት ። ጥብሱ በጣም ጥሩ ነበር ። ብዙ ሬስቶራንቶች ውስጥ እንደሚታየው በጥብሱ ውስጥ ፀጉር አላገኘሁም ። ጥብሱን ያዘጋጀው ሼፍ መላጣ ሳይሆን አይቀርም ።
፧
ከካፍቴርያው ከወጣሁ በኋላ ሳልፈልግ ራሴን ከአስተናጋጁ ጋር ማነጻጸር ጀመርሁ ። ልጁ በመልኩ እና በዩኒፎርሙ ጥራት ይበልጠኛል ። በተጨማሪም ኮካ በትከሻው ላይ አስቀምጦ መክፈት ይችልበታል ። በርግጥ ኮካን ትከሻህም ላይ ክፈተው፣ ጠረጴዛ ላይ ጣዕሙን አይቀይረውም ። ግን በቃ ተስተናጋጁ ኮካ አዝዞ የሰርከስ ትርኢት ይመረቅለታል ። አስተናጋጁ በዚህ ረገድ ሊደነቅ ይገባል ። በሒሳብ ግን አይደርስብኝም ፤ የእኔን ጨምሮ የሦስት ደንበኞችን ሒሰብ ሲሳሳት አይቻለሁ ። ይህ ሰው በባቄላ ፍሬ ሲያሰላ ያደገ ሳይሆን አይቀርም ብዬ አሰብሁ ። ጓደኛዬ ... እንደነገረኝ የጥንት ኢትዮጵያውያን በጦርነት የተሞላ ኑሯቸው የሒሳብ ዕውቀታቸውን ለማዳበር ጊዜ ስላልሰጣቸው መደመር እና መቀነስን የሚሰሩት የባቄላ ፍሬን በመጠቀም ነበር ። ነገሩ እውነት ከሆነ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የባቄላ ዝምድና ከአተር ጋር ብቻ ሳይሆን ከካልኩሌተር ጋር ጭምር ነው ።
📄📄📄
ምንጭ 📚 "መግባትና መውጣት" ገጽ 10-12
ደራሲ 🖊 በዕውቀቱ ሥዩም
❣ THANK YOU ❣
#share #participate #comment👇
@R_e_a_d_e_rs
@zhangidaa
@infho
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ከወደዱት ለወዳጆ ያጋሩ
https://t.me/Readers_To_Know/281
"መግባትና መውጣት" ከተሰኘው የ 'በዕውቀቱ ሥዩም' መጽሐፍ የተቆነጠረ...
📖📖📖
ቀኑ ደመናማ በመሆኑ፣ ፀሐይዋ ያለውትሮዋ በመራቋ አውሮፕላን ጀርባ ላይ ካልተሰጣ በቀር የረጠበው ልብሴ እንደማይደርቅ ገባኝ ይሁን እንጂ ወዲያው ብልሃት መጣልኝ ። መንገዱ ዳር ወደሚገኝ ካፌ ገብቼ ትኩስ ነገር ለመውሰድ ለመውሰድ አሰብሁ። ሆዴ በጣም ከሞቀ ቢያንስ ካናቴራዬ ይደርቃል። ገባሁና አስተናጋጇን ጠርቼ ጦመኛ ስለ ሆንኩ ሻይ እና ችብስ እንዲያመጣልኝ ነገርሁት። አሻግሬ ወደ ውጭ መመልከት ጀመርሁ ። ማዶ ካለው አሮጌ አጥር ሥር አንድ መጽሐፍ አዟሪ ጎረምሳ ብልቱን በጳውሎስ ኞኞ መጽሐፍ ጋርዶ ሽንቱን ይሸናል ። እየሸና ሰው አየኝ አላየኝ ብሎ ሲገላመጥ ከእኔ ጋራ ተገጣጠምንና በእጄ ምልክት ጠራሁት ። ሽንቱን ሳይቋጭ ተንደርድሮ ገባ ። አንዱን መጽሐፍ እየመዘዝሁ ፣ "በቢንላደን ላይ መጽሐፍ ጽፈውበት ነው?" ብዬ ጠየቅሁት ።
፧
"ቢንላደን አይደለም፤ ኦሾ ነው!" አለኝ አዟሪው እየሳቀ ። ከኦሾ መጽሐፍ ለናሙና ሁለት አንቀጽ አንብቤ የእግዜርን ህልውና ስለ ተጠራጠርሁ፣ አስተናጋጁ ችብሱን ትቶ ጥብስ እንዲያመጣልኝ ነገርሁት ። ጥብሱ በጣም ጥሩ ነበር ። ብዙ ሬስቶራንቶች ውስጥ እንደሚታየው በጥብሱ ውስጥ ፀጉር አላገኘሁም ። ጥብሱን ያዘጋጀው ሼፍ መላጣ ሳይሆን አይቀርም ።
፧
ከካፍቴርያው ከወጣሁ በኋላ ሳልፈልግ ራሴን ከአስተናጋጁ ጋር ማነጻጸር ጀመርሁ ። ልጁ በመልኩ እና በዩኒፎርሙ ጥራት ይበልጠኛል ። በተጨማሪም ኮካ በትከሻው ላይ አስቀምጦ መክፈት ይችልበታል ። በርግጥ ኮካን ትከሻህም ላይ ክፈተው፣ ጠረጴዛ ላይ ጣዕሙን አይቀይረውም ። ግን በቃ ተስተናጋጁ ኮካ አዝዞ የሰርከስ ትርኢት ይመረቅለታል ። አስተናጋጁ በዚህ ረገድ ሊደነቅ ይገባል ። በሒሳብ ግን አይደርስብኝም ፤ የእኔን ጨምሮ የሦስት ደንበኞችን ሒሰብ ሲሳሳት አይቻለሁ ። ይህ ሰው በባቄላ ፍሬ ሲያሰላ ያደገ ሳይሆን አይቀርም ብዬ አሰብሁ ። ጓደኛዬ ... እንደነገረኝ የጥንት ኢትዮጵያውያን በጦርነት የተሞላ ኑሯቸው የሒሳብ ዕውቀታቸውን ለማዳበር ጊዜ ስላልሰጣቸው መደመር እና መቀነስን የሚሰሩት የባቄላ ፍሬን በመጠቀም ነበር ። ነገሩ እውነት ከሆነ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የባቄላ ዝምድና ከአተር ጋር ብቻ ሳይሆን ከካልኩሌተር ጋር ጭምር ነው ።
📄📄📄
ምንጭ 📚 "መግባትና መውጣት" ገጽ 10-12
ደራሲ 🖊 በዕውቀቱ ሥዩም
❣ THANK YOU ❣
#share #participate #comment👇
@R_e_a_d_e_rs
@zhangidaa
@infho
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ከወደዱት ለወዳጆ ያጋሩ
https://t.me/Readers_To_Know/281
Telegram
ካነበብነው📖📜📰🗞
🌲🎄 ገናችን 🎄🌲
“በገና ጨዋታ አይቆጡም ጌታ” እየተባለ እንደሚጨፈረው ሁሉ፣ ቂምና በቀል በገና ጨዋታ አይታሰብም፡፡ ከጨዋታው በኋላ መብል መጠጡ ተሰናድቶ፣ ድግሥ ላይ ጌታውም ሎሌውም እኩል ይቀጣሉ፡፡ አብረው ይበላሉ። አብረው ይጠጣሉ፡፡ ይህን ልምድ ደራሲና ጋዜጠኛ መምህር ካህሳይ ገ/እግዚአብሔር፤ ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ውልደት ጋር በማቆራኘት ያብራሩታል፡-
“የኢየሱስ ውልደትም የሰውን ልጅ እኩልነት…
“በገና ጨዋታ አይቆጡም ጌታ” እየተባለ እንደሚጨፈረው ሁሉ፣ ቂምና በቀል በገና ጨዋታ አይታሰብም፡፡ ከጨዋታው በኋላ መብል መጠጡ ተሰናድቶ፣ ድግሥ ላይ ጌታውም ሎሌውም እኩል ይቀጣሉ፡፡ አብረው ይበላሉ። አብረው ይጠጣሉ፡፡ ይህን ልምድ ደራሲና ጋዜጠኛ መምህር ካህሳይ ገ/እግዚአብሔር፤ ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ውልደት ጋር በማቆራኘት ያብራሩታል፡-
“የኢየሱስ ውልደትም የሰውን ልጅ እኩልነት…
🦅🖊 ስነ_ግጥም 🖌🦅
ጐጆ ቤት
....
ሀገርስ ጐጆ ናት !!!
መሪዋም ምሰሶ
ሹማምንቷም ማገር
አንዳንዶቹም ቋሚ
ሌሎቹም ወጋግራ
ሰራዊቷም አጥር!
ሀገርስ ጐጆ ናት !!!
ሕዝቡም ክዳን ሆኖ
ጐጆውን አልብሶ
እንደሳር ቢቀጥን፤ ቢኖር ተራ መስሎ
ከዝናብ ያድናል፤ ውርጩን አሰናብቶ
ፀሃይን ይከላል፤ በጥላው ከልሎ…
ሀገርስ ጐጆ ናት !!!
እውነትም ጐጆ ናት
ሊቃውንቷም እሣት
ላንዱ ጭስ ሲደርሰው
ለሌላው ትኩሣት፡፡
ምሰሶው ቢተልቅ - መሪው ገዝፎ ቢታይ
ጐጆው ከቶ አይሞቅም - ካልጫሩበት እሣት
ጐጆው ቤት አይሆንም - ሳር ከሌለው በአናት…
… ሀገርስ ጐጆ ናት !!!...
..
(እንዳለጌታ ከበደ፣ልብ ሲበርደው፣2000)
❣️ THANK YOU ❣️
#share #participate #comment👇
@R_e_a_d_e_rs
@zhangidaa
@infho
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ከወደዱት ለወዳጆ ያጋሩ
https://t.me/Readers_To_Know/281
ጐጆ ቤት
....
ሀገርስ ጐጆ ናት !!!
መሪዋም ምሰሶ
ሹማምንቷም ማገር
አንዳንዶቹም ቋሚ
ሌሎቹም ወጋግራ
ሰራዊቷም አጥር!
ሀገርስ ጐጆ ናት !!!
ሕዝቡም ክዳን ሆኖ
ጐጆውን አልብሶ
እንደሳር ቢቀጥን፤ ቢኖር ተራ መስሎ
ከዝናብ ያድናል፤ ውርጩን አሰናብቶ
ፀሃይን ይከላል፤ በጥላው ከልሎ…
ሀገርስ ጐጆ ናት !!!
እውነትም ጐጆ ናት
ሊቃውንቷም እሣት
ላንዱ ጭስ ሲደርሰው
ለሌላው ትኩሣት፡፡
ምሰሶው ቢተልቅ - መሪው ገዝፎ ቢታይ
ጐጆው ከቶ አይሞቅም - ካልጫሩበት እሣት
ጐጆው ቤት አይሆንም - ሳር ከሌለው በአናት…
… ሀገርስ ጐጆ ናት !!!...
..
(እንዳለጌታ ከበደ፣ልብ ሲበርደው፣2000)
❣️ THANK YOU ❣️
#share #participate #comment👇
@R_e_a_d_e_rs
@zhangidaa
@infho
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ከወደዱት ለወዳጆ ያጋሩ
https://t.me/Readers_To_Know/281
Telegram
ካነበብነው📖📜📰🗞
🌲🎄 ገናችን 🎄🌲
“በገና ጨዋታ አይቆጡም ጌታ” እየተባለ እንደሚጨፈረው ሁሉ፣ ቂምና በቀል በገና ጨዋታ አይታሰብም፡፡ ከጨዋታው በኋላ መብል መጠጡ ተሰናድቶ፣ ድግሥ ላይ ጌታውም ሎሌውም እኩል ይቀጣሉ፡፡ አብረው ይበላሉ። አብረው ይጠጣሉ፡፡ ይህን ልምድ ደራሲና ጋዜጠኛ መምህር ካህሳይ ገ/እግዚአብሔር፤ ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ውልደት ጋር በማቆራኘት ያብራሩታል፡-
“የኢየሱስ ውልደትም የሰውን ልጅ እኩልነት…
“በገና ጨዋታ አይቆጡም ጌታ” እየተባለ እንደሚጨፈረው ሁሉ፣ ቂምና በቀል በገና ጨዋታ አይታሰብም፡፡ ከጨዋታው በኋላ መብል መጠጡ ተሰናድቶ፣ ድግሥ ላይ ጌታውም ሎሌውም እኩል ይቀጣሉ፡፡ አብረው ይበላሉ። አብረው ይጠጣሉ፡፡ ይህን ልምድ ደራሲና ጋዜጠኛ መምህር ካህሳይ ገ/እግዚአብሔር፤ ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ውልደት ጋር በማቆራኘት ያብራሩታል፡-
“የኢየሱስ ውልደትም የሰውን ልጅ እኩልነት…
ካነበብነው📖📜📰🗞 via @like
💫🌪 ጥቆማ 🌪💫
በአብዲሳ ቶላ የተተረጎመው " ሳፒያንስ "
ከጦር ውርወራ እስከ ተወንጫፊ ኒዩክለር ሚሳይሎች የተደረገ የዘረ ሰብ ጉዞ
የሰው ልጆች ሥነ ልቦና፣ ኢኮኖሚ፣ ሐይማኖት፣ ፖለቲካ፣ ሳይንስ… ከጥንታዊው የአደንና ቅርሚያ ህይወት እስከ ዘመናችን የካፒታሊስትሥርዓት የተዳሰሰበት፡፡
---------------!!----------------------------
ከዛሬ 3.8 ቢሊየን ዓመታት በፊት፣ መሬት በምትባል ፈለክ ላይ፣ አንዳንድ ሞለኪሎች ውህደቶችን በማካሄድ ውስብስብ የሆነ ዘአካል ወይም ኦርጋኒዝም አስገኙ፤ የነዚህ ዘአካሎች አፈጣጠርና እንቅስቃሴ ሥነ-ህይወት ወይም ባዮሎጂ ይባላል፡፡
ሰው በታሪክ ሂደት ውስጥ ሦስት ወሳኝ የሚባሉ አብዮቶችን አካሂዷል፡፡ እነኝህም ከ70,000 ዓመታት በፊት ሰው ከልምዱ እየተማረና እያወቀ - ይህንን እውቀቱን ደግሞ ማከማቸት የጀመረበት ኮግኒቲቭ ሪቮሊሽን (Cognitive Revolution) የሚባለው፣ ከ12,000 ዓመታት በፊት የጀመረው የግብርና አብዮት (Agricultural Revolution) እንዲሁም ከ500 ዓመታት በፊት ጀምሮ ማካሄድ የጀመረው የሳይንስ አብዮት (Scientific Revolution) ናቸው፡፡ ይህ መጽሐፍ እነኝህ ሦስት አብዮቶች በዘረ ሰብና ሌሎች ዘአካሎች ላይ ስላደረሱት ተጽእኖ የሚተርክ ነው፡፡
አንብቡት ብዙ ቁም ነገር አለው።
❣️ THANK YOU ❣️
#share #participate #comment👇
@R_e_a_d_e_rs
@zhangidaa
@infho
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
በአብዲሳ ቶላ የተተረጎመው " ሳፒያንስ "
ከጦር ውርወራ እስከ ተወንጫፊ ኒዩክለር ሚሳይሎች የተደረገ የዘረ ሰብ ጉዞ
የሰው ልጆች ሥነ ልቦና፣ ኢኮኖሚ፣ ሐይማኖት፣ ፖለቲካ፣ ሳይንስ… ከጥንታዊው የአደንና ቅርሚያ ህይወት እስከ ዘመናችን የካፒታሊስትሥርዓት የተዳሰሰበት፡፡
---------------!!----------------------------
ከዛሬ 3.8 ቢሊየን ዓመታት በፊት፣ መሬት በምትባል ፈለክ ላይ፣ አንዳንድ ሞለኪሎች ውህደቶችን በማካሄድ ውስብስብ የሆነ ዘአካል ወይም ኦርጋኒዝም አስገኙ፤ የነዚህ ዘአካሎች አፈጣጠርና እንቅስቃሴ ሥነ-ህይወት ወይም ባዮሎጂ ይባላል፡፡
ሰው በታሪክ ሂደት ውስጥ ሦስት ወሳኝ የሚባሉ አብዮቶችን አካሂዷል፡፡ እነኝህም ከ70,000 ዓመታት በፊት ሰው ከልምዱ እየተማረና እያወቀ - ይህንን እውቀቱን ደግሞ ማከማቸት የጀመረበት ኮግኒቲቭ ሪቮሊሽን (Cognitive Revolution) የሚባለው፣ ከ12,000 ዓመታት በፊት የጀመረው የግብርና አብዮት (Agricultural Revolution) እንዲሁም ከ500 ዓመታት በፊት ጀምሮ ማካሄድ የጀመረው የሳይንስ አብዮት (Scientific Revolution) ናቸው፡፡ ይህ መጽሐፍ እነኝህ ሦስት አብዮቶች በዘረ ሰብና ሌሎች ዘአካሎች ላይ ስላደረሱት ተጽእኖ የሚተርክ ነው፡፡
አንብቡት ብዙ ቁም ነገር አለው።
❣️ THANK YOU ❣️
#share #participate #comment👇
@R_e_a_d_e_rs
@zhangidaa
@infho
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
🔑 ቅምሻ 🔑
🦅 ክፍል አስራ አምስት 🦅
" የሶለን ማስታወሻ "
"............ ሞት ግን ምንድነው? የማይለመድ የማይዳሰስ። ሞትን ለማቆም ካልሆነም ለማዘግየት የማይደረግ ነገር የለም። ሞት መለያየት መሆኑ ከባድ እንደሚያደርገው ግልጽ ነው። በተጨማሪም የምንሞትበትን ቀንና ሰዓት አለማወቃችን ነው ሞትን ምስጢር የሚያደርገው። ተሒዶ የሚመጣበት የደርሶ መልስ ቲኬት ያለው ቢሆን ምን አልባት ያንን ያህል ግራ አያጋባንም ነበር። ወይስ ለመሞት ስላልተፈጠርን ይሆን ሞትን እንደሸሸን የምንሞተው? ከሞተም በኋላ ሰው ህይወት ቢኖር ብሎ ይናፍቃል። ሥቃይም ይኖር ይሆን ብሎ ይሰጋል፤ ይህም የጽድቅንና የኩነኔን ጉዳይ በቀላሉ የማይተው ጉዳይ ያደርገዋል። ....
🦅 ክፍል አስራ አምስት 🦅
" የሶለን ማስታወሻ "
"............ ሞት ግን ምንድነው? የማይለመድ የማይዳሰስ። ሞትን ለማቆም ካልሆነም ለማዘግየት የማይደረግ ነገር የለም። ሞት መለያየት መሆኑ ከባድ እንደሚያደርገው ግልጽ ነው። በተጨማሪም የምንሞትበትን ቀንና ሰዓት አለማወቃችን ነው ሞትን ምስጢር የሚያደርገው። ተሒዶ የሚመጣበት የደርሶ መልስ ቲኬት ያለው ቢሆን ምን አልባት ያንን ያህል ግራ አያጋባንም ነበር። ወይስ ለመሞት ስላልተፈጠርን ይሆን ሞትን እንደሸሸን የምንሞተው? ከሞተም በኋላ ሰው ህይወት ቢኖር ብሎ ይናፍቃል። ሥቃይም ይኖር ይሆን ብሎ ይሰጋል፤ ይህም የጽድቅንና የኩነኔን ጉዳይ በቀላሉ የማይተው ጉዳይ ያደርገዋል። ....
👆👆👆👆👆👆👆👆
"የተቆለፈበት ቁልፍ 🗝"
ከሚለው መጽሐፍ በጥቂቱ የተወሰደ
ደራሲ :- ዶክተር ምህረት ደበበ
❣ THANK YOU ❣
#share #participate #comment👇
@R_e_a_d_e_rs
@zhangidaa
@infho
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
"የተቆለፈበት ቁልፍ 🗝"
ከሚለው መጽሐፍ በጥቂቱ የተወሰደ
ደራሲ :- ዶክተር ምህረት ደበበ
❣ THANK YOU ❣
#share #participate #comment👇
@R_e_a_d_e_rs
@zhangidaa
@infho
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
🎥📻 ከታሪክማህደር 🎙🎞
👇👇ሮማነወርቅ ካሳሁን..... በኢትዮጵያ የመጀመሪያዋ ሴት ጋዜጠኛ 👇👇
ደራሲ ከበደ ሚካኤል በትምህርትና ስነ-ጥበብ ሚኒስቴር ኃላፊ በነበሩበት ወቅት በ1948 ዓ.ም ትምህርት ቤቶች ሲዘጉ ባደረጉት ንግግር ስለወይዘሮ ሮማነወርቅ (የመጀመሪያዋ ኢትዮጵያዊ ሴት ጋዜጠኛ) እና ሌሎች በአርዓያነት ስለሚጠቀሱ ሴቶች እንዲህ በማለት ምስክርነታቸውን ሰጥተው ነበር …
‹‹…ከጦርነቱ ወዲህ ግን በአዲስ አበባም ሆነ በየጠቅላይ ግዛቱ የሚታየው የሴት ተማሪዎች ቁጥር አስደሳች እየሆነ መጥቷል፡፡ እነስንዱ ገብሩ፣ እነሮማነወርቅ ካሳሁን (ሬዲዮ አንባቢዋ) እነ ዮዲት እምሩ፣ እነአልማዝ ፋሲካ ከማዕድ ቤት ወጥተው በማኅበረሰቡ መካከል በመገኘት አገር እየረዱ ነው:: በተለይም የሮማነወርቅ ካሣሁን የሬዲዮ ትምህርት አቀራረብ የመማር እድል ላላገኙት ሴቶች ጭምር ተስፋ የሚሰጥ ስለሆነ የኅብረተሰቡ ግማሽ አካል የሆኑ የሴቶች ትምህርት በብዛት እንዲቀጥልና ለትምህርት የሚመደበውም ገንዘብ ከፍ እንዲል በትህትና አሳስባለሁ …››
አዲስ ዘመን ረቡዕ ነሐሴ 8 / 2011
አንተነህ ቸሬ
❣ THANK YOU ❣
#share #participate #comment👇
@R_e_a_d_e_rs
@zhangidaa
@infho
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
👇👇ሮማነወርቅ ካሳሁን..... በኢትዮጵያ የመጀመሪያዋ ሴት ጋዜጠኛ 👇👇
ደራሲ ከበደ ሚካኤል በትምህርትና ስነ-ጥበብ ሚኒስቴር ኃላፊ በነበሩበት ወቅት በ1948 ዓ.ም ትምህርት ቤቶች ሲዘጉ ባደረጉት ንግግር ስለወይዘሮ ሮማነወርቅ (የመጀመሪያዋ ኢትዮጵያዊ ሴት ጋዜጠኛ) እና ሌሎች በአርዓያነት ስለሚጠቀሱ ሴቶች እንዲህ በማለት ምስክርነታቸውን ሰጥተው ነበር …
‹‹…ከጦርነቱ ወዲህ ግን በአዲስ አበባም ሆነ በየጠቅላይ ግዛቱ የሚታየው የሴት ተማሪዎች ቁጥር አስደሳች እየሆነ መጥቷል፡፡ እነስንዱ ገብሩ፣ እነሮማነወርቅ ካሳሁን (ሬዲዮ አንባቢዋ) እነ ዮዲት እምሩ፣ እነአልማዝ ፋሲካ ከማዕድ ቤት ወጥተው በማኅበረሰቡ መካከል በመገኘት አገር እየረዱ ነው:: በተለይም የሮማነወርቅ ካሣሁን የሬዲዮ ትምህርት አቀራረብ የመማር እድል ላላገኙት ሴቶች ጭምር ተስፋ የሚሰጥ ስለሆነ የኅብረተሰቡ ግማሽ አካል የሆኑ የሴቶች ትምህርት በብዛት እንዲቀጥልና ለትምህርት የሚመደበውም ገንዘብ ከፍ እንዲል በትህትና አሳስባለሁ …››
አዲስ ዘመን ረቡዕ ነሐሴ 8 / 2011
አንተነህ ቸሬ
❣ THANK YOU ❣
#share #participate #comment👇
@R_e_a_d_e_rs
@zhangidaa
@infho
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ካነበብነው📖📜📰🗞 via @like
🔑 ቅምሻ 🔑
🦅 ክፍል አስራ ስድስት 🦅
" የሶለን ማስታወሻ "
"............ ብዙ ሰዎች ባሕርይና ችሎታ ግንኙነት የላቸውም ብለው ማሰባቸው ትክክል አይመስለኝም። ይህ ውሀውን የያዘው ጠርሙስ ከውሀው ጋር ያለው ግንኙነት ያን ያህል ጠቃሚ አይደለም እንደ ማለት ነው። ይዘቱ በመያዣው በብዙ መንገድ ይወሰናል። ለምሳሌ የመያዝ ዐቅሙ (ጭላጭ ውሀ ብቻ መያዝ የሚችል እቃና 100 ሊትር ሊይዝ የሚችል እኩል አይደለም)፣ ውበቱ (በወርቅ ብርጭቆ ወይም በቅል ሽክና መጠጥ ቢሰጠን እኩል ደስታ አይሰማንም) ፣ ንፅህናውና ጥራቱ (በቆሻሻ እቃ ተቀድቶ ንፁሕ ውሀ ቢሰጠን ልዩነቱ ሰፊ ነው) ፣ እንዲሁም በጥቅም ላይ ለማዋል ማስቻሉ ( እንደ ወንፊት በሚያፈስ ወይም በታሸገና ከጠብታ በላይ በማያሳልፍ ዕቃ የቀረበ ውሀ እንደሌለ ነው) ። ይህ ሁሉ ከይዘቱ እኩል መያዣውም አስፈላጊ እንደሆነ ነው የሚያሳየው። ታዲያ የሰውን ችሎታ የሚሸከመውን ባሕሪይ እንዴት ነው አስፈላጊነቱን ለማየት የሚያዳግተው? ባህርይ እኮ ችሎታን ተሸካሚ መያዣ መሆኑን ማንም ሊክድ አይችልም። ስለዚህም መልካም ባሕሪይ የሌላቸው ጎበዝ ሰዎች ባጭር ቃል የባከኑ ችሎታዎች ከመሆንም ዐልፈው ጎጂ ስጦታዎችም ሊሆኑ ይችላሉ። ........."
~~~~ ይቀጥላል ~~~~
"የተቆለፈበት ቁልፍ 🗝"
ከሚለው መጽሐፍ በጥቂቱ የተወሰደ
ደራሲ :- ዶክተር ምህረት ደበበ
❣ THANK YOU ❣
#share #participate #comment👇
@R_e_a_d_e_rs
@zhangidaa
@infho
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
🦅 ክፍል አስራ ስድስት 🦅
" የሶለን ማስታወሻ "
"............ ብዙ ሰዎች ባሕርይና ችሎታ ግንኙነት የላቸውም ብለው ማሰባቸው ትክክል አይመስለኝም። ይህ ውሀውን የያዘው ጠርሙስ ከውሀው ጋር ያለው ግንኙነት ያን ያህል ጠቃሚ አይደለም እንደ ማለት ነው። ይዘቱ በመያዣው በብዙ መንገድ ይወሰናል። ለምሳሌ የመያዝ ዐቅሙ (ጭላጭ ውሀ ብቻ መያዝ የሚችል እቃና 100 ሊትር ሊይዝ የሚችል እኩል አይደለም)፣ ውበቱ (በወርቅ ብርጭቆ ወይም በቅል ሽክና መጠጥ ቢሰጠን እኩል ደስታ አይሰማንም) ፣ ንፅህናውና ጥራቱ (በቆሻሻ እቃ ተቀድቶ ንፁሕ ውሀ ቢሰጠን ልዩነቱ ሰፊ ነው) ፣ እንዲሁም በጥቅም ላይ ለማዋል ማስቻሉ ( እንደ ወንፊት በሚያፈስ ወይም በታሸገና ከጠብታ በላይ በማያሳልፍ ዕቃ የቀረበ ውሀ እንደሌለ ነው) ። ይህ ሁሉ ከይዘቱ እኩል መያዣውም አስፈላጊ እንደሆነ ነው የሚያሳየው። ታዲያ የሰውን ችሎታ የሚሸከመውን ባሕሪይ እንዴት ነው አስፈላጊነቱን ለማየት የሚያዳግተው? ባህርይ እኮ ችሎታን ተሸካሚ መያዣ መሆኑን ማንም ሊክድ አይችልም። ስለዚህም መልካም ባሕሪይ የሌላቸው ጎበዝ ሰዎች ባጭር ቃል የባከኑ ችሎታዎች ከመሆንም ዐልፈው ጎጂ ስጦታዎችም ሊሆኑ ይችላሉ። ........."
~~~~ ይቀጥላል ~~~~
"የተቆለፈበት ቁልፍ 🗝"
ከሚለው መጽሐፍ በጥቂቱ የተወሰደ
ደራሲ :- ዶክተር ምህረት ደበበ
❣ THANK YOU ❣
#share #participate #comment👇
@R_e_a_d_e_rs
@zhangidaa
@infho
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ካነበብነው📖📜📰🗞 via @like
🧞♂👣 ከዚም_ከዛም 👣🧞♂
የአብርሀም ሊንከን መሳጭ ንግግሮች
🔸 ጠላቶቼን ጒደኞቼ ባደርጋቸዉ በዘዴ አጠፋዋቸዉ ማለት አይደል?
🔹በዝግታ የምራመድ ብሆንም በፍፁም ወደ ኋላ አልመለስም።
🔸ስለ ወደፊቱ መልካሙ ነገር አንድ ቀን በሆነ ሰዓት መምጣቱ ነዉ።
🔹እዉነት በስም ማጥፋት ላይ ከሁሉ የበለጠ በቀል ነዉ።
🔸ዛፍ እዉነተኛ ነገር ሲሆን፣ጥላዉ ደግሞ ስለ
እሱ የምናስበዉ ነገር ነዉ።
♦ዛሬ መስራት የምችለውን ነገር ለነገ አታሳድር
♦ ነፃነት የምድር የመጨረሻዉ ተስፋ ነዉ!!
ምንጭ: ከመጽሐፍ ዓለም የፌስቡክ ግሩፕ
❣ THANK YOU ❣
#share #participate #comment👇
@R_e_a_d_e_rs
@zhangidaa
@infho
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚
የአብርሀም ሊንከን መሳጭ ንግግሮች
🔸 ጠላቶቼን ጒደኞቼ ባደርጋቸዉ በዘዴ አጠፋዋቸዉ ማለት አይደል?
🔹በዝግታ የምራመድ ብሆንም በፍፁም ወደ ኋላ አልመለስም።
🔸ስለ ወደፊቱ መልካሙ ነገር አንድ ቀን በሆነ ሰዓት መምጣቱ ነዉ።
🔹እዉነት በስም ማጥፋት ላይ ከሁሉ የበለጠ በቀል ነዉ።
🔸ዛፍ እዉነተኛ ነገር ሲሆን፣ጥላዉ ደግሞ ስለ
እሱ የምናስበዉ ነገር ነዉ።
♦ዛሬ መስራት የምችለውን ነገር ለነገ አታሳድር
♦ ነፃነት የምድር የመጨረሻዉ ተስፋ ነዉ!!
ምንጭ: ከመጽሐፍ ዓለም የፌስቡክ ግሩፕ
❣ THANK YOU ❣
#share #participate #comment👇
@R_e_a_d_e_rs
@zhangidaa
@infho
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚
ካነበብነው📖📜📰🗞 via @like
🧞♂👣 ከዚም_ከዛም 👣🧞♂
ጥቂት ስለ እንስሳት
🔸ሰጎን በፍጥነት ከፈረስ ይበልጣል ፣ ወንዱ ሰጎን የአንበሳን ድምፅ አስመስሎ ማግሳት ይችላል።
🔸 ካንጋሮ ጅራቷ ሚዛን መጠበቂያዋ ነው፣ ጅራቷ መሬት ካልነካ መዝለል አትችልም።
🔸 ነብር ላይ የምናየው መስመር የተሰመረው ፀጉራቸው ላይ ብቻ አይደለም። መሥመሩ እስከቆዳቸው ይዘልቃል፣ ሆኖም የአንዱ ነብር መስመር ከሌላኛው ነብር ጋር በጭራሽ አንድ አይሆንም።
❣ THANK YOU ❣
#share #participate #comment👇
@R_e_a_d_e_rs
@zhangidaa
@infho
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ጥቂት ስለ እንስሳት
🔸ሰጎን በፍጥነት ከፈረስ ይበልጣል ፣ ወንዱ ሰጎን የአንበሳን ድምፅ አስመስሎ ማግሳት ይችላል።
🔸 ካንጋሮ ጅራቷ ሚዛን መጠበቂያዋ ነው፣ ጅራቷ መሬት ካልነካ መዝለል አትችልም።
🔸 ነብር ላይ የምናየው መስመር የተሰመረው ፀጉራቸው ላይ ብቻ አይደለም። መሥመሩ እስከቆዳቸው ይዘልቃል፣ ሆኖም የአንዱ ነብር መስመር ከሌላኛው ነብር ጋር በጭራሽ አንድ አይሆንም።
❣ THANK YOU ❣
#share #participate #comment👇
@R_e_a_d_e_rs
@zhangidaa
@infho
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ካነበብነው📖📜📰🗞 via @like
📓🌓 ቅምሻ 🌗📓
🔘ሕይወት ባለብዙ አቅጣጫ ስለሆነች በአንድ መንገድ ብቻ አይተህ ተስፋ አትቁረጥ።
🔘 ሕይወትና ፍላጎት እንደ ተቆራኙ ወፎች ናቸው፤ ተያይዘው ይበራሉ። አንዱ እስካለ ሌላው ይኖራል።
🔘ሕይወት ጣፋጭነትንም ሆነ ጎምዛዛነቷ የሚታወቀው ቀምሰን ስናጣጥመው ብቻ ነው፡፡
🔘ለአመንው ለአቀድነው ነገር ህወታችንን መስዋት ማድረግ አስቸጋሪ አይሆንም፡፡
🔘በሕይወታችን የአንድ ደቂቃ ትዕግስት ማጣት የዘላለም ጸጸት ያስከትላል።
ምንጭ: በዓሉ ግርማ, ከአድማስ ባሻገር
❣ THANK YOU ❣
#share #participate #comment👇
@R_e_a_d_e_rs
@zhangidaa
@infho
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
🔘ሕይወት ባለብዙ አቅጣጫ ስለሆነች በአንድ መንገድ ብቻ አይተህ ተስፋ አትቁረጥ።
🔘 ሕይወትና ፍላጎት እንደ ተቆራኙ ወፎች ናቸው፤ ተያይዘው ይበራሉ። አንዱ እስካለ ሌላው ይኖራል።
🔘ሕይወት ጣፋጭነትንም ሆነ ጎምዛዛነቷ የሚታወቀው ቀምሰን ስናጣጥመው ብቻ ነው፡፡
🔘ለአመንው ለአቀድነው ነገር ህወታችንን መስዋት ማድረግ አስቸጋሪ አይሆንም፡፡
🔘በሕይወታችን የአንድ ደቂቃ ትዕግስት ማጣት የዘላለም ጸጸት ያስከትላል።
ምንጭ: በዓሉ ግርማ, ከአድማስ ባሻገር
❣ THANK YOU ❣
#share #participate #comment👇
@R_e_a_d_e_rs
@zhangidaa
@infho
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ካነበብነው📖📜📰🗞 via @like
🔑 ቅምሻ 🔑
🦅 ክፍል አስራ ሰባት 🦅
የሶለን ማስታወሻ
.......... አብሮ ከመብላት ይልቅ አብሮ መሥራት መቻል ብስለትን ይጠይቃል። በሰው ሐዘን አብሮ ከማልቀስ ይልቅ በሰው ደስታና ስኬት አብሮ መደሰት የትልቅነት እና የቅንነት ምልክት ይመስለኛል። ምቀኝነት አብሮ መስራትን ሲከለክል ክፉ ቅናት ደግሞ ለሌላው እንዳንደሰት እንቅፋት ይሆንብናል።
* * *
ሰዎች በበታችነት ስሜት የሚያሳዩት ባሕሪይ ከትሕትና ጋር በቀላሉ ሊያምታታ ይችላል ። በትዕቢትም ተወጥረው የበላይነት ስሜታቸው የነፋፋቸውን ሰዎች በራሳቸው የሚተማመኑ ጠንካራ ሰዎች ሊመስሉ ይችላሉ። የበታችነት ስሜት ቆስሎ የተሰባበረ ትዕቢት ሲሆን ትዕቢት ደግሞ እንደተወጠረ ፊኛ ጥቂት ነገር ጠቅ ብታደርገው የሚፈነዳ በፍርሀትና በባዶነት የተሞላ ማንነት ነው። ትሕትና ራስንም ሰውንም በተገቢው ደረጃ ማየትና ለራስም ለሰውም ትክክለኛውን ክብር በመስጠት፣ ከሌሎች ጋር ራስን ከማነፃፀር ተላቆ፣ ሰው ከራሱ ችሎታና ራዕይ ጋር በመወዳደር የተረጋጋ ኑሮ መኖር ሲችል የሚያሳየው ባሕሪይ ነው።.........
* * *
~~~~ ተፈፀመ ~~~~
"የተቆለፈበት ቁልፍ 🗝"
ከሚለው መጽሐፍ በጥቂቱ የተወሰደ
ደራሲ :- ዶክተር ምህረት ደበበ
እስካሁን ይህን መፅሀፍ እንደ ቅምሻ ያክል ያስተምራሉ ያልናቸውን በ17 ክፍላት አይተናል፤ ቀሪውን ደግሞ ለእናንተ ትተናል። በጣም ስለቆየ ይቅርታ🙏 እንጠይቃለን ትንሽ ተጨናንቀን ነበር። ያመለጣቹን ክፍል ወደላይ በመሔድ ማየት ትችላላችሁ።
❣ እናመሰግናለን !!! ❣
#share #participate #comment👇
@R_e_a_d_e_rs
@zhangidaa
@infho
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
🦅 ክፍል አስራ ሰባት 🦅
የሶለን ማስታወሻ
.......... አብሮ ከመብላት ይልቅ አብሮ መሥራት መቻል ብስለትን ይጠይቃል። በሰው ሐዘን አብሮ ከማልቀስ ይልቅ በሰው ደስታና ስኬት አብሮ መደሰት የትልቅነት እና የቅንነት ምልክት ይመስለኛል። ምቀኝነት አብሮ መስራትን ሲከለክል ክፉ ቅናት ደግሞ ለሌላው እንዳንደሰት እንቅፋት ይሆንብናል።
* * *
ሰዎች በበታችነት ስሜት የሚያሳዩት ባሕሪይ ከትሕትና ጋር በቀላሉ ሊያምታታ ይችላል ። በትዕቢትም ተወጥረው የበላይነት ስሜታቸው የነፋፋቸውን ሰዎች በራሳቸው የሚተማመኑ ጠንካራ ሰዎች ሊመስሉ ይችላሉ። የበታችነት ስሜት ቆስሎ የተሰባበረ ትዕቢት ሲሆን ትዕቢት ደግሞ እንደተወጠረ ፊኛ ጥቂት ነገር ጠቅ ብታደርገው የሚፈነዳ በፍርሀትና በባዶነት የተሞላ ማንነት ነው። ትሕትና ራስንም ሰውንም በተገቢው ደረጃ ማየትና ለራስም ለሰውም ትክክለኛውን ክብር በመስጠት፣ ከሌሎች ጋር ራስን ከማነፃፀር ተላቆ፣ ሰው ከራሱ ችሎታና ራዕይ ጋር በመወዳደር የተረጋጋ ኑሮ መኖር ሲችል የሚያሳየው ባሕሪይ ነው።.........
* * *
~~~~ ተፈፀመ ~~~~
"የተቆለፈበት ቁልፍ 🗝"
ከሚለው መጽሐፍ በጥቂቱ የተወሰደ
ደራሲ :- ዶክተር ምህረት ደበበ
እስካሁን ይህን መፅሀፍ እንደ ቅምሻ ያክል ያስተምራሉ ያልናቸውን በ17 ክፍላት አይተናል፤ ቀሪውን ደግሞ ለእናንተ ትተናል። በጣም ስለቆየ ይቅርታ🙏 እንጠይቃለን ትንሽ ተጨናንቀን ነበር። ያመለጣቹን ክፍል ወደላይ በመሔድ ማየት ትችላላችሁ።
❣ እናመሰግናለን !!! ❣
#share #participate #comment👇
@R_e_a_d_e_rs
@zhangidaa
@infho
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ካነበብነው📖📜📰🗞 via @like
🎥📻 ከታሪክ_ማህደር 🎙🎞
ጳውሎስ ኞኞ (1926 - 1984)
-----------------------
ጳውሎስ ኞኞ ከእናቱ ከወይዘሮ ትበልጫለሽ አንዳርጌና ከግሪካዊ አባቱ ሚስተር ኞኞ ህዳር 11 ቀን 1926 ዓ.ም. በቁልቢ ከተማ ተወለደ። ትውልዱ ቁልቢ ይሁን እንጂ የልጅነት ጊዜውን ያሳለፈው በድሬዳዋ ነው። እድሜው አስር ዓመት ገደማ ሲሆነው ድሬዳዋ ከተማ በሚገኘው ክርስቶስ ትምህርት ቤት ገብቶ የቀለም ትምህርቱን ጀመረ።
በትምህርት አቀባበሉ ፈጣን ስለነበር 'ደብል' እየመታ በአጭር ጊዜ ወደ አራተኛ ክፍል አለፈ። ነገር ግን ትምህርቱን ከዚህ በላይ መቀጠል አልቻለም። ወላጅ እናቱ ምንም ገቢ ስላልነበራቸው ገና በመማሪያ እድሜው እናቱን ለመርዳት ደፋ ቀና ማለት ጀመረ። ስዕል በመጠጥ ቤቶች አዙሮ በመሸጥ ራሱንና ደሀ እናቱን ያስተዳድር ነበር።
ጳውሎስ ኞኞ በ1943 ዓ.ም. ገደማ ገና የ17 ዓመት ታዳጊ ወጣት ሳለ በእርሻ ሚኒስቴር ተቀጠረ። በሚኒስቴሩ የእንስሳት ህክምና ክፍል የእንስሳት መርፌ ወጊ ሆኖ በወር ስምንት ብር እየተከፈለው በጊዜው አጠራር ሀረርጌ ክፍለ ሀገር ጨርጨር አውራጃ ለሶስት ዓመታት ሰርቷል።
በ1946 ዓ.ም. ወደ አዲስ አበባ ተመልሶ በዳግማዊ ምኒልክ ሆስፒታል በሰማንያ ብር ወርሀዊ ደመወዝ በድሬሰርነት፣ በፀሀፊነትና በሂሳብ ስራ አገልግሏል።
ጳውሎስ በአጭር የትምህርት ቤት ህይወቱ እንኳ ለተማሪዎች ግጥም እየፃፈ ያነብ ነበር። ትምህርቱን ቢያቋርጥም ከንባብና ከፅሁፍ አልራቀም። የኑሮ እጣ ፈንታው ገና በጠዋቱ ከትምህርት ቢያሰነባብተውም ከስራ መልስ ረፍት የሚያደርገው በመፃፍና በማንበብ ነበር። ለጋዜጠኝነት ህይወቱ መሰረት የሆነውም ይህ ነው።
ጳውሎስ ኞኞ ሲነሳ ጋዜጠኝነቱ፣ ከጋዜጠኝነቱም እያዝናኑ በሚያስረምሩ መጣጥፎቹ ይታወቃል። በተለይም "አንድ ጥያቄ አለኝ" በሚለው የጋዜጣ አምዱ በይበልጥ በህዝብ ዘንድ ተወዳጅነትን አስገኝቶለታል።
ጳውሎስን ከህዝብ ያስተዋወቀችው "የኢትዮጵያ ድምፅ" ጋዜጣ ናት። በጋዜጣዋ ከሪፖርተርነት እስከ አዘጋጅነት ለበርካታ ዓመታት ሰርቷል።
በ1957 ዓ.ም. "የኢትዮጵያ ድምፅ" ጋዜጣን ለቆ ወደ ኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ተዛወረ። ከጥቂት ወራት በኋላም ወደ አዲስ ዘመን ጋዜጣ ተዛወረ። በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከየካቲት 2 ቀን 1957 ዓ.ም. እስከ መስከረም 1970 ዓ.ም. በምክትል አዘጋጅነት እንዲሁም በተለያዩ ዓምዶች በዋና አዘጋጅነት ሰርቷል። . . . . .
ጳውሎስ ከጋዜጠኝነት ሙያው በተጨማሪ የአጫጭር ልብወለዶች ደራሲ፣ የታሪክ ተመራማሪና ፀሀፊ ነው። ግጥሞችንም ይሞካክራል።
ከልብ ወለድ ስራዎቹ መካከል፦
> የጌታቸው ሚስቶች
> የኔዎቹ ገረዶች
> የአራዳው ታደሰ
> የሴቶች እንባ
> ድብልቅልቅ
> እንቆቅልሽ
> ምስቅልቅል
> ቅይጥ ይጠቀሳሉ።
> በአምስት ቅፆች የቀረቡት "አስደናቂ ታሪኮች" ከኢ-ልብወለድ መፅሀፎቹ መካከል ናቸው።
ከጋዜጠኝነቱ ባልተናነሰ በታሪክ ፀሀፊነቱም ይታወቃል ጳውሎስ ኞኞ። በርካታ የታሪክ መረጃዎችንና ሰነዶችን አሰባስቦ አጠናቅሯል። በ1981 ዓ.ም. በጡረታ ከተገለለ በኋላ የታሪክ ምርምሩን አጠናክሮ በመቀጠል መፅሀፎችም ፅፏል።
ከበርካታ የታሪክ መፅሀፎቹ መካከል፦
> የኢትዮጵያና የኢጣሊያ ጦርነት
> አጤ ቴዎድሮስ
> አጤ ምኒልክ
> አፄ ምኒልክ በአገር ውስጥ የተፃፃፏቸው ደብዳቤዎች
> አፄ ምኒልክ ከውጭ ሀገራት ጋር የተፃፃፏቸው ደብዳቤዎች
> የኢትዮጵያ ታሪክ ኢንሳይክሎፒዲያ
መጥቀስ ይቻላል። ለህትመት ያልበቁ በርካታ የታሪክ መፃህፍትም አሉት።
ከ1983 ዓ.ም. በኋላ በርካታ መፅሄቶችና ጋዜጦች ለህትመት ይበቁ የነበረበት ጊዜ ነበር። ከነዚህም አንዷ "ሩህ" መፅሄት ነበረች። ጳውሎስ ኞኞ ደግሞ ዋና አዘጋጇ። ነገር ግን ከሦስት እትም በላይ ከመፅሄቷ ጋር መዝለቅ አልቻለም። ምክንያቱም ባደረበት ህመም ይሰቃይ ስለነበር።
ጋዜጠኛ፣ ደራሲ እና የታሪክ ተመራማሪ ጳውሎስ ኞኞ በመጨረሻም በአሜሪካን አገር ዋሽንግተን ከተማ በሚገኝ ሆስፒታል ህክምናውን ሲከታተል ቆይቶ ግንቦት 29 ቀን 1984 ዓ.ም. ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።
---------------------------------------
ምንጭ፦ የሥነ ጽሁፍ ሰዎችና ሥራዎቻቸው
ልቦለድ፣ የተውኔት ድርሰት እና ጋዜጠኝነት በኢትዮጵያ
[ከ1850 - 1960ዎቹ]
✍️ ሀብታሙ ግርማ ደምሴ
❣ እናመሠግናለን ❣
#share #participate #comment👇
@R_e_a_d_e_rs
@zhangidaa
@infho
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ጳውሎስ ኞኞ (1926 - 1984)
-----------------------
ጳውሎስ ኞኞ ከእናቱ ከወይዘሮ ትበልጫለሽ አንዳርጌና ከግሪካዊ አባቱ ሚስተር ኞኞ ህዳር 11 ቀን 1926 ዓ.ም. በቁልቢ ከተማ ተወለደ። ትውልዱ ቁልቢ ይሁን እንጂ የልጅነት ጊዜውን ያሳለፈው በድሬዳዋ ነው። እድሜው አስር ዓመት ገደማ ሲሆነው ድሬዳዋ ከተማ በሚገኘው ክርስቶስ ትምህርት ቤት ገብቶ የቀለም ትምህርቱን ጀመረ።
በትምህርት አቀባበሉ ፈጣን ስለነበር 'ደብል' እየመታ በአጭር ጊዜ ወደ አራተኛ ክፍል አለፈ። ነገር ግን ትምህርቱን ከዚህ በላይ መቀጠል አልቻለም። ወላጅ እናቱ ምንም ገቢ ስላልነበራቸው ገና በመማሪያ እድሜው እናቱን ለመርዳት ደፋ ቀና ማለት ጀመረ። ስዕል በመጠጥ ቤቶች አዙሮ በመሸጥ ራሱንና ደሀ እናቱን ያስተዳድር ነበር።
ጳውሎስ ኞኞ በ1943 ዓ.ም. ገደማ ገና የ17 ዓመት ታዳጊ ወጣት ሳለ በእርሻ ሚኒስቴር ተቀጠረ። በሚኒስቴሩ የእንስሳት ህክምና ክፍል የእንስሳት መርፌ ወጊ ሆኖ በወር ስምንት ብር እየተከፈለው በጊዜው አጠራር ሀረርጌ ክፍለ ሀገር ጨርጨር አውራጃ ለሶስት ዓመታት ሰርቷል።
በ1946 ዓ.ም. ወደ አዲስ አበባ ተመልሶ በዳግማዊ ምኒልክ ሆስፒታል በሰማንያ ብር ወርሀዊ ደመወዝ በድሬሰርነት፣ በፀሀፊነትና በሂሳብ ስራ አገልግሏል።
ጳውሎስ በአጭር የትምህርት ቤት ህይወቱ እንኳ ለተማሪዎች ግጥም እየፃፈ ያነብ ነበር። ትምህርቱን ቢያቋርጥም ከንባብና ከፅሁፍ አልራቀም። የኑሮ እጣ ፈንታው ገና በጠዋቱ ከትምህርት ቢያሰነባብተውም ከስራ መልስ ረፍት የሚያደርገው በመፃፍና በማንበብ ነበር። ለጋዜጠኝነት ህይወቱ መሰረት የሆነውም ይህ ነው።
ጳውሎስ ኞኞ ሲነሳ ጋዜጠኝነቱ፣ ከጋዜጠኝነቱም እያዝናኑ በሚያስረምሩ መጣጥፎቹ ይታወቃል። በተለይም "አንድ ጥያቄ አለኝ" በሚለው የጋዜጣ አምዱ በይበልጥ በህዝብ ዘንድ ተወዳጅነትን አስገኝቶለታል።
ጳውሎስን ከህዝብ ያስተዋወቀችው "የኢትዮጵያ ድምፅ" ጋዜጣ ናት። በጋዜጣዋ ከሪፖርተርነት እስከ አዘጋጅነት ለበርካታ ዓመታት ሰርቷል።
በ1957 ዓ.ም. "የኢትዮጵያ ድምፅ" ጋዜጣን ለቆ ወደ ኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ተዛወረ። ከጥቂት ወራት በኋላም ወደ አዲስ ዘመን ጋዜጣ ተዛወረ። በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከየካቲት 2 ቀን 1957 ዓ.ም. እስከ መስከረም 1970 ዓ.ም. በምክትል አዘጋጅነት እንዲሁም በተለያዩ ዓምዶች በዋና አዘጋጅነት ሰርቷል። . . . . .
ጳውሎስ ከጋዜጠኝነት ሙያው በተጨማሪ የአጫጭር ልብወለዶች ደራሲ፣ የታሪክ ተመራማሪና ፀሀፊ ነው። ግጥሞችንም ይሞካክራል።
ከልብ ወለድ ስራዎቹ መካከል፦
> የጌታቸው ሚስቶች
> የኔዎቹ ገረዶች
> የአራዳው ታደሰ
> የሴቶች እንባ
> ድብልቅልቅ
> እንቆቅልሽ
> ምስቅልቅል
> ቅይጥ ይጠቀሳሉ።
> በአምስት ቅፆች የቀረቡት "አስደናቂ ታሪኮች" ከኢ-ልብወለድ መፅሀፎቹ መካከል ናቸው።
ከጋዜጠኝነቱ ባልተናነሰ በታሪክ ፀሀፊነቱም ይታወቃል ጳውሎስ ኞኞ። በርካታ የታሪክ መረጃዎችንና ሰነዶችን አሰባስቦ አጠናቅሯል። በ1981 ዓ.ም. በጡረታ ከተገለለ በኋላ የታሪክ ምርምሩን አጠናክሮ በመቀጠል መፅሀፎችም ፅፏል።
ከበርካታ የታሪክ መፅሀፎቹ መካከል፦
> የኢትዮጵያና የኢጣሊያ ጦርነት
> አጤ ቴዎድሮስ
> አጤ ምኒልክ
> አፄ ምኒልክ በአገር ውስጥ የተፃፃፏቸው ደብዳቤዎች
> አፄ ምኒልክ ከውጭ ሀገራት ጋር የተፃፃፏቸው ደብዳቤዎች
> የኢትዮጵያ ታሪክ ኢንሳይክሎፒዲያ
መጥቀስ ይቻላል። ለህትመት ያልበቁ በርካታ የታሪክ መፃህፍትም አሉት።
ከ1983 ዓ.ም. በኋላ በርካታ መፅሄቶችና ጋዜጦች ለህትመት ይበቁ የነበረበት ጊዜ ነበር። ከነዚህም አንዷ "ሩህ" መፅሄት ነበረች። ጳውሎስ ኞኞ ደግሞ ዋና አዘጋጇ። ነገር ግን ከሦስት እትም በላይ ከመፅሄቷ ጋር መዝለቅ አልቻለም። ምክንያቱም ባደረበት ህመም ይሰቃይ ስለነበር።
ጋዜጠኛ፣ ደራሲ እና የታሪክ ተመራማሪ ጳውሎስ ኞኞ በመጨረሻም በአሜሪካን አገር ዋሽንግተን ከተማ በሚገኝ ሆስፒታል ህክምናውን ሲከታተል ቆይቶ ግንቦት 29 ቀን 1984 ዓ.ም. ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።
---------------------------------------
ምንጭ፦ የሥነ ጽሁፍ ሰዎችና ሥራዎቻቸው
ልቦለድ፣ የተውኔት ድርሰት እና ጋዜጠኝነት በኢትዮጵያ
[ከ1850 - 1960ዎቹ]
✍️ ሀብታሙ ግርማ ደምሴ
❣ እናመሠግናለን ❣
#share #participate #comment👇
@R_e_a_d_e_rs
@zhangidaa
@infho
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ካነበብነው📖📜📰🗞 via @like
ጥቆማ
ለዛሬ ስነፅሁፍ በስስት የምታያቸውና ምትዘክራቸው እነ ቶልስቶይና ቸኮቭን ካፈራችዉ ሩስያ የተገኘው ድንቅ ደራሲ ኒኮላይ ጎጎል የደረሰውን "dead souls-ሙት ነፍሳት " የተሰኘውን ግሩምና ዘመን አይሽሬ መፅሀፍ ለጥቆማ መርጠነዋል።
በብዙ አንባብያን እና ሀያስያን" a masterpice from a master mind "እየተባለ ሚሞካሸው ይህ መፅሀፍ በ ፊውዳል ዘመን ሩሲያ ከሀገር ሀገር እየዞረ የሞቱ ጭሰኞችን ነፍስ የሚገዛ ቺቺኮቭ የተሰኘ ገፀባህሪይ ላይ ያጠነጥናል።በቺቺኮቭ ጉዞ ውስጥ ጎጎል የሩሲያን ዉበትና ድሀ ገፅ፣የሰውን ልጅ ጥልቅ ማንነትና የህይወትን ወጣገባ በአስደማሚ ትረካ ያስቃኘናል። ለዚህም ይመስላል በብዙወች ከቶልስቶይ"war and peace" ቀጥሎ የሩስያን ጥጋጥግና የሰዉን ልጅ ውስብስብ ባህሪይ ቁልጭ አርጎ ሚያሳይ ድርሰት እየተባል የሚወደሰው።
ትደሰቱበት ዘንድ በአክብሮት ጋበዝን።መልካም ንባብ!!
#share #participate #comment👇
@R_e_a_d_e_rs
@zhangidaa
@infho
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ለዛሬ ስነፅሁፍ በስስት የምታያቸውና ምትዘክራቸው እነ ቶልስቶይና ቸኮቭን ካፈራችዉ ሩስያ የተገኘው ድንቅ ደራሲ ኒኮላይ ጎጎል የደረሰውን "dead souls-ሙት ነፍሳት " የተሰኘውን ግሩምና ዘመን አይሽሬ መፅሀፍ ለጥቆማ መርጠነዋል።
በብዙ አንባብያን እና ሀያስያን" a masterpice from a master mind "እየተባለ ሚሞካሸው ይህ መፅሀፍ በ ፊውዳል ዘመን ሩሲያ ከሀገር ሀገር እየዞረ የሞቱ ጭሰኞችን ነፍስ የሚገዛ ቺቺኮቭ የተሰኘ ገፀባህሪይ ላይ ያጠነጥናል።በቺቺኮቭ ጉዞ ውስጥ ጎጎል የሩሲያን ዉበትና ድሀ ገፅ፣የሰውን ልጅ ጥልቅ ማንነትና የህይወትን ወጣገባ በአስደማሚ ትረካ ያስቃኘናል። ለዚህም ይመስላል በብዙወች ከቶልስቶይ"war and peace" ቀጥሎ የሩስያን ጥጋጥግና የሰዉን ልጅ ውስብስብ ባህሪይ ቁልጭ አርጎ ሚያሳይ ድርሰት እየተባል የሚወደሰው።
ትደሰቱበት ዘንድ በአክብሮት ጋበዝን።መልካም ንባብ!!
#share #participate #comment👇
@R_e_a_d_e_rs
@zhangidaa
@infho
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ካነበብነው📖📜📰🗞 via @like
እንኳን ለጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!
ጥምቀት የክርስቶስን መገለጥ የምስራቅ አብያተክርስትያናት በዮሀንስ እጅ መጠመቁን፣የምዕራቡ ደግሞ የሶስቱን ሰብዓሰገል መምጣት በማሰብ የሚያከብሩት በዓል ነዉ።መልካም በዓል እየተመኘን የተለያዩ ሀገራት ጥምቀትን እንዴት እንደሚያከብሩት በጥቂቱ እናስቃኛችሁዋለን።
፩ ስፔን፦ የ ስፔን ህፃናት ለእየሱስ ስጦታን ያመጡት ንጉሳን ለነሱም እንደሚያመጡ በማመን የዋዜማው ቀን ጫማወቻቸዉን ወልውለው ያስቀምጣሉ።በበዓሉ ቀን ደግሞ የካርኒቫል ፈረስ በመጋለብና ባህላዊ ምግቦች በመመገብ ያሳልፋሉ።
፪ ታላቋ ብሪታንያ፦ የዋዜማዉ እለት 12ኛዉ ምሽት ለበዓሉ ሚዘጋጀዉ ግዙፍ የፍራፍሬ ኬክ ደግሞ 12ኛው ኬክ ይባላሉ።ውስጡ የገባዉን ባቄላ ያገኘዉ ሰው ለበዓሉ እንደ ንጉስ ተመርጦ ልዩ ክብር ይሰጠዋል።የቀረውን የበዓሉን ክፍል ሰብዓሰገል ጋር በሚገናኙ ተግባራት ያሳልፋታል።
፫ ሩስያ፦በዓሉ የክርስቶስን ጥምቀት ያስባል።ሊቃነ -ጳጳሳት ውሀውን ከባረኩ ቡሀላ ሁሉም ህዝብ እንደ በረዶ ሚቀዘቅዘው ውሀ ውስጥ ገብቶ ሶስቴ ብቅ ጥልቅ ይላል።ይሄም የጌታ ጥምቀት ተምሳሌት ነዉ።................
መልካም በዓል🍋
#share #participate #comment👇
@R_e_a_d_e_rs
@C_h_aa
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ጥምቀት የክርስቶስን መገለጥ የምስራቅ አብያተክርስትያናት በዮሀንስ እጅ መጠመቁን፣የምዕራቡ ደግሞ የሶስቱን ሰብዓሰገል መምጣት በማሰብ የሚያከብሩት በዓል ነዉ።መልካም በዓል እየተመኘን የተለያዩ ሀገራት ጥምቀትን እንዴት እንደሚያከብሩት በጥቂቱ እናስቃኛችሁዋለን።
፩ ስፔን፦ የ ስፔን ህፃናት ለእየሱስ ስጦታን ያመጡት ንጉሳን ለነሱም እንደሚያመጡ በማመን የዋዜማው ቀን ጫማወቻቸዉን ወልውለው ያስቀምጣሉ።በበዓሉ ቀን ደግሞ የካርኒቫል ፈረስ በመጋለብና ባህላዊ ምግቦች በመመገብ ያሳልፋሉ።
፪ ታላቋ ብሪታንያ፦ የዋዜማዉ እለት 12ኛዉ ምሽት ለበዓሉ ሚዘጋጀዉ ግዙፍ የፍራፍሬ ኬክ ደግሞ 12ኛው ኬክ ይባላሉ።ውስጡ የገባዉን ባቄላ ያገኘዉ ሰው ለበዓሉ እንደ ንጉስ ተመርጦ ልዩ ክብር ይሰጠዋል።የቀረውን የበዓሉን ክፍል ሰብዓሰገል ጋር በሚገናኙ ተግባራት ያሳልፋታል።
፫ ሩስያ፦በዓሉ የክርስቶስን ጥምቀት ያስባል።ሊቃነ -ጳጳሳት ውሀውን ከባረኩ ቡሀላ ሁሉም ህዝብ እንደ በረዶ ሚቀዘቅዘው ውሀ ውስጥ ገብቶ ሶስቴ ብቅ ጥልቅ ይላል።ይሄም የጌታ ጥምቀት ተምሳሌት ነዉ።................
መልካም በዓል🍋
#share #participate #comment👇
@R_e_a_d_e_rs
@C_h_aa
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ካነበብነው📖📜📰🗞 via @like
🌫🌊የጥምቀት በዓል 🌊🌫
ጥር 10 ቀን በዋዜማው ከተራ በሚል ስያሜ በሚታወቀው በዚሁ ዕለት ባሕረ ጥምቀት ከተዘጋጀ በኋላ በመላዋ ኢትዮጵያ በከተማም በገጠርም በመሐል አገርና በጠረፍ ጭምር ባሉት አብያተ ክርስቲያናት የሚገኙት ታቦታት ሁሉ ከመንበራቸው ተነሥተው ወደተዘጋጀው ባሕረ ጥምቀት በመውረድና በተዘጋጀላቸው ድንኳን ውስጥ በማደር በዚያው በአደሩበት ድንኳን ውስጥም ማኅሌቱና ሥርዓተ ቅዳሴው ከተከናወነ በኋላ ባሕረ ጥምቀቱ ተባርኮ ሕዝበ ክርስቲያኑ ሁሉ የበረከቱ ተሳታፊ ከመሆናቸውም በላይ በዓሉ ከዋዜማው (ከከተራው) ቀን ጀምሮ ታቦታቱ ወደየአብያተ ክርስቲያናቱ ተመልሰው በመንበራቸው ላይ እስኪያርፉ ድረስ ሁለት ቀን መሉ በየባሕረ ጥምቀቱና በየመንገዱ ሁሉ በድምቀት የሚከበር በዓል በመሆኑ ነው፡፡ ይህም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዓለማትን የፈጠረና ሁሉንም ያስገኘ ልዑል አምላክ ሲሆን ለእኛ አርአያና ምሳሌ ይሆን ዘንድ በተዋሐደው ሥጋ ትኅትናን ገንዘብ በማድረግ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ ሄዶ በአገልጋዩ በዮሐንስ መጥምቅ እጅ የመጠመቁ ምሳሌ መሆኑን ያስረዳል፡፡
ከሊቀ ብርሃናት ኢሳይያስ ወንድምአገኘሁ
🍀መ🍀ል🍀ካ🍀ም🍀 🍀በ🍀ዓ🍀ል🍀
#share #participate #comment👇
@R_e_a_d_e_rs
@zhangidaa
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ጥር 10 ቀን በዋዜማው ከተራ በሚል ስያሜ በሚታወቀው በዚሁ ዕለት ባሕረ ጥምቀት ከተዘጋጀ በኋላ በመላዋ ኢትዮጵያ በከተማም በገጠርም በመሐል አገርና በጠረፍ ጭምር ባሉት አብያተ ክርስቲያናት የሚገኙት ታቦታት ሁሉ ከመንበራቸው ተነሥተው ወደተዘጋጀው ባሕረ ጥምቀት በመውረድና በተዘጋጀላቸው ድንኳን ውስጥ በማደር በዚያው በአደሩበት ድንኳን ውስጥም ማኅሌቱና ሥርዓተ ቅዳሴው ከተከናወነ በኋላ ባሕረ ጥምቀቱ ተባርኮ ሕዝበ ክርስቲያኑ ሁሉ የበረከቱ ተሳታፊ ከመሆናቸውም በላይ በዓሉ ከዋዜማው (ከከተራው) ቀን ጀምሮ ታቦታቱ ወደየአብያተ ክርስቲያናቱ ተመልሰው በመንበራቸው ላይ እስኪያርፉ ድረስ ሁለት ቀን መሉ በየባሕረ ጥምቀቱና በየመንገዱ ሁሉ በድምቀት የሚከበር በዓል በመሆኑ ነው፡፡ ይህም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዓለማትን የፈጠረና ሁሉንም ያስገኘ ልዑል አምላክ ሲሆን ለእኛ አርአያና ምሳሌ ይሆን ዘንድ በተዋሐደው ሥጋ ትኅትናን ገንዘብ በማድረግ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ ሄዶ በአገልጋዩ በዮሐንስ መጥምቅ እጅ የመጠመቁ ምሳሌ መሆኑን ያስረዳል፡፡
ከሊቀ ብርሃናት ኢሳይያስ ወንድምአገኘሁ
🍀መ🍀ል🍀ካ🍀ም🍀 🍀በ🍀ዓ🍀ል🍀
#share #participate #comment👇
@R_e_a_d_e_rs
@zhangidaa
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ካነበብነው📖📜📰🗞 via @like
🧞♂👣 ከዚም_ከዛም 👣🧞♂
ጠቃሚ ምክሮች
1. ከአለስፈላጊ ክርክሮች ጭቅጭቆች እና እሰጣገባዎች ራቅ።
2. ራስህን ገንቢ ሃሳብ ከሌላቸው (negative) ሰዎች አርቅ። ምክንያቱም አንተን ራሱ
ሳትፈልገዉ እንደነሱ እንድታስብ ትገደድ ይሆናል፡፡
3. መቀበል የምትፈልገውን ስጥ።
4. ገንቢ ያለሆኑ ጎጂ አስታያየቶችን ከመስጠት ተቆጠብ።
5. ለሰዎች ፍቅርና አክብሮት ይኑርህ።
6. ይህ መቼም በእኔ አይደርስም አትበል፣የሕይወትን አቅጣጫ ሁሌም ቢሆን ማወቅ አንችልምና።
7. የመኪና የፊት መስታወት ትልቅ ሆኖ የኋላ መመልከቻውዠ መስታወት ግን ለምን ትንሽ የሆነ ይመስልሃል....ምክንያቱም የፊቱ ካለፈው ይልቅ አስፈላጊ ስለሆነ ነው። ስለዚህም
የኀላዉን ሳትዘነጋ በትልቁ የሕይወት መስታወት ወደፊት እያየህ ተጓዝ::
❣ እናመሠግናለን ❣
#share #participate #comment
@zhangidaa
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ጠቃሚ ምክሮች
1. ከአለስፈላጊ ክርክሮች ጭቅጭቆች እና እሰጣገባዎች ራቅ።
2. ራስህን ገንቢ ሃሳብ ከሌላቸው (negative) ሰዎች አርቅ። ምክንያቱም አንተን ራሱ
ሳትፈልገዉ እንደነሱ እንድታስብ ትገደድ ይሆናል፡፡
3. መቀበል የምትፈልገውን ስጥ።
4. ገንቢ ያለሆኑ ጎጂ አስታያየቶችን ከመስጠት ተቆጠብ።
5. ለሰዎች ፍቅርና አክብሮት ይኑርህ።
6. ይህ መቼም በእኔ አይደርስም አትበል፣የሕይወትን አቅጣጫ ሁሌም ቢሆን ማወቅ አንችልምና።
7. የመኪና የፊት መስታወት ትልቅ ሆኖ የኋላ መመልከቻውዠ መስታወት ግን ለምን ትንሽ የሆነ ይመስልሃል....ምክንያቱም የፊቱ ካለፈው ይልቅ አስፈላጊ ስለሆነ ነው። ስለዚህም
የኀላዉን ሳትዘነጋ በትልቁ የሕይወት መስታወት ወደፊት እያየህ ተጓዝ::
❣ እናመሠግናለን ❣
#share #participate #comment
@zhangidaa
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ካነበብነው📖📜📰🗞 via @like
💫🌪 ጥቆማ 🌪💫
"ፍልስፍና ከምንም ተነስቶ ወደ
ምንም የሚያደርስ መንገድ ነው"
---------------------------------------
የፍልስፍና መምህሩ ወደ ክፍል ውስጥ ይገባና ለተማሪዎቹ የመጨረሻውን ፈተና ሊሰጥ ተዘጋጀ። አንድ ወንበር በማንሳት ከጠረጴዛ ላይ አስቀመጠና፦
"እስከዛሬ በዚህ ኮርስ የተማራችሁትን ቁም ነገር ከግምት ውስጥ በማስገባት ይኽ ወንበር አለመኖሩን አረጋግጡልኝ" አለ።
በዚህ ጊዜ ተማሪዎች የዚያን ወንበር አለመኖር ወይም መኖሩ እውነት አለመሆኑን ለማረጋገጥ መፃፍ ጀመሩ። ብዙዎቹ ለሰዓታት የፈጀ ጥናታቸውንና ማብራሪያቸውን ሲፅፉ አንድ ተማሪ ግን በሰላሳ ሴኮንድ ውስጥ መልሱን ፅፎ ለመምህሩ በማስረከብ ክፍሉን ለቅቆ ሄደ።
በነጋታው ፕሮፌሰሩ የተማሪዎቹን ውጤት ይዞ መጣ። ከሁሉም ተማሪ ከፍተኛውን ውጤት ያገኘው በሰላሳ ሴኮንድ ፈተናውን ጨርሶ የሄደው ተማሪ ነበር።
ፕሮፌሰሩም "ብዙዎቻችሁ የወንበሩን አለመኖር ለማሳየት ብዙ ደክማችኋል። ይኽ ተማሪ ግን ከሁላችሁም በላቀ መንገድ ወንበሩ አለመኖሩን አረጋግጦልኛል" አለ።
✅ ተማሪው ለጥያቄው የሰጠው ምላሽ እንዲህ የሚል ነበር።
"የቱ ወንበር?"።
----------------------------
"ጥ በ ብ" - ከጲላጦስ
(ኃይለጊዮርጊስ ማሞ)
📖 📖 📖 📖 📖 📖 ❣️ እናመሠግናለን ❣️
#share #participate #comment
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
"ፍልስፍና ከምንም ተነስቶ ወደ
ምንም የሚያደርስ መንገድ ነው"
---------------------------------------
የፍልስፍና መምህሩ ወደ ክፍል ውስጥ ይገባና ለተማሪዎቹ የመጨረሻውን ፈተና ሊሰጥ ተዘጋጀ። አንድ ወንበር በማንሳት ከጠረጴዛ ላይ አስቀመጠና፦
"እስከዛሬ በዚህ ኮርስ የተማራችሁትን ቁም ነገር ከግምት ውስጥ በማስገባት ይኽ ወንበር አለመኖሩን አረጋግጡልኝ" አለ።
በዚህ ጊዜ ተማሪዎች የዚያን ወንበር አለመኖር ወይም መኖሩ እውነት አለመሆኑን ለማረጋገጥ መፃፍ ጀመሩ። ብዙዎቹ ለሰዓታት የፈጀ ጥናታቸውንና ማብራሪያቸውን ሲፅፉ አንድ ተማሪ ግን በሰላሳ ሴኮንድ ውስጥ መልሱን ፅፎ ለመምህሩ በማስረከብ ክፍሉን ለቅቆ ሄደ።
በነጋታው ፕሮፌሰሩ የተማሪዎቹን ውጤት ይዞ መጣ። ከሁሉም ተማሪ ከፍተኛውን ውጤት ያገኘው በሰላሳ ሴኮንድ ፈተናውን ጨርሶ የሄደው ተማሪ ነበር።
ፕሮፌሰሩም "ብዙዎቻችሁ የወንበሩን አለመኖር ለማሳየት ብዙ ደክማችኋል። ይኽ ተማሪ ግን ከሁላችሁም በላቀ መንገድ ወንበሩ አለመኖሩን አረጋግጦልኛል" አለ።
✅ ተማሪው ለጥያቄው የሰጠው ምላሽ እንዲህ የሚል ነበር።
"የቱ ወንበር?"።
----------------------------
"ጥ በ ብ" - ከጲላጦስ
(ኃይለጊዮርጊስ ማሞ)
📖 📖 📖 📖 📖 📖 ❣️ እናመሠግናለን ❣️
#share #participate #comment
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ካነበብነው📖📜📰🗞 via @like
💫🌪 ጥቆማ 🌪💫
ፍልስምና ፩+፪+፫ የሚለው የደራሲ ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ መጽሐፍ ላይ ጋሽ ስብሃት ገ/እግዚአብሔር እና ቴዎድሮስ እንዲህ ሲሉ ያወጋሉ...
ከመጽሐፉ የተቀነጨበች ጽሑፍ...
፨፨፨
ቴዎድሮስ ፦ የወንድና የሴትን ትተን በተመሳሳይ ጾታዎች መሀል እኩል የሚባል ነገር ይኖራል? አንድ ወንድ ከሌላው ወንድ ጋር...?
#ስብሃት ፦ የውልህ..እኩል የሚለው እኮ ስታትስቲክስ ነው። #ሀሳብ ነው እንጂ እኩል የሚባል ነገር የለም። አንድ ሰው የማንም እኩል አይደለም። እያንዳንዳችን ራሳችንን የቻልን ዩኒቨርስ ነን። እኛ ብቻ ሳንሆን እያንዳንዷ የሰውነታችን ሴል ልዩ ናት። እኩል..ምናምን የምንለው ሃሳብ ነው እንጂ የለም።
፧
ቴዎድሮስ ፦ የሰው ልጅ መሞት የሚጀምረው መቼ ነው?
#ስብሃት ፦ የውልደቱ እለት ነው መሞት የሚጀምረውማ። ጥፍርህ ያበቅላል አይደለም? ግን ደግሞ እንደበቀለ ይሞታል። ተቆርጦ ሲሔድ አይሰማህም። ሞት እኮ ሁሌም አብሮህ ነው። ስትታጠብ ቆዳህ በመጠኑ እየተላጠ ይሄዳል። እየሞትክና እየተወለድክ ትኖራለህ ማለት ነው ።
ምንጭ ፦ / ፍልስምና ፩+፪+፫……ገጽ 77 /
ደራሲ ፦ ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ
ጋሽ ስብሃት ምን ለማለት ፈልጎ ይሆን...?
❣️ እናመሠግናለን ❣️
#share #participate #comment
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ፍልስምና ፩+፪+፫ የሚለው የደራሲ ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ መጽሐፍ ላይ ጋሽ ስብሃት ገ/እግዚአብሔር እና ቴዎድሮስ እንዲህ ሲሉ ያወጋሉ...
ከመጽሐፉ የተቀነጨበች ጽሑፍ...
፨፨፨
ቴዎድሮስ ፦ የወንድና የሴትን ትተን በተመሳሳይ ጾታዎች መሀል እኩል የሚባል ነገር ይኖራል? አንድ ወንድ ከሌላው ወንድ ጋር...?
#ስብሃት ፦ የውልህ..እኩል የሚለው እኮ ስታትስቲክስ ነው። #ሀሳብ ነው እንጂ እኩል የሚባል ነገር የለም። አንድ ሰው የማንም እኩል አይደለም። እያንዳንዳችን ራሳችንን የቻልን ዩኒቨርስ ነን። እኛ ብቻ ሳንሆን እያንዳንዷ የሰውነታችን ሴል ልዩ ናት። እኩል..ምናምን የምንለው ሃሳብ ነው እንጂ የለም።
፧
ቴዎድሮስ ፦ የሰው ልጅ መሞት የሚጀምረው መቼ ነው?
#ስብሃት ፦ የውልደቱ እለት ነው መሞት የሚጀምረውማ። ጥፍርህ ያበቅላል አይደለም? ግን ደግሞ እንደበቀለ ይሞታል። ተቆርጦ ሲሔድ አይሰማህም። ሞት እኮ ሁሌም አብሮህ ነው። ስትታጠብ ቆዳህ በመጠኑ እየተላጠ ይሄዳል። እየሞትክና እየተወለድክ ትኖራለህ ማለት ነው ።
ምንጭ ፦ / ፍልስምና ፩+፪+፫……ገጽ 77 /
ደራሲ ፦ ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ
ጋሽ ስብሃት ምን ለማለት ፈልጎ ይሆን...?
❣️ እናመሠግናለን ❣️
#share #participate #comment
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
ካነበብነው📖📜📰🗞 via @like
🧞♂👣 ከዚም_ከዛም 👣🧞♂
🔴 ከሁለት ቢልዮን ሰዎች አንድ ሰው ብቻ 116 👩🦳👨🦳 ዓመትና ከዛ በላይ የመኖር እድል አለው። አይዞአችሁ የላቹበትም 😜😜😜
🔷 በ1926 ቴሌ ቪዥንን ( Television )📺 የፈጠረው ሰው እንግሊዛዊው Baird ነበር።
🎥 Quote :- What lies ahead will always be a mystery. Do not be afraid to explore.
🔶 ባሕረ ሀሳብ ማለት የግዕዝ ቃል ሲሆን በአረብኛ አቡሻከር በአማርኛ የዘመን አቆጣጠር 📆ይባላል። የቀመረው 12ኛው የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ ድሜጥሮስ 👳♂ነበሩ።
🔷 ይህን ይሞክሩ!
ባለ ሶስት አሐዝ ቁጥር ይምረጡ። ከዛም በ 7፣ በ 11 እና በ 13 ያባዙት። የሚያገኙት ውጤት የባለሶስት አሐዙን ሁለት ጊዜ የተደገመ ይሆናል።
ለምሳሌ :- 574 ብንወስድና በ 7፣ በ 11 እና በ 13 ቢያባዙት የመጨረሻው መልስ 574,574 ይሆናል።🎞🎞🎞
❣ እናመሠግናለን ❣
#share #participate
for any comment 👇
@R_e_a_d_e_rs
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚
🔴 ከሁለት ቢልዮን ሰዎች አንድ ሰው ብቻ 116 👩🦳👨🦳 ዓመትና ከዛ በላይ የመኖር እድል አለው። አይዞአችሁ የላቹበትም 😜😜😜
🔷 በ1926 ቴሌ ቪዥንን ( Television )📺 የፈጠረው ሰው እንግሊዛዊው Baird ነበር።
🎥 Quote :- What lies ahead will always be a mystery. Do not be afraid to explore.
🔶 ባሕረ ሀሳብ ማለት የግዕዝ ቃል ሲሆን በአረብኛ አቡሻከር በአማርኛ የዘመን አቆጣጠር 📆ይባላል። የቀመረው 12ኛው የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ ድሜጥሮስ 👳♂ነበሩ።
🔷 ይህን ይሞክሩ!
ባለ ሶስት አሐዝ ቁጥር ይምረጡ። ከዛም በ 7፣ በ 11 እና በ 13 ያባዙት። የሚያገኙት ውጤት የባለሶስት አሐዙን ሁለት ጊዜ የተደገመ ይሆናል።
ለምሳሌ :- 574 ብንወስድና በ 7፣ በ 11 እና በ 13 ቢያባዙት የመጨረሻው መልስ 574,574 ይሆናል።🎞🎞🎞
❣ እናመሠግናለን ❣
#share #participate
for any comment 👇
@R_e_a_d_e_rs
📗📒📕📘📗📒📕👇
@Readers_To_Know
📚📚📚📚📚📚📚📚