💫ከታሪክ ማህደር💫
ክፍል ሁለት
በሚኒሊክ ጊዜ በጥቅምት 15 ቀን 1900 ዓ.ም በተደረገው ሹምሽር የመጀመሪያ ምርጫ ለማግኘት የታደሉትም ቀጥሎ የተመለከቱት ናቸው።
1. አፈንጉስ ነሲቡ መስቀሎ .... የፍርድ ሚኒስትር
2. ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ዲነግዴ .... የጦር ሚኒስትር
3. ጸሐፌ ትዕዛዝ ገብረ ሥላሴ ወልደ አረጋይ .... የጽሕፈት ሚኒሰትር
4. ሊቀ መኳስ ከተማ .... ያገር ግዛት ሚኒሰትር
5. በጅሮንድ ሙሉጌታ ይገዙ .... የገንዘብ ሚኒስትር
6. ነጋድራስ ኃይለ ጊዮርጊስ ወልደ ሚካኤል .... የንግድና የውጭ ጉዳይ ሚኒሰትር
7. ከንቲባ ወልደ ፃድቅ ጎሹ .... የእርሻ ሚኒስትር
8. ቀኝአዝማች መኮንን ተወንድበላይ .... የሥራ ሚኒስትር
9. አዛዥ መታፈሪያ መልከ ፄዲቅ .... የግቢ ሚኒስትር
10. ልጅ በየነ ይመር .... የፖስታ ቴሌግራፍ እና ቴሌፎን ሹም
11. መላከ ፀሐይ ኤስድሮስ .... የትምህርት ሚኒሰትር
📖📖📔ከ "አቤቶ እያሱ" መጽሐፍ በጥቂቱ የተቃረመ
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
ክፍል ሁለት
በሚኒሊክ ጊዜ በጥቅምት 15 ቀን 1900 ዓ.ም በተደረገው ሹምሽር የመጀመሪያ ምርጫ ለማግኘት የታደሉትም ቀጥሎ የተመለከቱት ናቸው።
1. አፈንጉስ ነሲቡ መስቀሎ .... የፍርድ ሚኒስትር
2. ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ዲነግዴ .... የጦር ሚኒስትር
3. ጸሐፌ ትዕዛዝ ገብረ ሥላሴ ወልደ አረጋይ .... የጽሕፈት ሚኒሰትር
4. ሊቀ መኳስ ከተማ .... ያገር ግዛት ሚኒሰትር
5. በጅሮንድ ሙሉጌታ ይገዙ .... የገንዘብ ሚኒስትር
6. ነጋድራስ ኃይለ ጊዮርጊስ ወልደ ሚካኤል .... የንግድና የውጭ ጉዳይ ሚኒሰትር
7. ከንቲባ ወልደ ፃድቅ ጎሹ .... የእርሻ ሚኒስትር
8. ቀኝአዝማች መኮንን ተወንድበላይ .... የሥራ ሚኒስትር
9. አዛዥ መታፈሪያ መልከ ፄዲቅ .... የግቢ ሚኒስትር
10. ልጅ በየነ ይመር .... የፖስታ ቴሌግራፍ እና ቴሌፎን ሹም
11. መላከ ፀሐይ ኤስድሮስ .... የትምህርት ሚኒሰትር
📖📖📔ከ "አቤቶ እያሱ" መጽሐፍ በጥቂቱ የተቃረመ
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
💫ከታሪክ ማህደር💫
ክፍል ሦስት
1. ቢትወደድ ኃይለ ጊዮርጊስ ወልደ ሚካኤል .... ጠቅላይ ሚኒስትር እና የንግድ ሚኒሰትር
2. ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ዲነግዴ .... የጦር ሚኒስትር
3. አፈ ንጉሥ ጥላሁን ሀብቴ .... የፍርድ ሚኒስትር
4. ደጅ አዝማች አብርሀ አርአያ .... የአገር ግዛት ሚኒስትር
5. በጅሮንድ ይገዙ በሀብቴ .... የገንዘብ ሚኒስትር
6. ፀሐፌ ትዕዛዝ አፈወርቅ ወልደ ማርያም .... የጽሕፈት ሚኒስትር
7. ቀኝአዝማች በየነ ይመር .... የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር
8. አዛዥ ግዛው .... የሥራ ሚኒስትር
9. መልአከ ፀሐይ ኤስድሮስ እስጢፋኖስ .... የትምህርት ሚኒስትር እና ሊቀ ካህናት
10. ነጋድራስ ተሰማ እሸቴ .... ፖስታ ሚኒስትር ነበሩ
📖📖📔ከ "አቤቶ እያሱ" መጽሐፍ በጥቂቱ የተቃረመ
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
ክፍል ሦስት
1. ቢትወደድ ኃይለ ጊዮርጊስ ወልደ ሚካኤል .... ጠቅላይ ሚኒስትር እና የንግድ ሚኒሰትር
2. ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ዲነግዴ .... የጦር ሚኒስትር
3. አፈ ንጉሥ ጥላሁን ሀብቴ .... የፍርድ ሚኒስትር
4. ደጅ አዝማች አብርሀ አርአያ .... የአገር ግዛት ሚኒስትር
5. በጅሮንድ ይገዙ በሀብቴ .... የገንዘብ ሚኒስትር
6. ፀሐፌ ትዕዛዝ አፈወርቅ ወልደ ማርያም .... የጽሕፈት ሚኒስትር
7. ቀኝአዝማች በየነ ይመር .... የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር
8. አዛዥ ግዛው .... የሥራ ሚኒስትር
9. መልአከ ፀሐይ ኤስድሮስ እስጢፋኖስ .... የትምህርት ሚኒስትር እና ሊቀ ካህናት
10. ነጋድራስ ተሰማ እሸቴ .... ፖስታ ሚኒስትር ነበሩ
📖📖📔ከ "አቤቶ እያሱ" መጽሐፍ በጥቂቱ የተቃረመ
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
💫ከታሪክ ማህደር💫
ክፍል አራት
ነጋድራስ ተሰማ እሸቴ የአቤቶ ታማኝ አገልጋይ እና በዐጤ ሚኒሊክ መልካም ፈቃድ በ1900 ዓ.ም ወደ ጀርመን ሔደው የተሽከርካሪ እደ ጥበባዊ ዕውቀት ( automotive skill ) ቀስመዋል። እንዲሁም በቆይታቸው "ሂስ ማስተርስ ቮይስ" ከሚባል ኩባንያ ጋር በመዋዋል 17 ዲስኮችን በዘለሰኛና መዲና በማስቀረፅ 17ሺህ የጀርመን ማርክ የተከፈላቸው የመጀመሪያው ዘመናዊ ኢትዮጵያዊ የኪነት ሰው ናቸው።
ነጋድራስ ተሰማ እሸቴ የመጀመሪያው ሹፌር መካኒክ ፣ የመጀመሪያው ዲስክ ያስቀረፀ ኢትዮጵያዊ ሠዓሊና የቅርፃ ቅርፅ ሥራ ባለሞያ ሲሆኑ ከዚህም ሁሉ በላይ አንቱ ባሰኟቸው በሠምና ወርቅ ቅኔዎቻቸው ይታወቃሉ።
የአፍሪካ ዋንጫ እንዲጀመር ትልቅ አስተዋፅኦ ያደረጉት ይድነቃቸው ተሰማ የነጋድራሱ ልጅ ነበሩ።
ጥቅምት 3 ቀን 1957 ዓ.ም በ87 ዓመታቸው ከዚህ አለም በሞት ተለዩ።😔😔😔😔
📖📖📔ከ "አቤቶ እያሱ" መጽሐፍ በጥቂቱ የተቃረመ
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
ክፍል አራት
ነጋድራስ ተሰማ እሸቴ የአቤቶ ታማኝ አገልጋይ እና በዐጤ ሚኒሊክ መልካም ፈቃድ በ1900 ዓ.ም ወደ ጀርመን ሔደው የተሽከርካሪ እደ ጥበባዊ ዕውቀት ( automotive skill ) ቀስመዋል። እንዲሁም በቆይታቸው "ሂስ ማስተርስ ቮይስ" ከሚባል ኩባንያ ጋር በመዋዋል 17 ዲስኮችን በዘለሰኛና መዲና በማስቀረፅ 17ሺህ የጀርመን ማርክ የተከፈላቸው የመጀመሪያው ዘመናዊ ኢትዮጵያዊ የኪነት ሰው ናቸው።
ነጋድራስ ተሰማ እሸቴ የመጀመሪያው ሹፌር መካኒክ ፣ የመጀመሪያው ዲስክ ያስቀረፀ ኢትዮጵያዊ ሠዓሊና የቅርፃ ቅርፅ ሥራ ባለሞያ ሲሆኑ ከዚህም ሁሉ በላይ አንቱ ባሰኟቸው በሠምና ወርቅ ቅኔዎቻቸው ይታወቃሉ።
የአፍሪካ ዋንጫ እንዲጀመር ትልቅ አስተዋፅኦ ያደረጉት ይድነቃቸው ተሰማ የነጋድራሱ ልጅ ነበሩ።
ጥቅምት 3 ቀን 1957 ዓ.ም በ87 ዓመታቸው ከዚህ አለም በሞት ተለዩ።😔😔😔😔
📖📖📔ከ "አቤቶ እያሱ" መጽሐፍ በጥቂቱ የተቃረመ
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
💫ቅምሻ 💫
መጣን ብለው ላኩ ድግሱ ቢያምራቸው፤
እኛም አልቀረንም ሔደን አየናቸው፤
አሉላ አባ ነጋ አስተናገዳቸው፤
አገር ብለው መጡ አገር ሰጠናቸው፤
የደከሙበትን አፈር አጋጥናቸው፤
ግብፆች ፀጋ ወጡ ጣይ ቢያቃጥላቸው፤
እሳት ሆኖ አሉላ አንድዶ ፈጃቸው።
ልብሳቸው በስብሶ ጣሊያኖች ከባሕር፤
የፀሐይዋን ሙቀት ፈልገውት ነበር፤
አሰጣው አሉላ ዘርሮ ከአፈር።
📖 አሉላ አባነጋ በማሞ ውድነህ
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
መጣን ብለው ላኩ ድግሱ ቢያምራቸው፤
እኛም አልቀረንም ሔደን አየናቸው፤
አሉላ አባ ነጋ አስተናገዳቸው፤
አገር ብለው መጡ አገር ሰጠናቸው፤
የደከሙበትን አፈር አጋጥናቸው፤
ግብፆች ፀጋ ወጡ ጣይ ቢያቃጥላቸው፤
እሳት ሆኖ አሉላ አንድዶ ፈጃቸው።
ልብሳቸው በስብሶ ጣሊያኖች ከባሕር፤
የፀሐይዋን ሙቀት ፈልገውት ነበር፤
አሰጣው አሉላ ዘርሮ ከአፈር።
📖 አሉላ አባነጋ በማሞ ውድነህ
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
💫ቅምሻ💫
አህያ ሁን አለኝ አህያ ሆንኩለት፤
አሰሱን ገሰሱን እንድሸከምለት።
መጋዣ ሁን ብሎ ፈረሱ አደረገኝ፤
በየዳገቱ ላይ ወስዶ ሚጋልበኝ፤
እንጃ ግን ሰሞኑን በግ ነህ ተብያለሁ፤
ሊያርደኝ ነው መሰለኝ አሁን ፈርቻለሁ።
ሎሬት ፀጋዬ ገብረ-መድህን
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
አህያ ሁን አለኝ አህያ ሆንኩለት፤
አሰሱን ገሰሱን እንድሸከምለት።
መጋዣ ሁን ብሎ ፈረሱ አደረገኝ፤
በየዳገቱ ላይ ወስዶ ሚጋልበኝ፤
እንጃ ግን ሰሞኑን በግ ነህ ተብያለሁ፤
ሊያርደኝ ነው መሰለኝ አሁን ፈርቻለሁ።
ሎሬት ፀጋዬ ገብረ-መድህን
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
💫 ከታሪክ ማህደር 💫
የመጀመሪያዋ ሴት የፓርላማ ተመራጭ የቀይ መስቀል መስራች ደራሲ ገጣሚ አርበኛ
ወይዘሮ ስንዱ ገብሩ
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
የመጀመሪያዋ ሴት የፓርላማ ተመራጭ የቀይ መስቀል መስራች ደራሲ ገጣሚ አርበኛ
ወይዘሮ ስንዱ ገብሩ
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
💫ቅምሻ💫
ክፍል አንድ
" አሁን የሰው ምንነት ግልጽ ብሎ ታየኝ። ሰው ማለት የተፈጠረ መፍጠር የማይችል የሚመግበውና የሚጠብቀው ያለው ነፍስና ሥጋ ያለው ከነፍስ ከሥጋ አንድ የሆነ በነፍስ አካልነት የቆመ የሚያስተውል ፣ የሚያስብ ፣ የሚናገር ፣ የሚንቀሳቀስ ፣ ሥጋ ብቻ ያልሆነ ፣ ነፍስም ብቻ ያልሆነ ፣ ፍፁመ ሥጋ ወነፍስ ፣ ፍፁመ ጸጋ ፣ ምሉዐ ጸጋ ፣ መንግል ያለው ፍጥረት ነው። "
ገፅ 94
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
ክፍል አንድ
" አሁን የሰው ምንነት ግልጽ ብሎ ታየኝ። ሰው ማለት የተፈጠረ መፍጠር የማይችል የሚመግበውና የሚጠብቀው ያለው ነፍስና ሥጋ ያለው ከነፍስ ከሥጋ አንድ የሆነ በነፍስ አካልነት የቆመ የሚያስተውል ፣ የሚያስብ ፣ የሚናገር ፣ የሚንቀሳቀስ ፣ ሥጋ ብቻ ያልሆነ ፣ ነፍስም ብቻ ያልሆነ ፣ ፍፁመ ሥጋ ወነፍስ ፣ ፍፁመ ጸጋ ፣ ምሉዐ ጸጋ ፣ መንግል ያለው ፍጥረት ነው። "
ገፅ 94
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
💫ቅምሻ💫
ክፍል ሁለት
" ኤርሚያስ ሲመራመር እግዚአብሔር አንድ ትዕዛዝ ሰጠው። ኤርምያስ ተመልከት አለው ኤርሚያስም እሺ ብሎ ሳለ አንድ ፈጣን ፈረሰኛ በፊቱ በታላቅ ፍጥነት እየጋለበ አለፈ። ፈጣሪም ኤርሚያስን 'ኤርምያስ ይህን ፈረሰኛ ተከተል' ብሎ ባዘዘው ጊዜ ኤርምያስ እንደነገረኝ ለመከተል ሞክሬ ነበር አለኝ። ከዚያስ ብለው አልቻልኩም አለኝ። ሌላ የሚገርም ነገር ልንገርህ፥ ፈጣሪዬም አዘዘኝ። አሁን ደግሞ ሌላ ፈረሰኛ መጣና ተከተለው አለኝ። ያሁኑ ፈረሰኛ ደግሞ ነፋስ ነበር። በሰንጋ ፈረሱ ተቀምጦ ለማየት በማይቻል ፍጥነት አለፈ። አሁንም ፈጣሪዬ ኤርምያስ ተከተለው አለኝ። እኔም አምላኬ ሆይ እንኳን የነፋስ ጋላቢውን የመጀመርያውን የሰው ጋላቢ መከተል አልቻልኩም ብዬ ብመልስ ፈጣሪዬም መለሰልኝ የሰው አቅምንም አስታወቀኝ።
🤔 እንቅልፍ ሲወስደው ራሱን ስለማያቅ የሰውነት ማንነት አቅምን ተረዳሁ። ፈጣሪዬም አየህ ኤርምያስ የመጀመሪያው ፈረሰኛ ያንተ ሐሳብ ነው። ሁለተኛው እኔ ነኝ። አንተም ለመከተል ሞክረህ የነበረው ደግሞ ያቃተህ እንኳን የኔን ነገር የራስህን ሐሳብ እንኳ ልትመረምርና ልታውቀው እንደማይችል ነው ፤ ብሎ አምላክ ገለጸልኝ ያለውን ካወጋኝ በኋላ ተለየኝ። "
ገፅ 119
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
ክፍል ሁለት
" ኤርሚያስ ሲመራመር እግዚአብሔር አንድ ትዕዛዝ ሰጠው። ኤርምያስ ተመልከት አለው ኤርሚያስም እሺ ብሎ ሳለ አንድ ፈጣን ፈረሰኛ በፊቱ በታላቅ ፍጥነት እየጋለበ አለፈ። ፈጣሪም ኤርሚያስን 'ኤርምያስ ይህን ፈረሰኛ ተከተል' ብሎ ባዘዘው ጊዜ ኤርምያስ እንደነገረኝ ለመከተል ሞክሬ ነበር አለኝ። ከዚያስ ብለው አልቻልኩም አለኝ። ሌላ የሚገርም ነገር ልንገርህ፥ ፈጣሪዬም አዘዘኝ። አሁን ደግሞ ሌላ ፈረሰኛ መጣና ተከተለው አለኝ። ያሁኑ ፈረሰኛ ደግሞ ነፋስ ነበር። በሰንጋ ፈረሱ ተቀምጦ ለማየት በማይቻል ፍጥነት አለፈ። አሁንም ፈጣሪዬ ኤርምያስ ተከተለው አለኝ። እኔም አምላኬ ሆይ እንኳን የነፋስ ጋላቢውን የመጀመርያውን የሰው ጋላቢ መከተል አልቻልኩም ብዬ ብመልስ ፈጣሪዬም መለሰልኝ የሰው አቅምንም አስታወቀኝ።
🤔 እንቅልፍ ሲወስደው ራሱን ስለማያቅ የሰውነት ማንነት አቅምን ተረዳሁ። ፈጣሪዬም አየህ ኤርምያስ የመጀመሪያው ፈረሰኛ ያንተ ሐሳብ ነው። ሁለተኛው እኔ ነኝ። አንተም ለመከተል ሞክረህ የነበረው ደግሞ ያቃተህ እንኳን የኔን ነገር የራስህን ሐሳብ እንኳ ልትመረምርና ልታውቀው እንደማይችል ነው ፤ ብሎ አምላክ ገለጸልኝ ያለውን ካወጋኝ በኋላ ተለየኝ። "
ገፅ 119
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
👆👆👆👆👆👆👆👆👆
ከላይ የምናያቸው
ሰው ምንድን ነው? (ምንትኑ ውእቱ ሰብእ?)
የማንነትን ትርጉም ፍለጋ ከሚለው የዶክተር ዘበነ ለማ መጽሐፍ የተወሰዱ ናቸው።
© 2011
ዋጋ 99.99 ብር
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
ከላይ የምናያቸው
ሰው ምንድን ነው? (ምንትኑ ውእቱ ሰብእ?)
የማንነትን ትርጉም ፍለጋ ከሚለው የዶክተር ዘበነ ለማ መጽሐፍ የተወሰዱ ናቸው።
© 2011
ዋጋ 99.99 ብር
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
ይህን መጽሐፍ የፃፉት
ዶክተር ዘበነ ለማ በነገረ መለኮት ትምህርት ከቅድስት ስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ የመጀመሪያ ዲግሪ በማስተርስ ዲግሪ ስለአለም እምነቶች ጥናትና ፍልስፍና በሀዋርድ ዩኒቨርስቲ በዶክትሬት ዲግሪ በሥነ አመራር እና አንትሮፖሎጂ ጥናት ከሀዋርድ ዩኒቨርስቲ በከፍተኛ ማዕረግ ተምረው ፈጽመዋል።
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
ዶክተር ዘበነ ለማ በነገረ መለኮት ትምህርት ከቅድስት ስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ የመጀመሪያ ዲግሪ በማስተርስ ዲግሪ ስለአለም እምነቶች ጥናትና ፍልስፍና በሀዋርድ ዩኒቨርስቲ በዶክትሬት ዲግሪ በሥነ አመራር እና አንትሮፖሎጂ ጥናት ከሀዋርድ ዩኒቨርስቲ በከፍተኛ ማዕረግ ተምረው ፈጽመዋል።
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
😂😂😂ለፈገግታ 😂😂😂
ወንዱ :- ይሄንን ቀን በጉጉት ስጠብቅ ነበር
ሴቷ :- ትቼህ እንድሄድ ትፈቅድልኛለህ ?
ወንዱ :- በፍፁም
ሴቷ :- ትወደኛለህ ?
ወንዱ :- አዎን
ሴቷ :- በላዬ ላይ ከሌላ ሴት ጋር
ታመነዝራለህ ?
ወንዱ :- በፍፁም አላደረገውም
ሴቷ :- ትስመኛለህ ?
ወንዱ :- ባገኘሁት አጋጣሚ ሁሉ
ሴቷ :- ትመታኛለህ ?
ወንዱ :- ምን በወጣኝ
ሴቷ :- ልመንህ ?
ወንዱ :- Yes
ሴቷ :- የኔ ፍቅር
” ከጋብቻ በኋላ ከታች ወደ ላይ አንብቡት ”
ምንጭ:-http://www.yasekal.com
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
ወንዱ :- ይሄንን ቀን በጉጉት ስጠብቅ ነበር
ሴቷ :- ትቼህ እንድሄድ ትፈቅድልኛለህ ?
ወንዱ :- በፍፁም
ሴቷ :- ትወደኛለህ ?
ወንዱ :- አዎን
ሴቷ :- በላዬ ላይ ከሌላ ሴት ጋር
ታመነዝራለህ ?
ወንዱ :- በፍፁም አላደረገውም
ሴቷ :- ትስመኛለህ ?
ወንዱ :- ባገኘሁት አጋጣሚ ሁሉ
ሴቷ :- ትመታኛለህ ?
ወንዱ :- ምን በወጣኝ
ሴቷ :- ልመንህ ?
ወንዱ :- Yes
ሴቷ :- የኔ ፍቅር
” ከጋብቻ በኋላ ከታች ወደ ላይ አንብቡት ”
ምንጭ:-http://www.yasekal.com
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
💫የእለቱ ጥቆማ💫
👉የ ወንድ ልጅ ምጥ
፩.አይነት፡የግጥም መድብል
፪.ደራሲ:ይስምዕከ ወርቁ
፫.የ መጀመርያ እትም:ሀምሌ 1999 ዓ.ም
፬.ገፅ ብዛት:80
፭.የግጥም ብዛት:60
፮.ልዩ ጥቆማ:
1.ፈሶሎጂ(ገፅ 35)
2.የወንድ ልጅ ምጥ(ገፅ75)
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
👉የ ወንድ ልጅ ምጥ
፩.አይነት፡የግጥም መድብል
፪.ደራሲ:ይስምዕከ ወርቁ
፫.የ መጀመርያ እትም:ሀምሌ 1999 ዓ.ም
፬.ገፅ ብዛት:80
፭.የግጥም ብዛት:60
፮.ልዩ ጥቆማ:
1.ፈሶሎጂ(ገፅ 35)
2.የወንድ ልጅ ምጥ(ገፅ75)
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
📺👉ከታሪክ ማህደር 👈📺
ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለ ማርያም በስልጣን ዘመናቸው ከተናገሯቸው በቴሌቪዥን መስኮት ከቀረቡት ውስጥ በጥቂቱ
📺 "እያንዳንዱ ደቂቃና ሴኮንድ በእያንዳንዱ ወገናችን ህይወት ላይ ይወስናል።እና ቅድም እንዳልኳቹ እነሱ ከእረኛ እስከ ምሁር ተነስተው ለእኩይ አላማቸው ተሰልፈው ሲያበቁ ይህን ያደርጋሉ።ንቀውናል ደፍረውናል ብታምኑም ባታምኑም በቁም ሞተናል። ውይይት ነው ሰላማዊ ሰልፍ ነው ወይስ እንደወያኔ ወጣቶች ታጥቃቹ ትሰለፋላቹ።"
📺 "አብዮታዊ ሰራዊታችን ከሕዝብ እንዳልተወለደ እና የሕዝብ ወገን እንዳልሆነ ሁሉ ፤ ይህንን ገበሬ እየሞተ ባለመሬት እንዳላደረገ ሁሉ ፤ እየለመነ ብስኩትና ዱቄት እንደማያድል ሁሉ ፤ ዛሬ በአክሱም በአደዋ በሽሬ ወዘተርፈ እንደ ጠላት ጦር ይሀው እርሱ ገበሬው እንደ አንበጣ ተሰባስበው እየተከተከው ነው። ......... ኋላቀሮች ረሀብተኞች ችጋራም የምንባለው ከዚሁ ክልል በሚመነጭ ችግር ነው።"
📺 "እንግዲ ሁሉም ለከትና መቼም ወሰን አለው። እኔ ግራህን ሲመቱህ ቀኙን ስጥ የሚባል እምነት የለኝም። በተለይ እንደንደዚህ አይነት የአካባቢያችን እብሪተኞች ደግሞ የሚገባቸው ቋንቋ ዲፕሎማሲ ሳይሆን አፍንጫቸውን ማለት ነው።"
📺 "ሁሉም አኩራፊ፤ ሁሉም ነፃ አውጪ ነኝ ባይ ፤ ሁሉም ተሳዳቢ እና ተቺ ፤ ወርቅ ቢያነጥፉለት ፋንዲያ ነው የሚል ፤ ምን አደረጋችሁልኝ እንጂ እኔ ምን አደረኩ የማይል ቁጥር ጥቂት ባልሆነበት ሁኔታ ውስጥ ምን ተዓምር እንድንሰራ ይጠበቅብናል።"
📺 "እኔ በበኩሌ እኔ ብሎ መናገር ልምዴ እንዳልሆነና እንደማልወደውም ታውቃላችሁ። በዚህ የታሪክ አጋጣሚ በኢትዮጵያ ሕዝብ ፍላጎትና ፈቃድ በተሰጠኝ ሀላፊነት እና በተጣለብኝ እምነትና አደራ ለእናት ሀገሬና ወገኔ ካለኝ ጥልቅ ፍቅር ምን አስተዋፅኦ አደርጋለሁ በሚል እንጂ ከዚህ በተረፈ ቅንጣት ታህል እደግመዋለሁ ቅንጣት ታህል የሥልጣን ጥማትና ምኞት የለኝም።"
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለ ማርያም በስልጣን ዘመናቸው ከተናገሯቸው በቴሌቪዥን መስኮት ከቀረቡት ውስጥ በጥቂቱ
📺 "እያንዳንዱ ደቂቃና ሴኮንድ በእያንዳንዱ ወገናችን ህይወት ላይ ይወስናል።እና ቅድም እንዳልኳቹ እነሱ ከእረኛ እስከ ምሁር ተነስተው ለእኩይ አላማቸው ተሰልፈው ሲያበቁ ይህን ያደርጋሉ።ንቀውናል ደፍረውናል ብታምኑም ባታምኑም በቁም ሞተናል። ውይይት ነው ሰላማዊ ሰልፍ ነው ወይስ እንደወያኔ ወጣቶች ታጥቃቹ ትሰለፋላቹ።"
📺 "አብዮታዊ ሰራዊታችን ከሕዝብ እንዳልተወለደ እና የሕዝብ ወገን እንዳልሆነ ሁሉ ፤ ይህንን ገበሬ እየሞተ ባለመሬት እንዳላደረገ ሁሉ ፤ እየለመነ ብስኩትና ዱቄት እንደማያድል ሁሉ ፤ ዛሬ በአክሱም በአደዋ በሽሬ ወዘተርፈ እንደ ጠላት ጦር ይሀው እርሱ ገበሬው እንደ አንበጣ ተሰባስበው እየተከተከው ነው። ......... ኋላቀሮች ረሀብተኞች ችጋራም የምንባለው ከዚሁ ክልል በሚመነጭ ችግር ነው።"
📺 "እንግዲ ሁሉም ለከትና መቼም ወሰን አለው። እኔ ግራህን ሲመቱህ ቀኙን ስጥ የሚባል እምነት የለኝም። በተለይ እንደንደዚህ አይነት የአካባቢያችን እብሪተኞች ደግሞ የሚገባቸው ቋንቋ ዲፕሎማሲ ሳይሆን አፍንጫቸውን ማለት ነው።"
📺 "ሁሉም አኩራፊ፤ ሁሉም ነፃ አውጪ ነኝ ባይ ፤ ሁሉም ተሳዳቢ እና ተቺ ፤ ወርቅ ቢያነጥፉለት ፋንዲያ ነው የሚል ፤ ምን አደረጋችሁልኝ እንጂ እኔ ምን አደረኩ የማይል ቁጥር ጥቂት ባልሆነበት ሁኔታ ውስጥ ምን ተዓምር እንድንሰራ ይጠበቅብናል።"
📺 "እኔ በበኩሌ እኔ ብሎ መናገር ልምዴ እንዳልሆነና እንደማልወደውም ታውቃላችሁ። በዚህ የታሪክ አጋጣሚ በኢትዮጵያ ሕዝብ ፍላጎትና ፈቃድ በተሰጠኝ ሀላፊነት እና በተጣለብኝ እምነትና አደራ ለእናት ሀገሬና ወገኔ ካለኝ ጥልቅ ፍቅር ምን አስተዋፅኦ አደርጋለሁ በሚል እንጂ ከዚህ በተረፈ ቅንጣት ታህል እደግመዋለሁ ቅንጣት ታህል የሥልጣን ጥማትና ምኞት የለኝም።"
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
💫ከዚም ከዛም💫
#1. ሉሲ (ድንቅነሽ) ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘችው በታዋቂዎቹ ሳይንቲስቶች ዶናልድ ጆሀንሰን እና ይቬስ ካኘንስ ነበር።
#2. አሜሪካ ስያሜዋን ያገኘችው አሜሪጎ ቬስፑቺ ከተሰኘውና በ1499 ሀገሪቱን ካገኘው ኢጣሊያዊ የባሕር አሳሽ ነው።
#3. የመጀመሪያዋ የሴት መንኮራኩር አብራሪ የ26 አመቷ ቫለንቲና ተሬሽኮቫ ትባላለች።
#4. ከኢትዮጵያ አንደኛ ከአፍሪካ አራተኛ የሆነው ራስዳሽን 4620m ከባሕር ጠለል በላይ እርዝማኔ አለው።
#5. ንብ አንድ ፓዎንድ የሚመዝንን ማር ለመስራት 55,000 ማይል እና 2,000,000 አበባዎችን መቅሰም አለባት።
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
#1. ሉሲ (ድንቅነሽ) ለመጀመሪያ ጊዜ የተገኘችው በታዋቂዎቹ ሳይንቲስቶች ዶናልድ ጆሀንሰን እና ይቬስ ካኘንስ ነበር።
#2. አሜሪካ ስያሜዋን ያገኘችው አሜሪጎ ቬስፑቺ ከተሰኘውና በ1499 ሀገሪቱን ካገኘው ኢጣሊያዊ የባሕር አሳሽ ነው።
#3. የመጀመሪያዋ የሴት መንኮራኩር አብራሪ የ26 አመቷ ቫለንቲና ተሬሽኮቫ ትባላለች።
#4. ከኢትዮጵያ አንደኛ ከአፍሪካ አራተኛ የሆነው ራስዳሽን 4620m ከባሕር ጠለል በላይ እርዝማኔ አለው።
#5. ንብ አንድ ፓዎንድ የሚመዝንን ማር ለመስራት 55,000 ማይል እና 2,000,000 አበባዎችን መቅሰም አለባት።
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
💫 ጥቆማ 💫
ሮሜዎና ዡልዬት
ቴአትር
ከከበደ ሚካኤል
ይህ መጽሐፍ አርተር ብሩክ የሚባል አንድ የእንግሊዝ ባለቅኔ መዠመሪያ በግጥም ጻፈው።ቀጥሎ ሼክስፒር ይህን ቅኔ መሠረት አድርጎ በመከተል ቴአትር አድርጎ አቀረበው።ከበደ ሚካኤልም በዚህ መጽሐፉ በግጥም ዘውግ ወደ አማርኛ ለመግለጥ እንዲመቸው አድርጎ አቅርቦታል።
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
ሮሜዎና ዡልዬት
ቴአትር
ከከበደ ሚካኤል
ይህ መጽሐፍ አርተር ብሩክ የሚባል አንድ የእንግሊዝ ባለቅኔ መዠመሪያ በግጥም ጻፈው።ቀጥሎ ሼክስፒር ይህን ቅኔ መሠረት አድርጎ በመከተል ቴአትር አድርጎ አቀረበው።ከበደ ሚካኤልም በዚህ መጽሐፉ በግጥም ዘውግ ወደ አማርኛ ለመግለጥ እንዲመቸው አድርጎ አቅርቦታል።
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
💫 ከታሪክ ማህደር 💫
ከበደ ሚካኤል በኢትየጵያ ስነጽሑፍ ታሪክ ውስጥ ገናና ከሆኑት ደራስያን አንዱ ናቸው። ጥቅምት 23፣ 1909 የተወለዱት ባለቅኔ የቤተክህነትን ትምህርት ካገባደዱ በኋላ በአሊያንስ ፍራንሴዝና በላዛሪስት ሚስዮን ዘመናዊ ትምህርትን ተከታትለዋል።
የግሪክ፣ የሮማውያን፣ የእንግሊዝ፣ የፈረንሳይ፣ የጀርመን፣ የሩስያና የጣልያንን በርካታ መፃህፍት ከመረመሩም በኋላ 26 መፃህፍትን ለወገኖቻቸው አበርክተዋል።
የአዲስ አበባ ዪኒቨርሲቲ ለዚሁ አስተዋፅኦዋቸው የክብር ዶክተርነት ዲግሪን በ1990 ሰጥቷቸዋል።
በሜጋ አሳታሚ ድርጅት ታትመው ለአንባብያን ከቀረቡት መሀከል
1. ታሪክና ምሳሌ (፩ኛ መጽሐፍ)
2. ታሪክና ምሳሌ (፪ኛ መጽሐፍ)
3. የቅኔ ውበት
4. ሮሜዎና ዡልዬት
5. የዕውቀት ብልጭታ
6. ጃፓን እንደምን ሠለጠነች
7. ታላላቅ ሰዎች
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫
ከበደ ሚካኤል በኢትየጵያ ስነጽሑፍ ታሪክ ውስጥ ገናና ከሆኑት ደራስያን አንዱ ናቸው። ጥቅምት 23፣ 1909 የተወለዱት ባለቅኔ የቤተክህነትን ትምህርት ካገባደዱ በኋላ በአሊያንስ ፍራንሴዝና በላዛሪስት ሚስዮን ዘመናዊ ትምህርትን ተከታትለዋል።
የግሪክ፣ የሮማውያን፣ የእንግሊዝ፣ የፈረንሳይ፣ የጀርመን፣ የሩስያና የጣልያንን በርካታ መፃህፍት ከመረመሩም በኋላ 26 መፃህፍትን ለወገኖቻቸው አበርክተዋል።
የአዲስ አበባ ዪኒቨርሲቲ ለዚሁ አስተዋፅኦዋቸው የክብር ዶክተርነት ዲግሪን በ1990 ሰጥቷቸዋል።
በሜጋ አሳታሚ ድርጅት ታትመው ለአንባብያን ከቀረቡት መሀከል
1. ታሪክና ምሳሌ (፩ኛ መጽሐፍ)
2. ታሪክና ምሳሌ (፪ኛ መጽሐፍ)
3. የቅኔ ውበት
4. ሮሜዎና ዡልዬት
5. የዕውቀት ብልጭታ
6. ጃፓን እንደምን ሠለጠነች
7. ታላላቅ ሰዎች
👇👇👇👇👇👇👇👇
@Readers_To_Know
💫💫💫💫💫💫💫💫