በማህበራዊ ሚዲያ አንዲት ታዳጊ ስትደበደብ የሚያሳይ ቪዲዮን በተመለከተ ፖሊስ አስፈላጊውን ምርመራ ማጣራቱን አስታወቀ፡፡
ፈርዶስ መሃመድ ፣ ኤደን ዳዊት እና ሃኒ ሁሴን የተባሉ ታዳጊ ተማሪዎች በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 አለም ባንክ አካባቢ ጓደኛቸውን ሲደበድቧት የሚያሳይ አሳዛኝ ቪዲዮ በማህበራዊ ሚዲያ መሰራጨቱን ተከትሎ ድርጊቱን የፈፀሙት ግለሰቦች በህግ እንዲጠየቁ ህብረተሰቡ አስተያየት እየሰጠ መሆኑ ይታወቃል፡፡
ድርጊቱ ጥቅምት 14 ቀን 2018 መፈፀሙን የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቆ ቪዲዮው በማህበራዊ ሚዲያ ከመሰራጨቱ ከወራት በፊት ወንጀሉን የፈፀሙትን ሦስት ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ ማጣራቱን ፖሊስ ገልጿል፡፡
በወንጀሉ የተጠረጠሩት ሦስት ተማሪዎች ፍርድ ቤት ቀርበው በጊዜ ቀጠሮ ታስረው ፖሊስ አስፈላጊውን ማስረጃ በማሰባሰብ የምርመራ መዝገቡን አጠናቆ መዝገቡን ለሚመለከተው የፍትህ አካል መላኩን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡
ልጅቷ ስትደበደብ የሚያሳየው ቪዲዩ መለቀቁ በልጅቷም ሆነ በቤተሰቧ ላይ አሉታዊ ጫና የሚያሳድር በመሆኑ ቪዲዮውን የለቀቀውን አካል ለማረጋገጥ ፖሊስ ሦስቱን ተጠርጣሪዎች በድጋሚ በቁጥጥር ስር አውሎ ተጨማሪ ምርመራ እያጣራ መሆኑን ገልጿል፡፡
ህብረተሰቡ ድርጊቱን በማውገዝ ወንጀሉን የፈፀሙ ሰዎች በህግ መጠየቅ እንዳለባቸው ያሳየውን መቆርቆር የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አድንቋል፡፡
የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ
ፈርዶስ መሃመድ ፣ ኤደን ዳዊት እና ሃኒ ሁሴን የተባሉ ታዳጊ ተማሪዎች በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 አለም ባንክ አካባቢ ጓደኛቸውን ሲደበድቧት የሚያሳይ አሳዛኝ ቪዲዮ በማህበራዊ ሚዲያ መሰራጨቱን ተከትሎ ድርጊቱን የፈፀሙት ግለሰቦች በህግ እንዲጠየቁ ህብረተሰቡ አስተያየት እየሰጠ መሆኑ ይታወቃል፡፡
ድርጊቱ ጥቅምት 14 ቀን 2018 መፈፀሙን የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቆ ቪዲዮው በማህበራዊ ሚዲያ ከመሰራጨቱ ከወራት በፊት ወንጀሉን የፈፀሙትን ሦስት ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ ማጣራቱን ፖሊስ ገልጿል፡፡
በወንጀሉ የተጠረጠሩት ሦስት ተማሪዎች ፍርድ ቤት ቀርበው በጊዜ ቀጠሮ ታስረው ፖሊስ አስፈላጊውን ማስረጃ በማሰባሰብ የምርመራ መዝገቡን አጠናቆ መዝገቡን ለሚመለከተው የፍትህ አካል መላኩን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡
ልጅቷ ስትደበደብ የሚያሳየው ቪዲዩ መለቀቁ በልጅቷም ሆነ በቤተሰቧ ላይ አሉታዊ ጫና የሚያሳድር በመሆኑ ቪዲዮውን የለቀቀውን አካል ለማረጋገጥ ፖሊስ ሦስቱን ተጠርጣሪዎች በድጋሚ በቁጥጥር ስር አውሎ ተጨማሪ ምርመራ እያጣራ መሆኑን ገልጿል፡፡
ህብረተሰቡ ድርጊቱን በማውገዝ ወንጀሉን የፈፀሙ ሰዎች በህግ መጠየቅ እንዳለባቸው ያሳየውን መቆርቆር የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አድንቋል፡፡
የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ
“አዲስ አበባ ከ5 ሚሎዮን በላይ ህዝብ የሚኖርባት፤ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ መኪኖች ያሉባት ከተማ ነች፡፡ የዛሬ ሶስት እና አራት አመት ገደማ ብዙ ፓርኪንግ ካመኖሩ የተነሳ አስፓልቱ የመኪና ማቆሚያም ነው፣ መንቀሳቀሻም ነው የእግረኛም መሄጃ ከመሆኑ የተነሳ ለአደጋ ሲያጋልጥ ነበር፡፡” - ክቡር ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አህመድ (ደ/ር)
ዛሬስ ምን ለውጥ ተገኘ? ከዘገባው ይከታተሉ
ዛሬስ ምን ለውጥ ተገኘ? ከዘገባው ይከታተሉ
WOW Dr. Birhanu M Lenjiso
አጭር ግን ተሻጋሪ ሃሳብ፣
ግልፅ ደግሞም እጅግ ጠቃሚ ንግግር
እናመሠግናለን ዶ/ር ብርሃኑ ሌንጂሶ
አጭር ግን ተሻጋሪ ሃሳብ፣
ግልፅ ደግሞም እጅግ ጠቃሚ ንግግር
እናመሠግናለን ዶ/ር ብርሃኑ ሌንጂሶ
#ታግዷል❗️
ከ2.2 ቢሊዮን ብር በላይ ጥሬ ገንዘብ፣ ዋጋቸው ከ220 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ አክሲዮኖች፣ ከ5 ሚሊዮን ካሬ ሜትር በላይ መሬት፣ ከ200 በላይ ቤቶች፣ ከ300 በላይ ተሽከርካሪዎች እና 69 ከባድ ማሽነሪዎች…
በኢትዮጵያ በታክስና ግብር ስወራ፣ በሙስና፣ በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር፣ በኦንላይን ማጭበርበር እና ከሌሎች ከባድ ወንጀሎች ጋር ግንኙነት አለው የተባለ በቢሊየን ብር የሚቆጠር ንብረት መታገዱን የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስታውቋል።
በ2018 ዓ.ም ብቻ በተከናወነ የምርመራና የሕግ ማስከበር ሥራ፣ በ544 የክስ መዝገቦች ሥር የተካተቱ በርካታ ሀብቶች ታግደው የሕግ ሂደታቸውን በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ ተብሏል።
በዚህም መሠረት ከ2.2 ቢሊዮን ብር በላይ ጥሬ ገንዘብ፣ ዋጋቸው ከ220 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ አክሲዮኖች፣ ከ5 ሚሊዮን ካሬ ሜትር በላይ መሬት፣ ከ200 በላይ ቤቶች፣ ከ300 በላይ ተሽከርካሪዎች እና 69 ከባድ ማሽነሪዎች በቁጥጥር ሥር እንዲውሉና እንዲታገዱ መደረጉን ሸገር አኤፍ አኤም ዘግቧል።
ሥራ ላይ ከዋለ ከአንድ ዓመት በላይ የሆነው አዋጁ የሕገ-ወጥ ሀብት ምንጭን በጥብቅ በመመርመርና በማረጋገጥ፣ ንብረቱ ለመንግሥትና ለሕዝብ ጥቅም የሚወረስበትን ግልጽ ሕጋዊ አሰራር ዘርግቷል።
ሕጉ በጸደቀበት ወቅት እስከ 10 ዓመት ወደ ኋላ ተመልሶ ተጠያቂነት እንዲኖር መፍቀዱ በበርካቶች ዘንድ ከፍተኛ ክርክር አስነስቶ እንደነበር ይታወሳል።
በተለመደው የሕግ አሰራር አንድ ንብረት በሕገ-ወጥ መንገድ መገኘቱን ማስረዳት ያለበት ከሳሽ አካል ቢሆንም፤ በዚህ አዋጅ መሠረት ግን «ሀብቴ በሕጋዊ መንገድ የተገኘ ነው» ብሎ የማሳመንና የማስረዳት ሸክሙ ሙሉ በሙሉ የተከሳሹ ነው።
አዋጁ የታወቀ የገቢ ምንጭ ያላቸው ሰዎች ከሚያገኙት ገቢ ጋር ያልተመጣጠነና የተጋነነ የሀብት ልዩነት ሲገኝባቸው ወይም ምክንያታዊ ጥርጣሬ ሲኖር ምርመራ እንዲደረግባቸው ይደነግጋል።
በተመሳሳይ የታወቀ የገቢ ምንጭ የሌላቸው ግለሰቦች ያፈሩትን ሀብት እንዴትና በምን መንገድ እንዳጠራቀሙት ማስረዳት ካልቻሉ፣ ምርመራ ተካሂዶ ክስ በመመሥረት ንብረቱ እንዲወረስ ያዝል።
በጠቅላይ ዐቃቤ-ሕግ የሀብት ማስመለስ ዳይሬክቶሬት ምክትል ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ኃይሌ የአዋጁ ዋና ዓላማ በሕገ-ወጥ መንገድ የተገኘን ሀብት መለየት፣ መመርመር፣ ማገድና የፍርድ ቤት ሂደቱ ሲጠናቀቅ ደግሞ ሙሉ በሙሉ መውረስ እንደሆነ አስረድተዋል።
በ2018 ዓ.ም የታገዱት ጥሬ ገንዘቦች፣ አክሲዮኖች፣ መሬቶችና ሌሎች ንብረቶች ከጀርባቸው ትላልቅ የኢኮኖሚና የማህበራዊ ወንጀሎች ያሉባቸው እንደሆኑ የጠቆሙት ምክትል ዳይሬክተሩ፣ የወንጀል ጉዳዮቹ በሕግ ሂደት ውሳኔ ሲያገኙ የውርስ አቤቱታው በይፋ እንደሚቀጥል አብራርተዋል።
የሀብት ማስመለስ አዋጁ ትግበራ ወደፊትም ተጠናክሮ ይቀጥላል የተባለ ሲሆን፣ ሰሞኑንም የሀገሪቱን የፋይናንስ ሥርዓት የሚያናጉ ተግባራት ላይ የተሰማሩ ናቸው ተብለው የተጠረጠሩ 169 ግለሰቦች እንዲሁም በገቢዎችና ጉምሩክ ዘርፍ የተጠረጠሩ 109 ግለሰቦች ተለይተዋል።
ከእነዚህም መካከል እስካሁን 91 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ውለው ምርመራ እየተካሄደባቸው መሆኑን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ማስታወቁንም ነው ዘገባው ያመላከተው።
ከ2.2 ቢሊዮን ብር በላይ ጥሬ ገንዘብ፣ ዋጋቸው ከ220 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ አክሲዮኖች፣ ከ5 ሚሊዮን ካሬ ሜትር በላይ መሬት፣ ከ200 በላይ ቤቶች፣ ከ300 በላይ ተሽከርካሪዎች እና 69 ከባድ ማሽነሪዎች…
በኢትዮጵያ በታክስና ግብር ስወራ፣ በሙስና፣ በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር፣ በኦንላይን ማጭበርበር እና ከሌሎች ከባድ ወንጀሎች ጋር ግንኙነት አለው የተባለ በቢሊየን ብር የሚቆጠር ንብረት መታገዱን የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስታውቋል።
በ2018 ዓ.ም ብቻ በተከናወነ የምርመራና የሕግ ማስከበር ሥራ፣ በ544 የክስ መዝገቦች ሥር የተካተቱ በርካታ ሀብቶች ታግደው የሕግ ሂደታቸውን በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ ተብሏል።
በዚህም መሠረት ከ2.2 ቢሊዮን ብር በላይ ጥሬ ገንዘብ፣ ዋጋቸው ከ220 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ አክሲዮኖች፣ ከ5 ሚሊዮን ካሬ ሜትር በላይ መሬት፣ ከ200 በላይ ቤቶች፣ ከ300 በላይ ተሽከርካሪዎች እና 69 ከባድ ማሽነሪዎች በቁጥጥር ሥር እንዲውሉና እንዲታገዱ መደረጉን ሸገር አኤፍ አኤም ዘግቧል።
ሥራ ላይ ከዋለ ከአንድ ዓመት በላይ የሆነው አዋጁ የሕገ-ወጥ ሀብት ምንጭን በጥብቅ በመመርመርና በማረጋገጥ፣ ንብረቱ ለመንግሥትና ለሕዝብ ጥቅም የሚወረስበትን ግልጽ ሕጋዊ አሰራር ዘርግቷል።
ሕጉ በጸደቀበት ወቅት እስከ 10 ዓመት ወደ ኋላ ተመልሶ ተጠያቂነት እንዲኖር መፍቀዱ በበርካቶች ዘንድ ከፍተኛ ክርክር አስነስቶ እንደነበር ይታወሳል።
በተለመደው የሕግ አሰራር አንድ ንብረት በሕገ-ወጥ መንገድ መገኘቱን ማስረዳት ያለበት ከሳሽ አካል ቢሆንም፤ በዚህ አዋጅ መሠረት ግን «ሀብቴ በሕጋዊ መንገድ የተገኘ ነው» ብሎ የማሳመንና የማስረዳት ሸክሙ ሙሉ በሙሉ የተከሳሹ ነው።
አዋጁ የታወቀ የገቢ ምንጭ ያላቸው ሰዎች ከሚያገኙት ገቢ ጋር ያልተመጣጠነና የተጋነነ የሀብት ልዩነት ሲገኝባቸው ወይም ምክንያታዊ ጥርጣሬ ሲኖር ምርመራ እንዲደረግባቸው ይደነግጋል።
በተመሳሳይ የታወቀ የገቢ ምንጭ የሌላቸው ግለሰቦች ያፈሩትን ሀብት እንዴትና በምን መንገድ እንዳጠራቀሙት ማስረዳት ካልቻሉ፣ ምርመራ ተካሂዶ ክስ በመመሥረት ንብረቱ እንዲወረስ ያዝል።
በጠቅላይ ዐቃቤ-ሕግ የሀብት ማስመለስ ዳይሬክቶሬት ምክትል ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ኃይሌ የአዋጁ ዋና ዓላማ በሕገ-ወጥ መንገድ የተገኘን ሀብት መለየት፣ መመርመር፣ ማገድና የፍርድ ቤት ሂደቱ ሲጠናቀቅ ደግሞ ሙሉ በሙሉ መውረስ እንደሆነ አስረድተዋል።
በ2018 ዓ.ም የታገዱት ጥሬ ገንዘቦች፣ አክሲዮኖች፣ መሬቶችና ሌሎች ንብረቶች ከጀርባቸው ትላልቅ የኢኮኖሚና የማህበራዊ ወንጀሎች ያሉባቸው እንደሆኑ የጠቆሙት ምክትል ዳይሬክተሩ፣ የወንጀል ጉዳዮቹ በሕግ ሂደት ውሳኔ ሲያገኙ የውርስ አቤቱታው በይፋ እንደሚቀጥል አብራርተዋል።
የሀብት ማስመለስ አዋጁ ትግበራ ወደፊትም ተጠናክሮ ይቀጥላል የተባለ ሲሆን፣ ሰሞኑንም የሀገሪቱን የፋይናንስ ሥርዓት የሚያናጉ ተግባራት ላይ የተሰማሩ ናቸው ተብለው የተጠረጠሩ 169 ግለሰቦች እንዲሁም በገቢዎችና ጉምሩክ ዘርፍ የተጠረጠሩ 109 ግለሰቦች ተለይተዋል።
ከእነዚህም መካከል እስካሁን 91 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ውለው ምርመራ እየተካሄደባቸው መሆኑን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ማስታወቁንም ነው ዘገባው ያመላከተው።
👍1
"እኛ ኢትዮጵያውያን ሕብረ ብሔራዊነትን በማጠናከር በገዥ ትርክት ተሸምነን ተቋማዊ ለውጥን እያጠናከርንና ብሔራዊ ጥቅማችንን እያሳካን ሁለንተናዊ ብልጽግናን ማረጋገጥ አለብን" - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
በአሁኑ ወቅት የሚታየውን የዝናብ ሁኔታ ተከትሎ የጎርፍ አደጋ ሊከሰት ስለሚችል ጥንቃቄዎችን አድርጉ ሲል የአዲስ አበባ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ፡፡
ኮሚሽኑ የጥንቃቄ መልእክቱን በማህበራዊ ትስስር ገጹ ያጋራ ሲሆን ህብረተሰቡ በአሁኑ ወቅት የሚታየውን የዝናብ ሁኔታ ተከትሎ የጎርፍ አደጋ ሊከሰት ስለሚችል ጥንቃቄ ያድርግ ሲል አሳስቧል፡፡በዚህም በወንዝ ዳርቻና ዝቅተኛ ቦታዎች ላይ የሚገኙ ነዋሪዎች የውኃው መጠን ከመጨመሩ በፊት ጥንቃቄ ያድርጉ ብሏል።
በሉላ በኩልም የውኃ መውረጃዎችን መፈተሸ፣ በቤት ዙሪያ ያሉ ቦዮች በቆሻሻ አለመደፈናቸውን ማረጋገጥ እና የልጆችን ውሎ መጠበቅ አስፈላጊ መሆኑ ተጠቁሟል።
ዝናብ በሚዘንብበት ወቅት ልጆች ከቤት እንዳይወጡና ወደ ዋና ዋና የጎርፍ መውረጃዎች እንዳይጠጉ መቆጣጠር ይገባል ተብሏል፡፡
አደገኛ የጎርፍ ምልክት በሚታይበት ወቅት በአደጋ ጊዜ ስልክ 939 ላይ በመደወል ያሳውቁ ሲል ኮሚሽኑ አሳስባል።
ኮሚሽኑ የጥንቃቄ መልእክቱን በማህበራዊ ትስስር ገጹ ያጋራ ሲሆን ህብረተሰቡ በአሁኑ ወቅት የሚታየውን የዝናብ ሁኔታ ተከትሎ የጎርፍ አደጋ ሊከሰት ስለሚችል ጥንቃቄ ያድርግ ሲል አሳስቧል፡፡በዚህም በወንዝ ዳርቻና ዝቅተኛ ቦታዎች ላይ የሚገኙ ነዋሪዎች የውኃው መጠን ከመጨመሩ በፊት ጥንቃቄ ያድርጉ ብሏል።
በሉላ በኩልም የውኃ መውረጃዎችን መፈተሸ፣ በቤት ዙሪያ ያሉ ቦዮች በቆሻሻ አለመደፈናቸውን ማረጋገጥ እና የልጆችን ውሎ መጠበቅ አስፈላጊ መሆኑ ተጠቁሟል።
ዝናብ በሚዘንብበት ወቅት ልጆች ከቤት እንዳይወጡና ወደ ዋና ዋና የጎርፍ መውረጃዎች እንዳይጠጉ መቆጣጠር ይገባል ተብሏል፡፡
አደገኛ የጎርፍ ምልክት በሚታይበት ወቅት በአደጋ ጊዜ ስልክ 939 ላይ በመደወል ያሳውቁ ሲል ኮሚሽኑ አሳስባል።
👍1
ውሃ መንካት ብርቅ የሆነበት የባህር ዳርቻ
በቻይና ሺንዘን የሚገኘው የዳሜሻ የባህር ዳርቻ በአንድ ቀን እስከ 200 ሺህ የሚደርሱ ጎብኚዎችን በማስተናገድ የአለማችን የተጨናነቀ ስፍራ በመሆን ይታወቃል። በሞቃታማው ወቅት ቦታው እጅግ ከመጨናነቁ የተነሳ፣ ለመዋኘት የሄዱ ሰዎች ትከሻ ለትከሻ እየተገፋፉ የባህር ውሃውን እንኳን ሳይነኩ የሚመለሱበት አስገራሚ ሁኔታ ይፈጠራል።
ይህ ከትልቅ ኮንሰርት የማይተናነስ የህዝብ ብዛት የፈጠረውን ግፊት እና ቅሬታ ለመቅረፍ ባለስልጣናት እርምጃ ወስደዋል። በዚህም መሰረት ከግንቦት እስከ መስከረም ባለው ጊዜ የባህር ዳርቻውን በቀን የሚጎበኙ ሰዎች ቁጥር ከ80 ሺህ እንዳይበልጥ ገደብ ተጥሎበታል።
በቻይና ሺንዘን የሚገኘው የዳሜሻ የባህር ዳርቻ በአንድ ቀን እስከ 200 ሺህ የሚደርሱ ጎብኚዎችን በማስተናገድ የአለማችን የተጨናነቀ ስፍራ በመሆን ይታወቃል። በሞቃታማው ወቅት ቦታው እጅግ ከመጨናነቁ የተነሳ፣ ለመዋኘት የሄዱ ሰዎች ትከሻ ለትከሻ እየተገፋፉ የባህር ውሃውን እንኳን ሳይነኩ የሚመለሱበት አስገራሚ ሁኔታ ይፈጠራል።
ይህ ከትልቅ ኮንሰርት የማይተናነስ የህዝብ ብዛት የፈጠረውን ግፊት እና ቅሬታ ለመቅረፍ ባለስልጣናት እርምጃ ወስደዋል። በዚህም መሰረት ከግንቦት እስከ መስከረም ባለው ጊዜ የባህር ዳርቻውን በቀን የሚጎበኙ ሰዎች ቁጥር ከ80 ሺህ እንዳይበልጥ ገደብ ተጥሎበታል።
ፍየሎቹ በድንገተኛ የጎርፍ አደጋ ላለመወሰድ ያደረጉት ከባድ ትንቅንቅ
ሁለቱ የቤት እንስሶች በዙሪያቸው ከሚንደረደረው ጎርፍ ከወንዝ መኻል በተገኘ ዛፍ ተጠልለው አምልጠዋል።
ሁለቱ የቤት እንስሶች በዙሪያቸው ከሚንደረደረው ጎርፍ ከወንዝ መኻል በተገኘ ዛፍ ተጠልለው አምልጠዋል።
🙏2
ኢትዮጵያ ለኮንፈረንስ ቱሪዝም ትልቅ ትኩረት ሰጥታ እየሠራች ነው - የመንግሥት ኮሙኒኬሽን
🇪🇹🇺🇳 ኢትዮጵያ 76ኛውን የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣና የጤና ሚንስትሮች ኮሚቴ ስብሰባ ልታስተናግድ ነው።
ስብሰባው ከነሐሴ 17 እስከ 21 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል።
ኢትዮጵያ በ2017 ዓ.ም ከ150 በላይ፤ በ2018 ዓ.ም ደግሞ ከ250 በላይ ዓለም ዓቀፍ ጉባኤዎችን እና ስብሰባዎችን አስተናግዳለች።
🇪🇹🇺🇳 ኢትዮጵያ 76ኛውን የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣና የጤና ሚንስትሮች ኮሚቴ ስብሰባ ልታስተናግድ ነው።
ስብሰባው ከነሐሴ 17 እስከ 21 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል።
ኢትዮጵያ በ2017 ዓ.ም ከ150 በላይ፤ በ2018 ዓ.ም ደግሞ ከ250 በላይ ዓለም ዓቀፍ ጉባኤዎችን እና ስብሰባዎችን አስተናግዳለች።
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
"ኑ ጊዜያችሁን ከቤተሰባችሁ ጋር በዚህ ውቧ አራዳ ፓርክ አሳልፉ። ፓርኩ ለወጣቶች፣ ለአዛውንቶች፣ ለህፃናት ፣ለስፖርተኞች፣ ለነጋዴውና፣ ለአርቱ ማህበረሰብ እንዲሁም ለተማሪዎች በጠቅላላ ለሁሉም የማህበረሰብ ክፍሎች በነፃ የቀረበ የጋራ መገልገያ ነው" ክብርት ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ
🙏 🙏 🙏
🙏 🙏 🙏